ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት @sinksarr Channel on Telegram

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

@sinksarr


በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርሥትያን ስንክሣር ውስጥ የተጻፉ የቅዱሳን አባቶቻችንና የቅዱሳት እናቶቻችን ገድላቸውና አስገራሚ ታሪካቸው ዓመቱን ሙሉ ምንም ሳይቋረጥ በየቀኑ ይነገርበታል!

ለአሥትያየትዎ @abitago

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት (Amharic)

የስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት ተደነቁ፡፡ ይህ እንግሊዝ መንገድ አንደኛ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርሥትያን ስንክሣር መሆኑን ይቀንቁ፡፡ ይህ ቤተ ክርሥትያን ስንክሣር ውስጥ የተጻፉ የቅዱሳን አባቶቻችንና የቅዱሳት እናቶቻችን ገድላቸውና አስገራሚ ታሪካቸው ዓመቱን ሙሉ ምንም ሳይቋረጥ በየቀኑ ይነገርበታል፡፡ እናቶቻችንን እና አባቶቻችንን ስንዝርና ድንግልና በቤተ ክርሥትያን ስንክሣር ገድላቸውን በተለያዩ ሰለባዎች ማወቅ እና ቃል እንዲሰለላቸው ስንረዳን ከራሱ ጋር በነገራቸው እንዲጠናቀቁ ያስተምሩ፡፡ ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት ቤተ ክርሥትያን የቀኑን ምንም ዓለም ሲያደርጋቸው ለአሥትያየትዎ @abitago ወደተጨማሪ መረጃ በመሆኑ የመሞዋዌት አስተዳዳሪ የቤተ ክርሥትያን ስንክሣር ገድላቸውን የእውነተኛ ስርዓት ከሚለው ወልዳቸው ለውጥና በሽታ ስለሚመልሰው ወቅታዊ መረጃ እና ስንክሣር ፕሮፌር አስተባባሪ፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

11 Feb, 15:12


አውጥተው ከቅዱስ ገብርኤል ጋር ጎን ለጎን ሆነው በዛሬው ዕለት ኅዳር 5 ቀን ወደ ብሔረ ሕያዋን ይዟቸው ገባ፡፡
ብሔረ ሕያዋን ያሉ እነ ሄኖክና ኤልያስም ‹‹ሰው ከሚሞትበት ሀገር ሞት ወደሌለበት አገር ማን አመጣው?›› አሉ፡፡ መልአኩም በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር ባዘዘኝ ጊዜ እኔ ገብርኤል ነኝ ያመጣሁት›› አላቸው፡፡ ቀጥሎም መልአኩ ‹‹አንተ ሄኖክ ምንም ንጹሕ ብትሆን በሥርዓተ ሥጋ ተወልደህ በሥርዓተ ሥጋ አድገህ ሚስት አግብተህ ወልደሃል፣ እግዚአብሔርም እዚህ ያደረሰህ በንፅህናህ ነው፤ አንተም ኤልያስ ምንም ድንግል ብትሆን በሥርዓተ ሥጋ ተወልደህ በሥርዓተ ሥጋ አድገህ ከዚህ ደርሰሃል፤ ይህ አባ ዮሐኒ ግን ከተወለደ ጀምሮ የእናቱን ጡት አልቀመሰም፣ ቀን ቀን ሰሳ እያጠባችው ሌሊት ሌሊት ንስር አሞራ በክንፎቹ እያለበሰው አድጓል እንጂ›› ብሎ ነገራቸው፡፡ ቀጥሎም መልአኩ የአባ ዮሐኒን ገድል ዘርዝሮ ከነገራቸው በኋላ ሊሞት ያለበትንም የአሟሟቱን ነገር ከነገራቸው በኋላ ‹‹ታዲያስ እንዲህ ያለውን አምጥቼ ከብሔር ሕያዋን ባስገባው ፍርዴ እውነት አይደለምን/›› አላቸው፡፡ ሄኖክና ኤልያስም ይህን ጊዜ ‹‹ይገባዋል›› ብለው አባ ዮሐኒን በምስጋና ተቀበሉት፡፡
ከዚህም በኋላ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ወደ ደብረ ዓሣ ተመልሶ መጥቶ ለአባ አበይዶ ተገለጠላቸውና አባ ዮሐኒን ብሔረ ሕያዋን እንዳስገባው ነገራቸው፡፡ በመጀመሪያ ሄኖክና ኤልያስ አላስገባ ብለው እንደነበርና በኋላም መልአኩ ራሱ የአባ ዮሐኒን ገድላቸውን ከነገራቸው በኋላ በምስጋና እንደተቀበሉት ለአባ አበይዶ ነገራቸው፡፡ ቀጥሎም መልአኩ የአባ ዮሐኒን ገድላቸውን እንዲጽፉትና እንዲያስተምሩበት ለአባ አበይዶ አዘዛቸውና ዐረገ፡፡ አባ አበይዶም አባ ዮሐኒ ከገደሉ ተወርውረው ሲወደቁ አንድ ደስ የሚል ወንድ ሲቀበለው አይተው ነበርና አሁን መልአኩ ሲነግራቸው እጅግ ደስ አላቸው፡፡ አባ አበይዶም በታዘዙት መሠረት የአባ ዮሐኒን ገድል ጻፉት፡፡ እርሳቸውም ትናንት ኅዳር 4 ቀን በሰላም ዐረፉ፡፡
ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!
+ + +
ዳግመኛም በዚኽች ዕለት በአስቄጥስ ገዳም በሰማዕትነት ያረፉት የ49 መነኮሳትም በዚሁ ዕለት መታሰቢያቸው ሆነ፡፡ (የዕረፍታቸውን ዕለት ጥር ሃያ ስድስትን ይመልከቷል፡፡) ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

11 Feb, 15:12


የአባ ዕብሎይ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎት ይማረን!
+ + +
ዳግመኛም በዚህች ዕለት የኢትዮጵያዊያኑ ቅዱሳን የአቡነ አሞኒ ልደታቸው ሲሆን የልጃቸው የአቡነ ዮሐኒም መታሰቢያቸው በዓላቸው ነው፡፡ (የዕረፍታቸውን ዕለት ህዳር አምስትን ይመከለቷል)
አባ ዮሐኒን ያሳደጉት አስተምረው ያሳደጓቸው አባ አሞኒ ናቸው፡፡ የእናቱን ጡት ፈጽሞ ጠብቶ የማያውቀውን የመንፈስ ቅዱስ ልጃቸውን አባ ዮሐኒን እሳቸው እያጫወቱት የታዘዘ አሞራ በክንፎቹ እያለበሰው ቶራ (ሰሳ) እያጠባችው ነው ያደገው፡፡ መነሻ ታሪኩም እንዲህ ነው፡-
የተንቤን አውራጃ ገዥ የነበረው ሰው በዘመኑ ዐፄ ካሌብ የነበሩበት ዘመን ነበርና አብሯቸው ወደ ምድረ ኖባ ሄደው ሰባት ዓመታትን የፈጀ የጦር ዘመቻ ክርስያኖችን በሚያሠቃዩ ነገሥታት ላይ አዳሄዱ፡፡ የተንቤኑ አውራጃ ገዥም ወደ ዘመቻው ከሄደ ቆይቶ ነበርና ታናሽ ወንድሙ የገዥውን ሚስት ‹‹ወንድሜ የቀረው ሞቶ ነው እንደ ኦሪቱ ሕግ እኔው ላግበሽና ልጆቹን ላሳድግ›› አላት፡፡ እርሷም ‹‹ባሌ ቢሞት ይነገረኝ ነበረዘመቻ የሄደው ሁሉ አልተመሰም›› ብላ እምቢ ብትለው በግድ ተገናኛት፡፡ በዚህም ጊዜ አባ ዮሐኒ ተፀነሱ፡፡ በሚያዝያ 5 ቀንም ተወለዱ፡፡
ከዘጠኝ ወር በኋላ ማሏ ከዘመቻ መጣና ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡ የአካባቢውም ሰው ወጥቶ በክብር ሲቀበለው ሚስቱ ግን ምጥ ተይዛ ታማ ስለነበር ወጥታ አልተቀበለችውም፡፡ ‹‹የት ሄደች? ምንስ ሆነች?›› ብሎ ሲጠይቅ ልጅ አይደብቅምና አንድ ሕፃን ‹‹አርግዛ ልትወልድ በምጥ ላይ ትገኛለች›› አለው፡፡ የአውራጃውም ገዥ ያለችበት ድረስ ሄዶ ቢያያት ያማረ ወንድ ልጅ ታቅፋ አገኛት፡፡ ከዚህም በኋላ ከቤቱ ምሰሶ ጋር ጥፍንግ አድርግ አስሮ እየገረፋትና እያስጨነቃት ከማን እንዳረገዘች ጠየቃት፡፡ እርሷም የወንድሙን ምሥጢር ለመጠበቅና ወንድማማቾቹን ላለማጣላት ሥቃዩን ታግሳ ዝም አለች፡፡ በዚህ ቅጽበት የራማው ልዑል ቅዱስ ገብርኤል 40 ዓመት ሙሉ ዘግተው በበረሃ ለሚኖሩት ለአባ አሞኒ ተገለጠላቸው እንደ አውሎ ነፋስ አምዘግዝጎ ወስዶ አውራጃ አገረ ገዥው ቤት አደረሳቸው፡፡
እንደደረሱ ዓመተ ማርያም በጽኑ ድብደባና ግርፋት እየተሠቃየች እያለ አባ አሞኒ የጸጉራቸውን አጽፍ ለብሰው ራቁታቸውን ደጇ ላይ ቆመው አየቻቸው፡፡ በዚህም ጊዜ ለባሏ ‹‹ያውና ከዚህ መነኩሴ ነው የወለድኩት›› አለቸው፡፡ አተንቤቱ አውራጃ አገረ ገዥውም አባ አሞኒን ይዞ ጽኑውን ግርፋት በወታደሮቹ አስገረፋቸው፡፡ በመቀጠልም ገና የእናቱን ወተት እንኳን ያልቀመሰውን ጨቅላ ሕፃን አንሥቶ ‹‹እንካ ልጅህን ይዘህ ጥፋ ከዚህ›› ብሎ ሰጣቸው፡፡ አባ አሞኒም በዚህ ጊዜ ‹‹ዮ ሀበኒ ዮ ሀበኒ›› አሉ፡፡ በትግርኛ እሽ ስጠኝ ማለት ነው፡፡ ከዚህ በመነሳት ነው ሕፃኑ በኋላ ላይ ‹‹አባ ዮሐኒ›› የተባሉት፡፡ አባ አሞኒም ሕፃኑን ተረክበው ወደ ደብረ ዓሣ ተራራ ሥር ሄደው ልጁን ከወይራ ዛፍ ሥር አስተኝተው ‹‹አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! ኃጢአቴን ተመራምረህ ይህንን ሕፃን የሰጠኸኝ አላጠባው ጡት የለኝ አላበላው እህል የለኝ›› ብለው የጨቅላው ሕፃን ነገር እጅግ ቢያስጨንቃቸው ምርር ብለው አለቀሱ፡፡ ጸሎታቸውንም እንደጨረሱ ተራራውን በመስቀል ምልክት ቢባርኩት በተራራው መሐል ላይ እንደመደብ ያለ አልጋ በተአምራት ተሠርቶ አገኙት፡፡ ሕፃኑንም ከዚያ አስተኝተው ድጋሚ ጸሎት ሲጀምሩ ቶራ (ሰሳ) መጥታ እግርና እግሯን አንፈራጣ ሕፃኑን አጠባችውና ሄደች፡፡
አባ አሞኒም በዚህ ደስ ተሰኝተው ሕፃኑን ‹‹የምግብህ ነገር ከተያዘ ግዴለም›› ብለው ሌሊቱን ሙሉ ሲጸልዩ አድረው መለስ ቢሉ ዳግመኛም ሕፃኑን የታዘዘ ንስር አሞራ በክንፎቹ ጋርዶ አልብሶትና አቅፎት እንዳደረ ተመለከቱ፡፡ አባታችንም እጅግ ደስ ተኝተው እግዚአብሔርን አመሰገኑት፡፡ እንደዚሁ ሁሉ ቀን ቀን ቶራዋ እያጠባችው ሌሊት ሌሊት ንስር አሞራው አልብሶት እያደረ ሕፃኑ ሦስት ዓመት ሆነው፡፡ አባ አሞኒም ከሰባት ዓመቱ ጀምረው እስከ 12 ዓመቱ ድረስ ፊደል፣ ንባብ ከነትርጓሜው፣ ብሉይንና ሐዲስን፣ ምግባር ሃይማኖትን ሥርዓተ ቤተ ክርስያንን ሁሉ አስተማሩት፡፡
አባ አሞኒ ልጃቸው አድጎ 12 ሲሆነው ከዚህም በኋላ ዲቁና ሊያሾሙትና አክሱም ጽዮን ወስደው ሊያስባርኩት ቤተ ካህናት ከተባለው ቦታ ይዘውት ሲሄዱ ልዩ ስሙ ሲሂታ ከሚባለው ቦታ ሲደርሱ ከወገባቸው በላይ እራታቸውን የሆኑ እንስራ የተሸከሙ ዓሥር ሴቶች አገኙ፡፡ አባ ዮሐኒም አባታቸውን ‹‹አባቴ እነዚህ ደረታቸው ላይ ቀንድ ያላቸው ጽጉራቸው የረዘመ ምንድናቸው? እንደእኛ የሆኑ መስህታን የሚባሉት እነዚህ ናቸውን?›› አሏቸው፡፡ አባ አሞኒም ‹‹አይደሉም ልጄ ዝም ብለህ ሂድ›› አሏቸው፡፡ በኋላ ግን ትዝ ሲላቸው ‹‹በዱር እንስሳት ያሳደኩት ልጄ ወንድና ሴት ለይቶ ሲያውቅ በዚያው ሊሳሳት አይደልምን?›› ብለው በማሰብ ዲቁናና ክህነቱ ይቅርበት ብለው ተመልሰው ወደ በዓታቸው ይዘውት ገቡ፡፡
ከዚህም በኋላ አባ አበይዶ ወደ አባ አሞኒ መጣና እሳቸውን ከአባ ዮሐኒ ጋር እያገለገሏቸው ተቀመጡ፡፡ ዮሐኒ እየጻፈ አበይዶ የሚጻፍበትን ቆዳ እያዘጋጁ ሦስቱም በአንድነት በተጋድሎ መቀመጥ ጀመሩ፡፡
አባ ዮሐኒ 20 ዓመት አባ አሞኒ ደግሞ 40 በሆናቸው ጊዜ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ለአባ አሞኒ ተገለጠላቸውና ‹‹አሞኒ ሆይ ከእንግዲህስ እግዚአብሔር ወደኔ ና ብሎሃል›› አላቸው፡፡ እሳቸውም ልጆቻቸውን አባ ዮሐኒንና አባ አበይዶን ጠርተው ‹‹በሉ እንግዲህ እኔ ወደ እግዚአብሔር መሄዴ ነውና ጸልዩልኝ›› አሏቸው፡፡ ከማረፋቸውም በፊት አባ ዮሐኒን ለብቻቸው ጠርተው ‹‹አንተ አባ ዮሐኒ ካሁን በፊት ሲሂታ ላይ ያየሃቸው ሴቶች ናቸው፣ አዳምንም ከገነት ያስወጡ ናቸው፡፡ ወደፊትም እንደ እነርሱ ያለ የደረሰብህ እንደሆነ ካለህበት ገደል ተወርውረህ ውደቅመ በባሕር ውስጥ ጥለቅ›› ብለው ነግረዋቸው በዛሬዋ ዕለት ኅዳር 5 ቀን በሰላም ዐረፉና ወደ ጠራቸው እግዚአብሔር ሄዱ፡፡
አባ አሞኒ ካረፉ ከ12 ዓመት በኋላ የአባ ዮሐኒ ወላጅ እናታቸው የልጇን ነገር ስታጠና ኖራ ነበርና አሁን ባሏም ስለሞተ አባ አሞኒም ስላረፉ ልጇን ልታይ ከ32 ዓመት በኋላ መጣች፡፡ ቀሚስ ለብሳ ፀጉሯን ተሠርታ በሴትነቷ ልጇ ካለበት ቦታ በመሄድ ማነጋገር እንደማትችል ስላወቀች ፀጉሯን ተላጭታ የወንድ ልብስ ቁምጣ ለብሳ በሁለመናዋ ወንድ መስላ ወደ ደብረ ዓሣ ተራራ አመራች፡፡ እዚያም እንደደረሰች በቅዱሳን ሥርዓት መሥረት ሦስት ጊዜ ‹‹አውሎ ግሶን፣ አውሎ ግሶን፣ አውሎ ግሶን›› አለች፡፡ ሰይጣን ይህን ስም ሲሰማ 40 ክንድ ይርቃል፡፡ የደብረ ዳሞ መነኮሳት እንደ ሰላምታ መለዋወጫ ይጠቀሙበታል፡፡ አባ ዮሐኒም ይህን ድምጽ ከውጭ በሰሙ ጊዜ ‹‹አንተ ማነህ?›› አሉ፡፡ እርሷም ‹‹ዓመተ መንፈስ ቅዱስ ነኝ›› አለቻቸው፡፡ አባታችንም አንድም ድምፁዋ ወትሮ ከሚያውቁት ድምፅ ስተለየባቸው ደግሞም ትዝ ሲላቸው እነዚያ እንስራ አዝለው ደረታቸው ላይ ቀንድ ያላቸው ሆነው ውኃ ቀድተው ሲሄዱ በመነገድ ያዩአቸው ሴቶች ድምፅ ሆነባቸው፡፡ ደግሞም ‹‹ወልደ እከሌ፣ ክንፈ እከሌ›› ሲባል እንጂ ‹‹ዓመተ፣ ወለተ›› ሲባል ሰምተው አያውቁም ነበርና አባታቸው አባ አሞኒ የነገሯቸው ትዝ አላቸው፡፡ በዚያውም ቅጽበት የሚጽፉባትን ብዕር ጆሮአቸው ላይ እንደሰኩ 500 ሜትር ርዝመት ካለው ትልቅ ተራራ ላይ ራሳቸውን ቁልቁል ወረወሩ፡፡ ነገር ግን መሬት ሳይደርሱ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በአየር ላይ እንዳሉ ተቀበላቸው፡፡ ብዕራቸው ግን መሬት ላይ ወድቃ ሸምበቆ ሆነች፡፡ ወዲያውም አባ ዮሐኒ ክንፍ

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

11 Feb, 15:12


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
የካቲት 5-አስቀድሞ ‹‹ያልሠራሁት የትኛውን ኃጥአት ነው›› እያለ በመግደል በማመንዘር በመስረቅ የኖረውና በኋላም የእግዚአብሔር ትዕግስቱ ምሕርቱና ይቅር ባይነቱ የታየበት የተነሳሒውን የአባ ዕብሎይ ዕረፍቱ ነው፡፡
+ አስቀድሞ በድሎት ብቻ ይኖር የነበረውና በኋላም ነፍሱ ተነጥቃ ሲኦልን አይቶ ከተመለሰ በኋላ በታላቅ መንፈሳዊ ተጋድሎ የኖረው አባ ቢሾይ ዕረፍቱ ነው፡፡
+ የኢትዮጵያዊያኑ ቅዱሳን የአቡነ አሞኒ ልደታቸው ሲሆን የልጃቸው የአቡነ ዮሐኒም መታሰቢያቸው በዓላቸው ነው፡፡
+ በአስቄጥስ ገዳም በሰማዕትነት ያረፉት የ49 መነኮሳትም መታሰቢያ በዓላቸው ነው፡፡
አባ ቢሾይ ዘላዕላይ ግብፅ፡- ከላይኛው ግብፅ አክሚም ከሚባል አገር የተገኘ ታላቅ አባት ነው፡፡ በጎልማሳነቱም ጊዜ ክፉ ሥራዎችን ሁሉ የሚሠራ ሆኖ ነበር፡፡ በመብላትና በመጠጣት የሚደሰት ሰው ሆኖ ሳለ እግዚአብሔር የነፍሱን ድኅነት ሽቶለት ጽኑ ደዌን አመጣበትና ለመሞት ተቃረበ፡፡ ነፍሱንም በተመስጦ አውጥቶ የሥቃይ ቦታዎችን ሁሉ አሳየው፡፡ ይህንንም ባየ ጊዜ ከልቡ አዝኖ አለቀሰ፡፡
ከዚህም በኋላ ነፍሱ ተመለሰችለትና ወደ ጌታችን ልመናውን አቀረበ፡፡ ‹‹ፈጣሪዬ ሆይ ከዚህ መከራ ደዌ ካዳንከኝ ስለ ኃጢአቴ ንስሓ በመግባት በፍጹም ልቡናዬ አመልክሃለሁ፣ የሴትንም ፊት ለዘላለሙ አላይም›› ብሎ ማለ፡፡ ጌታችንም ከደዌው አዳነውና ብንዋይ ወደሚባል ገዳም ገብቶ ብዙ ከተፈተነ በኋላ መነኮሰና በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመረ፡፡ እህልም ሳይቀምስ እስከ አንድ ወር የሚቆይ ሆነ፡፡ ሌሊቱንም ሁሉ ሲጸልይና ሲሰግድ ያድራል፡፡ የትሩፋቱም ዜና በግብጽ አገር ሁሉ ተሰማ፡፡ ለመነኮሳትም ትምህርት የሚሆኑ ብዙ ድርሳናትንና ተግሣጻትን ደረሰ፡፡ ሰዎች የሚሠሩት ሁሉ ጽድቅም ሆነ ኃጢአት ቢሆን ሁሉም በፊቱ ግልጽ ሆኖ ይታው ነበር፡፡ አባ ቢሶይ በእንደዚህ ዓይነት በታላቅ ተጋድሎ ተጠምዶ 38 ዓመት ከኖረ በኋላ የካቲት 5 በታላቅ ክብር ዐርፏል፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎት ይማረን!
+ + +
ተነሳሒው አባ ዕብሎይ፡- ይህ ታላቅ ጻድቅ አስቀድሞ ራሱን ለኃጢአት በማስገዛት ኖረ፡፡ ይኸውም 40 ዘመን ቀማኛ፣ ዘራፊና ገዳይ ሆኖ ይኖር የነበረ ሲሆን በኋላ ግን በንስሓ ተመልሶ ገዳም ገብቶ ጽኑ ተጋድሎ አድርጎ ለትልቅ ክብር የበቃ አባት ነው፡፡ በቀድሞ ሕይወቱ የበግ አርቢ የነበረ ሲሆን ራሱን ለሰይጣን በማስገዛት ከኃጢአት ሥራ ምንም የቀረው የለም ነበር፡፡ ያመነዝራል፣ ይሰርቃል፣ ይቀማል፣ ይገድላል…. እንዲህ ያሉ የሰይጣን ሥራዎችን ሁሉ እየሠራ 40 ዓመት ኖረ፡፡
በአንዲት ዕለትም ከበጎቹ ጋር በዱር ሳለ የመውለጃዋ ጊዜ የደረሰ ያረገዘች ሴትን አየ፡፡ ሰይጣንም በልቡ ክፉ ሀሳብን ጨመረበትና እንዲህ ብሎ አሰበ፡- ‹‹የተረፈችኝ ኃጢአት አንዲት አለች፣ እርሷም ያረገዘችን ሴት ሆዷን ሰንጥቄ በእናቱ ሆድ ሕፃኑ የሚተኛበትን አይ ዘንድ ነው›› አለ፡፡ በዚያን ጊዜም ተሰውሮ በመሄድ ሴትዮዋን ያዛትና የራስ ፀጉሯን ይዞ ከምድር ላይ ጣላት፡፡ ሾተሉንም አንስቶ ሆዷን ሰነጠቀ፡፡ ሕፃኑንም በማኅፀኗ ውስጥ እንዴት ሆኖ እንደተኛ አየው፡፡ እርሷም በጻዕር ብዛት ክፉኛ ተጨንቃ አስቀድማ ሞተች፡፡ ሕፃኑ ግን በጻዕር እየተሠቃየ ሳይሞት ብዙ ጊዜ ቆይቶ ሞተ፡፡
በግ አርቢውም የሠራውን ይህ ታላቅ ኃጢአት ተመልክቶ ደነገጠ፡፡ እጅግም አዘነና መራራ ልቅሶን አለቀሰ፡፡ በጎቹ እንደተበተኑ ትቷቸው በእጁ የያዛትን መጠበቂያ በትሩን ብቻ ይዞ አስቄጥስ ገዳም እስከሚደርስ እያለቀሰ ተጓዘ፡፡ ወደ አረጋውያን መነኮሳት አልገባም ይልቁንም ዓሥር ምዕራፍ ያህል ርቆ ከበረሃው ውስጥ ገባ፡፡ ከዱር አራዊት ጋር በጫካ ያድራል እንጂ በቤት ውስጥም አያድርም ነበር፡፡ የሚመገውም የዕፅዋትን ፍሬ ብቻ ሆነ፡፡ በየለቱም እያለቀሰ አምላኩን መለመኑን አላቋረጠም፡፡ ‹‹አቤቱ በደልኩ ክፉ ሥራንም ሠራሁ ይቅር በለኝ እኔ ኃጢአተኛ የሆንኩ ክፉ ባሪያ ነኝ፡፡ አንተ ቸር አምላክ ይቅር ባይ አባት ነህና የማይበድል ባሪያ የማይምር ጌታ የለምና አቤቱ ይቅር በለኝ…›› እያለ በዕንባ ዘወትር ይጸልይ ነበር፡፡ በእንደዚህ ዓይነት ተጋድሎው 40 ዓመት ኖረ፡፡ ከሌሊት ቁርና ከቀን ፀሐይ ሐሩርና የተነሣ ሥጋው ደርቆ ጠቆረ፡፡ ከዚህም በኋላ ‹‹ስለ ሴቲቱ ደም ጌታ ይቅር ብሎሃልና ጽና በርታ›› የሚለውን ድምፅ ሰማ፡፡ ይህም እንዳይታክትና ዳግመኛ ወደ በኃጢአት ውስጥ እንዳይወድቅ ነው፡፡
የታዘዘ መልአክም ከአባ ዕብሎይ 15 ምዕራፍ ያህል ርቀው ለሚገኙና በበረሃው ውስጥ 70 ዓመት ዘግተው ለሚኖሩ አንድ አረጋዊ አባት ተገለጠላቸውና ‹‹አንተ ካለህበት ቦታ ወደ ውጭ ሂድና አንድ ሽማግሌ ታገኛለህ፣ ኃጢአቱን ካመነልህ አጽናናው፣ ኃጢአትህ ሁሉ ስለ ሕፃኑም መገደል ተሠርዮልሃል በለው›› ብሎ አዘዛቸው፡፡ ያ አባትም ከበዓታቸው ወጥተው ሲሄዱ አባ ዕብሎይን እያለቀሱ አገኟቸው፡፡ ምን እንደሆኑም ሲጠይቋቸው አባ ዕብሎይ የሠሩትን ኃጢአት አንድ በአንድ ዘርዝረው ነገሯቸው፡፡ የተላኩት አረጋዊው አባትም ‹‹ኃጢአትህ ሁሉ ተሠርዮልሃል፣ አባቴ ሆይ ደስ ይበልህ ነገ የእግዚአብሔር መልአክ ወደ አንተ መጥቶ የክርስቶስን ሥጋና ደም ያቀብልሃል›› አሏቸው፡፡ በቀጣዩ ቀንም መልአኩ ለአባ ዕብሎይ በሰው አምሳል ተገልጦላቸው ካጽናናቸው በኋላ ሥጋ ወደሙን አቀብሏቸው ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ አባ ዕብሎይም ሥጋ ወደሙን ከቀበሉ በኋላ ሰውነታቸው እንደ በረዶ የነጣ እንደ ፋናም የሚያበራ ሆኖ ታደሰላቸው፡፡ አባታችን አሁንም ቢሆን ጸሎታቸውን ባለቋረጥ ‹‹እኔ ኃጢአተኛ የሆንኩ ክፉ ባሪያ ነኝ፡፡ አንተ ቸር አምላክ ይቅር ባይ አባት ነህና የማይበድል ባሪያ የማይምር ጌታ የለምና አቤቱ ይቅር በለኝ…›› እያሉ እየጸለዩ ኖሩ፡፡ በቀጣዩም ቀን አረጋዊው ሽማግሌም አባ ዕብሎይን ‹‹ገዳማዊ ወንድሜ ዕብሎይ ና በውኃ ታጠብ ደስ ይበልህም በዚህች ሰዓት ከተቀበልከው መከራ ታርፋለህና›› አሏቸው፡፡ ከዚህም በኋላ የታዘዘ መልአክ መጥቶ አባ ዕብሎይንና አረጋዊውን ሽማግሌ በድጋሚ ሥጋ ወደሙን አቀበላቸው፡፡ አባ ዕብሎይም የካቲት 5 ቀን ዐረፉና መላእክት ነፍሳቸውን ተሸክመው እስከ አርያም በረሩ፡፡
ያ አረጋዊ ሽማግሌም የአባ ዕብሎይን ሥጋ ለመቅበር ሸምግለው ስለነበር በዚህም እያሰቡ እያለ ሁለት አንበሶች መጥተው ለአባ ዕብሎይ ሥጋ ሰግደው መቃብራቸውን ቆፍረው ሥጋቸውን እንደ ሰው ተሸክመው ወስደው ቀበሯቸው፡፡ አረጋዊውንም ሽማግሌ እጅ ነሥተዋቸው እሳቸውም ባርከዋቸው በሰላም ሄዱ፡፡ አረጋዊውም ሽማግሌ ከ3 ቀን በኋላ እንደሚያርፉ ከሰማይ ድምፅ መጣላቸው፡፡ እሳቸውን የሚቀብሩ ሦስት ሰዎች ተልከው እንደሚመጡም ተነገራቸው፡፡ እሳቸውም ለሦስቱ ሰዎች የአባ ዕብሎይን ታሪክ እንዲነግሯቸው ታሪካቸው ተጽፎ ለትውልድ እንዲነገር ከእግዚአብሔርም ምሕረት የተነሣ ተስፋ እንዳይቆርጡ በኃጢአት ለወደቁ ሁሉ አለኝታ ይሆኑ ዘንድ እንዲጽፉት አዘዟቸው፡፡ አረጋዊውም ሽማግሌ ባረፉ ጊዜ ሁለቱ አንበሶች ደግመው መጥተው ቆፍረው ቀበሯቸውና ሦስቱን ሰዎች መርተው ገዳመ አስቄጥስ አደረሷቸው፡፡ በገዳሙም የበግ ጠባቂው የአባ ዕብሎይ ገድል ተጽፎ ሁልጊዜ እሑድ እሑድ ያነቡት ጀመር፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

11 Feb, 07:31


ነበር፡፡ አሁንም ከተማው በገቡ ጊዜ ቅዱስ ዮሐንስ ምክንያት በመፍጠር ሮምና ለምትባል ሴት የውሽባ ቤቷ እሳት አንዳጅ ሆኖ አብሮኮሮስም ዕቃ አጣቢ ሆነው ተቀጠሩ፡፡ የቀጠረቻቸው ሴትም እጅግ ታሠቃያቸው ጀመር፡፡ ባሮቿ እንደሆኑ ተስማምተው ስለጻፉላት ትደበድባቸውም ነበር፡፡

እነርሱም በታላቅ ጉስቁልና ውስጥ እየኖሩ እያለ በአንዲት ዕለት የአገረ ገዥው ልጅ ለመታጠብ ወደ ውሽባው ቤት ገባ፡፡ በውሽባ ቤቱም የሰይጣን ኃይል ስለነበረበት የመኰንኑን ልጅ አንቆ ገደለው፡፡ የአገሪቱም ሰዎች ሁሉ ለሞተው የመኰንን ልጅ ሊያለቅሱ ሲሰበሰቡ ቅዱስ ዮሐንስም አብሮ ቆሞ ሲመለከት ሮምና መጥታ ‹‹በጌታዬ ልጅ ሞት ልትደሰት መጣህን›› እያለች ረገመችው፡፡ እርሱም ‹‹አይዞሽ አትዘኚ›› አላትና ወደ ሞተው ልጅ ቀርቦ በመስቀል ምልክት ካማተበበት በኋላ በፊቱ እፍ አለበት፡፡ የሞተውም ልጅ ድኖ ተነሣ፡፡ የሀገሪቱም ሰዎች እጅግ ደነገጡ፡፡ ሮምናም ደንግጣ ‹‹እግዚአብሔር የሚሉት አምላክ አንተ ነህን›› ብላ ጠየቀችው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም ‹‹በፍጹም እኔ አምላክ አይደለሁም፣ እኔ የእርሱ አገልጋዩና ሐዋርያው ነኝ እንጂ›› አላት፡፡ ሮምናም ስለበደለቻቸው በደል ሁሉ መሪር ዕንባን እያለቀሰች ይቅር እንዲሏት ለመነቻቸው፡፡ እነርሱም አረጋጉዋት፡፡ ከሕዝቡም ውስጥ ብዙዎቹ በጌታችን አመኑ፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም ሌሎች ብዙ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን እያደረገ ወንጌልን እየሰበከ ከጣዖት አገልጋዮች በቀር ሁሉንም አሳምኖ አጠመቃቸው፡፡ አገልጋዮችን ኤጲስቆጶሳትን፣ ቀሳውስትንና ዲያቆናትን ከሾመላቸው በኋላ ወደ ሌሎች አቅራቢያ አገሮች ሄደ፡፡

በመጨረሻም በከሃዲውና በጨካኙ በድምጥያኖስ ዘመን በጣዖት አምላኪዎች ተከሶ ለፍርድ ቀረበ፡፡ በፈላ ውኃ ካሠቃዩት በኋለ በፍጥሞ ደሴት አጋዙት፡፡ በዚያም ሳለ ራእዩን ተመልክቶ ጻፈው፡፡ ድምጥያኖስም ከተገደለ በኋላ ከግዞቱ ተመልሶ ሦስቱን መልእክታቱንና ቅዱስ ወንጌሉን ጽፏል፡፡ ጌታችንም አስቀድሞ ሞትን እንደማይቀምስ ለዮሐንስ ቃል ገብቶለት ነበርና (ዮሐ 21፡22) ጥር 4 ቀን እንደ ኤልያስና ሄኖክ ሞትን እንዳያይ ወደ ብሔረ ሕያዋን ወስታል፡፡

ጌታችን ለዮሐንስ ያልነገረው እርሱም ያላስተማረው ምሥጢር የለም፡፡ ወንጌሉን መጻፍ ሲጀምር ‹‹በመጀመሪያ ቃል ነበረ፣ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ…›› ብሎ የጌታችን ነገር ተመራምሮ ለመድረስ ሲል በመሀል መልአኩን በዮርዳኖስ ባሕር ላይ ሲሄድ አገኘው፡፡ መልአኩም የዮርዳኖስን ባሕር በእንቁላል ቅርፊት እየጨለፈ ወደ ውጭ ሲያፈስ ተመለከተው፡፡ ዮሐንስም ተገርሞ ‹‹ምን ማድረግህ ነው›› አለው፡፡ መልአኩም ‹‹የዮርዳኖስን ባሕር ቀድቼ እየደፋሁ ልጨርሰው ነው›› ሲለው ዮሐንስም መልሶ ‹‹ታዲያ በእንቁላል ስባሪ ነውን?›› አለው፡፡ መልአኩም ‹‹አዎን›› አለው፡፡ ዮሐንስም ‹‹በከንቱ ደከምክ›› አለው፡፡ ይህን ጊዜ መልአኩም መልሶ ‹‹አንተስ እንጂ ደግሞ የአምላክን መገኘት፣ አኗኗሩንም ተመራምረህ በጥበብ ለማግኘት ብለህ ‹በመጀመሪያ ቃል ነበረ፣ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ..› ብለህ ጀምረህ የለምን? አንተ ጌታን ተመራምረህ ካገኘህና ከደረስክበት እኔም የዮርዳኖስን ወንዝ በዚህ እንቁላል ቅርፊት ቀድቼ እጨርሰዋለሁ›› አለው፡፡ ዮሐንስም ይህን ጊዜ ደንግጦ ዝቅ ብሎ ‹‹ስሙ ዮሐንስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ…›› ብሎ ሀሳቡን ለወጠና ሌላ ታሪክ ቀጠለ፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ ጌታችንን እስከ እግረ መስቀሉ ድረስ በመከተሉ ክርስቲያኖችን ሁሉ ወክሎ እመቤታችንን በአደራ የተቀበለ እርሱም ለመቤታችን በአደራ የተሰጠ ሲሆን እመቤታችንን ከወሰዳት በኋላ ለ16 ዓመት እየተንከባከበ ጠብቋታል፡፡ እናቱም በሕፃንነቱ ስለሞተች እመቤታችን ናት እየተንከባከበች ያሳደገችው፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ በመልኩም ከጌታችን ጋር ይመሳል ነበር፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ሥዕል የመሳል ተሰጥኦም ነበረው፡፡ ጌታችን በተሰቀለበት ዘመን የነበረው ጢባርዮስ ቄሳር ልጁ በሽተኛ ነበር፡፡ የጌታችንን የማዳን ሥራ እየሰማ እነ ጲላጦስም ስለጌታችን የሚጽፉለትን ይሰማ ስለነበር ልጁን ከጌታችን መቃብር ላይ እንዲያኖሩለት ላከው፡፡ ልጁም ፈጥኖ ተፈወሰለት፡፡ ጢባርዮስ ቄሳርም በልጁ መዳን ምክንያት የጌታችንን ውለታ ማስቀመጥ ፈልጎ የጌታችንን ሥዕሉን የሚሥልለትን ሲያጠያይቅ ዮሐንስን አገናኙት፡፡ ዮሐንስም ጌታችንን ልክ በዕለተ ዓርብ እንደተሰቀለ አድርጎ በመሣል ለጢባርዮስ ቄሳር ሰጠው፡፡ ሲሥለውም በመጀመሪያ ጌታችንን ልክ እንደተሰቀለ አድርጎ ራቁቱን ነበር የሳለው፡፡ ዮሐንስ የሳለው የጌታችን ሥዕልም አፍ አውጥቶ ‹‹በመጀመሪያ አይሁድ በኢየሩሳሌም ራቁቴን ሰቀሉኝ፣ አሁን ደግሞ አንተ ድጋሚ በሮም ራቁቴን ትሰቅለኝን?›› ብሎ ተናገረው፡፡ ዮሐንስም እጅግ ደንግጦ ‹‹እንዴት አድርጌ ልሳልህ?›› ብሎ የሳለውን ሥዕል ቢጠይቀው ሥዕሉም ‹‹ከለሜዳ አልብሰህ ሳለኝ›› አለው፡፡ ዮሐንስም እንዳለው ከለሜዳ አልብሶ ከሳለው በኋላ ሥዕሉን ትኩር ብሎ ተመልክቶ ቢስመው ከንፈሩ አንድ ቀን ተኩል ያህል ተጣብቆ ቆይቷል፡፡ ዛሬም ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የምትጠቀምባቸውን የጌታችንን ስነ ስቅለት የሚያሳዩ ሥዕሎች መገኛቸው ይህ ወንጌላዊው ዮሐንስ የሳለው ሥዕል ነው፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ በተለያዩ ስሞች ይጠራል፡፡ በሕይወቱና በኑሮው ሁሉ ጌታችንን ለመምሰል ይጥር ነበርና ጌታችንም እጅግ ይወደው ስለነበር ‹‹ፍቁረ እግዚእ›› ተባለ፡፡ የታላቁ ያዕቆብ ታናሽ ወንድም ስለሆነና አባቱም ዘብድዮስ ስለሚባል ‹‹ዮሐንስ ወልደ ዘብድዮስ›› ተባለ፡፡ ለጌታችን ባለው ቅናትና ከወንድሙ ጋር ሆነው ባሳዩት የኃይል ሥራ እንዲሁም የጌታችንን አምላክነት በመግለጡ ‹‹ወልደ ነጎድጓድ›› ተብሏል፡፡ ነገረ መለኮትን ከሌሎቹ በበለጠ ሁኔታ አስፍቶና አምልቶ በማስተማሩ ‹‹ነባቤ መነኮት ወይም ታኦሎጎስ›› ተብሏል፡፡ ኃላፊውንና መጻዒውን ጊዜ በራእዩ ስለገለጠ ‹‹አቡቀለምሲስ›› ተባለ፣ ይህም በግሪክኛ ባለራእይ ማለት ነው፡፡ የጌታችንን መከራ መስቀሉን እያስታወሰ 70 ዘመን ሙሉ እያለቀሰ ስለኖረና ፊቱም በሀዘን ስለተቋጠረ ‹‹ቁዱረ ገጽ›› ተብሏል፡፡ የቅዱስ ዮሐንስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

11 Feb, 07:31


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
የካቲት 4 ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ ሐዋርያ የከበረ ቅዱስ አጋቦስ በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡ ይኽም ቅዱስ ጌታችን ከመረጣቸውና የከበረች ወንጌልን ይሰብኩ ዘንድ ወደ ዓለም ከላካቸው ከሰባ ሁለቱ አርድእት ውስጥ ነው፡፡ በጽርሐ ጽዮን አጽናኝ መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜ ከከበሩ ሐዋርያት ጋር ስጦታውን ተቀብሏል፡፡ ከዚህም በኋላ እግዚአብሔር የትንቢትን ሀብት ሰጠው፡፡ ስለ እርሱ በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ እንደተነገረ የቅዱስ ጳውሎስን መታጠቂያ አንሥቶ እግሮቹን አሠረባና ‹‹የዚህችን መታጠቂያ ባለቤት በኢየሩሳሌም አይሁድ እንዲህ ያስሩታል›› ብሎ ትንቢትን ተባገረ፣ ትነቢቱም ተፈጸመች፡፡
ሐዋርያው ቅዱስ አጋቦስ የከበረች ወንጌልን ይሰብክ ዘንድ ከሐዋርያት ወጣ፡፡ ወደ ብዙ አገሮችም ሄዶ የተለያዩ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን እያደረገ ወንጌልን እየሰበከ ብዙዎችን ከአምልኮተ ጣዖት እግዚእአብሔርን ወደማምለክ መለሳቸው፡፡ ከአይሁድና ከዮናናውያንም ብዙዎችን የክብር ባለቤት ወደሆነ ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅን ሃይማኖት አስገባቸው፡፡ በከበረች በክርስትና ጥምቀትም አጠመቃቸው፡፡
ቅናትን የተሞሉ ክፉዎቸ አይሁድ ግን ድንገት ብቻውን ሳለ ይዘውት ታላቅ ግርፋትን ገረፉት፡፡ በአንገቱም ገመድ አስገብተው ከከተማው ውጭ አውጥተው በመጎተት እጅግ ካሠቃዩት በኋላ ነፍሱ እስካለፈች ድረስ በድንጋይ ወገሩት፡፡ በዚያም ጊዜ ከሰማይ ብርሃን ወርዶ በሥጋው ላይ እንደምሰሶ ተተከለ፡፡ ይህም በቅዱስ አጋቦስ ሥጋ የተተከለው ብርሃን እስከሰማይ ደርሶ አሕዛብ ሁሉ እስኪያዩት ድረስ ግልጽ ሆነ፡፡ እግዚአብሔርም የአንዲቱን አይሁዳዊት ሴት ልቡናዋን ገለጠላት፡፡ እርሷም በውስጧ ሽንገላ፣ ቅናት፣ ጠብ የሌለባት ናት፡፡ የኦሪትንም ሕግ የምትጠብቅ መልካም ሴት ነበረች፡፡ እርሷም ይህንን ብርሃን አይታ ‹‹ይህ ሰው እውነተኛ የእግዚአብሔር ሰው ነው›› አለች፡፡ ያንጊዜም በላይዋ ብርሃን ወረደ፡፡ ከዚህም በኋላ ጮኻ ‹‹እኔ በቅዱስ አጋቦስ ፈጣሪ የእግዚአብሔር ልጅ በሆነ በጌታ ኢየሱስ የማምን ክርስቲያን ነኝ›› አለች፡፡ እንዲህም እያለች የቅዱስ አጋቦስ አምላክ ልዑል እግዚአብሔርን ስታመሰግን ክፉዎች አይሁድ በድንጋይ ወግረው ገደሏትና የሰማዕትነት አክሊልን ተቀዳጀች፡፡ የቅዱስ አጋቦስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡
////////////////////////

ዳግመኛም በዚኽች ቀን በምግባር ፍጹም የሆነ ተጋድሎውም የበዛ አባ ዘካርያስ ዐረፈ፡፡ መ እርሱንም ቅድስት ነፍሱ ከሥጋው በምትለይ ጊዜ አባ ሙሴ ‹‹ወንድሜ ሆይ! ምን ታያለህ/›› አለው፡፡ አባ ዘካርያስም ‹‹ለእኔስ ዝምታ ይሻለኛል›› አለ፡፡ ነፍሱም ስትወጣ አባ ኤስድሮስ ሰማይ ተከፍቶ አየ፡፡ ‹‹ልጄ ዘካርያስ ሆይ! የመንግሥተ ሰማያት በር ተከግቶልሃልና ደስ ይበልህ አለው፡፡ አባ ዘካርያስም በእንዲህ ያለ ሁኔታ ዐረ፡፡ በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡
///////////////////////

ክፍለ ሀገር ስለሄድኩ ከጥር 4-10 ድረስ ተቋርጦ የነበረው ስንክሳር ከየካቲቱ ወር ጋር ቀኖቹ ላይ ድራቢ በማድረግ ማለትም የጥር 4ቱን ከየካቲቱ 4 ጋር እያደረግሁ ከዚህ ቀን ጀምሮ በተከታታይ አቀርባለሁ፡፡ አምላከ ቅዱሳን ከሁላችን ጋር ይሁን፡፡
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ጥር 4 ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ወልደነጎድጓድ የፍልሰቱ መታሰቢያ ዕለት ነው፡፡ በሕይወት ዘመናቸው ሁሉ ሁልጊዜ ዐርብ ዐርብ ያከፍሉ የነበሩት የጌታችንን መከራ እያሰቡ አናታቸውን አቁስለው ሲተላ ትሉን ለወፎች ይመግቡ የነበሩትና ዋሽራን ለ30 ዓመታት በሹመት ያገለገሉት የዋሸራው አቡነ መልከጼዴቅ ዕረፍታቸው ነው፡፡
ዳግመኛም በዚኽች ዕለት ስንክሳሩ ‹‹ተጋዳይ የሆነ በጥላው ብቻ ከይሲን የገደለ የደብረ ቢዘኑ አባ ናርዶስ የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው፡፡ እርሱም እግሮቹ እስኪያብጡ ድረስ ቆሞ በመጸለይ የተጋደለ ነው›› በማለት በአጭሩ የገለጸው ጻድቁ አባ ናርዶስ ዕረፍቱ ነው፡፡ በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡

አቡነ መልከጼዴቅ ዘዋሸራ፡- መርሐቤቴ ያሉት ማለትም በደጃቸው የተቀበረውን ሰው ዐፈር የማስበሉት ጻዲቅ የሚዳው አቡነ መልከጼዴቅና የዋሸራው አቡነ መልከጼዴቅ ሁለቱ የተለያዩ ናቸው፡፡ የሚዳው አቡነ መልከጼዴቅ በ13ኛው መ/ክ/ዘ መጨረሻ በንጉሥ ዐፄ በእደ ማርያም ዘመነ መንግሥት የነበሩ የአምላካቸውን የክርስቶስን መከራ ለማሰብ ገዳመ ቆሮንቶስን የመሰለ ዋሻ ቆፍረውና በዚያ ገብተው ቀንና ሌሊት ዘግተው በረደኝ ፀሐይ ልሙቅ፣ ጨለመኝ ብርሃን ልይ ሳይሉ በጸሎት ብቻ ዘግተው በመኖር ራሳቸውን በችንካር ይቸነክሩ ነበር፡፡ የወዳጆቹን መከራ የማይዘነጋ፣ የሰውን የድካሙን ዋጋ ፈጽሞ የማያስቀር አምላክ ሠራዊተ መላእክትን አስከትሎ መጥቶ ‹‹መገረፍህ፣ ስለ እኔ መገረፍ ይሁንልህ፣ የደምህ መፍሰስ ስለ እኔ ደም መፍሰስ ይሁንልህ፣ መቸንከርህም ስለ እኔ መቸንከር ይሁንልህ፣ ሞትህም ስለ እኔ ሞት ይሁንልህ፤ ከዚህ ቦታ መጥቶ የተሳለመውን እምርልሃለሁ፤ ነፍሱ በአንተ ቃልኪዳን የማይማር በአንተ ቦታ ለመሳለምም፣ ንስሓ ለመግባትም ሆነ ለመቀበር አላቀርብብህም፤ መጥቶም የተቀበረውን ሥጋውን አፈር አይበላውም›› የሚል እጅግ ድንቅ ቃልኪዳን የሰጣቸው በደጃቸው የተቀበረውን ሰው ዐፈር የማስበሉት ጻድቅ የሚዳው አቡነ መልከጼዴቅ ናቸው፡፡

እኚህኛው የዋሸራው አቡነ መልከጼዴቅ ከአባታቸው ከዘካርያስና ከእናታቸው ስነ ክርስቶስ የተወለዱት አቡነ መልከጼዴቅ ዘዋሸራ ትውልድ ሀገራቸው ጎጃም ዋሸራ ሲሆን በታላቅ ተጋድሎና በሹመት ያገለገሉትም በዚሁ ነው፡፡ ዲቁናንና ቅስናን ከግብፅ ተቀብለው በዋሽራ 30 ዓመት በሹመት አገልግለዋል፡፡ ጻድቁ የሚታወቁበት ትልቁ ተጋድሎአቸው በሕይወት ዘመናቸው ሁሉ ሁልጊዜ ዓርብ ዓርብ ያከፍሉ ነበር፡፡ የመድኃኔዓለምን 13ቱን ሕመማተ መስቀሎች በማሰብ አናታቸውን በድንጋይ እያቆሰሉ ቁስሉ ሲተላ ትሉን ለወፎች ይመግቡ ነበር፡፡ በ40 ቀን ውስጥ አንዷን ቀን ብቻ ነው ውኃ ይጠጡ የነበረው፡፡ ጻድቁን የቅኔ ተማሪዎች በዋሸራ ይዘክሯቸዋል፡፡ ዕረፍታቸውም ጥር 4 ነው፡፡ በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን፡፡
///////////////////////////

ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ፡- ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌልን ለመስበክ ዕጣ የደረሰው እስያ ስለነበር ደቀ መዝሙሩን አብሮኮሮስን አስከትሎ ሄደ፡፡ ይኽችውም ኤፌሶን በጥንቱ በታናሽ እስያ በዛሬው የቱርክ ግዛት ውስጥ ከተማ ናት፡፡ ዛሬ ኢያዞሎክ ተብላ የጥንት ታሪኳ ጠፍቷል፡፡ አስቀድሞ ቅዱስ ጳውሎስ ወንጌልን ሰብኮባታል፡፡ ደቀ መዝሙሩን ቅዱስ ጢሞቴዎስንም በከተማዋ ላይ ኤጲስቆጶስ አድርጎ ሾሞት ነበር፡፡ እርሱም በግፍ እስከተገደለበት ጊዜ ድረስ ቅዱስ ዮሐንስን እየረዳው በከተማዋ ብዙ አገልግሏል፡፡ በኋላ ግን በግፍ ገድለውታል፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ ወደ ኤፌሶን ለመሄድ በመርከብ ሲሳፈር መርከቡ በማዕበል ተሰበረ፡፡ ደቀ መዝሙሩን አብሮኮሮስን መዕበሉ ወደ አንዲት ደሴት አደረሰው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ግን በመርከቡ ስባሪ ተንጠልጥሎ በባሕሩ ማዕበል መካከል 40 ቀንና 40 ሌሊት ከኖረ በኋላ ማዕበሉ ተፍቶ አብሮኮሮስ ካለበት ደሴት አደረሰውና ተያይዘው ኤፌሶን ከተማ ገቡ፡፡ የከተማይቱም ሰዎች እጅግ ክፉዎች ስለነበሩ መጀመሪያ ላይ ቅዱስ ወንጌልን መስበክ አልቻሉም ነበር፡፡ እነርሱም እጅግ ክፉዎች መሆናቸውን ስላወቀ ቅዱስ ዮሐንስ ገና ዕጣው ሲደርሰው በሀዘን አልቅሶ

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

10 Feb, 05:15


ጾመ ሰብአ ነነዌ
‹‹ጾመ ሰብአ ነነዌ፤ የነነዌ ሰዎች ጾም›› የሦስት ቀን ጾም የጾሙት በነነዌ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች ናቸው፡፡ ከተማዋም (ነነዌ) በጤግሮስ ወንዝ ዳርቻ የምትገኝ ስትኾን መሥራቿም ናምሩድ ነው (ዘፍ.፲፥፲፩-፲፪)፡፡ ጥንታዊቷ የነነዌ ከተማ ለአሦር መነሻ የሆነች፤ እጅግ ሰፊና ያማረች፤ የቅጥሯ ርዝመትም ፲፪ ኪሎ ሜትር የሚሸፈን ነበር፡፡ በከተማዋ ንጉሡ ሰናክሬም ብዙ ሕንጻዎችን ገንብቶ ነበር (ዮናስ ፬፥፲፩)፡፡

በዚያ ዘመን የነበሩ የነነዌ ሰዎች ኃጢአታቸው በዝቶ እግዚአብሔር ሊያጠፋቸው ሲል ዮናስ የስሙ ትርጓሜ ‹ርግብ› የሆነ በዳግማዊ ኢዮርብዓም ዘመነ መንግሥት የነበረ ነቢይን ቸርነትና ምሕረቱ የማያልቅበት እግዚአብሔር መክሮ፣ ዘክሮ እንዲመልሳቸውና ንስሐ እንዲገቡ ነቢዩ ዮናስን ወደ ነነዌ ሕዝብ ላከው (ሉቃ.፲፩፥፴)፡፡ ይህ ነቢይ መኖሪያው በገሊላ በጋትሔፌር ድንበር ከተማ ነበረ፤ አባቱም አማቴ ይባላል፡፡ በዚያን ጊዜ ኢዮርብዓም ሶርያውያንን አባሮ የእስራኤልን ድንበር እንዲመልስ ነቢዩ ዮናስ ትንቢትን ተናገረ (፪ኛነገ.፲፬፥፳፭፤ ዮናስ ፩፥፩)፡፡ ነቢዩ ኤልያስ ያስነሣው የሰራጵታዋ መበለት ሕፃን ነቢዩ ዮናስ እንደ ሆነ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ያስረዳል (፩ኛነገ.፲፯፥፲፱)፡፡ መድኃኒታችን ክርስቶስም የዮናስን ከዓሣ ሆድ መውጣት የራሱ ትንሣኤ ምሳሌ አድርጎ ነግሮናል (ማቴ.፲፪፥፲፱-፵፪፤ ሉቃ.፲፩፥፴-፴፪)፡፡

እግዚአብሔር አምላክም ‹‹ሔደህ በነነዌ ላይ ስበክ›› ባለው ጊዜ ነቢዩ ዮናስ ‹‹አንተ መሐሪ ነህ፤ ልትጠፉ ነው ብዬ ተናግሬ ብትምራቸው ሐሰተኛ ነቢይ እባላለሁ›› ብሎ ላለመታዘዝ እስራኤልን ለቆ በመርከብ ወደ ተርሴስ ሸሸ፡፡ እግዚአብሔርም ታላቅ ነፋስን አስነሥቶ መርከቧ በማዕበል እንድትመታ አደረገ፡፡ ከዮናስ ጋር በመርከቧ ተሳፍረው የነበሩ ነጋድያንም ያላቸውን ሀብት ወደ ባሕሩ መጣል ሲጀምሩ ነቢዩ ዮናስ ጥፋቱን ተገንዝቦ ‹‹ማዕበሉ በእኔ ምክንያት የመጣ ስለሆነ ንብረታችሁን ሳይሆን እኔን ወደ ባሕር ጣሉኝ›› ብሎ ተማጸናቸው፡፡ እነርሱም ‹‹ስለዚህ ሰው ነፍስ እንዳንጠፋ፣ ንጹሕም ደም በእኛ ላይ እንዳይደረግብን አይሆንም›› አሉ፡፡ ወደ ባሕሩ ለመጣል ዕጣ በተጣጣሉ ጊዜም ዕጣው በዮናስ ላይ ስለ ወጣ ነጋድያኑ ዮናስን ወደ ባሕሩ ጣሉት፡፡ ወዲያውኑ ከእግዚአብሔር ዘንድ የታዘዘ ታላቅ ዓሣ አንበሪ ዮናስን በአፉ ተቀብሎ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት አሳድሮ ወደ ነነዌ አደረሰው፡፡ እግዚአብሔር የቅል ተክልን ምሳሌ በማድረግ ቅጠሉ በመድረቁ ዮናስ ባዘነ ጊዜ ‹‹አንተ ላልደከምክበት እና በአንድ ቀን በቅሎ ላደገ ቅል ስታዝን እነሆ በታላቂቱ ነነዌ ከተማ ያሉ ከአንድ መቶ ሃያ ሺሕ በላይ ሕዝብና እንስሳቱ የእጄ ፍጥረቶች ስለ ሆኑ ያሳዝኑኛል›› በማለት ነቢዩ ዮናስም ውሸታም ላለመባል መኮብለሉ ስሕተት መሆኑን አስረድቶታል፡፡

ዮናስም ነነዌ መሬት ላይ መድረሱን ባወቀ ጊዜ ከእግዚአብሔር መሸሽ አለመቻሉን ተረዳ፤ የነነዌ ሰዎችንም ‹‹ንስሐ ግቡ›› እያለ መስበክ ጀመረ፡፡ የነነዌ ሰዎችም ንስሐ በገቡ ጊዜ እግዚአብሔር ይቅር ብሎ ከጥፋት አድኗቸዋል፡፡ ሐሰት እንዳይባልም እሳቱ እንደ ደመና ሆኖ ከላይ ታይቶአል፡፡ የታላላቁ ዛፍ ቅጠል እስኪጠወልግ ድረስ አድርቆ ለሕዝቡ አሳይቷቸዋል፡፡ ንስሐቸው በከንቱ እንዳልቀረ አስረድቷቸዋል (ትንቢተ ዮናስ)፡፡ ታኅሣሥ ፭ ቀን የሚነበበው የመጽሐፈ ስንክሳር ክፍል ‹‹ወበልዐ አሐደ ኀምለ›› በማለት ንስሐ ያልገቡ አንድ አገር ያህል ሰዎች በእሳቱ እንደ ጠፉ ይነግረናል፡፡

ጾመ ነነዌ የሦስት ቀን ሱባኤ ነው፤ በሦስት ቀናት ጾምና ጸሎት ንስሐ የገቡ የነነዌ ሰዎች ከጥፋት እንደ ዳኑ ሁሉ፣ በብሉይ ኪዳን አስቴር ሦስት ቀን ጾማ፣ ጸልያ በእስራኤል ላይ የመጣውን መቅሠፍት እንዲመለስ አድርጋለች (አስ.፬፥፲፭-፲፮)፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ከበዓል ስትመለስ ሕፃኑ ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ መንገድ ላይ ጠፍቶአት ከሦስት ቀን ፍለጋ በኋላ በቤተ መቅደስ አግኝታዋለች (ሉቃ.፪፥፵፮)፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ለሄሮድስ በሰጠው ምላሽ መልስ ሦስት ቀን የሱባኤ ፍጻሜ መሆኑን ገልጿል (ሉቃ.፲፫፥፴፪)፡፡

ጾመ ነነዌ የእግዚአብሔርን ቸርነትና መሐሪነት የምናስታውስበት ጾም ነው፡፡ ይኸውም እኛ ፍጡራኑ በበደልን ጊዜ ፈጽሞ ከማጥፋት ይልቅ ምክንያት ፈልጎ እንድንድን ያደርገናል፡፡ ዮናስ ለስብከት ፈቃደኛ ባይሆን እንኳን እግዚአብሔር በተለየ ጥበቡ እንዲሔድ አድርጎታል፡፡ በእርግጥ እግዚአብሔር ሌላ የሚልከው ነቢይ አጥቶም አይደለም፤ እርሱንም ጭምር ሊያስተምረው ስለ ፈለገ እንጂ፡፡ የነነዌ ሰዎች የተነሳሕያን ምሳሌ ናቸው፡፡ ይህም ማለት ሰው ጥፋቱን አምኖ ንስሐ ከገባ እግዚአብሔር ይቅር ማለቱን አይተውም፡፡ ለዚህም ነው ዮናስን ‹‹አንተ ላልደከምክበት እና በአንድ ቀን በቅሎ ላደገ ቅል ስታዝን እነሆ በታላቂቱ ነነዌ ከተማ ያሉ ከአንድ መቶ ሃያ ሺሕ በላይ ሕዝብና እንስሳቱ የእጄ ፍጥረቶች ስለ ሆኑ ያሳዝኑኛል›› ያለው፡፡

ቀደምት የቤተ ክርስቲያን አባቶቻችን ይህን እና ሌሎች አጽዋማትን እንድንጾም የወሰኑልን ያለ ምክንያት አይደለም፡፡ ሕጉ የተዘጋጀልን እንደ ነነዌ ሰዎች እኛም ጾመን፣ ጸልየን ከኃጢአታችን እንነጻ ዘንድ ነው፡፡ ዛሬ ዓለማችን በኃጢአት ማዕበል እየተናወጠች ባለችበት ወቅት እኛም እንደ ነነዌ ሰዎች ከበደላችን ብንመለስ እና ንስሐ ብንገባ ቸሩ ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ይቅርታና ምሕረት የባሕርይ ገንዘቡ ስለ ሆነ ‹‹ወደ እኔ ተመለሱ፤ እኔም ይቅር እላችኋለሁ፤›› ይለናል፡፡

ስለሆነም በነቢዩ ዮናስ ላይ የተደረጉ ተአምራትንና ካለመታዘዝ የሚመጣ ቅጣት ቀላል አለመሆኑን በማስተዋል፣ ለነነዌ ሰዎች የወረደውን ምሕረት በመገንዘብ ለእግዚአብሔርም ሆነ ለሃይማኖት አባቶች እና ለወላጆቻችን መታዘዝ ይገባናል፡፡ ስንጾምም እግዚአብሔር አምላካችን መዓቱን በምሕረት፣ ቍጣውን በትዕግሥት መልሶ በኃጢአት ለጠፋው ዓለም ይቅርታውን ይልካል፡፡ በመጾማችን ራሳችን ከመዓትና ከመቅሠፍት ከመዳናችን ባሻገር በእኛ በደል ምክንያት ሀገራችን፣ ዕፀዋቱና እንስሳቱም ሳይቀር ከድርቅና ከቸነፈር ይተርፋሉና፡፡ (ርእሰ ደብር ብርሃኑ አካል)

ቍጣውን በትዕግሥት መዐቱን በምሕረት ይመልስልን!!!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

09 Feb, 17:13


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን

የካቲት 3-የባሕታዊያን አለቃ ኑሯቸውም የመላእክትን ኑሮ የሚመስል ቅዱሳን መላእክትም ክብራቸውን የመሰከሩላቸው፣ በሌላ ቦታ ያሉ ሰዎችን በቃላቸው ብቻ ይፈውሱ የነበሩት አቡነ ዕብሎይ ዕረፍታቸው ነው፡፡

ሰይጣን በፈተና ጥሏቸው የነበሩና በኋላም ምግብ ሳይበሉ ሳር ብቻ እየተመገቡ 30 ዓመት የኖሩት እግዚአብሔርም ይቅር ብሏቸው ስለእርሳቸው ብሎ በድርቅ ወቅት ዝናብ ያዘነበላቸው አቡነ ያዕቆብ ዕረፍታቸው ነው፡፡
ቅዱስ ኤፍሬም የሥጋው ፍልሰት ሆነ፡፡

አቡነ ያዕቆብ በልጅነቱ የመነኮሰ ሲሆን ኑሮውንም በአንዲት ዋሻ አድርጎ ይኖር ነበር፡፡ ከበዓቱም ባለመውጣት በታላቅ ተጋድሎ ይኖር ነበር፡፡ የሴትንም ፊት አያይም ነበር፡፡ በእንደዚህም ዓይነት በታላቅ ተጋድሎው 15 ዓመት ኖረ፡፡ ከዚህም በኃላ ዲያብሎስ እርሱን ከሚከተሉት ክፉ ሰዎች ውስጥ አንዷን ሴት በምክንያት አድርጎ ወደ በዓቱ እንድትገባ አደረጋት፡፡ በገባችም ጊዜ የኃጢአትን ሥራ እያስታወሰች በአባ ያዕቆብ ፊት ትጫወት ጀመረች፡፡ እርሱም ገሠጻት፣ በገሀነም እሳትም ዘላለም እየተቃጠሉ ስለመኖር አሳሰባትና ደንግጣ ንስሓ ገብታ እግዚአብሔርንም የምታገለግል ሆነች፡፡
ነገር ግን ሰይጣን አሁንም መፈታተኑን አላቆመም፡፡ የአንዱን ታላቅ የመንግሥት ሴት ልጅ አደረባትና ይጥላት ጀመር፡፡ አባቷም ይፈውስለት ዘንድ ወደ አባ ያዕቆብ አመጣትና በጸሎታቸው አዳኗት፡፡ ንጉሡ አባቷም ‹‹ሰይጣኑ እንዳይመለስባት ትንሽ ትቆይ›› በማለት ከታናሽ ብላቴና ወንድሟ ጋር አባ ያዕቆብ ዘንድ ትቷት ሄደ፡፡ ሰይጣንም በልጅቱ ላይ አድሮ አባ ያዕቆብን በፈተና ጣለውና በዝመት እንዲወድቅ አደረገው፡፡ ሰይጣን አባ ያዕቆብን በኃጢአት እንዲወድቅ ካደረገው በኋላ ስለ እርሷ እንዳይገድሉት በመፍራትና ኃጢአቱ እንዳይገለጥበት በሚል ሰበብ ድጋሚ ሌላ ኃጢአት እንዲሠራ አደረገው፡፡ ይኸውም ልጅቷንና ወንድሟን ገደላቸው፡፡

ከዚህም በኋላ ሰይጣኑ ቀቢጸ ተስፋ በልቡ አሳደረበትና ፍጹም ተስፋ እንዲቆርጥ አደረገው፡፡ አባ ያዕቆብም ከበዓቱ ወጥቶ ወደ ዓለም ይሄድ ዘንድ ተጓዘ፡፡ የኃጢአተኛውን መጥፋት የማይወድ እግዚአብሔርን ግን ጻድቅ የሆነ አንድ መነኮሴ ላከለትና በመንገድ ተገናኙ፡፡ ጻድቁ መነኩሴም አባ ያዕቆብን ‹‹ምነው ፈጽመህ ተክዘህና አዝነህ አይሃለሁሳ?›› ብሎ ጠየቀው፡፡ አባ ያዕቆብም ያደረገውን ሁሉ ነገረው፡፡ መነኩሴውም የእግዚአብሔርን መሐሪነትና ይቅር ባይነት እያስታወሰ ካስተማረው በኋላ የጾም የጸሎትና የስግደት ቀኖና እንዲይዝ አዘዘው፡፡ አባ ያዕቆብም ከአንድ ፍርኩታ ውስጥ ገብቶ በውስጡ ራሱን እሥረኛ አደረገ፡፡ በብዙ ችግርና ሥቃይም መጋደል ጀመረ፡፡ ምግብም ሳይበላ ሳር ብቻ እየተመገበ ‹‹እግዚአብሔር ይቅር ይለኝ ይሆን?›› እያለ 30 ዓመት ኖረ፡፡

እግዚአብሔርም ንስሓውን የተቀበለው መሆኑን ለመግለጽ ወደደ፡፡ በሀገሪቱም ታላቅ ርሃብ ሆነና ጌታችን ለሀገሪቱ ኤጲስ ቆጶስ ‹‹በፍርኩታ ውስጥ ከሚኖር ከመነኮስ ያዕቆብ ጸሎት በቀር ይህ ርሃብ አይጠፋም›› አለው ።
ኤጲስ ቆጶሱም ካህናቱንና ሕዝቡን ይዞ ወደ አባ ያዕቆብ መጥቶ እንዲጸልይላቸው ለመኑት፡፡ እርሱም ‹‹እኔ ለራሴ ኃጢአተኛ ነይና ተውኝ›› ሲላቸው ኤጶስ ቆጶሱም ይህ እንዲሆን የእግዚአብሔር ትእዛዝ መሆኑን ነገረው፡፡ በዚያም ጊዜም ከበዓቱ ወጥቶ ከሕዝቡ ጋር ተቀላቅሎ እንዲህ ብሎ ጸለየ ፦

‹‹አቤቱ በጌትነትህ ክብር ፊት የረከሰች አፌን እንዴት እገልጣለሁ? በኃጢአት ብዛት የጠቆረ ፊቴንስ እንዴት ቀና አደርጋለሁ? ነገር ግን እንደ ቸርነትህ መጠን ሕዝብህን ይቅር በል አንተ በባሕርይ ይቅር ባይ ነህና…›› እያለ በጸለየ ጊዜ ወዲያው ዝናብ ዘነበ፡፡ እርሱም ኃጢአቱን እግዚአብሔር ይቅር እንዳለው ዐወቀ፡፡ ነፍሱንም እየገሠጸ ከበፊቱ በበለጠ ሁኔታ እየተጋደለ ኑሮ የካቲት 3 ቀን በሰላም ዐረፈ፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!
አባ ዕብሎይ፡- በዕብሎይ ስም የተጠሩት ይኸኛው አባት ‹‹የባሕታዊያን አለቃ›› የተባሉ ኑሯቸውም ‹‹የመላእክትን ይመስላል›› የተባለላቸው ታላቅ አባት ናቸው፡፡ ቅዱስ አትናቴዎስ ከስደቱ በተመለሰ ጊዜ ወደ ቂሳርያው ኤጲስቆጶስ አባ ባስልዮስ ዘንድ መጥቶ አንድ ላይ አድረው በግብፅ ገዳም ስለነበሩ ቅዱሳን እየተጨዋወቱና እያወዳደሩ ሲወያዩ አደሩ፡፡ በማግስቱም ቅዱስ አትናቴዎስ ታላቅ ራእይን አየ፡፡ ይኸውም እስከ ሰማይ የምትደርስ ታላቅ ዛፍ ነበረች፣ ቅርንጫፎቿ እስከ ባሕር ደርሰዋል፡፡ ብዙ ሰዎችም ከቅርንጫፎቿ በታች ተጠልለዋል፡፡ በመካከሏም መሠዊያ ታቦት አለ፡፡ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ለአባ አትናቴዎስ ተገለጠላቸውና ‹‹ያየኸውን ራእይ ከአባ ባስልዮስ ጋር ተነጋገር ምሥጢሩን እኔ እገልጥልሃለሁ›› አለው፡፡ መልአኩም ምሥጢሩን ለሁለቱ ቅዱሳን አባቶች ተረጎመላቸው፡፡ ‹‹ዛፏ በግብፅ አውራጃ የምትሠራ ገዳም ስትሆን ቅርንጫፎቿ መነኮሳት ናቸው፡፡ መሠዊያውም መላእክት የሚጎበኙት የእግዚአብሔር ማደሪያ ርኩሳን መናፍስትን የሚሽር የሐዋርያት አለቃ የጴጥሮስ አምሳል የሆነ አባ ዕብሎይ ነው›› በማለት ገልጾላቸዋል፡፡
አባ ዕብሎይ እጅግ ታላላቅ ተአምራትን በማድረግ ይታወቃሉ፡፡ መልካቸው እየተለወጠ እንደሚነድ እሳት እየሆኑ ሰውነታቸው የሚያቃጥልበት ጊዜ አለ፡፡ በቃላቸው ብቻ ለምጻሞችን ያነጹ ነበር፡፡ በእስክንድርያ የሚኖር አንድ የመቶ አለቃ የአባ ዕብሎይን ዜና ሰምቶ በረከታቸውን ይቀበል ዘንድ ወደ አባ ዕብሎይ እንዲልከው ሊቀ ጳጳሳቱን ቅዱስ አትናቴዎስን ለመነውና እርሱም ከ7 መነኮሳት ጋር ላከው፡፡ የመቶ አለቃውም አባ ዕብሎይን ባገኛቸውና በተሳለማቸው ጊዜ ዕውር የነበረቸው አንድ ዐይኑ ወዲያው በራችለት፡፡ ዳግመኛም ‹‹ሚስቴ በለምጽ ደዌ ትጨነቃለችና እርሷም በአስኬማህ የተማጸነች ናትና እኔ ያገኘሁትን ጸጋህን ለእርሷም ይድረሳት›› እያለ ለመናቸው፡፡ አቡነ ዕብሎይም ‹‹በክብር ባለቤት በጌታችን ስም ፈውስ ይሁንላት›› ብለው በተናገሩበት ቅጽበት የመቶ አለቃው ሚስት ባለችበት ሆና ከደዌዋ ተፈወሰች፡፡
አቡነ ዕብሎይ ለመኮሳቱ ‹‹ጌታችን ዛሬ በዚህ ቦታ ይገለጣልና በዚህ ቆዩ›› እያሉ ይነግሯቸው ነበር፡፡ እንዳሉትም ጌታችን በአካል ተገልጦላቸው ቤተ መቅደሱን የሚሠሩበትን ቦታ አሳይቷቸዋል፡፡ በመጨረሻም የካቲት 3 ቀን ሊያርፉ ሲሉ ፊታቸው ተለውጦ የእግዚአብሔርን መልክ መሰለ፡፡ መነኮሳት ልጆቻቸውንም ተሰናብተዋቸውና ባርከዋቸው በሰላም ዐረፉ፡፡
የአቡነ ዕብሎይ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!

ዳግመኛም በዚህች ዕለት የቅዱስ ኤፍሬም የሥጋው ፍልሰት ሆነ፡፡ (የዕረፍቱን ዕለት ሐምሌ ዓሥራ አምስትን ይመለከቷል፡፡)
ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

08 Feb, 15:56


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን !
የካቲት 2 -የመላእክት ወገን የሆኑ የገዳማውያን ሁሉ አለቃ የከበሩ አባ ጳውሊ ዕረፍታቸው ነው፡፡
+ የቅዱሳን ዐፅም ቃል በቃል በማናገር የሃይማኖትን ነገር የተረዱት የደብረ ዝጋጉ አባ ለንጊኖስ ዕረፍታቸው ነው፡፡
+ ዳግመኛም በዚህች ዕለት የከበረ ሐዋርያ ቅዱስ ቶማስ አስገራሚ ተአምራት በማድረግ ብዙዎችን አስተምሮ አጥምቋል፡፡

አባ ለንጊኖስ ዘደብረ ዝጋግ፡- ትውልዳቸው ኪልቂያ ሲሆን በልጅነታቸው ገዳም ገብተው በመመንኮስ የአባ ሉክያኖስ ደቀ መዝሙር ሆነው በተጋድሎ ኖረዋል፡፡ መምህራቸው አባ ሉክያኖስን አበ ምኔትነት ሊሾሟቸው ሲሉ ውዳሴ ከንቱን በመጥላት አባ ለንጊኖስን ይዘው በድብቅ ወደ ሶርያ ሄዱ፡፡ በአንዲት ቤተ ክርስቲያንም ተቀምጠው ብዙ አስገራሚ ተአምራትን ያደርጉ ነበር፡፡ ዜናቸው በሁሉም ዘንድ ሲሰማ አሁንም ውዳሴ ከንቱን በመራቅ በአባታቸው ምክር አባ ለንጊኖስ ወደ ግብጽ ሄደው ደብረ ጽጋግ ገዳም ገቡ፡፡ በዚያም አበምኔቱ ሲያርፉ በእግዚአብሔር ትእዛዝ አባ ለንጊኖስን አበ ምኔት አድርገው ሾሟቸው፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ መምህራቸው አባ ሉክያኖስ መጥተው የመርከብ ጣሪያ እየሠሩ አብረው በአንድ ልብ ሆነው በተጋድሎ ኖሩ፡፡ ድንቅ ድንቅ ተአምራት እያደረጉ ብዙ ከኖሩ በኋላ አባ ሉክያኖስ ሲያርፉ ‹‹የውሾች ጉባዔ›› እየተባለ የሚጠራውና ጌታችንን ‹ሁለት ባሕርይ› የሚለው የሮም የረከሰ እምነት በጉባዔ ተወሰነ፡፡ ከሃዲው ንጉሥ መርቅያኖስም በሀገሮች ሁሉ የጉባዔውን ደብዳቤ መላክ ጀመረ፡፡

የንጉሡንም ደብዳቤ መልአክተኞቹ ለአባ ለንጊኖስ አመጡላቸውና ‹‹በዚህ ጽሑፍ እንድታምኑና እንድትፈርሙበት ንጉሡ አዟል›› ብለው ሰጧቸው፡፡ አቡነ ለንጊኖስም ‹‹ከቅዱሳን አባቶቼ ጋር ልማከርበት እኔ ምንም ምን መሥራት አልችልም እንድንማከርበት እናንተም ከእኔ ጋር ኑ›› ብለው የቅዱሳን ዐፅም ወዳለበት ዋሻ ውስጥ ይዘዋቸው ሄዱ፡፡ አባታችንም ለአፅሞቹ እንዲህ ብለው ተናገሩ፡- ‹‹የከበራችሁ ቅዱሳን አባቶቼ ሆይ! እናንተ ዐርፈን ተኝተናል አትበሉ፣ እነሆ አንዱን ክርስቶስን ሁለት ባሕርይ የሚያደርግ በውስጡ የተጻፈበትን ይህን ደብዳቤ አምጥተዋልና በቃሉ አምን ዘንድ በውስጡም እፈርም ዘንድ ታዙኛላችሁን?›› እያሉ ዐፅሞቹን ጠየቋቸው፡፡ ያን ጊዜም የተላኩት ሰዎች ሁሉ እየሰሙ ከቅዱሳኑ አስክሬን ውስጥ እንዲህ የሚል ቃል ወጣ፡- ‹‹የአባቶቻችንን የሐዋርያትንና የ318ቱን የቀናች ሃይማኖትን አትተው፣ ይህንንም የረከሰ ደብዳቤ አትከተል፣ ከአስክሬናችን ቦታ አርቀው እንጂ›› የሚል ቃል ከቅዱሳኑ አስክሬን ወጣ፡፡ ይህንንም የሰሙት የንጉሡ መልእክተኞች እጅግ አድንቀው ወደ ንጉሡ አልተመለሱም፤ ይልቁንም ራሳቸውን ተላጭተው በዚያው መነኮሱ እንጂ፡፡ እስከ ዕለተ ዕረፍታቸውም በታላቅ ተጋድሎ ኖሩ፡፡ የከበሩ አባ ለንጊኖስም ያማረ ተጋድሎአቸውን ጨርሰው በሰላም ዐርፈዋል፡፡ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!
+++
የከበረ ሐዋርያ ቅዱስ ቶማስ ተአምራት በማድረግ ብዙዎችን እንዳጠመቀ፡- ይኸውም ጌታችን ወዳዘዘው ቦታ የከበረች ወንጌልን ሊያስተምር በወጣ ጊዜ ከመንገድም ፈቀቅ ብሎ ሳለ መልኩ በጣም የሚያምር ድንገት የሞተ አንድን ጎልማሳ አገኘ፡፡ ቅዱስ ቶማስም ‹‹አቤቱ ይህን ጥፋት አይ ዘንድ ወደዚህ አመጣኸኝን ነገር ግን ፈቃድህ ይሁን›› አለ፡፡ ከዚህም በኋላ ስለሞተው ሰው ጸለየ፣ ያንጊዜም ታላቅ ከይሲ ከድንጋዮች ውስጥ ወጥቶ በጅራቱ ምድርን እየደበደበ መጣና ‹‹የክርስቶስ ሐዋርያ ሆይ! እኔ ከአንተ ጋራ ምን አለኝ? ሥራዬን ልትዘልፍ ልታጋልጥ መጣህን!›› ብሎ በታላቅ ድምጽ ጮኸ፡፡ ቅዱስ ቶማስም ‹‹ሥራህን ተናገር›› አለው፡፡ ከይሲውም ‹‹በዚህ ቦታ መልከ መልካም ሴት ነበረች፣ እኔ የምወዳት ናት፡፡ ይህም ጎልማሳ ሲስማት አየሁት፡፡ በሰንበት ቀንም ከእርሷ ጋር አደረ፡፡ ስለዚህም ነክሼ በመርዝ ገደልኩት›› አለው፡፡ ሐዋርያውም ‹‹በል አሁን መርዝህን ከእርሱ ትወስድ ዘንድ በጌታዬ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አዝዤሃለሁ›› አለው፡፡ ከይሲውም ሄዶ ከዚያ ከሞተው ሰው መርዙን መጠጠና ወሰደ፡፡ ወዲያውም ተነፍቶ አበጠና ተሰንጥቆ ሞተ፡፡ ሞቶ የነበረው ጎልማሳ ግን በሐዋርያው ጸሎት ከሞት ተነሣ፡፡ ስለዚህችም የሐዋርያው የቅዱስ ቶማስ ተአምር ብዙዎች በክብር ባለቤት በጌታችን አመኑ፡፡ ቅዱስ ቶማስም የቀናች ሃይማኖትን አስተምሮ አጠመቃቸው፡፡
የቅዱስ ቶማስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!++++
ርዕሰ ገዳማውያን አቡነ ጳውሊ፡- አባታቸው የገንዘቡን መጠን እንኳን የማያውቁት እጅግ ባለጸጋ ነበሩ፡፡ አባታቸው ከሞቱ በኋላ ወንድማቸው ጴጥሮስ ንብረታቸውን በትክክል አላካፍላቸው ስላለ ተጣልተው ወደ ዳኛ ሄዱ፡፡ በመንገድ ላይ ሳሉ አንድ ሰው ሞቶ ሊቀብሩት ሲወስዱት አይተው አባ ጳውሊ አገኟቸው፡፡ የሞተው ማን እንደሆነም ሲጠይቁ የሞተው ሰው እጅግ ባለጸጋ እንደነበር በኃጢአት ውስጥም ሆኖ እንደሞተ ተነገራቸው፡፡ ከዚህም በኋላ አባ ጳውሊ ‹‹የዚህ የኃላፊ ዓለም ገንዘብ ለእኔ ምኔ ነው?›› ብለው ወደ ወንድማቸው ዞረው ወደ ዳኛ መሄዳቸውን ትተው ወደቤት እንዲመለሱ ለመኑት፡፡ የአባታቸውንም የተትረፈረፈ ሀብትና ንብረት ፈጽሞ እንደማይፈልጉት ነገሩት፡፡
ከወንድማቸውም ተደብቀውና ሸሽተው በመውጣት በአንዲት በመቃብር ቤት ገብተው መጸለይ ጀመሩ፡፡ በ4ኛ ቀናቸውም የታዘዘ መልአክ መጥቶ ነጥቆ ወስዶ ከአንድ በረሃ ውስጥ አደረሳቸው፡፡ አባ ጳውሊም ወደ አንዲት ኩርፍታ ገብተው ተጋድሎአቸውን ጀመሩ፡፡ በዚያች ዋሻ ውስጥም የሰውን ፊት ሳያዩ በጾም በጸሎት ብቻ ተወስነው 80 ዓመት ኖሩ፡፡
ልብሳቸውም ከሰሌን ቅጠል የተሠራ ነው፡፡ እግዚአብሔር እንደ ነቢዩ ኤልያስ ቁራን እየላከ ምግባቸውን ይሰጣቸው ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ ጌታችን የጳውሊን ክብር ይገልጥ ዘንድ መልአኩን ወደ አባ እንጦንስ ዘንድ ላከው፡፡ አባ እንጦንስም በበረሃ ውስጥ በታላቅ ተጋድሎ ከኖሩ በኋላ በበረሃ መኖር የጀመሩት እሳቸው እንደሆኑ በልባቸው ማሰብ ጀምረው ነበር፡፡ መልአኩም ተገልጦላቸው ‹‹እንጦንስ ሆይ ከአንተ የሁለት ቀን ጎዳና ርቆ በበረሃ ውስጥ የሚኖር ሰው አለ፤ የዓለም ሰዎች ከሚረግጥባቸው የእግሩ ጫማዎች እንደ አንዲቱ ሊሆኑ የማይገባቸው ስለ እርሱም ጸሎት ዓለም ተጠብቆ የሚኖር ነው…›› እያለ የአባ ጳውሊ ክብር ነገራቸው፡፡
አባ እንጦንስም የአባ ጳውሊን በዓት ፈልገው አግኝተው ሄደው በብዙ ምልጃ በሩን ከፍተውላቸው ተገናኝተው ሁለቱም አብረው ከጸለዩ በኋላ ስለ ተጋድሎአቸውና ስለ አኗኗራቸው ተወያዩ፡፡ የታዘዘው ቁራ ሌላ ጊዜ የጳውሊን ምግብ የሚያመጣው ግማሽ እንጀራ ነበር ዛሬ ግን ሙሉ እንጀራ ስላመጣላቸው ሁሉቱም ቅዱሳን ደስ ተሰኝተው እግዚአብሔርን አመሰገኑ፡፡ አባ እንጦንስም ሥጋ ወደሙን ከወዴት እንደሚቀበሉ አባ ጳውሊን ሲጠይቋቸው በየሳምንቱ ቅዳሜና እሁድ መልአክ እያመጣ ሥጋ ወደሙን እንደሚያቀብላቸው ነገሯቸው፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

08 Feb, 15:56


ከዚህም በኋላ አባ እንጦንስ ‹‹ይህ አስኬማ በምድር ላይ ይበዛ እንደሆነ ወይም አለመብዛቱን ትነግረኝ ዘንድ እሻለሁ›› አሏቸው፡፡ አባ ጳውሊም ወደፊት ስለሚመጡ መነኮሳት በመጸለይ ወደ ሰማይ ካዩ በኋላ በመጀመርያ ፈገግ አሉ፡፡ አባ እንጦንስም ‹‹ምን አየህ?›› ቢሏቸው አባ ጳውሊ ‹‹ነጫጭ ርግቦች በጠፈር መልተው አንተ እየመራሃቸው ተከትለውህ ሲሄዱ አየሁ›› አሏቸው፡፡ ‹‹ይህስ ምንድን ነው?›› ቢሏቸው ‹‹እሊህማ በዚህ በቆቡ የምትወልዳቸው ንጹሐን ጻድቃን ልጆችህ ናቸው›› አሏቸው፡፡ ‹‹ሁለተኛ አመልክትልኝ›› አሏቸው፡፡ ጳውሊም ካመለክቱ በኋላ አዝነውና ተከፍተው ተመለከቷቸው፡፡ ‹‹ምነው?›› ቢሏቸው ‹‹በክንፋቸው ጥቁር ተቀላቅሎባቸው አየሁ›› አሉ፡፡ ‹‹ምንድን ናቸው?›› ቢሏቸው ‹‹ጽድቅና ኀጢአት እየቀላቀሉ የሚሠሩ ልጆችህ ናቸው›› አሏቸው፡፡ እንጦንስም ካዘኑ በኋላ ‹‹ሦስተኛም አመልክትልኝ›› አሏቸው፡፡ አባ ጳውሊም ለሦስተኛ ጊዜ ካመለከቱ በኋላ በድንጋጤ ቃላቸውን ከፍ አድርገው ጮኹ፡፡ አባ እንጦንስም ‹‹ምነው?›› ቢሏቸው አባ ጳውሊ እንዲህ አሉ፡- ‹‹ነገር ግን በመጨረሻ ዘመን የሚነሡቱ እንደ ቁራ ጠቁረው አየሁዋቸው›› አሉ፡፡ ‹‹ምንድን ናቸው?›› ቢሏቸው ‹‹ሀሳሲያነ ሢመት (ሹመት ፈላጊዎች)፣ መፍቀሪያነ ንዋይ (ገንዘብ የሚወዱ) እና ከመኳንንትም ጋር በጥዋት ማዕድ የሚቀመጡ በፍጻሜ ዘመን የሚነሡ ኀጥአን ልጆችህ ናቸው›› አሏቸው፡፡ ይህን ጊዜ አባ እንጦንስ ‹‹ያለ ንስሓ ባይጠራቸው እስኪ አመልክትልኝ›› አሉ፡፡ አባ ጳውሊም አመለከቱ ነገር ግን የዚህ ምላሽ አልመጣላቸውም፡፡

ከዚህም በኋላ አባ ጳውሊ አባ እንጦንስን ወደ በዓታቸው ሄደው ቈስጠንጢኖስ ለሊቀ ጳጳሳት አትናቴዎስ የሰጣቸውንና አትናቴዎስ ደግሞ ለእሳቸው የሰጧቸውን የከበረች ልብስ አምጥተው በእርሷ ይገንዟቸው ዘንድ ጠየቋቸው፡፡ አባ እንጦንስም አባ ጳውሊ የተሰውረውን ሁሉ በማወቃቸው አደነቁ፡፡ ዳግመኛም አባ ጳውሊ ስለ ቆቡ አባ እንጦንስን ‹‹እንግዲህ ይህን ከራስህ ያደረግኸውን ለኔ ስጠኝ ላንተ ሌላ ሠርተህ አድርግ›› አሏቸው፡፡ አባ እንጦንስም ‹‹ይህንንስ እንዳልሰጥህ ከባለቤቱ ተቀብዬዋለሁ፡፡ ነገር ግን ሥራውን ለምጄዋለሁ ሌላ ሠርቼ ላምጣልህ›› አሏቸው፡፡ ጳውሊም ‹‹እንግዲያስ አትዘግይ ቶሎ ሠርተህ አምጣልኝ›› አሏቸው፡፡ እንጦንስም የ2 ሰዓት መንገድ ተጉዘው ወደ በዓታቸው ሄደው ቆቡን ሠርተው ይዘው ሲመጡ ጳውሊ ዐርፈው ነፍሳቸውን መላእክተ ብርሃን ይዘዋት ሲያርጉ ተመለከቱ፡፡

መላእክቱም ‹‹ጳውሊ ዐርፏልና ሄደህ ቅበረው›› አሏቸው፡፡ ‹‹ይህንሳ የያዝኩትን ቆብ ልተወውን?›› ቢሏቸው፡፡ ‹‹አትተው አድርግለት›› ብለው መለሱላቸው፡፡ ይህም በምንኩስና የሠሩት ሥራ ከንቱ እንዳይደለ ለማጠየቅ ነው፡፡ አባ እንጦንስም ቢሄዱ አባ ጳውሊ መጽሐፋቸውን ታቅፈው፣ አጽፋቸውን ተጎናጽፈው፣ ከበዓታቸው ዐርፈው አገኟቸው፡፡ እርሳቸውም የአባ ጳውሊን ሥጋ በልብሱ ሸፍነው በጸሎታቸው እንዲያስቧቸው እየተማጸኑ አለቀሱ፡፡ የሥጋቸውንም ጉዳይ ከእሳቸው ጋር እንዳልተማከሩ ሲያስቡ የታዘዙ አንበሶች መጥተው እጅ ከነሷቸውና እግራቸውን ከላሱ በኋላ የአባ ጳውሊን ሥጋ የሚቀብሩበትን ቦታ አሳይተዋቸው ቆፈሩላቸው፡፡ አንበሶቹም ቆፍረው ሲጨርሱ ወጥተው ሰግደውላቸው እሳቸውም ባርከዋቸው ሄዱ፡፡
አባ ጳውሊንም በክብር ከቀበሯቸው በኋላ ወደ እስክንድርያ ሄደው ለአባ አትናቴዎስ የሆነውን ሁሉ ከነገሯቸው በኋላ የሰሌን አጽፋቸውን ሰጧቸው፡፡
የከበረ ሊቀ ጳጳሳት አባ አትናቴዎስም ያችን የአባ ጳውሊን አጽፍ በክብር አስቀምጠው በዓመት ሦስት ጊዜ ብቻ ማለትም በልደት፣ በጥምቀትና በትንሣኤ በዓል ብቻ ይለብሷት ነበር፡፡
በሞተም ሰው ላይ ጥለዋት ሙት አስነሥተውባታል፡፡
የርዕሰ ገዳማውያን የአቡነ ጳውሊ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን! አሜን።

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

08 Feb, 09:35


በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ማይ ሽጉርቲ እና ሴሮ የሚገኙት የአቡነ እንድርያስ ኹለት ገዳማት። ከበዓለ ዕረፍታቸው ረድኤት በረከት ይክፈለን።

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

08 Feb, 09:35


የካቲት 1-ገድለ አቡነ እንድርያስ፣ ገድለ አቡነ ሲኖዳ፣ 150ው የቍስጥንጥንያ ቅዱሳን አበው እና መልእክት በወቅታ...
https://youtube.com/watch?v=OOLlW8BzqGg&si=hi5YJk1yu30Z1fV2

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

03 Feb, 17:28


አገልጋዩም ያችን በፍታ ወደ አገሩ ወስዶ ምን እንደሚያደርግ እያሰበ ሳለ ቅዱስ ቢፋሞን ተገለጠለትና ለወዳጁ ለቴዎድሮስና ለአገሩ ሰዎችም ሁሉ ገድሉን እንዲነግር አዘዘው፡፡ እርሱም በመርከብ ተሳፍሮ ሲሄድ በመርከብ ሳለ ጌታችን በዚያች በቅዱስ ቢፋሞን ደም በታለለች በፍታ ብዙ ተአምር አደረገ፡፡ ዲዮጋኖስም የቅዱሱን ገድል ነገራቸው፡፡ እነርሱም እያደነቁ ወደ አገሩ አውሲም አደረሱት፡፡
ዲዮጋኖስም አውሲም እንደደረሰ ለቅዱስ ቴዎድሮስና ለአገሩ ሰዎች ሁሉ የቅዱስ ቢፋሞንን ገድል ነገራቸው፣ ያችንም በደሙ የታለለች በፍታ ሰጣቸው፡፡ እነርሱም ብዙ ተአምራት እያደረገችላቸው ከእነርሱ ጋር በክብር አኖሯት፡፡ የመከራው ዘመን አልፎ ደገኛው ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ከነገሠ በኋላ እግዚአብሔርም የከበረ የቅዱስ ቢፋሞንን ሥጋ ገለጠላቸው፡፡ እነርሱም ከቅዱስ ቢፋሞን ሥጋ በረከትን እየተቀበሉ በሰላም ኖሩ፡፡
የሰማዕቱ የቅዱስ ቢፋሞን ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!
+ + +
የሐዋርያው የቅዱስ ጢሞቴዎስ የከበረ ሥጋው ከኤፌሶን አገር ወደ ቁስጥንጥንያ ከተማ እንደፈለሰ፡- ይኸውም ጻድቁ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ በነገሠ ጊዜ የከበሩ የሐዋርያትን እና የሰማዕታትን ሥጋቸውን ከየአገሩ ሁሉ እየሰበሰበ ወደ ቁስጥንጥንያ በክብር አስመጣው፡፡ የሐዋርያው የቅዱስ ጢሞቴዎስም ቅዱስ ሥጋው በኤፌሶን አገር እንዳለ ሲሰማ ካህናትንና ዲቆናትን ምእመናንንም ልኮ በክብር ወደ ቁስጥንጥንያ አስመጣው፡፡ በከበሩ በሐዋርያት ቤተ መቅደስም ውስጥ አኖረው፡፡ የሐዋርያው የቅዱስ ጢሞቴዎስን ዜና ዕረፍቱን ጥር 23 ቀን ጽፈነዋል፡፡ ሙሉ ታሪኩን ከዚያ ላይ ይመለከቷል፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!
+ + +
ዕርገተ ሄኖክ፡- አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር ስላደረገ በሞት ፋንታ የተሰውረው ነቢዩ ቅዱስ ሄኖክ የዕርገቱ መታሰቢያ በዚህች ዕለት ሆነ፡፡ ዘፍ 5፡21፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም "ሄኖክ ሞትን እንዳያይ በእምነት ተወሰደ፥ እግዚአብሔርም ስለ ወሰደው አልተገኘም። ሳይወሰድ እግዚአብሔርን ደስ እንዳሰኘ መስክሮለታልና" በማለት ገልጾታል፡፡ ዕብ 11፡5፡፡ ነቢዩ ሄኖክ ብዙ ሰማያዊ ምሥጢራትን ያየ ነው፡፡ ስለጌታችንም እንዲህ ብሎ ትንቢትን ተናገረ፡- ‹‹የዘመናት አለቃ ወደሆነው የሰው ልጅ ተጠራ፣ ዓለም ከመፈጠሩ አስቀድሞ የነበረ ሆነ፣ ሁለተኛም ለጻድቃን የጽድቅ በትር ለአሕዛብም ብርሃን ተስፋ ለሌላቸውም አለኝታ ይሆናል›› አለ፡፡ ዳግመኛም ስለምኩራብ ሲናገር ‹‹ያንን አሮጌ ቤት እስኪያሳንሰው ድረስ አየሁ፣ ምሰሶዎቹንም ከውስጡ አውጣ፡፡ ስለ ቤተ ክርስቲያንም ጌታ አዲስ የበጎች ቤት አምጥቶ ሲሠራ አየሁ፣ ከቀድሞውም የበለጠ ነው፣ በጎችም ሁሉ በውስጧ ይሰማራሉ›› አለ፡፡ ስለ ምእመናንም ‹‹የእነዚህ በጎች ፀጉራቸው ንጹሕ ነጭ ነው፣ የተበተኑትም ከአራዊት ጋራ ይሰማራሉ፤ ሁሉም በአንድነት ተሰብስበው ገራሞች ሆነዋል›› አለ፡፡
የነቢዩ የቅዱስ ሄኖክ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!
ከገድላት አንደበት

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

03 Feb, 17:28


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ጥር 27-የከበረ ቅዱስ ሰራብዮን በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡
+ አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር ስላደረገ በሞት ፋንታ የተሰውረው ነቢዩ ቅዱስ ሄኖክ የዕርገቱ መታሰቢያ ነው፡፡
+ ገና ሲወለድ 500 ዓመት የሆነውን ሙት ያስነሣውና በተወለደ በ3ኛ ቀኑም ‹‹ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ›› ብሎ አምላኩን ያመሰገነው በኋላም በእሳት ተቃጥሎ በሰማዕትነት ያረፈው ቅዱስ ቢፋሞን የሰማዕትነቱ ፍጻሜ ሆነ፡፡
+ መልአኩ ቅዱስ ሱርያል ዓመታዊ መታሰቢያ በዓሉ ነው፡፡ ይኸውም ለዕዝራ የተሰወረውን ምሥጢር ሁሉ የገለጠለት ነው፡፡
+ ሐዋርያው ቅዱስ ጢሞቴዎስ የከበረ ሥጋው ከኤፌሶን አገር ወደ ቁስጥንጥንያ ከተማ የፈለሰበት ዕለት ነው፡፡
ሰማዕቱ ቅዱስ ሰራብዮን፡- ይኸውም ቅዱስ ከደቡባዊ ግብጽ ከምስር አውራጃ የተገኘ ሰማዕት ነው፡፡ እርሱም በሀብትና ንብረት የበለጸገ ነው፡፡ አብዝቶ መመጽወትን የሚወድ ነው፡፡ ከሃዲው መኮንን ኄሬኔዎስ ክርስቲያኖችን በያሉበት እያሳደደ በሚያሠቃይበትና በሚገድልበት ወቅት ቅዱስ ሰራብዮንም ሰማዕትነትን ይቀበል ዘንድ ወደደ፡፡ ወዲያውም ቅዱስ ሰራብዮን ቴዎድሮስና ሰርማ ከሚባሉ ሁለት ወዳጆቹ ጋር ወደ ከሃዲው መኮንን ዘንድ በመሄድም በፊቱ ቆሞ የጌታችንን ክብር መሰከረ፡፡ መኮንኑ ሁሉንም አሠራቸው፡፡ የሀገሩ ሰዎችም የቅዱስ ሰራብዮን መታሰር በሰሙ ጊዜ ሁሉም ተሰብስበው መኮንኑን ገድለው ከእጁ ለማስጣል በማሰብ ብዙ መሣርያ በመያዝ ለጦርነት ተዘጋጁ ነገር ግን ቅዱስ ሰራብዮን ከለከላቸው፡፡ ‹‹እኔ ራሴ በጌታዬ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ደሜን አፈስ ዘንድ በፈቃዴ የመጣሁ ነኝ›› አላቸው፡፡
መኮንኑም ይዟቸው ከዚያ በመውጣት በመርከብ ተሳፍሮ ወደ እስክንድርያ አገር ደረሰ፡፡ በዚያም ቅዱስ ሰራብዮንን ጽኑ በሆኑ ልዩ ልዩ ማሠቃያዎቸ አሠቃየው፡፡ በመጀመሪያ በመንኮራኩር ውስጥ በመጨመር አሠቃየው፡፡ የእሳት ምድጃም ውስጥ በመጨመር በእሳት አቃጠለው፡፡ ከነዳጅ ድፍድፍና ከቅመማ ቅመም ጋር አድርጎ በትልቅ ድስት አስቀቀለው፡፡ የሥጋውንም ሥሮች አስቆረጣቸው፡፡ በብረት አልጋም ላይ አስተኝቶ በችንካሮች አስቸነከረው፡፡ ቅዱሱም ይህንን ሁሉ ሥቃይ የሚታገስ ሆነ፡፡ የታዘዘ የእግዚአብሔር መልአክም ሥቃዩን ሁሉ እንዲችል ያስታግሰው ከቁስሎቹም ይፈውሰው ነበር፡፡
ከዚህም በኋላ መኮንኑ ቅዱስ ሰራብዮንን በእንጨት ላይ ሰቅሎ በፍላጻዎች አስነደፈው፡፡ የቅዱሱ የዘወትር ጠባቂ የሆነው መልአክም እርሱን ከተሰቀለበት አውርዶ በእርሱ ፈንታ መኮንኑን አሥሮ ሰቀለው፡፡ ቅዱስ ሰራብዮንም በዚህ ጊዜ መኮንኑን ‹‹በክርስቶስ ስም የታሰሩትን ሁሉንም ከእሥር ቤት እስከምታወጣቸውና የሞታቸውን ፍጻሜ እስከምታዝ ድረስ ከዚህ ከተሰቀልክበት እንጨት እንደማትወርድ ዕወቅ›› አለው፡፡ መኮንኑም የቅዱስ ሰራብዮንን ትእዛዝ በመቀበል በእስር ቤት ያሉትን ሁሉንም እንዲያወጧቸውና ራስ ራሶቻቸውን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ፡፡ እንዳዘዘውም እንዲሁ አደረጉና አንገታቸውን ቆረጧቸው፣ የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀዳጁ፡፡ የእነዚህም ሰማዕታት ቁጥራቸው 540 ሆነ፡፡ በረከታቸው ይደርብን፡፡
ከዚህም በኋላ የከበረ ቅዱስ ሰራብዮንን ወደ ሌላ አገር ወስዶ ያሠቃየው ዘንድ ከሀሳቡም ካልተመለሰ ራሱን በሰይፍ ይቆርጠው ዘንድ ኄሬኔዎስ አንዱን መኮንን አዘዘው፡፡ መኮንኑም በመርከብ ይዞት ሄደ፡፡ ሌሊትም በሆነ ጊዜ ከአንድ ወደብ ደርሰው ሲተኙ መርከቧ በእግዚአብሔር ፈቃድ ያለ አቅጣጫዋ ከቅዱስ ሰራብዮን አገር ደረሰች፡፡ ሲነጋም በነቁ ጊዜ የመሄጃቸው አቅጣጫ ተለውጦ አገኙት፡፡ ‹‹ሰራብዮን ሆይ! እነሆ ይህች ሰማዕትነትህን የምትፈጽምባት አገርህ ናት›› የሚል ድምጽ ከሰማይ መጣ፡፡ በዚህም ጊዜ ቅዱስ ሰራብዮንን ከመርከብ አውርደው ታላቅ ሥቃይን አሠቃይተው በመጨረሻ ራሱን በሰይፍ ቆረጡት፡፡ በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ፡፡ የሰየፈው መኮንንም ልብሶቹን አውጥቶ ገንዞ ለዘመዶቹ ሰጠው፡፡
የሰማዕቱ የቅዱስ ሰራብዮን ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!
+ + +
ሰማዕቱ ቅዱስ ቢፋሞን፡- ይኸውም ቅዱስ ገና ሲወለድ 500 ዓመት የሆነውን ሙት አስነሥቷል፡፡ በተወለደ በ3ኛ ቀኑም ‹‹ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ›› ብሎ አምላኩን አመስግኗል፡፡ አባቱ ከከበሩ ወገኖች የሆነ ስሙ አንስጣስዮስ እናቱ ሶስና ይባላሉ፡፡ እነርሱም መመጽወትን የሚወዱ ደገኛ ክርስቲያኖች ናቸው፡፡ በእመቤታችንና በቅዱሳን የበዓላት ቀን ለድኆችና ለጦም አዳሪዎች ምጽዋትን በመስጠት ያከብራሉ፡፡ የሚኖሩትም በምስር አገር አውሲም በሚባል ቦታ ነው፡፡
እግዚአብሔርም ደግነታቸውን ተመልክቶ መልኩ እጅግ ያማረ ልጅ ቅዱስ ቢፋሞንን ሰጣቸው፡፡ እነርሱም ገና ሲወልድ ጀምሮ ብዙ ተአምራት አድጎላቸዋልና እጅግ ደስ አላቸው፡፡ በሃይማኖት በምግባር ኮትኩተው አሳደጉት፡፡ ዘጠኝ ዓመትም በሆነው ጊዜ ሃይማኖትንና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን እንዲማር ለአንድ መምህር ሰጡት፡፡ ከመምህሩም ዘንድ ጥበብንና ተግሣጽን የቤተ ክርስቲያንንም መጻሕፍት ሁሉ አጠና፡፡ ከልጅነቱም ጀምሮ በጾም በጸሎት በስግደት ይጋደል ነበር፡፡ እግዚአብሔር ለቅዱስ ቢፋሞን ገና በልጅነቱ በእጆቹ ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን የማድረግ ጸጋ ሰጠው፡፡ በቁስል ደዌ እጆቹንና እግሮቹን የታመመ አንድ ድኃ ቅዱስ ቢፋሞንን ምጽዋት ቢለምነውና ቅዱሱም በእጆቹ ቢነካው ወዲያው ከደዌው ድኖ ጤነኛ ሆነ፡፡
ሁለተኛም በሌላ ጊዜ በቅዱስ ዳዊት መዝሙር ሲያመሰግን ከዚያ አንድ ጋኔን የሚጥለው ሰው ነበረና ‹‹የእግዚአብሔር ቅዱስ ሆይ ተወኝ፣ ከዚህ ቦታ ልጥፋ›› ብሎ ጮኸ፡፡ ቅዱስ ቢፋሞን ወደ ጌታችን ጸልዮ ያንን ጋኔን ያደረበትን ሰው አዳነው፡፡ መምህሩም ይህን አይቶ በዚህ ሕፃን ልጅ ያደረውን ጸጋ አደነቀ አከበረውም፡፡ በመምህሩም ዘንድ 8 ዓመት ኖረ፡፡ ጌታችንም ቅድስት እናቱን ድንግል ማርያምንና ቅዱሳኑን እያስከተለ እየመጣ ይገለጥለት ነበር፡፡
ቅዱስ ቢፋሞን በየሰባት ቀን በመጾም ተጋድሎውን ጨመረ፡፡ ከሰንበት በቀር አይበላም ነበር፡፡ ዕድሜው ከፍ ሲል ወላጆቹ ሚስት ሊያጋቡት አሰቡ፡፡ እርሱ ግን ‹‹በዚህ እንደጤዛ በሚያልፍ ዓለም ከሴት ጋር መኖር ለእኔ ምኔ ነው? ፍላጎቱም ዓለሙም ሁሉም ያልፋል›› አላቸው፡፡ ከዚህም በኋላ በሰባተኛው ወር አባቱ ሲያርፍ ቅዱስ ቢፋሞን ንብረቱን ሁሉ አውጥቶ ለጦም አዳሪዎች ሰጣቸውና በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የተጠመደ ሆነ፡፡ በዚያም ወራት የፋርስ ሰዎች በሮም ሰዎች ላይ ጦርነት አስነሥተው ነበር፡፡ የሮሙ ንጉሥ በጦርነቱ ስለሞተ ሮም ያለንጉሥ ቀረች፡፡ መኳንንቱና የመንግሥት ታላላቅ ሰዎችም ተሰብስበው ከአገሮች ሁሉ ተዋጊዎች የሆኑ አርበኞችን ይሰበስቧቸው ዘንድ በየአገሩ አዘዙ፡፡ ከላይኛው ግብፅ ልበ ደንዳና የሆነ ስሙ አግሪጳዳ የሚባል ሰይጣን በልቡ ያደረበት ፍየል ይጠብቅ የነበረ ኃይለኛ ሰው ተገኘ፡፡ እርሱንም ወደ አንጾኪያ አገር ወስደው የፈረሶች ባልደራስ አድርገው ሾሙት፡፡
በአንዲት ዕለትም ሸንበቆ አንሥቶ ዋሽንት ሠርቶ ሲነፋ በፈረሶቹ ላይ ሰይጣን አደረባቸውና ፈረሶቹም እያሽካኩ ይጨፍሩ ጀመር፡፡ በጦርነት የሞተው ንጉሥ ሴት ልጅም በቤተ መንግሥት አዳራሽ ሆና ሲዘፍንና ዋሽንት ሲነፋ አግሪጳዳን አይታ ወደደችው፡፡ ሰይጣንም በልቧ የዝሙትን ፍላጻ ጨመረባትና ወደ እርሷ አስመጣችውና አገባችው፡፡ ስሙንም ዲዮቅልጥያኖስ ብላ ሰየመችውና አነገሠችው፡፡ ታናሽ እኅቷም በእርሷ ቀንታ መክስምያኖስ የሚባለውን አንዱን መኮንን መልምላ አገባችና ልብሰ መንግሥት አልብሳ አነገሠችው፡፡ መክስምያኖስና

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

03 Feb, 17:28


ዲዮቅልጥያኖስም በአንጾኪያና በሮም ተስተካክለው ነገሡ፡፡ ከዚህም በኋላ ሰይጣን ተገለጠላቸውና እንዲህ አላቸው፡- ‹‹በንጉሡ ሴቶች ልጆች ላይ የዝሙትን ፍቅር በልባቸው ላይ አሳድሬ እንዲወዷችሁና እንዲያገቧችሁ ያደረኩት እኔ ነኝ፤ አሁንም ትእዛዜን ከሰማችሁ በምድር የሚኖረውን ሕዝብ ሁሉ በእጃችሁ ውስጥ አደርግላችኋለሁ፤ እናንተም ስገዱልኝ የብርና የወርቅ ምስልም ሠርታችሁ አማልክት በሏቸው፡፡ ስማቸውንም አጵሎን አርዳሚስ ብላችሁ ጥሯቸው፡፡ ሰዎችም ሁሉ ዕጣን እንዲያሳርጉላቸውና እንዲሰግዱላቸው እዘዙ፤ ያልሰገዱላቸውንም ራስ ራሶቻቸውን በሰይፍ ቁረጡ፤ ይህን ካደረጋችሁ መንግሥታችሁን አሰፋላችኋለሁ ካለዚያ ግን መንግሥታችሁ ታልፋለች›› አላቸው፡፡
እነዚህም ሁለት ሰነፎች መክስምያኖስና ዲዮቅልጥያኖስም ለሰይጣን ሰገዱለትና ‹‹ያዘዝከንን ሁሉ እናደርጋለን ብቻ መንግሥታችንን አጽናልን›› አሉት፡፡ በዚህም ጊዜ ኄሬኔዎስንና አርያኖስን በግብጽ አገር ላይ መኳንንት አድርገው ሾሟቸው፡፡ ለጣዖት የማይሰግዱትን ሁሉ እንዲገድሉ አዘዟቸው፡፡ የከበረ ቅዱስ ቢፋሞንም ይህንን ትእዛዝ በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ፡፡ ወዳጁን ቴዎድሮስን ጠራውና በክብር ባለቤት በጌታችን ስም ደማቸው አፍስሰው ሰማዕት ይሆኑ ዘንድ በምክር ተስማሙ፡፡
የቅዱስ ቢፋሞን ዜናው በሁሉ ዘንድ የታወቀ ነውና ወሬው ከሃዲው ንጉሥ መክስምያኖስ ዘንድ ተሰማ፡፡ መኳንንቶቹም ‹‹በምስር አውራጃ በአውሲም ከተማ የሚኖር ስሙ ቢፋሞን የሚባል ሰው አለ፣ እርሱም የነገሥታትን ትእዛዝ የሚተላለፍ አማልክትን የሚረግምና የሚያቃልል ነው›› ብለው ለንጉሥ መክስምያኖስ ነገሩት፡፡ በዚህም ጊዜ ንጉሡ ቅዱስ ቢፋሞን ለአማልክት ካልሰገደ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጠው ትእዛዝ ጽፎ ለጨካኙ መኮንን ለአርያኖስ ላከለት፡፡ ደብዳቤውም ከመኮንኑ ዘንድ ሳይደርስ የታዘዘ የእግዚአብሔር መልአክ ለቅዱስ ቢፋሞን ተገለጠለትና በሰማዕትነት እንደሚሞት እናቱና አገልጋዩ ዲዮጋንዮስም አብረውት እንደሚሞቱ ከነገረው በኋላ ሰማዕትነቱን በትዕግስት እንዲፈጽም ነገረው፡፡ የተዘጋጀላቸውንም የክብር አክሊላት አሳየው፡፡ ቅዱስ ቢፋሞን ተነሥቶ ለእናቱ መልአኩ የነገረውን ነገራት፡፡ መልአኩ ለእርሷም ተገልጦ ይህንኑ እንደነገራት ለልጇ ነገረችውና ለሰማዕትነት በመመረጣቸው በአንድነት እጅግ ደስ አላቸው፡፡ ሲጸልዩ አደሩና በነጋታው ቅዱስ ቢፋሞን ወዳጁን ቴዎድሮስን አስጠራውና ሁሉን ነገረው፡፡ ቀጥሎም ‹‹የመከራው ጊዜ ካለፈ በኋላ አንተ በዚህች አገር ላይ ኤጲስቆጶስነት ትሾማለህ ያንጊዜም በስሜ ቤተ ክርስቲያን ትሠራለህ›› ብሎ ትንቢት ነገረው፡፡ ወዲያም ሰላምታ ተሰጣጡና ተሳስመው ተለያዩ፡፡
ከጥቂት ቀኖች በኋላ በአውሲም ከተማ መኮንኑ አርያኖስ ደረሰ፡፡ የሀገሩን ታላላቅ ሰዎችንም አቅርቦ ስለከበረ ቅዱስ ቢፋሞን ጠየቃቸው፡፡ የአገር ሽማግሎችም ስለእርሱ አዘኑ-እርሱ ተአምራትን የሚያደርግ አማልክትንም የሚረግም መሆኑን ያውቃሉና፡፡ ወዲያውም ቅዱስ ቢፋሞን ቤተሰቦቹን ተሰናብቶ ያማሩ ልብሶቹን ለብሶ ፈረስ ጋልቦ የሀገሩ ሽማግሎችና መኮንኑ ካሉበት ቦታ ደረሰ፡፡ መኮንኑ አርያኖስም ባየው ጊዜ ደስ ብሎት በክብር ሰላምታ ሰጠው፡፡ ቅዱስ ቢፋሞንም ‹‹የሰላም ትርጓሜው ደስታ ነው፣ እኔ በጌታዬና በፈጣሪዬ በኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ደስታ አለኝ አንተና ባልንጀሮችህ ግን በሰማያት ደስታ የላችሁም›› አለው፡፡ አርያኖስም ‹‹እኔ ክፉ ነገርን እንድትነግረኝ አልመጣሁም፣ ለአማልክት እንድትሠዋ በንጉሡ ደብዳቤ ታዝዤ መጣሁ እንጂ›› አለው፡፡ ቅዱስ ቢፋሞንም ‹‹አማልክቶቻችሁ አፍ እያላቸው የማይናገሩ፣ እጅ እያላቸው የማይዳስሱ፣ ጆሮ እያላቸው የማይሰሙ፣ ዐይን እያላቸው የማያዩ፣ አፍ እያላቸው የማይተነፍሱ ናቸውና የሠሩአቸውና የሚያመልኳቸውም እንደ እነርሱ ይሁኑ፡፡ እኔ ግን ሰማይንና ምድርን በውስጣቸውም ያለውን ሁሉ ለፈጠረ ለጌታዬ ለፈጣሪዬ ለኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ አሰግዳለሁ›› አለው፡፡ መኮንኑ አርያኖስም ይህንን ነገር ከቅዱስ ቢፋሞን አፍ በሰማ ጊዜ እጅግ ተቆጣ፡፡ ጽኑ በሆኑ ልዩ ልዩ ማሠቃያዎችም አሠቃየው፡፡ ዳግመኛም በፈረሶች ላይ አሥሮ መሬት ለመሬት እየጎተተ ከተማውን ሁሉ አዞረው፡፡ የቅዱስ ቢፋሞን እናቱና አገልጋዩ በመጡ ጊዜ በከበረች የወንጌል ቃል አጽናናቸው፡፡ እነርሱና ሌሎችም የከተማው ሰዎች ‹‹እኛም በቅዱስ ቢፋሞን አምላክ የምናምን ነን፣ ሰማዕትም እንሆን ዘንድ እንወዳለን›› ብለው ጮኹና የመኮንኑን ወንበር ገለበጡት፡፡ መኮንኑም ጥልቅ ጉድጓድ አስቆሮ እሳት አስነድዶ ከዚ ውስጥ ጨመራቸውና ሰማዕትነታቸውን በድል ፈጽመው የድል አክልሊን ተቀዳጁ፡፡ ቁጥራቸውም አምስት መቶ ሆነ፡፡ እነዚህም 500 ቅዱሳን ምስክርነታቸውን እስኪፈጽሙ ድረስ ቅዱስ ቢፋሞን ያጽናናቸውና ያበረታቸው ነበር፡፡ የከበረች እናቱም በላይዋ ላይ እንዲጸልይ ለመነችው፣ እርሱም በመስቀል ምልክት በላይዋ አማተበና በሰላም ሂጂ አላት፡፡ እርሷም ወዲያው ማንም ሳይነካት ዘላ ከእሳቱ ገባች፡፡ የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለች፡፡
የከበረ ቅዱስ ቢፋሞንን ግን አርያኖስ ወደ ንጉሡ መክስምያኖስ ሰደደው፡፡ ንጉሡም ‹‹የነገሥታቱን ትእዛዝ የምትተላለፍ ለአማልክት የማትሠግድ ሥራየኛው ቢፋሞን አንተ ነህን?›› አለው፡፡ ቅዱሱም ‹‹እኔ ሥራይን አላውቅም፣ ለረከሱ አማልክትህ ግን አልሰግድም፣ አንተም እነርሱም በአንድነት ወደ ገሃነመ እሳት ትወርዳላችሁ›› አለው፡፡ ንጉሡም ይዞ በእጅጉ አሠቃው፡፡ ማሠቃየትም በሰለቸው ጊዜ ወደ መኮንኑ ኄሬኔዎስ ላከው፡፡ እርሱም ካሠቃው በኋላ መልሶ ለአርያኖስ ላከው፡፡ በእነዚህም ጊዜ ቅዱስ ቢፋሞን ምንም አልበላም ነበር፡፡ አርያኖስም በብረት ችንካሮች ቸነከረውና ‹‹ለአማልክት ካልሰገድክ አጠፋሃለሁ› አለው፡፡ ቅዱሱም ንጉሡንና አማልክቱን ረገማቸው፡፡ መኮንኑም በዚህ ጊዜ አሥሮ እየጎተተ በከተማው ሁሉ አዞረው፡፡ ከእንዴና ከተማ ውጭ አውጥቶ በእሳት አቃጠለው፤ ነገር ግን ጌታችን ቅዱስ ቢፋሞንን ከእሳቱ ውስጥ ያለምንም ጉዳት በደህና አወጣው፡፡ ቅዱሱም በእሳት ቆሞ ሳለ ከእግሮቹ ብዙ ደም ፈሰሰ፡፡ በዚያም ቦታ አንድ ዐይነ ሥውርና ለምጻም ሰው ነበረ፡፡ እርሱም ከቅዱስ ቢፋሞን ደም ወስዶ ዐይኑን ቢቀባው ወዲያው ማየት ቻለ፣ ከለምጹም ነጻ፡፡ ከዚህም በኋላ ‹‹እኔም በቅዱስ ቢፋሞን አምላክ በኢየሱስ ክርስቶስ አምኛለሁ›› ብሎ ጮኸ፡፡ ወዲያውም መኮንኑ ተናዶ ራሱን በሰይፍ አስቆረጠውና የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ፡፡
ከዚህም በኋላ መኮንኑ አርያኖስ የቅዱስ ቢፋሞንንም አንገት በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ፡፡ ቅዱስ ቢፋሞንም አገልጋዩን ዲዮጋኖስን ወደ እርሱ አቅርቦ ሥጋውን በስውር እንዲጠብቅ ደሙንም በበፍታ ልብስ እንዲቀበል ይኸውም ከመከራው ዘመን በኋላ ለበረከት እንዲሆን ነገረው፡፡ ገድሉንም ለምእመናን እንዲነገር ከነገረው በኋላ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ብሎ በመስቀል ምልክት አማተበና ወደ ጭፍሮቹ ሄዶ ‹‹የታዘዛችሁትን ፈጽሙ›› በማለት እንዲሰይፉት ራሱን አሳልፎ ሰጣቸው፡፡ እነርሱም ወደ ላይኛው ግብጽ አጥማ አውራጃ ወስደው ራሱን በሰይፍ ቆረጡትና የሰማዕትነት ፍጻሜው ሆነ፡፡ የተዘጋጀለትንና አስቀድሞ ያየውን የክብር አክሊል በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ፡፡ ከአንገቱም ብዙ ደም በፈሰሰ ጊዜ አገልጋዩ ዲዮጋኖስ በፍታውን ዘርግቶ ደሙን ተቀበለ፡፡ በቦታው መዓዛው እጅግ ጣፋጭ የሆነ ሽታ በሸተተ ጊዜ ጭፍሮቹ ደንግጠውና ፈርተው ከቦታው ሸሹ፡፡ ምእመናንም መጥተው ሥጋውን ወስደው በክብር ገንዘው ቀበሩት፡፡ ከመቃብሩም ብዙ ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራት ተገለጡ፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

02 Feb, 15:06


ሆይ! ስለ እግዚአብሔር ብለህ በላዬ ካለው በቀር በሌላ ልብስ እንዳትገንዘኝ›› ብላ ለመነችው፡፡ ወዲያውም ጸሎቷን ካደረገች በኋላ በምድር ላይ ተቀምጣ ዐረፈች፡፡
አባ ዳንኤልና ረድእ የነበረው መነኮስ በላይዋ አልቅሰው ሊገንዙዋት ሲሉ ረድኡ ወደ እርሷ ቀርቦ ቢያያት እንደ ቅጠል ደርቀው የቅድስት አትናስያን ጡቶች ተመለከተ-በተጋድሎ ብዛት እንዲህ ሆነዋልና፡፡ አባ ዳንኤልም አይቶ በማድነቅ ዝም አለ፡፡ እርሷን በክብር ከቀበሯትና ወደ በዓታቸው ከተመለሱ በኋላ ያ ረድእ በአባ ዳንኤል እግር ሥር ወደ ወድቆ ‹‹ስለ እግዚአብሔር ብለህ የዚህችን ቅድስት ገድሏን ንገረኝ›› አለው፡፡ አባ ዳንኤልም ቅድስት አትናስያ ከቁስጥንጥንያ ታላላቆች የመንግሥት ወገን እንደሆነችና ስለ ክርስቶስ ፍቅር ብላ የዚህን ዓለም ክብር ንቃ እንደተወች በዚያ ገዳምም በዋሻ ውስጥ ለብቻዋ ወንድ መስላ በመኖር ለ28 ዓመታት በታላቅ ተጋድሎ እንደኖረች ነገረው፡፡
ቅድስት አንስጣስያ ረድኤት በረከቷ ይደርብን በጸሎቷ ይማረን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

02 Feb, 15:06


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ጥር 26-በጻድቁ ንጉሥ በቴዎዶስዮስ ዘመነ መንግሥት 49 አረጋውያን መነኮሳት በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡ ከእነርሱም ጋር የንጉሡ መልአክተኛ ከልጁ ጋር አብሮ ሰማዕት ሆነ፡፡
+ ቅድስት አንስጣስያ በዓለ ዕረፍቷ ነው፡፡
አርባ ዘጠኙ አረጋውያን ሰማዕታት፡- የጻድቁ ንጉሥ አርቃዴዎስ ልጅ የሆነው ጻድቁ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ ልጅ አልነበረውምና ስለዚህም ጉዳይ በአስቄጥስ ገዳም ወደሚኖሩ አረጋውያን መነኮሳት እንዲጸልዩለት መልእክት ላከ፡፡ ከአረጋውያን መነኮሳትም ውስጥ አንዱ ቢስዱራ የሚባለው ጻድቅ ‹‹ከአንተ በኋላ ከሚነሡ መናፍቃን ጋር አንድ እንዳይሆን እግዚአብሔር ልጅ ይሰጥህ ዘንድ አልወደደም›› የሚል መልስ ለንጉሡ ጻፈለት፡፡ ንጉሥ ቴዎዶስዮስም ፈቃደ እግዚአብሔርን በማወቁ ደስ ብሎት ልቡን አሳረፈ፡፡
ዳግመኛም ክፉ ሰዎች ሌላ ሚስት አግብቶ ከእርሱ በኋላ በዙፋኑ የሚቀመጥ ወንድ ልጅ እንዲወልድ መከሩት ነገር ግን ንጉሥ ቴዎዶስዮስ ‹‹በአስቄጥስ ገዳም ከሚኖሩ ከአረጋውያን ምክር ሌላ ምንም ምን ማድረግ አልችልም›› አላቸው፡፡ ስለዚህም አረጋውያንን ይጠይቅ ዘንድ ንጉሡ መልእክተኛውን ላከ፡፡ ይኸውም መልእክተኛው ወንድ ልጅ ነበረውና ከመነኮሳቱ በረከትን ይቀበል ዘንድ አብሮት ወደ አስቄጥስ ገዳም ሄደ፡፡ መልእክተኛውም ልጁን ይዞ አስቄጥስ ገዳም ቢደርስ አባ ቢስዱራ በሞት ዐርፎ አርፎ ነበር፡፡ ነገር ግን አረጋውያን መነኮሳቱ የንገሡን መልእክት ካነበቡ በኋላ መልእክቷን ይዘው የአባ ቢስዱራ ሥጋ ወዳለበት በመሄድ ‹‹አባት ሆይ! እነሆ የንጉሡ መልእክት ወደ እኛ ደረሰች፣ ምን እንደምንመልስለት አናውቅም›› አሉ፡፡ በዚያም ጊዜ አረጋዊ አባ ቢስዱራ ተነሥቶ ‹‹‹እግዚአብሔር ልጅን ሊሰጥህ አልፈቀደም አላልኩህምን አለ› በሉት›› አላቸው፡፡ ዳግመኛም ‹‹ንጉሥ ከአላውያን ጋር አንድ ሆኖ እንዳይረክስ ሌሎች ሴቶችንም ቢያገባ ልጅን አይሰጠውም›› ብሏቸው ተመልሶ ተኛ፡፡
አረጋውያን መነኮሳትም ይህንን የአባ ቢስዱራን መልእክት በክርታስ ጽፈው ለንጉሡ መልአክተኛ ሰጡት፡፡ እርሱ መልእክቱን ይዞ ሊመለስ ሲል አረማውያን የሆኑ የበርበር ሰዎች ወደ ገዳሙ መጡ፡፡ አባ ዮሐንስ የተባለውም ታላቅ አባት ‹‹እነሆ የበርበር ሰዎች ይገድሉን ዘንድ መጥተዋልና ሰማዕት መሆን የሚሻ ከእኔ ጋር ይምጣ፣ የሚፈራ ግን ወደ ግንብ ሄዶ ይሰወር›› አለ፡፡ የሸሹም አሉ፡፡ ነገር ግን ከአባ ዮሐንስ ጋር ለሞት ተሰልፈው የጠበቁ 49 አረጋውያን መነኮሳት ቀሩ፡፡ የመልአክተኛውም ልጅ ከጎዳናው ዘወር ባለ ጊዜ በመነኮሳቱ ራስ ላይ ረቂቃን መላእክት የክብር አክሊልን ሲያኖሩ በግልጽ ተመለከተ፡፡ የዚያህም ልጅ ስሙ ድያስ ነው፡፡ ልጁም ለአባቱ ‹‹እነሆ በአረጋውያን ራሶች ላይ አክሊላትን ሲያኖሩ ቅዱሳን መላእክትን አያለሁና እኔም እንደ እነርሱ አክሊልን ለመቀበል እሄዳለሁ›› አለው፡፡ አባቱም ‹‹ልጄ ሆይ! እኔም ከአንተ ጋር እሄዳለሁ›› አለው፡፡ በዚያችም ጊዜ 49ኙ አረጋውያን መነኮሳት ለበርበሮች ተገለጡላቸውና አረማውያን ገደሏቸው፡፡ የምስክርነት አክሊልንም ተቀዳጁ፡፡
አረማውያንም መነኮሳቱን ከገደሉና ከሄዱ በኋላ ተሰውረው የነበሩት መነኮሳት ወጥተው የሰማዕታቱን ሥጋቸውን ሰበሰቡ፡፡ ገንዘውም በበዓት ውስጥ አኖሯቸው፡፡ ፍዩም ከሚባል አገር የሆኑ ሰዎች ከአረጋውያኑ መነኮሳት ጋር ሰማዕት የሆነው የመልእክተኛውን ልጅ የቅዱስ ድያስን ሥጋ ሰርቀው ወደ አገራቸው ወደሰዱት፣ ነገር ግን የታዘዘ መልአክ ነጥቆ ወስዶ መልሶ ከአባቱ ሥጋ ጋር አኖረው፡፡ መነኮሳቱም የድያስን ሥጋ ከአባቱ ለመለየት ብዙ ጊዜ ሞክረው ነበር ነገር ግን አልተቻላቸውም፡፡ ማታ በለዩአቸው ጊዜ ጠዋት አንድ ላይ ሆነው ያገኟቸዋል፡፡ ከዕለታትም በአንደኛው ቀን ከሥጋቸው ‹‹እኛ በሕይወተ ሥጋ ሳለን እርስ በእርሳችን አልተለያየንም፣ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድም አልተለያየንምና እናንተ ለምን ትለያዩናላችሁ?›› የሚል ድምጽ ተሰማ፡፡ ከዚያችም ቀን ወዲህ ሊለያያቸው ያሰበ የለም፡፡
አረማውያንም የአስቄጥስን ገዳም ባጠፉት ጊዜ የቅዱሳኑን ሰማዕታት ሥጋቸውን አፍልሰው ወስደው በከበረ በአባ መቃርስ ቤተ ክርስቲያን ጎን አኖሩዋቸው፡፡ የመቃብር ቦታም ሠሩላቸው፡፡ በላዩም በሊቀ ጳጳሳት ቴዎዳስዮስ ዘመን በስማቸው ቤተ ክርስቲያን ሠሩላቸው፡፡ ሊቀ ጳጳሳት አባ ቢንያሚንም ወደ አስቄጥስ ገዳም በመጣ ጊዜ የካቲት 5 ቀን በዓላቸውን አከበረላቸው፡፡ ይኸውም ሥጋቸው የተገለጠበት ዕለት ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያናቸውም እስከዛሬ አለች፡፡ በቅብጥ ቋንቋ ብህም ብሲት በመባል ትታወቃለች-ይህም አርባ ዘጠኝ ማለት ነው፡፡
የሰማዕታቱ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!
+ + +
ቅድስት አንስጣስያ፡- ይኽችም ቅድስት ከቁስጥንጥንያ ታላላቆች ወገን የአንዱ ልጅ ናት፡፡ በመልኳም እጅግ ያማረች ናትና ንጉሡ ብስጥያኖስ ሊያገባትና ንግሥት ሊያደርጋት ፈለገ፡፡ እርሷ ግን ይህንን አልወደችም፡፡ የንጉሡም ሚስት በሕይወት ነበረች፡፡ አትናስያም ንጉሡ ሊያገባት እንሚፈልጋት ለንግሥት ሚስቱ ነገረቻት፡፡ ንግሥቲቱና አትናስያም ከተማከሩ በኋላ አትናስያን በድብቅ በመርከብ አሳፍራ ወደ ግብጽ አገር ላከቻት፡፡ ከእስክንርያም ውጭ ገዳም አሠራችላት፡፡
ቅድስት አትናስያም ንግሥቲቱ ባሠራችላት ገዳም በተጋድሎ ኖረች፣ ገዳሙም በስሟ ተጠራ፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሡ ቅድስት አትናስያ በግብጽ አገር እንዳለች በሰማ ጊዜ ፈልገው እንዲያመጡለት መልእክተኞችን ላከ፡፡ እርሷም ይህንን ነገር ተረድታ የወንድ ልብስ ለብሳ መስፍንን መሰለች፡፡ ወደ አስቄጥስ ገዳም በመግባት ለአባ ዳንኤል ምሥጢሯን ሁሉ ነገረችው፡፡ እርሱም ወስዶ በዋሻ ውስጥ ለብቻዋ አኖራት፡፡ እርሷም ሴት እንደሆነች ማንም አላወቀም፡፡ 40 ዓመት በአስቄጥስ ገዳም ሲኖር ከቅጠል በቀር ተመግቦ የማያውቀው ይኽ የገዳመ አስቄጥሱ አባ ዳንኤል ምሥጢራቸው የተሠወረውን የብዙ ቅዱሳንን ተጋድሎ እርሱ ግን ያውቅ ነበር፡፡ አንድ ቀን አባ ዳንኤል በሌሊት በበረሃ ውስጥ በጨረቃ ብርሃን ሲጓዝ በተራራ ላይ ቀምጣ ጠጉሯ መላ ሰውነቷን የሸፈናት በዚያም በረሃ ስትኖር በተሰነጠቀ ዓለት ውስጥ 38 ዓመት ብቻዋን ማንም ሳያያት የኖረች ጻድቅ እናት አግኝቶ ምሥጢሯን ሁሉ ነግራዋለች፡፡ እርሷም ቅድስት አመተ ክርስቶስ ናት፡፡ አባ ዳንኤልም 38 ዓመት ሙሉ በዚህ በረሃ ምንም ሰው ሳታይ የኖረችበትን ተገድሎዋን በዝርዝር ነግራቸዋለች፡፡ እርሳቸውም ወደ ገዳማቸው ተመልሰው ለአበ ምኔቱና ለመነኮሳቱ ታሪኳን በመንገር ልብስ ይዘውላት ቢመጡ ዐርፋ አግኝተዋታል፡፡
አባ ዳንኤል አሁንም የዚህችን የቅድስት የአትናስያን ምሥጢሯን ለማንም ሳይነግር ደብቆላት ኖረ፡፡ በየሳምንቱ የእንስራ ውኃ ቀድቶ ካለችበት ዋሻ ደጃፉ ላይ እንዲያኖረው አንዱን ደግ አረጋዊ መደበላት፡፡ ያም ደገኛ ሽማግሌ ታሪኳን አያውቅም፡፡ ቅድስት አትናስያም በዚያ አባ ዳንኤል በሰጣት ዋሻ ውስጥ 28 ዓመታት በታላቅ ተጋድሎ ኖረች፡፡ ውሃ ሲቀዳላት የነበረ ያ ሽማግሌም በሞት ባረፈ ጊዜ ውኃ እንዲቀዳላት አባ ዳንኤል ሌላ ሰው መደበላት፡፡ ቅድስት አትናስያም ገል (የሸክላ ስባሪ) ላይ ሀሳቧን እየጻፈች ደጃፏ ላይ ታኖረው ነበር፡፡ በአንዲት ዕለት ረዳቷ የጻፈችውን ወስዶ ለአባ ዳንኤል በሰጠው ጊዜ አባ ዳንኤል አለቀሰና ‹‹ልጄ ሆይ ተነሥ የዚያን ሰው ሥጋ ሄደን እንቅበር እርሱ ከዚህ ዓለም ይለያልና›› አለው፡፡ ሁለቱም ተያይዘው ወደ በዓቷ ሄደው ከእርሷ ተባረኩ፡፡ እርሷም አባ ዳንኤልን ‹‹አባቴ

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

01 Feb, 17:39


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ጥር 25-ከበሬ ጋር ተጠምደው በማረስ ሰማዕትነት የተቀበሉት አቡነ ሕፃን ሞዐ ልደታቸው ነው፡፡
+ የሮሙ ንጉሥ ልጅ ቅዱስ ስብስትያኖስ ምስክርነቱን ፈጽሞ በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡
+ ራሱን የሸጠው ቅዱስ ጴጥሮስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ይኸውም በቀድሞ ሕይወቱ ‹‹ርኅራኄ የሌለው፣ ንፉጉ ሰው›› እየተባለ እስከመጠራት ድረስ ለድኆች የማይራራ ባለጸጋ የነበረ ሲሆን በኋላም በተአምራት የምጽዋትን ጥቅም ዐውቆ ንብረቱን ሁሉ የመጸወተ ነው፡፡ ንብረቱንም ሁሉ መጽውቶ ለድኆች የሚሰጠው ቢያጣ ራሱን ሸጦ የጉልበት ሥራ በመሥራት የሚመጸውት ሆነ፡፡
+ ዳግመኛም ይህች ዕለት ሰማዕቱ ቅዱስ መርቆሬዎስ በሥዕሉ ላይ አድሮ ቅዱሳን የሆኑ ባስልዮስንና ጎርጎርዮስን በመርዳት ከሃዲውን ንጉሥ ዑልያኖስን የገደለባት ዕለት ናት፡፡
የሮሙ ንጉሥ ልጅ ሰማዕቱ ቅዱስ ስብስትያኖስ፡- አባቱ የሮሙ ንጉሥ ሃይማኖቱ የቀና እግዚአብሔርንም የሚወድ ስለነበር ልጁን የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት እያስተማረ ፈሪሃ እግዚአብሔርን እያስተማረ አሳደገው፡፡ አባቱም ከሞተ በኋላ ከሃዲያኑ ዲዮቅልጥያኖስና መክስምያኖስ ነገሡ፡፡ ቅዱስ ስብስትያኖስንም አገረ ገዥ አድርገው ሾሙትና እንደ አባቱ እጅግ አድርገው አከበሩት፡፡
ቅዱስ ስብስትያኖስ በጥበብና በማስተዋል የሚጓዝ ነው፡፡ በተጋድሎ ሕይወቱ የተመሰገነ ሆነ፡፡ እግዚአብሔርም በእጆቹ የተለያዩ ተአምራትን ገለጠ፡፡ ድውያንን ይሰውሳል፤ በጸሎቱም የዕውራንን ዐይኖች ያበራል፡፡ በእንዲህም ዓይነት በተጋደሎ ሲኖር ዲዮቅልጥያኖስ እግዚአብሔርን ክዶ በዓለም ላይ ያሉ እያሳረደ ክርስቲያኖችን አብያተ ክርስቲያናትን ማቃጠል ጀመረ፡፡ በዘመኑም ሰማዕት የሆኑት የክርስቲያኖች ቁጥር ከ470,000 (አራት መቶ ሰባ ሺህ) በላይ ናቸው፡፡ ይኸውም ከሃዲ አገረ ገዥ አድርጎ ሾሞትና በእጅጉ አክብሮት የነበረውን ቅዱስ ስብስትያኖስን አሁን ለጣዖት እንዲሰግድ ግድ አለው፡፡
ቅዱስ ስብስትያኖስ ግን የከሃዲውን ንጉሥ ትእዛዝ ቸል በማለት በፊቱ ቆሞ የጌታችንን የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ፤ ጣዖታቶቹንም ረገመበት፡፡ ንጉሡም በዚህ ጊዜ በታላቅ ቁጣ ሆኖ ቅዱስ ስብስትያኖስን ብዙ አሠቃየው፡፡ ከግንድ ጋር አሥሮ በብዙ ፍላጻዎች ሰውነቱን አስነደፈው፡፡ በዚህም ጊዜ እንደሞተ አስበው ትተውት ሄዱ፡፡ ምእመናንም ሥጋውን ለመውሰድ በሌሊት ቢመጡ በሕይወት አገኙትና ወስደው በደሴት መካከል አስቀመጡት፡፡
ዲዮቅልጥያኖስም የቅዱስ ስብስትያኖስን በሕይወት መኖር ሲሰማ ድጋሚ አስመጣውና በብረት ዘንጎች ሲያስገድበው ዋለ፡፡ ለብዙ ቀናትም እንዲሁ በብረት ዘንግ ሲያስደበድበው ቆየ፡፡ ቅዱስ ስብስትያኖስም በአንደኛው ቀን ነፍሱ ከሥጋው ተለየችና የሰማዕትነት ፍጻሜው ሆነ፡፡ ጌታችንም መታሰቢያውን ለሚያደርግና ስሙን ለሚጠራ የቸነፈር ሕመም እንዳይቀርበው ቃልኪዳን ሰጥቶታል፡፡ ቅዱስ ስብስትያኖስም ካረፈ በኋላ ውሉዱስና ለምትባል ለአንዲት ቅድስት ሴት ተገለጠላትና ቅዱስ ሥጋው ያለበትን ነገራት፡፡ እርሷም ወደ ከበሩ ቅዱሳን ጴጥሮስና ጳውሎስ መቃብር ወስዳ ቀበረችው፡፡ የቅዱስ ስብስትያኖስያኖስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!
+ + +
ራሱን የሸጠው ቅዱስ ጴጥሮስ፡- ይኸውም ለድኆች ለመመጽወት ሲል ራሱን በገንዘብ የሸጠ ታላቅ ጻድቅ ነው፡፡ አስቀድሞ ቀራጭ ነበር፡፡ እርሱም ልቡ የደነደነ ርኅራኄ የሌለው ንፉግ ሰው ነበር፡፡ የሚያውቁትም ሰዎች ሁሉ ‹‹ጨካኙ፣ ንፉጉ›› እያሉ ይጠሩት ነበር፡፡ የኃጢአተኛውን ሞት የማይሻ ጌታችንም ሊያስተምረው ፈልጎ አንድ የሚለምን ድኃ ሰው ወደ እርሱ ላከለት፡፡ ድኃውም ሰው ጴጥሮስን እየለመነው እያለ አገልጋዩ ከውስጥ እንጀራ ይዞ ሲወጣ ደረሰ፡፡ ጴጥሮስም አድርጎት የማያውቀውን ቶሎ ብሎ ቁራሽ እንጀራ ለዚያ ድኃ ጣለለትና ቶሎ ሂድልኝ አለው፡፡ እንጀራውንም የሰጠው ለድኃው ራርቶለት ሳይሆን ቶሎ ከፊቱ ዘወር እንዲልለትና ዳግመኛ መጥቶ እንዳይጠይቀው ነው፡፡ ምስኪኑም እንጀራውን ተቀብሎ ሄደ፡፡
ጴጥሮስም በዚያች ሌሊት ተኝቶ ሳለ በእጆቻቸው ሚዛን ይዘው መላእክተ ጽልመት የሰውን ኃጢአት እየመዘኑ በግራ በኩል ሲያስቀምጡ አየ፡፡ የጴጥሮስንም ኃጢአት በዚያው ሲያኖሩ አየ፡፡ መላእክተ ብርሃናትም በሚዛናቸው በቀኝ ባለው ሚዛን የሚያስቀምጡለት መልካም ነገር አጡበት፡፡ ከእነርሱም አንዱ መልአክ ጴጥሮስ ለድኃው የጣላትን እንጀራ አምጥቶ ‹‹ከዚህች እንጀራ በቀር ሌላ በጎ ሥራ አላገኘሁለትም›› አላቸው፡፡ ጴጥሮስም ይህንን ሕልም አይቶ እየፈራና እየተንቀጠቀጠ ከተኛበት ተነሣ፡፡ ከዚህች ቀን ወዲህ ስለ ክፉ ሥራው ማዘንና መጸጸት ጀመረ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ከዚህ በኋላ እጅግ የሚራራ ሆነ፡፡ ያለውን ንብረቱን ሁሉ አውጥቶ ሸጦ ለድኆችና ለጦም አዳሪዎች መጸወተ፡፡ በመጨረሻም ለድኆች የሚሰጠው አንዳች ነገር ቢያጣ ራሱንም ሸጦ በጉልበቱ እየሠራ የሚያገኘውን ይመጸውታል፡፡ ይህ ሥራውም በብዙዎች ዘንድ ሲታወቅበት ውዳሴ ከንቱን ሸሽቶ ከአባ መቃርስ ገዳም አስቄጥስ ገባ፡፡ በዚያም መነኮሰና በታላቅ ተጋድሎ ኖረ፡፡ እግዚአብሔርን ሲያገለግል ከኖረ በኋላ ፍጹም የሆነ ተጋድሎውን ፈጽሞ ዕለተ ዕረፍቱን ዐወቀ፡፡ ቀኑም ሲደርስ ቅዱሳንን ጠርቶ ተሰናበታቸውና በዚህች ዕለት ጥር 25 ቀን በሰላም ዐረፈ፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!
+ + +
ዳግመኛም በዚህች ዕለት ከበሬ ጋር ተጠምደው በማረስ ሰማዕትነት የተቀበሉት አቡነ ሕፃን ሞዐ ልደታቸው ነው፡፡ (የዕረፍታቸውን ዕለት ሐምሌ ሃያ አምስትን ይመለከቷል፡፡)
አቡነ ሕፃን ሞዐ፡- በአባታቸው አርከሌድስ እናታቸው ትቤ ጽዮን ይባላሉ፡፡ የተወለዱት ጥር 25 ነው፡፡ አቡነ ሕፃን ሞዐ እና ከእነ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ጋር የሥጋ ዝምድና አላቸው፡፡ ይኸውም አባታቸው አርከሌድስና ጸጋ ዘአብ ወንድማማቾቸ ናቸው፡፡ አርከሌድስና ጸጋ ዘአብ ሌሎች ሌሎች 4 ወንድሞች አሏቸው፡፡
እነርሱም እንድርያስ፣ ዘርዐ አብርሃም፣ ቀሲስ ዮናስ እና ቀሲስ ዮሐንስ ናቸው፡፡ አርከሌድስ ሕፃን ሞዐን ይወልዳል፣ ጸጋ ዘአብ ተክለ ሃይማኖትን ይወልዳል፣ እንድርያስ ሳሙኤል ዘወገግን፣ ዘርዐ አብርሃም ታላቁ አኖሬዎዮስን፣ ቀሲስ ዮናስ ገላውዲዮስንና የፈጠጋሩን ማትያስን፣ እና ቀሲስ ዮሐንስ ዜናማርቆስን ይወልዳሉ፡፡ እነዚህ የከበሩ ቅዱሳን አባቶቻችን በእናታቸውም ወገን ቢሆን እንዲሁ በዝምድና የተቆራኙ ናቸው፡፡ አቡነ ሕፃን ሞዐ በሌላኛው ስማቸው ሕፃን ዘደብረ በግዕ ተብለውም ይጠራሉ፡፡ ይኸውም የደብረ በግዕን ገዳም የመሠረቱት እርሳቸው ስለሆኑ ነው፡፡ ከ47ቱ የሀገራችን ቀደምት ቅዱሳን ውስጥ አንዱ ናቸው፡፡ በመንዝና በተጉለት የሚገኙ ታላላቅ ገዳማትን አብዛኞቹን የመሠረቷቸው አቡነ ሕፃን ሞዐ ናቸው፡፡ ጻድቁ በክፉዎች ወሬና ሴራ ምክንያት ከበሬ ጋር ተጠምደው ሰማዕትነት የተቀበሉ አባት ናቸው፡፡ ከበሬ ጋር ሲታረሱ ውለው በእጅጉ ከደከማቸው በኋላ በኃይል የተነፈሱባት ምድሪቱ ዛሬም ድረስ ልክ እንደሰው የሚሞቅ ትንፋሽ ታወጣለች፡፡ ያም በጻድቁ እስትንፋስ አምሳል ከመሬት ውስጥ የሚወጣው እስትንፋስ ለአስም በሽታ መድኃኒት ሆኖ ብዙዎችን እየፈወ ነው፡፡ ገዳማቸው ከደብረ ብርሃን ከተማ በእግር የ2 ሰዓት መንገድ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ ይኸውም ከወንይዬ ተክለ ሃይማኖት ገዳም አጠገብ ነው፡፡ ጻድቁ ጥር 25 ቀን ልደታቸው፣ ጥቅምት 25 ቃል ኪዳን የተቀበሉበት ዕለት ሲሆን ሐምሌ 25 ደግሞ ዕረፍታቸው ነው፡፡ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

01 Feb, 17:39


+ + +
ሰማዕቱ ቅዱስ መርቆሬዎስም በሥዕሉ ላይ አድሮ ቅዱሳን የሆኑ ባስልዮስንና ጎርጎርዮስን በመርዳት ከሃዲውን ንጉሥ ዑልያኖስን የገደለው በዚሁ ዕለት ነው፡፡ (የዕረፍቱን ዕለት ኅዳር ሃያ አምስትን ይመለከቷል፡፡)
‹መርቆሬዎስ›› ማለት የአብ ወዳጅ ማለት ነው፡፡ ዳግመኛም የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ማለት ነው፡፡ ወላጆቹ አስሊጥ ከምትባል ሀገር ቢሆኑም እርሱ ግን ተወልዶ ያደገው በሮሜ ከተማ ነው፡፡ አያቱና አባቱ ሥራቸው አውሬ ማደን ስለነበር አንድ ቀን እንደልማዳቸው አውሬ ሲያድኑ ከገጸ ከለባት ወገን የሆኑ ሁለት ወንዶች አግኝተዋቸው የመርቆሬዎስን አያት በሉት፡፡ አባቱንም ሊበሉት ሲሉ የታዘዘ መልአክ ከለከላቸው፡፡ ዙሪያቸውንም በእሳት አጥሮ ከበባቸው፡፡ እነርሱም በተቸገሩ ጊዜ ለመርቆሬዎስ አባት ሰገዱለት፡፡ በዚያን ጊዜም እግዚአብሔር ፍጥረታቸውን ወደገራምነት ለወጠውና እንደበጎች የዋሆች ሆነው አብረውት ወደ መንደር ገቡ፡፡
ከዚህም በኋላ ቅዱስ መርቆሬዎስ ተወለደና ስሙ ፒሉፓዴር ተባለ፡፡ የውሻ መልክ ያላቸውም በእርሱ ዘንድ ብዙ ዘመናት ኖሩ፡፡ ከዚህም በኋላ ክርስቲያኖች ሆኑ፡፡ የቅዱስ መርቆሬዎስም ወላጆች አስቀድመው አረማውያን ነበሩና የክርስትና ጥምቀትን በጸጋ ተቀበሉ፡፡ አባቱን ኖህ እናቱንም ታቦት ብለው ሰየሟቸው፡፡ ቀድሞ ፒሉፓዴር የነበረውም ስሙ ተለውጦ መርቆሬዎስ ተባለ፡፡ የውሻ መልክ ያላቸው ግን መልአኩ በተገለጠላቸው ጊዜ እንደነገራቸው ለቅዱስ መርቆሬዎስ አባት የሚታዘዙና የሚያገለግሉ ሆኑ፡፡ ንጉሡም የመርቆሬዎስን አባትና የውሻ መልክ ያላቸውን ዜናቸውን ሲሰማ ወታደሮቹን ልኮ በፊቱ አቆማቸው፡፡ እግዚአብሔርም የቀድሞ ፍጥረታቸውን መልሶላቸው አራዊት አደረጋቸውና ንጉሡን እጅግ አስፈሩት፡፡ ንጉሡም የቅዱስ መርቆሬዎስን አባት የአራዊት ተፈጥሮአቸውን ያርቅለት ዘንድ ለመነው፡፡ የቅዱስ መርቆሬዎስም አባት በለመነ ጊዜ ተፈጥሮአቸውን መልሶላቸው ገራሞች ሆኑ፡፡
ንጉሡም የመርቆሬዎስን አባት ገዥና የሠራዊቱ አለቃ አድርጎ ሾመው፡፡ የውሻ ፊት ያላቸውም አብረው ያገለግሉት ስለነበር ሁሉም ይፈራው ነበር፡፡ ንጉሡም የመርቆሬዎስን አባት ወደ ጦርነት ከላከው በኋላ ሳይመለስ ስለቀረ ሚስቱን ሊያገባት አሰበ፡፡ የመርቆሬዎስ አባትም የመርዶሳውያን አገሮች ሁሉ ገዢ በነበረው ንጉሥ ተይዞ ቢማረክም ገዥው ክርስቲያን መሆኑን አይቶ አከበረው፡፡ ቆይቶም በሀገሩ ላይ ሾመው፡፡ ሚስቱም ጠፍታ ከሀገሯ ወጥታ ሄዳ ስለነበር ከባሏ ተገናኝተው በዚያው መኖር ጀመሩ፡፡ መርቆሬዎስም አባቱና እናቱ ከሞቱ በኋላ ንጉሡ በአባቱ ፈንታ በመርዶሳውያን አገር ላይ ሾመው፡፡
መርቆሬዎስ መኰንንነት በተሾመም ጊዜ ገጸ ከለባቱ አብሮት ነበር፡፡ ለመዋጋትም በወጣ ጊዜ የቀድሞው የአራዊት የሆነ ተፈጥሮውን እግዚአብሔር ይመልስለት ስለነበር ማንም አይቋቋመውም ነበር፡፡ ለቅዱስ መርቆሬዎስ ታላቅ የድል አድራጊነት ኃይል ተሰጠውና ዜናው በሁሉም ሀገሮች ተሰማ፡፡ በሮሜ ሀገር ጣዖትን የሚያመልከው ዳኬዎስ የተባለውም ንጉሥ የበርበር ሰዎች ጋር ጦርነት ሊገጥም በወጣ ጊዜ እጅግ ሲበዙበት ፈራ፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስም በጦሩ መሀል የተሳለ ሰይፍ የያዘ የእግዚአብሔርን መልአክ ስላየ ንጉሡን እግዚአብሔር ያጠፋቸዋልና አትፍራ›› አለው፡፡ መልአኩም ሰይፉን ለቅዱስ መርቆሬዎስ ሰጠውና ‹‹ጦርነቱን ድል ባደረግህ ጊዜ እግዚአብሔርን አስበው›› አለው፡፡
ጦርነቱን ድል አድርጎ ሲጨርስም መልአኩ ድጋሚ ተገልጦለት ‹‹ለምን የፈጣሪህን ስም መጥራት እረሳህ?›› አለው፡፡ ከጦርነቱም በኋላ ንጉሥ ዳኬዎስ ለጣዖታቱ ዕጣን በማሳረግ በዓልን አደረገ፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስም በዚያ ስላልተገኘ ለጣዖታቱ ዕጣን በማሳረጉ እንዳልተባበረ ንጉሡ ሲያውቅ መልእክተኞችን ልኮ አስመጣው፡፡ ንጉሡም ‹‹ከእኔ ጋር ለምን አታጥንም?›› ባለው ጊዜ ቅዱስ መርቆሬዎስ ትጥቁንና ልብሱን አውልቆ ከወረወረለት በኋላ ‹‹ክብር ይግባውና አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስን ፈጽሞ አልክደውም፣ ለረከሱ ጣዖቶችህም አልሰግድም›› አለው፡፡ ንጉሡም ተናዶ ልዩ ልዩ በሆኑ ሥቃዮችም እጅግ አሠቃየው፡፡
ንጉሡም ስለ መርቆሬዎስ ብለው የአገሩ ሰዎች እንዳይነሱበት ፈርቶ በብረት ችንካር ቸንክሮ የቀጵዶቅያና የእስያ ክፍል ወደሆነች ወደ ቂሳርያ ከደብዳቤ ጋር ላከው፡፡ በዚያም እጅግ ካሠቃዩት በኋላ ንጉሡ ዳኬዎስ እንዳዘዘ ኅዳር 25 ቀን አንገቱን በሰይፍ ቆረጡትና የሰማዕትነት ተጋድሎውን ፈጸመ፡፡ የሕይወትንም አክሊል ተቀዳጀ፡፡ በዓለሙ ሁሉ አብያተ ክርስቲያናት ታነጹለት፡፡ እግዚአብሔርም ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን በቅዱስ መርቆሬዎስ ስም አደረገ፡፡
ከብዙ ተአምራቱም አንዱ የቂሳርያውን ሊቀ ጳጳስ ባስልዮስን እረድቶ ከሃዲውን ዑልያኖስን የገደለበት ነው፡፡ ዑልያኖስ ነግሦ የክብር ባለቤት ጌታችንን ክዶ ጣዖታትን ማምለክና ክርስቲያኖችን ማሠቃየት ጀመረ፡፡ የቂሳርያው ሊቀ ጳጳስ ባስልዮስም አስተምሮ ሊመልሰው ወደ ንጉሡ ቢመጣ ክብር ይግባውና ዑልያኖስ ጌታችንን ሰድቦ ባስልዮስንም አሰረው፡፡ ባስልዮስም በእሥር ቤት ሳለ በቅዱስ መርቆሬዎስ ሥዕል ፊት ጸለየ፡፡ ሥዕሉም ወዲያው ተሰወረው፡፡ ያንጊዜም ወደ ከሃዲው ንጉሥ ዑልያኖስ ዘንድ ሄዶ በጦር ወግቶ ገደለውና ወዲያው ወደ ቦታው ተመለሰ፡፡ ከጦሩም አንገት ደም ይንጠፋጠፍ ነበር፡፡ ቅዱስ ባስልዮስም ከሃዲውን ንጉሥ እንደገደለው ዐውቆ ‹‹የክርስቶስ ምስክር ጌታዬ ሆይ የእውነት ፀር የሆነ ዑልያኖስን ገደልከውን?›› አለው፡፡ ሥዕሉም ያን ጊዜ አዎን እንደሚል ራሱን ዘንበል አደረገ፡፡ ቅዱስ ባስልዮስም ደስ ብሎት እግዚአብሔርን አመሰገነ፡፡
ሌላው ሰማዕት ቅዱስ መርቆሬዎስ በተአምሩ ከእስልምና እምነት መልሶ ክርስቲያን ያደረገው አንድ እስላም ሰው አለ፡፡ ይኸውም የቅዱስ መርቆሬዎስ ቤተ ክርስቲያኑ በተሠራችበት በምስር አገር የሚኖር ከመሳፍንት ወገን የሆነ ወጣት ነበረ፡፡ ከብዙ ሰዎችም ጋር ሆኖ ወደ መሐመድ መቃብር ለመሄድ እንዳሰበ ለአባቱ ሲነግረው ስንቅ ሰንቀው በሰላም ወደ መካ መዲና ሸኙት፡፡
መካ ደርሰውም ሥራቸውም ፈጽመው ወደቤታቸው እየተመለሱ ሰባት ቀን ተጓዙ፡፡ በሌሊትም ሲጓዙ ስለ ሥጋዊ ግዳጁ ያ እስላም ወጣት ከግመል ላይ ወርዶ ለመጸዳዳት ዘወር አለ፡፡ እነርሱም አብሯቸው የሚጓ መስላቸው ስለነበር ባልንጀሮቹም በበረሃው ውስጥ ትተውት ሄዱ፡፡ እርሱም ወዴት እንደሚሄድ ስላላወቀ አራዊትም እንዳይበሉት ፈርቶ እጅግ ደነገጠ፡፡ በዚያም ጊዜ በምስር አገር በአባቱ ቤት አቅራቢያ ያለች የሰማዕቱ የቅዱስ መርቆሬዎስን ቤተ ክርስቲያን አስታውሶ በልቡ ቅዱስ መርቆሬዎስን እንዲያድነው በመለመን ተሳለ፡፡ ወዲያውም ቅዱስ መርቆሬዎስ በፈረሱ ተቀምጦ ወደ እርሱ መጣና ‹‹ከወዴት ነህ? ከዚህ በረሃ ውስጥስ እንዴት ጠፋህ?›› አለው፡፡ ወጣቱ እስላምም የሆነውን ነገረው፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስም ‹‹ና በኋላዬ በፈረሱ ላይ ተፈናጠጥ›› አለውና በአየር ላይ እየበረረ በምስር አገር ወዳለች የቅዱስ መርቆሬዎስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንደ ዐይን ጥቅሻ አደረሰውና እንደተዘጋች በውስጧ አስገባውና ከእርሱ ተሰወረ፡፡ ይህም ወጣት በኋላ አምኖ ተጠምቆ ብዙ ሰማዕትነት ተቀብሏል፡፡ ገዳምም ገብቶ ብዙ ከተጋደለ በኋላ እንደገና ወደ አገሩ ተመልሶ ብዙዎችን ወደ ክርስትና አምጥቷል፡፡ በቅዱስ መርቆሬዎስ ስም ቤተ ክርስቲያን አሠርቶ አበ ምኔትም ሆኖ ብዙ መነኮሳትን አፍርቷል፡፡
የሰማዕቱ የቅዱስ መርቆሬዎስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

31 Jan, 17:03


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ጥር 24-ሐዲስ ሐዋርያ ፀሐይ ዘኢትዮጵያ አቡነ ተክለሃይማኖት የመነኮሱበትና አንድ እግራቸው በጸሎት ብዛት የተሰበረበት ዕለት ነው፡፡
+ በዓቷን በማጽናት ለ22 ዓመታት ዘግታ የኖረችውና የላመ የጣፈጠ ቀምሳ የማታውቀው ቅድስት ማርያ ዕረፍቷ ነው፡፡
+ የሸዋው እጨጌ መርሐ ክርስቶስ ዕረፍታቸው ነው፡፡
ቅድስት ማርያ፡- ይኽችም ቅድስት ከታላላቅ ወገኖች የሆነች የከበረች ተጋዳይ ናት፡፡ ወላጆቿ ደጋግ ክርስቲያኖች ናቸው፡፡ እነርሱም በልጃቸውን ማርያን በሃይማኖት በምግባር አሳደጓትና ዕድሜዋ ሲደርስ ሊያገቧት አሰቡ፡፡ ነገር ግን ቅድስር ማርያ አግታ በዓለም መኖርን አልወደደችምና እሺ አላለቻቸውም፡፡ ወላጆቿም በሞቱ ጊዜ የተውላትን ብዙ ወርቅና ንብረት ሁሉንም ለድኆችና ለጦም አዳሪዎች ሰጥታ ከእስክንድርያ ውጭ ወዳሉ ገዳማት ሄዳ ወደ አንዱ ገባች፡፡
ወደ ገዳምም ገብታ ከመነኮሰች በኋላ ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለች፡፡ ሁልጊዜ እስከማታ ድረስ በመጾም ሌሊቱንም ሁሉ እየጸለየች ለ12 ዓመታት ከቶ ምንም ሳትተኛ ተጋድሎዋን አበዛች፡፡ የክብር አስኬማን ከለበሰች በኋላም ከጥጥ ባዘቶ የተሠራ ልብስ ከላይዋ ላይ ጥላ ለበሰች፡፡ በዓቷም ለመዝጋት ወሰነች፡፡ ይህንንም ሀሳቧን ትፈቅድላት እንደሆነ ወደ እመ ምኔቷ ዘንድ በመሄድ መልካም ፈቃዷን ጠየቀቻት፡፡ እርሷም ፈቀደችላት፡፡ ከዚህም በኋላ ቅድስት ማርያ በዓቷን ዘጋች፡፡ የዕለት ጉርሷን የምትቀበልበት ትንሽ መስኮት ቀደደች፡፡ ቅዱስ ሥጋ ወደሙንም በዚያው ትቀበላለች፡፡ በዚያችም በዓቷ ውስጥ ለ22 ዓመታት ዘግታ ኖረች፡ በዚህ ሁሉ ጊዜ ቁማ ትጸልያለች፣ በእንቅልፍም ጊዜ ጥቂት ታርፋለች፡፡ ሌሊቱንም ሁሉ ቁማ ታድራለች፡፡ በየሁለት ቀኑ በውኃ ብቻ የራሰ እንጀራ እየተመገበች ኖረች፡፡ ዓቢይ ጾምም በመጣ ጊዜ በየሦስት ቀኑ እየጾመች በውኃ የራሰ ሽምብራ ብቻ ትቀምስ ነበር፡፡
ጥር 11 ቀን የከበረ የጥምቀት በዓል በሆነ ጊዜ ከተባረከው ውኃ ያመጡላት ዘንድ ለምና አመጡላት፡፡ ቅዱስ ሥጋ ወደሙን ከተቀበለች በኋላ ከጥምቀቱ ውኃ ጠጣች፡፡ ከዚህም በኋላ የዕረፍቷ ጊዜ እንደደረሰ ዐውቃ እስከ ጥር 21 ቀን ቅዱስ ሥጋ ወደሙን ተቀብላ ተኛች፡፡ እመ ምኔቷን አስጠራቻትና ስትመጣላት እጆቿንና እግሮቿን እየሳመች ‹‹ወደ ክብር ባለቤት ወደ ጌታዬ ክርስቶስ ላደረሱኝ እግሮችሽ እገዛለሁ›› አለቻት፡፡ ደናግሉንም ሁሉ አስጠርታ ተሳለመቻቸውና ከ3 ቀን በኋላ ሁሉም ተመልሰው መጥተው እንዲጎበኟት ለመነቻቸው፡፡ ይኸውም በጥር 24 ቀን ነው፡፡ እነርሱም እንደለመነቻቸው በሦስተኛው ቀን ተመልሰው ቢመጡ ቅድስት ማርያን ዐርፋ አገኟት፡፡ በክብር ገንዘው ከደናግል አስክሬን ጋር አኖሯት፡፡ ረድኤት በረከቷ ይደርብን በጸሎቷ ይማረን!
+ + +
እጨጌ መርሐ ክርስቶስ፡- ጻድቁ የገዳማት ሁሉ አባት እየተባሉም ይጠራሉ፡፡ ትውልዳቸው ሸዋ መራቤቴ ሜዳ ሲሆን ለገዳማት ብዙ የደከሙ አባት ናቸው፡፡ በተለይም በእጅጉ የሚታወቁበት አንድ ገድል አላቸው፡፡ ይኸውም እንደ ነዳይ ሆነው ለምነው ያገኙትን ለጦም አዳሪዎች በመመጽወት ይታወቃሉ፡፡ ከባለ ሀብቶች ለምነው ያገኙትን ለድሆች ይመጸውቱትና በቀረው ቤተ ክርስቲያን ይሠሩበታል፡፡ አስደናቂ ገድላቸውና ዐፅማቸው በደብረ ሊባኖስ ይገኛል፡፡ በትግራይም ትልቅ ገዳም አላቸው፡፡ ዕረፍታቸው ጥር 24 ቀን ሲሆን ሕዝቡ ግን የሚያከብረው በዓለ ልደታቸውን ነው፡፡ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!
+ + +
ሐዲስ ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዘደብረ ሊባኖስ፡- ተክለ ሃይማኖት ማለት ‹‹የሃይማኖት ተክል፣ ተክለ አብ ተክለ ወልድ ተክለ መንፈስ ቅዱስ›› ማለት ነው፡፡
እግዚአብሔር አምላካችን ለኢትዮጵያ ሐዲስ ሐዋርያ አድርጎ የመረጣቸው ጻድቁ አባታችን ተክለ ሃይማኖት በሊቀ መላእክት በቅዱስ ሚካኤል አብሳሪነት ከአባታቸው ከካህኑ ጸጋ ዘአብና ከእናታቸው ከቅድስት እግዚእ ኀረያ መጋቢት 24 ቀን ተፀንሰው ታኅሣሥ 24 ቀን 1197 ዓ.ም ተወለዱ፡፡ ጻድቁ በተወለዱ በሦስተኛው ቀን ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው ‹‹አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ›› ማለትም ‹‹አንዱ አብ ቅዱስ ነው አንዱ ወልድ ቅዱስ ነው አንዱ መንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ነው›› በማለት የፈጠራቸውን አምላክ አመስግነውታል፡፡ ወላጆቻቸውም ስማቸውን ፍሥሐ ጽዮን አሏቸው፡፡ ይኸውም የጽዮን ተድላዋ ደስታዋ ማለት ነው፡፡ የወላጆቻቸው የቀድሞ ስማቸው ዘርዐ ዮሐንስና ሣራ ይባል ነበር፡፡
ቅዱሳን አባቶቻችን እነ አቡነ ተክለ ሃይማኖትና እነ አቡነ ዜና ማርቆስ ሌሎቹም እነ አቡነ ሳሙኤል ዘወገግ፣ አቡነ ሕፃን ሞዐ፣ አቡነ አኖሪዮስ(ትልቁ)፣ አቡነ ገላውዲዮስ፣ አቡነ ማትያስ ዘፈጠጋርና አቡነ ቀውስጦስ ዘመሐግል የትውልዳቸው መሠረት ኢያሱ ለሌዋውያን ክፍል ትሆን ዘንድ ከለያት ከኢየሩሳሌም ነው፡፡ ስማቸውን የጠቀስኳቸው እነዚህ ቅዱሳን አባቶቻችን የወንድማማቾች ልጆች ሲሆኑ ከአዳም ጀምሮ 61ኛ ትውልድ ናቸው፡፡ ይኸውም እንዴት ነው ቢሉ ትውልዱ ከአዳም ጀምሮ በካህኑ አሮን በኩል የሆነውና የሌዋዊያን ሊቀ ካህን የነበረው የሳዶቅ ልጅ አዛርያስ በንጉሥ ሰሎሞን ዘመን ከታቦተ ጽዮንና ከብዙ ሌዋዊያን ካህናት ጋር ሊቀ ካህን ሆኖ ከኢየሩሳሌም ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ አክሱም ተቀምጦ ኖረ፡፡ የኦሪትንም ሕግ እየዞረ ለኢትዮጵያ ሰዎች አስተማረ፡፡ ትውልዱም በአብርሃ ወአጽብሓና በአባ ሰላማ ዘመን እስከነበረው እንበረም የሚባለው ጻድቅ ድረስ ደረሰ፡፡ የእንበረምም ትውልድ ደገኛው ሕይወት ብነ በጽዮን ድረስ ደረሰ፡፡ ሕይወት ብነ በጽዮንም የደማስቆ ምድር ከሚሏት ከወለቃ ሀገር የመኮንን ልጅ የሆነችውን ወለተ ሳውልን አግብቶ አበይድላን ወለደ፡፡ አበ ይድላም በንጉሡ ድልዓዥን ዘመነ መንግሥት ለ150 ካህናት አለቃ ሆኖ በወለቃ ሀገር የክርስቶስን የወንጌል ሕግ እያስተማረ ብዙዎችን አጠመቀ፡፡ እስከ ሸዋ ምድር ድረስ እያስተማረ መጥቶ በሸዋ ምድር ተቀመጠ፡፡ ብዙ አብያተ ክርስቲያናትንም አሳነጸ፡፡ እጅግ አስደናቂ ተአምራትንም ያደርግ ነበር፡፡ ‹‹በሸዋ ጽላልሽ ተቀምጦ ሲያስተምርም በአንዲት ቀን እስከ ሁለት መቶ ሺህ ሕዝብ ያጠምቅ ነበር›› በማለት ገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ይመሰክርለታል፡፡
አበይድላ በመጨረሻ በፈቃደ እግዚአብሔር ከሸዋ ጽላልሽ ምድረ ዞረሬ ሚስት አግቶ ሀበነ እግዚእን ወለደ፤ ሀበነ እግዚእም በኩረ ጽዮንን ወለደ፤ በኩረ ጽዮንም ሕዝበ ቀድስን ወለደ፤ እርሱም ነገደ እግዚእ የተባለ ነው፡፡ ሕዝበ ቀድስም ብርሃነ መስቀልን ወለደ፤ እርሱም ዐቃቢነ እግዚእ የተባለ ነው፡፡ ብርሃነ መስቀልም ሕይወት ብነን ወለደ፤ እርሱም ሴትን ወለደ፡፡ ሴትም ወረደ ምሕረትን ወለደ፡፡ ወረደ ምሕረትም ዘካርያስን ወለደ፡፡ ዘካርያስም የእነ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አባት የሆኑ 6 ወንድማማች ልጆችን ወለደ፡፡ እነርሱም እንድርያስ፣ አርከሌድስ፣ ዘርዐ አብርሃም፣ ዘርዐ ዮሐንስ ወይም ጸጋ ዘአብ፣ ቀሲስ ዮሐንስና ቀሲስ ዮናስ ናቸው፡፡ እንድርያስም ሳሙኤል ዘወገግን ወለደ፤ አርከሌድስም ሕፃን ሞዐን ወለደ፤ ዘርዐ አብርሃምም ታላቁን አኖርዮስን ወለደ፤ ዘርዐ ዮሐንስ ወይም ጸጋ ዘአብም ተክለ ሃይማኖትን ወለደ፤ ቀሲስ ዮሐንስም ዜና ማርቆስን ወለደ፣ ቀሲስ ዮናስ ደግሞ የፈጠጋሩን ማትያስንና ገላውዲዮስን ወለዳቸው፡፡ ገላውዲዮስም የመሐግሉ ቀውስጦስን ወለደ፡፡ እነዚህ ደጋግ ቅዱሳን በእናታቸውም በኩል እንዲሁ በዝምድና የተሳሰሩ ናቸው፡፡ ማቴዎስ የተባለው ደገኛ ክርስቲያን የሸዋ ገዥ

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

31 Jan, 17:03


የነበረ ሲሆን አንድ ወንድ ልጅ መድኃኒነ እግዚእንና ሦስት ሴቶች ልጆችን ወለደ፡፡ ሶስቱ ሴቶች ልጆችም እምነ ጽዮን፣ ትቤ ጽዮንና ክርስቶስ ዘመዳ ይባላሉ፡፡ ሦስቱ እኅትማማቾችም ደጋጎቹን አባቶቻችንን ወለዱልን፡፡ እምነ ጽዮን የእነ ዜና ማርቆስን እናት ማርያም ዘመዳንና ወለደች፡፡ ትቤ ጽዮንም ሕፃን ሞዐን ወለደች፡፡ ክርስቶስ ዘመዳ ደግሞ ታላቁን አኖሬዎስን ወለደች፡፡ የፈጠጋሩ ገዥ መድኃኒነ እግዚእ ደግሞ የተክለ ሃይማኖትን እናት እግዚእ ኀረያን ወይም በሌላ ስሟ ሣራን ወለደ፡፡
አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከልጅነታቸው ጀምሮ በወላጅ አባታቸው በካህኑ ቅዱስ ጸጋ ዘአብ ግብረ ዲቁናን ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን ሲያጠኑ ቆይተው በ15 እና በ22 ዓመታቸው ከእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ ከአቡነ ቄርሎስ (ጌርሎስ) ዲቁናንና ቅስናን ተቀብለዋል፡፡ ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን ቅድስት ቤተክርስቲያንን በወጣትነት ዕድሜያቸው ያገለግሉ እንደነበር በዚህ ይታወቀል፡፡
ከዕለታት በአንዱ ቀን አባታችን ከጓደኞቻቸው ጋር ለአደን ወደ ዱር ሄደው ሳለ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ተገልጦ ታያቸው፡፡ ቅዱስ አባታችንም ‹‹እንደዚህ ባለ ገናንነት የማይህ ጌታዬ ማነህ?›› ባሉት ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል ‹‹ዘወትር የምጠብቅህ ካንተ የማልለይ እናትህንና አባትህንም ስላንተ ከውኃ ስጥመትና ከምርኮ ያዳንኳቸው እኔ ሚካኤል ነኝ፡፡ ከእንግዲህ አውሬ አዳኝ አትሁን፤ ሰውን ወደ እግዚአብሔር ለመመለስ ሰውን በትምህርት የምታድን ሁን እንጂ፡፡ እነሆ እግዚአብሔር ጽኑዕ ሥልጣን ሰጥቶሃልና፤ ሙት ታስነሣለህ፤ ድውያንን ትፈውሳለህ፤ አጋንንትም አንተን በመፍራት ይሸሻሉ፡፡ ስምህ ፍሥሐ ጽዮን አይሁን፤ ተክለ ሃይማኖት ይሁን እንጂ፡፡ ትርጓሜውም ተክለ አብ፥ ተክለ ወልድ፥ ተክለ መንፈስ ቅዱስ ማለት ነው›› አላቸው፡፡
ቅዱስ ሚካኤል ይህን ሲነግራቸው ጌታችን በሥጋ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር እንደነበር ሆኖ መልከ መልካም ጎልማሳ መስሎ ታያቸው፡፡ ጌታችንም ‹‹ወዳጄ እንዴት ሰነበትክ? ቸር አለህን?›› አላቸው፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖትም ‹‹ጌታዬ ሆይ አንተ ማነህ?›› ብለው ሲጠይቁት ጌታችንም ‹‹እኔ የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ነኝ፤ በናትህ ማኅፀን ፈጥሬህ ያከበርኩህ እኔ ነኝ፡፡ በተወለድክ በሦስተኛው ቀን አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ብለህ ታመሰግነኝ ዘንድ የምስጋና ሀብት ያሳደርኩብህ እኔ ነኝ፡፡ በርሃብ ዘመን በቤት የሚያሻው ምግብ ሁሉ ቅቤው፣ የስንዴው ዱቄት በእናት በአባትህ ቤት ይመላ ዘንድ በእጅህ ሀብተ በረከት ያሳደርኩብህ እኔ ነኝ፡፡ ያንን ሰው አንተን በተጣላ ጊዜ በነፋስ አውታር የሰቀለኩት በመዓት ጨንገር የገረፍኩት እኔ ነኝ፡፡ ውኃ ጠምቶህ በለመንከኝ ጊዜ ከደረቅ መሬት የጣፈጠ ውኃ ያመነጨሁልህ እኔ ነኝ፡፡ ከልጅነትህ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ብዙ ተአምራት እያደረግሁ በአንተ እጅ የታመሙትን ያዳንኳቸው እኔ ነኝ፡፡ ወደፊትም አደርግልሃለሁ›› አላቸው፡፡ ይህንን ብሎ በእጆቹ ባረካቸውና ‹‹ንሣእ መንፈስ ቅዱስ›› ብሎ የሹመትን ሀብት አሳደረባቸው፡፡ ዳግመኛም ‹‹በምድር ያሰርከው በሰማይ የታሰረ ይሁን፤ በምድርም የፈታኸው በሰማይ የተፈታ ይሁን፤ አንተን የሰማ እኔን መስማቱ ነው፤ የላከኝ አባቴንም መስማቱ ነው፡፡ አንተን እንቢ ያለ እኔን እንቢ ማለቱ ነው፡፡ የላከኝ አባቴንም እንቢ ማለቱ ነው፡፡ ይህን ሥልጣን ቀድሞ ለሐዋርያት ሰጥቻቸው ነበር፡፡ ከሐዋርያትም ሹመትን የተቀበለ ጳጳሱ ትሾምና ትሽር፣ ትተክልና ትነቅል ዘንድ ሥልጣንን ሰጠህ፡፡ ይህንንም ያደረኩልህ የጳጳሱን ቃል በመናቅ አይደለም፡፡ የፍቅሬን ጽናት ባንተ እገልጽ ዘንድ ነው እንጂ፡፡ ሐዋርያት ወዳልደረሱበት ሕዝብ በመምህርነት እልክህ ዘንድ በሚካኤል ቃል አዲስ ስም አወጣሁልህ፡፡ አንተም በማናቸውም ሥራ ከእነርሱ አታንስም፣ ሐዲስ ሐዋርያ አድርጌሃለሁና፡፡ ሰውን ሁሉ በእኔ ስም እያስተማርክ ታሳምን ዘንድ፣ ሚካኤልም ባሰብከው ሥራ ሁሉ ረዳት ይሁንህ፣ ሁል ጊዜ ካንተ አይለይም፤ በምትሄድበትም ጎዳና ሁሉ እርሱ መሪ ይሁንህ፤ እኔም ባለ ዘመንህ ሁሉ አልለይህም›› ካላቸው በኋላ ሰላምታ ሰጥቷቸው ዐረገ፡፡
ብፁዕ አባታችንም እጅ ነሥተው ‹‹ለእኔ ለኀጥኡ የማይገባኝ ሲሆን ይህን ሁሉ ጸጋ የጠኸኝ ስምህ በሰማይ በምድር የተመሰገነ ይሁን›› አሉ፡፡ ከዚያች ቀን ጀምሮ ሀብተ ኃይልን የተመሉ ሆኑ፡፡ ወደቤታቸው ተመልሰው ያላቸውን ሀብት ንብረት ሁሉ ለቤተ ክርስቲያን፣ ለድኆችና ለጦም አዳሪዎች ሰጥተው ጨረሱ፡፡ ከዚያም ‹‹አቤቱ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! የመንግሥተ ሰማያትን በር ትከፍትልኝ ዘንድ እነሆ ቤቴን እንደተከፈተ ተውኩልህ›› ብለው ቤታቸውን እንደተከፈተ ትተው ወንጌልን ለማስተማር ወጡ፡፡ ጻድቁ አባታችን በሀገራችን ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ ሕዝቡን ከኃጢአት ወደ ገቢረ ጽድቅ፣ ከክህደት ወደ ኃይማኖት ስለመለሱት በዚህም የተነሣ ለኢትዮጵያውያን ብርሃን ተብለዋል፡፡
አባታችን ለሰባት ዓመታት በአንድ እግራቸው በመቆም ያለምግብና ያለውኃ በትኅርምት ሌትና ቀን እንቅልፍ በማጣት እንደ ምሰሶ ጸንተው፤ በተመስጦ በትጋት ለሰው ዘር ሁሉ ድኅነትን ሲለምኑ ኖረዋል፡፡ ከሰባቱ ዓመታት ውስጥ ጥቂት ውኃ የቀመሱት በአራተኛው ዓመት ብቻ ነበር፡፡ በዚህ ጊዜ ውስጥ ጌታችን ተገልጦላቸው በሰው አእምሮ ሊታሰብና ሊለካ የማይችል ትልቅና ልዩ የመንግሥት አዳራሽ ከሰጣቸው በኋላ የመለኮትን ነገር የሚናገር የእሳት አንደበት ያላቸው የመንግሥት ልብስ አለበሳቸው፡፡ በመስቀል ምልክት የተጌጡት ሰባት የሕይወት አክሊላትን አቀዳጅቷቸዋል፡፡ ይኸውም ‹‹ስለ ቀናች ሃይማኖትህ፣ ሃይማኖትን ለማስተማር መላዋን ኢትዮጵያን ስለመዞርህ፣ ከአረማውያን ሕዝብ ጋር በሃይማኖት ስትታገል ደምህን ስለማፍሰስህ፣ ወደ ኢየሩሳሌም ወርደህ ልዩ ልዩ የቅዱሳን ቦታዎች ስለመሳለምህ፣ በሰባት ዓመታት ቊመት የአንዱ አገዳ እግርህ ስለመሰበሩ፣ ስለብዙ ጾም ጸሎት ስግደትህ፣ ስለልብህ ንጽሕናና ቅድስና›› በማለት የሕይወት አክሊላትን ካቀዳጃቸው በኋላ ዝክራቸውን በማዘከር መታሰቢያቸውን የሚያደርጉ ሁሉ በዚህ ዓለምም ሆነ በወዲያኛው ዓለም ፍጹም ዋጋና ፍጹም ክብር እንደሚሰጣቸው ጌታችን ታላቅ ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡ ሥጋቸውም ወዴት ይቀበር ዘንድ እንዳላቸው ሲነግራቸው ‹‹እስከ 57 ዓመት ሥጋህ ከዚህ ይቀበራል፤ ከ57 ዓመት በኋላ ግን ይህች ዋሻ ትናዳላች፡ በዚህም ገዳም አደባባይ በስምህ ታላቅ ቤተ ክርስቲያን ልጆችህ ሠርተው ሥጋህን አፍልሰው በውስጡ ያኖራሉ›› አላቸው፡፡ በመጨረሻም አባታችን ለ10 ቀናት ያህል በተስቦ ሕመም ቆይተው ፈጣሪያቸው የገባላቸውን ቃል ኪዳን ለመነኰሳት መንፈሳውያን ልጆቻቸው ከነገሯቸው በኋላ ነሐሴ 24 ቀን በታላቅ ክብር ዐርፈዋል፡፡
የቅዱስ አባታችን በዓላቶቻቸው እነዚህ ናቸው፡- መጋቢት 24 ቀን 1196 ዓ.ም ፅንሰታቸው፣ ታኅሣሥ 24 ቀን 1197 ዓ.ም ልደታቸው፣ ኅዳር 24 ቀን ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ ጋር በሕይወተ ሥጋ እያሉ የሥላሴን መንበር ያጠኑበት ነው፡፡ ነሐሴ 24 ቀን 1296 ዓ.ም ዕረፍታቸው ነው፤ ግንቦት 12 ቀን 1353 ዓ.ም ፍልሰተ ዐፅማቸው ነው፡፡ ጥር 4 ቀን 1289 ዓ.ም ደግሞ በጸሎት ብዛት አንድ እግራቸው የተሰበረበት ነው ነገር ግን የዕረፍታቸውን ቀን ይዞ በዚሁ በጥር ወር በ24 ከመነኮሱበት በዓላቸው ጋር አብሮ ይከበራል፡፡
የቅዱስ አባታችን ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!
ከገድላት አንደበት
✞ ✞ ✞

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

30 Jan, 17:37


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈሰ ቅዱስ ስም አሜን
ጥር 23-የሐዋርያው የቅዱስ ጳውሎስ ረዳት የሆነው ቅዱስ ጢሞቴዎስ ዐረፈ፡፡
+ አስቀድሞ ኃይለኛ ጠንቋይ የነበረውና በኋላ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ በተአምራቱ አሳምኖ ያስጠመቀው በመጨረሻም ሰማዕት የሆነው ቅዱስ አትናስዮስ ዕረፍቱ ነው፡፡
+ በካቶሊኮች እጅ ተሰይፈው ሰማዕት የሆኑት አቡነ ጊዮርጊስ ዘዋሸራ ዕረፍታቸው ነው፡፡
+ የከበሩ ሰማዕታት ጌርሎስ፣ አትናቴዎስና ጻድቁ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ መታሰቢያ በዓላቸው ነው፡፡
ቅዱስ ጢሞቴዎስ ሐዋርያ፡- ይኸውም አሕዛብን ለሚያስተምር ለቅዱስ ጳውሎስ ደቀ መዝሙሩ የሆነ የከበረ ሐዋርያ ነው፡፡ ልደቱና ዕድገቱ ልስጥራን ከሚባል አገር ነው፡፡ አባቱ ከዋክብትን የሚያመልክ ዮናናዊ ነው፡፡ እናቱ ግን በኦሪት ሕግ ጥላ ሥር ነበረች፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ በልስጥራ አገር በሰበከ ጊዜ ጢሞቴዎስ ትምህርቱን ሰምቶ እግዚአብሔርም በጳውሎስ እጅ የሚያደርጋቸውን ድንቅ ድንቅ ተአምራት አይቶ በጌታችን አምኖ ተጠመቀ፡፡ የቅዱስ ጳውሎስም ደቀ መዝሙር ሆኖ ወደ ብዙ አገሮች ተከትሎት በመሄድ ከእርሱ ጋር ስለ ወንጌል ብዙ ደከመ፡፡ ብዙ ታላላቅ መከራዎችና ብዙ ኃዘናት ደርሰውበታል፡፡ ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስም በኤፌሶን ውስጥ በአንዲት አገር ላይ ኤጲስ ቆጶስነት ሾመው፡፡ በአገሪቱም ላይ ቅዱስ ወንጌልን ሰብኮ ሕዝቡን ከአምልኮ ጣዖት መልሶ እግዚአብሔርን ወደማምለክ አምጥቷቸዋል፡፡ በዙሪያዋ ባሉ አገሮችም እየተዘዋወረ በማስተማር ብዙዎችን አጥምቆ የክርስቶስ ተከታዮች አድርጓቸዋል፡፡
ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስ ሁለት መጻሕፍትን በስሙ ጽፎ ልኮለታል፡፡ መልእክቶቹም በዋነኛነት ሕዝቡን እንዲያስተምርባቸውና ራሱም ከቢጸ ሐሳውያን የሚጠበቅባቸው ናቸው፡፡ ቅዱስ ጢሞቴዎስ ለቅዱስ ጳውሎስ ተወዳጅና ታማኝ ልጁ ስለነበር የተለያዩ መልእክቶቹንም ወደ ተለያዩ ሀገራት በእርሱ እጅ ይልክ ነበር፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ለልጁ ለቅዱስ ጢሞቴዎስ በጻፈለት ሁለት መልእክታት ውስጥ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ በእምነት ጉዳይ ላይ በዓለም የሚፈጠረውን ነገር ግልጽ አድርገው የሚያሳዩ ነጥቦችን በዝርዝር ነግሮታል፡፡
ቅዱስ ጢሞቴዎስ አይሁድንና ዮናናውያንን በትምህርቱ ይገሥጻቸው ሕዝቡንም እያስተማረ ያጠቃቸው ስለነበር ቀንተው በጠላትነት ተነሱበትና ተሰብስበው ይዘው ጥር 23 ቀን ገደሉት፡፡ ምእመናንም ሥጋውን አንሥተው ቀበሩት፡፡ ደገኛው ታላቁ ቈስጠንጢኖስም በነገሠ ጊዜ ጥር 27 ቀን ሥጋውን አፍልሶ ወደ ቍስጥንጥንያ በታላቅ ክብር አስመጥቶ በክብር አኑሮታል፡፡
የቅዱስ ጢሞቴዎስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱይማረን!
+ + +
አቡነ ጊዮርጊስ ዘዋሸራ:- ጻድቁ ትውልዳቸው ዋሸራ ነው፡፡ ገዳሙንም 40 ዓመት በሹመት አገልግለዋል፡፡ በካቶሊኮች እጅ በሰይፍ ተሰይፈው ሰማዕት የሆኑ ታላቅ አባት ናቸው፡፡ ካቶሊኮች የረከሰ ሃይማኖታቸውን በቅድስት ሀገራችን ላይ አውጀው እልፍ የሀገራችንን ሊቃውንት በአንድ ቀን በሰይፍ ሲፈጁ አቡነ ጊዮርጊስ ካቶሊኮችንና ዐፄ ሱስንዮስን እየረገሙ ሕዝቡን ግን እያስተማሩ በጽኑ ስለተቃወሟቸው በብዙ መከራ አሠቃይተዋቸዋል፡፡ ጎናቸውን በጦር ወግተው ለቀቋቸው፡፡ ጦሩም እንደተተከለባቸው ከጎንደር አዘዞ ወደ ዋሸራ ገዳም ተመልሰው ‹‹በመንክር ኃይላ›› ሥዕል ሥር ሲሰግዱ ቢውሉ ጌታችን ተገልጦ ጦሩን በመልአክ አስነቅሎላቸዋል፣ ጦሩም መልሶ ሰግዶላቸዋል፡፡ ከጎናቸውም ደም ውኃና ወተት ፈሰሰ፡፡ ጻድቁ በካቶሊኮች ተሰይፈው በሰማዕተነት ካረፉ በኋላ በዚያው በዋሸራ ተቀብረዋል፡፡
+ + +
ዳግመኛም በዚህች ዕለት የከበሩ ሰማዕታት የጌርሎስና የአትናቴዎስ የጻድቁ ንጉሥ የቴዎዶስዮስም መታሰቢያቸው መሆኑን ስንክሳሩ በስም ይጠቅሳቸዋል፡፡የሰማዕታቱ ረድኤት በረከታቸወ ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!
+ + +
አስቀድሞ ኃይለኛ ጠንቋይ የነበረውና በኋላም ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ በተአምሩ አሳምኖ አስጠምቆ ለሰማዕትነት ያበቃው ቅዱስ አትናስዮስ፡- ንጉሥ ዱድያኖስ ሰባ ነገሥታት ሰብስቦ ሰባ ጣዖታት አቁሞ ሲሰግድ ሲያሰግድ ቢያገኛቸው ለሃይማኖቱ ቀናዒ ነውና ከቤተመንግስቱ ገብቶ በከሃዲያኑ ሰባው ነገሥታት ፊት ክርስቲያን መሆኑን በመመስከር የጌታችንን አምላክነት መሰከረ፡፡ ዱድያኖስም የቅዱስ ጊዮርጊስን ማንነቱን ከተረዳ በኋላ ‹‹አንተማ የኛ ነህ በዐሥር አህጉር ላይ እሾምሃለሁ የኔን አምላክ አጵሎንን አምልክ›› አለው፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም ‹‹ሹመት ሽልማትህ ለአንተ ይሁን እኔ አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስን አልክደውም›› አለው፡፡ በዚህ ጊዜ ዱድያኖስ እጅግ ተናዶ ብዙ አሠቃቂ መከራዎችን አደረሰበት፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ግን ጌታችንን ‹‹ይህን ከሃዲ እስካሳፍረው ድረስ ነፍሴን አትውሰዳት›› በማለት መከራውን ይታገስ ዘንድ ለመነው፡፡ እግዚአብሔርም ጸሎቱን ሰምቶ ፈቃዱን ይፈጽምለት ብዙ በመከራው ሁሉ ጽናትን ሰጥቶታል፡፡ ሦስት ጊዜም ከሞት አስነሥቶታል፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም የደረሱበት እጅግ አሠቃቂ መከራዎች የሰው ኅሊና ሊያስባቸው እንኳን የማይችላቸው ናቸው፡፡ በመጀመሪያም ዱድያኖስ በእንጨት ላይ ካሰቀለው በኋላ ሥጋውን በመቃን አስፈተተው፣ ረጃጅም ችንካሮች ያሉበት የብረት ጫማ አጫምቶት ሂድ አለው፡፡ ጌታችንም ቅዱስ ሚካኤልን ልኮለት ፈውሶታል፡፡ ዳግመኛም በሰባ ችንካሮች አስቸንክሮ በእሳት አስተኩሶ አናቱን በመዶሻ አስቀጥቅጦ በሆዱ ላይ የደንጊያ ምሰሶ አሳስሮ እንዲያንከባልሉት አደረገ፡፡ ሥጋውንም በመጋዝ አስተልትሎ ጨው ነሰነሰበት፡፡ ሥጋውም ተቆራርጦ መሬት ላይ ወደቀ፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመንፈቀ ሌሊት በእጁ ዳስሶ ከፈወሰውና ‹‹ገና ስድስት ዓመት ለስሜ ትጋደላለህ፣ 3 ጊዜ ትሞታለህ፣ በ4ኛውም ታርፋለህ›› ካለው በኋላ በመከራውም ሁሉ እርሱ እንደማይለየው ነገረው፡፡
ዱድያኖስ ቅዱስ ጊዮርጊስን ከዚያ ካደረሰበት አሠቃቂ መከራዎች ሁሉ ድኖ ፍጹም ጤነኛ መሆኑን በተመለከተ ጊዜ እጅግ ደንግጦ ‹‹የሚያሸንፍልኝ ቢኖር ብዙ ወርቅ እሰጠዋለሁ›› ብሎ ተናገረ፡፡ አትናስዮስ የተባለ መሠርይ አንዲትን ላም በጆሮዋ ሲያንሾካሹክባት ለሁለት ተሰንጥቃ ስትሞት ለንጉሡ አሳየውና ቅዱስ ጊዮርጊስን እንዲሚያሸንፍ ምልክት አሳየ፡፡ ንጉሡም ‹‹ያሸንፍልኛል›› ብሎ ደስ አለው፡፡ መሠርይውም ሆድ በጥብጦ አንጀት ቆራርጦ የሚገድል መርዝ ቀምሞ አስማተ ሰይጣን ደግሞበት እንዲጠጣው ለቅዱስ ጊዮርጊስ ሰጠው፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ግን ስመ እግዚአብሔርን ጠርቶ ቢጠጣው እንደ ጨረቃ ደምቆ እንደ አበባ አሸብርቆ ተገኝቷል፡፡ በዚህም ጊዜ ጠንቋዩ እጅግ ተገርሞ ‹‹ማረኝ›› ብሎ ከቅዱስ ጊዮርጊስ እግሩ ሥር ወደቀ፡፡ ዳግመኛም ‹‹አምላክህ አምላኬ ይሁነኝ›› ብሎ ለመነው፡፡ ሰማዕቱም የዚያን መሠርይ ጠንቋይ መመለሱንና ማመኑን አይቶ የቆመባትን መሬት በእግሩ ረግጦ ውሃን አፍልቆ ወደ ጌታችን በጸሎት ቢያመለክት ሐዋርያው ቶማስ በመንፈስ መጣና መሠርይ የነበረውን ሰው አትናስዮስን አጠመቀው፡፡ አትናስዮስም ‹‹ከቅዱስ ጊዮርጊስ አምላክ በቀር ሌላ አምላክ የለም›› በማለት የጌታችን አምላክነት በከሃድያኑ ነገሥታት ፊት መስክሮ በዛሬዋ ዕለት አንገቱን ለሰይፍ ሰጥቶ በሰማዕትነት ዐርፏል፡፡
የቅዱስ ጊዮርጊስና የቅዱስ አትናስዮስ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!
ከገድላት አንደበት
✞ ✞ ✞

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

21 Jan, 08:41


ዐፅማቸው ያረፈበት ታላቅ ገዳም ሆኗል፡፡ ገዳሙ ‹‹የቅድስት ዴሚያና የሴቶች አንድነት ገዳም›› የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን የእርሷን ፈለግ የተከተሉ ክርስቶስን በድንግልና
የሚያገለግሉት ሴቶች መነኰሳይያት በንጽሕና በቅድስና የሚኖሩበት ታላቅ ገዳም ነው፡፡ ዛሬ ላይ በኤርትራ ያለውም የቅድስት ዴሚያና ገዳም እንዲሁ ሴቶች ደናግል
መነኰሳይያት ብቻ የሚኖሩበት ቤተ ደናገል ገዳም ነው፡፡
የሰማዕቷ የቅድስት ዴሚያና እንዲሁም የአርባው ደናግል ሰማዕታት ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን፡፡

(ምንጭ፦ የሰማዕቷን ታሪክ እኅታችን መምህርት ዘውዴ እንደጻፈችው።)

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

21 Jan, 08:41


ቅዱስ ማርቆስም ሐምሌ ስምንት ቀን ሰማዕትነት ከመቀበሉ በፊት አስቀድሞ ጌታችንን ስለ ስሙ መስክሮ በሰማዕትነት እንዲሞት ስለፈቀደለት እጅግ አድርጎ ያመሰግነው ነበር፡፡
ዲዮቅልጥያኖስም ታማኝ ሹመኛው ነበርና ቅዱስ ማርቆስን ካስገደለው በኋላ መጸጸትና መናደድ ጀመረ፣ ቅዱስ ማርቆስም በመጀመሪያ እሽ ብሎት ወደ ጣዖት አምለኮው ከገባለት በኋላ እንደገና በክርስቶስ ወደማመን ተመልሶ እስከሞት ድረስ ለመታመን የቻለው በልጁ በቅድስት ዴሚያና ምክንያት እንደሆነ አጣርቶ ደረሰበት፡፡ እርሷም አባቷን አስተምራ አሳምና ለሰማዕትነት እንዳበቃችው ሲሰማ ዲዮቅልጥያኖስ የት እንዳለች ከጠየቀ በኋላ
በአስቸኳይ ይዘው እሽ ካለች እንዲያከብሯት፣ ነገር ግን ለጣዖታቱ ካልተገዛች አሰቃይተው እንዲገድሏት በማዘዝ አንዱን መኰንን ከመቶ ጭፍሮች ጋር ላከው፡፡ የተላከው መኰንንም ጭፍሮቹን አስከትሎ ሔዶ ቅድስት ዴሚያናን አገኛትና በንጉሡ ትእዛዝ መሠረት ለጣዖታት እንድትሰግድ ሲጠይቃት እርሷም ‹‹ሰማይንና ምድርን፣ ውቅያኖስንና በውስጡ ያሉትን ሁሉ ከፈጠረ ከአንድ እግዚአብሔር ከአብ ከወልድ ከመንፈስ ቅዱስ በቀር ሌላ አምላክ የለም…›› በማለት በእምነቷ ጸናች፡፡ ሐሳቧንም እንድትለውጥ የዲዮቅልጥያኖስ መኰንን ብዙ ጊዜ ሲያባብላት እርሷም እስከመጨረሻው በእምነቷ ስለጸናች መኰንኑ እጅግ ተበሳጭቶ ከዓሥር በላይ የተለያዩ መከራዎችን
አደረሰባት፡፡ በመጀመሪያ በድንጋይ መጭመቂያ መሣሪያ ጨምቀው አሰቃዩዋት፣ ደሟም በምድር ላይ እንደውኃ ፈሰሰ፣ ነገር ግን ቅድስት ዴሚያና እንደ ቅዱስ እስጢፋኖስ
ለገዳዮቿ ምሕረትን ትለምን ነበር፡፡ ጭፍሮቹም በእሥር ቤት ጥለዋቸው ሳለ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ተገልጦላት ሰውነቷን በመዳደድ ከቊስሏ ፈወሳትና ምንም እንዳልነካት ሆነች፡፡ በቀጣዩ ቀንም ሞታ እንደሆን ለማየት መኰንኑ ሲመጣ እንደቀድሞው ደኅና ሆና አገኛት፣ ይህንንም አይተው በቅድስት ዴሚያና አምላክ ያመኑትን በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ገድላቸውና የሰማዕትነት ክብርን ተቀዳጁ፡፡

ዳግመኛም መኰንኑ የቅድስት ዴሚያናን ሰውነት በተሳለ ብረት እንዲፈቀፍቁት አዘዘና ሥጋዋን ፋቋት፣ በዚኽም ሳያበቁ እንደገና በፈቀፈቋት ሰውነቷና በቊስሏ ላይ የሚያቃጥል
አሲድና ኮምጣጤ ጨምረው አሰቃዩአት፤ እርሷ ግን በዚህ ሁሉ ትደሰትና ታመሰግን ነበር፡፡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤልም ለኹለተኛ ጊዜ በእሥር ቤት ውስጥ ሳለች ተገልጦላት ፈወሳት፡፡ ይኽንንም ተኣምር ያዩ በርካታ ሰዎች በቅድስት ዴሚያና አምላክ አመኑ፡፡ መኰንኑም እንደገና በታላላቅ የብረት መዶሻ እንዲመቷት አዘዘና ከመሬት ላይ ወድቃ መነሣት እስከማትችል ድረስ በኀይል በብረት መዶሻ ቀጠቀጧት፡፡ ዳግመኛም መኰንኑ በዚህ አልበቃ ብሎት በቲአትር መመልከቻ አደባባይ ላይ አውጥቶ በላይዋ ላይ ቅባት ካፈሰሱባት በኋላ በእሳት አቃጠሏት፣ እሳቱም ወደላይ እስኪወጣ ድረስ ዕንጨት በመጨመር ቢቃጥሏትም ቅድስት ዴሚያና ግን ልዑል እግዚብሔርን ታመሰግን ነበር፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም ለሦስተኛ ጊዜ መጥቶ ከዚህ መከራ አዳናት፡፡ ይኽንንም ታላቅ ተአምር ያዩ ሁሉ በጌታችን አምነው ስለ ስሙ መስክረው በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡

ዳግመኛም መኰንኑ ‹‹…ይሄ ሁሉ ሕዝብ በአንቺ ምክንያት ሲሞት አንቺ ግን ፊትሽ በደስታ ያበራል›› እያለ ሲዘልፋት እርሷ ግን ‹‹…ለክርስቶስ መሥዋዕት አድርጌ ያቀረብኳቸው ናቸው›› አለችው፡፡ በዚኽም ጊዜ የራሷን ቆዳ በስለታማ ብረት
እንዲላጩትና የፈላ ዘይትና አሲድ እንዲጨምሩበት ጭፍሮቹን አዘዛቸው፣ እንደታዘዘውም አደረጉባትና አሰቃዩአት፡፡ ዳግመኛም ዐይኖቿን እንዲያወጡት አደረገ፤ የመላ ሰውነቷንም ቆዳ እንዲገፉት አደረገና የፈላ ዘይት እንዲጨምሩበት አዘዘ፡፡ ቅድስት ዴሚያናም በዚህ
ሁሉ መከራ ውስጥ እያለች የእግዚአብሔርን ምስጋና አላቋረጠችም ነበር፡፡ በዚህም ጊዜ ጌታችን በሕዝቡ ሁሉ ፊት ከመከራውና ከሕማሙ ሁሉ ፈወሳት፡፡ ለአራተኛም ጊዜ ይህን ተኣምር የተመለከቱ ሁሉ በጌታችን አምነው በሰማዕትነት ዐርፈው የክብር አክሊልን ተቀዳጁ፡፡ መኰንኑም ለአምስተኛ ጊዜ በእሥር ቤት ውስጥ አሠራት፡፡ በማግስቱም እየተሽከረከረ ከሚዞር ብረት ጋር አጣብቀው እንዲቸነክሯትና በዚያም አካሏ እስከሚበታተን ድረስ እንዲያሰቃዩአት አዘዘ፤ በትእዛዙም መሠረት ከሰውነቷ ጋር የታሰረውን ስለት ያለው
የብረት ማጣበቂያ ጎተቱትና አጥብቀው ሲቸነክሯት ቅድስት ነፍሷ ከሥጋዋ ተለየች፡፡ መኰንኑም ከተኣምራቷ የተነሣ ከሞት ልትነሣ ትችላለች ብሎ ሥጋዋን እንዲበሉት ለዱር
አራዊት ሰጠው፡፡ ነገር ግን ወዲያው ከሰማይ ታላቅ የነጎድጓድ ድምፅ ተሰማ፣ በዚያ የነበሩ ሰዎችም ተፍገምግመው ወደቁ፣ እንደሞቱም ሆኑ፡፡ ወዲያውም የክብር ባለቤት ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሠራዊተ መላእክት ታጅቦ ክብርት እመቤታችን በቀኙ ሆና
በታላቅ ግርማ ወረደና የቅድስት ዴሚያና አካሏ ወደተበላበት ተመለከተና ‹‹የተባረክሽ ልጄ ዴሚያና ሆይ! ተነሺ›› በማለት ሲያዝ ወዲያው በአራዊት ተቆራርጦ የተበላው አካሏ
ተሰበሰበ፣ ዴሚያናም ከእንቅልፏ እንደምትነሣ ፈጥና ተነሣችና ከሞት ካስነሣት አምላኳ እግር ሥር ወድቃ ሰገደችለት፡፡ ጌታችንም ሦስት አክሊላትን ካቀዳጃትና ቃልኪዳን ከገባላት በኋላ በዚያ ቦታ ላይ በስሟ ቤተ ክርስቲያን እንደሚሠራ ነግሯት በክብር ዐረገ፡፡

ከዚኽም በኋላ ቅድስት ዴሚያና ፈጥና ወደ መኰንኑ ዘንድ ሔዳ ‹‹ጌታዬ መድኀኒቴ ከሞት አስነሣኝ…›› ብላ መሰከረች፡፡ ስትሞት ያዩዋትም ሁሉ አሁን ላይ ድጋሚ ቆማ ስትመሰክር ሲያዩዋት እጅግ ተገርመው በአምላኳ በክርስቶስ አምነው መስክረው እነርሱም በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡ መኰንኑም የሽንፈትና የሐፍረት ስሜት ስለተሰማው ጭፍሮቹን
ሰብስቦ የቅድስት ዴሚያናን አንገት በሰይፍ ቆርጠው ወደ ንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስ በቶሎ እንዲመለሱ ተማከሩ፡፡ ከዚኽም በኋላ ቅድስት ዴሚያና እና አርባው ደናግል እንዲሁም በክርስቶስ ያመኑት ሁሉ እንዲገደሉ ደብዳቤ ጻፈ፡፡ በዚኽም መሠረት ሁሉንም ይዘው ከከተማው አውጥተው በሰይፍ ሰየፏቸው፡፡ በቅድስት ዴሚያና አምላክ ያመኑ 400 ሰዎችም በሰማዕትነት ዐርፈው ለክብር በቁ፡፡ የቅድስት ዴሚያናም ዕረፍቷ ጥር 13 ቀን ተፈጸመው፡፡

የንግሥት ዕሌኒ ልጅ ደገኛው ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ በእግዚአብሔር ፈቃድ ሲነግሥ አብያተ ክርስቲያናትን አስከፍቶ ክርስቲያኖችን ከእሥር አስለቅቆ የተሰደዱትንም
መልሶ አከበራቸው፡፡ ንግሥት ዕሌኒም ስለ ቅድስት ዴሚያና ተጋድሎና ስለተቀበለችው መከራ ስትሰማ ከእርሷ በረከትን ታገኝ ዘንድ የሰማዕታቱ ቅዱስ ሥጋቸው ወዳለበት ቦታ
ሔደች፡፡ የሰማዕታቱም ሥጋቸው ምንም ሳይሆን በክብር ተቀምጦ አገኘችና የሁሉንም በተለይም የቅድስት ዴሚያናንም ቅዱስ ሥጋዋን በክብረ ልብስ ጠቅልላ በልዩ መቃብር ውስጥ አስቀመጠችውና ታላቅ ቤተ ክርስቲያን አሠራችላቸው፤ ግንቦት 12 ቀንም ቅዳሴ ቤታቸው ተከበረ፡፡ ከሥጋቸውም ብዙ ድንቅ ድንቅ ተኣምራት ተገልጠው ታዩ፡፡
ለቅድስት ዴሚያና ወላጅ አባቷ ቅዱስ ማርቆስ መጀመሪያ ላይ ባሠራላት ቤተ መንግሥት በኋላም እርሷ ወደ ገዳምነት የቀየረችው ቤት ዛሬ ላይ ግብፅ ውስጥ የሰማዕታቱ ቅዱስ

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

21 Jan, 08:41


በዚኽች ዕለት ጥር 13 ቀን በዓመታዊ የዕረፍት በዓላቸው ተከብረው የሚውሉት አቡነ ዘርዐ ቡሩክ ሙታንን አንዳስነሡ የሚናገር ተአምር ይኽ ነው፡- በእግዚአብሔር ሰው በአቡነ ዘርዐ ቡሩክ አገር ውስጥ በብዙ ዓይነት በሽታ የታመመች በጽኑ ደዌ የተያዘች አንዲት ሴት ነበረች፡፡ ዘመዶቿና ቤተሰቦቿ የበሽታዋን ብዛት የደዌዋንም ጽናት አይተው ከበሽታዋ እንዲያድናት ‹‹ሕመምተኞችን በጸሎቱ ለሚያድን ሙታንን በአማላጅነቱ ለሚያስነሣ ለአቡነ ዘርዐ ቡሩክ ሄደን በሽታዋን እንንገረው…›› እያሉ ያዝኑ ነበር፡፡ ደርሰውም የልጃቸውን በጽኑ መታመም ነገሩት፡፡ ‹‹አባታችን ሆይ! በጸሎትህ በሽተኞች እንደሚድኑ ሙታንም እንደሚነሡ እናምናለንና የልጃችንን የበሽታዋን ጽናት ልንነግርህ መጥተናል፤ አሁንም ልጅህን በጸሎትህ አትርሳት፣ እንዲትሞትም አትተዋት›› ብለው ከእግሩ ሥር ወደቁ፡፡
አባታችንም የልጅቱን ወላጆች የኀዘናቸው መጠን አይቶ እርሱም እንደእነርሱ አዘነ፤ ‹‹ወደ ቤታችሁ ሒዱ እግዚአብሔር ከበሽታዋ አድኖ ያስነሣላችሁ›› አላቸው፡፡ እነሱም ይህንን ነገር ከጻድቁ አባታችን ከአቡነ ዘርዐ ቡሩክ ሰምተው ወደ አገራቸው ሔደው ከታማሚዋ ዘንድ በደረሱ ጊዜ በሽታው ጸንቶባት ስላገኟት እጅግ አዘኑ፡፡ ስለ መዳኗም ልባቸው ተስፋ ቆረጠ፡፡ የበሽታዋን ጽናት አይተው ወደ አቡነ ዘርዐ ቡሩክ አመጧት፡፡ ወደ አባታችንም እየወሰዷት ሳለ በመንገድ ላይ እያለች ሞተች፡፡ እናትና አባቷም እጅግ አዝነውና ደንግጠው ወደ አባታችን በዓት ወስደው አስክሬኗን በፊቱ አስቀመጡ፡፡
አባታችንም በመንገድ የሞተችውን ሴት አምጥተው ከፊቱ እንደጣሏት ባየጊዜ ከእነርሱ ዘወር ብሎ ወደ በዓቱ ገባ፡፡ የሞትና የምሕረት ጊዜ እንዳልሆነም በመንፈስ ቅዱስ ተገልጦለት ከጥቂት ቆይታ በኋላ አምጥተው ከቤቱ እንደያስገቧት አዘዘ፡፡ እነርሱም እንዳዘዛቸው ከቤት አስገቧት፡፡ ያንጊዜም አቡነ ዘርዐ ቡሩክ አስነሥቶ ያመነኩሳት ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፡፡ በቅዱስ መስቀል ምልክት ባርኮ በእርሷ ጸሎት አደረገ፡፡ ወዲያውም ከእንቅልፉ እንደሚነቃ ሰው ፈጥና ተነሣች፤ ከሞትም ዳነች፡፡
ዘመዶቿና ቤተሰቦቿ ከዚያ ያሉ ሁሉ እጅግ ደስ አላቸው፡፡ ይህንንም ተአምር ያዩ ሁሉ አደነቁ፡፡ እርስ በእርሳቸውም ‹‹ይህ ጻድቅ አባታችን ሙት በማስነሣት ድውይ በመፈወስ እንደ እግዚአብሔር ተአምራት ያደርጋል ለእኛ ግን ሲበላና ሲጠጣ ስላየነው እንደእኛ ሰው መስሎን ነበር›› ተባባሉ፡፡
ተአምራቱንም ካዩ በኋላ በጻድቁ አባታችን ጸሎት ሙታ ከተነሣች ከዚያች ሴት ጋር በለመኑት ልመና ሙታንንን ያስነሡ ዘንድ ሥልጣንን የሚሰጥ እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ወደቤታቸው ተመለሱ፡፡ ያች ሴትም እግዚአብሔርን አመሰገነችው፡፡ በጸሎቱ ከሞት ያስነሣት ብፁዕ አባታችንን አቡነ ዘርዐ ቡሩክንም አመሰገነችው፡፡ እርሷም እስካሁን ይህ መጽሐፈ ገድል እስከተጻፈበት ዕለት ድረስ በሕይወት አለች፡፡

የአቡነ ዘርዐ ቡሩክ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፤ በጸሎታቸው ይማረን።

(የገዳማቱ ፎቶ፦ አዴት እና ቲሊሊ ግሽ አባይ እንዲሁም ገርዓልታ ተራራ ላይ የሚገኙት የተአምረኛው አባት የአቡነ ዘርዐ ቡሩክ ገዳማት)

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

21 Jan, 08:40


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈሰ ቅዱስ ስም አሜን
ጥር 13-በቀን ለሰባት ሰዓት ያህል ሲኦል ውስጥ ገብተው ይጸልዩ የነበሩትና ጥንባሆ ስለሚጠጡ ሰዎች ጌታችን ታላቅ ምሥጢርን የነገራቸው አቡነ ዘርዐ ቡሩክ ዕረፍታቸው ነው፡፡በአሁኑ ሰዓት በዓለም ላይ ካለው ነባራዊ ሁኔታ ስንነሣ ጥናቶች እንደሚያሳዩትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አንዱ ክፍል (UNODC-united nation’s office on Drug and crime) በጥናቱ ይፋ እንዳደረገው በየዓመቱ 200,00 (ሁለት መቶ ሺህ) ሰዎች አደንዛዥ ዕፅን መጠቀማቸውን ተከትሎ ለሞት ይዳረጋሉ፡፡ በአሜሪካን አገር ብቻ በየቀኑ ከ95 በላይ ሰዎች በአደንዛዥ ዕፅ ምክንያት ይሞታሉ፡፡ አደንዛዥ ዕፅን በክትባት መልክ (injection) ከሚወስዱት ውስጥ አብዛኛዎቹ በደማቸው ውስጥ የHIV ቫይረስ ይገኛል፡፡ በአሜሪካን አገር በአደንዛዥ ዕፅ ምክንያት የሞቱት ሰዎች ቁጥር በመኪና አደጋ እና በድንገተኛ እሳት አደጋ ምክንያት ከሞቱት ሰዎች ቁጥር በ10% ብልጫ አለው፡፡ አደንዛዥ ዕፅንና ሱስን በተመለከተ ዓለም መፍትሄ አጥታ ትባዝናለች፡፡ ችግሩ በዓለም ላይ ይህን ያህል የገዘፈውንና ብዙ ቀውሶችን እያስከተለ ያለውን የጥንባሆን (የአደንዛዥ ዕፅን) ጉዳይ አባቶቻችን እነ አቡነ ዘርዐ ቡሩክ ምሥጢሩን አግኝተውታል፡፡ ሚሥጢሩንም ከፈጣሪ አግኝተው ከተረዱ በኃላ ጤናን የሚጎዳ ከመሆኑም በላይ ለዘለዓለም የነፍስን ቅጣት እንደሚያስከትል አደንዛዥ ዕፁም ከሰይጣን እንደተገኘ በግልጽ ነግረውናል፡፡ ጻድቁ አቡነ ዘርዐ ቡሩክ ጥንባሆን ስለሚጠጡ (አደንዛዥ ዕፅን ስለሚጠቀሙ) ሰዎች ታላቅ ምሥጢርን ከጌታችን የተነገራቸው ናቸው፡፡ በቅድሚያ የጻድቁን ሙሉ ታሪካቸውን በማየት ቀጥሎ የጥንባሆውን ምሥጢር እናያለን፡-
አቡነ ዘርዐ ቡሩክ እንደተጋድሎአቸውና እንደጽድቃቸው መጠን እንደተሰጣቸውም እጅግ ድንቅ ቃልኪዳን መጠን በሁሉም አካባቢ እንደሌሎቹ አንጋፋ ቅዱሳን በደንብ ያልታወቁ እጅግ የከበሩ ታላቅ አባት ናቸው፡፡ አባታቸው ደመ ክርስቶስ እናታቸው ማርያም ሞገሳ ይባላሉ፡፡ ሀገራቸው ጎጃም ግሽ ዓባይ ነው፡፡ ዋሸራ ገዳም ካቀኑት አባቶች ውስጥ አንዱ የሆኑት ተስፋ ኢየሱስ የተባሉት ጻድቅ ወንድማቸው ናቸው፡፡ የመጀመሪያ ስማቸው ጸጋ ኢየሱስ ይባላል፡፡ ነሐሴ 27 ቀን ተወልደው ሃይማኖትን ተምረው ካደጉ በኋላ ‹‹ዘርዐ ቡሩክ›› ብሎ ስም ያወጣላቸውና ጳጳስ አድርጎም የሾማቸው ራሱ ጌታችን መድኃኔዓለም ክርስቶስ ነው፡፡
አቡነ ዘርዐ ቡሩክ ከመወለዳቸው አስቀድሞ ትንቢት ተነግሮላቸው ነበር፡፡ አባታቸው ደመ ክርስቶስ ዐይነ ሥውር የነበረ ሲሆን አቡነ ዘርዐ ቡሩክ በተወለዱ ጊዜ ግን የአባታቸውን ዐይን አብርተውለታል፡፡ አባታችን ዘርዐ ቡሩክ ገና በሰባት ዓመታቸው ነው ረቡዕና ዓርብ መጾም የጀመሩት፡፡ በዚሁ በሰባት ዓመታቸውም ‹‹ይህን ዓለም ክፋቱን እንዳላይ ዐይኖቼን አሳውርልኝ›› በማለት ዐይናቸውን እንዲያጠፋላቸው አምላካቸውን ለምነው እንደፈቃዳቸው ዐይነ ሥውር ሆነዋል፡፡ ነገር ግን ከሰባት ዓመት በኋላ በ12 ዓመታቸው ጌታችን ‹‹ለዓለም የምታበራ ብርሃን አደርግሃለሁና ዐይንህም ይብራ›› በማለት ዐይነ ብርሃናቸውን መልሶላቸው እንዲያዩ አድርጓቸዋል፡፡ በዚህም ዕድሜያቸው (በ12 ዓመታቸው) ሰባቱንም አጽዋማት ይጾሙ ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ ጌታችን የቅዱሳት መጻሕፍትን ምሥጢር ሁሉ ገለጠላቸው፡፡ መጻሕፍተ ብሉያትን፣ መጻሕፍተ ሐዲሳትን፣ መጻሕፍተ ሊቃውንትን፣ መጻሕፍተ መነኮሳትን፣ አዋልድ መጻሕፍትን ሁሉ ገልጦላቸዋል፡፡ ከሟርት መጻሕፍት በቀር ያስቀረባቸው ነገር አልነበረም፤ የቅዱስ ያሬድንም ዜማ እንዲሁ ገለጠላቸው፡፡
ጻድቁ ከሁሉ ቅዱሳን በበለጠ ሁኔታ ዐሥራ ሁለት ክንፍ የተሰጣቸው ሲሆን በ12 ክንፎቻቸውም የሰማይን ደጆች ሁሉ ገሃነመ እሳትንም አልፈው በመሄድ ቀጥታ በሥሉስ ቅዱስ ዙፋን ፊት ይቆሙ እንደነበር ቅዱስ ገድላቸው ይናገራል፡፡ እጅግ በሚደንቅና ከአእምሮ በላይ በሆነ ሁኔታ አባታችን ለሰባት ቀናት በየቀኑ ለሰባት ሰዓት ያህል በሲኦል ውስጥ ቆመው ይጸልዩ ነበር፡፡ ብዙዎቹ ቅዱሳን በምልጃቸው ነፍሳትን ከሲኦል ሲያወጡ ነው የምናውቀው እንጂ እንደ አቡነ ዘርዐ ቡሩክ በሲኦል ውስጥ ገብቶ ጸሎት የጸለየ ጻድቅ እስካሁን እኔ አላጋጠመኝም፡፡
አቡነ ዘርዐ ቡሩክ እንደ አባታችን ተክለሃይማኖት ለጸሎት በመቆም ብዛት አንድ እግራቸው እስኪሰበር ድረስ በብዙ መከራ ተጋድለዋል፡፡ ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ጋር መንበሩን ያጥኑ ዘንድ ከፈጣሪአቸው ታዘው አጥነዋል፡፡ ጌታችን ለአቡነ ዘርዐ ቡሩክ ፍጥረታትን ከመፍጠር በቀር ያልሰጣቸው ሥልጣን የለም፡፡ ‹‹እግዚአብሔር ብፁዕና ቅዱስ ለሚሆን አባታችን ዘርዐ ቡሩክ ‹እኔ ከሥልጣኔ ሥልጣንን፣ ከክብሬም ክብርን፣ ከጥበቤም ጥበብን፣ ከተአምራቴም ተአምራትን፣ ከስጦታዬም ስጦታን፣ ከትዕግስቴም ትዕግስትን፣ ከፍቅሬም ፍቅርን፣ ከትሕትናዬም ትሕትናን፣ ከባለሟልነቴም ባለሟልነትን ሰጥቼሃለሁና ሁሉ ከሥልጣንህ በታች ሆኖ ይታዘዝልህ› የሚል እጅግ ድንቅ ቃልኪዳን ነው የሰጣቸው፡፡ ልዩ ልዩ ሀብታትን ሁሉ ሰጣቸው፡፡ ‹‹ለሥላሴ ከሚገባ ከስግደትና በቃልና በሥልጣን ፍጥረታትን ለመፍጠር በቀር ምንም ያልሰጠሁህ የለም›› ብሎ ጌታችን በማይታበል ቃሉ እንደነገራቸውና ቃል እንደገባላቸው በቅዱስ ገድላቸው ላይ ተጽፏል፡፡ (የአባታችን ገድላቸው ከመጥፋቱ የተነሣ በአሁኑ ሰዓት አንዳንድ ነጋዴዎች አንዱን ፍሬ ከ3 ሺህ ብር በላይ እየሸጡት ነበር፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ ቲሊሊ የሚገኘው ገዳማቸው በድጋሚ አሳትሞታል፡፡)
አቡነ ዘርዐ ቡሩክ በወቅቱ በነበረው ገዥ ፊት በሐሰት ተከሰው ለ5 ዓመታት ያህል በእስርና በእንግልት ሲኖሩ በእነዚህ ጊዜያት ሁሉ ምግብ የሚባል አይቀምሱም ነበርና ከእስር ሲፈቱ አምስት ዓመት ሙሉ ሲሰጣቸው ያጠራቅሙት የነበረው ምግብ ትኩስ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ ያሳሰራቸውንም ንጉሥ ገና ሕፃን ሳለ እናቱ ልታስባርከው ወደ አባታችን ዘንድ ወስዳው ነበር፡፡ አቡነ ዘርዐ ቡሩክም ሕፃኑን ከባረኩት በኋላ ለእናቱ ‹‹ይህ ልጅሽ ወደፊት ይነግሣል በንግሥናው ዘመንም እኔን ያስርና ያንገላታኛል›› ብለው ይህ እንደሚሆን አስቀድመው ትንቢት ተናግረው ነበር፡፡ እንዳሉትም ልጁ አድጎ ሲነግሥ ጭፍሮቹ ‹‹ንጉሥ ሆይ አንተን የማይወድ ለቃልህም የማይታዘዝ አንድ መነኩሴ አለ›› በማለት ምንም እንኳን ንጉሡ ባያውቃቸውም በሐሰት ነገር ስለከሰሱለት በግዞት እንዲኖሩና እንዲታሰሩ አድርጓቸዋል፡፡ ጻድቁ በግዞት ሲወሰዱ ‹‹እነዚህን መጻሕፍቶቼን ለሰዎች አደራ ብሰጣቸው ይክዱኛል፣ ቤተ ክርስቲያን ባስቀምጣቸው ይጠፉብኛል›› በማለት ሰባት መጽሐፎቻቸውን ለግዮን (ለዓባይ) ወንዝ አደራ የሰጡ ሲሆን ከ5 ዓመት በኋላ ከእስር ተፈተው ሲመለሱ በወንዙ አጠገብ እንደደረሱ ጸሎት ካደረጉ በኋላ ‹‹ግዮን ሆይ በእግዚአብሔር ፊት በአደራ የሰጠሁሽን መጽሐፎቼን ግሺ (ትፊ)›› ብለው እጃቸውን ወደ ወንዙ ሰደው መጽሐፎቻቸው ሳይረጥቡና ሳይበሰብሱ ከወንዙ ውስጥ አውጥተዋቸል፡፡ እንዲያውም አቧራውን ከመጻሕፍቶቻቸው ላይ እፍ ብለው አራግፈውታል፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ እንደተጠቀሰው የጠለቀው ምሳር እየተንሳፈፈ ወደ ኤልሳዕ እንደመጣ ሁሉ አሁንም እንዲሁ የቅዱስ አባታችን መጽሐፎች አብሯቸው ከነበረውና ዘሩባቤል ከሚባለው ደቀ መዝሙራቸው ጋር ወዳሉበት ተንሳፈው ሊመጡ ችለዋል፡፡ መጽሐፎቻቸውንም አብሯቸው ለነበረው ደቀ መዝሙራቸው ካሳዩት በኋላ እንዲይዛቸው ሰጥተውታል፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

21 Jan, 08:40


የግዮን ወንዝ ‹‹ግሺ ዓባይ›› ወይም ‹‹ዓባይ›› እየተባለ መጠራት የጀመረው አቡነ ዘርዐ ቡሩክ ‹‹ግዮን ሆይ በእግዚአብሔር ፊት በአደራ የሰጠሁሽን መጽሐፎቼን ግሺ (ትፊ)›› ብለው እጃቸውን ወደ ወንዙ ሰደው መጽሐፎቻቸው ሳይረጥቡና ሳይበሰብሱ ከወንዙ ውስጥ ካወጡበት ጊዜ ጀምሮ ነው፡፡ አባታችን በቦታው ላይ 30 ዓመት ሙሉ ቆመው ጸልየው ቦታውን የባረኩት ሲሆን ጌታችንም በቦታው ላይ ትልቅ ቃልኪዳን ሰጥቷቸዋል፡፡ ‹‹ብፁዕ አባታችን ለግዮን ወንዝ መጽሐፎቹን በአደራ ሰጥተው በኋላም ከደቀ መዝሙራቸው ከዘሩባቤል ጋር መጽሐፎቹን ከግዮን ምንጭ ውስጥ ከተቀበለ በኋላ ‹በግዮን ውኃ ውስጥ ሳይረጥቡ በደረቅ መጽሐፎቼን የጠበቀ እግዚአብሔር ይመስገን› ብሎ ፈጣሪውን አመሰገነ፡፡ ‹ያንጊዜም በውስጥሽ ታላቅ ድኅነት ይደረግብሽ፣ ሕመምተኞች ሁሉ ይዳኑብሽ፣ መካኖች ይውለዱብሽ› ብሎ ግዮንን በቃሉ መረቃት፣ በእጁም ባረካት፡፡ ብፁዕ አባታችንም በዚህች ቦታ ላይ ፈውስ፣ ረድኤት፣ በረከት ይደረግብሽ ብሎ ብዙ ዘመን ቆሞ ጸለየ፡፡ እግዚአብሔርም ጸሎቱን ሰምቶ ‹ይህ በረከት፣ ረድኤት፣ ሀብት፣ ፈውስ እንደወደድህ እስከዘለዓለሙ በዚህ ቦታ ይሁንልህ› አለው›› ተብሎ ነው በቅዱስ ገድላቸው ላይ የተጻፈው፡፡
ጻድቁ አቡነ ዘርዐ ቡሩክ ሌላው የሚታወቁበት ‹‹ብሄሞትና ሌዋታን›› የተባሉ እጅግ ግዙፍ የሆኑ ሁለት ዘንዶዎችን ጥርሳቸውን ቆጥረው ምላሳቸው ሲጣበቅ የዓለም ፍጻሜ እንደሚሆን አስቀድመው ያወቁ ድንቅ ነቢይ የሆኑ አባት በመሆናቸው ነው፡፡ እነዚህም እጅግ ግዙፍ የሆኑ ሁለት እንስሳት ሴትና ወንድ ሆነው ምድርን እንደመቀነት ከበው የያዙ ናቸው፡፡ ዝርዝር ታሪካቸው በመጽሐፈ አክሲማሮስ (ሥነ ፍጥረትን በሚያስረዳው መጽሐፍ) ላይ በስፋት ተጠቅሰዋል፡፡ (ታሪካቸውንና ሚሥጢራቸውን ሌላ ጊዜ እናየዋለን)
አቡነ ዘርዐ ቡሩክ ሳይጠመቁ ለሚሞቱ አሕዛብም ጭምር ትልቅ ቃልኪዳን የተሰጣቸው ታላቅ አባት ናቸው፡፡ ይኸውም በቅዱስ ገድላቸው ላይ እንዲህ ተብሎ ተጽፏል- ‹‹በሥራው ሁሉ ፍጹም የሆነና ገድሉ ያማረ ቅዱስ አባታችንን በአድማስ ራስ ቆሞ ምሥራቁንና ምዕራቡን፣ ሰሜኑንና ደቡቡን እንዲባርክ በአፉ እስትንፋስም የምሕረት እስትንፋስን እፍ እንዲል እስትንፋሱንም ከአድማስ እስከ አድማስ ጽንፍ እስከ ጽንፍ ይደርስ ዘንድ እግዚአብሔር አዘዘው፡፡ በእግዚአብሔር በቅዱስ ስሙ ያልተጠመቁ አሕዛብ በእስትንፋሱ ምክንያት ልጅነት አግኝተው እንዲከብሩ በቃል ኪዳኑ ተማፅነው ሳይጠመቁ በሚሞቱበት ጊዜ ‹ይህ ከእኔ የተቀበልከው ቃልኪዳን ከጎኔና ከሰውነቴ እንደፈሰሰው ደሜ ይሁንላቸው› በማለት ለዓለም መድኃኒት አድርጎ ቃልኪዳን ሰጠው፡፡ ዳግመኛም በቅዱስ አባታችን ዘርዐ ቡሩክ ስም ከእግዚአብሔር ምሕረትን ለምነው በሚሞቱበት ጊዜ በውኃና በመንፈስ ቅዱስ እንደተጠመቁ ይሁንላቸው ብሎ ነገረው፡፡ በከበረና በገናና ስሙ የተጠመቁ ሕዝቡም በኃጢአታቸው በወደቁ ጊዜ በሥራቸውም በረከሱ ጊዜ በጻድቁ ጸሎት ቢማጸኑ በቃልኪዳኑ ቢያምኑ ይህ እስትንፋሱ የኃጢአት ማስተሠርያ ይሁናቸው ብሎታል፡፡ ጻድቁ አባታችንም የእግዚአብሔርን ትእዛዝ በሰማ ጊዜ ከዚያ በፊት ለሌሎች ያልተሰጠ ቃልኪዳን ተቀብሎ በአድማስ ላይ ቆመ፡፡ በዚያም ቆሞ መንፈሳዊ እስትንፋሱን በምድር ላይ እፍ አለ፡፡ ያም የሕይወት እስትንፋስ በአራቱ ማዕዘን ደርሶ በኃጢአታቸው መከራ የተቀበሉ ለበደላቸውም የተገዙ ሰዎች በፈጣሪያቸው ስም እንዲከብሩ ዓለሙን ሁሉ ባረከ›› ይላል ቅዱስ ገድላቸው፡፡ ይህም የሚያሳያየው መድኃዓለም ክርስቶስ የሰውን ልጆች ምን ያህል እንደወደዳቸውና በትንሽ ምክንያት የመዳንን መንገድ ያዘጋጀላቸው መሆኑን ነው፡፡
ሌላው አቡነ ዘርዐ ቡሩክ እሳቸው በባረኳት ምድርና በልጆቻቸው ላይ ችግርና ርኀብ እንደማይደርስባቸው ቃልኪዳን የተሰጣቸው ድንቅ አባት ናቸው፡፡ ይኸውም በቅርቡ እንኳን በ1977ቱ የርሃብ ዘመን በግልጽ ስለታየ ታሪክ ይመሰክረዋል፡፡ በዚህ ወቅት ከወሎና ከሌሎችም ቦታዎች በርሃብ ተሰዶ ጎጃም ለመጣው የሀገራችን ሕዝብ የአቡነ ዘርዐ ቡሩክ በረከት ከበቂ በላይ ነበር፡፡
ጻድቁ በጎጃም ባሕር ዳር አካባቢ ሁለት ቤተ ክርስቲያን አላቸው፡፡ የዓባይ ምንጭ መነሻ የሆነው ፈለገ ግዮን ግሽ ዓባይ ከባሕር ዳር ከተማ 174 ኪ.ሜ የሚርቅ ሲሆን ከባሕር ዳር ቲሊሊ፣ ከቲሊሊ ሠከላ በመሳፈር በቦታው ላይ ለብዙ ዘመን ቆመው በመጸለይ ታላቅ ቃልኪዳን የተቀበሉበትን እጅግ ተአምረኛና ፈዋሽ የሆነውን ጸበላቸውን ማግኘት ይቻላል፡፡ ቦታው መጽሐፋቸውን ለዓባይ ወንዝ አደራ የሰጡበት ነው፡፡ ሌላኛው ቤተ ክርስቲያናቸው ከባሕር ዳር የሁለት ሰዓት የመኪና መንገድ ርቀት ላይ በምትገኘውና አዴት በምትባለው ቦታ የሚገኘው ነው፡፡ የአቡነ ዘርዐ ቡሩክ መካነ መቃብራቸውና ከሰማይ የወረደላቸው መስቀል እዚህ ይገኛሉ፡፡ ቦታውን የረገጠ ሁሉ ከመካነ መቃብራቸው ላይ እምነት ይወስዳል፣ በመስቀሉም ይባረካል፡፡ ነገር ግን ጻድቁ በቃል ኪዳናቸው መሠረት በዚህ መስቀላቸው የተባረከ ሁሉ ዲቁናን፣ ክህነትን መቀበል ስለሚችል ሴቶች አይባረኩበትም፡፡ መካነ መቃብራቸው ቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ ከመቅደሱ ውጭ የሚገኝ ሲሆን ከመቃነ መቃብራቸው ላይ ያለው አፈር ሁልጊዜ እየፈላ መጠኑ ይጨምራል፡፡ ይህን የእምነቱን አፈር ቢዝቁት አያልቅም፣ ባዶ እንኳን ቢደረግ በተአምራት ሞልቶ ይገኛል፡፡ ለብዙ ሕመምተኞች ፍጹም ፈውስ የሆነው ይህ እምነት አጠቃላይ ሁኔታው ለዕይታ አመቺ ስለሆነ ይህንን ማንኛውም ሰው ወንዶችም ሆኑ ሴቶች ማየትና እምነቱን ወስደው መጠቀም ይችላሉ፡፡
ጻድቁ አባታችን በ482 ዓመታቸው በዚህች ዕለት ጥር 13 ቀን በታላቅ ክብር ያረፉበት በዓላቸው በድምቀት ይከበራል፡፡ በዕረፍታቸው ዕለት ከቤተ ክርስቲያኑ አደባባይ ላይ አትሮንስ ወጥቶ ገድላቸው ይነበባል፡፡ ገድላቸው ሲነበብም ከአትሮንሱ ሥር ሰባት ጠርሙሶችና አንድ ማሰሮ ይቀመጥና በጠርሙሶቹ ውስጥ አንድ አንድ ስኒ ውኃ ይደረግባቸዋል፡፡ የአባታችን ቅዱስ ገድላቸው ሲነበብ ውኃው ይፈላል፣ ገድሉ ተነቦ እንዳለቀ ጠርሙሶቹና ማሰሮው በተአምራት ተሞልተው ይገኛሉ፡፡
ጌታችን ለአቡነ ዘርዐ ቡሩክ ትንባሆን ስለሚጠጡ ሰዎች ታላቅ ምሥጢርን እንደነገራቸው በቅዱስ ገድላቸው ላይ ተጽፏል፡፡ ቅዱስ አባታችን በየቀኑ ለሰባት ሰዓት ያህል በሲኦል ውስጥ ቆመው በመጸለይ ብዙ ነፍሳትን ከእሳት ያወጡ ነበር፡፡ አንድ ቀን ብዙ ነፍሳትን ካወጡ በኋላ አንዲት ነፍስ ግን ከሲኦል ግደግዳ ጋር እንደ ሰም ተጣብቃ እምቢ አለቻቸው፡፡ አባታችንም ያቺን ነፍስ አወጣለሁ ሲሉ ቆመው ይጸልዩበት የነበረው የሲኦል እሳት አሁን ያችን ነፍስ አወጣላሁ ባሉ ሰዓት ግን አቃጠላቸው፡፡ እሳቸውም ያችን ነፍስ እዚያው ሲኦል ጥለው በመውጣት ጌታችንን ‹‹የዚያች ነፍስ ኃጢአቷ ምንድን ነው?›› አሉት፡፡ የዚህን ጊዜ ነው ጌታችን ትንባሆን ስለሚጠጡ ሰዎች ታላቅ ምሥጢርን የነገራቸው፡፡ ይኸውም አባ ሐዊ የሚባሉ ጻድቅ ያስተላለፉትን ውግዘትና ግዝት የጸና እንደሆነ ነው ጌታችን ለአቡነ ዘርዐ ቡሩክ የነገራቸው፡፡ ዝርዝር ታሪኩም በድርሳነ መድኃዓለም ላይ እንዲህ ተጽፎ ይገኛል፡-

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

21 Jan, 08:40


ትንባሆ የሚጠጡ ሰዎች ለምን ለማቆም እንደሚቸገሩና መጨረሻቸውም ምን እንደሆነ፡- ‹‹ይቅርታውና ምሕረቱ ከሁላችን የጥምቀት ልጆች ጋር ይሁንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መድኃኔዓለም ያደረገው ተአምር ይህ ነው፡- አባታችን ዘርዓ ቡሩክ መድኃኔዓለምን እንደወደደውና በየወሩ በሃያ ሰባት ቀን በዓሉን እንደሚያከብር በአሥራ ስድስት ቀንም ኪዳነ ምሕረትን እንደሚያከብር እነሆ እንነግራችኋለን፡፡ ባለሟልነትን ባገኘ ጊዜና መድኃኔዓለም የእሳት ፈረስንና የመስቀል ምልክት ያለበት የወርቅ በትርን በሰጠው ጊዜ ‹ወደ ሲዖል ሂድና መሸከም የምትችለውን ያህል ነፍሳትን አውጣ› አለው፡፡ ሄዶም ወደ ሲዖል ገባ፣ ነፍስ በነፍስ ላይ እንደ ንብ እየተጨናነቁ በሰውነቱ ላይ ታዘሉ፡፡ ነፍሳትንም ይዞ ሲወጣ አንድ ኃጢአተኛ ‹ዘርዓ ቡሩክ ብቻዬን ቀረሁ፣ አውጣኝ› አለው፡፡ ዘርዓ ቡሩክም ወደ እርሱ ተመልሶ ሳበው፡፡ ሰም ከፈትል ጋራ እንደሚጣበቅ ከሲዖል ጥልቅ ጋራ ተጣብቆ እምቢ አለው፡፡ የእሳቱ ነበልባልም ዘርዓ ቡሩክን አቃጠለው፣ እርሱም ተወው፡፡ ክብር ይግባውና እነዚያን ነፍሳት ይዞ ወደ ጌታው ወደ መድኃኔዓለም ሄደ፡፡
ሄዶም ‹ጌታዬ ሆይ! አንዲት ነፍስ ስሜን እየጠራች ቀርታለች ማርልኝ› አለው፡፡ መድኃኔዓለምም ‹ዘርዓ ቡሩክ ሆይ! በእኔ ዘንድ ባለሟልነትን ብታገኝ ትንባሆ የሚጠጣውን ማርልኝ ትለኛለህን?› አለው፡፡ እርሱም ‹ጌታዬ ሆይ! ይህቺ እንጨት በምን ትከፋለች?፣ ከሁሉ ኃጢአትስ በምን ትበልጣለች?› አለው፡፡ ወይቤሎ መድኅን ኢሰማዕከኑ ግብራ ለዛቲ ዕፅ ዘከመ ዘርዓ ሰይጣን ውስተ ገራህተ ዓለም፡፡ መድኃኔዓለምም ‹የዚህችን እንጨት ሥራ በዓለም እርሻ ሰይጣን እንደዘራት አልሰማህምን?› አለው፡፡ እነሆም እንነግራችኋለን፣ ስሙ ሐዊ የሚባል የፈጣሪውንም ሕግ የሚጠብቅ አንድ መምህር ነበረ፡፡ በዓርብ ቀንም ወደ ሰማይ ይሔዳል፤ በቀዳሚት ሰንበትና በእሑድ ከፈጣሪው ጋር ይነጋገራል፡፡ በሰኞ ቀንም ወደ ቦታው ይመለሳል፡፡ ለሀገር ሰዎችም በጉባኤ ይነግራቸዋል፣ በአዋጅ ነጋሪ ቃልም ይሰበሰባሉ፡፡ ይህቺ ሀገር ትልቅ ናትና እስከ ዓርብም ያስተምራቸዋል፡፡ በዚያን ጊዜ ሰይጣን ቀና፡፡ አባ ሐዊም እንደልማዱ በዕለተ ዓርብ ወደ ሰማይ በሄደ ጊዜ ያ ሰይጣን በመቀመጫው ተቀምጦ በእርሱ በሐዊ ተመስሎ በቀዳሚት ሰንበት ቀንም ተገልጦ ‹ፈጣሪያችን የሚወዳትን ነገር እነግራችሁ ዘንድ ሁላችሁም ተሰብሰቡ› አለ፡፡ ሁላቸውም ተሰበሰቡ፡፡ ‹አባት ሆይ! ያለ ልማድህ ዛሬ ለምን መጣህና ጠራኸን?› አሉት፡፡ ያ ጠላት ዲያብሎስም ‹ጌታዬ ለሕዝቦቼ የዚያችን በቤትህ አንፃር ያለችውን እንጨት ቅጠል በጥርሳቸው ይጨምሩ ዘንድ፣ በአፋቸውም ያጤሱ ዘንድ ዛሬ ካልነገርሃቸው ወዳጄ አይደለህም አለኝ› አላቸው፡፡ ይህችንም እንጨት ባያት ጊዜ እንዲህ አደረገ፣ ሔዋንን በእንጨት እንዳሳታት አሳታቸው፡፡ ዛሬ እንደሚያደርጉትም የጥንባሆ ዕቃን አደረጉ፡፡ ቅጠሏንም አምጥተው ቀጥቅጠው በእሳት አጢሰው ትንሹም ትልቁም፣ የከበረውም የጎሰቆለውም ሁላቸውም ጠጡ፡፡
ሐዊም በሰማይ ሳለ በጸጋ አውቆ አዘነ፣ ነገር ግን ስለ ሰንበታት ክብር ብሎ አደረ፡፡ ሰኞ በነግህም ሐዊ መጣ፣ ሰይጣንም እንደ ጢስ በኖ ጠፋ፡፡ እርሱም ሰዎቹን ሰብስቦ ‹ይህን ማን አስተማራችሁ?› አላቸው፡፡ ‹አንተ ነህ› አሉት፡፡ ‹ሰይጣን ነው እንጂ እኔ አይደለሁም፣ ከዛሬ ጀምሮ ተው› አላቸው፡፡ ‹ትናንት ጠጡ፣ ዛሬ ተው› ይለናል ብለው እምቢ አሉት፡፡ እርሱም አወገዛቸው፡፡ ‹በእርሻው የዘራት፣ በአፉም የጠጣት፣ በእጁም የያዛት የተረገመ ይሁን› አላቸው፡፡ ጋኔኑም በቅሉ ውስጥ ሆኖ ይነጋገራል፣ በውጭ ያሉትንም አጋንንት ይጠራቸዋል፡፡ በዚህን ሰዓት የተውም አሉ፣ እምቢም ያሉ አሉ፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ያቺ እንጨት ተረገመች፡፡ ሰውም በጠጣት ጊዜ የአምስት ቀፎ ሙሉ ንቦችን የሚያህሉ አጋንንት ይመጣሉ፡፡ በሁለቱ ዓይኖቹ ውስጥ፣ በሁለቱ አፍንጫዎቹም፣ በሁለቱ ጆሮዎቹም፣ በአፉም፣ በታች በሰገራ መውጫም በእነዚህ ሁሉ እንደ ቀፎ ንብ ይገባሉ፣ ይወጣሉ፡፡ ትምክህትን፣ ትዕቢትን፣ መግደልን፣ ሥርቆትንም፣ ክፉውንም ሁሉ ይመሉታል፡፡ ወሶበ ይሰትያ ብእሲ ይመጽኡ አጋንንት ዘየአክሉ መጠነ ፭ቱ ቀፈዋት ዘመልኡ አንህብት ወይበውኡ ውስቴቱ፡፡ በ፪ አዕይንቲሁ፣ ወበ፪ አዕናፊሁ፣ ወበ፪ አዕዛኒሁ ወበመንፈሱ ዘታህት በአፉሁ በዝንቱ ኵሉ ከመ ንህብ ዘቀፎ ይበውኡ ወይወጽኡ፡፡ ወይመልእዎ ትምክህተ፣ ወትዕቢተ፣ ቀትለ፣ ወሠሪቀ ወኵሎ ዕከያተ እንዲል መጽሐፍ፡፡ አባታችን ዘርዓ ቡሩክም ይህን ሰምቶ እጆቹን በትከሻው አመሳቅሎ አለቀሰ፣ በሥዕሉም አለ፣ በዚያን ጊዜ ወደ ዓለም ወጣ፡፡ ይህችን የተረገመች እንጨት እንዲህ ብሎ አወገዛት፡- ‹በአፉ የጠጣት፣ በእጁም የያዛት፣ የዘራት፣ የሸጣት፣ የገዛትም የጥምቀት ልጅ አይደለም፤ በሥጋው አይጠቀምም፣ ነፍሱም ወደ ሲዖል ትወርዳለች፡፡ ልጄ የሆነ ግን መድኃኔዓለምንና ኪዳነ ምሕረትን ያክብር፡፡ ጥንባሆንም አይጠጣ› አለ፡፡ የዚህ ጻዲቅ በረከቱ ያልታዘዝንውን ከመብላት ይጠብቀን አሜን›› በማለት ተአምረ መድኃኔዓለም ወገድለ መባዓ ጽዮን ነገረ ጥንባሆን በሰፊው ዘግቦታል፡፡ በሌላም በኩል ትንባሆን በተመለከተ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ለአቡነ ዘርዐ ቡሩክ የሰጣቸው ቃልኪዳን በራሳቸው በዘርዐ ቡሩክ ገድል ላይ የተጻፈውን ወደፊት እናያለን፡፡ እንዲሁም ይህችን የተረገመች ዕፅ የሚጠቀሙባት ሁሉ የሰይጣን ማደሪያዎች እንደሚሆኑና ክፉውንም ሁሉ እንደሚያሠሩት በሌላም ቦታ በአቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ገድል ላይ በሰፊው ተጽፏል፡፡
ማስታወሻ፡- ከላይ እንደተጠቀሰው ሰይጣን የዕፅዋን ዘር በዓለም ወስዶ በመዝራት እርሷን በተለያየ መንገድ የሚጠቀሙባት ሁሉ ርጉማን እንዲሆኑ አድርጓል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ አንድ መታወቅ ያለበት ነገር አለ፡፡ የሥነ ፍጥረት አስገኚው ልዑል እግዚአብሔር ብቻ ነው፡፡ ከተፈጠሩት 22 ፍጥረታት ውስጥ ለክፉ ተግባር የተፈጠረ ፍጥረት ፈጽሞ የለም፡፡ ፍጥረታትም ከተፈጠሩበት ዓላማ አንጻር ሊኖርም አይችልም፡፡ የሰው ልጅ ለአምላኩ ሕግ የመገዛቱና የመታዘዙ ውጤት የሚያስገኝለት በረከትና የሚያመጣበት መርገም እንዳለ እርግጥ ነው፡፡ እናም የሰው ልጅ የፈጣሪውን ሕግ ስለሻረ በደረሰበት መርገም ምክንያት ባሕርይው ጎስቁሎ በነፍስም በሥጋም ሞት የተፈረደበት ሆኖ ወደ ምድር መጣ፣ ትውልዱም ምድርን በኃጢአቱ አረከሳት፡፡ ነገር ግን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሞቱ ሞትን አጥፍቶ የጎሰቆለውን የሰውን ልጅ ባሕርይ አድሶ፣ የቀደመ ክብሩን መልሶለት፣ የረከሰችውን ምድር በወርቀ ደሙ ቀድሶ፣ ጽድቅንና ተድላን በሰማይና በምድር ፈጽሟል፡፡ ስለዚህ ሲጀመር ሃያ ሁለቱም ፍጥረታት ከተፈጠሩበት ዓላማ አንጻር ምንም ለክፋት ተብሎ የተፈጠረ ፍጥረት የለም፡፡ ሲቀጥል በሰው ልጆች ኃጢአት ያደፈችው ዓለምም በክርስቶስ ደም ነፅታለች፡፡ ነገር ግን የሰው ልጅ ፍጥረታትን በተለይም ዕፅዋትን የሚጠቀምበት መንገድና ሁኔታ መጥፎም ጥሩም ሆኗል፡፡ ለምሳሌ ቃልቻዎችና ክፉ ደብተራዎች ኅብረታቸውን ከአጋንንት ጋር አድርገው ሥር ምሰው ቅጠል በጥሰው የተለያዩ የሟርት፣ የጥንቆላና የክፋት ሥራዎችን ሁሉ ይሠራሉ፡፡ ስለዚህ አሁን የሰው ልጅ ፍጥታትን (ዕፅዋትን) ለመጥፎ እንደተጠቀመበት ሁሉ ቀድሞውንም ሰይጣን ኃጢአት የሆነውን ክፉውን ሥራ ሁሉ ለማሠራት ሲል በገድላቱ ላይ እንደተጠቀሰው ያችን የዕፅ ዘር በዓለም ሁሉ ወስዶ መዝራቱን በቀላሉ መገንዘብ እንችላለን፡፡ በእርግጥ በጠንቋዮችም ላይ አድሮ የሚሠራ እርሱ ነው፡፡ ጥንተ ጠላት ሰይጣን ሔዋን እናታችንን አዳም

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

21 Jan, 08:40


እንዳረፈ መጻተኞችና ደገኞች አባቶች ነገሯቸው፡፡ የአባ ነካሮ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!
(ምንጭ፡- ገድለ አቡነ ዘርዐ ቡሩክ፣ በድርሳነ መድኃኔዓለምና በገድለ መብዐ ጽዮን፣ ገድለ አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን፣ ከገድላት አንበት መጽሐፍ)

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

21 Jan, 08:40


አባታችንን በዕፅ አስቶ ሞት እንዳመጣባቸው ሁሉ አሁንም በዘመናችን በዚያች አባቶቻችን ባወገዟት ዕፅ አማካኝነት ሰይጣን ትውልዱን ወደ ሲኦል እያጋዘው ይገኛል፡፡
ያቺን ሰይጣን በዓለም ሁሉ ወስዶ የዘራትን ዕፅ በተለያየ መንገድ (ማለትም በሐሺሽ በጫት በሲጋራ) የሚጠቀሙ ሰዎች ኃጢአታቸው የክርስቶስን ክቡር ሥጋና ደም፣ ቅድስት ድንግል ማርያምን እንዲሁም ቅዱስ መስቀሉን ከካዱ ሰዎች ጋር የሚስተካከል እንደሆነ በገድለ ዘርዐ ቡሩክ የተጠቀሰውን ማየት ተገቢ ነው፡፡ ‹‹ዳግመኛም እግዚአብሔር ዘርዐ ቡሩክን እንዲህ አለው፡- ‹ብዙ ኃጢአት ከሠሩ ከክርስቲያንም ወገን ቢሆኑ፣ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ያልተጠመቁ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ከድንግል ማርያም የተወለደ የክርስቶስን ሥጋና ደም ካልተቀበሉ ከአረማውያንም ወገን ቢሆኑ ንስሓ ገብተው በጸሎት ቢማፀኑ በቃልኪዳንህም ቢያምኑ ከገሃነመ እሳትና ከሁለተኛ ሞት ይድናሉ› ብሎ ቃልኪዳንና ጽኑ መሐላ ሰጠው፡፡ ‹እኔን ከካዱ የባሕርይ አባቴ አብን የባሕርይ ሕይወቴ መንፈስ ቅዱስን ከካዱ ሰዎች በቀር፣ እናቴንና መስቀሌን፣ ሥጋዬንና ደሜን ከካዱ ሰዎች በቀር፣ ስሙ ትንባሆ የሚባል የተረገመ ቅጠልን ከጠጡ ሰዎች በቀር ንስሓ ገብተው በጸሎትህ ቢማፀኑ ከዘለዓለም እሳትና ከሁለተኛ ሞት አድናቸዋለሁ› አለው›› ተብሎ ነው የተጻፈው፡፡
አቡነ ዘርዐ ቡሩክም ጌታችን ያንን የትንባሆን ምሥጢር ከነገራቸው በኋላ እንዲህ አሉት፡- ‹‹አቤቱ ፈጣሪዬ ሆይ ለእኔ የነገርኸኝን ይህን ቃል ሳይሰሙ የዋሐን ሰዎች ይህን ቅጠል (ትንባሆ) ቢጠጡ ፈጣሪዬ ሆይ ያንተ ቃል ከሚሆን ከእኔ ቃል ከሰሙ በኋላ ቃልህን እንዳቃለሉ ሰዎች ይጠፋሉን?›› አለው፡፡ ፈጣሪውም የወዳጁ ብፁዕ አባታችን ዘርዐ ቡሩክን ነገር ሰምቶ ‹‹ሳያውቁ የጠጡትን ምሬልሃለሁ፣ ባለማወቅም ስላደረጉት ኃጢአታቸውንም ይቅር ብዬአቸዋለሁ›› አለው፡፡ ቅዱስ አባታችን ዘርዐ ቡሩክም ይህን ቃል ከፈጣሪው አንደበት ሰምቶ በዚህ በተረገመ ቅጠል (ትንባሆ) መቅሰፍተ ነፍስ የዘለዓለም ቅጣት እንዳለ ሳያውቁ ያን የተረገመ ቅጠል በጠጡ ሰዎች ላይ ስለተደረገው ምህረት እጅግ ደስ አለው፡፡ ዳግመኛም እግዚአብሔር ቅዱስ ዘርዐ ቡሩክን እንዲህ አለው፡- ‹‹ከአንተ አስቀድመው ለነበሩ ሰዎች ያልገለጥሁትን ለአንተ ግን የነገርኩህንና የገለጥኩልህን ነገር ከአንተ የሰማውን ነገር ንቆ ሞት የሚያመጣ የተረገመ ቅጠልን ከዛሬ ጀምሮ የጠጣውን ታላቅ በቀልን እበቀለዋለሁ፤ መንጸፈ ደይንም አወርደዋለሁ፤ በይቅርታዬና በቸርነቴም ወደ እርሱ አልመለስም›› አለው፡፡ ከጥበበኞች የተደበቀ፣ ከአዋቂዎችም የተሰወረ ይህን ስውር ምሥጢር ለወዳጁ ለብፁዕ አባታችን ዘርዐ ቡሩክ የገለጠለት ልዑል እግዚአብሔር የተመሰገ ይሁን፡፡ ዳግመኛም እግዚአብሔር እንዲህ አለው፡- ‹‹ብዙ ኃጢአት ከሠሩ ከክርስቲያንም ወገን ቢሆኑ፣ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ያልተጠመቁ፣ ከሰማየ ሰማያት ወርጄ ከድንግል ማርያም የተወለድኩ የእኔን ሥጋዬንና ደሜን ካልተቀበሉ ከአረማውያንም ወገን ቢሆኑ ንስሓ ገብተው በጸሎት ቢማፀኑ በቃልኪዳንህም ቢያምኑ ከገሃነመ እሳትና ከሁለተኛ ሞት ይድናሉ›› ብሎ ቃልኪዳንና ጽኑ መሐላ ሰጠው፡፡ ‹‹እኔን ከካዱ የባሕርይ አባቴ አብን የባሕርይ ሕይወቴ መንፈስ ቅዱስን ከካዱ ሰዎች በቀር፣ እናቴንና መስቀሌን፣ ሥጋዬንና ደሜን ከካዱ ሰዎች በቀር፣ ስሙ ትንባሆ የሚባል የተረገመ ቅጠልን ከጠጡ ሰዎች በቀር ንስሓ ገብተው በጸሎትህ ቢማፀኑ ከዘለዓለም እሳትና ከሁለተኛ ሞት አድናቸዋለሁ›› አለው፡፡
አደንዛዥ ዕፅንና ሱስን በተመለከተ በአሁኑ ሰዓት ዓለም ላይ ያለውን ችግር ሁሉም ሰው በደንብ ያውቃዋል፡፡ በቅዱሳት ገድላቱም ላይ (ማለትም በገድለ መባዓ ጽዮን፣ በገድለ ዘርዐ ቡሩክና በአባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ገድል) ላይ የተጻፈው ነገር አሁን ዓለም ላይ ያለውን ችግር ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ በመልእክቱ ‹‹ከእግዚአብሔር እንደሆንን ዓለምም በመላው በክፉው እንደተያዘ እናውቃለን›› በማለት እንደተናገረው ሱስ የሰይጣን ስውር የክፋት ሥራ መሆኑን በቀላሉ መረዳት እንችላለን፡፡ 1ኛ ዮሐ 5፡19፡፡ በቀላሉ ሱስ ውስጥ የገቡ ሰዎች ለምን ሱሱን ማቆም እንደሚቸገሩ፣ መጀመሪያውንም በቀላሉም ወደ ሱሱ እንዴትና ለምን እንደሚገቡ፣ ሱስ የሚጠቀሙ ሰዎችም የተለያዩ ወንጀሎችን ለምን እንደሚፈጽሙ…. እነዚህ ሁሉ የሰይጣን ሥራዎች በእኛ ዘንድ የተገለጡ ናቸው፡፡ ‹‹…ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ያቺ እንጨት ተረገመች፡፡ ሰውም በጠጣት ጊዜ የአምስት ቀፎ ሙሉ ንቦችን የሚያህሉ አጋንንት ይመጣሉ፡፡ በሁለቱ ዓይኖቹ ውስጥ፣ በሁለቱ አፍንጫዎቹም፣ በሁለቱ ጆሮዎቹም፣ በአፉም፣ በታች በሰገራ መውጫም በእነዚህ ሁሉ እንደ ቀፎ ንብ ይገባሉ፣ ይወጣሉ፡፡ ትምክህት፣ ትዕቢትን፣ መግደልን፣ ስርቆትንም፣ ክፉውንም ሁሉ ይመሉታል…›› ተብሎ ነው በገድለ መባዓ ጽዮን ላይ የተጻፈው፡፡ ይህ እጅግ አስፈሪ ነው በእውነት!
ዓለም በመላ ስለ ገድልና ድርሳን ሲነገረው አይዋጥለትም፣ እንዲያውም ‹ተረት ነው› ይለዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት በዓለም ላይ ካለው ነባራዊ ሁኔታ ስንነሣ ጥናቶች እንደሚያሳዩትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አንዱ ክፍል (UNODC-united nation’s office on Drug and crime) በጥናቱ ይፋ እንዳደረገው በየዓመቱ 200,00 (ሁለት መቶ ሺህ) ሰዎች አደንዛዥ ዕፅን መጠቀማቸውን ተከትሎ ለሞት ይዳረጋሉ፡፡ በአሜሪካን አገር ብቻ በየቀኑ ከ95 በላይ ሰዎች በአደንዛዥ ዕፅ ምክንያት ይሞታሉ፡፡ አደንዛዥ ዕፅን በክትባት መልክ (injection) ከሚወስዱት ውስጥ አብዛኛዎቹ በደማቸው ውስጥ የHIV ቫይረስ ይገኛል፡፡ በአሜሪካን አገር በአደንዛዥ ዕፅ ምክንያት የሞቱት ሰዎች ቁጥር በመኪና አደጋ እና በድንገተኛ እሳት አደጋ ምክንያት ከሞቱት ሰዎች ቁጥር በ10% ብልጫ አለው፡፡ አደንዛዥ ዕፅንና ሱስን በተመለከተ ዓለም መፍትሄ አጥታ ትባዝናለች፡፡ ችግሩ በዓለም ላይ ይህን ያህል የገዘፈውንና ብዙ ቀውሶችን እያስከተለ ያለውን የጥንባሆን (የአደንዛዥ ዕፅን) ጉዳይ አባቶቻችን እነ አቡነ ዘርዐ ቡሩክ ምሥጢሩን አግኝተውታል፡፡ ሚሥጢሩንም ከፈጣሪ አግኝተው ከተረዱ በኃላ ጤናን የሚጎዳ ከመሆኑም በላይ ለዘለዓለም የነፍስን ቅጣት እንደሚያስከትል አደንዛዥ ዕፁም ከሰይጣን እንደተገኘ በግልጽ ነግረውናል፡፡ ጻድቁ አቡነ ዘርዐ ቡሩክ ጥንባሆን ስለሚጠጡ (አደንዛዥ ዕፅን ስለሚጠቀሙ) ሰዎች ታላቅ ምሥጢርን ከጌታችን የተነገራቸው ናቸው፡፡
ገድላቱ እንደሚናገሩት እኔም ከላይ እንደጠቀስኩት ሰይጣን ያችን እነ አባ ሐዊና እነ አቡነ ዘርዐ ቡሩክ ያወገዟትን ዕፅ በተለያየ መንገድ በዓለም ዘርቷት ሰዎችም በተለያየ መንገድ ይጠቀሙባታል፡፡ ኮኬይን ይሁን ሄሮይን፣ ጫት ይሁን ሲጋራ፣ መልኳና ዓይነቷ ይለያይ እንጂ አንደዛዥ ዕፁዋን ሰይጣን ሰዎችን ለማሳት ተጠቅሞባታል፡፡ በቀላሉ ሱስ ውስጥ የገቡ ሰዎች ለምን ሱሱን ማቆም ይቸገራሉ? መጀመሪያውንም በቀላሉም ወደ ሱሱ እንዴትና ለምን ገቡ? ሱስ የሚጠቀሙ ሰዎችም የተለያዩ አስከፊ ወንጀሎችን ለምን ይፈጽማሉ? ….

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

21 Jan, 08:40


እነዚህ ሁሉ የሰይጣን ሥራዎች በቅዱሳን አባቶቻችን ዘንድ የተገለጡ ናቸው፡፡ ‹‹…ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ያቺ እንጨት ተረገመች፡፡ ሰውም በጠጣት ጊዜ የአምስት ቀፎ ሙሉ ንቦችን የሚያህሉ አጋንንት ይመጣሉ፡፡ በሁለቱ ዓይኖቹ ውስጥ፣ በሁለቱ አፍንጫዎቹም፣ በሁለቱ ጆሮዎቹም፣ በአፉም፣ በታች በሰገራ መውጫም በእነዚህ ሁሉ እንደ ቀፎ ንብ ይገባሉ፣ ይወጣሉ፡፡ ትምክህት፣ ትዕቢትን፣ መግደልን፣ ስርቆትንም፣ ክፉውንም ሁሉ ይመሉታል…››
መፍትሄ፡-
+++ ‹‹ሰው ለተሸነፈበለት ለእርሱ ባሪያ ነው›› (2ኛ ጴጥ 2፡19)፤ ‹‹ኃጢአትን የሚያደርግ ከዲያብሎስ ነው፤ ዲያብሎስ ከመጀመሪያ ኃጢአትን ያደርጋልና፡፡ ስለዚህ የዲያብስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ›› (1ኛ ዮሐ 3፡8)፤ ‹‹ሰውነታችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተመቅደስ እንደሆነ አታውቁምን? በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ (1ኛ ቆሮ 6፡19)፣ ‹‹የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደሆናችሁ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንዲኖርባችሁ አታውቁምን? ማንም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል፤ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ ነውና፥ ያውም እናንተ ናችሁ›› (1ኛቆሮ 3፡17)
አምላከ ቅዱሳን መድኀኔዓለም ክርስቶስ ከአቡነ ዘርዐ ቡሩክ ረድኤት በረከት ይክፈለን!
+++
+ ዳግመኛም በዚኽች ዕለት ጤና አግኝተው እንዳይተኙ ከምንጣፋቸው በታች እሾህ ይጎዘጉዙ የነበሩት ጻድቅ አባ ነካሮ ዕረፍታቸው ነው፡፡
+ በዳኬዎስ ዘመን 372 ዓመት በሞት አንቀላፍተው የነቁትና ስለትንሣኤ ሙታን የመሰከሩት ሰባቱ ደቂቅ የዕረፍታቸው መታሰቢያ ነው፡፡ እነዚህም ሰባት ቅዱሳን በከሃዲው ንጉሥ በዳኬዎስ ዘመን በሞት ካንቀላፉ ከ372 ዓመት በኋላ ተነሥተው ‹ትንሣኤ ሙታን የለም› ለሚሉ ከሃድያን ምስክር የሆኑ ናቸው፡፡ እነርሱም ስማቸው አርሰሌዳስ፣ ዱአሚዶስ፣ አውጋንዮስ፣ ድሜጥሮስ፣ ብርጥስ፣ እስጢፋኖስ፣ ኪራኮስ ይባላሉ፡፡ እነዚህም ሰባት ቅዱሳን ሃይማኖታቸው የቀና የታላላቅ ሀገር ሰዎች ልጆች ናቸው፡፡ እነርሱም ምግባር ሃይማኖታቸው የሰመረ፣ ትሩፋት ተጋድሎአቸው ያማረ ነው፡፡ እጅግ ክፉ የነበረው ከሃዲው ንጉሥ ዳኬዎስ ጌታችንን ክዶ ጣዖትን ማመለክና የክርስቲያኖችን ደም እንደ ውኃ ማፍሰስ በጀመረ ጊዜ እነዚህ ሰባት ቅዱሳን መስተጋድላን ስለ ሃይማኖታቸው መስክረው ሰማዕት ይሆኑ ዘንድ በምክር ተስማሙ፡፡ ወደ ንጉሡም ዘንድ በቀረቡ ጊዜ ለጣዖት እንዲሰግዱ ግድ አላቸው፣ እነርሱ ግን የጌታችንን አምላክነት በመመስከር የንጉሡን አማልክት ረገሙት፡፡ ንጉሥ ዳኬዎስም ከልባቸው ጋር ይመክሩ ዘንድ ትንሽ ጊዜ ሰጣቸውና ወደ ተግባሩ ሄደ፡፡
እነዚህም የተባረኩ ሰባት ቅዱሳን ወደቤታቸው በመሄድ ገንዘባቸውንና ያላቸውን ሁሉ ለድኆችና ለጦም አዳሪዎች ሰጡ፡፡ የቀረውንም ለስንቃቸው ይዘው ከከተማው በስተ ምስራቅ በአንድ ዋሻ ውስጥ ተሠወሩ፡፡ ብልህና አስተዋይ ዱአሚዶስ የተባለ አንድ ወጣት ወደ ከተማ እየሄደ ምግባቸውን በመግዛት የሚያገለግላቸው ሆነ፡፡ በከተማውም የሰማውን ነገር ሁሉ ይነግራቸዋል፡፡ ንጉሥ ዳኬዎስም ከሄደበት በተመለሰ ጊዜ እነዚህን ሰባት ቅዱሳን ፈለጋቸው፡፡ በዋሻ ውስጥ ተሸሽገው እንዳሉ ሲሰማ የዋሻውን መግቢያ አፉን በታላቅ ድንጋይ እንዲዘጉት አዘዘ፡፡ የቅዱሳኑንም ነፍሳቸውን በተኙ ጊዜ ጌታችን ወሰደ፡፡ 372 ዓመትም እንዲያንቀላፉ አደረጋቸው፡፡ ከንጉሡ አሽከሮች ውስጥ ቴዎድሮስና መቅዶስዮስ የተባሉት የእርሳስ ሰሌዳ ወስደው የእነዚህን ቅዱሳን ዜናቸውንና የዘመኑን ቁጥር ጽፈው ቀርጸው ከዋሻው አፍ አኖሩት፡፡

ከዚህም በኋላ ንጉስ ዳኬዎስ ሞተና እስከ ደጉ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ ዘመነ መንግሥት ድረስ ብዙ ነገሥታት ነገሡ፡፡ በዚህም ደግ ንጉሥ ዘመን ‹‹ትንሣኤ ሙታን የለም›› የሚሉ መናፍቃን ተነሡ፡፡ እነዚህ ሰባት ቅዱሳን ከሞት የሚነቁበት ጊዜ እንደደረሰ አንዱ መኮንን ለበጎች ማደሪያ ሊያሠራ ፈልጎ ድንጋይ እየፈለገ ሳለ የዋሻውን በር ከፈተው፡፡ ቅዱሳኑም ከ372 ዓመት በኋላ ከሞት በነቁ ጊዜ ምግባቸውን ይገዛላቸው ዘንድ ዱአሚዶስን ወደ ገበያ ላኩት፡፡ ዱአሚዶስም ሊገዛ ወደ ገበያ እንደሄደ የአገሩ ሰዎች የንጉሥ ዳኬዎስ ስም የተጻፈበትን ዲናር በእጁ ይዞ ቢያዩት የተሸሸገ የወርቅ ሣጥን ያገኘ መሰላቸውና ወስደው ወደ ዳኞችና ኤጲስቆጶሳት አቀረቡት፡፡ ዱአሚዶስንም በመረመሩት ጊዜ ሌሎችም ወንድሞቹ በዋሻው ውስጥ መኖራቸውን ነገራቸው፡፡ እነርሱም የቀሩትንና በዋሻ ያሉትን ለማየት ተያይዘው ወደ ዋሻው ቢሄዱ ቀሪዎቹን ስድስቱን ቆመው ሲጸልዩና ፊታቸውም እንደጸሐይ ሲያበራ አገኟቸው፡፡ ኤጲስቆጶሱም የእርሳሱን ሰሌዳ አየውና አንሥቶ ሲያነበው የቅዱሳኑን ገድላቸውንና የዘመኑን ቁጥር ባነበበ ጊዜ በንጉሥ ዳኬዎስ ዘመን እንዳንቀላፉ ለሕዝቡ ጮሆ ነገራቸው፡፡ ሁሉም እጅግ አድንቀው ምስጉን የሆነ እግዚአብሔርን አመሰገኑት፡፡ ወደ ደገኛው ንጉሥ ቴዎዶስዮስም መልአክት ላኩበትና ንጉሡ መጥቶ ቅዱሳኑን እጅ ነሣቸው፡፡ ቅዱሳኑም ንጉሡንና ሠራዊቱንም ሁሉ ባረኳቸው፡፡ እነዚህም ሰባት ቅዱሳን ወደ ኤፌሶን ከተማ ወጥተው ለሰባት ቀናት ያህል ሕዝቡን ሲያስተምሩ ቆዩ፡፡ በወቅቱም ተነሥተው የነበሩትንና ‹ትንሣኤ ሙታን የለም› የሚሉት ከሃድያንን ምስክር ሆነውባቸው አሳፈሯቸው፡፡ ከዚህም በኋላ እነዚህ ቅዱሳን በምድር ላይ መልሰው አንቀላፍተው ቅድስት ነፍሳቸውን ለእግዚአብሔወር አሳልው ሰጡ፡፡ ንጉሡም በወርቅ ሣጥን አድርጎ በዚያችም ዋሻ ውስጥ በክብር ቀብሯቸው፡፡
የቅዱሳኑ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!
+ + +
ጻድቁ አባ ነካሮ፡- ጤና አግኝተው እንዳይተኙ ከምንጣፋቸው በታች እሾህ በመጎዝጎዝ በቀንና በሌሊት በእጅጉ ሲጋደሉ የነበሩ ታላቅ አባት ናቸው፡፡ ከትሑትነታቸው የነተሣ የገዳሙ በር ጠባቂና አትክልት ተንከባካቢ ሆነው እያገለገሉ በጾም በጸሎት በጽኑ ይጋደሉ ነበር፡፡ በዚያም ገዳም በመንፈስ ቅዱስ የተሰወረውን ሁሉ በግልጽ የሚያይ አንድ የበቃ መነኩሴ አለ፡፡ ይህም የበቃ መነኮስ በአንድ ሌሊት ራእይ አየ፡፡ በከፍታ ቦታ ላይ ቆሞ ከበታቹ ፍሬው ወንዞች የከበቡት በየዓይነቱ የሆነ አትክልት አለ፡፡ አባ ነካሮ በመካከላቸው ሆኖ በወዲያ በወዲህ ውኃ ያጠጣቸው ነበር፣ ያ መነኮስም ‹‹አባ ነካሮ ሆይ! ይህ አትክልት የማነው?› አለው፡፡ አባ ነካሮም ‹‹እኔ የተከልኳት ናት›› አለው፡፡ መነኮሱም ‹‹ከፍሬዋ ትሰጠኝ ዘንድ እሻለሁ›› ባለው ጊዜ አባ ነካሮ ሦስት የሮማን ፍሬዎችን ቆርጦ ሰጠው፡፡ መነኮሱም በልብሱ ቋጠራቸው፡፡
ያም መነኮስ ከእንቅልፉ በነቃ ጊዜ እነዚያን የሮማን ፍሬዎች አገኛቸው፡፡ ወዲያውኑ ወደ አባ ነካሮ ሄዶ ‹‹ወንድሜ ነካሮ ሆይ! በዚህች ሌሊት አይተኸኛልን?› ብሎ ጠየቀው፡፡ አባ ነካሮም ‹‹አዎን አይቼሃለሁ ሦስት የሮማን ፍሬዎችንም ሰጥቼሃለሁ›› አለው፡፡ በዚህም ጊዜ ያ መነኮስ እየሮጠ ወደ ገዳሙ ሄዶ የሆነውን ለአበ ምኔቱና ለመነኮሳቱ ሁሉ ተናገረ፣ እነዚያንም የሮማን ፍሬዎች አውጥቶ አሳቸው፡፡ መነኮሳቱም ከአባ ነካሮ ቅድስና የተነሣ አደነቁ፡፡ የሮማን ፍሬ የሚያፈራው በክረምት ስለሆነ በዚያን ጊዜ ወቅቱ በጋ ስለነበረር የሮማን ፍሬ በበጋ አይገኝም፡፡ መነኮሳቱም አባ ነካሮን በዝቅተኛ ማዕረግ ላይ ስላደረጉት አዝነው በከፍተኛ ማዕረግ ሊያደርጉት ፈልገው ወደ እርሱ በሄዱ ጊዜ አጡት፣ ተሰውሮአቸዋልና፡፡ እነርሱም ባጡት ጊዜ እጅግ አዘኑ፡፡ ከዚህም በኋላ በዚህች ዕለት

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

19 Jan, 18:50


በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን (ከገድላት አንደበት), [19/01/2025, 19:15]
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ጥር 12-በዚኽች ዕለት የክብር ባለቤት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የገሊላ ክፍል በሆነች በቃና በሠርግ ቤት ያደረገው የተአምራቱ መታሰቢያ ይደረግ ዘንድ ቅዱሳን አባቶቻችን ሥርዓትን ሠሩልን፡፡
+ ታላቁ ሰማዕት ቅዱስ ቴዎድሮስ በናድልዮስ ሰማዕትነቱን በድል ፈጸመ፡፡
+ የአክሱሙ አቡነ ሳሙኤል ዘጣሬጣ ዕረፍታቸው ነው፡፡
+ የከበሩ ቅዱስ ለውንዲዮስ እና መኰንኑ ቅዱስ ኒቆሮስ በሰማዕትነት ዐረፉ፡
+ የመላእከት ሁሉ አለቃ ቅዱስ ሚካኤል እስራኤል ወደተባለ ያዕቆብ እግዚአብሔር ልኮታልና ከወንድሙ ከኤሳው ፈርቶ ሳለ አዳነው፡፡ ዮርዳኖስንም አሻግሮት ወደ እናቱ ወንድም ወደ ላባ ሄደ፡፡ እርሱም ሁለቱን ልጆቹን ልያንና ራኄልን አጋባው፡፡ ከዚህም በኋላ ከብዙ ገንዘቡና ከልጆቹ ጋር መንገዱን እየጠረገና እያቀና በሰላም በጤና ወደ አገሩ መለሰው፡፡ ወንድሙ ኤሳውም በፍቅር በሰላም ተቀበለው፣ ስለዚህም የሊቀ መላእከት የቅዱስ ሚካኤል የበዓሉ መታሰቢያ ሆነ፡፡ የያዕቆብም የልደቱ መታሰቢያ ነው፡፡
በዚህች ዕለት የክብር ባለቤት ጌታችንና ፈጣሪያች ኢየሱስ ክርስቶስ የገሊላ ክፍል በሆነች በቃና በሠርግ ቤት ያደረገው የተአምራቱ መታሰቢያ ይደረግ ዘንድ ቅዱሳን አባቶቻችን ሥርዓትን ሠሩልን፡፡
ቅዱስ ወንጌል እንደተናገረ ይህች የተአምራቱ መጀመሪያ ናት፣ በድንግል እናቱ ምልጃ ውኃውን ለውጦ መዓዛው እጅግ የሚጥም ጣፋጭ ወይን አድርጎታልና፡፡ በዚህም የእናቱን አማላጅነትና የእርሱን አምላክነት ገለጠ፣ ደቀ መዛሙርቱም አመኑበት፡፡ የተአምራቱ መጀመሪያ መባሉ መጥምቁ ዮሐንስ ጌታችንን ለዓለም ከገለጠውና ካጠመቀው በኋላ ጌታችን ያደረገው ተአምር ስለሆነ ነው እንጂ ለእርሱስ በዚህ ጊዜ ተአምር ማድረግ ጀመረ ተብሎ አይነገርለትም፡፡ የሰርጉም ባለቤት (ሙሽራው) የሐዋርያው የቅዱስ ናትናኤል የአባቱ ወንድም የሆነ የዮካን ልጅ ዶኪማስ ነው፡፡ ጌታችን ወደ ሠርግ ተጠርቶ የሄደው ዶኪማስ ናትናኤልን ‹‹ሠርጌን እንዲባርክልኝ ጌታ ኢየሱስን ከእናቱ ጋር ጥራልኝ›› ብሎት በናትናኤል ጠሪነትና ልመና ነው፡፡ ጌታችን በክብርት እናቱ አማላጅነት ውኃውን ወደ ወይንነት የለወጠበት ትክክለኛ ቀኑ የካቲት 23 ነው፡፡ ጌታችን ጥር 11 ቀን ተጠምቆ ወዲያው ወደ ገዳመ ቆሮንቶስ በመሄድ ከቆመ ሳይቀመጥ ከዘረጋ ሳያጥፍ 40 ቀንና 40 ሌሊት ጾመ፣ ጸለየ፡፡ የካቲት 21 ቀን ከጾሙ ከተመለሰ በኋላ ሐዋርያቱን ሰብስቦ ነው ወደ ሠርጉ ቤት ሄዶ የታደመው፡፡ ነገር ግን ቅዱሳን አባቶቻችን በመንፈስ ተረድተው የውኃን በዓል ከውኃ ማድረግ ይባል ብለው የቃና ዘገሊላን በዓል ጥር 12 ቀን እንዲሆን ሥርዓትን ሠሩልን፡፡ የመድኃኔዓለም ቸርነቱ ለኹላችን ይደረግልን!
+ + +
አቡነ ሳሙኤል ዘጣሬጣ፡- የትውልድ ሀገራቸው ትግራይ ክፍለ ሀገር ሽሬ ጣሪጣ ከተባለው ቦታ ነው፡፡ በሕፃንነታቸው ወደ ደብረ በንኮል ገዳም ገብተው መጻሕፍተ ብሉያትንና መጽሐፍተ ሐዲሳትን የሥርዓት መጻሕፍትንም በሚገባ ተማሩ፡፡ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ካመነኮሷቸው ከሰባቱ ከዋክብት ውስጥ አንዱ ናቸው፡፡ ጻድቁ ራሳቸው የገደሙት የአንድነት ገዳማቸው ከአክሱም ወጣ ብሎ ከሚገኘው ከአቡነ መድኃኒነ እግዚእ ገዳም አጠገብ ይገኛል፡፡ ጻድቁ መከራ ሲመጣ ሕዝቡን ለማስተማር ሲወጡ ጥቁር ልብስ ይለብሱ ነበር፣ ሕዝቡም በፍርሃት ይሰማቸዋል፡፡ በትግራይ እስከ ሽሬ ድረስ እየተዘዋወሩ ወንጌልን በመስበክና ሕሙማንን በመፈወስ ካገለገሉ በኋላ ከፈጣሪያቸው ቃልኪዳን ተቀብለው ጥር 12 ቀን በታላቅ ክብር ዐርፈዋል፡፡ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!
+ + +
ሰማዕቱ ቅዱስ ቴዎድሮስ በናድልዮስ፡- ሰማዕቱ ቅዱስ ቴዎድሮስ በናድልዮስ በሌላኛው ስሙ ‹‹ቴዎድሮስ ምሥራቃዊ›› እየተባለም ይጠራል፡፡ ከአንጾኪያ አገር ሰዎች ከመንግሥት ወገን የተገኘ ታላቅ ሰማዕት ነው፡፡ አባቱ ሲድራኮስ የንጉሡ የኑማርያኖስ የጭፍራ አለቃ ሲሆን እናቱ በጥሪቃ ደግሞ የቤት እመቤት ናት፡፡ ከሃዲው ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ለጣዖት ያልሰገዱትን ሁሉ በሰይፍ እየፈጀ አብያተ ክርስቲያናትን እያቃጠለ በነበረበት ወቅት የተገኘ ሰማዕት ነው፡፡ ጌታችን ተገልጦለት ለሰማዕትነት እንደመረጠውና ለስሙም እንደሚሞት ከነገረው በኋላ ነው በሃዲው ንጉሥ በዲዮቅልጥያኖስ ፊት ቀርቦ ስለ ጌታችን አምላነት በመመስከር ሰማዕትነትን የተቀበለው፡፡ ንጉሡም የቅዱስ ቴዎድሮስን ተከታዮች በሰይፍ ከጨረሳቸው በኋላ እርሱን ግን ሥቃዩን በማብዛት በእጅጉ አሠቃየው፡፡ በ153 ችንካሮች ቸንክሮ ሰቅሎ ካሠቃየው በኋላ ነው ሰማዕትነቱን የፈጸመው፡፡
ይኸውም የሆነው እንዲህ ነው፡- ንጉሡ ኑማርያኖስ በጦርነት ውስጥ በሞተ ጊዜ ልጁ ቅዱስ ዮስጦስም በሌላ ቦታ በጦርነት ውስጥ ስለነበር መንግሥትም ያለ ንጉሥ ነበረች፡፡ የቴዎድሮስ በናድልዮስ አባት ሲድራኮስና ቅዱስ ፋሲለደስ ዲዮቅልጥያኖስ ነግሦ ሃይማኖቱን እስከካደ ድረስ የመንግሥቱን አስተዳደር ይመሩ ነበር፡፡ በመጀመሪያ ታላቁ የአንጾኪያ ንጉሥ ኑማርያኖስ የፋርስና የቁዝ ሰዎች በጦር በርትተው በመጡበት ጊዜ ቅዱስ ፋሲለደስንና ህርማኖስን ጠርቶ ‹‹እነሆ እኔና የተረፉት ሠራዊት ሄደን የቁዝን ሰዎች እንዋጋለን እናንተ ቤተ መንግሥቱን ጠብቁ፣ ልጆቼን ለእናንተ አደራ ሰጥቻለሁ›› አላቸው፡፡ ንጉሡም የመንግሥቱን ልብስ አውልቆ ዘውዱን ጥሎ ተራ ልብስ ለብሶ ሲዋጋ በጦር ተወግቶ ሞተ ነገር ግን የቁዝ ሰዎች አላወቁትም ነበር፡፡ ጦርነቱም ባለቀ ጊዜ የሮም መንግሥት ያለንጉሥ ብቻዋን ቀርታ አንድ ዓመት ሙሉ ቅዱስ ፋሲለደስና ህርማኖስ የመንግሥት ሕጓንና ሥርዓቷን እየጠበቁ ቆዩ፡፡ የቁዝ ሰዎችም የሮም መንግሥት ያለ ንጉሥ መሆኗን ሲያውቁ ዳግመኛ ሊያጠፏቸው በጦር በርትተው መጡ፡፡ የሮም ሰዎችም ተሰብስበው ቅዱስ ፋሲለደስን ‹‹በስራችን ወዳሉ ግዛቶች ወደ ግብጽም ተዋጊ አርበኞችን ይልኩልን ዘንድ እንይቃቸው›› አሉት፡፡ መኳንንቱም ወደ ግብጽ ወርደው በጦር ኃይለኛ የሆኑ ሰዎችን ይዘው ተመለሱ፡፡ ከግብጽ ካመጧቸው ኃይለኛ ሰዎች ውስጥ ከላይዕላይ ግብጽ ስሙ ከርቢጣ የሚባል ፍየል የሚጠብቅ አንድ ኃይለኛ ሰውን ወደ አንጾኪያ አመጡ፡፡
ቅዱስ ፋሲለደስና ህርማኖስም ይህ ሰው የሚያስፈራ በሥራውም ኃይለኛ ጉልበቱ የጸና ጨካኝ መሆኑን አይተው በንጉሡ ፈረስ ላይ ባልደራስ ወይም ሹም አድርገው ሾሙት፡፡ ከጥቂት ወራትም በኋላ ታላቂቱ የንጉሡ ልጅ ከቤተ መንግሥት ሆና በመስኮት በኩል ሆና ሲወጣ ባቱን ሲገባ ደረቱን አይታ በሀፀ ዝሙት ተነድፋ እጅግ ወደደችው፡፡ እርሱንም ሰይጣን ከልጅነቱ ጀምሮ ይከተለው ነበር፡፡ የንጉሡም ልጅ ወስዳ አገባችውና ስሙን ዲዮቅልጥያኖስ አለችው፡፡
የእናቷ ወንደም ቅዱስ ፋሲለደስ ሳያውቅ ንጉሥ አደረገችው፡፡ ሰይጣንም በእርሱ አድሮ ያነጋግረው ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ ቅዱስ ፋሲለደስን ጠርቶት ስለ መንግሥት ሥራ ተነጋገሩ፡፡ ለጦርነትም ሰራዊት ሰበሰቡ፡፡ ቴዎድሮስ በናድልዮስ የሠራዊቱ አለቃ ሆኖ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ጦሩን እየመሩ ወደ ጦርነት ሄዶ፡፡ ዲዮቅልጥያኖስም ቅዱስ ፋሲለደስንና ህርማኖስን የመንግሥትን ሥራ ይሠሩ ዘንድ ከቤተ መንግሥት ተዋቸው፡፡ ምሥራቃዊ ቴድሮስም በጦርነቱ በርትቶ የቁዝ አገርን ሠራዊት ፈጃቸው፡፡

በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን (ከገድላት አንደበት), [19/01/2025, 19:15]

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

19 Jan, 18:50


የቁዝን የንጉሡን ልጅ ኒጎሚዶስን ማርኮ አምጥቶ ለዲዮቅልጥያኖስ ሰጠው፡፡ የቁዝ ሰዎችም ሸሹ፡፡ ንጉሡም የተማረከውን የቁዝን ንጉሥ ልጅ ይዞ ወደ አንጾኪያ ተመለሰ፡፡ በዚያም ወራት የአጾኪያው ሊቀ ጳጳስ እስጢፋኖስ ዐርፎ በእርሱ ምትክ ዮሐናዳኬዎስ ነግሦ ነበርና ንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስ ሊቀ ጳጳሱን ጠርቶ ‹‹ጠብቅልኝ›› ብሎ በአደራ ሰጠው፡፡ የቁዝ ንጉሥም ልጁ በሊቀ ጳጳሱ ዘንድ መኖሩን ሲሰማ በልጁ ሚዛን ልክ ወርቅ አምጥቶ ለሊቀ ጳጳሱ ሰጥቶት ልጁን ከምርኮ አስመለሰ፡፡ የቁዝ ሰዎችም የንጉሣቸው ልጅ ከምርኮ መመለሱን በሰሙ ጊዜ እጅግ ተደስተው ዳግመኛ ዲዮቅልጥያኖስን በጦር ይገጥሙት ዘንድ መልእክት ልከው ለጦርነት ተዘጋጅ አሉት፡፡ ንጉሡም ይህንን ሲሰማ እጅግ ተቆጥቶ ሊቀ ጳጳሱን መልክተኛ ልኮ ‹‹የሰጠኹህ ልጅ ከአንተ ዘንድ አለ ወይስ የለም?›› አለው፡፡ ሊቀ ጳጳሱም ‹‹አለ›› ብሎ ዋሸ፡፡ ንጉሡም በልቡ ያለ ሰይጣን እያበረታው ከብዙ ጦር ጋር ዘምቶ ሳለ የቁዝን ንጉሥ ልጅ ከእነርሱ ጋር አየው፡፡ ምስራቃዊ ቴዎድሮስንም ጠርቶት ‹‹ይህ የማየው ልጅ አንተ ማርከህ አምጥተህ የሰጠኸኝ አይደለምን›› አለው፡፡ ቅዱስ ቴዎድሮስ በናድልዮስም ‹‹አዎን›› አለው፡፡ ንጉሡም ‹‹ዳግመኛ ልጁን ማርከህ ካጣህልኝ ብዙ ወርቅና ብር እሰጥሃለሁ›› አለው፡፡ ቴዎድሮስም ‹‹እኔስ ወርቅና ብር ሥልጣንም አልሻም ነገር ግን የተማረኩ ወንድሞቼ ዮስጦስና አውሳብዮስ በሕይወት ካሉ እነርሱን ማምጣት ነው የምፈልገው›› አለው፡፡ በጦርነቱም ወቅት ቴዎድሮስ እጅግ በረታና የቁዝን ሠራዊት ማርኮ የንጉሡንም ልጅ ዳግመኛ በመማረክ አምጥቶ ለንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ሰጠው፡፡
ንጉሡም ልጁን ከመረመረው በኋላ የሊቀ ጳጳሱን እኩይ ሥራ ተመልከቶ መኳንንቱን ሰብስቦ የልጁን ዳግመኛ መማረክ በምሥጢር እንዲጠብቁ ነገራቸው፡፡ ወደ አንጾኪያም በተመለሰ ጊዜ ንጉሡ ቅዱስ ፋሲለደስን ጠርቶ ሊቀ ጳጳሱ ስለ ወርቅ ፍቅር ያደረገውን ነገር ነገረውና ልጁን በቤተ መንግሥት ይጠብቀው ዘንድ በአደራ ሰጠው፡፡ ንጉሡም ሊቀ ጳጳሱ አስቀድሞ ‹‹ልጁ ከእኔ ጋር አለ›› ብሎ ስለዋሽው አሁን ‹‹ልጁን አምጣልኝ ከአባቱ ጋር ታርቄአለሁና›› አለው፡፡ ሊቀ ጳጳሱም ‹‹ልጁማ ሞቶ አስክሬኑን እየጠበቅሁ ነው›› አለው፡፡ ንጉሡም ‹‹አስክሬኑን አምጣልኝ›› አለውና ሊቀ ጳጳሱ ሌላ የሞተ ሰው ሬሳ ይዞለት መጣ፡፡
ንጉሡም ተገርሞ ‹‹በእውኑ ይሄ የቁዝ አገር ንጉሥ ልጅ የኒጎሚዶሚስ አስክሬን ነውን›› ብሎ ሲጠይቀው ሊቀ ጳጳሱም በውሸት ‹‹አዎን›› አለው፡፡ ያንጊዜም ንጉሡ ‹‹በል ዛሬ ቅዳሴ ቀድሰህ ቁርባን ሠርተህ እኔንና ሕዝቡን አቁርበን›› አለው፡፡ ሊቀ ጳጳሱም ቅዳሴ ገብቶ ሥጋወደሙን ለማቀበል ከመቅደስ ወጥቶ ድርገት ሲወርድ ንጉሡ ወደ እርሱ ቀርቦ ‹‹በል ይሄ ሬሳ የቁዝ አገር ንጉሥ ልጅ ነው ብለህ በሥጋ ወደሙ ማልልኝ›› አለው፡፡ ሊቀ ጳጳሱ በሥጋ ወደሙ ማለለት፡፡ ንጉሡም ሊቀ ጳጳሱ በጌታችን ሥጋወደሙና በታቦቱ ፊት በውሸት እንደማለ ባየጊዜ እሳት ወዲያው ወርዶ ሊቀ ጳጳሱን የሚያቃጥለው መስሎት ነበር፡፡ ወዲያውም ቅዱስ ፋሲለደስን ልጁን እንዲያመጣው አዘዘውና ልጁን አመጣለት፡፡ ልጁም አባቱ ብዙ ወርቅ ከሊቀ ጳጳሱ ከፍሎ እንደወሰደው በሕዝቡ ሁሉ ፊት መሰከረ፡፡
ጌታችን ስለ ሥጋ ወደሙ ክብር ሲል በሊቀ ጳጳሱ ላይ ተአምር ሊያሳይበት ነበር ነገር ግን ንጉሡን ሰይጣን ለክፋት ያፋጥነው ነበርና ንጉሡ ቸኩሎ ፈጣሪውን ክዶ ሊቀ ጳጳሱም የተቀበለውን ወርቅ አስመጥቶ ወርቁን በእሳት አስፈልቶ የፈላውነ ወርቅ በሕይወት ሳለ ቢያስጠጣው ሊቀ ጳጳሱ ወዲያው ለሁለት ተሰንጥቆ ሞተ፡፡ ንጉሡም በሥጋ ወደሙ በሐሰት ሲምል እሳት ከሰማይ ወርዶ ያልበላው ለምንድነው ብሎ ወደ ክህደት ገባ፡፡ ወዲያውም እርሱ በሚገዛበት አውራጃ ሁሉ አብያተ ክርስቲያናት እንዲዘጉ በምትካቸውም የጣዖታት ቤቶች እንዲከፈቱ አዘዘ፡፡ ዳግመኛም የአብያተ ክርስቲያናት አገልጋዮችም በሙሉ ለጣዖታቱ እንደሠው ያልሠዋ ቢኖር ግን እንዲገደል አዘዘ፡፡ የትእዛዙንም ደብዳቤ በግዛቶቹ ሁሉ ላከ፡፡
ጌታችንም ለታላቁ ሰማዕት ቅዱስ ፋሲለደስ ተገለጠለትና ሰላምታ ከሰጠው በኋላ ስለ ስሙ ይቀበል ዘንድ ስላለው መከራና በሰማይም ስለሚያገኘው ክብር ነገረው፡፡ ሰማዕታት ይሆኑ ያላቸውንም ሁሉን ስማቸውን እየጠራ ነገረው፡፡ አባድርና እኅቱ ኢራኒ፣ የህርማኖስ ልጅ ፊቅጦር፣ ምሥራዊ ቴዎድሮስ፣ ገላውዴዮስ፣ አራቱም ልጆቹ አውሳብዮስና መቃርስ እንዲሁም ሁለቱ ሴቶች ልጆቹ፣ የንጉሡ ልጅ ዮስጦስና አቦሊ ሚስቱም ታውክልያ… እነዚህንና ሌሎቹንም ሁሉ ስማቸውን እየጠራ ጌታችን ሰማዕት እንደሚሆኑ ለቅዱስ ፋሲለደስ ነገረው፡፡ እነዚህ ሁሉ ከእግዚአብሔር ልዩ ኃይል የተሰጣቸው በጦርነት ማንም የማያቆማቸው እጅግ ኃያላን ናቸው፡፡ ጌታችንም ቅዱስ ፋሲለደስን ከሌሎቹ ተለጥቶ ከብዙ ተጋድሎ በኋላ ሰማዕት እንደሚሆን ነገረው፡፡ በሌሎቹ ሰማዕታትም ሆነ በእርሱ ላይ የሚደረስበትን መከራ እና በኋላም የሚያገኙትን ክብር ሁሉ በዝርዝር ነገረው፡፡ ብዙ ቃልኪዳንም ገባለት፡፡ የሰማዕታትንና የቅዱሳንን መኖሪያ ካሳየው በኋላ ሰማዕትነቱን ሲፈጽም የሚያገኘውን ክብር መሆኑን ነግሮት በገነት ውኃ በምለአኩ እጅ እንዲጠመቅ ካደረገው በኋላ ወደ ምድር መለሰው፡፡
መልአክቱም በመላ ዓለም ተሠራጨ፡፡ የሊቀ ጳጳሱንም ወርቅ አቅልጦ 35 የወንድና 35 የሴት ጣዖታትን አሠርቶ ሰው በሚመላለስበት አደባባይ አቆማቸውና ሁሉም ለእነርሱ እንዲሰግድ አዘዘ፡፡ ንጉሡ ላቆማቸው ለእነዚህ ጣዖታት ያልሰገደ ቢኖር ግን ‹‹ይገደል ንብረቱም ይዘረፍ›› አለ፡፡ ሕዝቡንም ሁሉ ሰብስቦ እርሱ ለጣዖታቱ ሰገደላቸው፡፡ ከንጉሡ ቀጥሎ የወታደሮቹ አለቃ ህርማኖስም ሰገደ፡፡ 900 ባለሥልጣናትና 40 ሺህ ወታደሮችም እንዲሁ በየተራ ሰገዱ፡፡ ሕዝቡም ሁሉ እንዲሁ ሰገዱ፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

19 Jan, 18:50


ቅዱስ ቴዎድሮስ በናድልዮስ ለጌታችን የታመነ ስለነበር ኃይልንና መፈራትን አሳድሮበታል፡፡ እርሱም በጦርነት ኃይለኛና የሚያስፈራ ግርማ ያለው ስለነበር የፋርስ ሰዎች ቴዎድሮስ መጣ ከተባሉ ልባቸው ይደነግጥ ነበር፡፡ ከእነርሱም ውስጥ ‹‹የሮማውያን አምላክ ነው›› ብለው የሚሉትም ነበሩ፡፡ ቅዱስ ቴዎድስሮስ በጦርነት ቦታ ቡናቢስ በሚባል ወንዝ አጠገብ ከወዳጁ ለውንድዮስ ጋር ሳለ ታላቅ ራእይ አየ፡፡ ይህም ያዕቆብ በሎዛ ያየውን ዓይነት ራእይ ነው፡፡ ከምድር እስከ ሰማይ መሰላል ተዘርግቶ በላዩ ጌታችን ተቀምጦ ዙሪያውን መላእክት ከበውታል፡፡ ከታች ደግሞ ጠላት ከይሲ ነበረ፡፡ ጌታችንም ቴዎድሮስ በናድልዮስን ‹‹ቴዎድሮስ ሆይ ለእኔ ልጄ ትሆነኝ ዘንድ ትወዳለህን?›› አለው፡፡ ቴዎድሮስም ‹‹አቤቱ አንተ ማነህ?›› ባለው ጊዜ ጌታችን መልሶ ‹‹እኔ የአብ አካላዊ ቃል ኢየሱስ ነኝ፣ ለአንተም ስለ ስሜ ደምህ ይፈስ ዘንድ አለህ›› አለው፡፡ በዚያን ጊዜም ቴዎድሮስ በዙሪያው ከቆሙት መላእክት ውስጥ እንደ አንዱ ሆነ፡፡ ሁለመናውም በመንበሩ ዙሪያ እንደቆሙት ሆነ፡፡ ቴዎድሮስም ጌታችንን ‹‹ጌታዬ ከወዳጄ ከለውንዲዮስ መለየት አልሻም›› ባለው ጊዜ ጌታችንም ‹‹እርሱ ብቻ አይደለም ለቍዝ ሠራዊት መኰንን የሆነ ኒቆሮስም ነው እንጂ›› አለው፡፡ እነርሱንም በእሳት ባሕር ሲያጠምቋቸው አየ፡፡ ከዚህም በኋላ ቴዎድሮስና ለውንድዮስ አብረው ተያይዘው የቍዝ የሠራዊት አለቃ ወደ ሆነው ወደ ኒቆሮስ ዘንድ ሄደው ተገናኙት፡፡ አስቀድመውም ጠላቶች ነበሩና ንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስ ይህን ሲሰማ ‹‹እንዴት ከጠላት ጋር ሰላም ይፈጥራል?›› ብሎ ተናደደ፡፡ መልእክተኞቹንም ልኮ ወደ እርሱ እንዲመጡ አደረጋቸው፡፡ እነርሱ

በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን (ከገድላት አንደበት), [19/01/2025, 19:15]
ሦስቱም በአንድነት በሰማዕትነት ሊሞቱ ተስማምተው ቃል ተገባቡ፡፡
ቴዎድሮስ በናድልዮስም ወደሚመራው የጦር ሠራዊት ፊቱን አዙሮ ‹‹ነፍሱን ከሰይፍ ሊያድን የሚወድ ቢኖር ወደፈለገው ይሂድ፡፡ በጌታችንም ስም መጋደልን የሚሻ ግን ከእኛ ጋር ይቆይ›› በማለት ሠራዊቱን በተነ፡፡ እነርሱም ‹‹በጌታችን ታምነን ከአንተ ጋር አብረን እንሞታለን›› አሉት፡፡ እርሱም ‹‹ነገራችሁ እውነት ከሆነ ወደ ወንዝ ገብታችሁ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ተጠመቁ›› አላቸው፡፡ እነርሱም አምነው ሄደው ተጠመቁ፡፡ ተጠምቀውም ሲወጡ ከሰማይ ‹‹አይዟችሁ እኔ ከእናንተ ጋር ነኝ›› የሚል የሚያጽናና ቃልን ሰሙ፡፡
ቴዎድሮስ በናድልዮስም ሠራዊቱን ከከተማ ውጭ ትቶ ከሁለቱ ወዳጆቹ ጋር ወደ አንጾኪያ ከተማ ገብቶ ንጉሡን ዲዮቅልጥያኖስን አገኘውና በፊቱ ስለ ጌታችን በመመስከር ሃይማኖቱን ክዶ ጣዖት ስላማምለኩ ዘለፈው፡፡ ንጉሡም ‹‹ለአጵሎን ስገድ›› አለው፡፡ ቴዎድሮስም ንጉሡን ከገሠጸው በኋላ ጣዖቱን ረገመበት፡፡ ንጉሡም እጅግ ተቆጥቶ ሁለቱን ወዳጆቹን ወደ ሚዶን አገር በግዞት ላካቸውና በዚያ ተሠቃይተው እንዲሞቱ አዘዘ፡፡ እነርሱም ከብዙ ሥቃይ በኋላ ጥር 12 ቀን ሰማዕትነታቸውን ፈጸሙ፡፡
ቅዱስ ቴዎድሮስ በናድልዮስን ግን በታላቅ እንጨት ላይ አስተኝቶ ቁጥራቸው 153 በሆኑ ረጃጅም የብረት ችንካሮች አስቸነከረው፡፡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤልም ተገልጦለት ካጽናናው በኋላ ከቁስሉ ፈወሰው፡፡ ከብዙ ሥቃይም በኋላ ጌታችን ተገልጦለት አነጋገረውና ከሕማሙ ሊፈውሰው ሲል ቴዎድሮስ በናድልዮስ ጌታችንን ‹‹ጌታዬ ሆይ ተወኝ በስምህ መሞት ይሻለኛል›› አለው፡፡ ጌታችንም ፈቃዱን ፈጸመለትና ሦስት አክሊላትን አዘጋጀለት፡፡ በጦርነት፣ በእስርና በመከራ ያሉ ሁሉ በስሙ ቢማፀኑ እንደሚምርለትና ለሃዘናቸውም ጽናትና ብርታት እንደሚሰጣቸው ቃልኪዳን ሰጥቶት የሚጠብቀውንም ክብሩን ካሳየው በኋላ ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ ‹‹በሁሉ ቦታ ስምህን የሚጠራ ቢኖር ከመከራው ሁሉ አድነዋለሁ›› ብሎታል፡፡
ቅዱስ ቴዎድሮስ በናድልዮስም ሰማዕትነቱን ጨርሶ ካረፈ በኋላ ዲዮቅልጥያኖስ ሠራዊቱን ሁሉ ለጣዖቱ ይሰግዱ ዘንድ የጣዖታቱን ካህናት ላካቸው፡፡ አዋጅ ነጋሪም በከተማው አዞረ፡፡ የበናድልዮስ ሠራዊትም በአንድ ላይ ሆነው ‹‹የነገሥታት ንጉሥ የጌቶች ጌታ ከሆነ ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ሌላ አምላክ የለም›› ብለው ጮሁ፡፡ ንጉሡም ሰምቶ እጅግ ተናደደ፡፡ ራስ ራሶቻቸውንም ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ፡፡ 250ሺህ የሚሆኑ የቴዎድሮስ በናድልዮስ ማኅበርተኞች የሆኑ ሠራዊቶችም በሰማዕትነት ተሰየፉ፡፡ በዚያን ጊዜም በቁጥራቸውም ልክ አክሊልን የሚያኖሩ ብርሃናውያን መላእክት አየሩን ሞልተውት ታዩ፡፡
የታላቁ ሰማዕት የቅዱስ ቴዎድሮስ በናድልዮስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!
(ምንጭ፡- ታላቁ ሊቅ አለቃ አያሌው ታምሩ የተረጎሙት ገድለ ቴዎድሮስ በናድልዮስ እና የጥር ወር ስንክሳር፣ ሐመረ ተዋሕዶ ዘዕሥራ ምእት)

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

19 Jan, 03:00


በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን (ከገድላት አንደበት), [19/01/2025, 05:58]
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ጥር 11 ኢትዮጽያዊዩ ጻድቅ አቡነ ሐራ ድንግል ዓመታዊ የዕረፍት በዓላቸው ነው።
አቡነ ሐራ ድንግል ከአባታቸው ከሬማው ካህን ከቅዱስ ዮሐንስ ከእናታቸው ብፅዕት ወለተ ጊዮርጊስ የተወለዱት ጥቅምት 19 ቀን 1534 ዓ.ም ነው፡፡ የትውልድ ሀገራቸው ጥንት በጌምድር ደብረ ታቦር አውራጃ ደራ ወረዳ ይባል በነበረው አሁን በምዕራብ ጎጃም ዞን ባሕር ዳር ዙሪያ ወረዳ ላጉና ቀበሌ ነው፡፡ ቅዱሳን የሆኑ ወላጆቻቸውም አባታችንን ከልጅነታቸው ጀምሮ በሃይማኖት በምግባር ኮትኩተው አሳደጓቸው፡፡ አባታችንም የቤተ ክርስቲያንን መጻሕፍት በሙሉ ተምረው በታላቅ መንፈሳዊ ተጋድሎና አገልግሎት ከኖሩ በኋላ ዓለምን ፍጹም ንቀው መንነው ወደ ሸዋ ተጉዘው ግራርያ ከሚባል አገር ደረሱ፡፡ በዚያም ዘመዶቻቸው ፈልገው ስላገኙዋቸውና ወደ ሀገራቸው ስለመለሷቸው በሌላ ጊዜ ጥቅጥቅ ያለውን ጫካ አቋርጠው አሁን ገዳማቸው ካለበት ጫካ ውስጥ ገቡና ገዳመ ወንያትን መሠረቱ፡፡ በዚያም ፈተናውን ሁሉ ድምጸ አራዊቱን፣ ግርማ ሌሊቱን፣ ብርዱን፣ ሐሩሩን፣ ረሃብ፣ ጥማቱን ታግሰው በታላቅ ተጋድሎ ኖሩ፡፡ ሰይጣንም በፈተና ሊጥላቸው አንድ ጊዜ በተዋበች ቆንጆ ሴት እየተመሰለ አንድ ጊዜ ደግሞ በሞተ ሰው እየተመሰለ እስከ ሰባት ተከታታይ ቀናት ድረስ ቢፈትናቸውም ድል አድርገውታል፡፡
አባታችን ቀን ላይ ጸሎት እያደረጉ እያለ ነብር የሚያባርራት አንዲት ሚዳቋ መጥታ ከቤት ገብታ ከአቡነ ሐራ ድንግል እግር ስር አረፈች፡፡ ነብሩም ደርሶ ከደጅ እየተቆጣ ቆመ፡፡ ይህን ጊዜ አባታችን ‹‹እርሷን ገድለህ ትበላ ዘንድ እግዚአብሔር አልሰጠህምና ሂድ›› ባሉት ጊዜ ቃላቸውን ሰምቶ ሄደ፡፡ ሚዳቆዋም እዛው አድራ ሲነጋ በሰላም አሰናብተዋታል፡፡
አባታችን መንኩሰው በገዳማቸው ከገቡበት ፈጽመው ሳይወጡ ለ14 ዓመት በተአቅቦ ተቀምጠዋል፡፡ በአንድ ወቅት ጠላት ተነስቶ አካባቢውን በሙሉ በመውረር ሁሉን ሲማርኩ ገዳሟን አይተው ወደ እርሷም ሊገቡ ሲሉ በተአምራት ባሉበት ተይዘው ቆመው በመቅረታቸው ጉዳት ሳይደርሱባት ተመልሰዋል፡፡ ሱስንዮስ ‹‹ሁለት ባሕርይ ሁለት አካል›› የሚለውን የሮማን የረከሰ ሃይማኖት በሀገራችን ላይ እውጆ ብዙዎች ሰማዕትንትን ሲቀበሉ አቡነ ሐራ ድንግል በገዳማቸው ለብዙዎች መጠጊያ ሆነው ሃይማኖታቸውን ሲያስተምሯቸውና ሲያፀኗቸው ነበር፡፡ በንጉሡም ፊት ቀርበው በድፍረት ‹‹አንድ አካልና አንድ ባሕርይ የሆነውን መለኮትና ትስብእትን ለምን ከሁለት ወገን ትከፍለዋለህ?›› ብለው ሲገስፁት ፈርቶ አሽከሮቹን ‹‹ይህን መነኩሴ ከቤቴ አውጥታችሁ በፍጥነት ወደ ገዳሙ አድርሱልኝ›› ብሏቸዋል፡፡ እመቤታችንን እጅግ አድርገው ይወዷት ነበርና ምስጋናዋን ሲያደርሱ ሦስት ክንድ ከምድር ከፍ ይሉ ነበር፡፡ ቅዱስ ገብርኤልም የሁልጊዜ ጠባቂያቸው ነበር፡፡ በ1574 ዓ.ም አሁን በስማቸው ወደሚጠራው ገዳመ ወንያት መንነው ገቡ፡፡ በዚያም ወንጌልን እያስተማሩ፣ እጅግ ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን እያደረጉ፣ ሙት እያስነሱ፣ ድውያንን እየፈወሱ እግዚአብሔርን ሲያገለገሉ ኖረዋል፡፡
አባታችን ሐራ ድንግል ‹‹የማነ ብርሃን›› የሚባል ታማኝ አገልጋይ አህያ ነበራቸው፡፡ አህያውም ጸሎታቸው ይጠብቀው ነበር እንጂ እረኛ አልነበረውም፡፡ አንገቱ ላይ ቃጭል አስረው ወደ ገበሬው አውድማ ይልኩትና አህያውም ቃጭሉን እያጮኸ ወደ አውድማው ሁሉ ሄዶ እየዞረ ‹‹ማርያም ባርኪ›› በረከት ሰፍረው ይጭኑታል፡፡ አህያውም ከገበሬው ሁሉ የሰበሰበውን እህል ይዞ ወደ አቡነ ሐራ ድንግል ይገባል፡፡ በፈለጉትም ሰዓት ራሱ አውቆ ይመጣላቸው ነበር፡፡ አህያውም አርጅቶ ሲሞት እንደ ሰው አልቅሰውና በአዲስ ጨርቅ ጠቅልለው ቀብረውታል፡፡ አህያቸው የማነ ብርሃን ከተቀበረበት ቦታ ላይ ጸበል ፈልቆ አስደናቂ ተአምራትን አድርጓል፡፡ የቅዱሳኑ በረከታቸው እስከምን ድረስ እንደሆነ ልብ ይሏል፡፡
ታላላቆቹ ቅዱሳን እንደነ በትረ ማርያም፣ ጽጌ ድንግል፣ ወለተጴጥሮስ ያሉ ሌሎችም በርካታ ደጋግ ቅዱሳን ዝናቸውን እየሰሙ ከያሉበት እየሄዱ ይጎበኙዋቸውና በረከታቸውን ይቀበሉ ነበር፡፡ አባታችን አቡነ ሐራ ድንግልም በክብር ካረፉ በኋላ በመካነ መቃብራቸው ላይ ለ40 ቀን ብርሃን ሲወርድ በገሃድ ታይቷል፡፡ አፅማቸውም ከዚያው ከገዳማቸው በክብር አርፎ ይገኛል፡፡ በጸሎታቸው ያፈለቁት ጸበልና የመቃብራቸው አፈር ሕመምተኞችን ከተለያዩ ደውያት ሰውንም እንስሳትንም እየፈወሰ ይገኛል፡፡ አፈራቸውና ጸበላቸው ለሥጋ ደዌ፣ ለእብጠት፣ ለቁስል፣ ለለምፅና ለመሳሰሉት ፍቱን መድኃኒት ነው፡፡ በዓለ ዕረፍታቸው ጥር 11 ቀን 1624 ዓ.ም ነው፡፡
+++
ገዳመ ወንያት አቡነ ሐራ ድንግል አንድነት ገዳም!

ረድኤት በረከታቸው ይደርብንና በዛሬዋ ዕለት ጥር 11 ቀን በዓመታዊ የዕረፍት በዓላቸው ታስበው የሚውሉት አቡነ ሐራ ድንግል ያደረጉት ተአምር ይኽ ነው፡- ዲማ በሚባል አገር አንድ ሰው ነበር፡፡ እርሱም በንዳድ በሽታ በጸና ታሞ ስለነበር ዘመዶቹ ከዲማ ወደ አቡነ ሐራ ድንግል ገዳም አመጡት፡፡ ፈውስን ለማግኘት እንዲማጸንበት በገዳሙ ውስጥ አኖሩት፡፡ በዚያም ተቀምጦ 7 ወር በጽኑ ደዌ ታመመ፡፡ በአቡነ ሐራ ድንግል በበዓሉ ዕለት (እንደዛሬዋ ባለችው በዕረፍቱ ዕለት) ብዙ ታላላቅ ሰዎች ከሁሉም ቦታ ተሰብስበው የአባታችንን በዓል ለማክበር ወደ ገዳሙ ሲመጡ አየ፡፡ የታመመውም ሰው ከደዌው ጽናት የተነሣ አቡነ ሐራ ድንግልን "እነዚህ ኹሉ በበዓልህ ቀን የተሰበሰቡ መዳንን ፈልገው አይደለምን? እኔንስ ብታድነኝ ምነው አባቴ?" ብሎ ለመናቸው፡፡ እንዲህም እያለ በጸሎት ሲለምን ወዲያው እንቅልፍ መጣበትና በእንቅልፉ ወደ ሰማይ ወጥቶ አቡነ ሐራ ድንግል እግዚአብሔርን እንዲህ እያሉ ሲለምኑ አያቸው፡- "...በእኔ የተማጸነውን በገዳሜ ውስጥም ያለውን ይኽንን የታመመ ሰው አድንልኝ፣ ጌታዬ ሆይ! እነሆ አንተ ራስህ በማይታበል ቅዱስ ቃልህ የምሕረት ኪዳን ሰጥተኸኛልና፡፡"ያንጊዜም ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ መጥቶ በእግዚአብሔር ፊት ቆመና "አምላኬ ሆይ! ይኽን ሕመምተኛ ሰው ማርልኝ በእኔም ተማጽኗልና መታሰቢያዬንም አድርጓልና" ብሎ ለመነ፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር የኹለታቸውንም ነገር ሰምቶ እንደማይሰማ ዝም አለ፡፡
አባታችን ሐራ ድንግልም በስሙ የተማጸነውንና በገዳሙ ውስጥ ያለውን ይኽን የታመመ ሰው ባልማረለት ጊዜ አዘነ፡፡ እግዚአብሔርም የአባታችንን ኀዘኑን ባየጊዜ "ወዳጄ ሐራ ድንግል ሆይ! በጸሎትህ የተማጸነውን ሰው ምሬልሃለሁ፣ በፈቃድህ አኑረው" አለው፡፡ አባታችንም ወዲያው ያንን የታመመ ሰው እጁን ይዞ ወሰደው፡፡ ወደ ገሃነምም አድርሶ ጨለማውን፣ እሳቱን በዚያ ያሉትን የኃጥአንን እጅግ የከፋ የሥቃይ አኗኗራቸውን ካሳየው በኃላ አባታችን ሕመምተኛውን "...የክፋት ሥራ ብትሠራ በዚያ ትኖራለህ" አለው፡፡ ከዚያም ወደ መንግሥተ ሰማያት አንጻር አደረሰውና በውስጧ ያሉትን ብርሃንና ክብርን ብዙ ደስታንም አሳየውና "መልካም ብትሠራ በዚህ የብርሃን ከተማ ከቅዱሳን ጋራ ትኖራለህ" አለው፡፡

በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን (ከገድላት አንደበት), [19/01/2025, 05:58]

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

19 Jan, 03:00


በመጨረሻም አባታችን ይህንን ከጽኑ ደዌ ያዳነውን ሰው "እኔን ታውቀኛለህን?" ሲል ጠየቀው፡፡ ሰውየውም "በክብር አይሃለሁ እንጂ ማን እንደሆንህ አላወኩህም" አለው፡፡ አባታችንም የእኔ በጸሎቴ የተማጸንክብኝ ሐራ ድንግል ነኝ፣ አሁንም ወደ ቀደመ ኑሮህ ተመለስ እግዚአብሔር በልመናዬ ከሞት አድኖሃልና" አለው፡፡ እርሱም ከሰማይ ወደ ቀደመ ኑሮው ተመለሰ፡፡ ወደቦታውም ደርሶ አባታችን ሐራ ድንግል ያደረጉለትን ታላቅ ተአምር ለሰው ሁሉ ተናገረ፡፡ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!

+++
ዲማ በሚባል ሀገር የሚኖር በንዳድ በሽታ የታመመ አንድ ሰው ነበር። ዘመዶቹም ያንን ሰው ከዲማ ወደ አቡነ ሐራ ድንግል ገዳም አመጡት። በገዳሙም ተቀምጦ ሲማጸን ከቆየ በኋላ በጻድቁ በበዓላቸው ቀን ተኝቶ ሳለ በራእይ አቡነ ሐራ ድንግል እግዚአብሔርን "በእኔ የተማጸነውን በገዳሜ ውስጥም ያለውን ይኽን ሕመምተኛ አድንልኝ፣ በማይታበል ቃልህ የምሕረት ኪዳንን ሰጥተኸኛልና" እያሉ ሲለምኑ አየ። እግዚአብሔርም የአቡነ ሐራ ድንግልን ጸሎት ተቀብሎ "ምሬልሃለሁ፣ በፈቃድህም አኑረው" አላቸው።

አቡነ ሐራ ድንግልም ወዲያውኑ የዚያን ሕመምተኛ እጁን ይዘው ወሰዱትና ገሃነምንና በውስጡ ያለው እጅግ ጽኑ መከራ አሳይተውት "የክፋት ሥራ ብትሠራ በዚያ ትኖራለህ" አሉት። ከዚያም ወደመንግስተ ሰማያት አድርሰውት በውስጧ ያለውን ክብር ፍጹም ደስታ ካሳዩት በኋላ "መልካም ሥራ ብትሠራ በዚህ የብርሃን ከተማ ከቅዱሳን ኹሉ ጋር ትኖራለህ" አሉት። ከዚያም "...ከደዌህ ያዳንኩህ የተማጸንክብኝ እኔ ሐራ ድንግል ነኝ፣ ወደቀደመ ኑሮህ ተመለስ፣ እግዚአብሔር በልመናዬ ከሞት አድኖሃልና" አሉት። እርሱም ከሰማይ ወደ ቀደመ ኑሮው ተመለሰ። ወደቦታውም ደርሶ አባታችን ያደረጉለትን ተኣምር ለሰው ሁሉ ተናገረ።
+ + +

ዳግመኛም አባታችን ሐራ ድንግል ይኽን ተኣምር አደረጉ፦ ዐይኖቿ የታወሩ አንዲት መነኰሳይት ሴት ከሌላ ሀገር ወደ አባታችን ሐራ ድንግል ገዳም መጣች። በገዳሙም የሚኖሩትን ሰዎች "አባታችን ሐራ ድንግል የታወሩ ዓይኖቼን በረድኤቱ ያበራልኝ ዘንድ በገዳማችሁ 7 ቀን አኑሩኝ፣ ዓይኖቼን እንደሚያበራልኝ በእርሱ ታምኛለሁ ተስፋም አድርጌያለሁና" በማለት ለመነቻቸው። እነርሱም ከባለ ተስፋ ሰዎች ውስጥ አንዱን ሰጥተዋትና አቡነ ሐራ ድንግልን እየተማጸነች ቆየች።

አባታችንም ጸሎቷን አሰምተው ዐይኖቿን በተኣምራት አበሩላት። ወደሌላ ገዳምም ሄዳ አባታችን ሐራ ድንግል ያደረጉላትን ለሰው ኹሉ እየተናገረች ኖረች።
+ + +

ዳግመኛም በዚኽች ዕለት ጥር 11 ቀን የከበሩ አባ ወቅሪስ እና ከፋርስ አገር ሰዎች ወገን የሆነ ቅዱስ እንጣልዮስ ዕረፍታቸው ነው፡፡
ሰማዕቱ ቅዱስ እንጣልዮስ፡- ይህም ቅዱስ አስቀድሞ በሮም አገር የሠራዊት አለቃ መኮንን ሆኖ በሥልጣን 15 ዓመት ኖረ፡፡ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ የክብርን ባለቤት ጌታችንን ክዶ ጣዖት በማምለክ በዓለም ላይ ከ470,000 ሺህ በላይ ክርስቲያኖችን በግፍ ሲያስገድል ይህ ቅዱስ እንጣልዮስ ምድራዊውን የመንግሥት አገልግሎቱን ርግፍ አድርጎ ትቶ ሰማያዊውን መንግሥት መረጠ፡፡ ስለዚህም ወደ ሃዲው ንጉሥ ወደ ዲዮቅልጥያኖስ ዘንድ ሄዶ በፊቱ በመቆም እርሱንና የረከሱ አማልክቶቹን ረገመበት፡፡ ንጉሡም ስለ ድፍረቱ ደነገጠ፡፡
ንጉሡም ቅዱስ እንጣልዮስ ከፋርስ ታላላቅ ሶች ወገን እንደሆነ ባወቀ ጊዜ በሽንገላ ቃላት ሊያባብለው ሞከረ፡፡ ቅዱሱም በእምነቱ እንደጸና ባየ ጊዜ ንጉሡ እንዲያባብልለትና እምነቱን እንዲያስተወው ለሠራዊቱ አለቃ ለኅርማኖስ ሰጠው፡፡ ይህም ኅርማኖስ የገዛ ልጁን ታላቁን ሰማዕት ቅዱስ ፊቅጦርን በችንካር አስቸንክሮ በሰይፍ ያስገደለ ከሃዲና አረመኔ ነው፡፡ እርሱም ቅዱስ እንጣልዮስን እምነቱን ለማስካድ ብዙ በማባበል የሽንገላ ቃላትን ተናገረው፡፡ ነገር ግን ኅርማኖስ በማባበልና በሽንገላ ቅዱስ እንጣልዮስን እምነቱን አስክዶ ለጣዖታት ማሰገድ ስላልቻለ ቅዱሱን ብዙ ካሠቃየው በኋላ መልሶ ለንጉሡ ሰጠው፡፡
ንጉሡም በተራው ጽኑ በሆኑ ልዩ ልዩ ማሠቃያዎች አሠቃየው፡፡ ነገር ግን ጌታችን መልአኩን ልኮ ቅዱስ እንጣልዮስን ያበረታው ነበር፡፡ ቅዱሱም በብዙ የተለያዩ ሥቃዮች እጅግ እየተሠቃየ ለረጅም ጊዜ ቆየ- ብዙጊዜ ደጋግመው ሰቅለውታልና፡፡ ከዚህም በኋላ አርደው ቆዳውን ገፈፉት፣ ምላሱንም ቆረጡት፡፡ ለነጣቂ አራዊትም ጣሉት፡፡ በጨለማ ቤትም ዘጉበት፡፡ በጽኑ ሥቃይ እያሠቃዩ ሦስት ጊዜ ቢገድሉትም እግዚአብሔር ግን መልአኩን እየላከ ቅዱስ እንጣልዮስን ከሞት ያስነሣውና ከሃድያን የሆኑ ገዳዮቹን ያሳፍራቸው ነበር፡፡ ብዙዎችም በቅዱሱ ላይ የሚታየውን ተአምር እያዩ በጌታችን እያመኑ ሰማዕት ሆኑ፡፡ በመጨረሻም ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ቅዱስ እንጣልዮስን ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ አንገቱን በሰይፍ ይቆርጡት ዘንድ አዘዘና አንገቱን ቆረጡት፡፡ እግዚአብሔርም የሰማዕትነት ፍጻሜውን በዚሁ አደረገለትና የሰማዕትነት አክሊልን በመንግሥተ ሰማያት አቀዳጀው፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!
+ + +
ጻድቁ አባ ወቅሪስ፡- ይህም ጻድቅ በታላቁ አባት በቅዱስ ባስልዮስ ዘንድ ያደገ ነው፡፡ እርሱም አስተምሮ ቅስና ሾመው፡፡ በደም ግባቱና በመልኩ የተዋበ ነው፡፡ በቀደመ ግብሩ ወጣት ሆኖ ሳለ የሹመኛውን ሚስት ተመኛት እጅግ ወደዳት፣ እርሷም ወደደችው፡፡ ከዚህም በኋላ ወደሌላ አገር ሄደው የፍላጎታቸውን ይፈጽሙ ዘንድ ተማከሩ፡፡ ለዚህም ነገር ሲዘጋጁ አባ ወቅሪስ በሕልሙ ራእይ አየ፡፡ እርሱ ታስሮ በፍርድ አደባባይ ቆሞ ነበር፡፡ ሌሎችም እሥረኞች ነበሩና ሁሉንም ወንጀላቸውን በመረመሯቸው ጊዜ አባ ወቅሪስ በልቡ ‹‹የታሠርኩት በምን ይሆን? ባሏን ልነጥቀው ስለፈለኩ ስለዚያች ሴት ነውን? አዎ እርሱ ከሶኝ ነው ወደዚህ ታላቅ ግዳጅ ላይ ያደረሰኝ … ›› እያለ መሸበር ጀመረ፡፡
አባ ወቅሪስ እየፈራና እየተሸበረ እያለ በቀድሞ ወዳጁ አምሳል አንድ ሰው መጣና ‹‹የታሰርከው በምንድነው?›› አለው፡፡ አባ ወቅሪስም ስለኃጢአቱ አፍሮ ሊሰውረው በወደደ ጊዜ ሰውየው ግድ አለው፡፡ ከዚህም በኋላ አባ ወቅሪስ ምሥጢሩን ነገረውና ‹‹ወዳጄ ሆይ! እገሌ ስለሚስቱ የከሰሰኝ ይመስለኛል፣ ስለዚህም ፈርቼ እሸበራለሁ›› አለው፡፡ በወዳጁ አምሳል ወደ አባ ወቅሪስ የመጣው መልአክም ‹‹ወዳጄ ሆይ! ይህን ሥራ እንዳትሠራ ወደ እርሱም እንዳትመለስ በቅዱስ ወንጌል ማልልኝ፣ እኔም ዋስ እሆንሃለሁ›› አለው፡፡ አባ ወቅሪስም በቅዱስ ወንጌል ስም ማለለት፡፡ በዚያን ጊዜም ከእንቅልፉ ነቃ፣ ያየው ራእይም ዕውነት እንደሆነ ዐወቀ፡፡
ስለዚህም አባ ወቅሪስ አገሩን ትቶ ወደ እስክንድርያ ሄደ፡፡ በዚያም ስሟ ኄራኒ የምትባል እግዚአብሔርን የምትፈራ ደገኛ ሴት አገኘ፡፡ እርሱም የልቡን ሁሉ ስለነገራት እርሷም ‹‹እነዚህን ያማሩ ልብሶችህን ተው፣ ተርታ ልብስንም ለብሰህ በተጋድሎ እግዚአብሔርን አገልግል›› ብላ መከረችው፡፡ ከዚህም በኋላ አባ ወቅሪስ ወደ በረሃ ሄዶ በብዙ ተጋድለ መኖር ጀመረ፡፡ ከተጋድሎውም ብዛት የተነሣ ሆዱ እንደ ድንጋይ እስከደረቀ ድረስ ቅጠል እየተመገበ ኖረ፡፡ ጌታችንም ወደ እርሱ መጥቶ ተገልጦለት ፈወሰውና አረጋጋው፣ ተስፋውንም ሰጠው፡፡

በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን (ከገድላት አንደበት), [19/01/2025, 05:58]

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

19 Jan, 03:00


አባ ወቅሪስ አጋንንት ይፈታተኑትና ያሠቃዩት ነበር፣ እርሱም በጾም በጸሎት በመጋደል ያሸንፋቸዋል፡፡ ክረምት በሆነም ጊዜ ራቁቱን ቆሞ ያድራል፡፡ ከዕለታትም በአንደኛው ቀን ሃይማኖትን በለወጡና በካዱ በአርዮስ፣ በንስጥሮስና በማኒ አምሳል ሆነው ሦስት ሰይጣናት ወደ እርሱ መጥተው በሃይማኖታቸው ተከራከሩት፡፡ ነገር ግን አባ ወቅሪስ በቅዱሳት መጻሕፍት ቃላትና ሃይማኖታቸው በቀናች አባቶች ትምህርት ረታቸውና አሳፈራቸው፡፡
ቅዱሳን መላእክት ወደ አባ ወቅሪስ እየመጡ ሰማያዊ ኅብስትና መጠጥን ይመግቡት ነበር፡፡ ሰማያዊ ሀብት ተሰጥቶ ራእዮችን ሁሉ ይተረጉም ነበር፡፡ በአንዲት ዕለትም ስሙ ቡላ የሚባል ገዳማዊ ደገኛ ሰው ወደ አባ ወቅሪስ መጥቶ ‹‹ወንድሜ ወቅሪስ ሆይ! ብቻህን አትሁን፣ ጥቂት ወንድሞችን ከአንተ ጋር አኑር፤ ያረጋጉህ ዘንድ ከሰይጣንም ጦርነት እንድትድን›› አለው፡፡ አባ ወቅሪስም እንዳለው አደረገ፡፡ እርሱም ድንቅ ድንቅ የሆኑ ታላላቅ ተአምራትን አደረገ፡፡ ወደ ቤተክርስቲያን በሄደ ጊዜ በሩ በታላቅ ቁልፍ የተዘጋ ሆነ፡፡ መነኮሳቱም ቁልፉን ፈልገው ቢያጡት አባ ወቅሪስ በበሩ ላይ አማትቦ በሩ ተከፍቶለት ገባ፡፡ ከዕለታትም በአንደኛው ቀን ‹‹አባትህ ሞተ›› ቢሉት አባ ወቅሪስ ግን ‹‹አባቴስ የማይሞት ሰማያዊ ነው›› ብሎ የወላጅ አባቱን ሞት ሊነግሩት ለመጡት መልአክተኞች ነግሯቸዋል፡፡ አባ ወቅሪስ በበረሃ ስለሚኖሩ መናንያን፣ በአንድነት ስለሚኖሩ መነኮሳትና ስለ ካህናት ሦስት ድርሰቶችንም ደረሰ፡፡ ፈጽሞ ባረጀም ጊዜ ወደ ወደደው እግዚአብሔር ሄደ፡፡ የአባ ወቅሪስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!

✞ ✞ ✞

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

06 Jan, 13:43


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ታኅሣሥ 28 እና 29-የበዓላት ሁሉ ራስ የሆነች እጅግ የከበረች የጌታችን የአምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደቱ በዓል በእነዚህ ሁለት ቀናት በታላቅ ድምቀት ትከበራለች፡፡ እንኳን አደረሰን!
‹‹ከቅድስት ሥለሴ አንዱ ወልድ መዋረዳችንን አይቶ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ባሕርዩን ዝቅ አደረገና መጥቶ በድንግል ማኅፀን አደረ፤ ከብቻዋ ከኃጢአት በቀርም እንደ እኛ ሰው ሆነ፡፡ ነቢያት ትንቢት እንደተናገሩለት በቤተልሔም ተወለደ፤ ፈጽሞ አዳነን፣ ወገኖቹም አደረገን፡፡›› ቅዱስ ኤፍሬም፡፡
አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች ክብርት እመቤታችን አምላክን ከመውለዷ ከ1520 ዓመት በፊት የፈላስፋዎችን የፍልስፍና መጽሐፈ ሕግ መርምሮ የሚያውቅ በለዓም የሚባል አንድ ታላቅ ፈላስፋ ነበረ፤ እርሱም የፈላስፎች ሁሉ አለቃ ነው፡፡
ከዕለታትም በአንደኛው ቀን ከአዳም እስከ ሙሴ ዘመን ያሉትን የሰዎች ትውልድ ቁጥር የያዙ የፍልስፍና መጻሕፍትን ሁሉ ሰበሰበ፡፡ ዳግመኛም እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ በየጊዜው የሚነሡትን የሰዎች ቁጥርና ትንቢት የያዘ መጽሐፍ አቅርቦ መረመረ፡፡ እነዚህንም መጻሕፍት ገልጦ ሲመረምር በውስጣቸው አምላክን የወለደች ክብርት እመቤታችንን አገኛት፡፡ ባገኛትም ጊዜ እርሷ ድንግል ስትሆን ልጇን ክርስቶስን ታቅፋ አያት፤ በአጠገቧም ታላቅና ብሩህ ኮከብ ነበረ፡፡ በዚያን ጊዜም በለዓም ቀደ መዝሙሩን ዘረደሸትን እና ከእርሱ በታች ያሉትን ፈላስፎች ሁሉ ሰብስቦ በብራናው ላይ የተሣለውን የእመቤታችንንና የልጇን የመድኃኔዓለምን ሥዕል በአጠገባቸውም ያለውን ኮከብ አሳያቸው፡፡ ፈላፋው መሰግልም በእርሱ ዘንድ ለተሰበሰቡት ፈላስፎች ‹‹ይህ ኮከብ በእናንተ ዘመን ወይም በልጆቻችሁ ዘመን ምልክት ቢያሳይ ወይም ቢገለጥ የዚያን ጊዜ ድንግል ከነልጇ ወዳለችበት መርቶ ያደርሳችሁ ዘንድ እርሱን ተከተሉት›› አላቸው፡፡ ይህንንም ምልክት ከነገራቸው በኋላ ፈላፋው በለዓምና የእርሱ ተከታዮች ሁሉ ሞቱ፡፡ ነገር ግን በሕይወት ያሉትና ከእነርሱም በኋላ የተነሡት ሰዎች ያችን ሥዕል በቤተ መዛግብት ውስጥ አኖሯት፡፡ ያችም ሥዕል ለሚጎበኟት ሁሉ በኋለኛው ዘመን የሚደረገውን አባቶቻቸው የተናገሩትን ትንቢት ይነግሯቸው ነበር፡፡
ከአንድ ሺህ አምስት መቶ ዓመታት በኋላ ጌታችን በቤተልሔም ሊወለድ ሁለት ዓመት ሲቀረው ያ ኮከብ በሀገራቸው ላይ በግልጽ ታየ፡፡ በዚያጊዜም ያንን ሥዕል ከቤተ መዛግታቸው አወጡና በሥዕሉ አጠገብ ያለውን የኮከብ ሥዕል ቢመለከቱ በአየር ላይ ከተገለጸላቸው ኮከብ ጋር አንድ መልክ ወይም ትክክል መሆኑን አረጋገጡ፡፡ አባታቸው ዘደረሸት እንዳስረዳቸው የሀገሩ ፈላስፎችና መኳንንቶች ሁሉ ከሠራዊቶቻቸው ጋር እጅ መንሻውን ይዘው ሥዕሉን ተሸክመው ለመሄድ ተነሡ፡፡ ኮከቡም ከሰው ቁመት ርቀቱ 75 ሜትር በሆነ ከፍታ ላይ ሆኖ በፊት በፊታቸው ይመራቸው ነበር፡፡ ከእነርሱ ወገን ያልሆነ ልዩ ጠባይ ወይም ባሕል ወይም ቁም ነገረኛ ያልሆነ ሰው የተከተላቸው ወይም በመሀላቸው የተገኘ እንደሆነ ኮከቡ ይሰወራቸው ነበር፡፡ ነገር ግን እነርሱ ከእርሱ ወገን ያልሆነውን ተመራምረው ከመካከላቸው ባስወገዱት ጊዜ ኮከቡ እንደቀድሞው ተገልጾ ይመራቸው ነበር፡፡ በመሸም ጊዜ ወደ ማደሪያ ቦታ ያደርሳቸውና ሲነጋ ዳግመኛ ይመራቸዋል፡፡ ኮከቡም መልኩ በብዙ ዓይነት ልውጥ ነበር፡፡ ሕፃን የታቀፈች ድንግል ብላቴናን ይመስላል፡፡ በእንዲህ ዓይነት ጉዞ እየተጓዙ ጌታችን ከተወለደበት ቦታ ኢየሩሳሌም በሁለት ዓመት ደረሱ፡፡
ኢየሩሳሌም እንደደረሱ ያ እየመራ ያመጣቸው ኮከብ ተሠውራቸው፡፡ እነርሱም እጅግ አዝነው የሚያደርጉትን አላወቁም ወደ ከተማ ገብተው ስለተወለደው ንጉሥ ጠየቁ፡፡ የእነዚህም ሰዎች አጠቃላይ ቁጥራቸው ሠላሳ ሺህ ነው፣ ነገሥታቱም ሦስት ናቸው፡፡ ለእያንዳንዱ ንጉሥ 10 ሺህ ሠራዊት ነበረውና ሄሮድስ ይህን ያህል ሰው የተወለደውን የአይሁድን ንጉሥ ለማየት መምጣታቸው እጅግ አስደነገጠው፡፡ መላዋ ኢየሩሳሌምም ከሄሮድስ ጋር ታወከቸ፡፡ ሄሮድስም የካህናት አለቆችንና የሕዝቡን ጸሐፊዎች ጠርቶ ‹‹ክርስቶስ በየት ይወለዳል?›› አላቸው፡፡ እነርሱም ‹‹በነቢይ ‹የአፍራታ ዕፃ ቤተልሔም አንቺም ከይሁዳ ነገሥታት አታንሺም ወገኖቼ እስራኤልን የሚጠብቅ ንጉሥ ካንቺ ይወለዳልና› ተብሎ ተነግሯልና በቤተልሔም ይወለዳል›› አሉት፡፡ ከዚህም በኋላ ሄሮድስ ሰብዓ ሰገልን ጠርቶ ኮከቡ የታየበትን ዘመን ከእነርሱ ተረዳ፡፡ ‹‹ሄዳችሁ የሕፃኑን ነገር መርምራችሁ ያገኛችሁት እንደሆነ እኔም መጥቼ እሰግድለት ዘንድ በእኔ በኩል ተመልሳችሁ ኑ›› አላቸው፡፡ እነርሱም የነገራቸውን ሰምተው ከንጉሡ ዘንድ ሄዱ፡፡ እነሆ ያ በምሥራቅ ያዩትና ይመራቸው የነበረው ኮከብ ዳግመኛ ወደ ቤተልሔልም እስኪያደርሳቸው ድረስ ይመራቸው ነበር፡፡ ሕፃኑም ካለበት ዋሻ ላይ ደርሶ ቆመ፡፡ ኮከቡንም ባዩት ጊዜ እጅግ ደስ አላቸው፡፡ ሕፃኑንም ድንግል እናቱ በክንዷ እንደታቀፈችው እነርሱ ከያዙት ሥዕል ጋር አንድና ትክክል ሆኖ ሆኖ ባገኙት ጊዜ እጅግ አደነቁ፤ ፈጽመውም ተደሰቱና እጅ ነሱት፤ ወድቀውም ሰገዱለት፡፡ ሣጥናቸውንም ከፍተው ወርቅ፣ ዕጣን፣ ከርቤውን እጅ መንሻ አቀረቡለት፡፡
ከዚህም በኋላ ወደ ርጉም ሄሮድስ እንዳይመለሱ በሕልም ተረድተው በሌላ መንገድ ወደሀገራቸው ተመለሱ፡፡ አምላክ በሥጋ ስለመገለጡ ዓዋጅ ነጋሪዎችና ሰባኪዎች ሆኑ፡፡ ይህችም ዕለት ነቢዩ ኢሳይያስ እንዲህ ብሎ ትንቢት የተናገረላት ናት፡- ‹‹እነሆ ድንግል ፀንሳ ወንድ ልጅ ትወልዳለች፣ ስሙንም ዐማኑኤል ትለዋለች፣ ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ ማለት ነው፡፡ ስለዚህችም የበከረች ድንግል ነቢይ ሕዝቅኤል ‹‹እግዚአብሔርም አለኝ ‹ይህች በር ተዘግታ ትኖራለች፣ አትከፈትም፣ የሚገባበትም የለም የእስራኤል ፈጣሪ እግዚአብሔር እንደተዘጋች ይገባባታልና ተዘግታ ትኑር››› አለ፡፡
ነቢዩ ዳንኤልም ‹‹ሌሊት በራእይ አየሁ ‹እነሆ ታላቁ እንደ ሰው ልጅ በሰማይ ደመና መጣ፤ ዘመኑን ወደሚያስረጅ ደረሰ፣ ከፊቱም አቀረቡት፣ የዘላለም አገዛዝ፣ ጌትነት፣ መንግሥት ተሰጠው፡፡ ሕዝቡና አሕዛቡ ሁሉ መንደር መንድረው የሚኖሩትና ነገዱም ነገሥታቱም ሁሉ ይገዙለታል፤ አገዛዙም የዘላለም አገዛዝ ነው፤ መንግሥቱም የማያልፍ የማይጠፋ ነው››› አለ፡፡
ዳግመኛም ኢሳይያስ ‹‹እግዚአብሔር እንደ እኔ የሥጋ መጋረጃ በመጋረድ ተገለጠልኝ›› አለ፡፡ አሁንም ደግሞ ‹‹አዲስ ሰማይ አዲስ ምድር እሠራ ዘንድ አለኝ›› አለ፡፡ ሁለተኛም ‹‹በእሴይ ሥር በትር ትወጣለች፣ ከእርሷም ጽጌ አበባ ይወጣል›› አለ፡፡ ዳግመኛም ‹‹ሕፃን ተወልዶልናልና ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና ይኸውም ሥልጣን በጫንቃው የሆነ ክርስቶስ ነው፣ ስሙም ድንቅ መካር፣ ኃያል አምላክ፣ የዘላለም አባት፣ የሰላም አለቃ ይባላል›› አለ፡፡ ነቢዩ ኤርምያስም ስለ እግዚአብሔር ‹‹በዚያን ወራት ለዳዊት ብርሃንን አወጣለሁ፣ በምድርም የቀና ፍርድን ያደርጋል፣ እግዚአብሔርም ያመኑትን ያድናቸዋል›› አለ፡፡ ኤልሳም ‹‹እግዚአብሔር ከሰማይ ይወርዳል፣ በእስራኤል ልጆች አደባባይም በመመላለስ ለሕዝቡ ዕውነትን ያስተምራቸዋል፡፡ ከአብርሃም ልጅነት ልዩ ከሆኑ ወገኖች በቀር አሕዛብ ሁሉ ይታዘዙለታል›› አለ፡፡ ናሆምም ‹‹እግዚአብሔር በእኔ አርአያ ይመጣል፣ ልብሱም እንደልብሴ ነው›› አለ፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

06 Jan, 13:43


የሚገኝበት አለ፡፡ ይኸንም ለመረዳት ወንጌላዊ ሉቃስ የጻፈውን እንመልከት፡፡ በይሁዳ ንጉሥ በሄሮድስ ዘመን ከአብያ ክፍል የሆነ ዘካርያስ የሚባል አንድ ካህን ነበረ፡፡ ሚስቱም ከአሮን ልጆች ነበረች፡፡ ስምዋም ኤልሳቤጥ ነበረ፡፡ ሁለቱም በጌታ ትእዛዝና ሕግጋት ሁሉ ያለነቀፉ እየሄዱ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ነበሩ፡፡
ኤልሳቤጥም መካን ነበረችና ልጅ አልነበራቸውም፣ ሁለቱም በዕድሜያቸው አርጅተው ነበር፡፡ እርሱም በክፍሉ ተራ በእግዚአብሔ ፊት ሲያገለግል፣ እንደ ካህናት ሥርዓት ወደ ጌታ ቤተ መቅደስ ገብቶ ለማጠን ዕጣ ደረሰበት፡፡ በዕጣንም ጊዜ ሕዝቡ ሁሉ በውጭ ቁመው ይጸልዩ ነበር፡፡ የጌታም መልአክ በዕጣኑም መሠዊያ ቀኝ ቆሞ ታየው፡፡ ዘካርያስም ባየው ጊዜ ደነገጠ፣ ፍርሃትም ወደቀበት፡፡ መልአኩም እንዲህ አለው፡፡ ዘካርያስ ሆይ ጸሎትህ ተሰምቶልሃልና አትፍራ፣ ሚስትህ ኤልሳቤጥም ወንድ ልጅ ትወልድልሃለች፣ ስሙንም ዮሐንስ ትለዋለህ ደስታና ተድላም ይሆንልሃል፣ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል፡፡ በጌታ ፊት ታላቅ ይሆናልና /ሉቃ.1፡5-15/፡፡
ወንጌላዊ ከተረከው የተገኘ ቅርጸ ሐሳብ የቱ ነው? ተብሎ ቢጠየቅ ትክክለኛ ጥያቄ ሆኖ ይገኛል፡፡ ፍሬ ሐሳቡ መልአኩ ገብርኤል ለዘካርያስ ስለመጥምቁ ዮሐንስ መወለድ ያበሠረበት ጊዜ መቼ ነው? የሚለው ነው፡፡ ይኸ በዕብራውያን ዘንድ በዓለ አስተሥርዮ ተብሎ ይከበር የነበረው ቀን መሆኑ ነው፡፡ በዓለ ሥርየትም ሲባል ደግሞ በዕብራውያን አቈጣጠር በሰባተኛው ወር ማለት /ጥቅምት አሥር ቀን የሚውል ታላቅ በዓል ነው/ /ዘሌ.16፡29-34/፡፡ /ዘኊ.29፡7-11/፡፡
እነሆ ዘካርያስ ወደ ቤተ መቅደስ በገባ ጊዜ መልአኩ ያበሠረው በዚህ ጊዜ ነው፡፡ /ሉቃ. 1፡8-10፡21/፡፡ ይህ ዘካርያስ የተበሠረበት ቀን በአይሁድ በዓለ ሥርየት የዋለበት በዕብራውያን የዘመን አቈጣጠር ጥቅምት 10 ቀን ለመሆኑ ከጥንት አባቶች ዮሐንስ አፈወርቅ ማር.ዮሐንስ መስክረዋል፡፡
አሁንም ደግሞ ይህ ቀን ከኢትዮጵያ የቀን አቈጣጠር ያለው ተዛምዶ እንደሚከተለው ነው፡፡ መጀመሪያ ነገር በባሕረ ሐሳቡ የአቈጣጠር ሕግ እንደሚታወቀው ሁሉ 5500ዓመተ ዓለምን በዐቢይ ቀመር፣ በንዑስ
ቀመር፣ በማዕከላዊ ቀመር ተተንትኖ ተከፋፍሎ ውጤቱ የ5500 ዓመተ ዓለም ተረፈ ቀመር 9 ሆኖ ስለሚገኝ አንድን ለዘመን አትቶ መንበሩ 8 ይሆናል፡፡ 8x11=88-60=28 አበቅቴው 28 ካለፈው የተያዘ 11
የጨረቃ እና ዕለቱ 28 አበቅቴ ሲደመር ሠረቀ ሌሊቱ፣ 10 ሆኖ መጥቅዑም 2 ይሆናል፡፡ በሠረቀ ሌሊቱ 10+4=14 ጨረቃ ሆነ፡፡ እንግዲህ 14 የጨረቃ ሌሊት ይዘን እስከ መስከረም 16 ቀን ብንሄድ በዚያን ጊዜ የጨረቃ ብርሃን 29 መሆኑን ያሳየናል፡፡ መስከረም 18 ቀን ደግሞ የጨረቃ ብርሃናዊ ልደት ነው፡፡ የአይሁድ የቀዳማዊ ወርኅ ታሥሪን /መባቻ/ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ፀሐያዊ አቈጣጠር መስከረም ስለ አላለቀ እንዲህ እያልን እሰከ መስከረም 27 ቀን እንሄዳለን፡፡
በዕብራውያን ጥቅምት 10 ቀን ሲሆን በእኛ ደግሞ መስከረም 27 እንደነበረ እንረዳለን፡፡ በዚሁ ዘካርያስ ልጅ እንደሚወልድ ተበሠረ፡፡ ዘካርያስም ይህን አገልግሎት ከፈጸመ በኋላ ከበዓለ ሥርየት በኋላ እስከ 15ኛው የጥቅምት ጨረቃ በዓል ስለአልነበረ ወደ ቤቱ ገባ መጥምቁ ዮሐንስ ተጸነሰ፡፡ ይህም ሊቁ ኢትዮጵያዊው ቅዱስ ያሬድ ከሁለት ቀንም በኋላ ኤልሳቤጥ ጸነሰች፡፡ በማለት አስረድቶናል፡፡ አቡን /ብርሃነ ሕይወት/ ድጓ የታኅሣሥ ገብርኤል/ ቅዱስ ያሬድ ከሁለት ቀን በኋላ ኤልሳቤጥ ጸነሰች ያለው ቀንና ዘካርያስ ልጅ እንደሚወልድ እስከ ተበሠረበት ድረስ ያለው ቀን ብንደምረው ከመስከረም ይዘነው የመጣን 27 ቀን፣ የክህነት አገልግሎቱን ፈጽሞ ወደ ቤቱ እስከ ተመለሰበት ድረስ ያለው ጊዜ 3 ቀን፣ 27+3=30 ቀናት ይሰጠናል፡፡
ሐዋርያው ሉቃስ ወደ ጻፈው ቃል እንመለስ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ኤልሳቤጥ ከጸነሰች በስድስተኛው ወር ወደ ቅድስት ድንግል ማርያም መላኩ፣ እና ቅዱስ ሉቃስም ዮሐንስ ከተጸነሰ በኋላ ኢየሱስ ክርስቶስም በስድስተኛው ወሩ ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋን፣ ከነፍስዋ ነፍስን ነሥቶ ሰው የሆነበት ዕለት፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የትርጓሜና የቊጥር መምህራን በማያሻማ መልኩ ተንትነው ቀምረው ለዚህ ትውልድ ማድረሳቸው እግዚአብሔር ከእነሱ ጋር እንደ ነበር ቋሚ ማስረጃ ነው፡፡ እንግዲህ የዮሐንስ ትንቢታዊ መጸነስ ክርስቶስ ሰው ለሚሆንበት ቀን የዕለታት ፋናው እያበራ ክርስቶስ ተጸንሶ እስከ ተወለደበት ዕለት ያደርሰናል፡፡
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መጋቢት 29 ቀን ተጸንሶ ታኅሣሥ 29 ቀን ስለመወለዱ
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መቼ ተጸንሶ መቼ እንደተወለደ ለማወቅና ለመረዳት ሐዋርያው ሉቃስ ወደተለመልን የአኀዝ ቊጥር እንመለሳለን፡፡ እነሆም በስድስተኛው ወር መልአኩ ገብርኤል በናዝሬት ወደም ትኖር ወደ ድንግል ማርያም ተልኮ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን እንደምትጸንስና እንደምትወልድ ነገራት /ሉቃስ. 1፡26-38/ ይህም ቀን በኢትዮጵያ አቈጣጠር መጥምቁ ዮሐንስ ከተጸነሰበት ዕለት ጀምሮ ተቈጥሮ መጋቢት 29 ቀን መሆኑ እንገነዘባለን፡፡ ለምሳሌ ጥቅምት፣ ኅዳር ታኅሣሥ፣ ጥር፣ የካቲት፣ መጋቢት ድምር 6 ወር ነው፡፡
ስለዚህ መጋቢት 29 ቀን ቃል /ቃለ እግዚአብሔር ወልድ/ ሰው ሥጋ የሆነበት፤ በድንግል ማኅፀን ያደረበት፤ በዓለ ትስብእት ነው፡፡ አሁን /ሰው የመሆኑ/ ሰው የሆነበት ቀን ከተረዳን፤ የተወለደበት ቀንና ወር ለማረጋገጥ ከመጋቢት 29 ቀን እስከ ታኅሣሥ 28 ቀን ጳጒሜን ጨምሮ ያለው ጊዜ 275 ቀናት ይሆናሉ፡፡ ይህም 275 ለ30 ሲካፈል 9 ወር ከአምስት ቀን ይሆናል፡፡ ይህም ማለት ከመጋቢት 2 ቀን፣ ከሚያዝያ እስከ ኅዳር መጨረሻ ወር ያሉት ወራት (8x30=240) ቀናት፣ 5 ቀናት የጳጒሜን፣ 28 ቀን ከታኅሣሥ፤ አጠቃላይ ድምር 275 ቀናት ናቸው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከርሠ ድንግል 9 ወር ከአምስት ቀን ከቈየ በኋላ በዕለተ ሠሉስ ታኅሣሥ 29 ቀን በ1ዓ.ም ከሌሊቱ 7 ሰዓት እስከ 10 ሰዓት ባለው ጊዜ በቤተልሔም ተወለደ፡፡ /ጊዮርጊስ ወልደ አሚድ ገጽ 158 እና 159/፡፡
ይህም በሒሳባዊ መንገድ የሚደረስበት ስለሆነ አያጠራጥርም፡፡ ሕጋዊ የሆነ የወንድ ልጅ በእናቱ ማኅፀን ተጸንሶ እስከሚወለድበት ጊዜ ድረስ የሚቈይባቸው ቀናት ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን ለመሆኑ ከብዙ ዘመናት ጀምሮ ታምኖበት የቈየ ነው፡፡ አንዳንድ የቀናት መብዛትና ማነስ የሚታየው ህጸጽ አይነካውም /ኢሳ 7፡14፣ ገላ4፡4/፡፡ እነሆ ምሥራቃዊ ኮከብ ሰብአ ሰገልን የተወለደው ሕፃን እስከ አለበት ቦታ እየመራ እንዳደረሳቸው ሁሉ ወንጌላዊው ሉቃስም እያነጣጠረ ያመለከተው ዘካርያስ የተበሠረበት ኮከባዊ ቀንም ፋናውን እየተቈጣጠረች ለምትከታተል ኢትዮጵያዊት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕፃኑ ኢየሱስ ክርስቶስ እስከ ተወለደበት እንዳደረሳት ታምናለች፡፡ ስለዚህ ኢትዮጵያዊት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የጌታን ልደት ታኅሣሥ 29 ቀን በታላቅ ምሥጋና ታከብረዋለች፡፡ /ማቴ. 2፡1-11፣2ጴጥ.1፡19-21/፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

06 Jan, 13:43


ኢዩኤልም ‹‹የእግዚአብሔር ዙፋን የሆነች ብላቴና ድንግልን አየሁ፣ እርሷም እንደ እሳት ያልባት ነበር፡፡ ስለእርሷ ‹ይህች ማናት?› ብዬ ኪሩብን ጠየቅሁት፡፡ እርሱም ‹ከአዳም ልጆች የተመረጠች የእግዚአብሔር ዙፋን ይህች ድንግል ናት፣ በእርሷም የተጎሳቆሉ አሕዛብ ይድናሉ፤ ለአመነባትም ረድኤትና መጠጊያ ናት› ብሎ ነገረው፡፡›› ዳዊትም በመዝሙሩ ‹‹እግዚአብሔር አንተ ልጄ ነህ፣ ዛሬም በተዋሕዶ ወለድኩህ አለኝ፡፡ ለምነኝ አሕዛብን ርስት አድርጌ እሰጥሃለሁ፣ ግዛትህም በመላው ዓለም ነው፡፡›› ዳግመኛም አብ አለ ‹‹ቀዳማዊ ወልድ በኃይል ቀን ካንተ ጋራ ሳለሁ ከአጥቢያ ኮከብ በፊት ከሆድ ወለድኩህ፣ እንደ መልከ ጸዴቅ ሥርዓት አንተ የዓለሙ አገልጋይ ካህን ነህ ብሎ እግዚአብሔር ማለ፣ ከማለም አይፀፀትም፡፡››
ቤዛ ይስሃቅ በግዕ ከኅቱም ዕፀ ሳቤቅ እንደተገኘ፣ ለእስራኤልም በበረሃ ውስጥ ከኅቱም ዓለት ውኃ እንደፈለቀ፣ የደረቀ የአሮን በትርም እንደለመለመችና እንዳፈራች፣ በሶምሶንም እጅ ውስጥ ከአህያ መንጋጋ አጥንት ውኃ እንደፈሰሰ እንዲሁ የጌታችን ልደት በኅቱም ድንግልና ሆነ፡፡ በዕፀ ጳጦስ ውስጥ እሳት እንደነደደች፣ ዕፂቱም እንዳልተቃጠለች እንዲሁ የመለኮቱ እሳት ድንግልን አላቃጠላትም፡፡
ነቢያት በትንቢታቸው ‹‹በሬ የገዢውን አህያም የጌታውን ጋጣ አወቀ›› (ኢሳ 1፡3)፣ ‹‹አቤቱ ድምፅህን ሰምቼ ፈራሁ ሥራህንም አይቼ አደነቅሁ፤ በሁለት እንስሳ መካከል አየሁህ›› (ዕን ፫፥፪) ብለው እንደተናገሩት ጌታችን በበረት ውስጥ አህያና ላም ትንፋሻቸውን ገብረውለታል፡፡ የሌሊቱን ቁር ለመግለጽ ነው፡፡ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም ዓለምን የሚገዛው በኪሩቤል ሠረገላ ላይ የሚቀመጠው የባሕርይ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ በከብቶች በረት የመወለዱን ነገር በማንሣት በአድናቆት ‹‹በበረት ውስጥ የዓለም ገዢ መተኛት እጅግ ድንቅ ነው፤ በበረት ከጽርሐ አርያም ይልቅ ረዘመ፤ ከምድር ዳርቻም ሰፋ፤ ሕዝቅኤል ካየው ሠረገላ ዳንኤልም ካየው ኪሩባዊ ዙፋን በረት በለጠ (ሕዝ 1፡18-23፣ ዳን 7፡9)፤ በረት ነባቢ ለሆነ መሥዋዕት መሻተቻ መንበርን ሆነ፤ ይኸውም የቅድስቲቱ እንቦሳ ልጅ ንጹሕ በግ ነው፤ ሰማይና ምድና የማይወስኑትን በረት ቻለው፤ ወሰነውም›› አለ፡፡ በሌሊት መንጋቸውን የሚጠብቁ እረኞች ነበሩ፡፡ መልአኩ መጥቶ እንዲህ አላቸው፡- ‹‹እነሆ! ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና፡፡ ይህም ምልክት ይሆንላችኋል፤ ሕፃን ተጠቅልሎ በግርግምም ተኝቶ ታገኛላችሁ›› አላቸው፡፡ ሉቃ2፡10-12፡፡ ከመለአኩም ጋራ ሠራዊተ መላእክት መጥተው ‹‹ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወሰላም በምድር ለዕጓለ እመሕያው-ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ›› አሉ፡፡ ቅዱሳን መላእክትም ከእነርሱ ተለይተው ወደ ሰማይ በወጡ ጊዜ እረኞቹ እርስ በርሳቸው ‹‹እንግዲህ እስከ ቤተ ልሔም ድረስ እንሂድ፣ እግዚአብሔርም የገለጠልንን ይህን የሆነውን ነገር እንይ›› ተባባሉና ፈጥነው መጡ፡፡ ማርያምንና ዮሴፍን ሕፃኑንም በግርግም ተኝቶ አገኙ፡፡ አይተውም ስለዚህ ሕፃን የተነገረላቸውን ነገር ገለጡ፤ የሰሙትን ሁሉ እረኞቹ በነገሩአቸው ነገር አደነቁ፤ የብርሃን እናቱ እመ አምላክ ግን ይህን ነገር ሁሉ በልብዋ እያሰበች ትጠብቀው ነበር፡፡ ሉቃ 2፡13-19፡፡
መላእክትም ሰማይ መንበሩ ምድር የእግሩ መረገጫ የሆኑለት አምላክ በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ በጎል ተኝቶ በጨርቅ ተጠቅልሎ አይተውት ደስ ብሏቸው ወደ ሰማይ ቢያርጉ ከባሕርይ አባቱ ከአብ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በዕሪና ከመንበሩ አይተውት ‹‹ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት›› ብለው አመስግነውት በጣዕም ላይ ጣዕም፤ በጸጋ ላይ ጸጋ ተጨምሮላቸው ደስ ብሏቸዋል፡፡ ልደቱን ይሹታልና፤ መላእክትም ብቻ አይደሉም እንስሳትም አራዊትም ደስ ብሏቸዋል፡፡ ይህም ሊታወቅ አንድ ባሕታዊ ቋርፍ ሲምስ ምዳቋ ‹‹ዮም ተወልደ መድኃኔዓለም ዮም ተወልደ ቤዛ ኵሉ ዓለም ዮም ተወልደ ከሣቴ ብርሃን›› እያለች ስትዘል አይቷል። በጌታችን በልደቱ የባሕር ውኃ ወተትና ማር ተራሮች እንጀራ እንጨቶችም የበረከት ፍሬ ሆነዋል፡፡
ልደቱንም በኮከብ ተረድተው ሰብአ ሰገል (የጥበብ ሰዎች) ስማቸውም ማንቱሲማር፣ ሜልኩ በዲዳስፋ የተባሉ የፋርስ ነገሥታት ከገነት የተገኘ ወርቅ፣ ዕጣን ከርቤ አምጥተው ገብረውለታል፡፡ ይህንንስ ከምን አገኙት? ቢሉ አዳም ከገነት ከወጣ በኋላ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ቅዱስ ገብርኤል እና ቅዱስ ሩፋኤል ወርቅ ዕጣን ከርቤ አምጥተው ሰጡት፡፡ እርሱ ለሔዋን ሰጣት። ሔዋን ለሴት ሰጠችው። ከሴት ሲወርድ ሲዋረድ ከኖኅ ደረሰ። ኖኅ ከመርከብ ከወጣ በኋላ ለሴም ሰጠው። ሴም መልከጼዴቅን አስጠበቀው፤ መልከጼዴቅ ለአብርሃም ሰጠው። ከአብርሃም ሲወርድ ሲዋረድ በዳዊት በሰሎሞን አድርጎ ከአካዝ ደረሰ። በሱ ዘመን ቴልጌልፌልሶር ማርኮ ወስዶ ከቤተ መዛግብቱ አኑሮታል። አባታቸው ዥረደሽት ይባላል፤ ፈላስፋ ነበር። አንድ ቀን በቀትር ከውኃ ዳር ሆኖ ሲላሰፍ በሰሌዳ ኮከብ ድንግል ሕፃን ታቅፋ አየ። ያየውን በሰሌዳ ቀርጾ አስቀመጠው። ሲሞት ልጆቼ እንዲህ ያለ ኮከብ ሲወጣ ባያችሁ ጊዜ ሰማያዊ ንጉሥ ይወለዳልና ይህን ወስዳችሁ እጅ ንሱ ብሎ ሰጥቷቸዋል። አንድም በለዓም ‹‹ከያዕቆብ ቤት ኮከብ ይወጣል›› ያለውን ሰምተው ይዘው መጥተዋል፡፡ ዘኅ 20፡17፡፡
አንድም ትሩፋን በባቢሎን ሳሉ ነገሥተ ተርሴስ ወደ ስያት ስጦታ (ገጸ በረከት) አመጡ፤ ንግሥተ ሳባ ወዓረብ እጅ መንሻ ያመጣሉ እያሉ ሲጸልዩ ይሰሙ ነበረና ይኸን ይዘው መጥተዋል፡፡ አንድም ባሮክ አቴና
ወርዶ ነበር። ያን ጊዜ ዛሬ የሀገራችሁን ንጉሥ የሚገብረውን ወርቅ ኋላ ከእኛ ወገን ንጉሥ ሲወለድ ይገብረዋል ብሎ የነገራቸውን ይዘው ነው። የተወለደ ዕለት ኮከቡን አይተው አባታችን የነገረን ደረሰ ብለው 12 ሆነው ሠራዊቶቻቸውን አስከትለው ተነሱ። ብዙም ሳይርቁ ጠላት ተነስቶባቸው ዘጠኙ ተመለሱ። እኒህ ሦስቱ ግን ኮከቡ እየመራቸው ኢየሩሳሌም ደርሰው በሄሮድስ በኩል አድርገው ቤተልሔም ወርደው አግኝተው ገብረውለታል። ምሥጢሩም ወርቅ መገበራቸው፡- ይኸን የምንገብርላቸው ነገሥታት ቀድሞም ፍጡራን ኋላም ኀላፍያን ናቸው። አንተ ግን ቀድሞም ያልተፈጠርህ ነህ፤ ኋላም የማታልፍ ነህ ሲሉ፤ አንድም ወርቅ ጽሩይ ነው፤ ጽሩየ ባሕርይ ነህ ሲሉ፤ እንዲሁም በአንተ ያመኑ ምዕመናንም ጽሩያነ ምግባር ወሃይማኖት ናቸው ሲሉ። አንድም ወርቅ የሃይማኖት ምሳሌ ነው። የሃይማኖት ጽሩይነቱና ግብዝነቱ የሚታወቅ መከራ ሲቀበሉበት ነውና።
ዕጣን መገበራቸው፡- ይኸንን የምናጥናቸው ጣዖታት ቀድሞም ፍጡራን ኋላም ኀላፍያን ናቸው። አንተ ግን ቀድሞም ያልተፈጠርህ ኋላም የማታልፍ ነህ ሲሉ። አንድም ዕጣን ምዑዝ ነው፤ አንተም በባሕርይ ምዑዝ ነህ ሲሉ እንዲሁ ደግሞ በአንተም የሚያምኑ ምእመናንን ምዑዛነ ምግባር ወሃይማኖት ናቸው ሲሉ። አንድም ዕጣን የተስፋ ምሳሌ ነው። ዕጣን ከሩቅእንዲሸት ተስፋ ያልያዙትን እንደያዙት ያላዩትን እንዳዩት ታደርጋለችና።

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

06 Jan, 13:43


ከኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጋር በዓለ ልደትን የሚያከብሩ አገሮች ወይም አብያተ ክርስቲያን፣ ግብጽ፣ ሶርያ፣ ህንድ፣ ኢትዮጵያ፣ አርመን ሲሆኑ ከሩቅ ምሥራቅ አብያተ ክርስቲያናት ደግሞ የግሪክ ኦርቶዶክስ የሩሲያ ቤተ ክርስቲያን ናቸው፡፡ አውሮፓውያን በዓለ ልደትን የሚያከብሩት ከእኛ 13 ቀናት ቀደም ብለው ነው፡፡ ይህም ማለት በእኛ አቈጣጠር ታኅሣሥ 16 ቀን ነው እንደ አውሮፓውያን ዘመን አቈጣጠር December 25 ቀን ነው፡፡ ልዩነቱ ለማወቅ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በዓለ ልደትን የምታከብረው ታኅሣሥ 29 ቀን ነው ይህም ማለት ከ29-16=13 ቀናት ወይም 16+13=29 ቀን ይሆናል፡፡ ይህ ቁጥር የሚያሳየን አውሮፓውያን ከእኛ በ13 ቀናት ቀድመው በዓለ ልደትን ሲያከብሩ ኢትዮጵያውያን ግን ከ13 ቀናት በኋላ ቈይተው ታኅሣሥ 29 ቀን በዓለ ልደትን ያከብራሉ፡፡

ጌታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ ታኅሣሥ 29 ቀን ለመወለዱ የመሰከሩ ሊቃውንት
1. ማሪ.ኤፍሬም ሶርያዊ
2. ሰዒ.ድ ወ/በጥሪቅ
3. መበንጋዊ/ማኅቡብ
4. ጊዮርጊስ ወልደ አሚድ
5. ወልደ መነኮስ
6. በዲድስቅልያ አንቀጽ 29 ገጽ 37
7. የኢትዮጵያ መምህራን ሁሉ ናቸው
‹‹በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩ ሰዎች ታላቅ ብርሃን ወጣላቸው፤ በቅዱሳን ላይ የሚያድር እግዚአብሔር እኛን ለማዳን ልዩ ከሆነች ድንግል ሰው ሆኗልና ኑ ይህን ድንቅ እዩ፤ ስለተገለጠልን ምሥጢር ምስጋና አቅርቡ፤ ሰው የማይሆን ሰው ሆኗልና ቃል ተዋሕዷልና ጥንት የሌለው ሥጋ ጥንታዊ ቀዳማዊ ሆነ፣ ዘመን የማይቆጠርለት መለኮት ዘመን ተቆጠረለት፡፡ የማይታወቅ ተገለጠ፣ የማይታይ ታየ፣ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ በእርግጥ ሰው ሆነ፡፡››
‹‹ሰው ሆይ! ፈጽመህ ደስ ይበልህ፣ እግዚአብሔር ዓለሙን ወዶታልና አንድ ልጁንም የሚያምንበት ሁሉ እስከ ዘለዓለም ፈጽሞ ይድን ዘንድ አሳልፎ ሰጥቷልና ልዑል ክንዱን ሰደደልን፡፡››
ሰው ሆይ! ፈጽመህ ደስ ይበልህ!!!
ፍጹም መዳን ይሆንላችሁ ዘንድ በስሙ አምናችሁ ለአምላክነቱ የምትገዙለት የክርስቶስ ወገኖች በእናቱም በወላዲተ አምላክ በድንግል ማርያም ፍጹም አማላጅነት የምትታምኑ የተዋሕዶ ልጆች ሁላችሁ እንኳን ደስ አላችሁ፣ እንኳን ደስ አለን፡፡ እንኳን አደረሳችሁ፣ እንኳን አደረሰን፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

06 Jan, 13:43


ከርቤ መገበራቸው፡- ምንም ቀድሞ ያልተፈጠርህ በኋላም የማታልፍ ብትሆንም በሰውነትህ መራራ ሞትን ትቀበላለህ ሲሉ፤ አንድም ከርቤ የተሰበረውን ይጠግናል፤ የተለየውን አንድ ያደርጋል። አንተም ከማኅበረ መላእክት የተለየ አዳምን አንድ ታደርገዋለህ፤ ጽንዓ ነፍስ ሰጥተህ ታጸናዋለህ ሲሉ። አንድም በዕለተ ዓርብ ያቀምሱታልና ከርቤ አመጡለት። ከርቤ የምዕመናን ምሳሌ ነው። በፍቅር አንድ ይሆናሉና። ከርቤ የፍቅር ምሳሌ ነው። ከርቤ አንድ እንዲያደርግ ፤ ፍቅርም አንድ ታደርጋለችና። በአጠቃላይ ሰብአ ሰገል ወርቅ፣ እጣን ከርቤ የገበሩለት ሃይማኖት፣ ፍቅር፣ ተስፋ፣ ገንዘቦችህ ናቸው ሲሉ ነው። በሌላ መልኩ ወርቅ ለመንግሥቱ፣ ዕጣን ለመለኮቱ፣ ከርቤ ለሞቱ ምሳሌ ናቸው።
ሰብዓ ሰገል እጅ ነስተው ከወጡ በኋላ አንዱ እንዴት ያለ ሽማግሌ ነው ብሎ አደነቀ። ሁለተኛው የምን ሽማግሌ ጎልማሳ ነው እንጅ አለ። ሦስተኛው ደግሞ ሕፃን ነው እንጂ አለ። ገብተን እንይ ተባብለው ቢገቡ ሽማግሌ መስሎ ለታየው ጎልማሳ፤ ጎልማሳ መለስሎ ለታየው ሕፃን፤ ሕፃነ መስሎ ለታየው ሽማግሌ መስሎ ታያቸው። ወጥተው እንዳንተ ነው እንዳንተ ነው ይባባሉ ጀመር። መልአኩ መጥቶ እንደሁላችሁም ነው አላቸው። በጆሮ የሰሙትን በዓይን ቢያዩት ይረዳል ብለው ለሦስተኛ ጊዜ ገቡ። ሽማግሌ ጎልማሳ መስሎ ለታየው ሕፃን፤ ጎልማሳ ሕፃን መስሎ ለታየው ሽማግሌ፤ ሕፃን ሽማግሌ መስሎ ለታየው ጎልማሳ መስሎ ታያቸው። እጹብ እጹብ ብለው አመስግነው፤ አምላክነቱን ተረድተዋል። በሚሄዱበትም ጊዜ እመቤታችን የገብስ እንጀራ ጋግራ ሰጠቻቸው። ሀገራቸው እስኪገቡ ድረስ ከሠራዊቶታቸው ጋር (እያንዳንዳቸው አስር ሺህ፤ አስር ሺህ ሠራዊት) ሲመገቡ ቆይተው ከከተማቸው ሲደርሱ ይህን ቅዱስ ምግብ ከከተማችን አናስገባም ብለው ከከተማው በር ቀብረውት ገቡ። ደርሳችሁ መጣችሁን? አሏቸው። አዎን በአርባ ቀን መጣነው፤ እናቱም የሰጠችንን የገብስ እንጀራ እኛ እና ሠራዊቶቻችን ስንመገበው መጥተን ከከተማችን አናገባም ብለን ከከተማው በር ቀብረነዋል አሏቸው። አሳዩን አሉ። ተያይዘው ቢሄዱ ሲጨስ አግኝተውታል።
የልደት በዓል መቼ መከበር ጀመረ? ቀኑስ ምን ቀን ይውላል?
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተወለደበትን እርግጠኛውን ዕለት ለማወቅ የአስትሮኖሚ፣ የአርኬዎሎጅና የታሪክ ምርምር ሰዎች /ሊቃውንት/ ብዙ ጥናት አድርጓል፡፡ ዳሩ ግን በአንድ ሐሳብ ሊስማሙ ባመቻላቸው፣ የክርስቲያኑ የቀን መቈጠሪያዎች በዚሁ ሁኔታ አንድ ሳይሆኑ ቀርተዋል፡፡ ይሁን እንጂ በኢትዮጵያ መከበር የተጀመረው ከአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ እንደሆነ ታሪክ ያስረዳል፡፡ ለዚህም በጎርጎርዮሳውያን የዘመን ለቈጣጠር የሚጠቀሙት የዓለም ሕዝቦች የክርስቶስን ልደት እኛ ኢትዮጵያውያን ከምናከብረው የልደት በዓል 13 ቀን ቀድመው ያከብራሉ፡፡
የሮም ቤተ ክርስቲያን የጌታችን ልደት በታኅሣሥ 25 ቀን ታከብር እንደ ነበር ከ336ዓ.ም ጀምሮ ግልጽ ነው፡፡ ይህ ቀን በአህዛብ ዘንድ የፀሐይ በዓል እየተባለ ይከበር ስለነበር ክርሰቲያኖች ይኽንን የጣኦት አምልኮ ጠባይ ያለውን በዓል ለማጥፋት ሲሉ የጌታን ልደት በዚሁ ቀን ማክበር ጀመሩ፡፡ የምሥራቅ ቤተ ክርስቲያንም ቅድሚያ ሰጥታ የምታከብረው እ.ኤ.አ ጥር 6 ቀን የሚውለን የኤጲፋንያ በዓል ነበር፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን የጌታን ጥምቀቱና ልደቱን ጥር 6 ቀን ስታከብር እንደቆየች የእውቀትና የታሪክ መድበል /ኢንሳይክሎፕዲያ/ ይገልጻል፡፡
ቤተ ክርስቲያን አንዲት ስትሆን በክርስቲያን ዓለም ውስጥ እንዲህ ያለ ልዩነት እንዴት ሊፈጠር ቻለ?
በመሠረቱ ዓለም ከመለያየት በስተቀር አንድ ለመሆን ያሰበበት ወቅት ምን ጊዜ የለም፡፡ (በታሪክ እንደምንረዳው) ልዩነቱ እንዴት እንደሆነ እንመልከት ከጌታ ልደት አስቀድሞ /በፊት/ በ46ዓ.ዓ ጁሊዮስ የተባለው የሮማ ቄሣር በጊዜው የከዋክብት መርማሪ የነበረው ሶስግነስን አስጠርቶ ተመሰቃቅሎ የነበረውን የዘመናት አቈጣጠር እንዲያስተካክል አዘዘው፡፡ ይኸም፣ ሊቅ ፈቃደኛ ሆኖ ዓመቱንም በ12 ወሮች ከፋፍሎ እያንዳንዱን ወር ከየካቲት በስተቀር በማፈራረቅ 31 እና 30 ቀናት እንዲኖራቸው አድርጎ አዘጋጀ፡፡ የካቲት ወር ግን 29 ቀን እንዲኖረው አደረገ፡፡ ነገር ግን በየአራቱ ዓመቱ አንድ ቀን ትርፍ ስለሚመጣ በአራተኛው ዓመት የካቲት 30 ቀን እንዲሆን ወሰነ፡፡ ጁሊየስ ቄሣርም የሮማው ሕዝብ በዚሁ እንዲገለገል አዋጅ አወጀ፡፡
በተጨማሪም ጁሊየስ የዓመት መለወጫ መጋቢት የነበረውን ለውጦ /አዛውሮ/ ጥር እንዲሆን አደረገ፡፡ በዚሁም የጁሊየስን የዘመን አቈጣጠር ብዙ ሀገሮች ለ1500 ዓመታት ያህል ሲገለገሉበት ቈይተዋል፡፡ ምክንያቱም የዓመቱ ቀናት ተቀምረው 365 ቀን ከሩብ ሊሆን መቻላቸው ነበር፡፡ ይህም ሆኖ የጁሊየስ አቈጣጠር ህጸጽ አልታጣበትም ምክንያቱም 11 ደቂቃ ከ14 ሰኮንድ ትርፍ ያሳይ ነበርና፡፡ ከዚህም የተነሳ እ.ኤ.አ በ1582ዓ.ም የነበረው የሮማው ፖፖ ጎርጎርዮስ /ስምንተኛ/ የከዋክብትን ሊቃውንት ሰብስቦ ከተመካከረበት በኋላ የዘመኑ አቈጣጠር ተሻሽሎ እንዲሰራበት አዋጅ አስተላለፈ፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን በጎርጎርዮስ የዘመን አቈጣጠር መቈጠር ጀመረች፡፡ በእምነት ተከታዮቻቸው የሆኑትም አገሮች ተቀብለው ወድያውኑ በሥራ ላይ ሲያውሉት የጀርመን ግዛቶች ግን እስከ
17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ድረስ በጁሊዮስ አቈጣጠር ይጠቀሙ ነበር፡፡ እንግሊዝም ብትሆን አዋጁን የተቀበለችው በ1752ኛ.ም እ.ኤ.አ ነው፡፡ ከዚያ ወዲህ ግን ምዕራባውያን አገሮች ተቀብለውታል፡፡
ይህም ሊሆን የቻለው በ1582ዓ.ም የተጨመሩት 10 ቀናት ተጠራቅመው ጎርጎርዮስና ጁሊዮስ በተባለው የዘመን አቈጣጠር መኻከል ልዩነት ስለፈጠሩ ነው፡፡
በዘመን አቈጣጠር ልዩነት የተነሣ የምዕራባውያንና ኢትዮጵያውያን የልደት በዓልን በማክበር በ13 ቀናት ይለያያሉ፡፡ ይሁን እንጂ በመጀመሪያው እንደተናገርኩት ዓለም ብዙ ጊዜ ስለ ዘመን አቈጣጠር ችግር ገጥሟት እንደ ነበረ ግልጽ ቢሆንም ኢትዮጵያ ግን በዘመነ ኦሪትም ሆነ በዘመነ ሐዲስ እንደ ንጋት ኮከብ የሚያበሩ ልጆች ስለነበሯት በቊጥር ግራ አልተጋባችም፡፡ ቀድሞም ዛሬም ባህልዋንና ቀመርዋን እንደያዘች ትገኛለች፡፡ ስለዚህ የኢትዮጵያ አቈጣጠር ደግሞ እንደሚከተለው እንመልከት፤
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አቈጣጠር
በዘመናችን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የጌታ ልደት ሌሎች አብያተ ክርስቲያናት እንደሚያከብሩት ለምን አታከብርም? የሚል ጥያቄ በየአቅጣጫው ከተሰማ ውሎ አድሯል፡፡ አንድ ነገር መታወቅ ያለበት ግን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በዓለ ልደትን 29 ቀን የምታከብረው ብቻዋን ሳትሆን ከእስክንድርያ ቤተ ክርስቲያን ጋር በመሆኑ ነው፡፡
በቀን አከባበር ስለተፈጠረው መለያየት ምክንያቱንና የነገሩን ምንጭ ከእነማስረጃው አትቶ "በእንተ ልደት ድንግልናዌ" በሚል ርዕስ የእስክንድርያው ሊቅ ዮሐንስ አቤል ሄረም ጽፎት ይገኛልና ከዚያ መመልከት ይጠቅማል /አንቀጽ 84/ ዓይነተኛ ጉዳዩ ግን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በመጽሐፍ ቅዱስ ማስረጃነት የተመሠረተ ነው ብላ ስለአመነችበት እንጂ ብዙ ዘመናት ሲሠራበት በመቈየቱ ወይም ደግሞ የእስክንድርያ ቤተ ክርስቲያን ስለምታከብረው ብቻ አይደለም፡፡ በቅዱሳት መጻሕፍት ስለ አለው ማስረጃ እንደሚከተለው እንረዳለን፡፡ መጥምቁ ዮሐንስ የተጸነሰበትም ቀን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በድንግል ማኅፀን ለተጸነሰበትና ለተወለደበት ቀን መነሻ ሆኖ

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

06 Jan, 03:18


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ታኅሣሥ 28- በዚች ዕለት የገና በዓል ሆነ። ይኸውም የልደት በዓል ነው።
+ ከእንዴናው አገር ሰዎች መቶ ሃምሳ ወንዶች ሃያ አራት ሴቶች በሰማዕትነት ሞቱ።
ታኅሣሥ ሃያ ስምንት በዚህች ዕለት የገና በዓል ሆነ። ይኸውም የልደት በዓል ነው። ይህም እንዲህ ነው በአምላካችን በረቀቀ ጥበቡ ሰዎች ሁሉ ይቈጠሩ ዘንድ ስማቸውንም ይጻፋና ይመዘገቡ ዘንድ ከንጉሥ ቄሣር ትእዛዝ መጣ። ስለዚህም ከእመቤታችን ከከበረች ድንግል ማርያም ጋር ሊቆጠር ዮሴፍ ከናዝሬት ወደ ቤተልሔም የርሱንና የቡርክት ድንግል ማርያምን ስም ሊያስመዘግብ ወጣ እርሱ ከይሁዳ ነገድ ከዳዊት ወገን ነውና ቤተልሔምም የዳዊት ቦታው ናትና።
የከበረ ወንጌል እንደተናገረ ከዚህም በኋላ ከዚያ ሳሉ የምትወልድበት ቀን ደረሰ የበኵር ልጇንም ወለደች አውራ ጣቱንም አሠረችው በጨርቅም ጠቅልላ በበረት አስተኛችው ለማደሪያቸውም ቦታ አልነበራቸውምና። በዚያ ሰፈር እረኞች ነበሩ ሌሊትም በየተራቸው ተግተው መንጋቸውን ይጠብቁ ነበር። እነሆ የእግዚአብሔር መልአክ አጠገባቸው ቆመ የእግዚአብሔርም ብርሃን በላያቸው በራ ታላቅ ፍርሀትም ፈሩ መልአኩም "ለእናንተና ለመላው ዓለም ደስታ የሚሆን ታላቅ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ" አላቸው።
"እነሆ ዛሬ በዳዊት አገር መድኅን የሆነ ጌታ ክርስቶስ ተወልዶላችኋልና። ለእናንተም ምልክት እንዲህ ነው ሕፃኑ አውራ ጣቱን ታሥሮ በጨርቅ ተጠቅልሎ በበረት ውስጥ ተኝቶ ታገኙታላችሁ" አላቸው። ድንገትም ከዚያ መልአክ ጋር ብዙ የሰማይ ሠራዊት እግዚአብሔርን እያመሰገኑ "በሰማይ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በምድርም ሰላም በሰው በጎ ፈቃድ እያሉ መጡ።
ከዚህም በኋላ መላእክት ከእነርሱ ዘንድ ባረጉ ጊዜ እነዚህ እረኞች ሰዎች እርስበርሳቸው "ኑ ወደ ቤተ ልሔም ሔደን ይህን እግዚአብሔር የገለጠውን ነገር እንወቅ" አሉ። ፈጥነውም ሔዱ ማርያምንና ዮሴፍን ሕፃኑንም በበረት ውስጥ ተኝተወው አገኟቸው። አይተውም የነገሩዋቸው ስለዚህ ሕፃን እንደሆነ አወቁ እረኞች የነገሩዋቸውን የሰሙ ሁሉ አደነቁ። እረኞችም ለሕፃኑ ሰግደው እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ወደ ቦታቸውም ተመለሱ።
ከወገናችን ሰው ሁኖ ለጐበኘንና ይቅር ላለን እግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።
+ + + + +
በዚችም ዕለት ደግሞ ከእንዴናው አገር ሰዎች መቶ ሃምሳ ወንዶች ሃያ አራት ሴቶች በሰማዕትነት አረፉ።
እሊህም ቀድሞ ከሀዲያን ነበሩ የእንዴናው መኰንን የከበረ ሶርያዊ ጳውሎስን በሚያሠቃየው ጊዜ ከዚያ ነበሩ ሲአሠቃየውም ይመለከቱ ነበር መኰንኑም ችንካሮችን በእሳት አግለው ዐይኖቹን እንዲአወልቁ አዘዘ ይህንንም ባደረጉበት ጊዜ ዐይኖቹ ወለቁ ከወህኒ ቤትም ጣሉት። በማግሥቱም እሊኒ ሰዎች ሊያዩት በሔዱ ጊዜ ያለ ምንም ጉዳት ድኖ ጤነኛ ሁኖ አገኙት የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አድኖታልና።
ይህንንም ድንቅ ተአምር አይተው እጅግ አደነቁ ጣዖቶቻቸውም ምንም መሥራት እንደማይችሉ አስተዋሉ። የክርስቲያኖች አምላክ እርሱ እውነተኛ አምላክ እንደ ሆነ አወቁ ወደከበረ ጳውሎስ ሒደው ሰገዱለት እንዲጸልይላቸውም ለመኑት እርሱም ባረካቸው እግዚአብሔር እምነታችሁን ተቀብሎ ከሰማዕታት ጋር ይቊጠራችሁ አላቸው።
ከዚህም በኋላ ወደ መኰንኑ ቀርበው በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመኑ መኰንኑም ራሶቻቸውን ቊረጡ ብሎ አዘዘና ቈረጧቸው በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕታት ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን።

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

04 Jan, 18:55


የእግዚአብሔር ሰው አባ በግዑ በእንዲህ ዓይነት ጽኑ በሆነ የተጋድሎ ሕይወት ሲኖር ሰውነቱ ላይ ከቆዳውና ከአጥንቱ በቀር የሚታይ ነገር እስኪጠፋ ድረስ ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለ፡፡ ውኃንም እስከ ሰባት ዓመት ድረስ አልጠጣም፡፡ መቆምም አይችልም ነበርና መነኮሳቶቹ ለቁርባን በቃሬዛ አድርገው ወደ ቤተ ክርስቲያን ይወስዱት ነበር፡፡ የእግዚአብሔር ሰው አባ በግዑ በእንደዚህ ዓይነቱ ለመስማት በሚከብድ እጅ የበዛ ጽኑ ተጋድሎ ካደረገ ከብዙ ድካም በኋላ በዚህች ዕለት ታህሳስ 27 ቀን ዐረፈ፡፡ ጌታችንም ተገልጦ ታላቅ ቃልኪዳን ሰጠው፡፡
ለሰው ምንም ውኃ ሳይጠጣ ሰባት ዓመት መኖር ይቻለዋልን!? ‹‹በብዙ ሲጋደሉ እንደኖሩ የቅዱሳንን ገድላቸውን ሰምተናል፡፡ ነቢይ ዕዝራ የዱር ዛፍ ፍሬ እየተመገበ ውኃም እየጠጣ በምድረ በዳ እየጾመ ኖረ፡፡ ነቢይ ኢሳይያስም የሜዳ ጎመን እየቆረጠ ከእርሱም እየተመገበ ውኃም እየጠጣ በተራራ እየጾመ ኖረ፡፡ እግዚአብሔር ስሙን ‹የበረሃ ኮከብ› ብሎ የጠራው የመነኰሳት በኩር የሆነ አባ እንጦንስና አባ መቃርስም በደረቅ ኅብስትና በውኃ ብቻ ሲጋደሉ ኖሩ፡፡ እኚህ ምድራዊያን ሲሆኑ ሰማያውያን ሆኑ፡፡ ነቢይ ኤልያስም በኅብስትና በውኃ ብቻ በምድረ በዳ ሲጋደል ኖረ፡፡ ይህ የእግዚአብሔር ሰው አባ በግዑ ግን ሰባት ዓመት ሙሉ ውኃ ሳይቀምስ ኖረ፡፡ ከመነነ በኋላ እስከሞተበት ዕለት ድረስ እህል የሚባል አልቀመሰም፡፡ እርሱ ግን ራሱን በእግዚአብሔር ፊት ዝቅ ያደርግና በትህትናም ሆኖ ስለ ኃጢአቱ ሁልጊዜ ያለቅስ ነበር፡፡ ይህም የእግዚአብሔር ሰው አባ በግዑ ይህን ሁሉ የተጋደለ በራሱ ኃይል አይደለም፤ በእግዚአብሔር ኃይል ነው እንጂ፡፡ አንተም ወንድሜ ሆይ ራስህን ዕወቅ፡፡ ምንም ተጋድሎን ብታደርግ ጾምኩ፣ ተራብኩ፣ ስለ እግዚአብሔርም ብዬ ራሴን አደከምኩ፣ እግዚአብሔርንም ስላገለገልኩ በሥራዬም እድናለሁ አትበል፡፡ መጨረሻህን አታውቅም፡፡ አንተ ግን ስለ እግዚአብሔር ብለህ ራስህን ኃጥእ አድርግ ያን ጊዜ እግዚአብሔር ያጸድቅሃልና፡፡ ወዳጄ ሆይ በእግዚአብሔር ዘንድ እንድትመሰገን ራስህን አታመስግን፤ ሌሎችም ያመሰግኑህ ዘንድ አትውደድ፡፡ ክብር ታገኝ ዘንድ ትሕትናን ገንዘብ አድርግ፡፡››

የእግዚአብሔር ሰው የአባ በግዑ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!

+ + +

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

04 Jan, 18:55


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ታኅሣሥ 27-አስቀድሞ ሽፍታ የነበረውና በኋላም በንስሓ ተመልሶ 7 ዓመት ሙሉ ምንም ውሃ ሳይቀምስ እስከመኖር ድረስ በታላቅ ተጋድሎ የኖረው የእግዚአብሔር ሰው አባ በግዑ ዕረፍቱ ነው፡፡

+ ሰማዕቱ አባ አብሳዲ ዕረፍቱ ነው፡፡
አባ አብሳዲ፡- ከላይኛው ግብፅ የተገኙት ይህ ጻድቅ ምግባር ሃይማኖታቸው፣ ትሩፋት ተጋድሎአቸው ያማረ ነው፡፡ በዘመናቸው ከሃዲዎች የነገሡበት ዘመን ነበር፡፡ አባ አብሳዲም ከአባ አላኒቆስ ጋር ሆነው ሕዝበ ክርስቲያኑን በቀናች ሃይማኖት እስከመጨረሻው እንዲጸኑ አደረጓቸው፡፡ እነዚህም ቅዱሳን የሆኑ ኤጲስቆጶሳት የአማልክትን አምልኮ እንዲሽሩና በጌታችን እንዲሚታመኑ ከሃዲው ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ በሰማ ጊዜ መልአክተኞችን ልኮ አስመጣቸው፡፡ ከእምነታቸውም ሊያወጣቸው በሞከረ ጊዜ እነርሱ ግን በእምነታቸው ጸኑ፡፡ በዚህም ጊዜ ንጉሡ ጽኑ በሆኑ ልዩ ልዩ ሥቃዮች አሠቃያቸው፡፡ አባ አብሳዲ ግን ቀድሶ ሕዝቡን እስኪያቆርብ ድረስ ትንሽ ጊዜ እንዲሰጡት የንጉሡን ጭፍሮች ለመናቸው፡፡ እርሱም ቀድሶ ካቆረባቸው በኋላ በሃይማኖት እስከ መጨረሻው እንዲጸኑ ካስተማራቸው በኋላ ተሰናብቷቸው መከራን ወደሚቀበልበትና ሊሞትበት ወዳለው ቦታ ወጥቶ ሄደ፡፡
ጭፍሮቹም አባ አብሳዲን ወደ እንዴናው ገዥ ወደ ጨካኙ አርያኖስ ዘንድ ወሰዱት፡፡ መኮንኑ አርያኖስም አባን ባየው ጊዜ ከግርማው የተነሣ አደነቀ፣ ራራለትም፡፡ ‹‹የከበርክና የምታስፈራ መነኮስ ሆይ! ለነፍስህ እዘን፣ የንጉሡንም ቃል ስማ›› አለው፡፡ አባ አብሳዲም ‹‹እኔ የንጉሡን ቃል ሰምቼ በዚህ በኃላፊው ዓለም ሕይወት መንግሥተ ሰማያትን አለውጥም›› አለው፡፡ መኮንኑም ብዙ አባበለው ነገር ግን አባ አብሳዲ በነገሩ እንዳልተባበረና በእምነቱ እንደጸና ባየ ጊዜ መኮንኑ በመኮራኩር አሠቃየው፡፡ ከእሳት ምድጃ ውስጥም ጨመረው፣ ነገር ግን እግዚአብሔር ያለምንም ጉዳት በጤና አስነሣው፡፡ ከዚህም በኋላ መኮንኑ አንገቱን በሰይፍ ይቆርጡት ዘንድ አዘዘ፡፡ አባ አብሳዲም ይህንን በሰማ ጊዜ በጣም ተደሰተ፤ ልብሰ ተክህኖውንም ለበሰና እጆቹን ዘርግቶ አንገቱን ለሰያፊዎቹ ሰጣቸው፡፡ እርነርሱም የከበረች ራሱን በዚህች ዕለት ቆረጡት፡፡ አባ አብሳዲም የሰማዕትነት አክሊልን በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ፡፡ የአባ አብሳዲ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!
+ + +
የእግዚአብሔር ሰው አባ በግዑ፡- አባ በግዑ በመጀመሪያ ሽፍታ የነበረ ሲሆን በመንገድ ላይ ንብረት የያዘን ሰው ማንንም የማያሳልፍ ቀማኛ ሰው ነበር፡፡ ከኃይለኛነቱ የተነሳ ሕዝቡም ሁሉ ይፈራው ነበር፡፡ በእጁ ሰይፍና ጦር ይዞ ሊዘርፍ ወደ ወደደው ሀገር ይገባል፡፡ እየዘረፈ በሚያገኘው ገንዘብም ራሱን በተለያዩ ምግቦችና መጠጦች ያስደስት ነበር፡፡ ባማሩ ልብሶችም ይዋብ ነበር፡፡ ገንዘቡ የተወሰደበት ሰውም እርሱ እንደወሰደበት ባወቀ ጊዜ ዳግመኛ መጥቶ የተረፈውን ቀምቶ እንዳይወስድበት ምንም አይከሰውም ነበር፡፡ በጉልምስናው ኃይለኛና ብርቱ ስለነበር ወደ እርሱ ማንም አይቀርብ ነበር፡፡
በእንደዚህ ያለ የውንብድና ሥጋ ብዙ ዓመታት ከኖረ በኋላ አባ በግዑ በስም ክርስቲያን ነበረና ከዕለታት በአንደኛው ቀን መንፈስ አነሳስቶት ወደ ቤተ ክርስቲያን ሄደ፡፡ ካህኑም ባየው ጊዜ ከመንገድ ገለል አደረገውና ‹‹የሕይወት ዘመንህን ሁሉ በከንቱ አሳለፍክ ዛሬ ስማ ልንገርህ፣ በዘመንህ ፍጻሜ እግዚአብሔር ይጎበኝሃል፣ በመንፈስ ቅዱስም ያድርብሃል፣ ፍጹም መነኩሴ ትሆናለህ፣ በብዙ መከራና ተጋድሎ ትኖራለህ በዚያም የነፍስህ መዳኛ ይሆናል፣ እግዚአብሔርንም ደስ ታሰኘዋለህ›› አለው፡፡ ከዚህም የበዛውን ብዙ ነገር ነገረው፡፡
ከዚህም በኋላ ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ቁርባን ተቀበለ፡፡ ወደቤቱም ከተመለሰ በኋላ ካህኑ የነገሩትን እያሰበ ‹‹እስከመቼ በስንፍናዬ እኖራለሁ? እስከመቼስ የነፍሴን መዳኛ ሳላስብ እኖራለሁ? …›› እያለ አሰበ፡፡ ከዚህም በኋላ ከዘመዶቹ ተለይቶ ከሀገሩ ወጥቶ ሄደና ወደ ባሕር ዳርቻ ደርሶ የቅዱስ እስጢፋኖስን ቤተ ክርስቲያን እጅ ነሣ፡፡ ከመነኮሳትም ማኅበር ገብቶ እነርሱን ማገልገል ጀመረ፡፡ አባ በግዑ በእግዚአብሔር ጥሪ ወደ ልቡ ተመልሶ ከመነነ በኋላ ግን እስከሞተበት ዕለት ድረስ የላመ እህል ሳይቀምስ ኖረ፡፡ ምግቡን የዛፍ ፍሬና ሜዳ ላይ የሚበቅል ቅጠል አደረገ፡፡ ዓቢይ ጾም ሲመጣም ከሰኞ እስከ ቀዳሚት ሰንበት ምንም ሳይቀምስ የሚጾም ሆነ፡፡ ውኃንም ሳይጠጣ ኖረ፣ ማንም ሰው ሳያውቅብ ለ5 ወር ምንም ውኃ ሳይጠጣ ተቀመጠ፡፡ ከ5 ወር በኋላም የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ወደ አባ በግዑ መጣና ‹‹የእግዚአብሔር ሰው ሰላም ለአንተ ይሁን! በምን ትታወካለህ? ምንስ ያሳዝንሃል? ››አለው፡፡ አባ በግዑም ‹‹ጌታዬ ከውኃ ጥም የተነሣ በጣም ስለተጨነቅሁ ነው›› አለው፡፡ መልአኩም ነጥቆ ወደ ገነት ወሰደውና ከገነት ቅጠል አንሥቶ አቀመሰው፡፡ ወዲያም የአባ በግዑ ሰውነት ታደሰች፡፡ ከዚህም በኋላ ‹‹ውኃ ሳልጠጣ ተጋድሎዬን እፈጽም ይሆን!›› የሚለው የኅሊና መታወክ ከእርሱ ጠፋለት፡፡
ከዕለታትም በአንደኛው ቀን አባ በግዑ ለሚወደው ለአንድ ወዳጁ ለማንም እንዳይናገር በእግዚአብሔር ስም ካስማለው በኋላ ለ5 ወር ምንም ውኃ እንዳልጠጣ ምሥጢሩን ነገረው፡፡ ያ ወዳጁም ይህን ሲሰማ ደንግጦ አለቀሰ፡፡ አባ በግዑም አብሮት አለቀሰ፡፡ ወዳጁም ‹‹እስከዛሬ ከውኃ የተከለከለ በማን ዘንድ ሰማህ? አሁንም ቅዱሳን መነኮሳትና አበ ምኔቱ አያምኑህም፡፡ ይህን ምሥጢር ዛሬ ብሸሽግ በመጨረሻ ይገለጣል፡፡ ሕዝቡ፣ ነገሥታቱና መኳንንቱም ይህን ነገር ይሰማሉ ነገር ግን አያምኑም፡፡ አሁንም የምነግርህን ስማኝና ትኅርምቱን ትተህ ውኃ ጠጣ›› አለው፡፡ የእግዚአብሔር ሰው አባ በግዑም ‹‹የነገርከኝ ሁሉ እውነት ነው ሐሰት የለውም ነገር ግን እኔ ከዚህ በኋላ እስክሞት ድረስ ዳግመኛ ውኃ እንዳልጠጣ ስለ እግዚአብሔር ትቻለሁ፡፡ ሰዎች ባያምኑ እኔ ምን ገዶኝ፣ ነገር ግን በዚህ ገድል እግዚአብሔር ረዳት ይሆነኝ ዘንድ ጸልይልኝ›› አለው፡፡
ከዚህም በኋላ የእግዚአብሔር ሰው አባ በግዑ ብረት አመጣና ሰንሰለቶችን ይሠራለት ዘንድ ለአንጥረኛ ሰጥቶ አሠራ፡፡ ያንን ወዳጁን ጠራውና እጆቹንና እግሮቹን በብረት ችንካር እንዲያስረው አዘዘው፡፡ ‹‹አበ ምኔቱን ጥራልኝ›› አለውና ጠራለት፡፡ አባ በግዑም አበ ምኔቱ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ሲመጣ በፊቱ ሰገደለትና ‹‹አባቴ ሆይ! የእግዚአብሔርን ትእዛዝ እፈጽም ዘንደ በላዬ ላይ ጸልይልኝ›› አለው፡፡ ‹‹ከዛሬ ጀምሮ ከበዓቴ አልወጣም፣ ሰውም ወደኔ አይገባም›› አለው፡፡ አቡነ ኢየሱስ ሞዐም በላዩ ከጸለየለት በኋላ ‹‹ለእኔም ጸልይልኝ›› አለው፡፡ አባ በግዑም በቅዱስ ሚካኤል በዓል ቀን በአባ ኢየሱስ ሞዐ እጅ ቁርባንን ከተቀበለ በኋላ እጆቹንና እግሮቹን በብረት ችንካር ታስሮ ብቻውን ዘግቶ በጽኑ የተጋድሎ ሕይወት ኖረ፡፡ በዓቱንም ዙሪያውን መውጫ መግቢያ እንዳይኖረው መረገው፡፡ ለምግብ የሚሆነውን የዛፍ ፍሬና የሜዳ ቅጠል ማስገቢያ የሚሆን ትንሽ ቀዳዳን አበጃና ያ ወዳጁ ያስገባለታል፡፡ አባ በግዑም ያንን በሦስት ቀን አንድ ጊዜ ብቻ ይመገባል፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

03 Jan, 17:55


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ታኅሣሥ 26-ከሮሜ አገር የከበረች ቅድስት አንስጣስያ በሰማዕትነት ዐረፈች፡፡ የዚህችም ቅደስት አበቷ ጣዖት የሚያመልክ ሲሆን እናቷ ግን ክርስቲያን ነበረች፡፡ እናቷም እንደወላደቻት አባቷ ሳያውቅ በድብቅ የክርስትና ጥምቀትን አስጠመቀቻት፡፡ ዐውቆስ ቢሆን ባላስጠመቃቻት ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ የቀናች ሃይማኖትን እያስተማረች አሳደገቻት፡፡ እርሷም ባስተማረቻት ትምህርት የጸናች ሆነች፡፡ አንስጣስያም ለአካለ መጠን በደረሰች ጊዜ አባቷ እንደ እርሱ ላለ ከሃዲ ወስዶ በግድ አጋባት፡፡ እርሷ ግን እጅግ አድርጋ ጠልታዋለችና ልትገናኘው አልፈለገችም፡፡ በሴቶች ላይ በሚሆነው ግዳጅና አንዳንድ ጊዜም በደዌ የምታመካኝ ሆና ራሷን ጠበቀች፡፡ ባሏም እንዲጠላትና ከእርሷ እንዲለይ ያደፉና የቆሸሹ ልብሶችን ትለብስ ነበር፡፡
ባሏም ወጥቶ ወደ ሥራው ሲሄድ አንስጣስያ ግን ስለ ቀናች ሃይማኖት የታሠሩ ሰማዕታትን እየሄደች ትጎበኛቸውና ታጽናናቸው ነበር፡፡ የሚሹትንም ሁሉ ታመጣላቸዋለች፡፡ ባሏም ይህን የምትሠራውን ባወቀ ጊዜ ወደ ውጭ እንዳትወጣ በቤት ውስጥ ዘጋባት፡፡ እርሷም ከዚህ ክፉ ሰው እጅ ያወጣት ዘንድ በመረረ ልቅሶ ሆና ወደ ጌታችን በጸለየች ጊዜ ያ ሰው ሞተ፡፡ እርሷም ገንዘቧን ሁሉ አውጥታ ስለቀናች ሃይማኖት ብለው ለታሰሩት ሁሉ የሚያስፈልጋቸውን አሟላችላቸው፡፡ የቀረውንም ገንዘቧን ሰጠቻቸው፡፡ የሮሜውም ንጉሥ ዜናዋን በሰማ ጊዜ ወደ እርሱ አስመጣትና ስለ ሃይማኖቷ ጠየቃት፡፡ አንስጣስያም በክርስቶስ የምታምን ክርስቲያን እንደሆነች በፊቱ ታመነች፡፡ ንጉሡም ብዙ ክብርና ማዕረግ እንደሚሰጣት ቃል እየገባላት ከእምነቷ ሊያስወጣት ሞከረ፡፡ እርሷ ግን በፍጹም ልቧ ታመነች፡፡ እርሱም እምነቷን ትታ ወደ እርሱ የጣዖት አምልኮ እንዳልገባችና እሺ እንዳላለችው ሲያውቅ ይዞ ብዙ አሠቃያት፡፡
ከብዙ ሥቃይም በኋላ ባአስሮ ወደ ባሕር ቢያሰጥማትም ባሕሩ በሕይወት እያለች ተፋት፡፡ ዳግመኛም በአራት ካስማ መካከል አስተኝቶ በማሠር ታላቅና ጽኑ የሆነ ግርፋትን አስገረፋት፡፡ ነገር ግን እርሷ እግዚአብሔር አስችሏታልና ምንም ጉዳት እንዳላገኛት ሆነች፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሡ ታላቅ በሆነ የእሳት ማንደጃ ውስጥ እንዲጨምሯት አዘዘ፡፡ ቅድስት አንስጣስያንም በጨመሯት ጊዜ ነፍሷን ለእግዚአብሔር አሳልፋ ሰጠች፡፡ በመንሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀዳጀች፡፡
የቅድስት አንስጣስያ ረድኤት በረከቷ ይደርብን በጸሎቷ ይማረን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

02 Jan, 15:38


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ታኅሣሥ 25-አምስቱ መቃባውያን በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡
+ ኢትዮጵያዊው አቡነ ዮሐንስ ከማ ዘእጨጌ ዕረፍታቸው ነው፡፡
+ የሀገረ ግብፁ አቡነ ዮሐንስ ከማ ዕረፍታቸው ነው፡፡
አቡነ ዮሐንስ ከማ ዘእጨጌ፡- አቡነ ዮሐንስ ከማ ዘእጨጌ የተባሉት ጻድቅ አባት ሀገራቸው ሰሜን ጎንደር ነው፡፡ በብዙዎቹ ቅዱሳን ገድል ላይ ታሪካቸው ተደጋግሞ የተጠቀሰ ሲሆን ቅዱስ ያሬድ በድርሰቱ ደጋግሞ ያመሰገናቸው ታላቅ አባት ናቸው፡፡ ከቀደምት አንጋፋ ቅዱሳን ውስጥ አንዱ ሲሆኑ መጽሐፍ ‹‹ኮከብ ዘገዳም›› ይላቸዋል፡፡ ብዙ ሰዎች ይህኛውንም አባት ግብፃዊ ናቸው ይሏቸዋል፡፡ ነገር ግን ስማቸውን ከላይ ከጠቀስናቸው ከግብፃዊው አባት ከአባ ዮሐንስ ከማ ጋር አንድ አይደሉም፡፡ ኢትዮጵያዊው አቡነ ዮሐንስ ከማ ትግራይ የሚገኘውን ቀብፅያ ገዳምን የቆረቆሩ ሲሆን ብዙ ቅዱሳን አባቶችንም በማመንኮስ የቤተ ክርስቲያን ከዋክብት የተባሉትን ቅዱሳን መነኮሳትን አፍርተዋል፡፡ በገዳማቸው ቀብፅያ የምትገኘው እጅግ አስገራሚዋና ተአምራትን የምትሠራው መቋሚያቸው ዛሬም ድረስ አለች፡፡ 1250 ዓመት ያስቆጠረችውን ይህችን የጻድቁን ተአምረኛ መቋሚያ ሀገሬው በጠመንጃ ይጠብቃታል፡፡ እንደ ሰው ድምፅ የምታሰማበት ጊዜ አለ፡፡ ጻድቁ ሰሜን ጎንደር ምድረ ጸለምት ትልቅ ገዳም አላቸው፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!
+ + +
አቡነ ዮሐንስ ከማ ዘሀገረ ግብፅ፡- ከደቡባዊ ግብጽ ፃ ከሚባል አውራጃ የተገኙ ታላቅ አባት ነው፡፡ ወላጆቹ እግዚአብሔርን በመፍራት ካሳደጉት በኋላ በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ሚስት አጋቡት፡፡ እርሱ ግን ወደ ጫጉላ ቤቱ ገብቶ ከመሽራዋ ጋር ተመካክረው ድንግልናቸውን በመጠበቅ በመንፈሳዊው ተጋድሎ ለመኖር ወሰኑ፡፡ እርሷም ‹‹ወላጆቼ አስገድደው ለአንተ አጋቡኝ እንጂ ሥጋዊ ፍትወትን እንዳላሰብኳት ሕያው እግዚአብሔር ምስክሬ ነው›› በማለት በደስታ ሀሳቡን ተቀበለችው፡፡ ከዚህም በኋላ በአንድ አልጋ እየተኙ ድንግልናቸውን በምሥጢር ጠብቀው በጾም በጸሎት እየተጋደሉ ብዙ ዘመን ኖሩ፡፡
ከጽድቃቸውም የተነሣ ማንም ያልዘራትና ያልተከላት የወይን ተክል በቤታቸው በቅላ አድጋ ከቤታቸው ጣሪያ በላይ ተገልጣ ታየች፡፡ ወላጆቻቸውም ብዙ ዘመን ሲኖሩ ልጅ ባለመውለዳቸው ያስቡ ጀመር፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ከማ እና ሚስቱ ድጋሚ በመመካከር ወደ ገዳም ሄደው ለመመንኮስ ወሰኑ፡፡ እርሷንም ወደ ደናግል ገዳም ከወሰዳት በኋላ በዚያ ታላቅ ተጋድሎ አድርጋ አበ ምኔት ሆና ብዙ ተአምራትን የምታደርግ ሆነች፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ከማም ወደ አስቄጥስ ገዳም ሲሄድ በመንገድ አንድ ፊቱ የሚያበራ ጻድቅ ሰው ተገልጦለት ክፍሉ የት እንደሆነ በመንገር በመቃርስ ገዳም ውስጥ ወደሚኖረው ወደ አባ ዳሩዲ ወሰደው፡፡ አባ ዳሩዲም ካስተማሩት በኋላ አመነኮሱት፡፡ መልአክም ተገልጦለት ከአባ ዮሐንስ ሐፂር ገዳም በስተ ምዕራብ አቅጣጫ ሄዶ በዓት ይሠራ ዘንድ አዘዘውና ሄዶ በዓቱን ሠርቶ በታላቅ ተጋድሎ ኖረ፡፡ 300 ሰዎችም ወደ እርሱ መጥተው በመመንኮስ አብረውት በተጋድሎ ኖሩ፡፡ አንዲት ዕለትም ሌሊት ላይ በጋራ የመቤታችንን ውዳሴዋን ሲጸልዩ ሐዋርያው ቅዱስ አትናቴዎስ ተገለጠለትና የረቀቁ ምሥጢራትን ገለጠለት፡፡ ከዚያችም ዕለት ወዲህ በሠለስቱ ደቂቅ ጸሎት ፍጻሜ ላይ የቅዱስ አትናቴዎስን ስም የሚጠሩ ሆኑ፡፡ እመቤታችንም ለአባ ዮሐንስ ተገልጣለት ሁልጊዜ ከእርሱና ከልጆቹ ጋር እንደሆነች ነገረችው፡፡ በላይኛው ግብፅ የሚገኙ ሌሎች ገዳማትም አባ ዮሐንስን እየጠሩት ሕጉን እንዲያስተምራቸው ይለምኑት ነበር፡፡ ተጋድሎውንም ፈጽሞ በሰላም ዐረፈ፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!
+ + +
አምስቱ መቃባውያን፡- እነዚህም ቅዱሳን በሜዶናውያንና በሞዓባውያን ዘመነ መንግሥት የነበሩ ናቸው፡፡ ክፋትን የሚወድ ስሙ ጺሩጻይዳን የሚባል አንድ ክፉ ንጉሥ ነበረ፡፡ ከሥልጣኑም በታች የጸኑ ጭፍሮች አሉት፡፡ የሚያመልካቸውም ቁጥራቸው በ50 ወንዶችና በ20 ሴቶች አምሳል የተሠሩ ጣዖታት አሉት፡፡ በጠዋትና በማታ መሥዋዕት ያቀርብላቸዋል፤ ሌሎችንም ሰዎች እንዲሰግዱላቸው ያስገድላቸዋል፡፡
ከብንያም ነገድ የሆነ ስሙ መቃቢስ የሚባል አንድ ደገኛ ሰው ነበረ፡፡ እርሱም መልከመልካም የሆኑ ሦስት ልጆች አሉት፡፡ ከእነርሱም ግስላውን እንደ ዶሮ አንቆ ይዞ የሚገድል አለ፣ አንበሳንም የሚገድል አለ፡፡ ጦርነት በሆነም ጊዜ በአንድ ጊዜ ሰልፍ መዘዛ መቶ ሰው የሚገድል አለ፡፡ እነርሱም ውበትንና ግርማን የተሸለሙ ናቸው፡፡ ከሁሉም ደግሞ የልባቸው ውበት ይበልጣል-እግዚአብሔርን የሚያመልኩና የሚፈሩ ናቸውና፡፡
ከሃዲው ንጉሥም ‹‹ለአማልክቶቼ ስገዱ›› ባላቸው ጊዜ ሁሉም በአንድ ቃል ሆነው ‹‹ለረከሱ አማልክቶችህ ፈጽሞ አንሰግድም፣ እኛንም አንተምን ለፈጠረ ሕዝቡንም በዕውነትና በቅንነት ትጠብቅ ዘንድ ላነገሠህ አንተ ግን ቸል ብለህ ለዘነጋኸው ለልዑል እግዚአብሔር እንደግዳለን እንጂ›› አሉት፡፡ እንዲህም ባሉት ንጉሡ ተራቡ አራዊት አሳልፎ ሰጣቸው፣ ነገር ግን አራዊቱ ለቅዱሳኑ ሰግደውላቸው ተመለሱና ከራሱ ከንጉሡ ወገን የሆኑትን ከካድያኑ 75 ሰዎችን ገደሉ፡፡ ጭፍሮቹም ቅዱሳኑን በጭንቅ ሆነው ወደ እሥር ቤት አስጋቧቸው፡፡ በበነጋታውም ሁለት ቅዱሳን የሆኑ ወንድሞቻቸው መጥተው ተቀላቀሏቸው፡፡ ንጉሡም አምስቱን ወንድማማቾች በእምነታቸው መጽናታቸውን አይቶ በእቶን እሳት ውስጥ እንዲጣሉ አዘዘ፡፡ እንዳዘዘውም ባደረጉ ጊዜ እግዚአብሔር የቅዱሳኑን ነፍስ በክብር አሳርፎ የሰማዕትነት አክሊልን አቀዳጃቸው፡፡
ንጉሡም ዳግመኛ የቅዱሳኑ ሥጋቸው አመድ እስከሚሆን ድረስ እንዲያቃጥሉት አዘዘ፣ ነገር ግን እሳቱ የቅዱሳኑን ሥጋቸውን ፈጽሞ ሳያቃጥለው ቀረ፡፡ ዳግመኛም ሥጋቸውን ከከባድ ድንጋይ ጋር አብሮ አስሮ ወደ ጥልቅ ባሕር ቢጥላቸውም ባሕሩ ሥጋቸውን ማስጠም አልቻለም፡፡ ለአራዊትና ለሰማይ ወፎች እንዲሰጥ ቢያደርግም አራዊቱ ሥጋቸውን እየተበቁ ወፎቹ ክንፎቻቸውን ጋርደው እየተበቁት የቅዱሳኑ ሥጋ ለ14 ቀን ተቀመጠ፡፡ ይልቁንም ሥጋቸው እንደፀሐይ ማብራት ጀመረ፡፡ ከዚህም በኋላ አንሥተው ቀበሯቸው፡፡
ሌሊትም በሆነ ጊዜ ንጉሡ ተኝቶ ሳለ እነዚህ ቅዱሳን ተቆጥተው ሰይፋቸውን መዘው በፊቱ ቆመው ታዩት፡፡ ደንግጦ በነቃም ጊዜ እጅግ ፈራ-የሚበቀሉት መስሎታልና፡፡ የከበሩ ሰማዕታት ግን ‹‹አንተ ክፉ ነገር ስላደረግህብን እኛም ክፉ ነገር አንከፍልህም በነፍስ ፍዳን የሚያመጣ እግዚአብሔር ነውና፡፡ ነገር ግን ስለ ዕውቀትህ ማነስና ስለ ልቡናህ ድንቁርና እኛ ደኅና እንደሆንን ታይ ዘንድ ተገልጠን ታየንህ፡፡ አንተስ እኛን የገደልከን መስሎስ መዳንን አዘጋጀህልን፡፡ የጣዖቶችህ ካህናትና አንተ ግን ለዘላለሙ መውጫ ወደሌለበት ወደ ገሃነም ትወርዳላችሁ›› አሉትና ከእርሱ ተሰወሩ፡፡
የሰማዕታቱ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

01 Jan, 08:58


‹‹ልጆቼ! አታልቅሱ፤ ነገር ግን የሽማግሌውን የአባታችሁን ቃል ስሙ፡፡ መጀመሪያ እምነታችሁ በእግዚአብሔር ላይ ይሁን፡፡ በዚህ ዓለም እንደተያዙ እንደ ዓለም ሰዎች ስለ ልብስና ስለ ምግብ አሳብ አታብዙ፡፡ በየጊዜው ሁሉ መጸለይን አታቋርጡ፣ ለቤተ ክርስቲያን ሌትና ቀን አገልግሉ፡፡ እግዚአብሔር በሚወደው ገንዘብ ንጽሐ ሥጋንና ጾምን ውደዱ፡፡ ውዳሴ ከንቱም የሚቀረውንም የዚህን ዓለም ክብር አትውደዱት፤ እናንተስ የቀደሙትን አባቶች በመከራና በድካም ብዛት ከዓለም የወጡትን በመጋደላቸውም ክፉውን ሀሳብ ድል የነሡትን ምሰሏቸው፡፡ ፍለጋቸውንም ካልተከተላችሁ ልጆቻቸው አትባሉምና፤ በመከራቸው ካልመሰላችኋቸው በደስታቸው አትመስሏቸውም፤ በድካማቸውም ካልተባበራችሁ ወደ ቤታቸው አትገቡም፡፡ የቀደሙትን ቅዱሳን አባቶቻቸሁን መስላችሁ ኃጢአተኛ አባታችሁን እኔን ደግሞ ምሰሉ፤ ስለትኅርምቱም በመብል በመጠጥ ልባችሁ እንዳይከብድ፣ ሥጋ ከመብላትና ጠጅ ከመጠጣት ተጠበቁ፡፡ ለመመካትም በዓለማዊ ልብስ አታጊጡ፡፡ የመላእክት አስኬማ ከዓለማዊ ሥራ ጋር አይስማማምና፤ ዓለምንም በዓለም ላይ ያለውን ሁሉ አትውደዱ፡፡ ዓለሙም ፈቃዱም ሓላፊ ነውና፣ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ግን ለዘለዓለም ይኖራል፡፡ ልጆቼ ሆይ! ትሩፋትን ሁሉ በችኮላ ሠርታችሁ በጎይቱን ሃይማኖታችሁን አስከትሏት፡፡ ለነፍሳችሁ እንጂ ለሆዳችሁ አትገዙ፡፡ ሁላችሁ ወንድማማች ሁኑ፡፡ እርስ በርሳችሁም ተፋቀሩ፤ ከመንፈስ ቅዱስ የሚገኝ ፍቅር ኃጢአትን ያጠፋልና፤ የነፍስና የሥጋን ርኲሰት ያነጻልና፡፡ ይህንንም ብትጠብቁ በእውነት ልጆቼ ናችሁ፡፡ የሕይወትንም ፍሬ የምታፈሩ ትሆናላችሁ፡፡ ወደ እግዚአብሔር ፊት በክብር ትደርሳላችሁ…ልጆቼ ሆይ! ሰላም ለእናንተ ይሁን፡፡››
አባታችን ይህንንና ይህን የመሳሰለውን በጎ የነፍስ ስንቅ ለልጆቻቸው ከመከሯቸው በኋላ ቅድስት ነፍስ ከሥጋቸው ተለየች፡፡ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ከድንግል እናቱና ከቅዱሳን መላእክቱ ጋር ተገልጾ ቅድስት ነፍሳቸውን ‹‹ንጽሕት ነፍስ ሆይ ወደኔ ነይ!›› በማለት በክቡራን እጆቹ አቅፎ ሳማት፡፡ ቅዱሳን መላእክቱ ‹‹የጻድቅ ሰው ሞቱ በእግዚአብሔር ፊት ክቡር ነው›› እያሉ በታላቅ ዝማሬ ወደ ላይ ካሳረጓት በኋላ በሥላሴ መንበር ፊት ሰገደች፤ ወስደውም አስቀድማ በሕይወተ ሥጋ ሳለች ወዳየችው የዘላለም ርስቷ አስገቧት፡፡ ጌታችንም በዐይን ያልታየ በሰውም ኅሊና ሊመረመር የማይችለውን ትልቅ የመንግሥት አዳራሽ አወረሳቸውና የመለኮትን ባሕርይ የሚናገር የእሳት አንደበት ያለው ልብሰ መንግሥት አለበሳቸው፡፡ በ5ቱ መንግሥተ ሰማያት በ15 አህጉረ ገነት ላይ ሾማቸው፡፡ ስማቸውን ከሚጠሩት ነፍሳት ሁሉ ጻድቅም ቢሆን ኃጥእም ቢሆን ወደ ክቡር አባታችን ተክለ ሃይማኖት ሳያደርሱት ወደ ዘላለም ርስቱ ወይም ወደ ሲኦል አያገቡትም፡፡ ይህችም ነፍስ ባየችው ጊዜ ‹‹አባቴ አባቴ ተክለ ሃይማኖት ሆይ!›› እያለች ትጮሃለች፡፡ ብፁዕ አባታችንም ወደዚያች ነፍስ ተመልክቶ በጎ ሥራ የተገኘባት እንደሆነ ስሙንም በመጥራት በአማላጅነቱ የታመነች እንደሆነ ‹‹አባትሽ እኔ እነሆኝ›› ይላታል፡፡ ወደ ፈጣሪው አማልዶ በተሰጠው ቃልኪዳን ወደ ዘላለም ሕይወት ያደርሳታል፡፡
የቅዱስ አባታችን በዓላት እነዚህ ናቸው፡- መጋቢት 24 ቀን 1196 ዓ.ም ፅንሰታቸው፣ ታኅሣሥ 24 ቀን 1197 ዓ.ም ልደታቸው፣ ኅዳር 24 ቀን ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ ጋር በሕይወተ ሥጋ እያሉ የሥላሴን መንበር ያጠኑበት ሲሆን ጥር 4 ቀን 1289 ዓ.ም ደግሞ በጸሎት ብዛት አንድ እግራቸው የተሰበረበት ነው (ነገር ግን የዕረፍታቸውን ቀን ይዞ በዚሁ በጥር ወር በ24 ይከበራል)፣ ነሐሴ 24 ቀን 1296 ዓ.ም ዕረፍታቸው፣ በግንቦት 12 ቀን 1353 ዓ.ም ፍልሰተ ዐፅማቸው ነው፡፡
ቅዱስ አባታችን በሞት ከማረፋቸው በፊት አስቀድሞ ጌታችን እንደነገራቸው ሥጋቸው ከነፍሳቸው ከተለየች ከ57 ዓመት በኋላ የካቲት 19 በጸሎት ላይ ለነበሩት ለአቡነ ሕዝቅያስ ተገልጠውላቸው ‹‹ጌታ የገባልኝን ቃል ይፈጸም ዘንድ ሥጋዬ የሚፈልስበት ደረሰ፣ ቀኒቱንም በምስጋናና በጸሎት መንፈሳዊ በዓል አድርጉ፤ እኔ ኃጥኡ በሞትኩበት ቀን እንደነበረው ምስጋና አቅርቡ፡፡ ሄደህ ለ12 መምህራንና ለልጆቼ ግንቦት 12 እንዲያከብሩ ንገራቸው፡፡ በፍልሰቴ ቀን አባቴ አባቴ የሚለኝ ሁሉ ይምጣ ያኔ እኔ፣ ወዳጄ ሚካኤልና ልጄ ፊልጶስ አብረን መጥተን እንባርካለን፡፡ ምልክት ይሆንህም ዘንድ በምመጣበት ጊዜ የጠፋው የመቅረዙ መብራት ይበራል›› አሉት፡፡ ከዚህም በኋላ አቡነ ሕዝቅያስ በአባታችን ተባርከው ሄደው በአራቱም አቅጣጫ ላሉት 12 መምህራንና ለክርስትያኖች ሁሉ አባታችን የነገሩትን የፍልሰታቸው በዓል ስለማድረግ ወደ ፍልሰቱ በዓል ያልመጣም በዚያች ቀን (በሰማይ ለምልጃ) አባቴ እንዳይለው እርሱም ልጄ እንዳይለው ጨምሮ መልእክቱን ላከላቸው፡፡ እነርሱም ከያሉበት ተሰብስበው መጥተው የቅዱስ አባታችንን ሥጋቸውን አውጥተው ወደ ቤተክርስቲያን አፍልሰው 3 ጊዜ መቅደሱን አዙረው በዓሉንም አባታችን እንዳሉት በዝማሬና በምስጋና አክብረው ወደ ውስጥ አስገቡት፡፡ በዚህም ጊዜ ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን ተክለ ሃይማኖት አስቀድመው እንደተናገሩት ጠፍቶ የነበረው መብራት ቦግ ብሎ በራ፡፡ ከቅዱስ ሚካኤልና ከልጃቸው ከአቡነ ፊልጶስ ጋር በመሆንም በዓሉን ያከብር የነበረውን የተክለ ሃይማኖት የጸጋ ልጆቻቸውን ሁሉም ይባርኩ ነበር፡፡
የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!
✞ ✞ ✞

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

01 Jan, 08:58


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ታኅሣሥ 24-ጌታችን በቃሉ ‹‹ሐዲስ ሐዋርያ›› ብሎ የሾማቸው የኢትዮጵያ ብርሃኗ የሆኑ የደብረ ሊባኖሱ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ልደታቸው ነው፡፡
+ ሰሎንቅያ በምትባል አገር ሰይጣን ገዝተው በግልጽ ያነጋገሩትና የሚያስትበትን ምሥጢር እንዲናገር ያደረጉት አባ ጳውሊ ዕረፍታቸው ነው፡፡
+ እስራኤልን የታደገች የአሚናዳብ ልጅ ቅድስት አስቴር ዕረፍቷ ነው፡፡
+ የአንጾኪያው አባ ፊሎንጎስ ዕረፍቱ ነው፡፡
+ የአንጾኪያው ሊቀ ጳጳሳት እጅግ የከበረና የተመሰገነ አቡነ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ የዕረፍቱ መታሰቢያ በዓሉ ነው፡፡
አባ ፊሎንጎስ፡- ይኽም ቅዱስ አስቀድሞ ሚስት አግብቶ አንዲት ልጅ ወለደ፡፡ ከዚህም በኋላ ሚስቱ ሞተች፡፡ እርሱም ከዚህ በኋላ የምንኩስና ልብስ ለብሶ ታላቅ ተጋድሎን እየተጋደለ ኖረ፡፡ ስለ መልካም ተጋድሎውትና ስለ ትሩፋቱ በአገልግሎትም ስለመጠመዱ በአንጾኪያ አገር ላይ ሊቀ ጳጳሳት እንዲሆን እግዚአብሔር መረጠው፡፡ በተሾመም ጊዜ የክርስቶስን መንጋዮች ምእመናንን በመልካም አጠባበቅ ጠበቃቸው፡፡ ከአርዮሳውያን ከመቅዶንዮስና ከሰባልዮስ ነጣቂ ተኩላዎች በሚገባ ጠበቃቸው፡፡ በሊቀ ጵጵስናውም የሹመት ወቅት አኗኗሩን እንደ መላእክት አደረገ፡፡ መልካም የሆነ ገድሉንም ፈጽሞ በዚህች ዕለት በሰላም ዐረፈ፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!
+ + +
አቡነ ጳውሊ ዘሀገረ ሰሎንቅያ፡- ሰለንቅያ በምትባል በምስር አገር ሰይጣንን ገዝተው በግልጽ ያነጋገሩትና ብዙ ምሥጢርን እንዲናገር ያደረጉት ታላቅ አባት ናቸው፡፡ የሰሎንቅያ አገር ሰዎች የሄሮድስ ወገን የሆኑ ክፉዎች ናቸው፡፡ ከዱሮ ጀምረው ሴቶችና ወንዶች ሆነው በጋራ በአንድነት ወደ አንድ ክፍል ገብተው እንስሳዊ ግብራቸውን ይፈጽማሉ፡፡ ብዙ ሆነው ገብተው በሩን ዘግተው መብራት አጥፍተው በእጃቸው የገባውን ይዘው ያድራሉ፡፡ እኅቱም ትሁን ልጁ ወደዚያ ቤት የገባ ሰው ሌላውን አይለየውም፡፡ ይህም ሰይጣናዊ ተግባራቸው ባሕላቸው ሆኖ በወር አንድ ጊዜ ያደርጉታል፡፡
አባ ጳውሊም ይህን ባየ ጊዜ ስለ ኃጢአታቸው በጣም አዝኖ ‹‹ለምን እንዲህ ታደርጋላችሁ?›› ቢላቸው እነርሱም ‹‹አባቶቻችን ያዘዙን ትእዛዝና ባሕላችን ነው›› አሉት፡፡ አባ ጳውሊም ወደዚያ ቤት ሲገቡ አይቶ እጅግ በማዘን ወደ ጌታችን ጸለየ፡፡ ጸሎቱንም እንደፈጸመ አንድ ጥቁር ሰው ከዝሙት ቤቱ ዕራቁቱን ሆኖ የእሳት ሰይፍ ተሸክሞ መጣ፡፡ አባ ጳውሊም ካማተበበት በኋላ ‹‹አንተ ማነህ? ማንንስ ትሻለህ?›› አሉት፡፡ ጥቁሩም ሰው ‹‹እኔ ሰይጣን ነኝ፣ አንተ ወደ ጌታህ በለመንህ ጊዜ ላከኝ›› አለው፡፡ አባ ጳውሊም ‹‹የምታስትበትን ነገር ሁሉ ትነግረኝ ዘንድ እጠይቅሃለሁ›› አለው፡፡ ሰይጣንም ‹‹የምትሻውን ጠይቀኝ›› አለው፡፡ አባም ‹‹ያለ እግዚአብሔር ፈቃድ በሰው ላይ ታድር ዘንድ ምክንያት እንዴት ታገኛለህ?›› አለው፡፡ ሰይጣንም ‹‹ሰው በእግዚአብሔር ሕግ ጸንቶ ሳለ የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ስም በጠራ ጊዜና በንጽሕና ሆኖ የክርስቶስ ሥጋና ደምን በሚቀበል ሰው ላይ ለማደር ሥልጣን የለኝም›› አለው፡፡ ከዚህም በኋላ የሚያስትበትን ሁሉ በዝርዝር ነገረው፡፡ ሊቀ ጳጳሳትን፣ ጳጳሳትን፣ መነኮሳትን፣ መእመናንን፣ ባለትዳሮችን፣ አዛውንቶችን፣ ወጣቶችና ሕፃናትን…ሁሉንም ነገር እያንዳንዱን በምን በምን እንደሚያስት ሁሉንም ነገር በዝርዝር ነገረው፡፡ ወዲያውም የሰይጣን መልኩ ተለውጦ እንደ እሳት ነበልባል ሲሆን አባ ጳውሊ ተመልክቶ እጅግ ደነገጠ፡፡ በዚያም ቅጽበት የታዘዘ መልአክ መጥቶ አባ ጳውሊን አበረታው፡፡
በዚያችም ሌሊት መቅሰፍት ወርዶ በዝሙት ቤት ያሉትን አጠፋቸው፡፡ ከ5 ወንዶችና ከ5 ሴቶች በቀር የተረፈ የለም፡፡ አባ ጳውሊም ‹‹ይህን ለምን ታደርጋላችሁ?›› ቢላቸው ‹‹በየወሩ አንዲት ቀን ወደ ውሽባ ቤት እየገባን በሩን ዘግተን መብራት አጥፍተን ከእጃችን የገባችዋን ሴት ይዘን አንተኛለን›› አሉት፡፡ ‹‹ከእናንተ ውስጥ እኅቱን ወይም ልጁን እንዴት ያውቃል?›› አላቸው፡፡ ‹‹እንደ እንስሳ በመሆን እንጃ ማወቅ የለም›› አሉት፡፡ ከዚህም በኋላ አባታችን የክርስቶስን ወንጌል ሰበከላቸውና አሳምኖ አጠመቃቸው፡፡ ሥጋ ወደሙንም አቀበላቸው፡፡ በሃይማኖት ካጸናቸው በኋላ ወደ በዓቱ ተመልሶ ገድሉን ፈጽሞ ታኅሣሥ 24 ቀን በሰላም ዐረፈ፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!
(ጻድቁ ሰይጣንን በግዝት ይዘው ብዙ ምሥጢርን እንዲያወጣ ያደረጉበትን እጅግ ጠቃሚ የሆነ ድርሳን ‹‹ተዋሥኦተ ቀሲስ አባ ጳውሊ›› በሚል ርዕስ ሐይቅ እስጢፋኖስ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ አንድነት ገዳም ከብራናው ላይ በግእዝና በአማርኛ አሳትሞታል፡፡ ድርሳኗ በጣም ብዙ ጠቃሚ ምሥጢራትን የያዘች ናትና መእመናን አግኝተው ቢያነቧት በእጅጉ ይጠቀሙባታል፡፡)
+ + +
የአሚናዳብ ልጅ ቅድስት አስቴር፡- የአይሁድ ወገን የሚሆን ስሙ መርዶክዮስ የሚባል የኢያኤሩ ልጅ ከብንያም ወገን የተወለደ የቄስዩ ልጅ አንድ ሰው በሱሳ አገር ነበረ፡፡ ከኢሩሳሌምም በባቢሎን ንጉሥ በናቡከደነጾር እጅ የተማረከ ነው፡፡ ያሳደጋት ልጅ ነበረችው፡፡ እርሷም የአባቱ ወንድም የአሚናዳብ ልጅ አስቴር ናት፡፡ ከዘመዶቿ ተለይታ በወጣች ጊዜ ልጅ ትሆነው ዘንድ አሳደጋት፡፡ እርሷም እጅግ መልከ መልካም ነበረች፡፡ በአንዲትም ዕለት ንጉሥ አርጢክስስ ብዙ ተድላ ደስታ አድርጎ መኳንንቶቹን ሁሉ ጠራ፡፡ የመኳንንቶቹንም አለቃ አማሌቃዊውን ሐማንንም ጠራው፡፡ እርሱ ከሁሉም መኳንንት የከበረ ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሥ 7ቱን ባለሟሎቹን ጠርቶ ንግሥቲቱን አስጢንን አምጥተው የእቴጌነት ዘውድ ያቀዳጇት ዘንድ እርሷ መልከ መልካም ናትና ለአሕዛብም አለቆች ሁሉ መልኳንና ውበቷን ያሳዩ ዘንድ አዘዛቸው፡፡ ንግሥቲቱ አስጢን ግን የንጉሡን ትእዛዝ ባለመቀበል እምቢ አለች፡፡ ከባለሟሎቿም ጋር ትመጣ ዘንድ ባለወደደች ጊዜ ንጉሡ እጅግ ተናዶ ከንግሥትነቷ ሻራት፡፡ ከዚህም በኋላ 127 ከሚሆኑ ከሚገዘቸው አገሮች አንድ ሺህ ቆነጃጅቶችን ይመርጡለት ዘንድ ንጉሡ አዘዘ፡፡ ከሺህ መቶ፣ ከመቶ ዓሥር፣ ከዓሥር ሦስት መረጡ፡፡ ከሁሉም በመልክ፣ በውበት፣ በደም ግባትም አንደኛ ሆና አስቴር ተመረጠች፡፡ ንጉሡም አስቴርን አነገሣት፡፡
ንጉሡም አስቴርን እጅግ አድርጎ ወደዳት፣ በሴቶቹም ሁሉ ላይ የበላይ አድርጎ ሾማት፡፡ ከዚህም አስቀድሞ መርዶክዮስ አገሩንና አደባባዩን ከሚጠብቁት ከንጉሡ ባለሟሎች ጋር በአደባባይ ኖረ፡፡ እነርሱም ስማቸው ታራ እና ገቦታ ይባላል፡፡ እርሱም እነዚህ ሁለቱ በንጉሡ ላይ ያሰቡትን ተንኮላቸውን ሰማ፡፡ ንጉሥ አርጤክስስን ይገድሉት ዘንድ ወንጀልን እንዳዘጋጁ ባወቀ ጊዜ መርዶክዮስ ሄዶ ለንጉሡ ነገረው፡፡ ንጉሡም ነገራቸውን መርምሮ ቀጣቸውና ይህን ነገር ታሪክና ወግ በሚጻፍበት ላይ ጻፈው፡፡ ሐማ ግን አማሌቃዊ ነበረና መርዶክዮስንና እስራኤላውያንን ይጠላቸው እጅግ ነበርና የአይሁድን ወገን ሁሉ ለማጥፋት ተነሣ፡፡ መርዶክዮስም ይህንን በሰማ ጊዜ ልብሱን ቀዶ ማቅ ለበሰ፡፡ መርዶክዮስም የሀዘኑን መርዶ ለአስቴር እንዲደርሳት አደረገ፡፡ አስቴርም ‹‹እስከ ሦስት ቀን ጹሙ ጸልዩ እኔም ደንገጡሮቼም እንጾማለን›› ብላ ላከችለት፡፡ ሱባኤዋንም እንደጨረሰች የማቅ ልብሷን አውልቃ ጥላ ወደ ንጉሡ አዳራሽ በገባች ጊዜ ‹‹እስከ መንግሥቴም እኩሌታ ቢሆን እሰጥሻለሁና የሆንሽውን ንገሪኝ›› አላት፡፡ በዓልንም አደረገና ሐማንና መኳንንቱን ሁሉ ጠራ፡፡ በበዓሉም ላይ ድጋሚ ‹‹ላደርግልሽ

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

01 Jan, 08:58


የምትፈቅጂውን ንገሪኝ›› አላት፡፡
ንጉሡም ለመርዶክዮስ ውለታ ያደረገለትን ሲያስብ ምንም እንዳላደረገለት ዐወቀ፡፡ ወዲያውም ሐማ መርዶክዮስን በመስቀል ላይ ሰቅሎ ሊገድለው እንደሆነ ተነገረ፡፡ ንጉሡም ሐማን ‹‹ንጉሥ የወደደውን ሰው ምን ያደርግለት ዘንድ ይገባል?›› አለው፡፡ ሐማም ‹‹ይህስ ለእኔ ነው›› ብሎ ‹‹በክብር ይሾም ዘንድ ሹመቱም አዋጅ ይነገርለት ዘንድ ይገባዋል›› አለ፡፡ ንጉሡም ለሐማ ይህን ጊዜ ‹‹መልካም ተናግረሃል፣ ለመርዶክዮስ እንዲሁ ይደረግለታል›› አለው፡፡ ሐማም የንጉሡን ትእዛዝ ተቀብሎ መርዶክዮስን በፈረስ አስቀምጦ በከተማው በማዞር በክብር መሾሙን በአዋጅ አስነገረለት፡፡
ከዚህም በኋላ ንጉሡና አስቴር ለማዕድ አብረው በተቀመጡ ጊዜ ንጉሡ ‹‹ጉዳይሽን የማትነግሪኝ ለምንድነው?›› አላት፡፡ እሷም ይህን ጊዜ ‹‹ንጉሥ ሆይ ዝም ባልኩ በወደድኩ ነበር ነግር ግን ወገኖቼና እኔ ለሞት ተላልፈን ተሰጥተናል›› በማለት ሐማ እስራኤላውያንን በአዋጅ ሊያጠፋ መሆኑን ነገረችው፡፡ ንጉሡም ‹‹ማነው ይህን በማድረግ የደፈረኝ?›› አላት፡፡ እሷም ሐማ መሆኑን ነገረችው፡፡ ንጉሡም ሐማ መርዶክዮስን ለመስቀል ባዘጋጀው መስቀል ላይ ራሱ ሐማን እንዲሰቅሉት አዘዘ፡፡ ሐማም ተሰቅሎ ሞተ፡፡ የእስራኤል ወገኖችም ሁሉ በጻድቂቱ አስቴር መዳናቸው በእርሷ ተደርጓልና ሁሉም አመሰገኗት፡፡ ምስጉን የሆነ እግዚአብሔርን አመሰገኑት፡፡
መጽሐፈ አስቴር አጭር ከመሆኑ የተነሣ በሌሎች አገሮች ላይ ባሉት መጽሐፍ ቅዱሶች ውስጥ ‹‹እግዚአብሔር›› የሚለው ስም በመጽሐፈ አስቴር ላይ ተጽፎ አይገኝም፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ባለው መጽሐፈ አስቴር ላይ ግን ‹‹እግዚአብሔር›› የሚለው ስም ከ21 ጊዜ በላይ ተጠቅሷል፡፡
127 አሕጉርን ይገዛ በነበረው የንጉሥአርጤክስስ ሚስት እስራኤላዊቷ አስቴር በ127ቱም አሕጉር ያሉትን ወገኖቿን በተንኮል ሊያጠፋ ከነበረው ከሐማ የክፋት ሥራ ሕዝቡን ሁሉ ለመታደግ ሦስት ቀን እንዲጾሙ ለመርዶክዮስ ነግራው፣ ሕዝቡም ጾማ ጸልየው እግዚአብሔርም ጾም ጸሎታቸውን ተቀብሎ እስራኤላውያን ሁሉ ሐማ ካወጀባቸው የሞት ፍርድ ድነው መርዶክዮስ ተሹሞ ሐማ ለእርሱ ባዘጋጀው መስቀል ላይ ተሰቅሎ እንደሞተ ሁሉ እኛም እስራኤል ዘነፍስ ምእመናን ዲያብሎስን በእመቤታችን በወላዲተ አምላክ ጸሎትና ቃልኪዳን ድል የምንነሣው ሆነናል፡፡ ሊቃውንት የማይሻር ከልጇ የተሰጣትን ቃልኪዳን በተናገሩበት መጽሐፍ ላይ ‹‹የአስቴር የጸሎቷ መሰላል ማርያም ይኽቺ ናት›› በማለት አስቴርን በምእመን በመመሰል አስተምረዋል፡፡ (ድርሳነ ኪዳነ ምሕረት ዘሰኑይ)
ረድኤት በረከቷ ይደርብን በጸሎቷ ይማረን!
+ + +
ዳግመኛም በዚህች ዕለት ጌታችን በቃሉ ‹‹ሐዲስ ሐዋርያ›› ብሎ የሾማቸው የኢትዮጵያ ብርሃኗ የሆኑ የደብረ ሊባኖሱ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ልደታቸው ነው፡፡ (የዕረፍታቸውን ዕለት ነሐሴ ሃያ አራትን ይመለከቷል፡፡)
ሐዲስ ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዘደብረ ሊባኖስ፡- ተክለ ሃይማኖት ማለት ‹‹የሃይማኖት ተክል፣ ተክለ አብ ተክለ ወልድ ተክለ መንፈስ ቅዱስ›› ማለት ነው፡፡
እግዚአብሔር አምላካችን ለኢትዮጵያ ሐዲስ ሐዋርያ አድርጎ የመረጣቸው ጻድቁ አባታችን ተክለ ሃይማኖት በሊቀ መላእክት በቅዱስ ሚካኤል አብሳሪነት ከአባታቸው ከካህኑ ጸጋ ዘአብና ከእናታቸው ከቅድስት እግዚእ ኀረያ መጋቢት 24 ቀን ተፀንሰው ታኅሣሥ 24 ቀን 1197 ዓ.ም ተወለዱ፡፡ ጻድቁ በተወለዱ በሦስተኛው ቀን ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው ‹‹አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ›› ማለትም ‹‹አንዱ አብ ቅዱስ ነው አንዱ ወልድ ቅዱስ ነው አንዱ መንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ነው›› በማለት የፈጠራቸውን አምላክ አመስግነውታል፡፡ ወላጆቻቸውም ስማቸውን ፍሥሐ ጽዮን አሏቸው፡፡ ይኸውም የጽዮን ተድላዋ ደስታዋ ማለት ነው፡፡ የወላጆቻቸው የቀድሞ ስማቸው ዘርዐ ዮሐንስና ሣራ ይባል ነበር፡፡
ቅዱሳን አባቶቻችን እነ አቡነ ተክለ ሃይማኖትና እነ አቡነ ዜና ማርቆስ ሌሎቹም እነ አቡነ ሳሙኤል ዘወገግ፣ አቡነ ሕፃን ሞዐ፣ አቡነ አኖሪዮስ(ትልቁ)፣ አቡነ ገላውዲዮስ፣ አቡነ ማትያስ ዘፈጠጋርና አቡነ ቀውስጦስ ዘመሐግል የትውልዳቸው መሠረት ኢያሱ ለሌዋውያን ክፍል ትሆን ዘንድ ከለያት ከኢየሩሳሌም ነው፡፡ ስማቸውን የጠቀስኳቸው እነዚህ ቅዱሳን አባቶቻችን የወንድማማቾች ልጆች ሲሆኑ ከአዳም ጀምሮ 61ኛ ትውልድ ናቸው፡፡ ይኸውም እንዴት ነው ቢሉ ትውልዱ ከአዳም ጀምሮ በካህኑ አሮን በኩል የሆነውና የሌዋዊያን ሊቀ ካህን የነበረው የሳዶቅ ልጅ አዛርያስ በንጉሥ ሰሎሞን ዘመን ከታቦተ ጽዮንና ከብዙ ሌዋዊያን ካህናት ጋር ሊቀ ካህን ሆኖ ከኢየሩሳሌም ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ አክሱም ተቀምጦ ኖረ፡፡ የኦሪትንም ሕግ እየዞረ ለኢትዮጵያ ሰዎች አስተማረ፡፡ ትውልዱም በአብርሃ ወአጽብሓና በአባ ሰላማ ዘመን እስከነበረው እንበረም የሚባለው ጻድቅ ድረስ ደረሰ፡፡ የእንበረምም ትውልድ ደገኛው ሕይወት ብነ በጽዮን ድረስ ደረሰ፡፡ ሕይወት ብነ በጽዮንም የደማስቆ ምድር ከሚሏት ከወለቃ ሀገር የመኮንን ልጅ የሆነችውን ወለተ ሳውልን አግብቶ አበይድላን ወለደ፡፡ አበ ይድላም በንጉሡ ድልዓዥን ዘመነ መንግሥት ለ150 ካህናት አለቃ ሆኖ በወለቃ ሀገር የክርስቶስን የወንጌል ሕግ እያስተማረ ብዙዎችን አጠመቀ፡፡ እስከ ሸዋ ምድር ድረስ እያስተማረ መጥቶ በሸዋ ምድር ተቀመጠ፡፡ ብዙ አብያተ ክርስቲያናትንም አሳነጸ፡፡ እጅግ አስደናቂ ተአምራትንም ያደርግ ነበር፡፡ ‹‹በሸዋ ጽላልሽ ተቀምጦ ሲያስተምርም በአንዲት ቀን እስከ ሁለት መቶ ሺህ ሕዝብ ያጠምቅ ነበር›› በማለት ገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ይመሰክርለታል፡፡
አበይድላ በመጨረሻ በፈቃደ እግዚአብሔር ከሸዋ ጽላልሽ ምድረ ዞረሬ ሚስት አግቶ ሀበነ እግዚእን ወለደ፤ ሀበነ እግዚእም በኩረ ጽዮንን ወለደ፤ በኩረ ጽዮንም ሕዝበ ቀድስን ወለደ፤ እርሱም ነገደ እግዚእ የተባለ ነው፡፡ ሕዝበ ቀድስም ብርሃነ መስቀልን ወለደ፤ እርሱም ዐቃቢነ እግዚእ የተባለ ነው፡፡ ብርሃነ መስቀልም ሕይወት ብነን ወለደ፤ እርሱም ሴትን ወለደ፡፡ ሴትም ወረደ ምሕረትን ወለደ፡፡ ወረደ ምሕረትም ዘካርያስን ወለደ፡፡ ዘካርያስም የእነ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አባት የሆኑ 6 ወንድማማች ልጆችን ወለደ፡፡ እነርሱም እንድርያስ፣ አርከሌድስ፣ ዘርዐ አብርሃም፣ ዘርዐ ዮሐንስ ወይም ጸጋ ዘአብ፣ ቀሲስ ዮሐንስና ቀሲስ ዮናስ ናቸው፡፡ እንድርያስም ሳሙኤል ዘወገግን ወለደ፤ አርከሌድስም ሕፃን ሞዐን ወለደ፤ ዘርዐ አብርሃምም ታላቁን አኖርዮስን ወለደ፤ ዘርዐ ዮሐንስ ወይም ጸጋ ዘአብም ተክለ ሃይማኖትን ወለደ፤ ቀሲስ ዮሐንስም ዜና ማርቆስን ወለደ፣ ቀሲስ ዮናስ ደግሞ የፈጠጋሩን ማትያስንና ገላውዲዮስን ወለዳቸው፡፡ ገላውዲዮስም የመሐግሉ ቀውስጦስን ወለደ፡፡ እነዚህ ደጋግ ቅዱሳን በእናታቸውም በኩል እንዲሁ በዝምድና የተሳሰሩ ናቸው፡፡ ማቴዎስ የተባለው ደገኛ ክርስቲያን የሸዋ ገዥ የነበረ ሲሆን አንድ ወንድ ልጅ መድኃኒነ እግዚእንና ሦስት ሴቶች ልጆችን ወለደ፡፡ ሶስቱ ሴቶች ልጆችም እምነ ጽዮን፣ ትቤ ጽዮንና ክርስቶስ ዘመዳ ይባላሉ፡፡ ሦስቱ እኅትማማቾችም ደጋጎቹን አባቶቻችንን ወለዱልን፡፡ እምነ ጽዮን የእነ ዜና ማርቆስን እናት ማርያም ዘመዳንና ወለደች፡፡ ትቤ ጽዮንም ሕፃን ሞዐን ወለደች፡፡ ክርስቶስ ዘመዳ ደግሞ ታላቁን አኖሬዎስን ወለደች፡፡ የፈጠጋሩ ገዥ መድኃኒነ እግዚእ ደግሞ የተክለ ሃይማኖትን እናት እግዚእ ኀረያን ወይም በሌላ ስሟ ሣራን ወለደ፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

01 Jan, 08:58


አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከልጅነታቸው ጀምሮ በወላጅ አባታቸው በካህኑ ቅዱስ ጸጋ ዘአብ ግብረ ዲቁናን ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን ሲያጠኑ ቆይተው በ15 እና በ22 ዓመታቸው ከእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ ከአቡነ ቄርሎስ (ጌርሎስ) ዲቁናንና ቅስናን ተቀብለዋል፡፡ ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን ቅድስት ቤተክርስቲያንን በወጣትነት ዕድሜያቸው ያገለግሉ እንደነበር በዚህ ይታወቀል፡፡
ከዕለታት በአንዱ ቀን አባታችን ከጓደኞቻቸው ጋር ለአደን ወደ ዱር ሄደው ሳለ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ተገልጦ ታያቸው፡፡ ቅዱስ አባታችንም ‹‹እንደዚህ ባለ ገናንነት የማይህ ጌታዬ ማነህ?›› ባሉት ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል ‹‹ዘወትር የምጠብቅህ ካንተ የማልለይ እናትህንና አባትህንም ስላንተ ከውኃ ስጥመትና ከምርኮ ያዳንኳቸው እኔ ሚካኤል ነኝ፡፡ ከእንግዲህ አውሬ አዳኝ አትሁን፤ ሰውን ወደ እግዚአብሔር ለመመለስ ሰውን በትምህርት የምታድን ሁን እንጂ፡፡ እነሆ እግዚአብሔር ጽኑዕ ሥልጣን ሰጥቶሃልና፤ ሙት ታስነሣለህ፤ ድውያንን ትፈውሳለህ፤ አጋንንትም አንተን በመፍራት ይሸሻሉ፡፡ ስምህ ፍሥሐ ጽዮን አይሁን፤ ተክለ ሃይማኖት ይሁን እንጂ፡፡ ትርጓሜውም ተክለ አብ፥ ተክለ ወልድ፥ ተክለ መንፈስ ቅዱስ ማለት ነው›› አላቸው፡፡
ቅዱስ ሚካኤል ይህን ሲነግራቸው ጌታችን በሥጋ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር እንደነበር ሆኖ መልከ መልካም ጎልማሳ መስሎ ታያቸው፡፡ ጌታችንም ‹‹ወዳጄ እንዴት ሰነበትክ? ቸር አለህን?›› አላቸው፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖትም ‹‹ጌታዬ ሆይ አንተ ማነህ?›› ብለው ሲጠይቁት ጌታችንም ‹‹እኔ የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ነኝ፤ በናትህ ማኅፀን ፈጥሬህ ያከበርኩህ እኔ ነኝ፡፡ በተወለድክ በሦስተኛው ቀን አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ብለህ ታመሰግነኝ ዘንድ የምስጋና ሀብት ያሳደርኩብህ እኔ ነኝ፡፡ በርሃብ ዘመን በቤት የሚያሻው ምግብ ሁሉ ቅቤው፣ የስንዴው ዱቄት በእናት በአባትህ ቤት ይመላ ዘንድ በእጅህ ሀብተ በረከት ያሳደርኩብህ እኔ ነኝ፡፡ ያንን ሰው አንተን በተጣላ ጊዜ በነፋስ አውታር የሰቀለኩት በመዓት ጨንገር የገረፍኩት እኔ ነኝ፡፡ ውኃ ጠምቶህ በለመንከኝ ጊዜ ከደረቅ መሬት የጣፈጠ ውኃ ያመነጨሁልህ እኔ ነኝ፡፡ ከልጅነትህ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ብዙ ተአምራት እያደረግሁ በአንተ እጅ የታመሙትን ያዳንኳቸው እኔ ነኝ፡፡ ወደፊትም አደርግልሃለሁ›› አላቸው፡፡ ይህንን ብሎ በእጆቹ ባረካቸውና ‹‹ንሣእ መንፈስ ቅዱስ›› ብሎ የሹመትን ሀብት አሳደረባቸው፡፡ ዳግመኛም ‹‹በምድር ያሰርከው በሰማይ የታሰረ ይሁን፤ በምድርም የፈታኸው በሰማይ የተፈታ ይሁን፤ አንተን የሰማ እኔን መስማቱ ነው፤ የላከኝ አባቴንም መስማቱ ነው፡፡ አንተን እንቢ ያለ እኔን እንቢ ማለቱ ነው፡፡ የላከኝ አባቴንም እንቢ ማለቱ ነው፡፡ ይህን ሥልጣን ቀድሞ ለሐዋርያት ሰጥቻቸው ነበር፡፡ ከሐዋርያትም ሹመትን የተቀበለ ጳጳሱ ትሾምና ትሽር፣ ትተክልና ትነቅል ዘንድ ሥልጣንን ሰጠህ፡፡ ይህንንም ያደረኩልህ የጳጳሱን ቃል በመናቅ አይደለም፡፡ የፍቅሬን ጽናት ባንተ እገልጽ ዘንድ ነው እንጂ፡፡ ሐዋርያት ወዳልደረሱበት ሕዝብ በመምህርነት እልክህ ዘንድ በሚካኤል ቃል አዲስ ስም አወጣሁልህ፡፡ አንተም በማናቸውም ሥራ ከእነርሱ አታንስም፣ ሐዲስ ሐዋርያ አድርጌሃለሁና፡፡ ሰውን ሁሉ በእኔ ስም እያስተማርክ ታሳምን ዘንድ፣ ሚካኤልም ባሰብከው ሥራ ሁሉ ረዳት ይሁንህ፣ ሁል ጊዜ ካንተ አይለይም፤ በምትሄድበትም ጎዳና ሁሉ እርሱ መሪ ይሁንህ፤ እኔም ባለ ዘመንህ ሁሉ አልለይህም›› ካላቸው በኋላ ሰላምታ ሰጥቷቸው ዐረገ፡፡
ብፁዕ አባታችንም እጅ ነሥተው ‹‹ለእኔ ለኀጥኡ የማይገባኝ ሲሆን ይህን ሁሉ ጸጋ የጠኸኝ ስምህ በሰማይ በምድር የተመሰገነ ይሁን›› አሉ፡፡ ከዚያች ቀን ጀምሮ ሀብተ ኃይልን የተመሉ ሆኑ፡፡ ወደቤታቸው ተመልሰው ያላቸውን ሀብት ንብረት ሁሉ ለቤተ ክርስቲያን፣ ለድኆችና ለጦም አዳሪዎች ሰጥተው ጨረሱ፡፡ ከዚያም ‹‹አቤቱ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! የመንግሥተ ሰማያትን በር ትከፍትልኝ ዘንድ እነሆ ቤቴን እንደተከፈተ ተውኩልህ›› ብለው ቤታቸውን እንደተከፈተ ትተው ወንጌልን ለማስተማር ወጡ፡፡ ጻድቁ አባታችን በሀገራችን ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ ሕዝቡን ከኃጢአት ወደ ገቢረ ጽድቅ፣ ከክህደት ወደ ኃይማኖት ስለመለሱት በዚህም የተነሣ ለኢትዮጵያውያን ብርሃን ተብለዋል፡፡ በዚህም መሠረት፡-
★ከ1219-1222 ዓ.ም በከተታ ሦስት ዓመት ወንጌልን አስተማሩ፡፡ ቀጥለውም ዘጠኝ ወር በዊፋት አገልግሎታቸውን ፈጸሙ፡፡
★ ከ1223-1234 ዓ.ም ዳሞት በተባለው ስፍራ ወይም በወላይታ ሀገር ለ12 ዓመታት ሕዝቡን በማስተማር ከአምልኮተ ጣዖት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር፤ ከገቢረ ኀጢአት ወደ ገቢረ ጽድቅ መልሰዋል፡፡ ቤተ ክርስቲያንንም አንጸዋል፡፡ በዚህ ሀገር ዲያብሎስ በዛፍ ላይ አድሮ ‹‹አምላክ ነኝ›› እያለ ለረጅም ዘመናት ሕዝቡን በማሳት የሚጠቀምበትን ዛፍ በተአምራት ከሥሩ ነቅለው አፍልሰውታል፡፡
★ ከ1234-1244 ዓ.ም ባለው ጊዜ ደግሞ በእግዚአብሔር ፈቃድና ትእዛዝ ወደ አማራ ሳይንት ወሎ በመሄድ ከአባ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ገብተው ሥርዓተ ምንኲስናን እየተማሩ ለ10 ዓመታት የተለያዩ ገቢረ ታምራትን በማድረግ በጉልበት ሥራም ሲያገለግሉ ኖሩ፡፡
★ ከ1244-1254 ዓ.ም አባ ኢየሱስ ሞዐ ወደሚገኙበት ሐይቅ ቅዱስ እስጢፋኖስ ገዳም በቅዱስ ሚካኤል መሪነት ሐይቁን በእግራቸው እንደ ደረቅ መሬት በመርገጥ ወደ ደሴቱ በመግባት የአገልግሎትና የትሩፋት ሥራን በማብዛት የምንኲስናን ተግባራቸውን በመቀጠል ከፍጻሜ አድርሰዋል፡፡ በአባ ኢየሱስ ሞዓ እጅም የንጽሕና ምልክት የሆነውን የምንኲስናን ቀሚስ ተቀብለዋል፡፡
★ ከ1254-1266 ዓ.ም ወደ ትግራይ ሄደው ከአቡነ አረጋዊ ገዳም ደብረ ዳሞ ገብተው በጊዜው ከነበሩት አበምኔት ከአባ ዮሐኒ ቆብና አስኬማ ተቀብለው ለ12 ዓመታት በገዳሙ በገድል በትሩፋት መንፈሳዊ ተጋድሎአቸውን ቀጠሉ፡፡ እዚህ ጋር የመነኮሳትን ትውልድ መመልከቱ ተገቢ ይሆናል፡፡ ርዕሰ መነኮሳት የሆኑት አቡነ እንጦንስ በእግዚአብሔር ፈቃድና ትእዛዝ ምንኩስናን ከሊቀ መልአኩ ከቅዱስ ሚካኤል እጅ ተቀበሉ፡፡ እንጦንስም ታላቁ መቃርስን አመነኮሷቸው፤ ታላቁ መቃርስም ጳኩሚስን አመነኮሷቸው፤ እንዲህ እንዲህ እያለ የአባቶቻችን የምንኩስና ትውልድ እስከ ጻድቁ አባታችን ተክለ ሃይማኖት የደረሰ ሲሆን እሳቸውም ያመነኮሷቸው እጅግ ብዙዎች ናቸው፡፡ ከእነዚህም መካከል ዋናዋናዎቹ፡- አቡነ ተክለሃይማኖት በአንብሮተ እድ የሾሟቸው 12ቱ ከዋክብት፡- የወረቡ አኖሬዎስ፣ የሞረቱ ዜና ማርቆስ፣ የጽላልሹ ታዴዎስ፣ የድምቤው ገብረ ክርስቶስ፣ የወገጉ ሳሙኤል፣ የእናርያው ዮሴፍ፣ የዳሞቱ አድኃኒ፣ የወጁ ኢሳይያስ፣ የመንዝ የመራቤቴውና የወለቃው መርቆሬዎስ፣ የመሐግሉ ቀውስጦስ፣ የፈጠጋሩ ማትያስ፣ የደዋሮው ተስፋ ሕፃን፣ የእንሳሮው ዳዊት፣ የዘልዓቱ ናታን ናቸው፡፡ ድጋሚ በአንብሮተ እድ የሾሟቸው 4 ዐይና የተባሉት 12ቱ ከዋክብት፡- ዕንባቆም፣ ያዕቆብ፣ ማትያስ፣ ሰማዕቱ ዮሐንስ፣ ዮሐንስ መጥኀር፣ ዘትረ ወንጌል፣ አብርሃም ሰላማዊ፣ እስረኛው ቆሞስ ዘወንጌል፣ ዘክርስቶስ ናቸው፡፡ እንዲሁም ነጫጭ ርግብ የተባሉትና ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት ቀጥሎ በደብረ ሊባኖስ የተሾሙት፡- ኤልሳዕ፣ ፊሊጶስ፣ ሕዝቅያስ፣ ቴዎድሮስ፣ ዮሐንስ ስውር፣ ዮሐንስ ከማ፣ እንድርያስ፣ ይምርሐነ ክርስቶስ፣ ጴጥሮስ ናቸው፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

01 Jan, 08:58


ወደ ቀደመው ነገር እንመለስና ብፁዕ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በመልአኩ ትእዛዝ ከደብረ ዳሞ ገዳም ወደሌላ ገዳም ለመሄድ ሲነሡ አበምኔቱ አባ ዮሐኒና መነኰሳቱ ሲሸኟቸው አቡነ ተክለሃይማኖት አርባ ክንድ ርዝመት ባለው ገመድ ገደሉን ለመውረድ እንደጀመሩ ገመዱን ሰይጣን ከካስማው ሥር ቆረጠባቸው፡፡ ቅዱስ አባታችን ግን በዚህ ጊዜ ስድስት የብርሃን ክንፎች ተሰጣቸውና እየበረሩ ክንፎቻቸውን እያማቱ ሦስት ምዕራፍ ሄደው ሲያርፉ አበምኔቱና መነኰሳቱ አይተዋቸው እጅግ ተደስተዋል፡፡ አባታችን ወደ ትግራይ ሄደው ከአቡነ አረጋዊ ገዳም ደብረ ዳሞ ገብተው በጊዜው ከነበሩት አበምኔት ከአባ ዮሐኒ ቆብና አስኬማ ከተቀበሉ በኋላ ተመልሰው ወደ ሐይቅ በመሄድ ለአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ቆብና አስኬማን ሰጥተዋቸዋል፡፡ ከዚያም ወደ ዋሊ ገዳም ገብተው ከቅዱሳን ጋር ተገናኝተው በትሩፋት ላይ ትሩፋትን በገድል ላይ ገድልን ጨምረዋል፡፡
★ ከ1266-1267 ዓ.ም ለአንድ ዓመት ያህል የትግራይን ገዳማት በሙሉ በመጐብኘት ወደ ኢየሩሳሌምና ወደ ግብፅም በመሄድ በዚያ ያሉ ቅዱሳት መካናትን ጎብኝተው መጥተዋል፡፡ ከዚህ በኋላ ‹‹ዳዳ›› በተባለ ስፍራ ይመለክ የነበረውን 75 ክንድ የሚረዝመውን ዘንዶ በጸሎት ኃይል በመስቀል ምልክት አማትበውበት በተአምራት ገድለውታል፡፡ በቦታው ላይ በአርባዕቱ እንስሳ ስም ቤተ ክርስቲያን አንጸው ታቦተ ሕግ አስገብተውላቸዋል፡፡ ከሴቶችና ከልጆች ሌላ ሦስት ሺህ በጣዖት የሚያመልኩ ወንዶችን አስተምረው መልሰው አጥምቀው አቊርበዋቸዋል፡፡
★ ከ1267-1289 ዓ.ም ባለው ጊዜ ደግሞ በደብረ ሊባኖስ ካለችው ገዳመ አስቦ ዋሻ በመግባት 8 ጦሮችን (ሁለቱን በፊት፣ ሁለቱን በኋላ፣ ሁለቱን በቀኝ፣ ሁለቱን ደግሞ በግራ አስተክለው እጆቻቸውን በትእምርተ መስቀል በመዘርጋት የክርስቶስን ሕማምና ሞት፣ ነገረ መስቀልን በማሰብ በተመስጦ ሌትና ቀን ያለማቋረጥ በጾምና በጸሎት በአርምሞ ተወስነው ሲጋደሉ ከቁመት ብዛት የተነሣ ጥር 4 ቀን 1289 ዓ.ም. አንዲቱ የእግራቸው አገዳ ተሰብራለች፡፡ ቅዱስ አባታችን በመዓልትና በሌሊት በትጋትና በቁመት በተጋድሎ ብዛት አንዲት የአገዳ እግራቸው ስትሰበር ዕድሜያቸው 92 ዓመት ሆኗቸው ነበር፡፡
★ ከ1289-1296 ዓ.ም ለሰባት ዓመታት በአንድ እግራቸው በመቆም ያለምግብና ያለውኃ በትኅርምት ሌትና ቀን እንቅልፍ በማጣት እንደ ምሰሶ ጸንተው፤ በተመስጦ በትጋት ለሰው ዘር ሁሉ ድኅነትን ሲለምኑ ኖረዋል፡፡ ከሰባቱ ዓመታት ውስጥ ጥቂት ውኃ የቀመሱት በአራተኛው ዓመት ብቻ ነበር፡፡ በዚህ ጊዜ ውስጥ ጌታችን ተገልጦላቸው በሰው አእምሮ ሊታሰብና ሊለካ የማይችል ትልቅና ልዩ የመንግሥት አዳራሽ ከሰጣቸው በኋላ የመለኮትን ነገር የሚናገር የእሳት አንደበት ያላቸው የመንግሥት ልብስ አለበሳቸው፡፡ በመስቀል ምልክት የተጌጡት ሰባት የሕይወት አክሊላትን አቀዳጅቷቸዋል፡፡ ይኸውም ‹‹ስለ ቀናች ሃይማኖትህ፣ ሃይማኖትን ለማስተማር መላዋን ኢትዮጵያን ስለመዞርህ፣ ከአረማውያን ሕዝብ ጋር በሃይማኖት ስትታገል ደምህን ስለማፍሰስህ፣ ወደ ኢየሩሳሌም ወርደህ ልዩ ልዩ የቅዱሳን ቦታዎች ስለመሳለምህ፣ በሰባት ዓመታት ቊመት የአንዱ አገዳ እግርህ ስለመሰበሩ፣ ስለብዙ ጾም ጸሎት ስግደትህ፣ ስለልብህ ንጽሕናና ቅድስና›› በማለት የሕይወት አክሊላትን ካቀዳጃቸው በኋላ ዝክራቸውን በማዘከር መታሰቢያቸውን የሚያደርጉ ሁሉ በዚህ ዓለምም ሆነ በወዲያኛው ዓለም ፍጹም ዋጋና ፍጹም ክብር እንደሚሰጣቸው ጌታችን ታላቅ ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡ ሥጋቸውም ወዴት ይቀበር ዘንድ እንዳላቸው ሲነግራቸው ‹‹እስከ 57 ዓመት ሥጋህ ከዚህ ይቀበራል፤ ከ57 ዓመት በኋላ ግን ይህች ዋሻ ትናዳላች፡ በዚህም ገዳም አደባባይ በስምህ ታላቅ ቤተ ክርስቲያን ልጆችህ ሠርተው ሥጋህን አፍልሰው በውስጡ ያኖራሉ›› አላቸው፡፡ በመጨረሻም አባታችን ለ10 ቀናት ያህል በተስቦ ሕመም ቆይተው ፈጣሪያቸው የገባላቸውን ቃል ኪዳን ለመነኰሳት መንፈሳውያን ልጆቻቸው ከነገሯቸው በኋላ ነሐሴ 24 ቀን በታላቅ ክብር ዐርፈዋል፡፡
አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቅድስት ነፍሳቸው ከቅድስት ሥጋቸው ተለይታ ከመውጣቷ በፊት ልጆቻቸውን ሁሉ እየባረኩ ሲሰናበቷቸው በመሀል አንዲት ሴት ‹‹አባታችን በቃልዎ የታሰሩ እንዳሉ ይፍቱ›› ስትላቸው እሳቸውም ‹‹ከሰው እስከ እንስሳ ድረስ የታሠሩ የዱር አራዊትም ሁሉ የተፈቱ ይሁኑ›› አሉ፡፡ በዚህም ጊዜ የዱር አራዊትና አእዋፍ በአባታችን ቃለ ግዝት ከታሠሩ ከ18 ዓመት በኋላ ተፈቱ፡፡ ይህችውም መነኩሲት ልትራቀቅ ወዳ ለእኛም ለእነርሱም ብዙ ድካም አመጣች፡፡ ይህንንም ተናግራ አራዊቱን ከእሥራታቸው ስታስፈታ በዚያ የነበሩ ሁሉም ደንግጠው ከፍርሃታቸው የተነሣ ወደ ውጭ ወጡ፡፡ አስቀድሞም አራዊቱ በብፁዕ አባታችን የተወገዙበት ምክንያት ደቀ መዛሙርቶቻቸው ለዕለት ምግብ ጥቂት የእርሻ ሥራን በመሥራት አተር ዘርተው ጎመን ተክለው ሳለ በወቅቱ ደብረ አስቦ ገና ምድረ በዳ ነበረችና እንደ ሽኮኮ፣ ጦጣ፣ ዝንጀሮ፣ ጃርትና ሌሎቹም አትክልትን የሚያጠፉ ሁሉ የዘሩትንና የተከሉት እያበለሹ አስቸገሯቸው፡፡ ለብፁዕ አባታችንም ‹‹አትክልታችንን አጠፉብን›› ቢሏቸው ቅዱስ አባታችን ‹‹እኛ ወደቤታቸው መጣንባቸው እንጂ እነርሱ ወደ እኛ አልመጡብንምና ተዋቸው፣ እንደ እኛም ሥጋውያን ደማውያን ናቸውና ተዋቸው አንግፋቸው›› አሏቸው፡፡ እየቆዩ ግን አውሬዎቹ እየበረቱባቸው ከልካቸው አለፉ፡፡ በአንዲት ቀን ቅዱስ አባታችን ሲመለከቱ አንድ ግመር ዝንጀሮ መጥቶ የመበለቲቱን እጅ ይዞ የያዘችውን ነጥቆ ወሰደባት፡፡ በኃይልም ስለደበደባት ጮኸችና መነኮሳቱ ደርሰው አስጣሏት፡፡
ቅዱስ አባታችንም ይህንን የዝንጀሮውን ግፍ ከተመለከቱ በኋላ ‹‹በዚህ ምድረ በዳ ያላችሁ አራዊት ሁላችሁ ቅዱሳን የደከሙበትን ገንዘባቸውን እንዳትዳፈሩ ከወሰኑላችሁ ከልካችሁ አልፋችኋልና እኔ በማገለግለው በእግዚአብሔር ቃል የታሰራችሁ ሁኑ›› ብለው አወገዟቸው፡፡ ከዚህችም ቀን ጀምሮ አእዋፍና አራዊት የታሠሩ ሆነው አህዮች ከጅብ ጋር በዱር ያድሩ ጀመር፡፡ አዝመራውንም የሚጠብቅ የለም ነበር፡፡ በዕለተ ዕረፍታቸው ግን ያች ችኩል መነኩሲት ‹‹አባታችን በቃልዎ የታሰሩ እንዳሉ ይፍቱ›› ስትላቸው አባታችን ለአራዊቱ ግዝታቸውን አንስተውላቸዋል፡፡ እሳቸውም ካረፉ በኋላ በበነጋታው ልጆቻቸው አዝመራውን ቢመለከቱት አራዊቱ የዘሩትን ሁሉ በልተው ጨርሰውት ነበርና ያገኙት አንዳች ነገር አልነበረም፡፡ አህዮችና ላሞችም በቀን በጅቦች ተበልተው ተገኙ፡፡
ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ለቀደ መዛሙርቶቻቸው አስቀድመው ‹‹ልጆቼ ሆይ! ሁሉም የመነኮሰ መንግሥተ ሰማይ ይገባል ማለት አይደለም ዓለምን በሚገባ የናቀ ብቻ ይገባል እንጂ፡፡ መጀመሪያ የእግዚአብሔርን ጽድቁን ብቻ ፈልጉ፤ ጾምና ጸሎትን አዘውትሩ፤ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ፤ ትእዛዛቱንም አጥብቃችሁ ጠብቁ›› እያሉ ከመከሯቸው በኋላ ስለራሳቸውም ሲናገሩ «ለዓለም ጨው ለራሴ አልጫ ሆንኩ፤ ለዓለም ብርሃን ለራሴ ጨለማ ሆንኩ፣ ከእውነተኛው ዳኛ ከጌታዬ ፊት ስቆም ምን እመልሳለሁ?» እያሉ በፍጹም ትህትና እና በልዩ መንፈሳዊ ተመስጦ ይጸልዩ ነበርና አሁንም አባታችን የከበረች ቅድስት ነፍሳቸው ከሥጋቸው ሳትለይና ይህን ዓለም ከሥጋ ከመለየታቸው በፊት የሚከተለውን የሃይማኖት ኑዛዜ አውርሰውናል፡-

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

31 Dec, 14:10


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ታኅሣሥ 23-ንጉሠ እስራኤል ቅዱስ ዳዊት ዕረፍቱ ነው፡፡
+ የከበረ አባ ጢሞቴዎስ ዕረፍቱ ነው፡፡
+ ቅዱሳን አባቶቻችን አባ ሳሙኤል፣ አባ ስምዖንና አባ ገብርኤል ዕረፍታቸው ነው፡፡
አባ ጢሞቴዎስ፡- ደጋግ የሆኑ ወላጆቹ የቤተ ክርስቲያንን ትምህት እያስተማሩ አሳደጉት፡፡ በደገም ጊዜ ዓለምን ንቆ መንሶ ገዳም በመግባት በተጋድሎ መኖር ጀመረ፡፡ መጻተኞችንና ጦም አዳሪዎችን ይመግባቸው ዘንድ ከገዳሙ አቅራቢያ መኖሪያን አበጀ፡፡ ነዳያንንም እየመገበ በመንፈሳዊ ተጋድሎው እየጸና 5 ዓመት ያህል ከኖረ በኋላ የበጎ ነገር ጠላት የሆነ ሰይጣን በቅናት ተነሣበትና የእጅ ሥራውን ትገዛ ዘንድ አንዲት ጋለሞታን ወደ እርሱ አመጣበት፡፡
እርሷም ወደ አባ ጢሞቴዎስ ከመመላለሷ የተነሣ የኃጢአት ፍቅር አድሮባቸው በመብል ጊዜ አብረው የሚመገቡ ሆኑ፡፡ ከዚህም በኋላ ከእርሷ ጋር በኃጢአት ወደቀና በኃጢአት ሥራ ውስጥ 7 ወር ያህል ኖረ፡፡ እግዚአብሔር ሁለቱንም አልጣላቸውምና በዕለተ ምፅዓት በፊቱ የሚቆሙ መሆናቸውን አሳሰባቸው፡፡ ከዚህም በኋላ አባ ጢሞቴዎስ ተነሥቶ ጥቅጥቅ ወዳለ ጫካ ገብቶ በዚያ እየታደለ ብዙ ዘመን ኖረ፡፡ እግዚአብሔርም ጣፋጭ የሆነች የውኃ ምንጭንና ቴምርን አዘጋጀለት፡፡ እርሷን እየተመገበ በተጋድሎ ሲኖር ሰይጣን ዳግመኛ በቅናት ተነሣበትና አስጨናቂ የሆድ ሕማም አመጣበት፡፡ አባ ጢሞቴዎስ ከሕማሙ ጽናት የተነሣ በግንባሩ ምድር ላይ የወደቀ ሆኖ ቀረ፡፡ በዚህም ጊዜ ነፍሱን ‹‹ነፍሴ ሆይ ይህ የሠራሽው የኃጢአትሽ ፍሬ ነውና በዚህ ደዌሽ ታገሺ›› ይላት ነበር፡፡ በዚህም አስጨናቂ ሕማም ውስጥ ሆኖ 4 ዓመት ኖረ፡፡
ከ4 ዓመት በኋላ መሐሪና ይቅር ባይ የሆነ እግዚአብሔር ለአባ ጢሞቴዎስ መልአኩን ላከለት፡፡ መልአኩም የአባ ጢሞቴዎስን ሆድ በእጁ አሸው፡፡ ጎኑንም በጣቱ ሰነጠቀና ጨንጓራውንና አንጀቱን አፀዳለት፡፡ በኋላም ወደቦታው መልሶ እንደቀድሞው አያይዞ አዳነውና ‹‹እነሆ እንግዲህ ጤነኛ ሆንክ፣ ዳግመኛ አትበድል ከዚህ የከፋ እንዳይደርስብህ›› አለው፡፡ አባ ጢሞቴዎስም በበረሃ እየተጋደለ 40 ዓመት ኖረ፡፡ ከዚያ በፊት በገዳም 17 ዓመት በዋሻ 10 ዓመት ኖሯል፡፡ በእነዚህም ዘመናቱ ከልብስ ተራቁቶ ኖረ፡፡ የራሱም ፀጉር ከፊትና ከኋላ ሸፍኖት ነበር፡፡ ስለ አገልግሎቱ፣ ስለ ተጋድሎውና ስለ አምልኮቱ የዱር አራዊት እስኪደግዱለትና የእግሩን ትቢያ እስኪልሱለት ድረስ እግዚአብሔር ትልቅ ጸጋን ሰጠው፡፡ አገልግሎቱንም ፈጽሞ በሰላም ዐረፈ፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!
+ + +
የከበሩ ቅዱሳን አባቶቻችን አባ ሳሙኤል፣ አባ ስምዖንና አባ ገብርኤል፡- አባ ሳሙኤል የተባለው ይኽም ቅዱስ ባሕታዊ ሆኖ ቀርጣሚን በምትባል አገር የሚኖር ነው፡፡ በዚያም አቅራፎስ የሚባል ሰማዕት ዐፅም ስለነበር ከእርሱ በረከትን እየተቀበለ/እየተሳለመ ይኖር ነበር፡፡ ሰሊባ የሚባል አንድ መኮንን ነበር፡፡ እርሱም ስምዖን የሚባል ልጅ አለው፡፡ ልጁም ለሞት በሚያበቃ ጽኑ ሕማም ታመመ፡፡ መኮንኑ በልጁ ላይ ይጸልይ ዘንድ ወደ አባ ሳሜኤል ላከ፡፡ ነገር ግን አባ ሳሙኤል ሲደርስ ልጁ ሞቶ አገኘው፡፡ አባ ሳሙኤልም በጸሎቱ ከሞት አስነሣው፡፡ ልጁ ስምዖንም ከሞት ከተነሣ በኋላ የአባ ሳሙኤል ደቀመዝሙሩ ሆነ፡፡ ሁለቱም በጋራ በተጋድሎ አብረው ኖሩ፡፡
ቅዱስ ስምዖን ውኃ ሊቀዳ ሲሄድ ሰይጣን እንስራውን ሰበረበት፡፡ አባቱም ሌላ መቅጃ ቢሰጠው እርሱንም ሰበረበት፡፡ የታዘዘ መልአክ ተገለጠላቸውና ወደ ሌላ ቦታ ሄደው ቤተ ክርስቲያን እንዲሠሩ አዘዛቸው፡፡ ንጉሥ አንስጣስዮስም ቤተ ክርስቲያኑን ሠራላቸው፡፡ እነርሱም ለመነኮሳትና ለነዳያን መኖሪያ 500 መኖሪያ ቤቶችን ሠሩ፡፡ አባ ሳሙኤልም ባረፈ ጊዜ መነኮሳት ልጆቹን ለአባ ስምዖን አስረክቦ በሰላም ዐረፈ፡፡ መነኮሳቱም 12 ሺህ እስኪሆኑ ድረስ በዙ፡፡ አባ ስምዖንም በሚገባ ይመራቸው ነበር፡፡ በዘመኑም ‹‹ትንሣኤ ሙታን የለም›› የሚል ሰይጣን በልቡ ያደረ አንድ መናፍቅ ተነሣ፡፡ አባ ስምዖንም ቢመክረውና ቢያስተምረው የማይለስ ሆነ፡፡ አባ ስምዖንም በሞተ ሰው ላይ ጸልዮ ያንን ሙት አስነሥቶ እንዲመሰክርለት ቢያደርገው አላምን አለው፡፡ ከዚህም በኋላ አባ ስምዖን ወደ እግዚአብሔር ቢጸልይ እሳት ከሰማይ ወርዶ ያንን መናፍቅ አቃጠለውና ክፉ አሟሟት ሞተ፡፡ አባ ስምዖንም አገልግሎቱን ፈጽሞ በዚህች ዕለት በሰላም ዐረፈ፡፡
ከአባ ስምዖንም በኋላ አባ ገብርኤል ተሹሞ መለኮሳቱን የሚጠብቅ እረኛ ሆነ፡፡ እርሱም ምግባሩ ያማረ ሃይማኖቱ የሰመረ በትሩፋት በተጋደሎ ያጌጠ ነው፡፡ ብዙ አስደናቂ ተአምራትንም የሚያደርግ ሆነ፡፡ ከዕለታም በአንደኛው ቀን መነኮሳቱ ለእንጀራ ማቡኪያ የሚሆን እጅግ ትልቅ የሆነ የድንጋይ ገንዳ ወደ ገዳሙ ሊያስገቡ ቢሉ ከክብደቱ የተነሣ እምቢ አላቸው፡፡ አባ ገብርኤልም በዚህ ጊዜ በገዳሙ ያሉት ሁሉ ወጥተው እንዲራዱ በቃላቸው ባዘዙ ጊዜ 10 ሺህ ሰዎች ከሙታን ተነሡ፡፡ አባ ገብርኤልም ይህን አይቶ ‹‹እናንተን ያልኩ አይደለም በሕይወት ያሉትን ነው እንጂ›› አሏቸውና ወዲያው ወደ መቃብራቸው ተመለሱ፡፡
ከዕለታትም በአንደኛው ቀን አንድ ሰው ብዙ የሆነ ወርቁን ከአንዱ መነኩሴ ዘንድ በአደራ አስቀምጦ ወደ ሩቅ አገር ሄደ፡፡ ሰውየውም በተመለሰ ጊዜ መነኩሴው ለማንም ሳይናገር በሞት ዐርፎ አገኘው፡፡ የመነኩሴውም ረድእ አባቱ ያስቀመጠበትን ቦታ እንዳልነገረው አስረዳ፡፡ ከዚህም በኋላ አባ ገብርኤል ወደሟቹ መነኩሴ መቃብር ሄዶ መቃብሩን ስለዚያ ወርቅ ጠየቀው፡፡ ሟቹም መነኮሴ ወርቁን ያኖረበትን ቦታ ለአባ ገብርኤል ነገረውና ወስዶ ለባለቤቱ ሰጠው፡፡ ባለወርቁም እጅግ እያደነቀ ወርቁን ተቀብሎ በሰላም ሄደ፡፡
የቅዱሳን አባቶቻችን ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸ ይማረን፡፡
+ + +
ንጉሠ እስራኤል ቅዱስ ዳዊት፡- ዳዊት ማለት ‹‹ኅሩይ›› ማለት ነው። አንድም ‹‹ልበ አምላክ›› ማለት ነው። ሐዋ 13፡22፡፡ ትውልዱ ከነገደ ይሁዳ ነው። አባቱ እሴይ እናቱ ሁብሊ ይባላሉ። ሁብሊ መልከ መልካም ሴት ነበረች። ከጎረቤታቸው ያለ ጎልማሳ መልኳን እያየ በሐጸ ዝሙት ተነደፈ። እሴይ የእሷም ፈቃድ እንደሆነ አውቆ መንገድ እሄዳለሁ ብሎ ስንቁን ይዞ ወጣ። የሄደ መስሎ ከዚያው ውሎ ሲመሽ በልብሱ ተሸፋፍኖ ድምጹን ለውጦ ያንን ሰው መስሎ ገብቶ ከእርሷ ጋር አድሮ ጎህ ሳይቀድ ወጥቶ ሄደ። ዳዊት በዚህ ዕለት ተጸንሷል። “እነሆ፥ በዓመፃ ተፀነስሁ፥ እናቴም በኃጢአት ወለደችኝ” (መዝ 50፡5) ማለቱ ስለዚህ ነው። ቅዱሱም ተወልዶ ጉልበቱ ከጸና በኋላ የአባቱን በጎች ሲጠብቅ አድጓል።
ንጉሥ ሳኦል ከጌታ ፈቃድ በወጣ ጊዜ እግዚአብሔር ሳሙኤልን ቅብዐ መንግስሥት እንዲቀባው አደረገ። 1ኛ ሳሙ 16፡1-13፡፡ ከዚህ በኋላ በረድኤተ እግዚአብሔር ጎልያድን በአንድ ጠጠር ገደለ። ግዳይ ጥሎ ሲመለስ ሴቶች “ሳኦል ሺህ ገደለ ዳዊት እልፍ ገደለ” እያሉ እየዘፈኑ ተቀበሉት። ቅንዐት አድሮበት ነገር ግን አስቀድሞ ምሎለት ነበርና የመቶ ፍልስጤማውያንን ሸለፈት ተቀብሎ ልጁ ሜልኮልን ዳረለት። አንድ ቀን ሊገድሉት ሲማከሩ ሜልኮል ሰምታ ሽሽ አለችው። ሳዖልም ሶስት ሺህ ሠራዊት ይዞ ተከተለው፡፡ ከሠራዊቱ ተለይቶ ሰውነቱን ለመፈተሽ ዳዊት ካለበት ዋሻ ውስጥ ገባ። ጨለማ ነበርና ሰው መኖሩን አላወቀም። አቢሳ ዳዊትን ጠላትህን አሳልፎ ሰጥቶሀልና ልውደቅበት አለ። ተው ኦሪት ‹‹በእግዚአብሔር መሢሕ ላይ እጅህን አታንሳ›› ትላለችና አይሆንም

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

31 Dec, 14:10


ከዚህም በኋላ ሕፃኑ ተወልዶ ታመመ። “እኔን በነፍሴ እንደማረኝ ሕፃኑንም በሥጋው ይማረው” ብሎ ማቅ ለብሶ አመድ ነስንሶ ያለቅስ ጀመር። ሕፃኑ ሞተ፤ ከወደቀበት ተነስቶ ተጣጥቦ ልብሰ መንግሥቱን ለብሶ ማዕድ ቀረበ። ከምሳ መልስ “ታመመ ስንልህ ማዘንህ ሞተ ስንልህ እንዲህ ማድረግህ ስለምንድር ነው?” አሉት። “ውኃ ከፈሰሰ ይታፈሳልን? እንዲሁ ወደርሱ እንሄዳለን እንጂ እርሱ ወደኛ አይመጣም” ብሏቸዋል። ጌታ የተናገረው አይቀርምና ቅዱስ ዳዊት ፍዳን ሊቀበል ሰይጣን የበኵር ልጁ አምኖንን በእኅቱ በትዕማር ፍቅር እንዲያድርበት አደረገ። ኢዮናዳብ የሚባል የአጎቱ ልጅ ሰውነቱ ከስቶ ፊቱ ገርጥቶ ቢያየው “አንተ የንጉሥ ልጅ ሆነህ ምን ያከሳሀል?” አለው። “ፈርቼ እንጂ እኅቴ ትዕማርን ወድጃታለሁ” አለው። “ታመምሁ ብለህ ተኛና አባትህ ሊጠይቅህ መጥቶ ልጄ ብላ ሲልህ በትዕማር እጅ ቢሆን ኖሮ ሁለት ሦስት እንጎቻ በበላሁ ነበር በለው ያዝልሀል” አለው። እርሱም እንደመከረው አደረገ፡፡ ዳዊትም ትዕማርን አስጠርቶ እንድታሰናዳለት አዘዛት። “እኅቴ አንቺን ብዬ እንጂ እህል የሚያቀርብልኝማ መቼ አጣሁ” ብሎ ያዛት። እርሷም “ወንድሜ ይህን አታድርገው እኔን የተናቀች የተጠላች ታደርገኛለህ፣ አንተም ከሰነፎች እንደ አንዱ ትቆጠራለህ” አለቸው። አምኖን ግን በግድ አስነወራት። ወዲያውም ፊት ከወደዳት መውደድ ይልቅ ኋላ የጠላት መጥላት በለጠና ‹‹ውጪልኝ›› አላት። “ከቀደመው የአሁኑ ክፋትህ ይከፋል ተወኝ” አለችው። ብላቴናውን ጠርቶ አስወጥቶ እንዲዘጋባት አደረገ። እርሷም የለበሰችውን ባለህብር ልብስ ቀዳ አመድ ነስንሳ እያለቀሰች ስትሄድ ወንድሟ አቤሴሎም አገኛት። ያስነወራት አምኖን መሆኑን ዐውቆ “ወንድምሽ ነውና አትግለጪበት” ብሎ አጽናንቶ ዳዊት በከተማ ያሠራው ቤት ነበርና ከዚያ አስቀመጣት።
ከሁለት ዓመት በኋላ አቤሴሎም ድግስ ደግሶ ዳዊትን ጠራው። “አስቀድመህ ብትነግረኝ መልካም ነበረ አሁን ግን እኔ ስመጣ መኳንንቱ፣ መሳፍንቱ ወይዛዝርቱ ስለሚከተሉኝ ይበዛብሃል አይሆንም” አለው። “ያም ባይሆን ታላቅ ወንድሜ አምኖን ይገኝልኝ” አለ። እርሱም ‹‹ይሂድልህ›› አለው። ከዚህ በኋላ አምኖን በልቶ ሲጠግብ፤ ጠጥቶ ሲሰክር አቤሴሎም ብላቴኖቹን አዝዞ አስገደለውና እርሱ ወደናቱ ሀገር ጌድሶር ሸሸ። ዳዊት ለልጁ ለአምኖን አለቀሰለት። ከሁለት ዓመት በኋላ አምኖንን እየረሳ አቤሴሎምን እያስታወሰ ሄደ። ቢትወደዱ ኢዮአብ ይህን ዐውቆ አንዲት ቴቁሄያዊት ልኮ አስታረቀው። አቤሴሎም ከአባቱ ጋር ከታረቀ በኋላ በሠረገላ ሆኖ እስራኤልን “ምን ዳኛ አለና ይፈርድላችኋል? እኔማ ይህችን መንግሥት ጥቂት ጊዜ ባገኛት ቀን በፀሐይ ሌሊት በመብራት ፈርጄ ኢየሩሳሌምን አቀናት ነበር” ሲል ሰንብቶ ዳዊትን ለምኖ ሥርዓተ መንግሥት አስወጥቶ ሁለት መቶ መኳንንት ይዞ ‹‹አቤሴሎም በኬብሮን ነገሠ›› እያለ ነጋሪት አስጎሠመ። ዳዊት ይህን ሰምቶ “ኑ ከኢየሩሳሌም እንሽሽ” አለ። ኢዮአብና አቢሳ ግን ‹‹እንዋጋለን›› አሉት። ቅዱስ ዳዊትም ‹‹ጌታ ልጅህ መንግሥትህን ይነጥቅሀል፣ እዋጋለሁ አትበል ብሎኛል አይሆንም›› ብሎ ተራ ልብስ ለብሶ ተራ ጫማ ተጫምቶ ከከተማው ወጥቶ ሦስት ወራት በጫካ ሲያዝን ኖሯል። ከሦስት ወር በኋላ አቤሴሎም ሲዋጋ ሞተ። ዳዊት ወደ ቤተ መንግሥቱ ቢመለስ ዓሥሩ ዕቁባቶቹን ልጁ አርክሷቸው ተገኘ። እርሱም እስከ ፍጻሜ ዘመኑ ሳይደርስባቸው ቀርቷል።
ከዚህም በኋላ ቅዱስ ዳዊት ብዙ ጊዜ ቆይቶ “የባሕርይህን ፍሬ በዙፋንህ ላይ አኖራለሁ›› ያለው ቃል ተፈጽሞለት ልጁ ሰሎሞንን በዙፋኑ አስቀምጦ በነገሠ በ40 ዘመኑ በሰላም ዐርፏል። 1ኛ ነገ 2፡12-14፡፡
ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት ነሐሴ 13 ቀን ተጸነሰ፣ በሚያዝያ 6 ቀን በይሁዳ በቤተልሔም ሀገር ተወልደ። 1ኛ ሳሙ 16፡10-11፡፡ እረኛና ብላቴና የነበረ ቢሆንም የፍልስጤማውያኑን ኃያል ሰው ጎልያድን በ12 ዓመቱ 5 ጠጠርን ከወንዝ ለቅሞ በወንጭፍ ወርውሮ ገድሏል፡፡ 1ኛ ሳሙ 12፡45-51፡፡ ንጉሥ ሳዖል በጌልቦአ ተራራ በራሱ እጅ ከሞተ በኋላ አስቀድሞ በይሁዳ 7 ዓመት በመላው እስራኤል 33 ዓመት ነግሡዋል፡፡ 2ኛ ሳሙ 2፡4፤ 5፡1-5፡፡ ‹‹እግዚአብሔር እንደ ልቡ የሆነ ሰው መርጦአል” (1ኛ ሳሙ 13፡14) ተብሎ በእግዚአብሔር የተመረጠና ነገረ ሥጋዌን፣ ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን፣ ዳግም ምጽዓትን፣ ነገረ ማርያምን፣ ክብረ ቅዱሳንን፣ በስፋትና በጥልቀት የተናገረ የብሉይ ኪዳን ‹‹ወንጌላዊ›› የተባለ ቅዱስ ነቢይ ነው። “ብዙ ውሾች ከብበውኛልና የክፋተኞች ጉባኤም ያዘኝ እጆቼንና እግሮቼን ቸነከሩኝ። አጥንቶቼ ሁሉ ተቈጠሩ እነርሱም አዩኝ ተመለከቱኝም። ልብሶቼን ለራሳቸው ተከፋፈሉ፥ በቀሚሴም ላይ ዕጣ ተጣጣሉ…” እያለ የጌታችንን መከራ መስቀል በትንቢት ተናግሯል፡፡ መዝ 21 (22)፡ 16-18፡፡
“አምላክ በእልልታ፥ እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ።”፣ “ከክብሩ ውበት ከጽዮን እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል። አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም እሳት በፊት ይቃጠላል፥ በዙሪያውም ብዙ ዐውሎ አለ…” እያለ የጌታችንን ዕርገቱንና ዳግመኛ ለፍርድ የሚመጣ መሆኑን በግልጽ ተናግሯል፡፡ መዝ 46(47)፡4-5፣ መዝ 49(50)፡ 1-5፡፡ “የንጉሦች ሴት ልጆች ለክብርህ ናቸው በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች” እያለ የእመቤታችንን ክብር አይቶ በትንቢት ተናግሯል፡፡ መዝ 44(45)፡9፡፡
ቅዱስ ዳዊት ታላቅና ገናና የከበረ ንጉሥ ከመሆኑ የተነሣ መንግሥቱ የመሢሕ መንግሥት ምሳሌ ሆኗል፤ መሢሑም ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዳዊት ስም ብዙ ጊዜ በመጽሐፍ ቅዱስ ተጠቅሶ ይገኛል። (ኢሳ 9፡7፣ ኤር 23፡5-6፣ ኤር 33፡14-17፣ ሕዝ 34፡23፣ ሆሴዕ 3፡5) በሐዲስ ኪዳንም ወንጌላዊያኑ ጌታችንን ‹‹የዳዊት ልጅ›› በማለት ነው መጀመሪያ ነገረ ልደቱን ማውሳት የጀመሩት፡፡ ማቴ 1፡1፡፡ ራሱ ጌታችንም ‹‹እኔ የእሴይ ሥርና የዳዊት ዘር ነኝ›› ብሏል፡፡ ራእ 22፡16፡፡
ቅዱስ ዳዊት 7 ሀብታት የተሰጡት ጻድቅ አባት ነው፡፡ እነዚህም የተሰጡት ሀብታት፡- ሀብተ ክህነት፣ ሀብተ መንግሥት፣ ሀብተ መዊዕ (የማሸነፍ ሀብት)፣ ሀብተ ትንቢት፣ ሀብተ ኃይል፣ ሀብተ በገና (ዝማሬ) እና ሀብተ ፈውስ ናቸው። ቅዱስ ዳዊት 24 ሰዓት ሙሉ የእግዚአብሔር ምስጋና እንዳይቋረጥ መዘምራንን መድቦ እንዲያገለግሉ ያደርግ ነበር፡፡ ራሱም 10 አውታር ባለው በገና ሌት ተቀን በፍጹም ተመስጦ ያመሰግን ነበር፡፡ በመዝሙሩም አጋንንትን ያቃጥል ነበር፡፡ መዝሙረ ዳዊት በውስጡ የያዘው ሚሥጢር እጅግ ጥልቅ ነው፡፡ አባቶቻችን ዛሬም በዱር በጫካ ሆነው መዝሙረ ዳዊትን አብዝተው ይደግማሉ፡፡ እንኳንስ የሰው ልጅ ይቅርና ‹‹መዝሙረ ዳዊትን›› ሰማያውያን ቅዱሳን መላእክትም እግዚአብሔርን ለማመስገኛነት ተጠቅመውበታል፡፡ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት እድሜ ዘመኑን እግዚአብሔርን በማገልገልና በመፍራት ኖሮ በታኅሣሥ 23 ቀን በሰላም ዐርፎ በኢየሩሳሌም ተቀብሯል፡፡
የልበ አምላክ የቅዱስ ዳዊት ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

31 Dec, 14:10


አለው። እርሱ የልብሱን ዘርፍ በሰይፉ ቀዶ ያዘ። ሲወጣ ተከትሎ ወጥቶ “ንጉሥ ሆይ ዳዊት ቢያገኝህ አይምርህም የሚሉህን ለምን ትሰማለህ እነሆ ዛሬ አሳልፎ ሰጥቶኝ ነበር። ነገር ግን የልብስህን ዘርፍ ከመቅደዴ በቀር ምንም ምን እንዳላደረግሁህ አንተ ታውቃለህ” ብሎ ቅዳጁን አሳየው። ሳኦልም ድምጹን ከፍ አድርጎ በማልቀስ ‹‹ልጄ ዳዊት ሆይ! እኔ ክፉ በመለስሁልህ ፋንታ በጎ መልሰህልኛልና አንተ ከእኔ ይልቅ ጻድቅ ነህ። እግዚአብሔርም በእጅህ አሳልፎ ሰጥቶኝ ሳለ አልገደልኸኝምና ለእኔ መልካም እንዳደረግህልኝ አንተ ዛሬ አሳየኸኝ። ጠላቱን አግኝቶ በመልካም መንገድ ሸኝቶ የሚሰድድ ማን ነው? ስለዚህ ለእኔ ስላደረግኸው ቸርነት እግዚአብሔር ይመልስልህ። አሁንም እነሆ! አንተ በእርግጥ ንጉሥ እንድትሆን የእስራኤልም መንግሥት በእጅህ እንድትጸና እኔ ዐአውቃለሁ›› አለው፡፡ 1ኛ ሳሙ ም 24፡፡ ከዚህም በኋላ ዳዊት በነገሠ ጊዜ ለልጆቹ እንዲራራላቸው ሳኦል ቃል አስገብቶት ወደ ቤተ መንግሥቱ መለሰው። ዳዊት ግን በረሀ በረሀውን ሲዞር ቆይቷል።
በሐቅለ-ፋራን ሳለ ናባል የሚባል ባለጸጋ ድግስ ደግሶ በጎቹን አሸልቶ ሲያበላ ሲያጠጣ ብላቶኖቹ “ምሳ ላክልኝ ብለህ ላክበት” አሉት። “ተው አይሆንም ያለ እንደሆነ እጣላዋለሁ” አለችው። “ይህን ያህል ጊዜ አንዲት ጠቦት እንኳ ሳትነካ ከብቶቹን ጠብቀህለት እምቢ ይላልን ላክበት ግድ የለህም አሉት።” እንኪያስ ሔዳችሁ ንገሩት አለ። ሄደው ቢነግሩት “የማነው ዳዊት” ብሎ አልሰጥም አለ። ዳዊት ይህን ሲሰማ ተቆጥቶ ሊጣላው ተነሳ። ሚስቱ አቤግያ ይህን ሰምታ 5 በግ አሳርዳ አሠርታ፣ 5ቱን አሰናድታ የበለስ የወይን ጥፍጥፍ 500 እንጀራ፣ 12 ጭነት ዱቄት አሲዛ ሄደች። ዳዊት ከመንገድ አገኛትና “ባልሽን ልታድኚው መጣሽን?” ብሎ ያመጣችውን ተቀብሏት ተመለሰ። ናባል ማታ ሰክሮ ነበርና አቤግያ ሳትነግረው አደረች። ሲነጋ ትናንት ዳዊት ሊጣላህ መጥቶ ነበር አለችው። ዳዊት ብሎ ደነገጠ። ልቡን አጥቶ ሰንብቶ በ10ኛው ቀን መልአኩ ቀስፎታል። እመቤታችንና ጌታችን ከአብራኳ አሉና እሷን ግን ኀዘኗን ከጨረሰች በኋላ ዳዊት ሚስት አድርጓታል። 1ኛ ሳሙ ም25፡፡
ከዚህ በኋላ ሳኦል ፍልስጤማውያን በጠላትነት ተነሱበትና ገጠማቸው። ከጠላቶቹ አንዱ ቀስቱን መርዝ ቀብቶ ጎኑን መታውና እንደ እሳት አቃጠለው። ሎሌውን ጠርቶ ገደልነው እንዳይሉ አንተ ጨርሰኝ” አለው። “ጌታዬ ንጉሥ ሆይ ባሪያህ ካንተ ጋር እሞታለሁ እንጂ እገድልሃለውን?” ብሎ እምቢ አለው። የገዛ ሠይፉን ከምድር ተክሎ ወደቀበት። ሌሎቹም እርሱን አይተው በገዛ ሠይፋቸው እየተወጉ ሞቱ። ዳዊት የርሱንና የልጁ የዮናታንን ሞት ሲሰማ አዘነ። ግጥም እየገጠመ አለቀሰላቸው። ከሳዖል ሞት በኋላ ዳዊት መንግሥቱን አጽንቶ ጽዮንን አቅንቶ ተቀመጠ። ታቦተ ጽዮንንም በዕልልታ በሆታ ወደከተማው አስገባ። የሳኦል ልጅ ሜልኮል ዳዊትን በታቦተ ጽዮን ፊት ሲዘምር አይታ በልቧ ናቀችው። ሲገባ ልትቀበለው ወጥታ “የእስራኤል ንጉሥ በባሪያዎቹ ቆነጃጅት ፊት ዕርቃኑን በመግለጹ ምን ይከብር?” ብላ በአሽሙር ዘለፈችው። በዚህ ቢያዝንባት መካን ሆና ሞታለች። “ሜልኮል እስከምትሞት ድረስ ልጅ አልወለደችም ነበር” እንዲል። 2ኛ ሳሙ ም6፡፡
በዘመኑ የነበረው ነቢይ ቅዱስ ናታን ነው። እርሱም ሊጠይቀው መጥቶ ሳለ አዝኖ አየው። “ምን ሆነህ ታዝናለህ?” አለው። ቅዱስ ዳዊትም “እኔ በጽድ በዝግባ በተሠራ ቤት ተቀምጬ ታቦተ ጽዮን በድንኳን ስትኖር ምነው አላዝን?” አለ። “ጠላት ጠፍቶልሀል፤ መንግሥትህም ጸንቶልሀል አታንጽምን?” አለው። “ያስ ቢሆን ያለፈቃደ እግዚአብሔር ይሆናልን?” አለ። ከዚህም በኋላ ሁለቱም ቀኖና ገቡ። የቤተ መቅደስ ነገር ለናታን ተገልጾለት “አንተ አይደለህም የምትሠራልኝ ከአብራክህ የተከፈለ ልጅህ ይሠራልኛል” ብሎታል። 2ኛ ሳሙ 7፡1-17፡፡ ለቅዱስ ዳዊት ግን የበለጠ የሥጋዌ ነገር ተገልጾለት “እነሆ በኤፍራታ ሰማነው” ብሏል። መዝ 131፡6፡፡
ኢዮአብና አቢሳ ጠላት ለመመለስ ታቦተ ጽዮንን አሲዘው ሠራዊት አስከትለው ወደ አራቦት ዘመቱ። ቅዱስ ዳዊት ግን ከከተማ ቀርቶ ነበር። በሰገነቱ ሲመላለስ ቤርሳቤህን በአፀደ ወይን ውስጥ ስትተጣጠብ አይቷት ፍቅረ ዝሙት አደረበት። “የማን ሚስት ናት?” አለ። “የኦርዮን” አሉት። ኦርዮን ዘምቶ ነበር። “የባልንጀራህን ሚስት አትመኝ” (ዘጸ 20፡14-17) ያለውን ተላልፎ አስጠርቶ ደረሰባትና ጸነሰች። ጽንስ ያሳስትልኛል ብሎ እቦ ኦርዮንን አስጠርቶ ስለጦሩ ሁኔታ ከጠየቀው በኋላ “ወደቤትህ ሂድ” አለው። ኦርዮን ግን ድንኳን አስተክሎ ከዘበኞቹ ጋር አደረ። “አልመጣም” ብሎ ላከችበት። ዳግመኛም የሚያሰክር መጠጥ አጠጥቶ “ወደቤትህ ግባ” አለው። “ጌታዬ ንጉሥ ሆይ ታቦተ ጽዮን ተማርካ እስራኤላውያንም ዋዕየ ፀሐዩን ቁረ ሌሊቱን ታግሠው በሜዳ ሲሆኑ እኔ ቤቴ ገብቼ ተድላ ደስታ አደርግ ዘንድ ይገባልን?” ብሎ እምቢ አለ። በማግሥቱ “ኦርዮንን ፊት መሪ አድርጉት ጦሩ ሲበረታ ትታችሁት ሽሹ እሱ በዚያ ይሙት” የሚል ጽፎ አትሞ “ለኢዮአብ ስጠው” ብሎ ሰጠው። የዋህ ነውና የሞቱን ደብዳቤ ይዞ ሄዶ ሰጠው። ኢዮአብ እንደታዘዘው ኦርዮን ከፊት አሳልፈው ጦሩ ሲበረታ ተጠቃቅሰው ወደኋላ ሸሹ። እርሱ መለስ ብሎ “ምን ሆናችሁ?” ቢላቸው ጠላቶቹ ደርሰው ልብ ራሱን ብለው ገድለውታል።
እግዚአብሔርም ለነቢዩ ናታን ተገለጸለት። ናታን ከል ለብሶ ከል ጠምጥሞ ጦር ይዞ ሄደ። ዳዊት “ነቢየ እግዚአብሔር አመጣጥህ በደኅና ነውን?” አለው። “የምነግርህ አለኝ” አለው። “መቶ በጎች ያሉት ሰው ነበር። ከአንዲት በግ ሌላ ምንም ምን የሌለው ጎረቤት ነበረው። መንገድ ሲሄድ አደራ ሰጥቶት ሄደ፡፡ ያ ሰው እንግዳ ቢመጣበት መቶ በጎቹን አስቀምጦ የእርሱን አንዲት በግ አርዶ እንግዳውን ሸኘበት። እርሱንም ለሰው እንዳይነግርብኝ ብሎ ገደለው። በዚህ እግዚአብሔር አዝኗል” አለው። ዳዊትም ይህን ጊዜ “ይህን የሚያደርግ በከተማዬ ካለ ሞት ይገባዋል” አለ። ነቢዩም ወዲያው “ንጉሥ ሆይ! ይህን ሁሉ ያደረግህ አንተ ነህ፣ በራስህ ፈረድህ ባለጸጋ የተባልህ አንተ ደኃ የተባለ ኦርዮን ነው። መቶ በጎች የተባሉ አሥሩ ዕቁባቶችህ ናቸው። አንዲት በግ የተባለች ቤርሳቤህ ናት። እንግዳ የተባለ ፈቃደ ሥጋ ነው። ፈቃደ ሥጋህ ቢነሳብህ 10ሩ ዕቁባቶችህን አስቀምጠህ ከቤርሳቤህ ደረስህ። ኦርዮንንም አስገደልከው። በዚህ እግዚአብሔር አዝኗል” አለው። ይህንንም ሲሰማ ዳዊት ልዋል ልደር ሳይል ዕለቱን ጉድጓድ አስምሶ ማቅ ለብሶ ሱባኤ ይዞ ሌት ተቀን ተንስቅስቆ አለቀሰ፡፡ እግዚአብሔርም ጥንቱን መርጦታልና ጸሎቱን ሰማው። ነቢዩ ናታን ዳግመኛ መጥቶ “በነፍስህ ምሬሀለሁ ብሎሀል። በሥጋህ ግን ኃጢአት ያለፍዳ አይነጻምና ለሦስት ወር ልጅህ መንግሥትህን ይነጥቅሀል፤ ዕቁባቶችን ይቀማሀል” አለው። ዳዊትም “ይህ እንዲሆን በምን ዐውቃለሁ?” አለ። “የሚወለደው ሕፃን ይሞታል፣ እርሷን ግን አግባት ወንድ ልጅ ትወልድልሀለች ስሙን ሰሎሞን ትለዋለህ” አለው። ቀን ከሌት አብዝቶ ያለቅስ ነበርና ከዕንባው ብዛት የተነሣ መሬቱ እርሶ ሠርዶ አብቅሎ ሰውነቱን ተብትቦ ይዞት ነበር። ብላቴኖቹ ቆርጠው አወጡት።

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

31 Dec, 14:10


መልክዐ ቅዱስ ዳዊት (ዘአኅተሞ ገብረ ሥላሴ)

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

30 Dec, 13:04


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ታኅሣሥ 22-ብርሃናዊው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ለእመቤታችን አምላክን እንደምትወልድ ያበሰረበት መታሰቢያ በዓል ነው፡፡
+ ዳግመኛም በዚህች ዕለት የብርሃን እናቱ ድንግል ወላዲተ አምላክ ለወዳጇ ለቅዱስ ደቅስዮስ ሰማያዊ ወንበርና ልብስ ሰጥታዋለቸ፡፡ የእርሱም ዕረፍቱ በዚሁ ዕለት ሆነ፡፡
‹‹ልዑል እግዚአብሔር ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤልን ‹ሂድና ለጽዮን ልጅ ለድንግል የእግዚአብሔር የባሕርይ ልጅ ወደአንቺ መጥቶ ኃይለ ልዑል ወልድ ሥጋሽን ለብሶ ሰው ይሆናል፤ ይኸውም ካንቺ የሚወለደው ጽኑዕ ነው ብለህ ንገራት› አለው፡፡ ‹ደንቆሮዎች የሚሰሙበት፣ ድዳዎቸ የሚናገሩበት፣ ዕውራንም የሚያዩበት፣ ሙታን የሚነሡበት፣ ለምጻሞች የሚነጹበት፣ ሐንካሳዎች የሚሄዱበት፣ በጨለማ ውስጥ የነበሩ ሰዎች ብርሃን የሚያዩበት ጊዜ እነሆ ደረሰ ብለህ ንገራት› አለው፡፡
ቅዱስ ገብርኤልም ይህን ሰምቶ በግንባሩ ተደፍቶ ልዑል እግዚአብሔርን ‹ጌታ ሆይ! የምትነግረኝ ይደረግ ዘንድ እንደምን ይሆናል?› አለው፡፡ ጌታም ‹የጀመርኩትን ቸርነት ፈጸምኩ፣ የወይን ግንድ ይቆረጣል (ወልደ እግዚአብሔር ይሞታል)፣ ወይራም ከበለስ ጋር ይተከላል (መስቀል ይተከላል)፣ ቅጽሮችም ይቀጸራሉ (ምግባር ከሃይማኖት ጋር ይሠራል)፣ የኤልፍና የሌሚ ወገን ይነሣል፡፡ ገብርኤል ሆይ! ሄደህ ለዳዊት ልጅ ‹እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነውና ደስ ይበልሽ› ብለህ አብሥራት› አለው፡፡ ‹ለዘለዓለም ነግሦ የሚኖረውን እነሆ ትፀንሳለሽ በላት› አለው፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልም ይህን ሰምቶ ሰገደ፡፡ ልብሱንም በላዩ ይዞ በመስቀል ቀኝ ይወርድ ዘንድ ወደደ፡፡ ጌታም ‹መግባትህና መውጣትህ በፍቅር አንድነት ይሁን› አለው፡፡ ‹ዘካርያስን ረግመህ አንደበቱን እንዳሰርህ እርሷን እንዳታሳዝናት ይልቁንም አብዝተህ ደስ አሰኛት አንጂ› አለው፡፡ ቅዱስ ገብርኤልም ይህን ሰምቶ ፈጽሞ ደስ እያለው ሊባኖስ ከሚባል ተራራ እስኪሰማ ድረስ ክንፉን እያማታ ወረደ፡፡ በዚህም ጊዜ በዙሪያው ያሉ ሁሉ ‹ይህ የምንሰማው ምንድነው?› ይሉ ነበር፡፡ የተደረገበትንም ቦታ አላወቁትም ነበር፡፡››
እመቤታችንን በ3 ዓመቷ እናትና አባቷ ብፅዓት አድርገው ለእግዚአብሔር ሰጥተዋታልና ካህናትም በቤተ መቅደስ ከመካነ ደናግል አስገብተዋት በመልአኩ በቅዱስ ፋኑኤል አማካኝነት ኅብስት ሰማያዊ ጽዋዕ ሰማያዊ እየመጣላት ያንን እየተመገበች ቅዱሳን መላእክት እየጎበኟት 12 ዓመት ኖራለች፡፡ በ15 ዓመቷ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ለእመቤታችን ጌታችንን እንደምትወልድ በዚህች ዕለት አብሥሯታል፡፡ በመጀመሪያ እመቤታችን ውኃ ቀድታ ስትመለስ የጠተማ ውሻ እያለከለከ ሲመጣ ብታየው ለፍጥረት ሁሉ የምትራራ ናትና በወርቅ ጫማዋ ለዛ ለተጠማው ውሻ ውኃ ስታጠጣ አብሯት የነበሩ ሴቶች ‹‹ማድጋሽን አጎደልሺው፣ ቀድቼ እሞለዋለሁ እንዳትይ ጉድጓዱ ጥልቅ ነው መቅጃም የለሽም›› አሏት፡፡ ክብርት እመቤታችንም ‹‹ውሃ የሚገኘው ከወደላይ ነው እንጂ ከወደታች ነውን? ፍጥረቱን ያጠጣ ጌታ ይሞላልኛል›› አለቻቸው፡፡ ማድጋዋም በተአምራት ሞልቶ ተገኘ፡፡ ሴቶቹም ዳግመኛ ‹‹በዚህ ዘመን አምላክ ከድንግል ይወለዳል ይላሉ ካንቺ ይሆን?›› እያሉ ሲዘብቱባት ወዲያው ከወደኋላዋ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል መጥቶ ‹‹እነሆ ትጸንሻለሽ›› አላት፡፡ እመቤታችንም ዞር ብትል የተናገራትን አጣችው፡፡ በዚህም ጊዜ ‹‹አባቴን አዳምን እናቴን ሔዋንን ያሳተ ጠላት ይሆናል›› ብላ ሄደች፡፡
ዳግመኛም እመቤታችን ከቤት ደርሳ ማድጋዋን ስታስቀምጥ መልአኩ አሁንም በድምፅ ‹‹እነሆ ትጸንሻለሽ›› አላት፡፡ እመቤታችንም ይህን ጊዜ ‹‹ምነው ይህስ ነገር ደጋገመኝ እንዲህ ያለውን ነገር ቤተ መቅደስ ሄደው ሊረዱት ይገባል›› ብላ ወደ ቤተ መቅደስ ሄዳ ወርቅና ሐር እያስማማች ስትፈት መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል እሁድ ቀን በ3 ሰዓት በገሃድ ተገለጸላትና እጅ እየነሳ እየሰገደ አበሠራት፡፡ ‹‹የዕውነተኛ ንጉሥ እናቱ እመቤታችን ላንቺ ፍቅር አንድነት ይባል›› አላት፡፡ ዳግመኛም ‹‹አንቺ ከሴቶች ይልቅ ተለይተሸ ንዕድ ክብርት ነሽ›› አላት፡፡ አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናቸ ክብርት እመቤታችንም የብርሃናዊውን መአልክ የቅዱስ ገብርኤልን ቃል በሰማች ጊዜ ‹‹እንዲህ ያለውን ሰላምታ እንደምን ይቀበሏል! እንዴትስ መቀበል ይቻላል? እንጃ›› አለችው፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልም ‹‹ማርያም ሆይ! መንፈስ ቅዱስ ያድርብሻል፣ ኃይለ ልዑል ወልድም ሥጋሽን ይለብሳልና አይዞሽ አትፍሪ›› አላት፡፡ ዳግመኛም ‹‹ይህ ካንቺ የሚወለደው ጽኑ ከሃሊ ነው፡፡ ስሙንም ኢየሱስ ትዪዋለሽ፣ እርሱ ታላቅ ይሆናል የልዑል ልጅም ይባላል፣ ጌታ አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል፣ በያዕቆብ ቤትም ላይ ለዘለላም ይነግሣል፣ ለመንግሥቱም መጨረሻ የለውም›› አላት፡፡ እመቤታችንም መልአኩን ‹‹ምድር ያለ ዘር ፍሬን አትሰጥምና እኔ ወንድ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆናል?›› አለችው፡፡ መልአኩም መልሶ ‹‹መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፣ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል። እነሆም ዘመድሽ ኤልሳቤጥ እርሷ ደግሞ በእርጅናዋ ወንድ ልጅ ፀንሳለች፡፡ ለእርስዋም መካን ትባል ለነበረችው ይህ ስድስተኛ ወር ነው፣ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና›› አላት፡፡ ክብርት እመቤታችንም ይህን ጊዜ ‹‹እነሆኝ የጌታ ባሪያ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ›› አለችው፡፡ መልአኩም ከእርሷ ዘንድ ሄዶ ተሠወረ፡፡ አካላዊ ቃልም በማኅፀኗ አደረ፡፡ በዚያችም ቅጽበት የእመቤታችን የፊቷ መልክ ተለወጠ፣ እንደፀሐይም አሸበረቀ፡፡ ከበዓለ ልደቱ በሰላም ያድርሰን!
+ + +
በዚህችም ዕለት ዳግመኛ አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናቸ ክብርት እመቤታችንን የከበረ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ባበሠራት መሠረት ቅዱስ ደቅስዮስ በዓልን አደረገ፡፡ በዓልን የማክበሩ ምክንያትም እንዲህ ሆነ፡- መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል እመቤታችንን ያበሠራትና የጌታችንም ፅንሰት የተከናወነው በመጋቢት ወር በ29ኛው ቀን በዕለተ እሁድ በ3 ሰዓት ነው፡፡ ታዲያ ምነው በታኅሣሥ 22 ብሥራቱና ፅንሰቱ ተከበረ? ቢሉ መጋቢት 29 ቀን ሰሙነ ሕማማት ላይ ይውላልና በዚህ ወቅት ደግሞ ፍጹም ሐዘን ልቅሶ ጾም ጸሎት ይያዛል እንጂ ደስታ ፌሽታ እልልታ ጭብጨባ የለም፡፡ ዓቢይ ጾም ፍጹም የሐዘን ወራት ነው፡፡ ታቦት አውጥቶ በዓል ማክበር ስህተት ነው፤ የአባቶችንም ሥርዓት ማፍረስ ነው፡፡ ምስጋና ይድርሳቸውና ቅዱሳን አባቶቻችን ሁሉንም ነገር በሥርዓት በሥርዓቱ አድርገው ሰፍረው ቆጥረው አስቀምጠውልናል፡፡ ከዓቢይ ጾም በኋላ ያሉትን 50 ቀናት ረቡዕና ዓርብንም ጭምር ሥጋ እንኳን እንድንበላ ነው ሥርዓት የሠሩልን፡፡ አባቶቻችን የሠሯት ሕግ ፍጽምት ናት፡፡ በዚህም መሠረት አባቶቻችን ሥርዓትን ሠሩልንና የመጋቢት 27 የጌታችንን የስቅለቱን በዓል ወደ ጥቅምት 27 ቀን አምጥተው እንዲሁም የመጋቢት 5 የአቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስን የዕረፍት በዓል ወደ ጥቅምት 5 ቀን አዙረው እንዲከበር አድርገዋል፡፡ የመጋቢት 29 የብሥራቱን በዓል ደግሞ ወደ ታኅሣሥ 22 ቀን አዙረውት በዚህ ዕለት እንዲከበር አድርገውታል፡፡ አንድም ነገረ ልደቱን ከማክበር አስቀድሞ ነገረ ፅንሰቱን ማዘከር ማክበር ተገቢና መሆንም ያለበት ነውና ነው፡፡ ይህንንም ያደረገው ታላቁ አባት ቅዱስ ደቅስዮስ ነው፡፡ በእመቤታችን ፍቅር ልቡ የነደደው ይህ ታላቅ አባት የእመቤታችንን

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

30 Dec, 13:04


ተዓምራቶቿን የጻፈላትም እርሱ ነው፡፡ እርሱም ከፍቅሩ ጽናት የተነሣ የእመቤታችንን የተአምራቷን መጽሐፍ ሰብስቦ አዘጋጀ፡፡
አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናቸ ክብርት እመቤታችንም ተገለጸችለትና መጽሐፉን በእጇ አንሥታ ይዛ ‹‹ወዳጄ ደውስዮስ ሆይ! ይህን መጽሐፍ ስለጻፍክልኝ ባንተ ደስ አለኝ፣ አመሰገንኩህ፣ እንዳከበርከኝ እኔም አከብርሃለው›› አለችው፡፡ ከዚህም በኋላ ከእርሱ ተሠወረች፡፡ ደቅስዮስም እመቤታችንን ከመውዱ የተነሣ ፈጽሞ ደስ አለው፡፡ ፍቅሯም እንደ እሳት አቃጠለው፡፡ የእርሷን ክብር አብዝቶ ይጨምር ዘንድ ምን እንደሚያደርግ የሚሠራውን ያስብ ጀመር፡፡
ከዚህም በኋላ በዚያን ጊዜ ጾም ስለነበር ሰዎች አስቀድመው ሊያከብሩት ያልተቻላቸውን መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ባበሠራት ቀን በዓሏን አከበረ፡፡ እርሱም የከበረ የሚሆን የልደትን በዓል ከማክበር አስቀድሞ በ8 ቀን አደረገ፡፡ ይኸውም ታኅሣሥ በባተ በ22ኛው ቀን ነው፡፡ ይኽችውም ሥርዓቱ እስካሁን ጸንታ ኖራለች፡፡ ሰዎቹም በዓሉን ባከበሩ ጊዜ እጅግ ደስ አላቸው፡፡ በዚህም ጊዜ አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናቸ ክብርት እመቤታችን በእጇ የከበረ ልብስ ይዛ ዳግመኛ ለቅዱስ ደቅሲዮስ ተገለጸቸለትና ‹‹አገልጋዬ የሆንክ ወዳጄ ደቅስዮስ ሆይ! በዕውነት አመሰገንኩህ፣ በአንተ ደስ አለኝ፣ ሥራህንም ወደድኩ፡፡ በእኔም ደስ እንዳለህና የከበረ መልአክ ገብርኤል እኔን በአበሠረበት ቀን በዓሌን ስላከበርክ ሰውንም ሁሉ ስለእኔ ደስ ስላሰኘህ እኔም ዋጋህን ልሰጥህ መጥቻለሁ፤ አንተ በዚህ ዓለም እንዳከበርከኝ እኔም በሰው ሁሉ ፊት አከብርህ ዘንድ እወዳለሁ›› አለችው፡፡ ይህንንም ካለችው በኋላ ‹‹እርሷን ትለብስ ዘንድ ይህችን ልብስ እነሆ አመጣሁልህ፤ በላዩም ትቀመጥ ዘንድ ይህን ወንበር አመጣሁልህ ፡፡ ከሰው ወገን አንድ ስንኳ ይህችን ልብስ ሊለብሳት በዚህችም ወንበር ላይ ሊቀመጥ የሚቻለው የለም፡፡ ይህንን ነገሬን የሚተላለፍ ቢኖር እኔ እበቀለዋለሁ›› አለችውና ሰማያዊ ልብስና ሰማያዊ ወንበር ሰጠችው፡፡ እመቤታችንም ይህንን ተናግራ ከባረከችው በኋላ ከእርሱ ተሠወረች፡፡
ከዚህም በኋላ ቅዱስ ደቅስዮስ በዚሁ በዓለ ብሥራትን ባከበረበት ዕለት ታኅሣሥ 22 ቀን ካረፈ በኋላ አንድ ሌላ ኤጲስቆጶስ በተሾመ ጊዜ እመቤታችን ለቅዱስ ደቅስዮስ የሰጠችውን ልብስ ለበሰ፣ በወንበሩም ላይ ተቀመጠ፡፡ ሰዎችም ይህን አይተው ‹‹እባክህ ይቅርብህ እመቤታችን እንዲህ ብላ ተናግራለችና›› ቢሉት በመታጀር ‹‹እርሱም (ደቅስዮስም) ሰው እኔም ሰው፣ እርሱም ኤጲስቆጶስ እኔም ኤጲስቆጶስ›› ብሎ በትዕቢት ተናገረ፡፡ በወንበሩም ላይ እንደተቀመጠ ወድቆ ሞተ፡፡ ይህንንም ያዩ ሁሉ ከእመቤታችን ተአምር የተነሣ አደነቁ፡፡ እጅግም ፈርተው እመቤታችንን አከበሯት፡፡
ለቅዱስ ደቅስዮስ የተለመነች ክብርን የተመላች ድንግል ወላዲተ አምላክ ለእኛም ትለመነን! አምላካችን ልጇ በምልጃዋ ይማረን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

29 Dec, 13:26


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ታኅሣሥ 21-ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በበግ እረኛ ተመስሎ የተገለጠበት ዕለት ነው፡፡
+ ዳግመኛም በዚኽች ዕለት ሐዋርያው ቅዱስ በርናባስ ዕረፍቱ ነው፡፡ በርናባስ ማለት የመጽናናት ልጅ ማለት ነው፡፡ ይኽም ቅዱስ ሐዋርያ ከሌዊ ነገድ የሆነ ሀገሩ ቆጵሮስ ነው፡፡ የቀድሞ ስሙ ዮሴፍ ነበር፡፡ ክብር ይግባውና ጌታችን ከመከራው በፊት ወንጌልን ይሰብኩ ዘንድ ከላላከቸው ከ72ቱ አርድእት መረጠውና ስሙን በርናባስ አለው፡፡
ከጌታችን ዕርገት በኋላ አጽናኝ መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜ ቅዱስ በርናባስ ከሐዋርያት ጋር የመንፈስ ቅዱስን ስጦታ ተቀብሎ በጌታችን ስም ወንጌልን ዞሮ አስተማረ፡፡ ቅዱስ በርናባስ ትልቅ የእርሻ ቦታ ነበረውና እርሱን ሸጦ ዋጋውን አምጥቶ ለድኆችና ጦም አዳሪዎች እንዲሰጠጥ ከሐዋርያት እግር ሥር አኖረው፡፡

ቅዱስ ጳውሎስ ከአሳዳጅነት ተመልሶ ወንጌልን መስበክ በጀመረ ጊዜ ራሳቸው ሐዋርያትም ቢሆኑ ጳውሎስ እንደተመለሰና ለጌታችን ሐዋርያ እንደሆነ አላመኑትም ነበር፡፡ ይኽ ቅዱስ በርናባስ ግን የጳውሎስን በትክክል መመለስ ዐውቆ ለሌሎቹ ሐዋርያት መሰከረላቸው፡፡ ‹‹… በርናባስ ግን ጳውሎስን ወስዶ ወደ ሐዋርያት አገባውና ጌታን በመንገድ እንዴት እንዳየውና እንደ ተናገረው በደማስቆም በኢየሱስ ስም ደፍሮ እንዴት እንደ ነገረ ተረከላቸው›› እንዲል ቅዱስ ወንጌል፡፡ ሐዋ 9፡27፡፡ ጌታችን ለጳውሎስ በመንገድ እንደተገለጠለትና እንዳናገረው ከዚያም በኋላ ጳውሎስም በጌታችን ስም በደማስቆ ወንጌልን ማስተማር መጀመሩን ነገራቸው፡፡ ከዚህም በኋላ የከበሩ ሐዋርያት የእግዚአብሔርን ሥራ ሲሠሩ ሲጾሙ ሲጸልዩ መንፈስ ቅዱስ ‹‹በርናባስንና ሳውልን ለጠራኋቸው ሥራ ለዩልኝ›› አቸው፡፡ ሐዋ 13፡2፡፡ ከዚህም በኋላ ሐዋርያት ጹመው ጸልየው በራሳቸው ላይ ጭነው በርናባስንና ጳውሎስ ሾሟቸው፡፡ ከመንፈስ ቅዱስም ተሹመው ወደ ሴሌውቅያ ወረዱ፡፡ ከዚያም ወደ በርናባስ አገር ወደ ቆጵሮስ ሄዱ፡፡ የእግዚአብሔርንም ቀል በሀገሩ ሁሉ እየዞሩ አስተማሩ፡፡

ከዚህም በኋላ በርናባስንና ጳውሎስ ልስጥራን በተባለ አገር ደርሰው በዚያ የነበረውን አንድ ልሾ (እግሩ የሰለለ) ሰው በፈወሱት ጊዜ የልስጥራን ሰዎች በሊቃኦንያ ቋንቋ ‹‹አማልክት ሰዎችን መስለው ወደ እኛ ወርደዋል›› ብለው መሥዋዕት ሊሠውላቸው ወደዱ፡፡ በርናባስን ‹‹ድያ›› ጳውሎስን ደግሞ ‹‹ሄርሜን›› አሏቸው፡፡ የከበሩ ሐዋርያት በርናባስንና ጳውሎስ ግን ይህን ሲሰሙ ልብሳቸውን ቀደው ወደ ሕዝቡ በመሄድ ድምፃቸውን ከፍ አድርገው እንዲህ አሏቸው፡- ‹‹እናንተ ሰዎች ይህ ነገር ምንድነው? እኛማ እንደናንተ የምንሞት ሰዎች ነን፣ ይህን ከንቱ ነገር ትታችሁ ሰማይና ምድርን በውስጣቸው ያለውንም ሁሉ ወደፈጠረ ወደ ሕያው እግዚአብሔር ትመለሱ ዘንድ እናስተምራችኋለን›› አሏቸው፡፡ እንዲህም ከሏቸው በኋላ መሥዋዕት ማቅረባቸው በጭንቅ አስተዋቸው፡፡ ሐዋ 14፡1-15፡፡

ከዚህም በኋላ በርናባስና ጳውሎስ ብዙ አገሮች ካስተማሩ በኋላ በርናባስ ከጳውሎስ ተለይቶ ማርቆስን ይዞ ወደ ቆጵሮስ ሄደ፡፡ በዚያም ብዙዎችን አስተምሮ ጌታችንን ወደማመን መለሳቸውና የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው፡፡ በዚህም በቆጵሮስ አገር ያሉ አይሁድ በቅዱስ በርናባስ ቀኑበትና በመኳንንት ዘንድ ወነጀሉት፡፡ ይዘውም በእግር ብረት አስረው ጽኑ ግርፋትን ገረፉት፡፡ ቀጥሎም በድንጋይ ወገሩት፡፡ ብዙ ካሠቃዩትም በኋላ በመጨረሻ ወስደው ከሚነድ እሳት ውስጥ ጨመሩት ሐዋርያው ሰማዕትነቱን በዚያው ፈጽሞ የክብር አክሊልን ተቀዳጀ፡፡

ሐዋርያት ዓለምን ዕጣ በዕጣ ተከፋፍለው ሲወጡ ቅዱስ በርናባስ ቅዱስ ማርቆስ እያስከተለው ይሄድ ስለነበር፡፡ አሁንም በዚህ መከራው ወቅት ማርቆስም አብሮት ነበር ነገር ግን የእርሱ የሰማዕትነት ጊዜው ስላልደረሰ ማርቆስን እግዚአብሔር ጠብቆት ነበር፡፡ እርሱም የቅዱስ በርናባስን ሥጋ ከእሳት ውስጥ አወጣው፡፡ እሳቱም ሥጋውን ከቶ አልካውም ነበር፣ የራስ ጸጉሩ እንኳን አልተቃጠለችም፡፡ ማርቆስም በርናባስን ባማረ ልብስ ገነዘውና ተሸክሞ ወስዶ ከቆጵሮስ ከተማ ውጭ በዋሻ ውስጥ አኖረው፡፡
የሐዋርያው ቅዱስ በርናባስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን፡፡
+ + +

ጌታችን በዚችህ ዕለት በበግ እረኛ ተመስሎ እንደተገለጠ፡- ጌታችንም ስለራሱ ሲናገር እንዲህ አለ፡- ‹‹መልካም እረኛ እኔ ነኝ፡፡ መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል፡፡ እረኛ ያልሆነው በጎቹም የእርሱ ያልሆኑ ሞያተኛ ግን ተኵላ ሲመጣ ባየ ጊዜ በጎቹን ትቶ ይሸሻል፤ ተኵላም ይነጥቃቸዋል በጎቹንም ይበትናቸዋል፡፡ ሞያተኛ ስለሆነ ለበጎቹም ስለማይገደው ሞያተኛው ይሸሻል፡፡ መልካም እረኛ እኔ ነኝ፣ አብም እንደሚያውቀኝ እኔም አብን እንደማውቀው የራሴን በጎች አውቃለሁ የራሴም በጎች ያውቁኛል፤ ነፍሴንም ስለ በጎች አኖራለሁ፡፡ ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል ድምፄንም ይሰማሉ፥ አንድም መንጋ ይሆናሉ እረኛውም አንድ፡፡›› ዮሐ 10፡11-16፡፡

ዳግመኛም የከበሩ ሐዋርያት እንዲህ አሉ፡- ‹‹በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ። እንደ በጎች ትቅበዘበዙ ነበርና አሁን ግን ወደ ነፍሳችሁ እረኛና ጠባቂ ተመልሳችኋል፡፡›› 1ኛ ጴጥ 2፡25፡፡
‹‹በዙፋኑ መካከል ያለው በጉ እረኛቸው ይሆናልና ወደ ሕይወትም ውኃ ምንጭ ይመራቸዋልና እግዚአብሔርም እንባዎችን ሁሉ ከዓይናቸው ያብሳል፡፡›› ራእ 7፡17፡፡
‹‹በዘላለም ኪዳን ደም ለበጎች ትልቅ እረኛ የሆነውን ጌታችንን ኢየሱስን ከሙታን ያወጣው የሰላም አምላክ…›› ዕብ 13፡20፡፡
‹‹ኢየሱስም ወጥቶ ብዙ ሕዝብ አየና እረኛ እንደሌላቸው በጎች ስለነበሩ አዘነላቸው፡፡›› ማር 6፡34፡፡
የመድኃኔዓለም ቸርነቱ የድንግል እናቱ ምልጃዋ ከሁላችን ጋር ይሁን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

28 Dec, 17:58


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ታኅሣሥ 20-ከሌዊ ነገድ ከአሮን ትውልድ የሆነ ነቢዩ ሐጌ ዕረፍቱ ነው፡፡ ‹‹ሐጌ›› ማለት የእግዚአብሔር መልእክተኛ›› ማለት ነው፡፡ እርሱም ከ12ቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ ነው፡፡ 12ቱ ቅዱሳን ደቂቀ ነቢያት የሚባሉትም ሆሴዕ፣ አሞጽ፣ ሚክያስ፣ ኢዩኤል፣ አብድዩ፣ ዮናስ፣ ናሆም፣ እንባቆም፣ ሶፎንያስ፣ ሐጌ፣ ዘካርያስ እና ሚልክያስ ናቸው፡፡ ዋና (ዓበይት) ነቢያት የሚባሉት አራት ሲሆኑ እነርሱም ኢሳይያስ፣ ኤርምያስ፣ ሕዝቅኤልና ዳንኤል ናቸው፡፡ ከሆሴዕ እስከ ሚልክያስ ድረስ ያሉት ነቢያት ‹‹ደቂቀ ነቢያት›› የተባሉት ምክንያት አንድም የነቢያት ልጆች በመሆናቸው ነው፡፡ ሌላው ደግሞ የጻፏቸው ትንቢቶቻቸው ዓበይት ነቢያቱ ከጻፏቸው ጋር በንፅፅር ሲታይ አነሥተኛ ስለሆነ ነው፡፡

‹‹ነቢይ›› ማለት እግዚአብሔር የመረጠውና የእግዚአብሔርን መልአክት ለሕዝቡ የሚያስተላልፍ ብሎም የተሠወረውንና የሚመጣውን ሁሉ በግልጽ የሚመለከት ማለት ነው፡፡ ነቢያት ሲባሉ በአጠቃላይ ምግባር ሃይማኖታቸው ያማረ፣ ትሩፋት ተጋድሎአቸው የሰመረ ነውና አካሄዳቸው ሁሉ ከእግዚአብሔር ጋር ነው፡፡ ነቢዩ ቅዱስ ሐጌም ትንቢትን በመናገር ሕዝበ እስራኤልን በመገሠጽ እግዚአብሔርን ያገለገለ ነው፡፡

ናቡከነጾር የኢየሩሳሌምን ሕዝብ በማረከ ጊዜ የዚህ ጻድቅ ወላጆች ከእስራኤል ልጆች ጋር ወደ ባቢሎን አገር ወርደው ሔዱ፡፡ ዳርዮስ የተባለው ኩርዝ በነገሠ ጊዜ በሁለተኛው ዘመነ መንግሥቱ ነቢዩ ሐጌ ትንቢት ተናገረ፡፡ ኩርዝ ዳርዮስ ካሰናበታቸው በኋላ የእስራኤል ልጆች ወደ አገራቸው እንደሚገቡ ትንቢት ተናገረ፡፡ ነገር ግን እነርሱም አገራቸው ከገቡ በኋላ ቤተ መቅደስን ከመሥራት ቸል ባሉ ጊዜ እነርሱ ባማሩና በተዋቡ ቤቶች ውስጥ ስለመኖራቸው እንዲህ አላቸው፡- ‹‹ሁሉን የሚገዛ እግዚአብሔር እንዲህ አለ፡- ‹የእኔ ቤት ፈርሷል፣ እናንተ ግን ሁላችሁም ቤታችሁን ታጸናላችሁ› ብሎ ገሠጻቸው፡፡ ስለዚህም ከምድር በላይ ያለች ሰማይ ዝናም ለዘር ትነሣለች ምድርም ፍሬዋን አትሠጥም›› አላቸው፡፡

ከሕዝቡም ውስጥ ደጋጎች የሆኑት ቃሉን ሰምተው እጅግ ፈርተው የእግዚአብሔርን መመስገኛ ቤት እንደሚገባ አድርገው አስውበው መሥራት ጀመሩ፡፡ ጻድቁ ነቢይ ሐጌም 70 ዓመት ከኖረ በኋላ የትንቢቱን ወራት ፈጽሞ በሰላም ዐረፈ፡፡ የትንቢቱም ወራት ለስም አጠራሩ ክብር ይግባውና ጌታችን ከመወለዱ በፊት በ430 ዓመት ነው፡፡
የነቢዩ የቅዱስ ሐጌ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

27 Dec, 14:23


መልክዐ አቡነ አባለ ክርስቶስ (ዘአኅተሞ ገብረ ሥላሴ)

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

30 Nov, 18:08


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ አሜን
ኅዳር 22-ቅዱሳን የሆኑ አምስቱ ወንድማማቾች ቆዝሞስ፣ ድምያኖስ፣ አንቲቆስ፣ ዮንዲኖስ እና አብራንዮስ ከእናታቸው ከቅድስት ቴዎዳዳ ጋር በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡
የእነዚህም አምስት ቅዱሳን እናታቸው ቅድስት ቴዎዳዳ እግዚአብሔርን የምትፈራ መጻተኞችንና ጦም አዳሪዎችን የምትረዳቸው ናት፡፡ አባታቸው ከሞተ በኋላም ብቻዋን በሃይማኖት በምግባር ኮትኩታ ነው ያሳገቻቸው፡፡ ከእነርሱም
ውስጥ ሁለቱ ቆዝሞስና ድምያኖስ የሕክምና ጥበብን ተምረው ሕመምተኞችን ያለዋጋ የሚፈውሱአቸው ይልቁንም ድኆችን አብዝተው የሚረዷቸው ሆኑ፡፡ የተቀሩት ሦስቱ ወንድሞቻቸው ግን ዓለምን ንቀው ወደ ገዳም ገብተው በመመንኮስ በጾም በጸሎት የሚጋደሉ ሆኑ፡፡ በእነዚህም ቅዱሳን ወንድማማቾች ዘመን አባ አጋግዮስ የተሰጣቸውን አደራ ባለመጠበቃቸው ምክንያት በቤተ ክርስቲያን ላይ ታላቅ መከራ መጣ፡፡ ይኸውም የሆነው እንዲህ ነው፡- ታላቁ የአንጾኪያ ንጉሥ ኑማርያኖስ በነገሠ ጊዜ የፋርስና የቁዝ አገር ሰዎች መንገሥቱን ለመጣል ተነሡበት፡፡ በዚህም ጊዜ እነ ቅዱስ ፋሲለደስም፣ ቅዱስ ፊቅጦር፣ ቅዱስ አውሳብዮስ፣ ቅዱስ ቴዎድሮስ በናድልዮስ፣ የንጉሡም ልጅ ቅዱስ ዮስጦስ ከተነሡባቸው ጠላቶቻቸው ጋር ለመዋጋት በጦር ሜዳ ዘመቱ፡፡ ንጉሡም በሌላ ቦታ ሆኖ በጦር ሜዳ የመንግሥቱን ልብስ አውልቆ ዘውዱን ጥሎ ተራ ልብስ ለብሶ ሲዋጋ በጦር ተወግቶ ሞተ ነገር ግን ጠላቶቹ ንጉሡ እንደሞተ አላወቁም ነበር፡፡ ጦርነቱም ባለቀ ጊዜ የሮም መንግሥት ያለንጉሥ ብቻዋን የቀረች መሆኗን ሲያውቁ ዳግመኛ ሊያጠፏቸው በጦር በርትተው መጡ፡፡ የሮም ሰዎችም ተሰብስበው ቅዱስ ፋሲለደስን ‹‹በስራችን ወዳሉ ግዛቶች ወደ ግብጽም ተዋጊ አርበኞችን ይልኩልን ዘንድ እንይቃቸው›› አሉት፡፡ መኳንንቱም ወደ ግብጽ ወርደው በጦር ኃይለኛ የሆኑ ሰዎችን ይዘው ተመለሱ፡፡ ከግብጽ ካመጧቸው ኃይለኛ ሰዎች ውስጥ ከላይዕላይ ግብጽ ስሙ ከርቢጣ የሚባል ፍየል የሚጠብቅ አንድ ኃይለኛ ሰውን ወደ አንጾኪያ አመጡ፡፡ ቅዱስ ፋሲለደስና ህርማኖስም ይህ ሰው የሚያስፈራ በሥራውም ኃይለኛ ጉልበቱ የጸና ጨካኝ መሆኑን አይተው በንጉሡ ፈረስ ላይ ባልደራስ ወይም ሹም አድርገው ሾሙት፡፡

ከጥቂት ወራትም በኋላ ታላቂቱ የንጉሡ ልጅ ከቤተ መንግሥት ሆና በመስኮት በኩል ሆና ሲወጣ ባቱን ሲገባ ደረቱን አይታ በሀፀ ዝሙት ተነድፋ እጅግ ወደደችው፡፡ እርሱንም ሰይጣን ከልጅነቱ ጀምሮ ይከተለው ነበር፡፡ የንጉሡም ልጅ ወስዳ አገባችውና ስሙን ዲዮቅልጥያኖስ አለችው፡፡ የእናቷ ወንድም ቅዱስ ፋሲለደስ ሳያውቅ ንጉሥ አደረገችው፡፡ ሰይጣንም በእርሱ አድሮ ያነጋግረው ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ ቅዱስ ፋሲለደስን ጠርቶት ስለ መንግሥት ሥራ ተነጋገሩ፡፡ ለጦርነትም ሰራዊት ሰበሰቡ፡፡ ምሥራቃዊ ቴዎድሮስ የሠራዊቱ አለቃ ሆኖ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ጦሩን እየመሩ ወደ ጦርነት ሄዶ፡፡

ዲዮቅልጥያኖስም ቅዱስ ፋሲለደስንና ህርማኖስን
የመንግሥትን ሥራ ይሠሩ ዘንድ ከቤተ መንግሥት ተዋቸው፡፡ ምሥራቃዊ ቴድሮስም በጦርነቱ በርትቶ የቁዝ አገርን ሠራዊትፈጃቸው፡፡ የቁዝን የንጉሡን ልጅ ኒጎሚዶስን ማርኮ አምጥቶ ለንጉሥዲዮቅልጥያኖስ ሰጠው፡፡ የቁዝ ሰዎችም ሸሹ፡፡ ንጉሡም የተማረከውን የቁዝን ንጉሥ ልጅ ይዞ ወደ አንጾኪያ ተመለሰ፡፡ በዚያም ወራት የአንጾኪያው ሊቀ ጳጳስ እስጢፋኖስ ዐርፎ በእርሱ ምትክ አባ አጋግዮስ ተሹሞ ነበርና ንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስ አባ አጋግዮስን ጠርቶ ‹‹ጠብቅልኝ›› ብሎ በአደራ ሰጠው፡፡ የቁዝ ንጉሥም ልጁ በአባ አጋግዮስ ዘንድ መኖሩን ሲሰማ በልጁ ሚዛን ልክ ወርቅ አምጥቶ ለአባ አጋግዮስ ሰጥቶት ልጁን ከምርኮ አስመለሰ፡፡ የቁዝ ሰዎችም የንጉሣቸው ልጅ ከምርኮ
መመለሱን በሰሙ ጊዜ እጅግ ተደስተው ዳግመኛ
ዲዮቅልጥያኖስን በጦር ይገጥሙት ዘንድ መልእክት ልከው ‹‹ለጦርነት ተዘጋጅ›› አሉት፡፡ ንጉሡም ይህንን ሲሰማ እጅግ ተቆጥቶ አባ አጋግዮስን መልክተኛ ልኮ ‹‹የሰጠኹህ ልጅ ከአንተ ዘንድ አለ ወይስ የለም?›› አለው፡፡ አባም ‹‹አለ›› ብሎ ዋሸ፡፡ ንጉሡም በልቡ ያለ ሰይጣን እያበረታው ከብዙ ጦር ጋር ዘምቶ ሳለ የቁዝን ንጉሥ ልጅ ከእነርሱ ጋር አየው፡፡ ምስራቃዊ ቴዎድሮስንም ጠርቶት ‹‹ይህ የማየው ልጅ አንተ ማርከህ አምጥተህ የሰጠኸኝ አይደለምን›› አለው፡፡ ቴዎድሮስም ‹‹አዎን›› አለው፡፡ ንጉሡም ‹‹ዳግመኛ ልጁን ማርከህ ካጣህልኝ ብዙ ወርቅና ብር እሰጥሃለሁ›› አለው፡፡ ቴዎድሮስም ‹‹እኔስ ወርቅና ብር ሥልጣንም አልሻም ነገር ግን የተማረኩ ወንድሞቼ ዮስጦስና አውሳብዮስ በሕይወት ካሉ እነርሱን ማምጣት ነው የምፈልገው›› አለው፡፡ በጦርነቱም ወቅትቴዎድሮስ እጅግ በረታና የቁዝን ሠራዊት ማርኮ የንጉሡንም ልጅ ዳግመኛ በመማረክ አምጥቶ ለንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ሰጠው፡፡ ንጉሡም ልጁን ከመረመረው በኋላ የአባ አጋግዮስን እኩይ ሥራ ተመልከቶ መኳንንቱን ሰብስቦ የልጁን ዳግመኛ መማረክ በምሥጢር እንዲጠብቁ ነገራቸው፡፡ ወደ አንጾኪያም በተመለሰ ጊዜ ንጉሡ ቅዱስ ፋሲለደስን ጠርቶ አባ አጋግዮስ ስለ ወርቅ ፍቅር ያደረገውን ነገር ነገረውና ልጁን በቤተ መንግሥት ይጠብቀው ዘንድ በአደራ ሰጠው፡፡ ንጉሡም አባ አጋግዮስን አስቀድሞ ‹‹ልጁ ከእኔ ጋር አለ›› ብሎ ስለዋሽው አሁን ‹‹ልጁን አምጣልኝ ከአባቱ ጋር ታርቄአለሁና›› አለው፡፡ አባም ‹‹ልጁማ ሞቶ አስክሬኑን እየጠበቅሁ ነው›› አለው፡፡ ንጉሡም ‹‹አስክሬኑን አምጣልኝ›› አለውና አባ አጋግዮስ ሌላ የሞተ ሰው ሬሳ ይዞለት መጣ፡፡

ንጉሡም ተገርሞ ‹‹በእውኑ ይሄ የቁዝ አገር ንጉሥ ልጅ
የኒጎሚዶሚስ አስክሬን ነውን?›› ብሎ ሲጠይቀው አባ አጋግዮስ በውሸት ‹‹አዎን›› አለው፡፡ ያንጊዜም ንጉሡ ‹‹በል ዛሬ ቅዳሴ ቀድሰህ ቁርባን ሠርተህ እኔንና ሕዝቡን አቁርበን›› አለው፡፡ ሊቀ ጳጳሱም ቅዳሴ ገብቶ ሥጋወደሙን ለማቀበል ከመቅደስ ወጥቶ ድርገት ሲወርድ ንጉሡ ወደ እርሱ ቀርቦ ‹‹በል ይሄ ሬሳ የቁዝ አገር ንጉሥ ልጅ ነው ብለህ በሥጋ ወደሙ ማልልኝ›› አለው፡፡ አባ አጋግዮስም በሥጋ ወደሙ ማለለት፡፡ ንጉሡም አባ አጋግዮስ በጌታችን ሥጋወደሙና በታቦቱ ፊት በውሸት እንደማለ ባየጊዜ እሳት ወዲያው ወርዶ አባን የሚያቃጥለው መስሎት ነበር፡፡ ወዲያውም ቅዱስ ፋሲለደስን ልጁን እንዲያመጣው አዘዘውና ልጁን አመጣለት፡፡ ልጁም አባቱ ብዙ ወርቅ ለአባ አጋግዮስ ከፍሎ እንደወሰደው በሕዝቡ ሁሉ ፊት መሰከረ፡፡

ጌታችን ስለ ሥጋ ወደመ ክብር ሲል በአጋግዮስ ላይ ተአምር
ሊያሳይበት ነበር ነገር ግን ንጉሡን ሰይጣን ለክፋት ያፋጥነው ነበርና ንጉሡ ቸኩሎ ፈጣሪውን ካደ፡፡ ንጉሡም አባ አጋግዮስን ከጠላት የተቀበለውን ወርቅ እንዲያመጣው ካስደረገው በኋላ ወርቁን በእሳት አስፈልቶ የፈላውን ወርቅ በሕይወት ሳለ ቢያስጠጣው ሊቀ ጳጳሱ ወዲያው ለሁለት ተሰንጥቆ ሞተ፡፡
ንጉሡም ‹‹በሥጋ ወደሙ በሐሰት ሲምል እሳት ከሰማይ ወርዶ ያልበላው ለምንድነው?›› ብሎ ወደ ክህደት ገባ፡፡ ወዲያውም እርሱ በሚገዛበት አውራጃ ሁሉ አብያተ ክርስቲያናት እንዲዘጉ በምትካቸውም የጣዖታት ቤቶች እንዲከፈቱ አዘዘ፡፡ ዳግመኛም የአብያተ ክርስቲያናት አገልጋዮችም በሙሉ ለጣዖታቱ እንደሠው ያልሠዋ ቢኖር ግን እንዲገደል አዘዘ፡፡ የትእዛዙንም ደብዳቤ

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

30 Nov, 18:08


በግዛቶቹ ሁሉ ላከ፡፡ ከዚህ በኋላ ነው እንግህ ንጉሥ
ዲዮቅልጥያኖስ በዓለም ላይ ከ500 ሺህ በላይ ክርስቲያኖችን በግፍ የገደለው፡፡ ከ90 ሺህ በላይ የሚሆኑትን ክርስቲያኖች ደግሞ በእሥር ቤት አሠቃያቸው፡፡ ደገኛው ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ እስከነገሠ ድረስ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዲዮቅልጥያኖስ አዋጅ ምክንያት እጅግ ብዙ የመከራና የሥቃይ ዘመናትን አሳልፋለቸ፡፡

ቅዱስ ቆዝሞስና ቅዱስ ድምያኖስም ይህ የዲዮቅልጥያኖስ
አዋጅ በዓለም አብያተ ክርስቲያናት ላይ በታወጀ ጊዜ እነርሱ ግን የጌታችንን ወንጌል ያስተምሩ ነበር፡፡ ዲዮቅልጥያኖስም ቅዱስ ቆዝሞስና ቅዱስ ድምያኖስ ወንጌልን እየሰበኩ ብዙዎችንም ክርስቲያን እያደረጓቸው መሆኑን በሰማ ጊዜ ጭፍሮቹን ልኮ አስመጣቸው፡፡ እርሱም እምነታቸውን በመረመራቸው ጊዜ በክርስቶስ የሚያምኑ ክርስቲያን መሆናቸውን ነገሩት፡፡ ንጉሡም በዚህ ጊዜ ብዙ እንዲያሠቃዩአቸው ለመኮንኑ አሳልፎ ሰጣቸው፡፡
እርሱም ወስዶ በተለያዩ ማሠቃያዎች አሠቃያቸው፡፡ በእሳት
አቃጠላቸው፤ ብዙ ግርፋትም ገረፋቸው ነገር ግን ጌታችን
መከራውን የሚታገሱበትን ኃይል ሰጣቸው፡፡ መኮንኑም ቅዱስ ቆዝሞስንና ቅዱስ ድምያኖስን ሌሎች ሦስት
ወንድሞች እንዳሏቸው በሰማ ጊዜ እነርሱንም (አንቲቆስን፣
ዮንዲኖስን እና አብራንዮስን) አስመጥቶ አምስቱንም አንድ ላይ መንኮራኩር ውስጥ ጨምሮ አሠቃያቸው፡፡ ከሚነድ እቶን እሳት ውስጥ በጨመራቸው ጊዜ በውስጡ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ቆዩ፡፡ ከሦስት ቀንም በኋላ ያለምንም ጥፋት ጤነኞች ሆነው ወጡ፡፡ ዳግመኛም ከብረት አልጋ ላይ አስተኝቶ ከሥር እሳት አነደደባቸው ነገር ግን አሁንም ያለ ምንም ጥፋት ፍጹም ጤነኛ አደረጋቸው፡፡ በዚህም ምክንያት ብዙዎች አመኑ፡፡ መኮንኑም እነዚህን አምስት ቅዱሳን ማሠቃየት በሰላቸው ጊዜ እነርሱም አልሞት ስላሉት መልሶ ወስዶ ለንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ሰጣቸው፡፡ ንጉሡም የተለያዩ ማሠቃያዎችን በማፈራረቅ ብዙ አሠቃያቸው፡፡
እግዚአብሔርም ከመከራቸው ሁሉ ያድናቸው ነበር፡፡ እናታቸው ቅድስት ቴዎዳዳ ልጆቿን እስከመጨረሻው ተጋድለው የሰማዕትነት አክሊልን እንዲቀዳጁ ታበረታቸው ነበር፡፡ ዳግመኛም እርሷ ሰማዕት ትሆን ዘንድ ተመኘች፡፡

ንጉሡንና የረከሱ ጣዖቶችንም እየረገመች ስትናገር ንጉሡ በታላቅ ቁጣ ሆኖ አንገቷን በሰይፍ አስቆረጠውና የተመኘችው የሰማዕትነት አክሊልን ከልጆቿ ቀድማ አገኘች፡፡
የቅድስት ቴዎዳዳ ሥጋዋ በመሬት ላይ ወድቆ በቀረ ጊዜ ልጇ
ቅዱስ ቆዝሞስ በሥቃይ ውስጥ ሆኖ ‹‹የዚህች አገር ሰዎች
ሆይ! ይህችን ደካማ መበለት ሥጋዋን አፈር አልብሶ ይሠውራት ዘንድ ከውስጣችሁ ርኅራኄ በልቡ ያደረበት የለምን›› ብሎ ጨኸ፡፡ በዚህም ጊዜ የንጉሡ የቅርብ አማካሪና ባለሥልጣን የነበረው የህርማኖስ ልጁ ቅዱስ ፊቅጦር ይህንን የቅዱስ ቆዝሞስን ቃል በሰማ ጊዜ ከመንግሥት ሰዎች መካከል ደፍሮ ሥጋዋን አንሥቶ ገንዞ ቀበራት፡፡ (ይህም ቅዱስ ፊቅጦር ስለ ክርስቶስ ፍቅር በኋላ በገዛ አባቱ እጅግ ተሰቃይቶ በ153 ችንካሮች ተቸንክሮ የሞተ እጅግ የከበረ ታላቅ ሰማዕት ነው፡፡)

ከዚህም በኋላ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ እነዚህን አምስት ቅዱሳን ወንድማማቾች ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ ራሶቻቸውን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ፡፡ በትእዛዙም መሠረት አምስቱንም ቅዱሳን በ303 ዓ.ም በየተራ ሁሉንም አንገታቸውን ሰየፏቸውና የሰማዕትነት ፍጻሜአቸው ሆነ፡፡ የክብር አክሊልንም ተቀዳጁ፡፡

የመከራውም ዘመን ሲያልፍ ምእመናን ቤተ ክርስቲያን
ሠርተውላቸው ሥጋቸውን በውስጧ አኖሩ፡፡ ከቅዱሳኑም ሥጋ ብዙ አስገራሚ ተአምራት ተፈጽመው ታዩ፡፡ ዳግመኛም ዛሬ የቅዱስ ቆዝሞስ ማኅበርተኞች የሆኑ 262 ወንዶችና 49 ሴቶች በሰማዕትነት ዐርፈዋል፡፡ በረከታቸውይደርብን፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

29 Nov, 19:29


ታቦትነቷን አጒልቶ አስተምሯል፡፡በተጨማሪም የእግዚአብሔር ታቦት ከቤተ አቢዳራ ወደ ዳዊት ከተማ ስትገባ፤ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት ከደስታው ብዛት የተነሣ የጌታ የክብሩ መገለጫ በኾነችው በታቦቷ ፊት እየዘለለ እንዳመሰገነ ኹሉ (፪ሳሙ ፭፥፲፪-፲፭)፤ አካላዊ ቃልን በማሕፀኗ የተሸከመች የአምላክ ታቦት ቅድስት ድንግል ማርያምም ወደ ተራራማው ሀገር ወደ ይሁዳ ከተማ ወደ ኤልሳቤጥ ቤት በኼደች ጊዜ፤ ታላቁ ነቢይ መጥምቁ ዮሐንስ በእናቱ ማሕፀን ኾኖ ከደስታው ብዛት የተነሣ እየዘለለ አመስግኗል (ሉቃ ፩፥፵፩-፵፭)፡፡
ይኽነን ምስጢር ሊቁ ቅዱስ ያዕቆብ ዘስሩግ ሲያብራራ ‹‹She, the palace of flesh, walked and ascended, and the king was in it…›› (የሥጋ ቤተ መንግሥት የኾነች እርሷ(ማርያም) ኼደች፤ ወረደች ንጉሡም በውስጧ ነበረ፤ በደስታ በእናቱ ኾድ ውስጥ ኾኖ ወደ ዘለለው ልጅ ደጃፍ ስትደርስ ቆመች፤ ኀያሉ አንኳኳ፤ ሠራተኛው በአባቱ ቤት ውስጥ ኹኖ ተንቀጠቀጠ፤ ንጉሡ ተናገረ፤ አገልጋዩ ሰገደለት አከበረው አመለከውም፤ ፈጣሪ ሲያየው የመካኗ ልጅ በደስታ ዘለለ፤ የእግዚአብሔር ልጅ ኀይል ሲገለጥ ፅንሱ ዘለለ፤ ሕፃናትን የሚፈጥረውን አምላክ ድምፅ በሰማ ጊዜ ፅንሱ ተነቃቃ፤ የኹሉን ቻይ ጌታ ፈቃድ ማሕፀኗን መልቷልና፤ ያ ዝም ያለው (ጌታ) ተመለከተ፤ ዝም ያለው (ዮሐንስ) አደነቀ፤ በሥጋ ውስጥ የተሰወረው አዟልና፤ ያ ያልተወለደው ድፍረቱን አሳየ፤ የድንግል ልጅ ሲፈቅድ የመካኒቱ ልጅ ተደመመ፤ የተሰወረው ሲጣራ፤ ዝም
ባለው ልጅ ላይም መደነቅ መላበት፤ የአንበሳ ደቦል በእናቱ ውስጥ አገሣ፤ ያዕቆብ እንደጻፈው፤ ጥጃው የሸመገለው ሰውዬ ልጅ ድምፁን ሲሰማ ተንቀጠቀጠ፤ ትንሿ ሴት (እመቤታችን) በአሮጊቷ ዦሮ (በኤልሳቤጥ) ደስ የሚያሰኝ ቃልን አሰማች፤ ድምፃ በዦሮዋ ሲሰማ አንዳች የሚያነሣሣ መንፈስ ዐደረባት፤ ፅንሱም በደስታና በአክብሮት ሊያመሰግን ተነሣሣ፤ በደስታ በታቦት ፊት በደስታ በዘለለው በዳዊት ልጅ ፊት ሳያቋርጥ የእናቱን ማሕፀን ገፋ፤ ሊወጣናሊያመልክም ፈለገ፤ ሊጐበኘው የመጣው ጌታ በበር እንዳይቆም… አንዱ ሌላኛውን አስቀድሞ ያሳየ ነበርና፡፡
የነቢያትን እና የነገሥታትን በእግዚአብሔር ፊት በደስታ መዘመር እስራኤላውያን ቀድሞውኑ የተለማመዱት ነገር ነበር፤ ንጉሡ ዳዊት በቃል ኪዳኑ ታቦት ፊት ይዘል ነበር፤ ከልቡ ደስታ የተነሣ ለንጉሣውያኑ ደንብ አልታዘዘም፤ እንዲኹ ዮሐንስ ደግሞ ገና ፅንስ ሣለ ከደስታው የተነሣ ከዳዊትም በላቀ ኹኔታ ዘለለ፤ ፅንስ ቢኾንም የእርሱ ባልኾነው በዚኽ ዕድሜ አልተገታም፤ ድንግል እና ቡርክት የኾነችው እናት የእግዚአብሔር ቤት ምስጢራት ከመሉባት ታቦትም በላይ ውብ ነበረች፤ ዳዊትም በአክብሮት በታቦቱ ፊት ዘለለ፤ ይህም ዮሐንስ በማርያም ፊት ሊዘል እንዳለ አስቀድሞ ያሳይ ነበርና፤ ከዳዊት በቀር ንጉሥመዝለሉ ተሰምቶ አይታወቅም ሕፃን መዝለሉም እንዲሁ፤ ነቢያት ካህናት የእግዚአብሔርን ልጅ መንገድ አስቀድመው አመለከቱ፤ እርሱም በመጣ ጊዜ ይሹት የነበሩትን ምልክቶች ፈጸማቸው፤ የጌታውን የንጉሡን ምልክት ይጠቁም ዘንድ፤ ዳዊት በደስታ በታቦቱ ፊት ዘለለ፤ዮሐንስ በማርያም ፊት የሚያደርገውን ነገር ምሳሌ በመኾን አሳየ፤ ያቺም ብላቴና እንዲኹ የእግዚአብሔር ታቦት ነበረችና፤ የምስጢራት ጌታ በእርሷ ዐደረ፤ ከዚኽም የተነሣ ልክ እንደዚያ ጀግና ንጉሥ ሕፃኑ በእርሷ ፊት በደስታ
ዘለለ፤እርሷ በቅዱስ ቃል እንደተመላ ታቦት የተሸከሟት ነበረች፤ የትንቢት ምስጢራት ፍቺ በእርሷ ዐደረ፤ ሞገሷ ከታቦቱ የበለጠ ይኾን ዘንድ፤ በድንቅ ኹኔታ አሸብርቃ ነበርና ሕፃኑ ዘለለ፤በተዘጋ ማሕፀን ውስጥ ሳለ ሕፃኑ የተሰማው ደስታ ያልተገደበ ነበር፤ እስከዚያን ዕለት በሐዘን በነበረ ማሕፀን ውስጥ ኹኖ በደስታ ፈነጠዘ) በማለት ይኽ የነገረ መለኮት ምሁር ቅድስት ድንግል ማርያምን በምስጢር የተመላች የአምላክ ታቦት መኾኗን በማብራራት ገልጦታል፡፡

ዳግመኛም ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት በእግዚአብሔር ታቦት ፊት በደስታ ሲያመሰግን አይታ የሳኦል ልጅ ሜልኮል ብትንቀው እግዚአብሔር ተቈጥቷት በሕይወቷ ዘመን ኹሉ የልጅ ጸጋ እንዳታገኝ በምክነት ቀጥቷታል (፪ሳሙ ፮፥፳-፳፫)፡፡ ይኸውም ማደሪያው የኾነች ታቦቷን በድፍረት ሊነካት የሞከረውን ኦዛን የቀሠፈ፤ ዳግመኛ የጌትነቱ መገለጫ በኾነች በታቦቷ ፊት ያመሰገነ ዳዊትን የናቀች ሜልኮልን በምክነት የቀጣ አምላክ፤ዛሬም ፱ ወር ከ፭ ቀን በማሕፀኗ የተሸከመችውን፤ የድንግልና ጡቶቿን የመገበችውን፤ በዠርባዋ ያዘለችውና በደረቷ የታቀፈችውን ቅድስት እናቱን በድፍረት የሚነቅፉ፤ ሔዋንን ያሳተ እባብ መርዝ ክሕደቱን በአፋቸው የረጨባቸው በልቡናቸው ያሳደረባቸው፤ ነቢያት ሐዋርያት ያስተማሩትን የሚያጣምሙ ፀረ ማርያሞች ለዚኽ ድፍረታቸው ንስሓ ካልገቡ የዘላለም ቅጣትና፤ በዚኽ ዓለምም ከድንግል ማርያም አማላጅነት የሚገኘውን ታላቅ በረከት በማጣት እንደ ሜልኮል የበረከትና የጸጋ ምክነት ያጋጥማቸዋል፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት ጽዮንን የሚጠሉ ኹሉ ስለሚደርስባቸው ዘላለማዊ ምክነት በመዝ )!፰፥፭-፰ ላይ ‹‹ጽዮንን የሚጠሉ ኹሉ ይፈሩ፤ ወደ ኋላቸውም ይመለሱ፤ በሰገነት ላይ እንደበቀለ ሣር ሳይነቀል እንደሚደርቅ ለሚያጭደው እጁን፤ ነዶዎቹን ለሚሰበስብ ዕቅፉን እንደማይመላ ይኹኑ፤ በመንገድም የሚያልፉ የእግዚአብሔር በረከት በእናንተ ላይ ይኹን በእግዚአብሔር ስም እንመርቃችኋለን አይሉም›› በማለት እንደተናገረ ጽዮን የተባለች የድንግል ማርያም አማላጅነት የሚቀዋወሙ የዲያብሎስ የግብር ልጆች መ*ናፍ*ቃን እንደ ሜልኮል ከእግዚአብሔር ጸጋ የራቁ ናቸው፤ ጥንቱን ዲያብሎስ በሄሮድስ ዐድሮ የአምላክ ታቦት የኾነችውን ቅድስት እናታችንን እንዳሳደደ፤ ዛሬም እንደ ሜልኮል ልባቸው በትዕቢት በተመላ በልበ መፍ*ቃ**ን ዐድሮ የኢየሱስ ክርስቶስን የባሕርይ አምላክነት የአማናዊት ታቦት የእናቱ የድንግል ማርያምን አማላጅነት በማመን ጸንተው ያሉ ምእመናንን እንደሚቀዋወም ዮሐንስ በራእዩ በምዕ ፲፪፥0፫-፲፯ ላይ ‹‹ዘንዶውም ወደ ምድር እንደተጣለ ባየ ጊዜ ወንድልጅ የወለደችውን ሴት ልጅ አሳደዳት፤ ከእባቡም ፊት ርቃ አንድ ዘመን፣ ዘመናትም፤ የዘመንም እኲሌታ ወደምትመገብበት ወደ ስፍራዋ ወደ በረሓ እንድትበር ለሴቲቱ ኹለት የታላላቅ የንሥር ክንፎች ተሰጣት፤ እባቡም ሴቲቱ በወንዝ እንድትወሰድ ሊያደርግ ወንዝ የሚያኽልን ውሃ ከአፉ በስተኋላዋ አፈሰሰ፤ ምድሪቱም ሴቲቱን ረዳቻት፤ ምድሪቱም አፍዋን ከፍታ ዘንዶው ከአፉ ያፈሰሰውን ወንዝ ዋጠችው፤ ዘንዶውም በሴቲቱ ላይ ተቆጥቶ የእግዚአብሔርን ትእዛዛት የሚጠብቁትን የኢየሱስም ምስክር ያላቸውን ከዘርዋ የቀሩትን ሊዋጋ ኼደ፤ በባሕርምአሸዋ ላይ ቆመ›› በማለት ዲያብሎስ በባሕር አሸዋ በተመሰሉ መ*ና*ፍ*ቃ*ን ልብ ዐድሮ ዘወትር የፈጣሪያችን የክርስቶስን የባሕርይ አምላክነትን፤ የአማናዊት ታቦት የድንግል ማርያምን የአምላክ እናትነት የሚያምኑ ምእመናን ሲቀዋወም እንደሚኖር በራእዩ
አስተምሯል፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

29 Nov, 19:29


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ኅዳር 21- አክሱም ጽዮን የእመቤታችን ጽላት የገባችበት ዓመታዊ ታላቅ በዓል ነው፡፡ በዚህች ዕለት ታቦተ ጽዮን ከነበረችበት ድንኳን ወጥታ ማንም ካህን ሳይሸከማት በተአምራት አብርሃና አጽብሓ ወዳሠሩላት ቤተ መቅደስ ራሷ
በመንፈስ ቅዱስ ገብታ ተገኘች፡፡

+ የታላላቆቹ ቅዱሳን አባቶቻችን የአቡነ ጎርጎርዮስ ገባሬ መንክራትና የአቡነ ቆዝሞስ ዕረፍታቸው ነው፡፡
አቡነ ጎርጎርዮስ ገባሬ መንክራት፡- ‹‹በጎርጎርዮስ›› ስም የሚጠሩ ብዙ እጅግ የከበሩ ታላላቅ ቅዱሳን አሉ፡፡ ከእነዚህም ውስጥ አቡነ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ፣ አቡነ ጎርጎሪዮስ ዘኑሲስ፣ አቡነ ጎርጎርዮስ ገባሬ መንክራት፣ አቡነ ጎርጎርዮስ ራእዩ ህቡአት፣ አቡነ ጎርጎርዮስ ዘላዕላይ ግብፅ፣ አቡነ ጎርጎርዮስ ዘአርማንያ እና ሌሎችም ብዙዎች አሉ፡፡ ከእነዚህ ውስጥ ዛሬ ኅዳር 21 ቀን የዕረፍቱን በዓል የምናከብርለት አቡነ ጎርጎርዮስ ገባሬ መንክራት የተባለውን ነው፡፡ ‹‹ጎርጎርዮስ ገባሬ መንክራት›› የተባለው አስደናቂ ተአምራትን በማድረግ ስለሚታወቅ ነው፡፡ ሀገሩ ሮም ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ጎርጎርዮስ ዘሮም እየተባለም ይጠራል፡፡ ከልጅነቱ ጀምሮ ብሉይንና ሐዲስን ጠንቅቆ የተማረ ሲሆን በሌላም በኩል ሕግ አዋቂና ተርጓሚ ሊቅ ስለነበር አንድ ቀን ለተበደለ ድኃ ሊከራከርለት ሲሄድ በመንገድ ላይ ሳለ መልአክ ጠርቶት ወደ ገዳም ገብቶ መነኮሰ፡፡ ከብዙ ቆይታውም በኋላ አረጋዊው የሀገሪቱ ኤጲስ ቆጶስ በሥራው እንዲራዳው በማሰብ ‹‹እኔን እርዳኝ፣ አንተ ተሾምና ገዳሙን አግልግል›› ቢሉት ሹመቱንና ውዳሴ ከንቱን አልፈልግም በማለት እምቢ አላቸው፡፡
አረጋዊው ኤጲስ ቆጶስም ግድ ቢሉት ሸሽቶና ተደብቆም ገዳም ገብቶ በተጋድሎ መኖር ጀመረ፡፡ ኤጲስ ቆጶሱም ካረፉ በኋላ ማንን እንደሚሾሙ ሲመካከሩ የእግዚአብሔር መልአክ መጥቶ ለመነኮሳቱ ‹‹የመለኮትን ነገር የሚናገር ገዳማዊ ጎርጎርዮስን ፈልጋችሁ ሹሙት›› ብሏቸው ተሰወረ፡፡
እነርሱም ሲፈልጉት አጥተውት ሲጨነቁ መልአኩ ድጋሚ ተገልጦ የክብር ልብሱን ሰጣቸው፡፡ መነኮሳቱም ወንጌልንና ልብሱን ከወንበሩ ላይ አኑረው እየጸለዩ እርሱ በሌለበት ሾሙት፡፡ ስሙንም ‹‹የመለኮትን ነገር በሚናገር በገዳማዊ ጎርጎርዮስ ስም ጎርጎርዮስ›› ብለው ሰየሙት፡፡ ለእርሱም በበዓቱ ውስጥ ሳለ የታዘዘ ብርሃናዊ መልአክ መጥቶ ‹‹ተነሥተህ ወደ እነርሱ ሂድ፣ እነሆ በላያቸው ኤጲስ ቆጶስነት ሾመውሃልና፤ ይህም ከእግዚአብሔር የሆነ ነው›› አለው፡፡ አቡነ ጎርጎርዮስም ተነሥቶ ሲሄድ በሌለበት በልብሱ ብቻ ሹመውት አገኛቸው፡፡ ቅዱስ ጎርጎርዮስም ‹‹ሹመቱን አልፈልግም›› ብሎ ከብቃቱ የተነሣፐበተአምር ከመካከላቸው ተሰውሮባቸው ሄደ፡፡ መልአኩም እየመራ ወስዶ ያለበትን ካሳያቸውና ለእርሱም ሹመቱ ፈቃደ እግዚአብሔር መሆኑን ነግሮት በሹመቱ እንዲጸና አድርጎታል፡፡

ከዚህም በኋላ እጅግ አስገራሚ ተአምራትን እያደረገ ሲያገለግል ኖሯል፡፡ ሁለት ወንድማማቾች በጋራ የሚጠቀሙበትና ብዙ ዓሣዎች የሚጠመድበት አንድ ባሕር ነበር፡፡ እነርሱም በእኔ ይገባኛል ተጣልተው ባለመስማማት አቡነ ጎርጎርዮስ ዘንድ ሄዱ፡፡ አባታችንም ሊያስማማቸው ቢሉ ወንድማማቾቹ እምቢ አሉ፡፡ አቡነ ጎርጎርዮስም ባሕሩን በተአምራት አድርቆ የሚታረስ መሬት አድርጎ ሰጣቸው፡፡ ወንድማማቾቹም ተካፍለው በማረስ
በሰላምና በፍቅር ኖሩ፡፡ እግዚአብሔርም በአቡነ ጎርጎርዮስ እጅ ሌሎች ብዙ እጅግ አስገራሚ ተአምራትን አደረገ፡፡ በዚህም ጻድቁ ‹‹ጎርጎርዮስ ገባሬ መንክራት›› ተብሎ ይጠራል፡፡ በስሙ አንድ ቅዳሴ አለው፣ ቅዳሴውም በዕለተ ሆሳዕና በዓል ይቀደሳል፡፡ ሃይማኖተ አበውና ሌሎቹም የሊቃውንት መጻሕፍት በስፋት የሚጠቅሱት ይህ ጻድቅ አገልግሎቱን ከፈጸመ በኋላ በተወለደበትና በተሾመበት ዕለት ኅዳር 21 ቀን በታላቅ ክብር ዐርፏል፡፡ በረከቱ ይድርብን በጸሎቱ ይማረን፡፡
+ + +

አቡነ ቆዝሞስ፡- ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት 54ኛ የሆኑት እኚህ አባት በእስላሞች ንጉሥ እጅግ የተሠቃዩና የተንገላቱ አባት ናቸው፡፡ እስላሞችም እርሳቸውና ክርስቲያኖችን ሁሉ ልብሳቸውን ሰማያዊ ቀለም እንዲያቀልሙት እንጂ ነጭ ልብስ እንዳይለብሱ በመከልከልና ሌሎችም ብዙ መከራዎችን አጸኑባቸው፡፡ እግዚአብሔርም በአባ ቆዝሞዝ እጅ ብዙ አስገራሚ ተአምራት ያደርግ ነበር፡፡
በአባ ቆዝሞስ ዘመን በእርሳቸውና በክርስቲያኖች ሁሉ ላይ በደረሰው መከራ ምክንያት በአስቄጥስ ገዳም በቅዱስ ሳዊሮስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያለች የእመቤታችን ሥዕል ከጎኗ ብዙ ደም ሲፈስ ታየ፡፡ ዳግመኛም በግብጽ ባሉ በሌሎች ገዳማት የሚገኙ የእመቤታችን ሥዕሎች ከዐይኖቻቸው ዕንባ ሲያፈሱ ታዩ፡፡
ከዚህም በኋላ እግዚአብሔር በጎውን ዘመን አመጣላቸውና አባታችንም ምእመናንን የሚያስተምሩና የሚያጽናኑ ሆኑ፡፡ በቀናች ሃይማኖትን አጸኗቸው፡፡ አቡነ ቆዝሞስ እግዚአብሔር ሲያገለግሉ ኖረው በዚህች ዕለት በሰላም ዐርፈዋል፡፡
በረከታቸው ይድርብን በጸሎታቸው ይማረን፡፡
+ + +

ታቦተ ጽዮን፡- እጅግ የከበሩ ቅዱሳን ነገሥታት አብርሃና አጽብሓ ወደ አክሱም ከተማ ሄደው ሄደው የአድባራት ሁሉ የበላይ የምትሆን የቅድስት ጽዮንን ቤተ ክርስቲያን በወርቅና በዕንቊ ሠሩና አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ቤተ ክርስቲያኗን ባርኮ ቀደሳት፡፡ ታቦተ ጽዮንም ከድንኳን ወጥታ ማንም ካህን ሳይሸከማት አብርሃና አጽብሓ ወዳሠሩላት ቤተ መቅደስ ራሷ በመንፈስ ቅዱስ ገብታ ተገኘች፡፡ አባታችንም በእመቤታችን በዓለ ዕረፍት ቀን ጥር 21 ቀን በውስጧ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲቀድስ ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል በግራ በቀኝ
እየተራዱት እርሱም ከምድር ሦስት ክንድ ከፍ ብሎ ሥርዓተ ቅዳሴውን ፈጽሞ ለነገሥታቱና ለሕዝቡም ሁሉ አቆረባቸው፡፡ የዚያን ዕለትም እጅግ ታላቅ በዓልን አደረጉ፡፡ እኛም ዛሬ ይህን በዓል ነው በድምቀት አክሱም ከተማ ላይ እያከበርን ያለነው፡፡
ሁላችንንም እንኳን አደረሰን!

ከዚህ ቀጥሎ ያለው ሙሉው ጽሑፍ
መጋቤ የሐዲስ ሮዳስ ታደሰ ‹‹ታቦተ ጽዮን›› በሚል ርዕስ የጻፉት ነው።

ፈጣሪያችን ክርስቶስን የወለደችልን ቅድስት ድንግል ማርያም በልዑል እግዚአብሔር ትእዛዝ ጥበብና ማስተዋልን በተቀበለ በባስልኤል እጅ በተሠራችው በቃል ኪዳን ታቦት ትመሰላለች (ዘጸ ፳፭፥፱-፳፤ ፴፯፥፩-፲፭)፡፡ ይኽቺ የቃል ኪዳን ታቦት በደብተራ ኦሪት በቅድስተ ቅዱሳን ውስጥ ተቀምጣ የኖረች፤ የዮርዳኖስን ባሕር የከፈለች (ኢያ ፫፥፲፬-፲፯)፤ ቅጽረ ኢያሪኮን ያፈረሰች (ኢያ ፮፥፩-፳፩)፤ ዳጎን የተባለ የፍልስጤማውያንን ጣዖት ቆራርጣ ያጠፋች (፩ሳሙ ፭፥፩-፭፤ ፪ቆሮ ፮፥፲፮)፤ በድፍረት ሊነካት የሞከረ ኦዛን የቀሠፈች (፪ሳሙ ፮፥፮-፯)፤ በአቢዳራ ቤት ሦስት ወር ተቀምጣ ቤቱን በበረከት የመላች
(፪ሳሙ ፮፥፲፩)፤ ከብዙ ዘመን በኋላ በታላቅ ክብር ወደ ሀገሯ ስትመለስ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት በታላቅ መንፈሳዊ ደስታ በፊቷ የዘመረላት (፪ሳሙ ፮፥፲፬-፳፫፤ ፩ዜና ፲፬፥፳፭-፳፰)፤ ልጁ ንጉሥ ሰሎሞንም ልዩና ውብ የኾነ በወርቅ የተጌጠ ቤተ መቅደስ ሠርቶ በክብር ያኖራት (፩ነገ ፰፥፲፩)፤ የእግዚአብሔር

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

29 Nov, 19:29


የክብሩ መገለጫ የኾነቺው ይቺ የእግዚአብሔር ታቦት፤ በንጽሕና በቅድስና የተጌጠችው የእግዚአብሔር ወልድ እናት የኾነቺው የአማናዊት ታቦት የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ናት፡፡
በመጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ ምዕራፍ ፪ቊጥር ፲፪ትን እንደምናነበው፤ ታቦተ ጽዮንን ያገለግሉ የነበሩት የካህኑ የኤሊ ልጆች አፍኒንና ፊንሐስ በሠሩት ታላቅ ኀጢአት ምክንያት እግዚአብሔር አዝኖባቸው የክብሩ መገለጫ የኾነችው ታቦት በፍልስጤማውያን እጅ እንድትማረክ አደረገ፤ፍልስጤማውያንም የእግዚአብሔርን ታቦት ከአቤንኤዘር ወደ አዛጦን በመውሰድ በድፍረት ከዳጎን አጠገብ አኖሯት፡፡ ነገር ግን ዳጎን በእግዚአብሔር ታቦት ፊት ወድቆ ተገኘ፤ እነሱም እንደገና ዳጎንን ወደ ስፍራው መልሰው ኼዱ፤ በነጋታው ለማየት ሲመጡፐየዳጎን እጅ እግሩ ተቆራርጠው ደረቱ ለብቻው ወድቆ ተገኘ፤ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ይኽነን ታሪክ ይዞ ‹‹የእግዚአብሔር ታቦትንስ በጣዖት ቤት ውስጥ የሚያኖር ማን ነው?›› (፪ቆሮ ፮፥፲፮) በማለት የታቦትን ክብር አስተምሮበታል፡፡

ኢትዮጵያዊዉ ሊቅም በሰቈቃወ ድንግል መጽሐፉ ላይ የአምላክ ማደሪያ የኾነችው ታቦት ወደ ፍልስጤም ሀገር ኼዳ ዳጎንን ሰባብራ እንዳጠፋች ኹሉ፤ አማናዊት የጌታ ታቦት ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታን ይዛ ወደ ግብጽ በተሰደደች ጊዜ የግብጽ ጣዖታት ኹሉ እየተሰባበሩ መውደቃቸውን እንዲኽ በማለት ገልጿል፤ ‹‹ታቦተ አምላከ እስራኤል ጽዮን ዘነገደት ምድረ ኢሎፍሊ ወቀጥቀጠቶ ለዳጎን ነፍሳተ ብዙኃን ማህጎሊ አመ ነገደት ቊስቋመ በኀይለ ወልዳ ከሃሊ ወድቁ አማልክተ ግብጽ መናብርተ ሰይጣን ሐባሊ ወተኀፍሩ ኲሎሙ ዘቦሙ አስጋሊ›› (ወደ ኢሎፍሊ ምድር ተማርካ የኼደች የእስራኤል አምላክ የቃል ኪዳኑ ታቦት ታቦተ ጽዮን፤ የብዙዎችን ነፍሳት ያጠፋ ዳጎንን ሰባበረችው፤ በዚች ታቦት የተመሰለች ድንግል ማርያምም ኹሉን ማድረግ ከሚችል ከልጇ ጋር ግብጽ ወደሚባል አገር በኼደች ጊዜ፤የሐሰተኛ ሰይጣን ዘፋኖች የኾኑ የግብጽ ጣዖታት ፈረሱ፤ጠንቋይ አስጠንቋይ ያላቸው ኹሉ ዐፈሩ) በማለት አነጻጽሯል፡፡

በእግዚአብሔር ታቦት ላይ ስለሠሩት ታላቅ የድፍረት ኀጢአት እግዚአብሔር ቀጣቸው ብዙዎቹ ሞቱ፤ ያልሞቱትም በእባጭ ተመቱ፤ የአይጥ መንጋም ምድራቸውን አጠፋባቸው፤ ያን ጊዜ በእግዚአብሔር ታቦት ላይ ምን እናድርግ? ወደ ስፍራው በምን እንስደደው? ብለው በመማከር፤ የሚያጠቡ ቀንበር ያልተጫነባቸው ኹለት ላሞችን በመውሰድ፤ በዐዲስ ሠረገላ ጠምደው እንቦሶቻቸውን (ጥጆቻቸውን) ከቤት ዘግተው
በማስቀረት፤ ታቦተ ጽዮንን እጅ መንሻውን በሠረገላው ላይ ጫኑ፤ ያን ጊዜ እነዚኽ ላሞች ጥጆቻቸውን ሳይናፍቁ ወደቀኝ ወደግራ ሳይሉ እምቧ እያሉ ወደ ቤተ ሳሚስ ወደሚወስደው መንገድ ታቦተ ጽዮንን ይዘው ገሠገሡ፤ ሠረገላውም ወደ ቤትሳሚሳዊው ወደ ኢያሱ እርሻ ሲደርስ ያን ጊዜ ሌዋውያን
ታቦት ጽዮንና ዐብሮ የነበረውን የወርቅ ዕቃ አውርደው በታላቅ ደንጊያ ላይ በማኖር፤ ሠረገላውን ፈልጠው ጊደሮቹን ሠውተዋቸዋል፡፡ ይኽም ለጊዜው ቢደረግም ለኋላው ግን ምሳሌ ነበር፤ ላሞቹ የሰማዕታት፤ ልጆች የልጆቻቸው፤ ሠረገላ የመስቀል፤ ልጆቻቸውን ከወደኋላ እንዳስቀሩ፤ ሰማዕታትም የልጅ የገንዘብ ፍቅር አያስቀራቸውምና፣ ሠረገላውን ፈልጠው እንደሠዋቸው ራሳቸውን በመስቀል ይሠዋሉና በማለት የብሉይ ኪዳን መተርጒማን ያመሰጥሩታል፡፡
የመልክአ ማርያም ደራሲ የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ የኾነችውን የኻያ መንፈቅ ማለት ዐሥሩ ቃላት የተጻፉባቸው ጽላት የተቀመጡባትን የእግዚአብሔርን ታቦት ጊደሮቹ ከልጆቻቸው ይልቅ በማስበለጥና በመውደድ ይዘዋት ወደፊት እንደነጎዱ፤ እሱም የልዑል ማደሪያ ለኾነችው ለቅድስት ድንግል ማርያም ያለውን ጥልቅ ፍቅር በድርሰቱ ላይ ‹‹ማርያም ጽዮን ታቦት ቃለ ጽድቅ መንፈቀ ዕሥራ ዕጐላት እምዕጐሊሆን ከመ ኪያኪ አፍቀራ አፍቀርኩኪ አፍቅርኒ እምይእዜ ለግሙራ›› (የኻያ እኩሌታ የሚኾን የእውነት ቃል ማደሪያ ጽዮን ማርያም ሆይ፤ ጊደሮች ከጥጆቻቸው ይልቅ አንቺን እንደአፈቀሩ፤
ወድጄሻለኹና ከዛሬ ዠምሮ ፈጽሞ ውደጅኝ) በማለት ገልጦታል፡፡

ሊቁ አባ ጊዮርጊስም በምስጢር በመራቀቅ ‹‹አንቲ ውእቱ ጽዮን ታቦተ አምላከ እስራኤል እንተ ነገደት ምድረ ኢሎፍሊ፤ ወበህየ አውደቀቶ ለዳጎን፤ ወቀሠፈቶሙ ለመጠዓውያን፤ ወበፀአታ ተወፈየት ሞጻ እምሰብአ አዛጦን፤ ወፈነውዋ ምስለ ሞጻሃ ዲበ ዕጎልተ አልሕምት አስተጽዒኖሙ፤ ምስሌሃ አፍቃደ ኤርጋብ ወኢሠርዑ ሥርዓተ ቤርሴክታን በገቦሃ ወባሕቱ ፈነውዋ ዘምስለ ቴሜርጋብ ወንዋየ ወርቅ በኀቤሃ ወበእትወታ ባረከ እግዚአብሔር ቤተ አቢዳራ አመ ንግደታ ሶበ አኅደራ›› (ወደ ኢሎፍሊ ምድር የኼደች የእስራኤል አምላክ ታቦት (ማደሪያ) ጽዮን አንቺ ነሽ፤ በዚያም ዳጎንን የጣለችው ጣዖት አምላኪዎቹንም የቀሠፈቻቸው በአመጣጧም ከአዛጦን ሰዎች ካሳን የተቀበለች፤ ከካሳዋም ጋር እንቦሳ ባላቸው ላሞች አስጭነው የሸኟት፤ ከርሷም ጋር የወርቅ ሳጥኖችን በጐኗም፤ የበድን ሣጥን ሥርዐትን አልሠሩም፤ ነገር ግን በርሷ ዘንድ ካለ ከወርቅ መሣሪያና ከሣጥን ጋራ ላኳት፤ በእንግድነቷ ወቅትም በአሳደራት ጊዜ ወደ ቤቱ በመግባቷ እግዚአብሔር የአቢዳራንፐቤት ባረከ) በማለት የምሳሌዋን እሙንነት በሰፊው ገልጧል፡፡
ይኽቺም የእግዚአብሔር ታቦት በቤተ ዐሚናዳብ ኻያ ዓመት ተቀምጣለች፤ ከዚያም የሳኦል ዘመን ዐልፎ የእግዚአብሔር ወዳጅ ዳዊት በነገሠ ጊዜ በዐዲስ ሠረገላ አድርገው ከቤተ ዐሚናዳብ አውጥተው በበገና፣ በመሰንቆ፣ በከበሮ፣ በነጋሪት፣በጸናጽል እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ይዘዋት ሲመጡ፤ የእግዚአብሔርን ታቦት ኦዛ በድፍረት በመያዙ እግዚአብሔር ቀሥፎት ወዲያውኑ በታቦቷ አጠገብ ሕይወቱ አልፏል፤ ያን ጊዜ ነቢዩ ዳዊት የእግዚአብሔር ታቦት ያደረገችውን ተአምራት ተመልክቶ፤ እግዚአብሔር በእርሷ እንዳደረ በማመን በፍርሃት ተውጦ ‹‹የእግዚአብሔር ታቦት ወደ እኔ እንዴት ይመጣል?›› በማለት ለታቦቷ ያለውን ታላቅ ክብር ገልጧል (፪ ሳሙ ፮፥፮-፲)፤ በዘመነ ሐዲስም በተመሳሳይ መልኩ ጌታን በማሕፀኗ የተሸከመች የልዑል እግዚአብሔር ማደሪያ አማናዊት ታቦት ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ኤልሳቤጥ ቤት በኼደች ጊዜ፤ ኤልሳቤጥ ልክ እንደ ዳዊት መንፈስ ቅዱስ መልቶባት፤ የጌታ ታቦት (ማደሪያው) መኾኗን ተረድታ፤ድምፁዋን አሰምታ ‹‹የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጪ ዘንድ እንዴት ይኾንልኛል?›› በማለት ለቅድስት ድንግል ማርያም ያላትን ታላቅ አክብሮት እንደ ዳዊት ገልጣለች(ሉቃ ፩፥፵፫-፵፮) ፡፡

ከዚያም ዳዊት ይኽነን ታላቅ ቃል ከተናገረ በኋላ የእግዚአብሔር ታቦት በአቢዳራ ቤት ለሦስት ወር ያኽል እንደተቀመጠች (፪ሳሙ ፮፥፲)፤ በተመሳሳይ መልኩ የአምላክ ማደሪያ ቅድስት ድንግል ማርያምም በካህኑ በዘካርያስ ቤት ለሦስት ወር ተቀምጣለች (ሉቃ ፩፥፶፮)፡፡ ኦዛ ተቀሥፎ ከሞተ በኋላ የእግዚአብሔር ታቦት ወደ አቢዳራ ቤት ገብታ ቤቱ ለሦስት ወር በበረከት እንደተመላ ኹሉ፤ በተመሳሳይ መልኩ ዘካርያስም የመልአኩን ቃል ባለመቀበሉ ከተረገመ በኋላ (ሉቃ ፩፥፳)፤እውነተኛዪቱ የአምላክ ታቦት ድንግል ማርያም ቤቱ ለሦስት ወር ተቀምጣለች፡፡ እግዚአብሔር በታቦቷ ምክንያት የአቢዳራን ቤት እንደባረከ ኹሉ የዘካርያስንም ቤት በእመቤታችን ምክንያት የባረከው መኾኑን ሊቁ ቅዱስ ያዕቆብ ዘስሩግ በመጽሐፉ ሲገልጽ ‹‹ድንግል በምስጢር የተመላ ታቦትን ኾና ትኖራለች፣ የካህናት ወገኖችም ደስ ይላቸዋል፣ ያከብሯታልም›› በማለት

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

29 Nov, 19:29


ከሊቃውንትም አባ ጽጌ ድንግልና አባ ገብረ ማርያም በማሕሌተ ጽጌ መጽሐፋቸው ላይ ‹‹እስከ መነነቶ ሜልኮል ቅድመ ታቦት ሕግ ከመ ዘፈነ ንጉሠ እስራኤል ኪያኪ ዘጸገየ ሥነ ቅድመ ገጸ ሥዕልኪ ድንግል እዘፍን አነ ዘይሜንን ተአምረኪ ወስብሐተኪ ቊርባነ በአፈ መላእክት ወሰብእ ለይኩን ምኑነ ›› (አንቺን ያስገኘ የእስራኤል ንጉሥ ዳዊት ሜልኮል እስከናቀችው ድረስ በእግዚአብሔር የሕግ ታቦት ፊት እንዳመሰገነ፤ ድንግል ሆይ እኔም በሥዕልሽ ፊት እዘምራለኍ፤ ድንቅ ታምርሽንና የቀረበ መንፈሳዊ ምስጋናሽን የሚንቅ በመላእክትና በሰው አንደበት የተረገመ ይኹን) በማለት ሲያስተምሩ በተጨማሪም ሊቁ ቅዱስ ያዕቆብ ዘስሩግ በምስጢር በመራቀቅ ቅድስት ድንግል ማርያምን በምስጢር የተመላች ታቦት፣ የቃል ኪዳን ታቦት፣ እሳትን የተመላች ታቦት፣ የቅዱስ ቃል ታቦት በማለት እያብራራ ያስተማረው የነገረ መለኮት ትምህርት እጅግ ጥልቅ ነው፡፡ ይኽ ሊቅ ድንግልን በምስጢር የተመላች ታቦት ሊል የቻለበት ምክንያት በታቦቷ በምሳሌነት ቀድሞ የተገለጠው ምስጢር በእውነት የታወቀባት ስለኾነ ነው፤ ዳግመኛም በምስጢር የተመላች ማለቱ እናትነትን ከድንግልና፤ ድንግልናን ከእናትነት አስተባብራ የተገኘች፤ ዘርዐ ወራዙት ያልወደቀባት፤ እደ ብእሲ ያልዳሰሳት፤ በግብረ መንፈስ ቅዱስ ሰማይና ምድር የማይወስኑትን ጌታ በተፈትሖ በማይመረመር ማሕፀኗ የቻለች ልዩ ምስጢርን የተረዳችና በምስጢር የተከበበች የምስጢር ታቦት በመኾኗም ጭምር ነው፤ ሊቁ ያዕቆብ ይኽነን ሲገልጥ ‹‹The virgin abides like an ark full of mysteries…›› (ድንግል በምስጢር የተመላ ታቦትን ኾና ትኖራለች፤ የካህናት ወገኖችም ደስ ይላቸዋል ያከብሯታልም) በማለት ምስጢራዊ ታቦትነቷን አጒልቶ አስተምሯል፡፡
ዳግመኛም ይኸው ሊቅ እሳተ መለኮት ጌታን ፱ወር ከ፭ቀን በማሕፀኗ የተሸከመች በመኾኗ እሳትን የተመላች ታቦት በማለት ገልጿታል፤ ይኸውም ኪሩቤልና ሱራፌል እሱን ከመፍራት የተነሣ፤ በኹለት ክንፋቸው ፊታቸውን ሸፍነው በኹለት ክንፋቸው እግራቸውን ሸፍነው ከፊቱ የሚቆሙለት፤ እሳተ መለኮት ጌታን ፱ወር ከ፭ቀን በማሕፀኗ የተሸከመች የአማናዊት ታቦት የቅድስት ድንግል ማርያም ነገር የቤተ ክርስቲያናችን ሊቃውንትን አስደንቋልና ነው፤ሊቁ አባ ሕርያቆስም በቅዳሴው ‹‹ድንግል ሆይ እሳተ መለኮት በኾድሽ ባደረ ጊዜ ፊቱ እሳት፣ ልብሱ እሳት፣ ቀሚሱ እሳት ነው እንደምን አላቃጠለሽ? ሰባት የእሳት ነበልባል
መጋረጃ በኾድሽ ውስጥ ወዴት ተዘጋጀ? ወዴትስ ተጋረደ? ከጐንሽ በቀኝ ነውን? ወይስ ከጐንሽ በግራ ነውን? ትንሽ አካል ስትኾኚ፤ የሚያንጸበርቅ ነደ እሳት የሚከበው ኪሩቤል የተሸከሙት ዙፋን በኾድሽ ውስጥ በወዴት ተዘጋጀ? ወዴትስ
ተተከለ? ታናሽ ሙሽራ ስትኾኚ›› በማለት እሳተ መለኮት ጌታን የተሸከመች የቅድስት ድንግልን ነገር አድንቋል)፡፡
ሊቁ ቅዱስ ያዕቆብ ዘስሩግም በድርሰቱ ይኽነን ሲገልጽ ‹‹They looked on her…›› (የእግዚአብሔር መኖሪያ ብለውም ይመለከቷታል፤ በእነርሱም ዘንድ እሳትን የተመላች ታቦት አድርገው ያከብሯታል) በማለት አስተምሯል::
በሦስተኛ ደረጃ ሊቁ በምስጢር በመራቀቅ የቅዱስ ቃል ታቦትሲል ያመስገነበት ምክንያት በብሉይ ኪዳን በአጽባዕተ እግዚአብሔር የተጻፉ ዐሥሩ ቃላት ያሉባቸው ጽላት በታቦቷ ላይ ይቀመጡ ነበር (ዕብ ፱፥፫-፭)፤ በዘመነ ሐዲስም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አካላዊ ቃልን በማሕፀኗ የተሸከመች ማኅደረ ቃለ አብ በመኾኗ ይኽነን ስያሜ ሰጥቷታል፡፡
የጌታ ወዳጅ የኾነው ቅዱስ ዮሐንስም በወንጌሉ ላይ የክርስቶስን የምስጢረ ተዋሕዶውን ነገር ሲገልጥ ‹‹ቃል ሥጋኾነ በእኛም ዐደረ›› (ዮሐ ፩፥፲፬)ብሎ እንደመሰከረ፤ አካላዊ ቃል ከሥጋዋ ሥጋን፤ ከነፍሷ ነፍስን ነሥቶ ሰው በመኾኑ የእግዚአብሔር ቃል በላይዋ ከተቀመጠባት ከታቦቷ ይልቅ የአካላዊ ቃል የጌታ እናቱ የኾነች የአማናዊት ታቦት የድንግል ማርያም ክብር እጅጉን መላቁን ሲገልጥ ‹‹she was carried as an ark full of scripture…›› (የቅዱስ ቃል ታቦት (ማደሪያ) ኾነች፤ የምስጢራትን ትርጉም ነቢያት የተናገሩለት በርሷ ዐድሯልና፤ በዚኽም ከጠረጴዛው ታቦት ይልቅ ክብሯ የላቀ ኾነ፤ በሚያስደንቅ ክብር አክብሯታልና) በማለት የአማናዊት ታቦት የቅድስት ድንግልን ክብር አድንቋል፡፡

የብርሃን እናቱ ድንግል ወላዲተ አምላክ ክብርት እመቤታችን ጽዮን ማርያም ከበዓሏ ረድኤት በረከት ትክፈለን!
የዓሥራትን ሀገሯን ቅድስት ኢትዮጵያን ትጠብቅልን፣ ትንሣኤዋን ታሳየን!

ከገድላት አንደበት

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

28 Nov, 18:54


ቅዱስ አንያኖስም ብዙዎችን አስተምሮ አጠመቃቸው፡፡ በቀናች ሃይማኖትም አጸናቸው፡፡ በግብፅ የመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን የሆነችው መኖሪያ ቤቱም ከእስክንርያ ከተማ ውጭ ትገኛለች፡፡ ዛሬ የታላቁ ሰማዕት የቅዱስ ሰርጊስ ቤተ ክርስቲያን ሆናለች፡፡

ቅዱስ ማርቆስም ወደ ሌሎች ሀገሮች ሄዶ ወንጌልን ሰብኮ ከ2 ዓመትም በኋላ ወደ እስክንድርያ ቢመለስ በቅዱስ አንያኖስ ትምህርት ክርስቲያኖችን ጸንተው ቤተ ክርስቲያን ሠርተው አገኛቸው፡፡ ወንጌላዊውም የትንሳኤን በዓል ለማክበር ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ገብቶ እየቀደሰ እያለ ጣዖት አምላኪዎች ሰብረው ገብተው ይዘውት አንገቱን አሥረው ቀኑን ሙሉ ከተማውን እየጎተቱት ሲያዞሩት ውለው በ68 ዓ.ም ሚያዝያ 30 ቀን ሰማዕትነቱን በዚያው ሲፈጽም በእርሱ ወንበር ቅዱስ አንያኖስ ተተክቶ ምእመናንን የሚጠብቅ ሆነ፡፡ ቅዱስ አንያኖስ እግዚአብሔርን እያገለገለ በወንጌላዊው በቅዱስ ማርቆስ ወንበር 12 ዓመት ከኖረ በኋላ በዚህች ዕለት በሰላም ዐረፈ፡፡ በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

28 Nov, 18:54


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ኅዳር 20-የሠራዊት አለቃ የነበረው ሰማዕቱ ቅዱስ ቴዎድሮስ ቤተ ክርስቲያኑ የከበረችበት ዕለት ነው፡፡
+ ከወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ ቀጥለው 2ኛ ሆነው በእስክንድርያ የተሾሙት አባ አንያኖስ ዕረፍታቸው ነው፡፡
ቅዱስ ቴዎድሮስ ሊቀ ሠራዊት፡-የሠራዊት አለቃ የተሰኘውና በዲዮቅልጥያኖስ ዘመን በሰማዕትነት ያረፈው ቴዎድሮስ ዋነኛው ነው፡፡ አባቱ ዮሐንስ ግብፃዊ ሲሆን ወደ አንጾኪያ ከሠራዊት ጋር ሄዶ የአንዱን ልጅ አገባ፡፡ እርሷም ጣዖት አምላኪ ነበረች፡፡ ይህ ቅዱስ ቴዎድሮስ ከተወለደም በኋላ ወደ ጣዖቷ አቅርባ አምኮቷን ልታስተምረው በፈለገች ጊዜ አባቱ ክርስትናን አስተማረው፡፡ በዚህም ጊዜ ባሏን አባረረችውና ልጇን አስቀረች፡፡

ቅዱስ ቴዎድሮስም ባደገ ጊዜ ወደ እውነተኛው መንገድ ይመራው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ዘወትር ይጸልይ ነበር፡፡
የክርስትና ጥምቀትንም ሲጠመቅ እናቱ አዘነች፡፡ ሲጎለምስም ንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስ የሠራዊቱ አለቃ አድርጎ ሾመው፡፡ ከምሥራቃዊው ቴዎድሮስ ጋር ሆነውም የፋርስን ሰዎች ወግተው ድል አደረጓቸው፡፡ የፋርስና የበርበር ሰዎችም በሮማውያን ላይ ተነሡባቸውና ብዙ ከተሞችን አጠፉ፡፡ ንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስም በዚህ ጊዜ ፈራ፡፡ ቅዱስ ቴዎድሮስንም ጠርቶ ‹‹ምን እናድርግ የጦር መሳሪያውንና ሠራዊቱን ሁሉ ይዘህ ውጣ›› ብሎ አዘዘው፡፡ ቴዎድሮስም ‹‹የአንተን ሠራዊትና የጦር መሣርያ ይዤ አልገጥማቸውም፣ በጌታዬ በክርስቶስ ስም አሸንፋቸዋለሁ፣ ያለ አንድ የራሴ ጦርና ፈረስ በቀር አልፈልግም›› አለው፡፡ ንጉሡም ጨንቆት ነበርና ‹‹በል የወደድከውን አድርግ›› አለው፡፡
በማግሥቱም ቴዎድሮስ ወደ ጦርነቱ ሲወጣ ንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስን ‹‹ሠራዊቱን ይዘህ እዚሁ ቆመህ ጠብቅ እኔ በጌታዬ ኃይል የምሠራውን ታያለህ›› ብሎት ሄደና ከጸለየ በኋላ ጦርነቱን ብቻውን ጀመረ፡፡ ንጉሡም ከሠራዊቱ ጋር ከሩቅ ሆኖ ያየው ነበር፡፡ ቴዎድሮስ የበርበርን ሰዎች ፈረሰኛም ሆነ እግረኛ ምንም ሳያስቀር በእግዚአብሔር ኃይል አጠፋቸው፡፡
የመኳንንቶቻቸውንም ቸብቸቦ ቆርጦ ለንጉሡ አቀረበለት፡፡ የአንጾኪያ ሰዎችም ወጥተው የበርበርን አገር ማረኩ፡፡
አውኪስጦስ በሚባል አገር የሚኖሩ ሰዎች ያመልኩት የነበረ ታላቅ ዘንዶ ነበርና ለእርሱ በየዕለቱ ሁለት ሁለት ሴቶች ልጆችን እንዲበላቸው ይሰጡት ነበር፡፡፡ ሁለት ልጆችም የነበሯት አንዲት ክርስቲያን ነበረችና ልጆቿን ወስደው ለዘንዶው አቀረቧቸው፡፡

ቅዱስ ቴዎድሮስም ወደዚያች አገር በደረሰ ጊዜ እናታቸው አልቅሳ ነገረችው፡፡ ከፈረሱም ወርዶ ወደ ምሥራቅ ዞሮ ከጸለየ በኋላ ሕዝቡም ሁሉ እየተመለከቱት ወደ ዘንዶው ቀርቦ በጦሩ ወግቶ ገደለውና ልጆቹን አዳናቸው፡፡ እርዝመቱም 24 ክንድ ሆነ፡፡

ከዚህ በኋላ ወደ ግብፅ ሄዶ አባቱን አገኘውና ተመልሶ ወደ አንጾኪያ ሲመጣ ንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስ በክርስቶስ ማመኑን ክዶ ይልቁንም ክርስቲያኖችን ሲያሰቃይ አገኘው፡፡ ከዚህም አስቀድሞ የአውኪስጦስ ሰዎች ዘንዶውን ስለገደለው ከሰውት በንጉሡ ፊት አቆሙት፡፡ ንጉሡንም ስለ ባዕድ አምልኮው እጅግ አድርጎ ዘለፈው፡፡ ንጉሡም በንዴት ጽኑ ሥቃይን አሠቃየው፡፡
እጆቹንና እግሮቹን ከግንድ ጋር ቸነከሩት፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም ተገልጦለት ከቁስሉ ፈውሶት ሰማዕትነቱን በትዕግስት እንዲፈጽም በመንገር አረጋጋው፡፡ ሕዝቡም ተሰብስቦ ንጉሡን ሰደቡት፡፡‹‹ከጠላቶቻችንና ከጠላቶችህ እጅ ያዳነንን ቴዎድሮስን ታሠቃያለህን? አንተ ከሀዲ ርጉም ነህ..›› እያሉም ረገሙት፡፡ ‹‹በቴዎድሮስም አምላክ አምነናል›› ባሉት ሁሉንም ሰየፋቸው፡፡
የብረት አልጋም አምጥቶ ቅዱስ ቴዎድሮስን በላዩ አስተኝቶ ከሥር እሳት አነደደበት፡፡ ጌታችንም ፈወሰውና በሚቀጥለው ቀን ሄዶ በንጉሡ ፊት ቆመና ስለአምላኩ ክብር ሲመሰክር የጦር ሠራዊቱም ሁሉ በእግዚአብሔር አመኑ፡፡ ንጉሡም ብዙ ካሠቃየው በኋላ በመጨረሻ ሐምሌ 20 ቀን አንገቱን በሰይፍ ቆረጠውና የሰማዕትነቱ ፍጻሜ ሆነ፡፡ ከአንገቱ ደም ውኃና ወተት ፈሰሰ፡፡ ሥጋውንም በእሳት አቃጥላለሁ ቢል እሳቱ ከቶ ሥጋውን አላቃጥል ብሎ እምቢ ብሎታል፡፡

በአገራችን በስሙ የተሠሩ አብያተክርስቲያናት አሉ፡፡ ቢሾፍቱ መስመር የረር በዓታ ጽላቱ ይገኛል፡፡ በየዓመቱ ግንቦት 21 ቀን ግብፅ በደብረ ምጥማቅ እመቤታችን ለሕዝበ ክርስቲያኑም ለአሕዛቡም ተገልጻ ስትታያቸው ሕዝቡም የተለያየ ጥያቄ ይጠይቃት ነበር፡፡ ግማሹ ‹‹አባታችን አዳምን አሳይን›› ሲሏት አዳምን ከገነት አምጥታ ታሳያቸዋለች፡፡ አዳምን ወይም ሄዋንን ካሏትም አምጥታ ታሳቸው ነበር፡፡ ዳዊትን ሲሏት ከነበገናው አምጥታ ታሳያቸዋለች፡፡ የጠየቋትን ነቢያት፣ ጻድቃንና ሰማዕታትን ሁሉ ከገነት እየጠራች እንዳሳየቻቸው ተአምረ ማርያም ላይ ተጽፏል፡፡ እመቤታችን ‹‹ሰማዕታትን አሳይን›› ባሏት ጊዜ ታላላቆቹን ሰማዕታት ማለትም ቅዱስ ጊዮርጊስን፣ ቅዱስ መርቆርዮስንና ይህንን ቅዱስ ቴዎድሮስ ሊቀ ሠራዊትን ነው ከገነት አምጥታ ያሳየቻቸው፡፡ ስለዚህም ቴዎድሮስ ሊቀ ሠራዊት በ3ኛ ደረጃ ያለ ታላቅ ሰማዕት እንደሆነ አባቶቻችን ይናገራሉ፡፡ ዛሬ ኅዳር 20 ቅዳሴ ቤቱ የከበረችበት ዓመታዊጰበዓሉ ነው፡፡
በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን፡፡
+ + +
አቡነ አንያኖስ፡- የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ አረማውያውን ናቸው፡፡ እርሱም ጫማ ሰፊ ነበረ፡፡ ወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ በጌታችን ትእዛዝ በ60 ዓ.ም ወደ ሰሜን አፍሪካ መጥቶ እስክንድርያ ደረሰ፡፡ በሀገሪቱም አምልኮተ ጣኦት በስፋት ተንሰራፍቶ ስለነበር ቅዱስ ማርቆስ ወንጌልን እንዴት አድርጎ መስበክ እንዳለበት እያሰበ በከተማዋ ሲዘዋወር እግሩ ተደናቅፎ ጫማው ተቆረጠበትና ለዚህ አንያኖስ ለተባለው ጫማ ሰፊ ሰጠው፡፡ ጫማ ሰፊው አንያኖስም ሲሰፋ መስፊያው እጁን ስለወጋው ‹‹ኤስታኦስ›› ብሎ በዮናናውያን ቋንቋ ጮኸ፡፡ ትርጉሙም ‹‹አንድ አምላክ›› ማለት ነው፡፡ ያን ጊዜም ቅዱስ ማርቆስ የእግዚአብሔር ስም ሲጠራ ሰምቶ ደስ አለውና አንያኖስን ‹‹ለመሆኑ አሁን የጠራሃውን አምላክ ታውቀዋለህን?›› ብሎ ጠየቀው፡፡ ጫማ ሰፊውአንያኖስም ‹‹ሲሉ እሰማለሁ እንጂ አላውቀውም›› አለው፡፡
ከዚህም በኋላ ቅዱስ ማርቆስ አፈር አንስቶ በምራቁ ጭቃ አድርጎ የአንያኖስን የቆሰለች እጁን ቀባውና ወዲያው በተአምራት ፈወሰው፡፡ አንያኖስ ይህን ተአምር ባየጊዜ እጅግ ተደሰተ፡፡ ቅዱስ ማርቆስም ወንጌልን ሰበከለት፡፡ አንያኖስም ወንጌላዊውን ወደ ቤቱ ወሰደውና ለቤተሰቡም ጭምር
ወንጌልን ይሰብክ ዘንድ ጋበዘው፡፡ ቅዱስ ማርቆስም ለአንያኖስ ቤተሰቦች ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ እስከ ዳግም ምጽዓት ድረስ ያለውን የሃይማኖትን ትምህርት አስተማራቸው፡፡ ይልቁንም ደግሞ የጌታችንን መከራና ፍጽምት የሆነች ወንጌልን ሰበከላቸው፡፡ አንያኖስና ቤተሰቡም አምነው ተጠመቁ፡፡የመንፈስ ቅዱስም ጸጋ በላያቸው ወረደ፡፡ በዚያውም በግብፅ የመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን በአንያኖስ ቤት ተመሠረተች።
ከዚህም በኋላ ቅዱስ አንያኖስ ሁልጊዜ ከቅዱስ ማርቆስ እግር ሥር ቁጭ ብሎ መማር ጀመረ፡፡ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንንም ሁሉ ተምሮ ጨረሰ፡፡ ቅዱስ ማርቆስም በግብጽ ተዘዋውሮ ካስተማረ በኋላ ወደ ሰሜን አፍሪካና ወደ ሌሎች አምስት ሀገሮች ሄዶ ወንጌልን ለማስተማር በተነሣ ጊዜ እጆቹን በአንያኖስ ላይ ጭኖ በግብጽ አገር ለወገኖቹ ወንጌልን ይሰብክ ዘንድ ሊቀ ጵጵስና ሾመው፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

27 Nov, 18:11


እስከመጨረሻው እንዲጸና እና ሰማዕተነቱን እንዲፈጽም ታበረታው ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ መነኮንኑ ቅዱስ ቴዎፍሎስን ለተራበ አንበሳ ሰጠው ነገር ግን አንበሳው ሄዶ ሰግዶ እግሮቹን ሳመው፡፡ ጌታችንን እነ አባ በብኑዳን፣ እነ አባ ኤጲፋንዮስን፣ መቃነ መቃብራቸውን የአንበሳ ሆድ እንዳደረገላቸው ሁሉ የዚህንም ቅዱስና የቤተሰቡን መቃብራቸውን የአንበሳ ሆድ አደረገላቸው፡፡ አንበሳውም ለቅዱስ ቴዎፍሎስ ከሰገደለትና እግሮቹን ከሳመ በኋላ ሥጋውን አቆሰለውና ነፍሱም በዚያው አለፈች፡፡ ሚስቱ ቅድስት ጰጥሪቃም ሥጋውን አንሥታ ከሣጥን በጨመረች ጊዜ መኮንኑ እርሷንም ለአንበሳው አሳልፎ ሰጣትና ነፍሷን ለእግዚብሔር ሰጠች፡፡ የ5 ወር ዕድሜ ብቻ ያለው ልጃቸው ቅዱስ ደማሊስም አንበሳውን ባየጊዜ ሳቀና አንደበቱን
ፈቶ ‹‹አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አምናለሁ›› ብሎ ተናገረ፡፡ ይህንንም ብሎ በአንበሳው አፍ ከእናቱ ጋር ተበላ፡፡ የቅዱስ ቴዎፍሎስና የቅድስት ጰጥሪቃ የልጃቸውም የቅዱስ ደማሊስ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

27 Nov, 18:11


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ኅዳር 19-ሐዋርያው ቅዱስ በርተሎሜዎስ ዓመታዊ መታሰቢያ በዓሉ ነው፡፡ እልዋህ በምትባልም አገር ድንቅ ተአምር ያደረገበት ዕለት ነው፡፡
+ እንጂፋቱ የአቡነ ዮሴፍ ልደታቸው ነው፡፡
+ ከ5 ወር ሕፃን ልጁና ከሚስቱ ጋር ሰማዕት የሆነው የቅዱስ ቴዎፍሎስ ዕረፍቱ ነው፡፡
+ ሩጻፋ በሚባል አገር የሰማዕቱ የቅዱስ ሰርጊስ ቤተ ክርስቲያኑ የከበረችበት ዓመታዊ መታሰቢያ በዓሉ ነው፡፡

የሰማዕቱ የቅዱስ ሰርጊስ ቤተ ክርስቲያኑ እንደከበረች፡- ይህም ቅዱስ ሰርጊስ በሩጻፋ አገር በሰማዕትነት ባረፈ ጊዜ ምእመናን ቅዱስ ሥጋውን ወስደው በክብር ገንዘው በእነርሱ ዘንድ አኖሩት፡፡ በፊቱም መብራቶችን አኖሩ፡፡ የመከራውም ዘመን እስኪያልፍ ድረስ በእነርሱ ዘንድ ተሰውሮ ኖረ፡፡ የመከራውም ዘመን ካለፈ በኋላ ያማረች ቤተ ክርስቲያንን
አነጹለት፡፡ 15 ኤጲስቆጶሳትንም ሰብስበው አከበሯትና የቅዱስ ሰርጊስን ሥጋ በውስጧ አኖሩ፡፡ ከሥጋውም ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራት ተገለጡ፡፡ ሕመምተኞችን የሚፈውሳቸው ሽታው እጅግ ጣፋጭ የሆነ የሽቱ ቅባት ከቅዱስ ሥጋው የሚፈስ ሆነ፡፡
የቅዱስ ሰርጊስን ዜና ሕይወቱን በዕረፍቱ ዕለት ጥቅምት 10 ቀን በዝርዝር ስላየነው ገድሉን ከዚያ ላይ መመልከት ይቻላል፡፡
በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን፡፡
+ + +

ሐዋርያው ቅዱስ በርተሎሜዎስ እልዋህ በምትባልም አገር ያደረገው ድንቅ ተአምር፡- ሐዋርያው በርተሎሜዎስ ወንጌልን ይሰብክ ዘንድ ዕጣ የደረሰው እልዋሕ በሚባል አገር ነው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ሊያደርሰው አብረው ወደ አልዋሕ ሄዱ፡፡ ወደ ከተማው ለመግባት ምክንያት ፈለጉና ቅዱስ ጴጥሮስ ቅዱስ
በርተሎሜዎስን ‹‹አትክልተኛ ባለሙያ ነው›› ብሎ የወይኑን ቦታ እንዲጠብቅለት ለአንድ ባለጸጋ መኰንን ባሪያ አድርጎ ሸጠው። ባለጸጋውም በርተሎሜዎስን በ30 እስቴታር ገዝቶት ሄደ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ገንዘቡን ደብቆ ለቅዱስ በርተሎሜዎስ በድብቅ ሰጥቶት እንዲመጸውተው ነግሮት ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ፡፡

አልዋሕ ከገባ በኋላ ቅዱስ በርተሎሜዎስ የወይን ቦታው አለቃ ሆኖ 40 ቀን ተቀመጠ፡፡ ወንጌሉን ባለመስበኩ በሀዘን እያለቀሰ ጌታችንን በጸሎት ጠየቀው፡፡ በገንዘቡ ገዝቶት ባሪያው ያደረገው ባለጸጋውም የወይኑን ቦታ ያይ ዘንድ እንደመጣ መርዘኛ እባብ ነድፎት ሞተ፡፡ ሕዝቡም ተሰብስቦ ሲያለቅስ በርተሎሜዎስ ግን ወደ ጌታችን ከጸለየ በኋላ ሄዶ ባለጸጋውን ሰው ከሞት አስነሣው፡፡ በዚህም ሕዝቡ ሁሉ አምነው ተጠምቀዋል፡፡ ይህም ታላቅ ተአምር የተፈጸመው በዛሬዋ ዕለት ነው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ በርተሎሜዎስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን፡፡
+ + +
አቡነ ዮሴፍ ዘእንጂፋት፡- ተአምረኛው ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ ዮሴፍ ዘእንጂፋት አባታቸው ንጉሡ ዐፄ ዳዊት እናታቸው ዳግም ሞገሳ ይባላሉ፡፡ ትውልድ ሀገራቸው ወሎ መቄት እንጂፋ ነው፡፡ ኅዳር 19 ቀን ሲወለዱ በርካታ ሙታን ተነሥተዋል፡፡ ጻድቁ ያላዩት የቅዱሳን ቦታ ያልተሳለሙት ገዳም የለም፡፡ በወሎ ላስታ ሰውንና ዝንጀሮን በቃልኪዳን ያስተሳሰሩ ታላቅ አባት ናቸው፡፡

ከዕለታት በአንዱ ቀን ዝንጀሮዎቹ ተሰብስበው መጥተው እጅ ነሷቸው፡፡ አቡነ ዮሴፍም ጌታችንን ‹‹ምን አበላቸዋለሁ?›› ብለው በጸሎት ጠየቁ፡፡ ጌታችንም ‹‹አንተን ያጅቡ፣ ቅጠሉን ቃርሚያውን ይብሉ›› ብሎ አዘዛቸው፡፡ ዝንጀሮዎቹም ጻድቁን ተከትለው ይጓዙ ጀመር፡፡ አንድ ቀን በመንገድ አብረው ሲሄዱ ዝንጀሮዎቹ ‹‹ራበን›› ብለው ለአባታቸን ቢነግሯቸው ድንጋዩን በጸሎታቸው ባርከው ምግባቸው አድርገው መግበዋቸዋል፡፡

አሁንም ድረስ ላስታ ውስጥ በሚገኘው በጻድቁ ገዳም አካባቢ እህሉ በሚትረፈረፍበት ቦታ ዝንጀሮዎች በብዛት ይገኛሉ፡፡ ዝንጀሮዎቹ የሰውን እህል እንዳይበሉ፣ ገበሬውም ቃርሚያውን እንዳያነሳ በአቡነ ዮሴፍ ቃልኪዳንና ግዝት ተይዘዋል፡፡ በዚህም መሠረት አሁንም ድረስ ዝንጀሮዎቹም የሰውን እህል አይበሉም፣ ገበሬውም ቃርሚያውን አያነሳም፡፡ ገበሬው ቃርሚያውን ቢያነሳ ግን ዝንጀሮዎቹ የእሱን እህል ብቻ ለይተው ይበሉበታል፡፡

በአካባቢው አደገኛና መርዛማ እባቦች በብዛት ቢኖሩም በጻድቁ የገዳሙ ክልል ውስጥ ግን በፍጹም ሰውን አይነኩም፡፡ አቡነ ዮሴፍ ለ40 ቀን ከሰው ጋር ሳይገናኙ ቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም በደመና እየተመላለሱ ጸሎት ያደርጉ ነበር፡፡ አባታችን የተለያዩ ተአምራትን እያደረጉ ባሕር ከፍለው እየተሻገሩ ሙታንን እያስነሱ ወንጌልን ዞረው አስተምረዋል፡፡ ወደ ሰማይም ተነጥቀው እመቤታችን ዕጣን ሰጥታቸው ከ24ቱ ካህናት ጋር አጥነዋል፡፡
ጻድቁ ያመነኮሷቸው መነኮሳት በጣም በርካታ ናቸው፡፡ አቡነ ዮሴፍ ከብዙ ተጋድሏቸው በኋላ ቃልኪዳን ተቀብለው በመጨረሻ ግንቦት 19 ቀን በክብር ዐርፈው በዚያው በገዳማቸው ተቀብረዋል፡፡ ኅዳር 19 ዓመታዊ የልደት በዓላቸው ነው፡፡ በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን፡፡
+ + +

ቅዱስ ቴዎፍሎስ ከ5 ወር ሕፃን ልጁና ከሚስቱ ጋር ሰማዕት እንደሆነ፡- ይህም ቅዱስ እግዚአብሔርን መፍራትና ሥርዓተ
ቤተ ክርስቲያንን እየተማረ አደገ፡፡ ምግባር ሃይማኖቱ የቀና ሆኖ ቢያገኙት ክፉዎች ሄደው ‹‹ቴዎፍሎስ የሚባል ክርስቲያን ከዚህ አለ›› ብለው ለከሃዲው መኮንን ወነጀሉት፡፡ መኮንኑ አንቲጳጦስም ወደ እርሱ ካስመጣው በኋለ እምነቱን መረመረው፡፡ ቅዱስ ቴዎፍሎስም ‹‹የክብርን ባለቤት ጌታዬን
ኢየሱስ ክርስቶስን የማምን ክርስቲያን ነኝ›› አለው፡፡ መኮንኑም ‹‹በክፉ አሟሟት እንዳትሞት ለአማልክት ሠዋ›› አለው፡፡ ቅዱስ ቴዎፍሎስም ‹‹ከጌታዬ ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ለረከሱ አማላክት ፈጽሞ አልሠዋም›› አለው፡፡

ከዚህም በኋላ መኮንኑ በቁጣ ቅዱስ ቴዎፍሎስን የሆድ ዕቃው እስኪታይ ድረስ ሰውነቱን በመሰነጣጠቅ አሠቃየው፡፡ ቅዱሱም በጌታችን ኃይል ጤነኛ ሆነ፡፡ዳግመኛም መኮንኑ እሳት አስነድዶ በውስጡ እንዲጨምሩት አዘዘ፡፡ እንዳዘዘውም በእሳት ውስጥ በጨመሩት ጊዜ ቅዱስ ቴዎፍሎስ ከእሳቱ ውስጥ ሆኖ ቢጸልይ ምንም ሳይቃጠል ቀረ፡፡ በደህናም ከእሳቱ ውስጥ ወጣ፡፡ በዚህም ጊዜ ብዙዎች በእርሱ አምላክ አመኑ። መኮንኑም ቅዱስ ቴዎፍሎስን በረሃብ ተሠቃይቶ ይሙት በማለት በእሥር ቤት ዘጋበትና ምንም የሚበላው ነገር እንዳይሰጡት ጠባቂዎቹን አስጠነቀቃቸው፡፡ ከ8 ቀን በኋላ ሚስቱ ያለበትን አፈላጋ መጥታ አጽናናችው፣ በጌታችንም ስም ሰማዕት ይሆን
ዘንድ አበረታችው፡፡ መኮንኑም ለቅዱስ ቴዎፍሎስ ምግብ የሰጠው ሰው እንዳለ ሊመረምር በመጣ ጊዜ የእሥር ቤቱን
ደጅ ሲፍት መዓዛው የሚያውድ የዕጣን ሽታ ሸተተው፡፡ ቅዱስ ቴዎፍሎስንም ሦስት ቅዱሳን መላእክት ማርና ወተት ሲመግቡት ተመለከተ፡፡ ይህንንም በተመለከተ ጊዜ ደንግጦ ወደኋላው ተመለሰ፡፡

በማግሥቱም ቅዱስ ቴዎፍሎስን ወደ አደባባይ አውጥቶ በሕዝቡ ፊት ‹‹ለአማልክት ሠዋ›› አለው፡፡ ቅዱሱም ‹‹እኔ ዓለምን ሁሉ ለያዘው ለእውነተኛው አምላክ ለጌታዬ ለኢየሱስ ክርስቶስ በቀር አልሠዋም›› አለው፡፡ የቅዱስ ቴዎፍሎስ ሚስቱም የ5 ወር ሕፃን ልጃቸውን ይዛ ባሏን ተከትላው

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

26 Nov, 15:10


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ኅዳር 18-ቁጥሩ ከ12ቱ ሐዋርያት የሆነው ሐዋርያው ቅዱስ ፊሊጶስ ዕረፍቱ ነው፡፡
+ ዳግመኛም በዚህች ዕለት ቅዱሳት ደናግል አጥራስስ እና ዮና በሰማዕትነት ዐርፈዋል፡፡
+ ቅድስት እንትያ እና ልጇ ኤላውትሮስም እንዲሁ በዚሁ ዕለት ነው በሰማዕትነት ያረፉት፡፡

ሐዋርያው ቅዱስ ፊሊጶስ፡- ሐዋርያው ቅዱስ ፊሊጶስ ቁጥሩ
ከ12ቱ ሐዋርያት ውስጥ ነው፡፡ በማቴዎስ ወንጌል 10፡3 ላይ እንተጠቀሰው ከ12ቱ ሐዋርያት ውስጥ በ5ኛ ደረጃ ተጠቅሷል፡፡
ከገሊላ የተገኘ የቤተ ሳይዳ ሰው ሲሆን የግሪክ ሰዎችን ወደ
ጌታችን ያቀረባቸው እርሱ ነው፡፡ ዮሐ 12፡20-22፡፡
ቅዱስ ፊሊጶስ ሐዋርያው ቅዱስ ናትናኤልን ‹‹የናዝሬቱን
ኢየሱስን አግኝተነዋል መጥተህ እይ…›› በማለት ወስዶ
ከጌታችን ጋር አገናኝቶታል፡፡ ዮሐ 1፡44-52፡፡ በኋላም ጌታችንን ‹‹አብን አሳየንና ይበቃናል›› ብሎ የጠየቀውም ይኸው ሐዋርያ ፊሊጶስ ነው፡፡ ይህም ጥያቄው ለእኛ ለሁላችን መሠረታዊውን የክርስትና እውቀት እንድናገኝ እረድቶናል፡፡ ጌታችንም ‹‹እኔን ያየ አብን አይቷል፣ እኔ በአብ እንዳለሁ አብም በእኔ እንዳለ እመኑኝ›› በማለት ነው መልስ የሰጠው፡፡ ዮሐ 14፡8-14፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ፊሊጶስ ወንጌልን ዞሮ በማስተማር ብዙዎች ጣዖት ማምለካቸውን ትተው በክርቶስ እንዲያምኑ አድርጓል፡፡

ከጌታችን ዕርገት በኋላ ሐዋርያው ፍርግያ፣ ሰማርያና ጋዛ
በሚባሉ አገሮች ወንጌልን ሰብኮ ብዙዎችን አሳምኖ
አጥምቆአል፡፡ ሐዋርያው በመጨረሻ ወደ ታናሽዋ እስያ ሄዶ
በሄራፖሊስ ከተማ ሲያስተምር ብዙዎችን በማሳመኑ ክፉዎች ይዘው አሠቃዩት፡፡ ከብዙ ሥቃይም በኋላ ጣዖት አምላኪዎች ኅዳር 18 ቁልቁል ሰቅለውት ሰማዕትነቱን ፈጽሞ የድል አክሊልን ተቀዳጅቷል፡፡

ክፉዎችም በግፍ ከገደሉት በኋላ ሥጋውን በእሳት ሊያቃጥሉት በወደዱ ጊዜ የታዘዘ መልአክ የሐዋርያውን ቅዱስ ሥጋ ከእጃቸው ነጥቆ ወሰደባቸውና ሰወረው፡፡ ይህንንም ድንቅ ተአምር በተመለከቱ ጊዜ ሁሉም በአንድ ድምፅ ‹‹ከቅዱስ ፊልጶስ አምላክ በቀር ሌላ አምላክ የለም›› ብለው ጮኹ፡፡

አሠቀይተው ስለገደሉትም ተጸጽተው እጅግ አዘኑ፡፡ ክብር
ይግባውና በጌታችን ካመኑ በኋላ የሐዋርያው የቅዱስ ፊሊጶስን ቅዱስ ሥጋውን ይሰጣቸው ዘንድ በጸሎት ለመኑ፡፡ ሰውን የሚወድ ቸር ይቅር ባይ ጌታችንም የቅዱስ ፊሊጶስን ቅዱስ ሥጋውን መልሶ ሰጣቸውና እጅግ ተደሰቱ፡፡ ከሐዋርያውም ቅዱስ ሥጋ ብዙ ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራት ተፈጸሙላቸው፡፡ የሐዋርያውም መካነ መቃብሩ እስካሁንም ድረስ በዚህች ከተማ ይገኛል፡፡ የሐዋርያው የቅዱስ ፊሊጶስን በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን፡፡
+ + +

ቅዱሳት ደናግል አጥራስስ እና ዮና፡- ይህችውም ቅድስት
አጥራስስ ጣዖትን ለሚያመልክ ንጉሥ እንድርያኖስ ልጁ ናት፡፡
ከሰው ወገን ማንም እንዳያያት አዳራሽ ውስጥ ለብቻዋ
አኖራት፡፡ እርሷ ግን ስለዚህ ዓለም ኃላፊነት የምታስብ ሆነች፡፡ እውነተኛውንና የቀናውን መንገድ ይመራት ዘንድ በቀንና በሌሊት እግዚአብሔርን ትለምን ነበር፡፡ በአንድ ቀን ሌሊት ‹‹ወደ ፍላጽፍሮን ልጅ ወደ ድንግሊቱ ዮና ላኪ፣ እርሷም የእግዚአብሔርን መንገድ ትመራሻለች›› የሚል
ራእይ አየች፡፡ በዚህም በልቧ እጅግ ደስ እያላት ወደ ድንግል
ዮና መልእክት ላከችና መጣች፡፡ አጥራስስም ከእግሯ ሥር
ወድቃ ከሰገደችላት በኋላ የእግዚአብሔርን ሃይማኖት
ታስተምራትና ትገልጥላት ዘንድ ለመነቻት፡፡

ድንግል ዮናም እግዚአብሔር ዓለምን ከፈጠረበት እስከ ጌታችን ለፍርድ ዳግም መምጣት ድረስ ያለውን እውነተኛውን ሃይማኖት አስተማረቻት ይልቁንም የመድኃኔዓለም ክርስቶስን ሰው መሆንና መከራ መስቀሉን በነገረቻት ጊዜ አጥራስስ ልቧ ይቃጠል ነበር፡፡ በመጨረሻም ስለ ጌታችን ስለስሙ ብለው መከራን ለሚቀበሉና ለሚደክሙ ሁሉ ሰማያዊ ሀብት የዘላለም መንግሥትን እንደሚያወርሳቸው መጻሕፍትን እየጠቀሰች አስረዳቻት፡፡ አጥራስስም የዮናን ትምህርት በሰማች ጊዜ ደስ ተሰኝታ በጌታችን አመነች፡፡

ከዚህም በኋላ እነዚህ ሁለት ደናግል ሌትና ቀን በተጋድሎ
ተጠምደው በአንድነት ተቀመጡ፡፡ ጣዖት አምላኪው ንጉሡ
የአጥራስስ አባቷም ይህን አያውቅም ነበር፡፡ ደናግሉም
በአንድነት በተጋድሎ እየኖሩ ሳለ በአንዲት ዕለት ጌታችን
ተገለጠላቸው፡፡ ክብርት እመቤታችንም እንዲሁ
ተገለጠችላቸውና እንደ ቁርባን ለልጇ አቀረበቻቸውና እርሱም ባረካቸው፡፡
ከዚህም በኋላ ንጉሡ ወደ ጦርነት ሄዶ በተመለሰ ጊዜ ወደ ልጁ አጥራስስ ገብቶ ‹‹ልጄ ሆይ! ወደ መሞሸሪያሽ ከመግባትሽ በፊት ለአምላክ ለአጵሎን ዕጣን ታሳርጊ ዘንድ ነይ›› አላት፡፡ በዚህም ጊዜ አጥራስስ ድንግል ‹‹አባቴ ሆይ! ነፍስህና ሥጋህ በእጁ ውስጥ የሆነ የፈጠረህን በሰማይ ያለ አምላክን ትተህ ነፍስ የሌላቸው የረከሱ ጣዖታትን ለምን ታመልካለህ›› ብላ ለአባቷ መለሰችለት፡፡ ንጉሡም ይህን ነገር ከዚህ በፊት ሰምቶ አያውቅም ነበርና ተደነቀ፡፡ በልጁም ላይ ምን እንደደረሰ ልቧንም ማን እንደለወጠው ሲጠይቅ የፍላጽፍሮን ልጅ ድንግል ዮና የልጁን ልብ እንደለወጠች ነገሩት፡፡ ንጉሡም ይህን ሲሰማ እጅግ ተቆጥቶ ደናግሉን ለአማልክቶቹ እንዲሰግዱና እንዲሠው ጠየቃቸው፡፡ እነርሱም ፈጽመው አልታዘዙትም ይልቁንም የረከሱ ጣዖቶቹን ረገሙበት፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሡ ልጁን ድንግል
አጥራስስንና ድንግል ዮናን በእሳት አሠቃይተው ይገድሏቸው
ዘንድ አዘዘ፡፡

በትእዛዙም መሠረት ትልቅ ጉድጓድ ቆፍረው በውስጡ እሳት
አነደዱ፡፡ የእሳቱም ነበልባል እጅግ ከፍ ከፍ አለ፡፡ ደናግሉንም
በወርቅና በብር የተጌጠ የግምጃ ልብሶችን እንደተሸለሙ ወደ እሳቱ ጉድጓድ አወጧቸው፡፡ ደናግሉ የነገሥታት ልጆች ናቸውና ከክብር ልብስ አላራቆቷቸውም፡፡ ቅድስት አጥራስስና ቅድስት ዮናም የሚነደውን የእሳት ነበልባል ባዩ ጊዜ ልባቸውን አጠነከሩ፡፡ የአገሪቱ ታላላቅ ወገኖችና ሕዝቡም ሁሉ ደናግሉ ጨክነው ሰውነታቸውን ለእሳት መስጠታቸውን ባዩ ጊዜ እያዘኑና እያለቀሱ ከሞት እንዲድኑና እምነታቸውን እንዲተው አጥብው ለመኗቸው፡፡ ቅድስት አጥራስስና ቅድስት ዮና ግን እጅ ለእጅ ተያይዘው ከጸለዩ በኋላ ወደ እሳቱ ውስጥ ዘለው ገቡ፡፡

ነፍሳቸውንም ለእግዚአብሔር አሳልፈው ሰጡ፡፡ እነርሱም
ሰማዕተነታቸውን ከፈጸሙ በኋላ እሳቱ ወዲያው ጠፋ፡፡ ቅዱሳት ደናግልም እሳቱ ፈጽሞ እንዳላገኛቸው ሆነው ተገኙ፡፡ የራስ ፀጉራቸው እንኳን አልተቃጠለም ነበር፡፡ ይህንንም ያዩ ሁሉ ‹‹እኛም በእነነዚህ ደናግል ሴቶች አምላክ አምነናል›› እያሉ በመመስከር ሰማዕት ሆኑ፡፡ ከዚህም በኋላ ምእመናን የቅድስት አጥራስይንና የቅድስት ዮናን ሥጋቸውን ወስደው የመከራው ዘመን እስኪፈጸም ድረስ በድብቅ አኖሩት፡፡ በኋላም ያማረች ቤተ ክርስቲያን ሠርተውላቸው ቅዱስ ሥጋቸውን በዚያ አኖሩ፡፡
ከሥጋቸውም ብዙ ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራት ተፈጽመው
ታዩ፡፡ የቅድስት አጥራስይና የቅድስት ዮና በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን፡፡
+ + +

ቅድስት እንትያ እና ልጇ ኤላውትሮስ፡- እነዚህም ቅዱሳን እናትና ልጅ ከሮሜ አገር የተገኙ ሰማዕታት ናቸው፡፡ ቅድስት እንትያም ልጇን በሃይማኖት በምግባር ኮትኩታ ካሳደገችው በኋላ ዲቁናና ቅስና እንዲማርላት አንቂጦስ ለሚባል ኤጲስቆጶስ ሰጠችው፡፡ ኤጲስቆጶሱም ኤላውትሮስን እያስተማረ አሳደገውና በ17 ዓመቱ ዲቁና ሾመው፣ ቀጥሎም ከዓመት በኋላ ቅስና ሾመው፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

26 Nov, 15:10


ከዚህም በኋላ ቅዱስ ኤላውትሮስ ምግባር ሃይማኖቱ፣ ተጋድሎ ትሩፋቱ ያመረ የሰመረ ነውና ገና በ20 ዓመቱ አላሪቆስ ለሚባል አገር ጵጵስና ተሾመ፡፡ እርሱም ምእመናንን እያስተማረ በበጎ ጎዳና የሚመራቸው ሆነ፡፡
ከዚህም በኋላ የቅዱስ ኤላውትሮስ ምግባር ሃይማኖቱ
ቅድስናውና ትምህርቱ በሁሉ ዘንድ ተሰማ፡፡ በዚያም ወራት
ከሃዲው ንጉሥ እንድርያኖስ ወደ ሮሜ አገር በመጣ ጊዜ
የቅዱስ ኤላውትሮስን ዜና ሰማ፡፡ ወደ እርሱም ያመጣው ዘንድ መኮንኑን ፊልቅስን ላከው፡፡ ፊልቅስም በሄደ ጊዜ ቅዱሱን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ምእመናንን ሲያስተምር አገኘውና ትምህርቱን ቢሰማ ልቡ ቀልጦ በዚያው በጌታችን አምኖ ተጠመቀ፡፡

ንጉሡም ሌሎች ጭፍሮቹን ልኮ ቅዱስ ኤላውትሮስ ወደ እርሱ ካስመጣው በኋላ ‹‹ለአማልክት ሠዋ፣ አንተ ነፃነት ያለህ ስትሆን ለተሰቀለ ሰው ለምን ትገዛለህ›› አለው፡፡ ቅዱስ ኤላውትሮስም ‹‹ነፃነትማ ሰማይንና ምድርን በፈጠረ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ነው›› አለው፡፡ በዚህም ጊዜ ንጉሡ ተናደደና ቅዱሱን ሰውነትን የሚቆራርጥ መንኮራኩር ካለው የእሳት ማንደጃ ውስጥ እንዲጨምሩት አዘዘ፡፡ ቅዱስ ኤላውትሮስንም በጨመሩት ጊዜ እሳቱ ፈጽሞ ጠፋ፣ መንኮራኩሩም ስብርብሩ ወጣ፡፡ ንጉሡም ይህን አይቶ አደነቀ፣ የሚያደርገውንም እስኪያስብ ድረስ ወህኒ ቤት ውስጥ ጣለው፡፡

ቅዱስ ኤላውትሮስ በወህኒ ቤት ሳለ የታዘዘች ርግብ ከገነት
መብልን አምጥታለት እርሱን ተመግቦ ሰውነቱ ታደሰ፡፡ ቆሊሪቆስ የሚባለው መኮንንም ይህን በግልጽ አይቶ በማድነቅ ‹‹በቅዱስ ኤላውትሮስ አምላክ አምኛለሁ›› ብሎ መስክሮ በሰማዕትነት አንገቱን ተሰይፎ የክብር አክሊልን ተቀዳጀ፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሡ ቅዱስ ኤላውትሮስን በፈረሶች ሠረገላ ላይ አስረው ሥጋው ተቆራርጦ እስኪያልቅ ድረስ ፈረሶቹን በቦታው ሁሉ እንዲያስሮጧቸው አዘዘ፡፡

እንደትእዛዙም በቅዱስ ኤላውትሮስ ላይ ይህንን ባደረጉ ጊዜ ሥጋው ተቆራርጦ ወደቀ፡፡ ወደጌታችንም በጸለየ ጊዜ መልአኩን ላከለት፡፡ መልአኩም የቅዱሱን ሥጋ ከፈረሶቹ ሠረገላ ላይ ነጥቆ ወስዶ በአንድ ከፍተኛ ተራራ ላይ አስቀመጠው፡፡ ቅዱስ ኤላውትሮስም እግዚአብሔርን እያመሰገነ ከአራዊት ጋር በዚያ ተቀመጠ፡፡

ከዕለታትም በአንደኛው ቀን የንጉሥ እንድርያኖስ ጭፍሮች
አራዊትን ያድኑ ዘንድ ወደዚያ ተራራ ሲወጡ ቅዱስ ኤላውትሮስን አገኙትና ወስደው ለንጉሣቸው ሰጡት፡፡ ንጉሡም ለተራቡ አንበሶች ሰጠው ነገር ግን አንበሶቹ እግሮቹን ሳሙለት የፊቱንም ልብ ጠረጉለት እንጂ አልነኩትም ይልቁንም ወደ ንጉሡ ሠራዊት ፈጥነው ተመልሰው 150 ሰዎችን ገደሉ፡፡ ንጉሥ እንድርያኖስም ይህንን አይቶ እጅግ በቁጣ ተመላ፡፡ ወታደሮቹንም ጠርቶ ቅዱስ ኤላውትሮስን ከቅድስት እናቱ ጋር በጦር እንዲወጓቸው አዘዘ፡፡ እናቱን ቅድስት እንትያንንም እንደልጇ ብዙ ካሠቃዩአት በኋላ
የልጇን አንገት እንዳቀፈች ከእርሱ ጋር አንድ ላይ በጦር
ወጓቸውና ነፍሳቸውን በእግዚአብሔር እጅ ሰጡ፡፡
ሰማዕትነታቸውንም ከፈጸሙ በኋላ የክብርን አክሊል ተቀዳጁ፡፡ ከሥጋቸውም ብዙ ተአምራ ተፈጽመው ታዩ፡፡

የሐዋርያውን የቅዱስ ፊሊጶስን፣ የቅዱሳት ደናግል
የአጥራስስንና የዮናን፣ የቅድስት እንትያንና የልጇን የቅዱስ
ኤላውትሮስን ረድኤት በረከታቸውን ያሳድርብን፣ በጸሎታቸው
ይማረን፡፡

(ምንጭ፡- ስንክሳር ዘወርሃ ኅዳር፣ ቤተ ክርስቲያንህን ዕወቅ-
ማኅበረ ቅዱሳን፣ ትንሣኤ መጽሔት ቁ.50 1974 ዓ.ም ከገድላት አንደበት)
✞ ✞ ✞

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

21 Nov, 06:38


‹‹ክብርህ ከመላእክት ኹሉ ክብር ከፍ ያለ የምሕረት መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ! መሬትና ውኃ ለአልተቀላቀለበት ከነፋስና እሳት ብቻ ለተፈጠረው መልአካዊ ገጽታህ ሰላም እላለሁ፤ ከላይ ከሰማይ ተልከህ በምትመጣበት ጊዜ በሲኦል የሚኖሩ ግዞተኞች ኹሉ ‹ቅዱስ ሚካኤል ሆይ! መጣኽልን ደረስኽልን› እያሉ ደስታቸውን ይገልጣሉ፡፡›› (መልክዐ ቅዱስ ሚካኤል)

በመላው ዓለም የምትኙ ኦርቶዶክሳውን እና ኦርቶዶክሳውያት ኹላችሁ እንኳን ለሊቀ መላእክት ለቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን! ለሀገራችን ሰላም ለሕዝባችን ፍቅር አንድነትን ያድለን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

20 Nov, 15:23


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ኅዳር 12-ከጽንፍ እስከ ጽንፍ የሚበር ንሥረ አርያም የሚባል ውዳሴው እንደ ማር የጣፈጠ ንዑድ ክቡር የሆነ ለፍጥረቱ ሁሉ የሚማልድ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል የተሾመበት ዕለት ነው፡፡
+ ጻዲቁ ንጉሥ በእደ ማርያም ዕረፍታቸው መሆኑን ስንክሳሩ በስም ይጠቅሳቸዋል፡፡
+ የመጥምቁ ዮሐንስ ራስ በደብረ ማህው የታየችበት ዕለት መሆኑን ስንክሳሩ ይጠቅሳል፡፡
የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል፡- ሚካኤል ማለት በዕብራይስጥ ቋንቋ ሚ-መኑ' ካ-ከመ' ኤል-አምላክ ማለት ሲሆን በአንድነት ሲነበብ ‹‹መኑ ከመ አምላክ-እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው›› ማለት ነው፡፡ አንድም ለእግዚአብሔር አሸናፊ ድል አድራጊ የቸርነትና የርህራሄ መገኛ መዝገብ ማለት ነው፡፡
ገናናው መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ዲያብሎስን ወደ ጥልቁ ጥሎት በእርሱ ምትክ ከሁሉ የበላይ ሆኖ በተሾመበት በዚህ ዕለት በበዓሉ መታሰቢያ በኅዳር 12 ቀን የክብር ባለቤት በሆነ በእግዚአብሔር ፈቃድ ክንፎቹን ወደ ሲኦል ያወርዳል፣ ኃጥአንንም ወደ አዲሲቱ ምድር ያወጣቸዋል ይኸውም የመላእክት አለቃ የሚካኤል ሠራዊት ይሆናሉ፡፡ ይቅርታ የተደረገላቸውና ምሕረት አግኝተው በአንድ ጊዜ በክንፉ ያወጣቸው ስፍር ቁጥር የላቸውም፡፡ ቅዱስ ሚካኤል በየዓመቱ በኅዳር 12 ቀን እንዲህ እያደረገ እልፍ ነፍሳትን ያወጣል፡፡ የቤተ ክርስቲያን ወገኖች የሆኑትን ሁሉ እንደሥራቸው ወደ ምሕረት ቤት ወደ ሰማያዊት ኢየሩሳሌም ይወስዳቸዋል፡፡ ከዚህም በኋላ ወደ አብ መጋረጃ ውስጥ ይገባል፣ በዚህች ዕለት ምድራዊትና ሰማያዊት ስለሆነች ምሕረቱም ከመንበሩ በታች ይሰግዳል፡፡ ስለውኃ ምንጮች፣ ስለ ወይን ቦታዎች፣ ስለ ምድር ፍሬዎች በምድርም ላይ ስለሚኖሩ ስለ ሰው ልጆች ነፍስ ሁሉ፣ ስለ እንስሳትም፣ ስለ ሰማይ ወፎችም፣ ስለ ባሕር ዓሣዎችም፣ በምድር ላይና በባሕር ውስጥ ስለሚንቀሳቀሱ ሁሉ የምሕረት ባለቤት ከሆነ ከአብ ዙፋን በታች ሁልጊዜ በማመስገን ይሰግዳል፤ ልመናውንም እስኪሰማውና የምሕረትንም ቃል እስኪያስተላልፍለት ድረስ ከእግረ መንበሩ ሥር አይነሣም፡፡
ለዚህ ዓለም ምሕረትን የሚለምኑ ቅዱሳን መላእክትም በየዓመቱ ኅዳር 12 ቀንበእግዚአብሔር የዙፋኑ ዓውደ ምሕረት ዙሪያ ተሰብስበው ስለ ሰውና ስለ እንስሳትም ሁሉ ምሕረትን የሚለምን ቅዱስ ሚካኤል ከአብ መጋረጃ ውስጥ በወጣ ጊዜ ቸርና መሐሪ አብ ለቅዱስ ሚካኤል የሰጠው ልብሱን እነዚያ መላእክት ይመለከታሉ፣ ይቅርታን የማግኘት ምልክታቸው ነውና፡፡ ስለዚህ እነዚህ ቅዱሳን መላእክት በምድር ላይ ምሕረት እንደተደረገ ሰውንም እንስሳትንም ይቅር እንዳለ በዚህ ዓለምም የሚሆነውን ሁሉ አይተው ቅዱስ ሚካኤል በለበሰው ልብስ አምሳል ያውቁታል፡፡
ስንክሳሩ እንደሚለው ይህ እጅግ የከበረ ገናና መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ‹‹ከቅዱሳን ሰማዕታት ጋራ በመሆን ገድላቸውን እስኪፈጽሙ ድረስ የሚያጽናናቸውና የዘወትር ጠባቂአቸው ሆኖ የሚራዳቸው እርሱ ነው፡፡›› የብዙዎቹንም ቅዱሳን ገድል ስንመለከት የዘወትር ጠባቂያቸው ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡
ቅዱሳን በሕይወት ሳሉ ይህ ገናና መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ረዳትና የዘወትር ጠባቂ፣ እንደጓደኛም አማካሪ ሆኖ የተበቃቸውን ስንቱን ቅዱሳን ዘርዝረን እንቸላለን፡፡ እርሱ ያልረዳው ቅዱስ የለም፡፡ መከራውን ያላስታገሰው ሰማዕት የለም፡፡ ለቅዱሳኑ እንዲህ እንደጓደኛቸው ሆኖ ሲጠብቃቸው ይኖራል፡፡ ነገር ግን ቅዱስ ሚካኤል ለኃጥአንና አምላካቸውን ለካዱ ሰዎች ደግሞ በቁጣ ለመቅሰፍት ይመጣባቸዋል፡፡ ሰናክሬም በእግዚብሔር ላይ ክፉ በመናገሩ በአንዲት ሌሊት ብቻ 185,000 (መቶ ሰማንያ አምስት ሺህ) ሠራዊቱን ቅዱስ ሚካኤል በብርሃን ሰይፉ ፍጅቷቸው አድሯል፡፡ 2ኛ ነገ 19፡35፣ ኢሳ 37፡36፡፡
እግዚአብሔርን ለሚወዱና እርሱንም ለሚያከብሩት መታሰቢያውንም ለሚያደርጉለት ግን ከሚፈልጉት ነገር ከቶ አያሳጣቸውም፣ ዘወትርም ይጠብቃቸዋል፣ በኋላም በአማላጅነቱም ከሲኦል እሳት ያድናለቸዋል፡፡ እነሆ ይህ ገናና ክቡር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ያደረገው ተአምር ይህ ነው፡- ‹‹የእግዚአብሔር ወዳጅ የሆነ ስሙ ዱራታዎስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፡፡ የሚስቱም ስም ቴዎብስታ ነው፡፡ እነርሱም ሁልጊዜ ያለማቋረጥ የዚህን የከበረ መልአክ የቅዱስ ሚካኤልን የበዓሉን መታሰቢያ ያደርጉ ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ በሀገር ውስጥ ችግር በሆነ ጊዜ ገንዘባቸው አለቀ፡፡ ለቅዱስ ሚካኤልም ለበዓሉ መታሰቢያ የሚያደርጉትን እስኪያጡ ድረስ ቸገራቸው፡፡ ዱራታዎስም ሸጦ ለመልአኩ በዓል መታሰቢያ ያደርገው ዘንድ የእርሱንና የሚስቱን ልብስ ይዞ ወጥቶ ሄደ፡፡
የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም በታላቅ መኮንን አምሳል ለዱራታዎስ ተገለጠለትና ወደ ባለጸጎች ሄዶ በእርሱ ዋስትና በአንድ ዲናር አንድ በግ እንዲወስድ፣ ሁለተኛም ወደ ባለ ስንዴ ዘንድ ሄዶ በእርሱ ዋስትና ስንዴን እንዲወስድ ዳግመኛም ወደ ዓሣ አጥማጅ ዘንድ ሄዶ አንድ ዓሣ እንዲወስድ ነገር ግን ወደቤቱ ሳይርስ የዓሣውን ሆድ እንዳይቀድ አዘዘው፡፡ ዱራታዎስም እንደታዘዘው አደረገ፡፡ ወደቤቱም በተመለሰ ጊዜ ቤቱ ሁሉ በበረከት ተመልቶ አገኘው፡፡ እርሱም እጅግ ተደስቶ የዚህን የክበር መልአክ የመታሰቢያውን በዓል አደረገ፡፡ ጦም አዳሪዎችንና ድኆችን ጠርቶ አጠገባቸው፡፡
ከዚህም በኋላ ለዱራታዎስና ለሚስቱ ቅዱስ ሚካኤል ሁለተኛ ተገለጠላቸው፡፡ ዱራታዎስንም የዓሣውን ሆድ እንድሰነጥቅ አዘው፡፡ በሰነጠቀውም ጊዜ 300 የወርቅ ዲናር በዓሣው ሆድ ውስጥ ተገኘ፡፡ ቅዱስ ሚካኤል ዱራታዎስንና ሚስቱን ቴዎብስታን እንዲህ አላቸው፡- ‹‹ከዚህ ዲናር ወስዳችሁ ለባለ በጉ፣ ለባለ ዓሣውና ለባለ ስንዴው ዕዳችሁን ክፈሉ፡፡ የቀረውም ለፍላጎታችሁ ይሁናችሁ እግዚአብሔር አስቧችኋልና በጎ ሥራችሁን፣ መሥዋዕታችሁንና ምጽዋታችሁን አስቦ በዚህ ዓለም አሳመረላችሁ፣ በኋለኛውም መንግሥተ ሰማያትን አጀጋጀላችሁ›› አላቸው፡፡
እነርሱም ይህን ነገር ሲሰሙ ደነገጡ፡፡ የከበረ ገናናው መልአክም ‹‹ከመከራችሁ ሁሉ ያዳንኳችሁ የመላእክት አለቃ እኔ ሚካኤል ነኝ፣ መሥዋዕታችሁንና ምጽዋታችሁን ወደ እግዚአብሔር ፊት ያሳረግሁ እኔ ነኝ፡፡ አሁንም በዚህ ዓለም ከበጎ ነገር እንድታጡ አላደርጋችሁም›› አላቸው፡፡ ይህንንም ከነገራቸው በኋላ ወደ ሰማያት ወጣ፡፡ እነርሱም በፍርሃትና በክብር ሰገዱለት፡፡››
የመላእክት አለቃ ቅዱስ የሚካኤል ጥበቃው አይለየን! ከበዓሉ በረከት ይክፈለን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

19 Nov, 18:55


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ኅዳር 11-ክብርት እመቤታችን ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክን የወለደቻት ቅድስት ሐና ዕረፍቷ ነው፡፡ ሐና ማለት ‹‹ጸጋ›› ማለት ነው፡፡ አምላክን የወለደች የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም እናት ናት፡፡ እርሷም ከኢየሩሳሌም አገር ከሌዊ ነገድ ከካህኑ አሮን ትውልድ የሌዊ የሜልኪ ልጅ ለሆነ ለማጣት ልጁ ናት፡፡ የቅድስት ሐና አባት ማጣትና እናቷ ሄርሜላ ከእርሷ በተጨማሪ ሶፍያና ማርያም የሚባሉ ሌሎች ሁለት ሴት ልጆችን ወልደዋል፡፡ ቅድስት ሐና ከይሁዳ ነገድ የሆነውን ጻድቅ ኢያቄምን አግብታ ቅድስት ድንግል ማርያምን ወለደች፣ ድንግል ማርያምም መድኃኔዓለም ክርስቶስን ወለደች፡፡ ሶፍያ ኤልሳቤጥን ወለደች፣ ኤልሳቤጥም መጥምቁ ዮሐንስን ወለደች፡፡ ከሦስቱም ታናሽ የሆነችው ‹‹ማርያም›› የተባለችው የማጣትና የሄርሜላ ልጅ ደግሞ ሰሎሜን ወለደቻት፡፡
ይህችም ታላቅ እናት ቅድስት ሐና አምላክን በድንግልና ሆና በሥጋ ለወለደችው ለቅድስት ድንግል ማርያም ወላጇ ትሆን ዘንድ የተገባት ሆናለችና ከሴቶች ሁሉ እንደምትበልጥና እንደምትከብር እንረዳ፡፡ ለዓለም ሁሉ ድኅነት የተደረገባትን ልዩ ስጦታ የሆነች ድንግል ማርያምን እርሷ አስገኘቻት፡፡ የዚህች ክብርት እናት የትውልዷ ጥንተ ነገሩ እንዲህ ነው፡- ጴጥርቃ እና ቴክታ የሚባሉ የከበሩ ደጋግ ሰዎች በኢየሩሳሌም በአንድነት ተጋብተው በሕገ እግዚአብሔር ይኖሩ ነበር፡፡ እነዚህም በእግዚአብሔር የሚያምኑ የተወደዱ ጻድቃን ደግ ሰዎች ናቸው፡፡ እነርሱም በእግዚአብሄርም በሰውም ዘንድ የተመሰከረለላቸው ባለጸጎች ነበሩ፡፡ ነገር ግን መካን ስለነነበሩ የሚወርሳቸው ልጅ አልነበራቸውም፡፡
አንድ ቀን ጴጥርቃ ቴክታን እንዲህ አላት፡- ‹‹እህቴ ሆይ! ይህን ሁሉ የሰበሰብነውን ገንዘባችንን ምን እናደርገዋለን? ልጅ የለን የሚወርሰን፣ አንቺም መካን ነሽ እኔም ካንቺ በቀር ሌላ ሴት አላውቅም›› አላት፡፡ እርሷም ‹‹ወንድሜ ሆይ! አምላከ እስራኤል ለእኔ ልጅ ቢነሳኝ አንተም እንደኔው ሆነህ ትቀራለህን? ከሌላ ደርሰህ ውለድ እንጂ›› ብላ ብታሰናብተው እንደዚህ ያለ ነገር እንኳንስ ላደርገው በልቦናዬም እንዳላስበው አምላከ እስራኤል ያውቃል›› አላት፡፡ እርሷም ‹‹አምላከ እስራኤል የሚያደርገውን የሚያውቅ የለም፣ ትላንትና ማታ በህልሜ ነጭ ጥጃ ከማኅፀኔ ስትወጣ ያችም ነጭ ጥጃ ሌላ ነጭ ጥጃ ስትወልድ እንዲሁ እስከ 7ት ትውልድ ሲዋለድ ሰባተኛይቱ ጨረቃን ስትወልድ፣ ጨረቃዋም ፀሐይን ስትወልድ አየሁ›› አለችው፡፡ እርሱም በጠዋት ከህልም ፈቺ ዘንድ ሔዶ የነገረችውን ሁሉ ነገረው፡፡ ያም ህልም ፈቺ ‹‹እግዚአብሔር በምሕረቱ አይቷችኋል፣ በሳህሉ መግቧአችኀል፣ 7 አንስት ጥጆች መውለዳችሁ 7 ሴቶች ልጆች እና የልጅ ልጆች ትወልዳላችሁ፤ ከቤታችሁ ሰባተኛይቱ ጨረቃ መውለዷ ከሰው የበለጠች ከመላእክትም የከበረች ደግ ፍጥረት ትወልዳላችሁ የፀሐይ ነገር ግን አልታወቀኝም›› አለው፡፡
ጴጥርቃም ሕልም ፈቺው የነገረውን ሁሉ ሔዶ ለሚስቱ ነገራት፡፡ እርሷም ‹‹እንጃ አምላከ እስራኤል የሚያደርገውን ማን ያውቃል!?›› ብላ ዝም አለች፡፡ ከዚያም ፀንሳ ሴት ልጅ ወለደች፡፡ ስሟንም ሄሜን ብለው አወጡላት፤ ሄሜንም አድጋ ለአካለ መጠን ስትደርስ አጋብተዋት ሴት ልጅ ወለደች፣ በስምንተኛ ቀኗም ዴርዲ ብለው ስም አወጡላት፡፡ ዴርዲም አድጋ እንዲሁ ሴት ወለደችና ቶና አለቻት፣ ቶናም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ሲካር አለቻት፣ ሲካርም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ሴትና አለቻት፣ ሴትናም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ሄርሜላ አለቻት፣ ሄርሜላም እንዲሁ ሴት ልጅ ወልዳ ንጽህት ቅድስት ክብርት የምትሆን እመቤታችንን የምትወልደውን ሐናን ወለደች፡፡
ይህቺም ሐና በሥርዓት አድጋ ለአእምሮ ስትበቃ አካለ መጠን ስትደርስ ከቤተ መንግስት ወገን ከነቅዱስ ዳዊት ወገን ከሆነው ከቅዱስ ኢያቄም ጋር አጋቧት፡፡ እነዚህ ቅዱሳን ኢያቄምና ሐና በአንድነት ተጋብተው ሲኖሩ ልጅ አጡ፡፡ እነርሱም እጅግ ደጋግ ሰዎች ነበሩ፡፡ አንድ ልጅ እንኳ ስላልነበራቸው እጅግ ያዝኑ ነበር፡፡ ወደ ቤተመቅደስ እየሄዱ እግዚአብሔር ልጅ ይሰጣቸው ዘንድ አጥብቀው ይለምኑት ነበር፡፡ መብዓ ይዘው ለሊቀ ካህኑ ሲሰጡት ሊቀ ካህኑም እንኳ ሳይቀር ‹‹እግዚአብሔር ብዙ ተባዙ ያለውን ሕግ በእናንተ ላይ እንዳይፈጸም አድርጎ ልጅ የከለከላችሁ ኃጢአተኛ ብትሆኑ ነውና መብዓችሁን አልቀበልም›› ብሎ በእጅጉ አሳዝኗቸዋል፡፡ በሊቀ ካህኑ እያዘኑና እየተከዙ ሲመለሱ ከድካማቸው ያርፉ ዘንድ ዛፍ ሥር ተቀመጠው ሳለ እርግቦች ጫጩቶቻቸውን ሲያጫውቱ ተመልክተው ‹‹ለእነዚህ ወፎች እንኳ ልጆችን የሰጠህ አምላክ ለእኛስ መች ይሆን ልጅ የምትሰጠን?›› ብለው እጅግ አምርረው አለቀሱ፡፡
ሲያዝኑ ሲጸልዩ ውለው ወደቤታቸው ሲመለሱ ርግብ ከልጆቿ ጋር ስትጫወት አይታ ‹‹አቤቱ ጌታዬ ለዚች እንስሳ ልጅ የሰጠህ አምላክ ምነው ለኔ ልጅ ነሳኸኝ?›› እያለች ምርር ብላ አለቀሰች፡፡ እንዲህ ብለው ሲያዝኑ ሲጸልዩ ውለው ከዘካርያስ ከሊቀ ካህናቱ ሄደው ‹‹አቤቱ ጌታችን ሆይ ወንድ ልጅ ብንወልድ ተምሮ ቤተ እግዚአብሔርን አገልግሎ እንዲኖር እንሰጣለን፤ ሴት ልጅም ብንወልድ ውኃ ቀድታ መሶብ ወርቅ ሰፍታ መጋረጃ ፈትላ ካህናትን አገልግላ እንድትኖር እንሰጣለን›› ብለው ስዕለት ገቡ፡፡ ዘካርያስም ‹‹እግዚአብሔር ጸሎታችሁን ይስማችሁ ስዕለታችሁን ይቀበልላችሁ የልቦናችሁን ሀሳብ ይፈጽምላችሁ›› ብሎ አሳረገላቸው።
ከዚህም በኋላ ቅድስት ሐና እና ቅዱስ ኢያቄም ዕለቱን ራእይ አይተው ነገር አግኝተው አደሩ፡፡ ራእዩስ እንዴት ነው ቢሉ ኢያቄም ‹‹7ቱ ሰማያት እንደ መጋረጃ ተገልጠው ከላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ›› አላት፡፡ ‹‹ወፍ›› የተባለው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፤ ነጭነቱ ንጽሐ ባህሪው ነው፤ ‹‹ከላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ›› ማለቱ የኢያቄምን (የሰውን) ባህርይ ባህርይ እንዳደረገው ዕወቅ ሲል ነው፡፡ 7ቱ ሰማያት የተባሉ የጌታችን ልዩ ልዩ ባሕርይው ምልአቱ ስፋቱ ርቀቱ ልዕልናው ናቸው፡፡ ሐናም ‹‹እኔም ደግሞ አየሁ እንጂ›› አለችው፡፡ ‹‹ምን አየሽ?›› ቢላት ‹‹ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማህጸኔ ስትተኛ አየሁ›› አለችው፡፡ ‹‹ርግብ›› የተባለች እመቤታችን ድንግል ማርያም ናት፤ ነጭነቱ ንጽህናዋ ቅድስናዋ ድንግልናዋ ነው፡፡ ‹‹ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ተቀምጣ ከራሴ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማኅፀኔ ስትተኛ አየሁ›› ማለቷ ብሥራተ ገብርኤልን በጆሮዋ ሰምታ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታችንን መፀነሷን ነው፡፡ ይህንኑም ራእይ ያዩት ሐምሌ 30 ዕለት ነው፡፡
እነርሱም እንዲህ ያለ ራእይ ካየን ነገር ካገኘን ብለው ዕለቱን በሩካቤ ሥጋ አልተገናኙም ይልቁንም ፈቃደ እግዚአብሔር ቢሆን ብለው አዳምንና ሔዋንን ‹‹‹ብዙ ተባዙ ምድርንም ምሉአት›› ብሎ ያበሰረ አምላክ ለእኛስ ይልክልን የለምን?›› ብለው ዕለቱን አልጋ ምንጣፍ ለይተው እስከ 7 ቀን ድረስ ለየብቻቸው ሰነበቱ፡፡ ነሐሴ በባተ በሰባተኛው ቀን ‹‹‹ከሰው የበለጠች ከመላእክት የከበረች ደግ ፍጥረት ትወልዳላቹህና ዛሬ በሩካቤ ሥጋ ተገናኙ› ብሎሏችኀል ጌታ›› ብሎ መልአኩ ለቅድስት ሐና ነገራት፡፡ በፈቃደ እግዚአብሔርር በብሥራተ መልአክ እመቤታችን እግዝእትነ ማርያምን ፀነሰቻት፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

19 Nov, 18:55


እግዚአብሔር አምላክ አብርሃምን እና ሳራን የተመለከተ አምላክ በኢያቄምና ሐና አማካኝነት ለዓለም ድኅነት ምክንያት የሆነችውን እና ዓለም ሳይፈጠር በአምላክ ልቦና ታስባ ትኖር የነበረች የተነገረላት ትንቢት ሊፈጸም የአባት የእናቷ የቅድመ አያቶቿ ራእይ ሊተረጎም ጌታ የፈቀደበት ጊዜ ሲደርስ እመቤታችን እግዝእትነ ማርያም እሁድ እለት ነሐሴ 7 ቀን በ16 ዓ.ዓ ተፀነሰች፡፡
እመቤታችን ከተፀነሰች በኋላ አይሁድ ቀንተው ተነሱባቸው ቅናቱ እንዴት ነው ቢሉ ሳሚናስ የሚባል የጦሊቅ ልጅ ከኤዶቅ ካጎቱ ቤት ሄዶ ሞተ፤ እነርሱም እንቀብራለን ብለው ባልጋ ይዘው ሲሄዱ ከመንገድ አሳረፉት፡፡ ቅድስት ሐናም የአጎቷ ልጅ ነበርና ለማልቀስ ብትደርስ ዘመዶቿ ሁሉ ተሰብስበው ሲላቀሱ ቆዯአት፤ እርሷም አብራ እየዞረች ስታለቅስ ጥላዋ ቢያርፍበት መግነዝ ፍቱልኝ ሳይል ብድግ ብሎ ተነሥቶ "ስብሃት ለኪ ማርያም እሙ ለፀሐየ ጽድቅ ለአብ ሙሽራው ለወልድ ወላዲቱ ለመንፈስ ቅዱስ ጽርሃ ቤቱ ተፈስሂ ደስ ይበልሽ" ብሎ ሰገደላት፡፡ አይሁድም ይህ ተአምር ሲደረግ ከዚያው ነበሩና "ምነው ሳሚናስ ምን አየህ? ምን ትላለህ?" ቢሉት "ከዚች ከሐና ማኅፀን የምትወለደው ሕፃን ሰማይ ምድርን አየርን የፈጠረ አምላክን ትወልዳለች እያሉ መላእክት ሁሉ ሲያመሰግኗት ሰማሁ" አላቸው፡፡ ዳግመኛም "እኔንም ያነሣችኝ የፈወሰችኝ ያዳነችኝ እርሷ ናት" አላቸው፡፡ አይሁድም "በል ተወው ሰማንህ" ብለው ቅናት ጀመሩ፡፡ ሐና በእርጅናዋ ጊዜ መፀነሷን የተመለከቱ ዘመዶቿና ያገሯ ሰዎች ተገርመው እየመጡ ይጠይቋት ነበር፡፡ እመቤታችን ማርያም በፅንስ እያለች ብዙ ታምራትን አድርጋለች። ከእነዚህም መካከል ዐይነ ስውር የነበረችው የአርሳባን ልጅ ወደ ሐና መጥታ እውነትም ሐና መጸነሷን ለማረጋገጥ ሆዷን ዳሰሰቻት፡፡ እርሷም ሳታስበው ዐይኗን ስትነካ ዐይኗ በራላት፡፡ እመቤታችንም በተፀነሰች በ9 ወር ከአምስት ቀን የግንቦት መባቻ ዕለት ግንቦት 1 ተወለደች፡፡
አምላክን የወለደች የድንግል ማርያም እናት የክብርት ሐና ዐፅሟን አባቶቻችን ከቅዱስ መስቀሉ ጋር ወደ አገራችን ኢትዮጵያ አምጥተውልናል፡፡ የጌታችን ቅዱስና ክቡር መስቀል ካለበት በወርቅ ከተለበጠው ከዕንጨቱ ሣጥን ውስጥ ዐፅማቸው በክብር ከተቀመጡ ብዙ የከበሩ ቅዱሳን ውስጥ አንዱ ይህ የእናታችን የቅድስት ሐና ዐፅም ነው፡፡ ይህንንም መጽሐፈ ጤፉት በደንብ ይገልጸዋል፡፡
የእናታችን የቅድስት ሐና ረድኤት በረከቷ ይደርብን፣ በጸሎቷ ይማረን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

19 Nov, 07:09


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ኅዳር 10-ቅድስት ሶፍያ ከ50 ቅዱሳት ደናግል ጋር በሰማዕትነት ዐረፈች፡፡
+ ዳግመኛም በዚህች ዕለት ቅዱሳን አባቶቻችን ስለ ጾም ሥርዓት የአንድነት ስብሰባ አድርገው የቅዱስ ዲሜጥሮስን ቀመር አቡሻህርን በሁሉም ዘንድ እንዲጠቀሙበት በጉባኤ ወሰኑ፡፡
ቅድስት ሶፍያ ዘሮም፡- ሶፍያ ማለት ጥበብ ማለት ነው፡፡ በሶፍያ ስም የሚጠሩ ከሰባት በላይ ቅዱሳት አንስት አሉ፡፡ ከእነዚህም ውስጥ ዛሬ የዕረፍቷን በዓል የምናከብርላት ቅድስት ሶፍያ ከሮም የተገኘች ሰማዕት ናት፡፡ ብዙ ቅዱሳት መነኮሳይያት ከያሉበት አገር ተሰብስበው በሮሜ አገር መንኩሰው በጋራ በታላቅ ተጋድሎ ይኖሩ ነበር፡፡ ምግባር ሃይማኖቷ፣ ትሩፋት ተጋድሎዋ ከሁሉ ይልቅ ያማረ ነውና ቅድስት ሶፍያም ለእነርሱ እመ ምኔት ሆና በምክር ታስተዳድራቸው ነበር፡፡ ቁጥራቸውም 50 ደናግል ነበሩ፡፡ ቅድስት ሶፍያ ጸጋንና ዕውቀት የተመላች ናትና ሁሉንም ደናግል ልጆቿንም የቅዱሳን ገድል እንዲያነቡ በማድረግ ጾም ጸሎትን በማብዛት በምድር ላይ እንደ መላእክት እስኪሆኑ ድረስ በመንፈሳዊ እድገት አሳደገቻቸው፡፡ ከእነርሱም ውስጥ በቅድስና 70 ዓመት የኖሩ አሉ፡፡
ከሃዲው ንጉሥ ዑልያኖስ ከፋርስ ንጉሥ ከሳቦር ጋር ሊዋጋ በሮሀ ሀገር በኩል በሚያልፍበት ጊዜ በውስጡ እነዚህ ቅዱሳት መነኮሳይያት ያሉበትን ገዳም አየና ‹‹ይህ ምንድነው?›› ብሎ ጠየቀ፡፡ የደናግል ገዳም እንደሆነ ሲነግሩት ወታደሮቹን ወደ ገዳሙ ገብተው ደናግሉን እንዲገድሏቸውና ንብረታቸውን እንዲዘርፉ አዘዘ፡፡ ወታደሮቹም እንደታዘዙት በማድረግ ወደ ገዳሙ በመግባት ቅድስት ሶፍያን ጨምሮ ሃምሳውንም ደናግል በሰይፍ ጨረሷቸው፡፡
ንጉሥ ዑልያኖስ ጭፍሮች ቅድስት ሶፍያንና ሁሉንም ደናግል ከገደሏቸው በኋላ ገዳሙን ዘርፈው ሊሄዱ ሲሉ ይህን ከሃዲ ንጉሥ እግዚአብሔር ተበቀለው፡፡ ያጠፋውም ዘንድ ሰማዕቱ ቅዱስ መርቆሬዎስን ላከበት፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስም በአካለ ነፍስ ሄዶ ከሃዲውን ንጉሥ ዑልያኖስ በጦር ወግቶ ገደለው፡፡ እርሱም ወደ ዘለዓለም ሥቃይ ሄደ፡፡ እነዚህም ቅዱሳት ደናግል እግዚአብሔርን በንጽሕናና በድንግልና ሲያገለግሉ ኖረው ኅዳር 10 ቀን በሰማዕትነት ዐርፈው የክብርን አክሊል ተቀዳጁ፡፡
የቅድስት ሶፍያና የቅዱሳት ደናግል ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን!
+ + +
በዚህች ዕለት ቅዱሳን አባቶቻችን ስለ ጾም ሥርዓት የአንድነት ስብሰባ አድርገው የቅዱስ ዲሜጥሮስን ቀመር አቡሻህርን በሁሉም ዘንድ እንዲጠቀሙበት በጉባኤ ወስነዋል፡፡ ይኸውም የሆነው እንዲህ ነው፡- በሐዋርያው በቅዱስ ማርቆስ መንበር 11ኛው ሊቀ ጳጳሳት የነበረው አቡነ ዮልዮስ ዕረፍቱ በደረሰ ጊዜ መልአክ ተገልጦለት ‹‹ነገ የወይን ዘለላ ይዞ ወደ አንተ የሚገባ ሰው አለ፣ ከአንተ በኋላ ሊቀ ጳጳሳት የሚሆነው እርሱ ነውና ያዘው›› አለው፡፡ በዚያችም ቀን ድሜጥሮስ ወደ አትክልቱ ቦታ ገብቶ ሳለ ያለጊዜዋ ያፈራች የወይን ዘለላ አገኘ፡፡ እርሱም ‹‹ይህችንስ የወይን ዘለላ ለሊቀ ጳጳሳቱ ሰጥቻቸው በረከት እቀበልባታለሁ›› ብሎ አሰበና ወደ አባ ዮልዮስ ዘንድ ይዞ ሄደ፡፡ በመንገድም ሳለ ሊቀ ጳጳሳቱ አባ ዮልዮስ ዐርፈው ጳጳሳቱና ሕዝቡ ሊቀብሯቸው ሲወስዷቸው አገኛቸው፡፡ እርሳቸውም ከማረፋቸው በፊት ከእርሳቸው በኋላ ማን እንደሚሾም ለሕዝቡ ምልክት ነግረዋቸው ነበር፡፡ ይኸውም ‹‹ያለጊዜዋ ያፈራች የወይን ዘለላ ይዞ የሚመጣውን ሰው በእኔ ቦታ እንድትሾሙት የእግዚአብሔር መልአክ አዞኛል›› ብለው ነግረዋቸው ስለነበር አሁን ሊቀብሩ ሲወስዷቸው ቅዱስ ድምጥሮስን ያለጊዜዋ ያፈራች የወይን ዘለላ ይዞ ሲመጣ አገኙትና ከቀብራቸው በኋላ ወስደው በሐዋርያው በቅዱስ ማርቆስ መንበር 12ኛው ሊቀ ጳጳሳት አድርገው በተወለደበት ዕለት መጋቢት 12 ቀን ሾሙት፡፡
ቅዱስ ዲሜጥሮስ አስቀድሞ በእርሻ ሥራ የሚተዳደር ምንም ያልተማረ መጻሕፍትን የማያውቅ ጨዋ ሰው ነበር፡፡ ተሾመና ቤተ ክርስቲያንን መምራት ከጀመረ በኋላ ግን እግዚአብሔር አእምሮውን ፈጽሞ ብሩህ አደረገለት የብሉይንና የሐዲስ መጻሕፍትን ሁሉ ጠንቅቆ ዐወቀ፡፡ ብዙዎቹንም ተረጎማቸው፡፡ ከዚህም በኋላ በመንፈስ ቅዱስ ገላጭነት ባሕረ ሐሳብ የተባለውን ድንቅ የዘመን መቁጠሪያ ደረሰ፡፡
በዚህ ቅዱስ ዲሜጥሮስ ቀመር መሠረት የደብረ ዘይት፣ የሆሳዕና፣ የትንሣኤና የጰራቅሊጦስ በዓላት ሁልጊዜ በየዓመቱ ከእሁድ አይወጡም፡፡ ስቅለትም ሁልጊዜ ከአርብ አይወጣም፡፡ የጌታችን የዕርገቱም በዓል ከሐሙስ አይወጣም፡፡ ቅዱሱም ቀመሩን አዘጋጅቶ ሲጨርስ ለኢየሩሳሌም፣ ለሮሜና ለአንጾኪያ አገሮች ሊቀ ጳጳሳት ለአባ አጋብዮስ፣ ለአባ ፊቅጦር፣ ለአባ መክሲሞስ ላከላቸው፡፡ እነዚህም የከበሩ ቅዱሳንና ሌሊችም ሊቃውንት በሮሜው ሊቀ ጳጳሳት በአባ ፊቅጦር አሰባሳቢነት ከተሰበሰቡ በኋላ ስለ ቅዱስ ዲሜጥሮስ ቀመር ተወያዩ፡፡ ቀመሪቱም ያማረች የሰመረች ከመንፈስ ቅዱስ የተገኘች እንደሆነች ከተለጠላቸው በኋላ እጅግ ደስ ተሰኝተው አባዝተው በመጻፍ ለሁሉም አገሮች ላኩት፡፡ ይህም ቅዱስ ዲሜጥሮስ ቀመር እስከዚህች ዕለት ጸንቶ የኖረ ነው፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም ይህ ጻድቅ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት የቀመረውን ይህን የድሜጥሮስን ቀመር በሚገባ ትጠቀምበታለቸ፡፡
የቅዱስ ድሜጥሮስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

18 Nov, 11:02


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ኅዳር 9- እጅግ የከበሩ ሃይማኖታቸው የቀና 318ቱ ቅዱሳን አበው ሊቃውንት በ325 ዓ.ም በኒቅያ አርዮስን ያወገዙበት ዕለት ነው፡፡ እነዚህም እጅግ የከበሩ ቅዱሳን አርዮስን አስተምረው ለመመለስ በኒቅያ የተሰበሰቡት መጀመሪያ መስከረም 21 ቀን ነው፡፡
ከ4ኛው መ/ክ/ዘመን ጀምሮ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በብዙ አቅጣጫ የተለያዩ ችግሮች ደርሰውባታል፡፡ ከጳውሎስ ሳምሳጢ የጀመረው የክህደት ትምህርት በተለያዩ ሰዎች በተለያየ ጊዜ ብዙ የክህደት ትምህርቶች እየተሰጡ ቤተ ክርስቲያን ስትታወክ ቆይታለች፡፡ በተለይም አርዮስ ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስን ‹‹ወልድ ፍጡር ነው›› ብሎ በመነሣቱ ቤተ ክርስቲያን ለብዙ ዓመታት እንድትታወክና እንድትበጠበጥ ምክንያት ሆኗል፡፡
ክህደትን ለመጀመሪያ ጊዜ ሰይጣን ለጳውሎስ ሳምሳጢን ነው ያስተማረው፡፡ ጳውሎስ ሳምሳጢን በገዳም ቅጠል እየበላ የሚኖር ተሐራሚ መናኝ ነበር፡፡ በጾም በጸሎት ሲኖር ሰይጣን ራሱን ሰውሮ መጥቶ ተገለጠለትና ‹‹ጸሎትህ በእግዚአብሔር ዘንድ ተሰምቶልሃል፤ ነገር ግን አምላክ ያለሩካቤ በድንግልና የተወለደ አይምሰልህ በሩካቤ ተወለደ እንጂ፤ ይህም ልጅ ደግ ሰው ሆነ፣ በ30 ዘመኑ በዮሐንስ እጅ በዮርዳኖስ ተጠመቀ፣ መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል በራ ላይ ተቀመጠ፣ ያን ጊዜም ይህ ሰው በጸጋ የሥላሴ ልጅ ሆነ›› ብሎ አስተማረው፡፡ ጳውሎስ ሳምሰጢንም ሰይጣን የነገረውን ነገር በልቡ አምኖ ለደቀ መዝሙሮቹ አስተማራቸው፡፡ የእርሱም ደቀ መዝሙሮች የክህደት ትምህርታቸውን ለተከታዮቻቸው እያወረሷትና እየተቀባበሏት እስከ አርዮስ፣ ተያስሮስ፣ ድያድርስ፣ መቅዶንዮስ፣ ንስጥሮስ፣ መርቅያንና ልዮን… አሁን እስካለንበት ዘመን ድረስ ደርሳለች፡፡ ይኸውም መልኳና ዓይነቷ ይለያይ እንጂ የሁሉም የምንፍቅናቸው መጨረሻ ምእመናንን ከክርስቶስ ኅብረት መለየትና ጌታችንንም ከክበሩ ማሳነስ ነው፡፡ ይህችም ሰይጣን በመጀመሪያ በገሃድ ለእነ ጳውሎስ ሳምሳጢን ያስተማራት የክህደት ትምህርት መልኳንና ዓይነቷን እየለዋወጠች ወደፊትም እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ትኖራለች እንጂ ጨርሳ አትጠፋም፡፡
እጅግ የከበሩ ቅዱሳን አበው ሊቃውንት አባቶቻችንም ከቅዱሳን ሐዋርያት የተረከቧትን አንዲት ርትዕት ቅድስት የሆነች ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነታችንን ለማጽናት በቃል ሊገለጽ የማይችል እጅግ ብዙ መሥዋዕትነት ከፍለዋል፡፡ በ325 ዓ.ም አርዮስ ቢነሣ አበው ሊቃውንት 318 ሆነው ኒቅያ ላይ ከየዓለሙ ሁሉ ተሰብስበው ሃይማኖትን አጸኑልን፡፡
በ381 ዓ.ም መቅዶንዮስና አቡሊናርዮስ ቢነሡ አበው ሊቃውንት 150 ሆነው ቁስጥንጥንያ ላይ ከየዓለሙ ሁሉ ተሰብስበው ሃይማኖትን አጸኑልን፡፡
ዳግመኛም በ431 ዓ.ም ንስጥሮስ ቢነሣ አበው ሊቃውንት 200 ሆነው ኤፌሶን ላይ ከየዓለሙ ሁሉ ተሰብስበው ሃይማኖትን አጸኑልን፡፡
451 ዓ.ም ላይ ግን የሮም ቫቲካን ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ለፖለቲካዊ ጥቅሟና ለነገሥታቶቿና ጳጳሳቶቿ ጥቅም ብላ ለመጀመሪያ ጊዜ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ለሁለት ከፈለች፡፡ የቅዱሳኑን የእነ ዲዮስቆሮስን ጥርስ እያወለቀች ገፍታ በግዞት በማባረር የራሷን ‹‹ጉባኤ ከለባት-የውሾች ጉባኤ›› የተሰኘ የራሷን ጉባኤ አደረገች፡፡ በዚህም ጣጣ ምክንያት ይኸው እስከዛሬ እንደ አሜባ እርባት እርስ በእርሳቸው እየተበጣጠሱ የሚከፋፈሉ ከ50 ሺህ በላይ የእምነት ድርጅቶች በክርስትና ስም በዓለም ላይ ተፈጠሩ፡፡
አርዮስ በ260 ዓ.ም አካባቢ በሰሜን አፍሪካ በሊብያ ነው የተወለደው፡፡ የትውልድ ዘሩ ግሪካዊ እንደሆነ ይነገራል፡፡ አርዮስ መሠረታዊ ትምህርቱን በሊብያ ካጠናቀቀ በኋላ ወደ እስክንድርያ በመጓዝ በእስክንድርያ ከፍተኛ ት/ቤት ትምህርት አጠናቆ እንደጨረሰ ወደ መካከለኛው ምሥራቅ ሄዶ በአንጾኪያ ከፍተኛ መንፈሳዊ ት/ቤት ገብቶ የትርጓሜ መጻሕፍትና የነገረ መለኮት ትምህርት ተምሯል፡፡ በጊዜውም ሉቅያኖስ ከተባለ መናፍቅ ዘንድ ተምሯል፡፡ አርዮስ አብዛኛውን የኑፋቄ ትምህርት ያገኘው ከሉቅያኖስና በአንጾኪያ ት/ቤት ከሚገኙ ሌሎች መናፍቃን ነው፡፡ በአንጾኪያ ትምህርቱን ከጨረሰ በኋላ ወደ እስክንድርያ ተመልሶ ኑሮውን በዚያው አደረገ፡፡
አርዮስ ብልህና ዐዋቂ አንደበተ ርቱዕና እምቅ የሆነ የግጥም ችሎታ ነበረው፡፡ በጊዜው የእስክንድርያ ፓትርያክ ከነበሩት ተፍጻሜተ ሰማዕት ቅዱስ ጴጥሮስ ዲቁና ተቀብሎ አገልግሎት ጀመረ፡፡ ለስም አጠራሩ ክብር ይግባውና ጌታችንን ‹‹ወልድ ፍጡር ነው›› ብሎ የተነሣውንና ሰይጣን በልቡ ያደረውን አርዮስን ከስህተቱ ይመለስ ዘንድ ቅዱስ ጴጥሮስ ብዙ መከረው፡፡ አርዮስ ግን ምክሩን ወደ ጎን ትቶ የክህደት ትምርቱን በሰፊው ማስተማር ቀጠለ፡፡ በዚህም ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስ ተፍጻሜተ ሰማዕት አርዮስን አውግዞ ከዲቁና ማዕረጉ ሻረው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ አርዮስን ያወገዘው ጌታችን ኢየሱስ በራእይ ተገልጦ በሰጠው ትእዛዝ መሠረት ነው፡፡ አንድ ሌሊት በራእይ ጌታችን በሕፃን ልጅ አምሳል እንደ ፀሐፍ የሚያበራ ረጅም ልብስ(ቀሚስ) ለብሶ ነበር፡፡ ልብሱ ግን ለሁለት የተቀደደ ሆኖ ያየዋል፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም ‹‹ልብስህን ማን ቀደደብህ?›› ብሎ ሲጠይቀው ጌታችንም ‹‹አርዮስ ልብሴን ቀደደብኝ›› ይላዋል፡፡ በዚያኑ ቀን ሁለቱን ተማሪዎቹን አኪላስንና እለእስክንድሮስን ጠርቶ የተገለጠለትን ራእይ በመግለጥ አርዮስን እንዳይቀበሉት ከእርሱም ጋር ኅብረት እንዳይኖራቸው አዘዛቸው፡፡
አርዮስ በክህደቱ ቅዱስ ጴጥሮስ ካወገዘው በኋላ አኪላስንና እለእስክንድሮስን ሄደው ጴጥሮስን ከውግዘቱ እንዲፈታው ለመናቸው፡፡ እነርሱም ሄደው ለቅዱስ ጴጥሮስ ቢነግሩለት እርሱ ግን ከውግዘት ላይ ውግዘት ጨመረበት፡፡ እንዲህም አላቸው፡- ‹‹ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ የተቀደደ ልብስ ለብሶ ተገለጠልኝ፤ ‹ልብሴን አርዮስ ቀደዳት› አለኝ፡፡ ይህም የባሕርይ አንድነቴን ለያት ማለት ነው፤ ውግዘቱንም እንድጨምርበት እርሱ አዘዘኝ›› እያለ ጌታችን ተገልጦ የነገረውን ነገር ሁሉ አስረዳቸው፡፡ ተፍጻሜተ ሰማዕት ቅዱስ ጴጥሮስም ይህን ሲነግራቸው በሰማዕትነት የሚሞትበት ጊዜው እንደደረሰ ያውቅ ነበር፡፡ አኪላስንና እለእስክንድሮስንም በእርሱ ፈንታ መጀመሪያ አኪላስ ቀጥሎ እለእስክንድሮስ እንደሚሾሙ ከነገራቸው በኋላ አርዮስን ከውግዘቱ እንዳይፈቱት አስጠነቀቃቸው፡፡
በዚያም ወራት የንጉሡን አማልክት እንዳያመልኩ በሁሉ ቦታ ቅዱስ ጴጥሮስ እያስተማረ መሆኑን ከሃዲው ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ሰማ፡፡ ወታደሮቹንም ልኮ አስሮ አስመጣው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም ሕዝቡ ሳያውቅ ንጉሡ በምሥጢር ሊገድለው መሆኑን ስላወቀ ነፍሱን አሳልፎ ሊሰጥ ወደደ፡፡ ሕዝቡንም በቀናች ሃይማኖት እንዲጸኑ ካስተማራቸው በኋላ አጽናንቶ አሰናበታቸው፡፡ አርዮስም ቅዱስ ጴጥሮስ በከሃዲው ንጉሡ ትእዛዝ እንደሚሞት ካወቀ በኋላ ከውግዘቱ እንዲፈታው አኪላስንና እለ እስክንድሮስን አማላጅ አድርጎ ድጋሚ ላካቸው፡፡ እነርሱም አርዮስን ከውግዘቱ እንዲፈታው ሄደው ቅዱስ ጴጥሮስ ለመኑት ነገር ግን እርሱ አሁንም ከውግዘቱ ላይ ሌላ ውግዘት ጨመረበት፡፡ አኪላስንና እለእስክንድሮስንም ‹‹ከአርዮስ ተጠበቁ፣ በክህነት ሥራም አትሳተፉ እርሱ ለክብር ባለቤት ለክርስቶስ ጠላቱ ነውና›› አላቸው፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

18 Nov, 11:02


ተፍጻሜተ ሰማዕት ቅዱስ ጴጥሮስም በዲዮቅልጥያኖስ ሰማዕት ሆኖ ካረፈ በኋላ አኪላስ በእርሱ ፈንታ በ303 ዓ.ም ሊቀ ጳጳስ ሆኖ ተሾመ፡፡ አርዮስም ወደ አኪላስ ቀርቦ ከውግዘቱ እንዲፈታው በከንቱ ውዳሴ አባበለው፡፡ አኪላስም የቅዱስ ጴጥሮስን አደራ በመዘንጋትና ለአርዮስም ከንቱ ውዳሴ ተሸንፎ አርዮስን ከውግዘቱ ፈታው፡፡ ደግሞም ቅስና ሾመው፡፡ ነገር ግን አኪላስም ብዙ ሳይቆይ በ6 ወሩ ተቀሰፈና ሞተ፡፡
ቀጥሎም እለእስክንድሮስ ፓትርያክ ሆኖ ተሾመ፡፡ አርዮስንም ከነጓደኞቹ አውግዞ አሳደደው፡፡ ብዙዎችም ወደ አባ እለእስክንድሮስ መጥተው አርዮስን ከውግዘቱ እንዲፈታው ቢለምኑትም እርሱ ግን ከውግዘቱ ላይ ውግዘት እንዲጨምርበት እንጂ እንዳይፈታው አባቱ ቅዱስ ጴጥሮስ እንዳዘዛቸው ነገራቸው፡፡ በዚህም ጊዜ አርዮስ ክህደቱን ከማሰራጨት አልታቀበም ነበር፡፡ እንደውም ሕዝቡ ትምህርቱን በቀላሉ እንዲቀበሉ የክህደት ትምህርቱን በግጥምና ንባብ እያዘጋጀ ማሰራጨት ቀጠለ፡፡ ሕዝቡ ግጥም ስለሚወድ ትምህርቱን ወደ መቀበል ደርሶ ነበር፡፡ የዚህ ጊዜ እለእስክንድሮስ እየተዘዋወረ ከአርዮስ ኑፋቄ እንዲጠበቁ በትጋት ያስተምር ነበር፡፡
በ320 ዓ.ም አንድ መቶ የሚሆኑ የሊቢያና የእስክንድርያ ኤጲስቆጶሳትን እለእስክንድሮስ ሰብስቦ የአርዮስን ክህደት ገለጸላቸው፡፡ ጉባኤውም ተመክሮ ተዘክሮ አልመለስ ያለውን አርዮስን በአንድ ልብ አውግዞ ከቤተ ክርስቲያን አንድነት ለየው፡፡ ከዚህም በኋላ አርዮስ ከጓደኞቹ አንዱ ወደ ነበረው ወደ የኒቆሜዲያ ኤጲስቆጶስ አውሳብዮስ ዘንድ በመሄድ ‹‹እለእስክንድሮስ በከንቱ አወገዘኝ›› ብሎ ነገር ጨምሮ ነገረው፡፡ አውሳቢዮስም አይዞህ ብሎ ተቀብሎ በሀገረ ስብከቱ የሚገኙትን ኤጲስ ቆጶሳትን ሰብስቦ በአርዮስ ጉዳይ ሲኖዶስ አደረገ፡፡ የአውሳቢዮስም ሲኖዶስ አርዮስ በግፍ መባረሩን አምኖ ከውግዘቱ ፈቱት፡፡
አርዮስም በ322 ዓ.ም ወደ እስክንድያ ተመልሶ ‹‹እለእስክንድሮስ ቢያወግዘኝ ተፈትቼ መጣሁ›› እያለ የበፊት የክህደት ትምህርቱን በስፋት ማስተማር ቀጠለ፡፡ በዚህም ጊዜ ቤተ ክርስቲያን ታመሰችና ጉዳዩ ጻድቁ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ዘንድ ደረሰ፡፡ በዚህም ጊዜ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ የእስፓኙን ጳጳስ ሆስዮስን ወደ እስክንድርያ ላከው፡፡ ሆስዮስንም ደርሶ ሲመለስ ‹‹ጉዳዩ የሃይማኖት ችግር እንጂ አስተዳደራዊ ስላልሆነ በጉባኤ መታየት አለበት›› ብሎ ለንጉሡ አማከረው፡፡ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስም በነገሠ በሃያ ዓመቱ በ325ዓ.ም ጉባኤ እንዲደረግ አዘዘ፡፡ በዚህም በኒቅያ 318 የከበሩ ሊቃውንት አባቶች ተሰበሰቡ፡፡
እነዚህ 318ቱ ቅዱሳን አበው ሊቃውንት እጅግ የከበሩ ናቸው፡፡ ቅዱስ እለእስክንድሮስ የጉባኤው ሊቀ መንበር ሲሆን ሊቁ ቅዱስ አትናቴዎስ ደግሞ ጸሐፊ ሆነ፡፡ እንደነ አቡነ ቶማስ ዘመርዓስ ያሉት ቅዱሳን በከሃድያን ነገሥታት 22 ዓመት በጨለማ ቤት ታሥረው እጅና እግሮቻቸውን በየተራ ተቆራርጠው ከእሥር ቤት ከወጡ በኋላ በቅርጫት ውስጥ ተደርገው በአህያ ላይ ተጭነው ነበር ወደ ጉባኤ ኒቂያ የሄዱት፡፡
የከሃዲው ንጉሥ የዲዮቅልጥያኖስ መኮንኖች አቡነ ቶማስን ቶሎ ብለው እንዲሞቱ ሳይሆን በሥቃይ ሆነው እንዲቆዩ በማድረግ ለ22 ዓመታት በጨለማ ውስጥ እያሰሩ አሠቃይተዋቸዋል፡፡ ከሃዲያኑም በየዓመቱ ወደ አሥር ቤቱ እየገቡ አንድ አካላቸውን ይቆርጡ ነበርና የአባታችንን እጅና እግሮቻቸውን በየተራ ቆራረጧቸው፡፡ አፍንጫቸውን፣ ከንፈሮቻቸውን፣ ጆሮዎቻቸውን ሁሉ በየተራ እየቆረጡ ለ22 ዓመትታት ጣዖቶቻቸውን ሲያጥኑበት ኖረዋል፡፡ አንዲት ደግ ክርስቲያን ሴት ግን አቡነ ቶማስ የተጣሉበትን ጉድጓድ አይታ ስለነበር በድብቅ ሌሊት እየሄደች ትመግባቸው ነበር፡፡ ደገኛውና ጻድቁ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ በነገሠ ጊዜ ይህች ሴት ሄዳ ስለ አቡነ ቶማስ ነግረችውና አባታችንን ከተጣሉበት ጉድጉድ አወጣቸው፡፡ ቆስጠንጢኖስም በአርዮስ ክህደት ምክንያት እጅግ የከበሩ 318 ቅዱሳን ሊቃውንትን በኒቅያ አገር እንዲሰበሰቡ ሲያደርግ አንዱ አቡነ ቶማስ ነበሩ፡፡ ወደ ጉባዔውም ሲሄዱ ደቀ መዛሙርቶቻቸው በቅርጫት አድርገው በአህያ ጭነው ወደ ጉባኤ ኒቂያ ይዘዋቸው ሄደዋል፡፡ በመንገድም ሳሉ ዐላዊያኑ አግኝተዋቸው አህዮቻቸውን ሌሊት ራስ ራሳቸውን ቆርጠው ጣሉባቸው፡፡ አቡነ ቶማስም ራሳቸው የተቆረጡትን አህዮች አምጡልኝ ብለው የጥቁሩን አህያ ራስ ከነጩ፣ የነጩን አህያ ራስ ከጥቁሩ ገጥመው ቢባርኳቸው ሁሉም አህዮች ከሞት ተነሥተዋል፡፡
አቡነ ቶማስ ከኒቅያ ጉባዔ ሲደርሱ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ጽድቃቸውን ዐውቆ ‹‹አባቴ በረከትዎ ትድረሰኝ›› በማለት በዐላዊያኑ የተቆራረጠ አካላቸውን ዳሶ ተባርኳል፡፡ አቡነ ቶማስ ዘመርዓስም ከሌሎቹ ቅዱሳን ሊቃውንት ጋር ሆነው በጋራ አርዮስን መክረውና አስተምረው እምቢ ቢላቸው አውግዘውት ወደ ሀገራቸው እንደተመለሱ ወዲያው በሰላም ዐርፈዋል፡፡
የመርዓሱን አቡነ ቶማስን ብቻ ላሳያ ያህል ብቻ አነሳን እንጂ 318ቱም የኒቅያ ጉባኤ ተሳታፊ የሆኑ አበው ሊቃውንት እጅግ የከበሩ ቅዱሳን ናቸው፡፡ ‹‹እጅግ የከበሩ ቅዱሳን›› የሚለው ቃል ራሱ የማይገልጻቸው ሁሉም ለየራሳቸው እጅግ ድንቅ የሆነ ገድል ያላቸው ናቸው፡፡ እነዚህም ቅዱሳን አርዮስን ተከራክረው ክህደቱን ግልጽ አደረጉበት፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከባሕርይ አባቱ ከአብ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በመለኮቱ ትክክል መሆኑን አስረዱት፡፡ በተለይም ሊቁ ቅዱስ አትናቴዎስ የአንበሳውን ድርሻ ይይዛል፡፡ ቅዱሳን አባቶቻችንም በቃላቸው ትምህርት እያስተማሩት በእጆቻቸው ተአምራት አድርገው እያሳዩት ቢያስተምሩትም ሰይጣን አንዴ አስቶታልና አርዮስ ከክህደቱ አልመለስ ቢላቸው አውግዘው ለዩት፡፡ በአንዲትም ቃል ሆነው ዛሬ ላይ የጸሎታችን መጀመሪያ የሆነውን ‹‹ጸሎተ ሃይማኖትን›› ደነገጉልን፡፡
የአርዮስ ፍጹም የሆኑ ክህደቶቹ እነዚህ ናቸው፡- ለስም አጠራሩ ክብርና ምስጋና ይግባውና ‹‹ክርስቶስ ዓለም ሳይፈጠር አልነበረም›› አለ፡፡ ዳግመኛ አርዮስ ‹‹ባሕርዩ ከአብ ያነሰ ነው›› ፣ ‹‹የተፈጠረ እንጂ ከአብ የተወለደ አይደለም›› እና ‹‹በመጀመሪያ ዓለሙን ይፈጥርበት ዘንድ እግዚአብሔር እርሱን ፈጠረው፣ እርሱም ዓለምን ፈጠረ›› የሚሉ ከሰይጣን የተገኙ ፍጹም ክህደቶች ናቸው፡፡
እነዚህ የአርዮስ አስተሳሰቦች ዛሬም ድረስ መልካቸውንና ይዘታቸውን ለውጠው በእኛው ቤተ ክርስቲያን ላይ በግልጽ ሲነገሩ መቆየታቸው እጅግ አስገራሚ ነው በእውነት!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

16 Nov, 17:02


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ኅዳር 8-አርባዕቱ እንስሳ (ኪሩቤል) የሥሉስ ቅዱስን መንበር ለመሸከም የተሾሙበት ዕለት ነው፡፡
+ ሊቀ መላእክት ቅዱስ አፍኒን የተሾመበት ዓመታዊ በዓሉ ነው፡፡
+ የአረማዊ መኮንን ልጅ የነበረው ቅዱስ ቅፍሮንያ ዕረፍቱ ነው፡፡ ይኸውም ቅዱስ አስቀድሞ የአረማዊ መኮንን ልጅ የነበረ ነው፡፡ እርሱም ልጅ ሆኖ ሳለ ከአባ ጳኩሚስ ገዳም ወደ አገሪቱ የመጣው ስሙ መርቆሬዎስ የሚባል መነኩሴ ይህ የአረማዊን ልጅ ደገኛ ክርስቲያን እንደሚሆን ትንቢት ተናገረ፡፡
ከጥቂት ወራትም በኋላ ቅፍሮንያ ገዳማትን ሊያጠፋ የአባቱን ሠራዊት ሰብበስቦ ወደ ግብፅ ዘመተ፡፡ ወደ አባ ጳኩሚስ ገዳም በደረሰ ጊዜ ግን የሆነው ሌላ ነው፡፡ የዚህም ቅዱስ ጥሪው የሐዋርያው የቅዱስ ጳውሎስን ጥሪ ይመስላል፡፡ ቅፍሮንያ ገዳሙን ለማጥፋት መጥቶ ሳለ ገና የገዳሙን ድንበር እንደረገጠ ልቡ ራደ፣ አእምሮው ታወከ፡፡ ዐይነ ልቡናውም በርቶላት አበ ምኔቱን ባያቸው ጊዜ ብቻቸውን ገለል አድርጎ እንዲያመነኩሱት ጠየቃቸው፡፡ እርሳቸውም ስለ እርሱ አስቀድመው በመንፈስ ዐውቀው ነበርና በጄ አሉት፡፡ ቅፍሮንያም ሠራዊቱን ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ነገራቸውና እርሱ በዚያው መንኩሶ ቀረ፡፡ ከዚህም በኋላ የምንኩስናን ሥራ ሌት ተቀን በመሥራት በመንፈሳዊ ተጋድሎው በረታ፡፡ ጾም ጸሎትን በማብዛት መጋደል እንደጀመረ ሰይጣን በፈተና ከሕይወት መንገድ ሊያስወጣው ነገረ ሠሪ አስነሣበት፡፡ በዚህም ምክንያት የአገሪቱ መኳንንት ሁሉ ‹‹‹አገራችን ያጠፋ የመኮንን ልጅ ከዚህ አለ›› ብለው ቅፍሮንያን ወስደው ሊገድሉ መጥተው ገዳሙን ወረሩት፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር ቅዱስ ቅፍሮንያን ሠወረባቸውና ፈጽመው ሊያገኙት አልቻሉም፡፡ እርሱንም ማግኘት ባልቻሉ ጊዜ ራሱን ነገረ ሠሪውን ገድለውት ተመለሱ፡፡
ቅዱስ ቅፍሮንያም በገድል ላይ ገድል እየጨመረ ትሩፋትን አበዛ፡፡ በየሰባት ቀንም ይጾም ጀመር፡፡ የሚመገበውን መራራ የአደንጓሬ ፍሬን ብቻ ሆነ፡፡ እርሱ በነበረበትም ወራት የምድር አውሬ እንስሶቻቸውን እየገደለ በገዳሙ ላይ ታላቅ ጥፋት አደረሰ፡፡ አባ ቅፍሮንያም ወደዚህ ክፉ አውሬ መጥቶ እንደበግ ይዞ አሠረው፡፡ ክፉውም አውሬ እንደታሠረ 10 ዓመት ኖሮ ሞተ፡፡ ከዚህም በኋላ ቅዱስ ቅፍሮንያ የታዘዘ መልአክ እየመራው ኢየሩሳሌም በአንዲት ቀን አደረሰው፡፡ በዚያም ብዙ ምሥጢርን እግዚአብሔር ገለጠለት፡፡ ከከበሩ ቦታዎችም ተባርኮ ወደ በዓቱ ተመልሶ ተጋድሎውን ፈጽሞ በሰላም ዐረፈ፡፡
ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!
+ + +
አርባዕቱ እንስሳ (ኪሩቤል)፡- እነዚህም የእግዚብሔርን መንበሩን የሚሸከሙ የእግዚአብሔር ሠረገላዎቹ ናቸው፡፡ ስለ እነርሱም ወንጌል የጻፈ ቅዱስ ዮሐንስ እንዲህ ሲል ጻፈ፡- ‹‹በዚያ ዙፋን ፊት በረድ የሚመስል ባሕር አለ፣ በዙፋኑም ዙርያ አራት እንስሶች አሉ በፊትም በኋላም ዐይንን ተመሉ ናቸው፡፡ የፊተኛው አንበሳ ይመስላል፣ ሁለተኛውም ላም ይመስላል፣ ሦስተኛውም የሰው መልክ ይመስላል፣ አራተኛውም ሚበር አሞራ ይመስላል፡፡›› እነዚህም የአራቱ እንስሶች እንያንዳንዱ ክንፋቸው ስድስት ስድስት ነው፣ ሁለተንተናቸውም ዐይኖችን የተመሉ ናቸው፡፡ በመዓልትና በሌሊት ዕረፍት የላቸውምና ‹‹የነበረ የሚኖር የአማልክት አምላክ እግዚአብሔር ጽኑዕ ክቡር ልዩ ነው›› እያሉ ያለመሰግናሉ፡፡ ራእ 4፡7፡፡
ዳግመኛም ነቢዩ ኢሳይያስ በራእይ ያየውን ሲናገር ስለ እነርሱ እንዲህ አለ፡- ‹‹ንጉሡ ዖዝያን በሞተበት ዓመት እግዚአብሔርን በረጅምና ከፍ ባለ ዙፋን ላይ ተቀምጦ አየሁት፤ የልብሱም ዘርፍ መቅደሱን ሞልቶት ነበር፡፡ ሱራፌልም ከእርሱ በላይ ቆመው ነበር፥ ለእያንዳንዱም ስድስት ክንፍ ነበረው፤ በሁለት ክንፍ ፊቱን ይሸፍን ነበር፥ በሁለቱም ክንፍ እግሮቹን ይሸፍን ነበር፣ በሁለቱም ክንፍ ይበር ነበር፡፡ አንዱም ለአንዱ ‹ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ምድር ሁሉ ከክብሩ ተሞልታለች እያለ ይጮኽ ነበር፡፡ የመድረኩም መሠረት ከጭዋኺው ድምፅ የተነሣ ተናወጠ፣ ቤቱንም ጢስ ሞላበት፡፡ ኢሳ 61-4፡፡
ነቢዩ ዳዊትም ‹‹እግዚአብሔር በኪሩቤል ላይ ተቀምጦ በረረ›› አለ፡፡ ሁለተኛም በኪሩቤል ላይ የተቀመጠ እርሱ ምድርን አናወጻት›› አለ፡፡ ሕዝቅኤልም ‹‹ከወደ ሰሜን እነሆ ጥቅል ነፋስ ሲመጣ አየሁ፣ ታላቅ ደመናም አለ፣ በዙሪያውም ብርሃን አለ፣ ከእርሱም እሳት ቦግ ብሎ ይወጣል፡፡ በደመናውም መካከል ባለ በእሳቱ ውስጥ እንደ አራት እራስ አሞራ መልክ የሚመስል አለ፣ በመካከሉም እንደ አራቱ ኪሩቤል መልክ ያለ አለ፡፡››
ወንጌላዊ ዮሐንስም ዳግመኛ እንዲህ አለ፡- ‹‹በዙፋኑ ዙሪያ የብዙ መላእክትን ድምፅ ሰማሁ፣ የእንስሶቹንም የእነዚያ አለቆችንም ቃል ሰማሁ ቁጥራቸውም እልፍ አለቆች ያሏቸው ብዙ የብዙ ብዙ ነው፡፡ ለዚያ ለተገደለው በግ ኃይል ባለጸግነትን ጥበብን ጽናትን መንግሥትን ክብርን ጌትነትን ምስጋናን ገንዘብ ሊያደርግ ይገባዋል›› ብለው በታላቅ ቃል ተናገሩ፡፡ ዳግመኛም ‹‹በሰማይና በምድር ከምድርም በታች በባሕር ውስጥ የተፈጠረው ፍጥረት ሁሉ ጌትነት ክብር ኃይል በረከት በዙፋኑ ለተቀመጠው ለእርሱ ለበጉም ለዘለዓለሙ ይባዋል፡፡›› እነዚህም አራቱ እንስሶች አሜን ይላሉ፣ እነኚያም አለቆች ይሰግዳሉ፡፡
ስለ እርባዕቱ እንስሳ ስለ ልዕልናቸውና ስለ ክብራቸው ከብሉይና ከሐዲስ ብዙ መጻሕፍት መስክረዋል፡፡ መሐሪ ይቅር ባይ ልዑል እግዚአብሔርም ስለሁሉ ፍጥረት ይለምኑት ዘንድ ቀራቢዎቹ አደረጋቸው፡፡ ገጸ ሰብእ ስለ ሰው ፍጥረት ይለምናል፣ ገጸ አንበሳ ስለ አራዊት ይለምናል፣ ገጸ ላሕም ስለ እንስሳት ይልምናል፣ ገጸ ንስርም ስለ አእዋፍ ይለምናል፡፡ ከሰማይ ሠራዊት ሁሉ እነርሱ በእግዚአብሔር ዘንድ በባለሟልነት እጅግ ቀረቡ ናቸውና፡፡ ስለዚህም በዓለሙ ሁሉ በስማቸው አብያተ ክርስቲያናት እንዲታነጹ በዚህችም ቀን መታሰቢያቸው እንዲደረግ አባቶች አዘዙ፡፡
+ + +
ዳግመኛም በዚህች ዕለት ሊቀ መላእክት ቅዱስ አፍኒን የተሾመበት ዓመታዊ በዓሉ ነው፡፡ ይህም ሱራፌልና ከኪሩቤል ጋር የልዑልን የጌትነቱን ዙፋን የሚጠብቅ ነው፡፡ ስለዚህም ክቡር መልአክ ሄኖክ እንዲህ አለ፡- ‹‹…ያንን ቤት ሱራፌልና አፍኒን ዙሪያውን እየዞሩ ይጠብቁታል፣ እነርሱም የልዑልን የጌትነቱን ዙፋን ሲጠብቁ የማያንቀላፉ ናቸው፡፡›› ቅዱስ ዮሐንስ በራእዩ ‹‹በእግዚአብሔር ፊት የሚቆሙ 7 መላእክትን አየሁ›› (ራዕ 8፡2) እንዳለ ሊቃነ መላእክት በቁጥር 7 ናቸው፡፡ እነርሱም፡- ቅዱስ ሚካኤል፣ ቅዱስ ገብርኤል፣ ቅዱስ ሩፋኤል፣ ቅዱስ ራጉኤል፣ ቅዱስ ዑራኤል፣ ቅዱስ ፋኑኤልና ኅዳር 8 ቀን የተሾመበትን ዓመታዊ በዓሉን የምናከብርለት ቅዱስ አፍኒን ናቸው፡፡

የሥሉስ ቅዱስን መንበር ለመሸከም የተሾሙ የአርባዕቱ እንስሳ (ኪሩቤል) እና የሊቀ መላእክት የቅዱስ አፍኒን ጥበቃና ምልጃ አይለየን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

15 Nov, 18:52


ልጅን እርስ በእርስ እንዲተያዩ አድርጎ በሁለት መስቀሎች ላይ እርቃናቸውን ሰቀላቸው፡፡ በዚያን ጊዜም ደመና መጥታ ሸፈነቻቸው፡፡ በዚህም ጊዜ ብዙዎች በጌታችን አመኑ፡፡
ዳግመኛም ንጉሡ ቅድስት ዘኖብያንና ልጇን ቅዱስ ዘኖቢስን በብረት ወንበሮች ላይ አስሮ በማስቀመጥ ከሥር በሚነድ እሳት አቃጠላቸው፡፡ ጌታችንም ከዚህ ሥቃይ አዳናቸው፡፡ በወንበሩም ላይ ሆነው በእሳት እየተቃጠሉ ሳለ ሕዝቡን ያስተምሩ ጀመር፡፡ ንጉሡም ይህንን ባየጊዜ እጅግ ተቆጥቶ ቁመቱና ጎኑ ሃያ ሃያ ክንድ የሆነ ጉድጓድ ቆፍረው በውስጡም እሳትን እንዲያነዱበትና ቅዱሳኑን ከዚያ እንጨምሯቸው አደረገ፡፡ ነገር ግን አሁንም ቅድስት ዘኖብያንና ልጇን ቅዱስ ዘኖቢስ ወደ እግዚአብሔር በጸለዩ ጊዜ እሳቱ ፈጥኖ ጠፋ፡፡
ንጉሡም ከዚህ በኋላ ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ በሰይፍ አንገታቸውን ቆርጠው እንገድሏቸውና እስከ ነገ ድረስ በድናቸውን ጠብቀው በእሳት እንዲያቃጥሉአቸው በነፋስም ውስጥ እንዲበትኑአቸው አዘዘ፡፡ ቅዱሳኑንም በገደሏቸው ጊዜ ነጎድጓድ መብረቅ ንውጽውጽታ ሆነ፣ ዝናብም ዘነበ፡፡ በዚህም ታላቅ ንውጽውጽታ ምክንያት 54 ሰዎች ሞቱ፡፡ በሌሊትም ምእመናን መጥተው የቅሱሳኑን ሥጋ በሥውር ወስደው ቀበሯቸው፡፡ በማግሥቱም ንጉሡ በድናቸውን በፈለገ ጊዜ የሆነውን ሁሉ ተረዳ፡፡ የሆነውን ሁሉ ባስተዋለ ጊዜ ዐይነ ልቡናው በራለትና በጌታችን አምኖ ንስሓ ገብቶ ተጠመቀ፡፡
+ + +
ሰማዕቱ አባ ናህርው፡- ይኸውም ቅዱስ ከግብጽ አገር ከፍዩም መንደር የተገኘ ታላቅ ሰማዕት ነው፡፡ ይኸውም ቅዱስ ፈሪሃ እግዚአብሔር በእጅጉ ያደረበት ደገኛ ክርስቲያን ነው፡፡ በእስክንድርያ አገር በከሃዲያን መኳንንት የሚሠቃዩትንና የሚሞቱትን የክርስቲያኖቹን ዜና በሰማ ጊዜ ለስም አጠራሩ ክብር ምስጋና ይሁንና ስለ ጌታችን ስለ ስሙ ሰማዕት ይሆን ዘንድ ተመኘ፣ የሰማዕትነት ክብርንም ይቀዳጅ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፡፡ እግዚአብሔር ጸሎቱን ሰማውና በራእይ ተገልጦለት ‹‹ወደ አንጾኪያ አገር ሂድ በዚያ በሰማዕትነት ትሞት ዘንድ አለህ›› አለው፡፡
አባ ናህርው ከዚህ በኋላ ወደዚያ እንዴት መድረስ እችላለሁ ብሎ ሲያስብ እግዚአብሔር ቅዱስ ሚካኤልን ላከለትና መልአኩ ይህንን ቅዱስ በክንፎቹ ተሸክሞ ወደ አንጾኪያ አገር አደረሰው፡፡ አንጾኪያ አገር ላይ ያለው ንጉሥ ደግሞ እጅግ ጨካኝ የሆነው የክርስቲያኖችን ደም በዓለም ዙሪያ ያፈስ የነበረው ዲዮቅልጥያኖስ ነበር፡፡ እናም አባ ናህርው በከሃዲው ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ፊት በደረሰ ጊዜ የእግዚአብሔርን ክብር መሰከረ፡፡ ንጉሡም ስሙንና አገሩን ጠየቀው፡፡ እርሱም ከግብጽ አገር እንደሆነ አስረዳው፡፡ ንጉሡም ቃሉን ከሰማ በኋላ ለጣዖታቱ ቢሠዋለት ብዙ ገንዘብና ሥልጣን እንደሚሰጠው ቃል ገባለት፡፡ ነገር ግን አባ ናህርው በጌታችን ታመነ፡፡ ንጉሡም ‹‹ትእዛዜን አልሰማም ካልክ አሠቃይቼ ለሞት እዳርግሃለሁ›› እያለ በተደጋጋሚ ቢናገረውም አባ ናህርው ግን ከሥቃዩ የተነሣ አልፈራም፡፡
ከዚህም በኋላ ንጉሡ ቅዱስ አባ ናህርውን በብዙ ዓይነት ሥቃዮች እንዲያሠቃዩት አደረገው፡፡ በእሳት ውስጥ ቢጨምሩት ረድኤተ እግዚአብሔር ጠብቆት ምንም ሳይቃጠል ቀረ፡፡ ዳግመኛም ለተራቡ አንበሶች ቢሰጡት አንበሶቹም ምንም ሳይነኩት ቀሩ፡፡ በሌላም ጊዜ በትልቅ ወጪት አድርገው በእሳት ቀቀሉት ነገር ግን አሁንም ምንም አልሆነም፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስ አባ ናህርውን ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ በዚህች ዕለት አንገቱን በሰይፍ አስቆረጠውና የቅዱስ አባታችን የሰማዕትነት ፍጻሜአቸው ሆነ፡፡
ከዚህም በኋላ የከሃዲውን ንጉሡ የዲዮቅልጥያኖስን ፍጻሜ ማየቱ ተገቢ ነው፡፡ ይህንን ከሃዲ ንጉሥ የልዳው ፀሐይ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ በተአምራት እንደገደለውና ፈጽሞ እንዳጠፋው በቅዱሱ ገድሉ ላይ ተጽፏል፡፡ እጅግ የከበሩ ታላላቆቹን ሰማዕታት እነ ቅዱስ ፋሲለደስንና አራቱን ልጆቹን አውሳብዮስን፣ መቃርስንና ሁለቱን ሴቶች ልጆቹን፣ ቅዱስ አባድርና እኅቱ ቅድስት ኢራኒን፣ ቅዱስ ፊቅጦርን፣ ምሥራዊ ቅዱስ ቴዎድሮስ፣ ቅዱስ ገላውዴዮስን፣ የንጉሡን ልጅ ቅዱስ ዮስጦስን፣ ቅዱስ አቦሊንና ቅድስት ታውክልያን… እነዚህንና ሌሎቹንም እጅግ የከበሩ ቅዱሳን ሰማዕታት በግፍ አሠቃይቶ የገደለው ከሃዲው ዲዮቅልጥያኖስ በዓለም ላይ እንደ እርሱ ያለ ቤተ ክርስቲያንን ያጠፋ የለም፡፡ በዓለም ላይ ከ470,000 ሺህ በላይ ሰማዕታትን በግፍ እንዳስገደለ በተለያዩ መዛግብት ላይ ተጠቅሷል፡፡
ኅዳር 7 ቀን የልዳው ፀሐይ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ በተአምራት ከሃዲውን ዲዮቅልጥያኖስን በክፉ አሟሟት ለገደለበት ተአምሩ መታሰቢያ በዓሉ ነውና አንድም ደግሞ ቅዳሴ ቤቱ ስለሆነ ይህንኑ ተአምሩን ቀጥሎ እንመለከታለን፡- በዚህች ዕለት የልዳው ፀሐይ የሊቀ ሰማዕታት የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያኑ የከበረችበት ዕለት ነው፡፡ ዳግመኛም ጌታችን በውስጧ ላደረገው ድንቅ ተአምር መታሰቢያ ሆነ፡፡ ይኸውም የሆነው እንዲህ ነው፡- በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ድንቅ ድንቅ ተአምራት እየተፈጸሙ እንደሆነ ከሃዲው ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ በሰማ ጊዜ ይህችን ቤተ ክርስቲያን ሊያፈርሳት ወደደ፡፡ ሄዶም ፈጽሞ እንዲያፈርሳት ስሙ አውህዮስ የተባለ መኮንኑንም ከብዙ ሠራዊት ጋር ትእዛዝ ሰጥቶ ላከው፡፡ ያም መኮንን ከቦታው ልዳ በደረሰ ጊዜ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ገብቶ በሚያበራ ብርጭቆ ቀንዲል ተተክሎ መብራት እየበራ በፊቱም የሰማዕቱን የቅዱስ ጊዮርጊስን ሥዕል በተመለከተ ጊዜ ተቆጣና ፈጥኖ መስቀለኛውን ቀንዲል ሰበረው፡፡ ነገር ግን ወዲያው የመስተዋቱ ቀንዲል ስባሪው በራሱ ላይ ተሰካበትና አናቱ ቆስሎ በሰበሰ፣ በትልም ተወረረ፡፡ ተዘርሮ በወደቀ ጊዜ ጭፍሮቹም እጅግ ደንግጠውና በፍርሃት ተውጠው ከቤተ ክርስቲያን ተሸክመው አውጥተው እስከ ባሕሩ ዳርቻ ድረስ በቃሬዛ ወሰዱት፡፡ በመርከብም ውስጥ ሳለ ተሠቃይቶ ክፉ አሟሟት ሞተና ወስደው ከባሕር ውስጥ ጣሉት፡፡ ወደ ሀገራቸውም አፍረው ተመለሱ፡፡
አንጾኪያ ደርሰው የሆነውን ሁሉ ለንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ነገሩት፡፡ እርሱም ይህንን በሰማ ጊዜ እጅግ ተቆጥቶ ከቀድሞው የበዛ ሠራዊት ይዞ የሰማዕቱን ቤተ ክርስቲያን ፈጽሞ ለማጥፋት እርሱ ራሱ ተነሥቶ ልዳ ወደምትባለው አገር ሄደ፡፡ ከቤተ ክርስቲያኒቱም ውስጥ ገባና በውስጣዊ ክፍል በመካከሉ ላይ ዙፋኑን ዘርግቶ ተቀመጠ፡፡ እግዚአብሔርም የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልንና ቅዱስ ጊዮርጊስን ከሰማይ ወደዚህ ከሃዲ ላካቸው፡፡ እነርሱም ሄደው የዲዮቅልጥያኖስን ዙፋን በገለበጡት ጊዜ በግራና በቀኝ የነበሩት የወርቅ አባባ ጌጦች ከግራና ከቀኝ ተገናኝተው በሁለቱም ዐይኖቹ ተሰኩና ዐይኖቹን አጠፉት፡፡ በዚህም ሠራዊቱ ሁሉ አፍረው ጥለውት እየሸሹ ወጡ፡፡ ከእርሱ ጋር አንድም ሰው እንኳን አልተገኘም ነበር፡፡ መንግሥቱም አለፈች፡፡ ከዚህም በኋላ ዲዮቅልጥያኖስ በታላቅ ሃፍረት ተመልቶ በእያንዳንዱ ምእመን ደጃፍ እየቆመ ምጽዋትን እስኪለምን ድረስ እጅግ የተዋረደ ሆነ፡፡
ከዕለታትም በአንደኛው ቀን ያንን ሁሉ ክፉ ሥራ ሲያሠራውና በዓለም ላይ ከ500 ሺህ በላይ ሰማዕታትን በግፍ ሲያስገድለው የኖረው ሰይጣን በገሃድ ለዲዮቅልጥያኖስ ተገለጠለትና ‹‹ወዳጄ ሆይ እንደምን አለህ?›› አለው፡፡ እርሱም ‹‹ወግድ ከእኔ ራቅ ክርስቲያኖች በመተታቸው እንደምታየኝ ይህን አደርገውብኛልና›› አለው፡፡ ሰይጣንም መልሶ ‹‹ዐይኖችህን ባበራልህና መንግሥትህንም ብመልስልህ ምን ወሮታ ትከፍለኛለህ?›› አለው፡፡ ዲዮቅልጥያኖስም ‹‹ይህንንስ ካደረክልኝ በምድር ላይ አንድ

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

15 Nov, 18:52


ስንኳ ክርስቲያን ሳላስቀር ጨርሼ አጠፋቸዋለሁ›› አለው፡፡ በዚህም ጊዜ ሰይጣኑ ተሳለቀበትና ‹‹እንግዲህስ ወዮልህ ወዮታ አለብህ፣ ፈጽመህ ሙተህ ኑሮህ ከእኔ ጋር በሲኦል ነው›› አለው፡፡ የሰይጣን መጨረሻው ይህ ነው፣ የሰው ልጅ በሕይወት ሳለ ሲያስክድ፣ ሲያስት ፣ ክፉ ሥራን ሲያሠራ ይኖርና በመጨረሻ መክዳትና በሲኦል ማጋዝ ባሕርይው ነው፡፡ በዚያም ለዘለዓለም የሲኦል ባሪያ አድርጎ በታላቅ ሥቃይ ሲያሠቃይ ይኖራል፡፡ ዲዮቅልጥያኖስም ይህን ቃል ከሰይጣን ከሰማ በኋላ ደንግጦ በክፉ አሟሟት ሞቶ ዘላለማዊ ፍርዱን አግኝቶ ወደ ሲኦል ወረደ፡፡
የልዳው ፀሐይ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና የሌሎቹም ሰማዕታት ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን!
+ + +
የአቡነ እንድርያስ አባታቸው ተንሥአ ክርስቶስ
እናታቸው አርሴማ ይባላሉ። ሁለቱም ደጋግ ቅዱሳን ናቸው። ዕድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ ለመምህር ሰጧቸው። መምህሩም ጸጋ እግዚአብሔር እንዳደረባቸው ዐውቀው ብዙዎችን የምታድን ጻድቅ ትሆናለህ ብለው ትንቢት ነግረዋቸዋል። የመጻሕፍትንም ትርጓሜ በሚገባ ካስተማሯቸው በኋላ ንፍታሌም ይባል የነበረውን ስማቸውን ለውጠው ገብረ እንድርያስ አሏቸው። ጻድቁ በአቡነ ዮሐንስ ከማ ገዳም ለረጅም ጊዜ በታላቅ ተጋድሎ አገልግለዋል። አባታችን ሙታንን በማስነሣትና ድውያንን በመፈወስ ብዙ ተአምራትን ሲያደርጉ ኖረዋል። የትዉልድ ሀገራቸው በቤተ አምሃራ ክፍል ሀገረ ወለቃ ከገዳማቸው ቅርብ ርቀት ላይ "ደብረ ደብቄ ማርያም" እንደሆነና የአቡነ ገብረ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር እንደነበሩ እንዲሁም የመጀመሪያ ስማቸው ንፌታሌም ይባል እንደነበር፣ ካህንና የአምስት ልጆች አባትም እንደሆኑ በገድላቸው ላይ ተጽፎ ይገኛል።

አቡነ ገብረ ክርስቶስ ጽኑ የሆነውን ተጋድሏቸውንና መልካም አገልግሎታቸውን ፈጽመው በሞት ከማረፋቸው በፊት የገዳሙ አበምኔት ሆነው እንዲያገለግሉ ንፌታሌምን (አቡነ ገብረ እንድርያስን) መርጠው እንደሾሟቸው በመጽሐፈ ገድላቸው ላይ ተጽፏል። አቡነ ገብረ እንድርያስ ዘደብረ ቆዘት ከሀገረ ወለቃ እስከ ጎጃም ድረስ ስብከተ ወንጌል እንዳስፋፉ የቤተ ክርስቲያን መዝገበ ቃላት በሚለው መጽሐፍ ላይ ተጽፎ ይገኛል።

አቡነ ገብረ እንድርያስ በደብረ ርስኩር (በአሁኑ ደብረ ብርሃን ሰኮሩ ሥላሴ) ቤተ ክርስቲያን በሱባኤ ላይ እንዳሉ መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል በወርቅ ጽዋ ሰማያዊ ወይንና ሰማያዊ ኅብስት መግቧቸዋል። እንዲሁም አምላክን የወለደች ክብርት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሦስት ጽዋ ማየ ሕይወት ካጠጣቻቸው በኋላ ሕሙማንን እንደፈወሱ፣ ዕዉራንን እንዳበሩ፣ ሙት እንዳስነሡ በገድላቸው ላይ ተጽፏል።

የአቡነ ገብረ እንድርያስ አባት የሆኑት የአቡነ ገብረ ክርስቶስ ጥንታዊ ውቅር ቤተ ክርስቲያን በአሁኑ ጊዜ ጠፍ ሆኖ ስለቀረ ከዚሁ ገዳም አቅራቢያ የልጃቸው የአቡነ ገብረ እንድርያስ ገዳም ተመሥርቶ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። አዲሱ ቤተ ክርስቲያን ለመጀመርያ ጊዜ የተሠራው በዐፄ ድል ነአድ ዘመነ መንግሥት ሲሆን ከዚያም በኋላ በተደጋጋሚ እድሳት ተደርጎለታል።

ጻድቁ አቡነ ገብረ እንድርያስ እግዚአብሔር ኀጥአንን እንዲምርላቸው ጣቀት ወንዝ ከተባለው ቦታ ላይ በአንገታቸው ላይ ትልቅ ድንጋይ እየተሸከሙ ይጸልዩ እንደነበርና ይጸልዩበት ከነበረው ወንዝ ውስጥ በተኣምራት መቍጠሪያ የሚሠራ ጸበል እንደፈለቀላቸው በገድላቸው ላይ ተጽፏል።

ከገዳሙ በስተደቡብ አቅጣጫ እግዚአብሔር ኀጥአንን እንዲምርላቸው ጣቀት ወንዝ ከተባለው ቦታ ላይ በአንገታቸው ድንጋይ አሥረው ይጸልዩበት ከነበረው ጣቀት ወንዝ ላይ በተኣምራት መቍጠሪያ የሚሠራው የአባ ጎርጎርዮስ ( ወንበረ ሥላሴ) ጠበል እና ሌሎችም በርካታ ጠበሎች ይገኛሉ። እነዚኽም ጠበሎች ሕሙማን ከተለያዩ በሽታዎች ለመፈወስ ከማገልገላቸውም በላይ መነኰሳት ለጸሎት የሚገለገሉበትን መቍጠሪያ በተኣምራት ይሰጣሉ። አዘገጃጀቱም እንዲህ ነው- በመጀመርያ በጠበሉ ላይ ገመድ ሣር ወይም ቀጭን ዕንጨት በመንከር ከቆይታ በኋላ በተነከረው ገመድ፣ ሣር ወይም ዕንጨት ላይ ጠንካራ ዓለት ይሠራል፤ ጠበሉ ውስጥ በተነከረው ገመድ ወይም ክር ላይ ውኃው በተኣምራት ወደ ጠንካራ ዓለትነት ይቀየራል። ከዚያም ገመዱን ወይም ክሩን ወይም ዕንጨቱን እሾልኮ በማውጣት ውስጡ ክፍት ስለሚሆን ያንን አስተካከለው እየከረከሙ መቍጠሪያ መሥራት ይቻላል።

አቡነ ገብረ እንድርያስ ዘወትር ዐርብ ዐርብ ወደ ኢየሩሳሌም ሔደው የጌታችን የአምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስን መካነ መቃብር ተሳልመው ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ተቀብለው ለመምጣት ይመላለሱ የነበረው በአንድ ትልቅ ድንጋይ ላይ ተቀምጠው ነው። ድንጋዩንም እንደ ደመና ይጠቀሙበት ነበር።

ከዚኸም ሌላ ጻድቁን የዛፍ ዋርካ እንደ ጥላ ሆኖ ያገለግላቸው ነበር። እርሳቸውም ድንጋይ
እንደ ሠረገላ፣ ዋርካውን እንደ ጥሳ እየተጠቀሙባቸው ወደ ኢየሩሳሌም ይመላለሱ እንደነበር በገድላቸው ላይ ተጽፏል። ያ እንደ ደመና ሠረገላ ሆኖ ለመጓጓዣነት ያገለግላቸው የነበረው ትልቅ ድንጋይ ዛሬም ድረስ በገዳማቸው ውስጥ በክብር ተቀምጦ ይገኛል። በዓለ ዕረፍታቸውም ኅዳር 7 ቀን በገዳማቸው በታላቅ ድምቀት ይከበራል።

አቡነ ገብረ እንድርያስ ታላቁን ጻድቅ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስን ያሟሟቱ ታላቅ ጻድቅ ናቸው፣ ይኸም ማለት አቡዪ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍል በሚገኘው ገዳማቸው በምድረ ከብድ ባረፉ ጊዜ አቡነ ገብረ እንድርያስ ከደቡብ ወሎ ወለቃ በእግዚአብሔር መንፈስ ተመርተው በቅዱሳንም ጥሪ ተደርጎላቸው ወደ ምድረ ከብድ መጥተዋል። ይኸም በአቡዬ ገድል ገጽ 83 ላይ እንዲህ ተብሎ በግልጽ ተጽፏል፤ የአባታችን የገብረ መንፈስ ቅዱስ ዕለተ ዕረፍቱ በደረሰ ጊዜ ብዙ ኅቡዓን ቅዱሳን ወደእርሱ መጡ ስማቸውም ፍሬ ቅዱስ ዘርዐ ቡሩክ፡ ያዕቆብ ብንያም፤ ዮሴፍ ነው አባታችንም በሞት እንደሚያርፍና ቃልኪዳን እንደተሰጠው ነገራቸው። እነርሱም ስለ አባታችን ዕረፍት አዘኑ እርሱ ርእሰ ባሕታውያን ነውና። በቀዳሚት ሰንበትም እያላበው በድካም እንደልማዱ ለፍጥረቱ ሁሉ ወደ አምላኩ መማለድን ሳያቋርጥ ዋለ። በመሸም ጊዜ ሰውነቱ ሁሉ ደከመ፤ መናገርም ተሳነው፣ እነዚያ ቅዱሳን ግን ዕረፍቱን አይቶ ምስክር ይሆን ዘንድ ገብረ እንድርያስን ሊጠሩት ሔዱ ቅዱሳኑም ወደ እርሱ ደርሰው የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስን ዕረፍት ነገሩት። እርሱም

በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ፤ መራራ ለቅሶንም አለቀሰ፤ ተነሥቶም ከእነርሱ ጋር ሔዶ ብፁዓዊ አባታችን ወዳለበት ደረሰ። ያንጊዜም ቅዳሜ ማታ ለእሑድ አጥቢያ ነበረ።”

የቅዱሳን አባቶቻችን የአቡነ ገብረ እንድርያስና የአቡነ ገብረ መንፈስ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን።

(ምንጭ ከበእንተ ቅዱሳን ኅሩያን መጽሐፍ)

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

15 Nov, 18:52


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ኅዳር 7-የልዳው ፀሐይ ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ በዓለም ላይ ከ470,000 ሺህ በላይ ሰማዕታትን በግፍ ያስገደለውን ከሃዲው ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስን በክፉ አሟሟት ለገደለበት ተአምሩ መታሰቢያ በዓሉ ነው፡፡ ቅዳሴ ቤቱም በዚሁ ዕለት ነው፡፡
+ በታላቅ ድንጋይ ላይ ተጭነው ወደ ኢየሩሳሌም ይመላለሱ የነበሩትና ፣ ድንጋዩም በደመና አምሳል ይታዘዛቸው የነበረ አስገራሚው ጠበላቸው ውስጥ እንጨት ሲነከርበት እንጨቱ በተአምራት ነጭ መቁጠሪያ የሚሆነው አቡነ ገብረ እንድርያስ ዕረፍታቸው ነው።
+ ዳግመኛም በዚህች ዕለት ሌላኛው የእስክንድርያው ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ዕረፍቱ ነው፡፡
+ አቡነ ሚናስ ዘሀገረ ተመይ ዕረፍታቸው ነው፡፡
+ ወንድማማቾቹ ሰማዕታት ቅዱስ መርቆሬዎስና ቅዱስ ዮሐንስ የሰማዕትነታቸው ፍጻሜ ሆነ፡፡
+ ቅድስት ዘኖብያ እና ልጇ ቅዱስ ዘኖቢስ በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡
+ አባ ናህርው በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡
ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ዘእስክንድርያ፡- አባቱ በእስክንድርያ አገር በንግድ ሥራ ይተዳደር የነበረ ሲሆን ልጅ ስላልነበረው በልዳው ኮከብ ቅዱስ ጊዮርጊስ ስም ወደተሠራች አንዲት ቤተ ክርስቲያን ሄዶ በቅዳሴ ቤቱ ክብረ በዓል ቀን ልጅ እንዲሰጠው ሰማዕቱን በስዕለት ጠየቀው፡፡ ስዕለቱም ተሰምቶለት ልጅ ሲወልድ ስሙን በሰማዕቱ ስም ጊዮርጊስ ብሎ ጠራው፡፡ ሚስቱም የእስክንድርያው አስተዳዳሪ የአርማንዮስ እኅት ናት፡፡ ጊዮርጊስ ከተወለደ በኋላ ብዙም ሳይቆዩ እናትና አባቱ ስለሞቱ አስተዳዳሪ አጎቱ ወስዶ አሳደገው፡፡ አጎቱም ጣዖትን የሚያመልክ ነው፡፡ ነገር ግን ጊዮርጊስ እስከ 20 ዓመቱ ድረስ በሃይማኖቱም እጅግ ጠንካራ ሆነ፡፡ በጾም በጸሎት እየተጋ ነዳያንን አብዝቶ ይመግብ ነበር፡፡ የጽድቅ ሥራውንም ሰው አያውቅበትም ነበር፡፡
የአስተዳዳሪው ብቸኛ ሴት ልጅ ልዩ ልዩ የተዋቡ ቦታዎችን ትጎበኝ ዘንድ ከቤት ወጥታ ወደ ደብረ ቁስቋም ስትደርስ የቤተ ክርስቲያንን የቅዳሴ ዝማሬ ሰምታ ልቧ እጅግ ደስ ተሰኘ፡፡ የአክስቷ ልጅ የሆነ ጊዮርጊስንም መነኮሳቱ ስለሚያሰሙት ዝማሬ ጠየቀችው፡፡ እርሱም ምንነቱን ካስረዳት በኋላ በዚያውም የሃይማኖትን ነገር በደንብ አስተማራት፡፡ ልጅቱም ወደ ከሃዲው አስተዳዳሪው አባቷ ዘንድ ቀርባ ስለ ጌታችን ክብር ትመሰክር ጀመር፡፡ አባቷም ሊሸነግላት ቢሞክር ነገሩን እንዳልሰማችው ሲያውቅ ብቸኛና አንድያ ልጁን አንገቷን በሰይፍ አስቆረጠው፡፡ ከዚህም በኋላ ‹‹ልጅህን አስተምሮ ያሳታት የእኅትህ ልጅ የሆነው ጊዮርጊስ ነው›› ብለው ለመኰንኑ ነገሩት፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስንም ይዞ ጽኑ ሥቃይን ካሠቃየው በኋላ ኅዳር 7 ቀን አንገቱን በሰይፍ ቆረጠውና ሰማዕትነቱን በድል ፈጸመ፡፡
+ + +
አቡነ ሚናስ ዘሀገረ ተመይ፡- ተመይ የምትባለው አገር ኤጲስ ቆጶስ የሆነው የአቡነ ሚናስ ወላጆቹ የመነኮሳትን ሥራ የሚሠሩ ደጋጎች ነበሩ፡፡ የቤተ ክርስቲያንንም ትምህርት እያስተማሩ አሳደጉት፡፡ ሲያድግም ያለፈቃዱ ሚስት አጋቡት፡፡ ወደ ጫጉላ ቤትም በገባ ጊዜ ድንግልናቸውን ይጠብቁ ዘንድ ከሚስቱ ጋር ተማክሮ ሁለቱም በንጽሕናና በድንግልና ሆነው በአንድነት ሊኖሩ ተስማሙ፡፡ ሌሊቱንም ሁሉ ለጸሎት ቆመው ያድሩ ነበር፡፡ እርሱም በዓለም እየኖሩ የምንኩስናን ሥራ ከመሥራት ይልቅ መንኩሶ ገዳም መግባት እንደሚሻል ለሚስቱ ሲነግራት ሸኝታ አሰናበተችው፡፡ አቡነ ሚናስም ወደ አቡነ እንጦንስ ገዳም ገባ ነገር ግን በንጉሡ ትእዛዝ ቤተሰቦቹ ቢያስፈልጉትም ጌታችን ሰውሮታል ሊያገኙት አልቻሉም፡፡ ከዚህም በኋላ ወደ አስቄጥስ ገዳም ሄደ፡፡

በዚያም ሁለቱ ብርሃን ከዋክብት አባ አብርሃምንና አባ ገዐርጊን በማገልገል ልጅ ሆናቸው፡፡ ተጋድሎአቸውንና ትምህርታቸውን በሚገባ ከተማረ በኋላ እርሱም በተጋድሎው አባ አብርሃምና አባ ገዐርጊ እስኪያደንቁትና እስኪገረሙበት ድረስ ከፍ ከፍ አለ፡፡ ከዚህም በኋላ ኤጲስ ቆጶስነት ይሾም ዘንድ ጌታችን መርጦት ለሊቀ ጳጳሳቱ እንዲሾመው ነገረው፡፡ ሊቀ ጳጳሳቱም ጠርተው ሲያስመጡት እምቢ ቢላቸውም የእግዚአብሔር ትእዛዝ መሆኑን ነግረውት ተመይ በሚባል አገር ላይ ሾሙት፡፡ አቡነ ሚናስ ከዚህም በኋላ ሀብተ ፈውስም ተሰጥቶት ብዙ ድውያንን የሚያድናቸው ሆነ፡፡ ሁለተኛም የተሰወረውን የማወቅ ሀብት ተሰጠውና በሰው ልቡና የታሰበውን የሚያውቅ ሆነ፡፡ አቡነ ሚናስ ለአራት ታላላቅ አባቶች አባት ሆኖ እጁን በላያቸው ላይ ጭኖ ሾሟቸዋል፡፡ እነርሱም ለእስክንድርያ አገር ሊቃነ ጳጳሳት የሆኑት አባ እለእስክንድሮስ፣ አባ ቆዝሞስ፣ አባ ቴዎድሮስና አባ ሚካኤል ናቸው፡፡ አባታችን በመጨረሻም ከዚህ ዓለም ድካም የሚያርፍበትን ጊዜ ዐውቆ ካህናቱንና ሕዝቡን ሁሉ ሰብስቦ በቀናች ሃይማኖት ጸንተው እንዲኖሩ ከመከሯቸው በኋላ ኅዳር 7 ቀን በሰላም ዐረፉ፡፡
+ + +
ሐዲስ ቅዱስ መርቆሬዎስና ወንድሙ ቅዱስ ዮሐንስ፡- እነዚህም ቅዱሳን የደጋግ ክርስቲያን ልጆች ናቸው፡፡ የታላቁ ስም ሙናሂ ነበር ሲመነኩስ ግን መርቆሬዎስ ተባለ፡፡ የታናሹም ስም አቡፈረዥ ነበር እርሱም ሲመነኩስ ዮሐንስ ተባለ፡፡ ሁለቱም ወንድማማቾች ወደ ሊቀ ሠራዊት ቅዱስ ቴዎድሮስ ገዳም ገብተው ጽኑ የሆነ ተጋድሎአቸውን ጀመሩ፡፡ ለመነኮሳቱ ሁሉ የሚላላኩና የሚያገለግሉ ሆኑ፡፡ ጣዕም ካላቸው ምግቦችና መጠጦች እንዲሁም ከእንቅልፍ እርቀው በታላቅ ተጋድሎ ኖሩ፡፡ የሚመገቡትም በሦስት ቀን አንድ ጊዜ ሆነ፡፡ የግብፅንና የሌላውንም ጽሕፈት ተምረው መጻሕፍትን መረመሩ፡፡ እነዚህም ወንድማማቾች አንድ ቀን አብረው ሳሉ የታዘዘ መልአክ ተገለጠላቸውና ወደ ምስክርነት አደባባይ ሄደው ስለጌታችን ስለ ስሙ እንዲመሰክሩና ሰማዕትነታቸውን እንዲፈጽሙ ነገራቸው፡፡
እነርሱም እንደታዘዙት በከሃዲው መኰንን ፊት ሄደው ስለ ጌታችን ክብር መሰከሩ፡፡ መኰንኑም የተለያዩ ጽኑ ሥቃዮችን አሠቃያቸው፡፡ ከብዙ ሥቃይም በኋላ በወህኒ ቤት ተጥለው ሳለ ሌላ መኰንን ተሹሞ እርሱም ሊተዋቸው በወደደ ጊዜ የአገሩ ሰዎች እነርሱን ካልገደልካቸው በንጉሡ ዘንድ እንከስሃለን›› አሉት፡፡ ይህም መኰንን ሕዝቡን ከመፍራቱ የተነሣ ፈቃዳቸውን ይፈጽምላቸው ዘንድ አሳልፎ ሰጣቸው፡፡ ሕዝቡም ኅዳር 7 ቀን ሐዲስ የተባለ የቅዱስ መርቆሬዎስንና የወንድሙ የቅዱስ ዮሐንስን ራስ በሰይፍ ከቆረጧቸው በኋላ የሰማዕትነት ፍጻሜአቸው ሆነ፡፡
+ + +
ቅድስት ዘኖብያ እና ልጇ ቅዱስ ዘኖቢስ፡- እነዚህም ቅዱሳን ተበይስ ከምትብል አገር ከታላላቅ ወገኖች የተገኙ ሰማዕታት ናቸው፡፡ እነርሱም ክርስቲያኖች እንደሆኑ በከሃዲው ንጉሥ ዘንድ ዜናቸው ተሰማ፡፡ ንጉሡም ወደ እርሱ ካስመጣቸው በኋላ እምነታቸውን መረመራቸው፡፡ እነርሱም ‹‹አገራችን ተበይስ ነው የምናመልከውም የክብርን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ነው›› አሉት፡፡
ከዚህም በኋላ ንጉሡ እናትና ልጅን ‹‹ለአማልክት ሠው›› አላቸው፡፡ ቅዱሳኑም ‹‹እኛስ ለእውነተኛው አምላክ ለክርስቶስ እንሠዋለን እንጂ ለረከሱ ጣዖታት አንሠዋም›› አሉት፡፡ ንጉሡም በዚህ ጊዜ እጅግ ተቆጥቶ ቅድስት ዘኖብያንና ልጇን ቅዱስ ዘኖቢስን ጽኑ በሆነ ሥቃይ አሠቃያቸው፡፡ ልብሳቸውን ገፈው በራሳቸው ጸጉር ሰቅለው እየደበደቡ እንዲያሠቃዩአቸው አደረገ፡፡ ቅዱሳኑም ወደ እግዚአብሔር በጸለዩ ጊዜ ማሰሪያው በተአምራት ተፈታላቸው፡፡ የብርሃን ልብሶችንም ለብሰው ሕዝቡ ሁሉ አዩአቸው፡፡ ይህንንም ባዩ ጊዜ ‹‹የእነዚህ ቀዱሳን አምላካቸው ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ይክበር ይመስገን እኛም በአምላካቸው አምነናል›› እያሉ ጮኹ፡፡ ንጉሡም በታላቅ ቁጣ ሆኖ እናትና

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

14 Nov, 16:53


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ኅዳር 6-በዚህች ዕለት ክብርት እመቤታችን ከተወደደ ልጇ ጋር ከስደት በሚመለሱበት ጊዜ ደብረ ቁስቋም ገብተው ካገኛቸው ድካም ዐረፉ፡፡
አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች ክብርት እመቤታችን ከስደት በተመለሰች ጊዜ እንዲህ ሆነ፡- የብርሃን እናቱ ክብርት እመቤታችን ልጇን ይዛ ከእነ ዮሴፍ ጋር ወደ ምድረ ግብፅ ስትሰደድ ግብፅ ደርሰው በዚያ ቢቀመጡም ነገር ግን ግብፅ አልተመቸቻውም፡፡ ሕዝቡም በሰላም አልተቀበላቸውም፡፡ እንዲያውም በምድረ ግብፅ ብዙ ተሠቃይተዋል፡፡ ከግብፅም ተነሥተው ወደ ኢትዮጵያ በመጡ ጊዜ ግን ኢትዮጵያ ሕዝብ ሁሉ በሰላምና በፍቅር ተቀበላቸው፡፡ ከመንገዱና ከርሃብ ጥሙ ጽናት የተነሣ እጅግ ደክማለችና የኢትዮጵያ ሰዎች እመቤታችንን አይተው እጅግ አዘኑላት፡፡ ‹‹ይህችስ የነገሥታት ዘር ትመሥላለች ነገር ግን አንዳች ችግር አጋጥሟት ተሰዳ ወደ ሀገራችን መጥታለች..›› ብለው እንክብካቤን አደረጉላት፡፡ እግራቸውን አጥበው በክብር ማረፊያዎች ላይ አሳረፏቸው፡፡ መልካም መስተንግዶም አደረጉላቸው፡፡ እመቤታችንም ከድካሟ ካረፈች በኋላ ሀገሪቱን በእጅጉ ወደደቻትና የተወደደ ልጇን ‹‹ይህን ሀገርና ሕዝቧን በመላ ወድጃቸዋልሁና በዚህ እስከ መጨረሻው እንኑር›› አለችው፡፡ ጌታችንም ክብርት እናቱን ‹‹ይህች ቅድስት ሀገር ናት፣ በኋለኛው ዘመን የቅዱሳን መነኮሳት ቦታ ትሆናለች፡፡ በውስጧም እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ እመሰገንባታለሁ፤ የአንቺም ስም ሳይጠራ አይውልባትም›› አላት፡፡
ከዚህም በኋላ ጌታችን ደመና ጠቅሶ በእርሷ ላይ ተቀመጡ፡፡ መልአኩ ቅዱስ ዑራኤልም መጣና እየመራቸው መላ ኢትዮጵያን ጎበኟት፡፡ እመቤታችንም ሀገሪቱንና ሕዝቦቿን ወዳቸዋለች ደስም ተሰኝታባቸዋለችና ጌታችን ለክብርት እናቱ ‹‹ይህችን ቅድስት ሀገር አሥራት አድርጌ ሰጠሁሽ›› አላት፡፡ እመቤታችንም እጅግ ተደስታ ‹‹ልጄ አምላኬ›› ብላ አመሰገነችው፡፡ ከዚህም በኋላ ከአንዱ ቦታ ወደ አንዱ ቦታ እየተዘዋወሩ መላዋ ኢትዮጵያን በኪደተ እግራቸው ባረኳት፡፡ ጌታችንም ‹‹በዚህ ቦታ እንዲህ ዓይነት ቤተ ክርስቲያን ይታነጻል፤ እከሌ የሚባል እንዲህ ዓይነት ቅዱስ ይነሣል…›› እያለ ብዙ ምሥጢራትን ለክብርት እናቱ ነገራት፡፡ ከዚህም በኋላ የስደቱ ዘመን ሲያልፍ ሄሮድስም በመጨረሻ ክፉ አሟሟትን ሲሞት መልአኩ ወደ ገሊላ አውራጃ እንዲመለሱ ነገራቸው፡፡ እመቤታችንም ‹‹ከዚህች ሀገርስ ባንሄድ እመርጣለሁ›› ስትለው የተወደደ ልጇ ግን ‹‹እናቴ ሆይ ጽድቅንና ፈቃድን ሁሉ ልንፈጽም ይገባናል›› ብሎ አጽናናትና ወደ ሀገራቸው ተመልሰው ሄዱ፡፡
ተመልሰውም ሊሄዱ ሲነሡ የኢትዮጵያ ሰዎች ልዩ ልዩ አምሐ እጅ መንሻ ሰጧቸው፡፡ ልዩ ልዩ ልብሶች፣ ወርቅ፣ ዕጣን፣ ከርቤ፣ ሽቱ እና ሥንቀቸውን በግመሎች ላይ ጭነው እመቤታችንንና የተወደደ ልጇንም በበቅሎ ላይ አስቀምጠው በክብር ሸኟቸው፡፡ እመቤታችንም ልጇን ታቅፋ በበቅሎ ተቀምጣ በበረሃው በመጓዝ ወደ መጣችበት አገር ሄደች፡፡ ኢትዮጵያንም የሰጧትን ብዙ እጅ መንሻዎች በግመሎች ጭና ይዛ ወደ አገሯ በተመለሰች ጊዜ ከአንድ ባሕር ዳር ደረሰች፡፡ ከዚያም የጀልባውን ባለቤት ‹‹እግዚአብሔርን ስለመውደድ አሻግረኝ›› ብላ ለመነችው፡፡ ባለጀልባውም ‹‹እነሆ ዕቃ የተጫኑ አምስት ግመሎችና ከአንቺ ጋር ከዚህም ሕፃን ጭምር አምስት ሰዎች እመለከታለሁ፣ አንቺ የተቀመጥሽባት በቅሎም አለች፡፡ ጀልባዋም ታናሽ ናት፣ የመቀመጫ ክፍሏም በውስጧ የተሳፈሩት ሰዎችም ተጨናንቀው ነው ያሉት፡፡ ስለዚህ እንዴት ላሻግርሽ እችላለሁ? ነገር ግን እመቤቴ ሆይ! ይቅርታ አድርጊልኝ ይህን በክፋት አላደረግሁትምና›› አላት፡፡
ክብርት እመቤታችንም የጀልባው ባለቤት ሊያሻግራት እንዳልቻለ በተረዳች ጊዜ ‹‹ልጄ ሆይ የእግዚአብሔር ልጅ እንደመሆንህ ይህን ትልቅ ወንዝ ለመሻገር የአምላክነትህን ሥራ ትሠራ ዘንድ እለምንሃለሁ›› ስትል ማለደችው፡፡ ያንጊዜም ጌታችን ክብርት እናቱን ‹‹የወለደሽኝ እናቴ ሆይ! አትዘኝ›› ብሎ አረጋጋት፡፡ ዳግመኛም ‹‹በእኔ ፈቃድ በአባቴ ፈቃድ በመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ ካንቺ ሰው ሆኛለሁና ሰው መሆኔንም ከአባቴ በቀር መስተፍሥሒ ከሚሆን ከመንፈስ ቅዱስም በቀር ያወቀ የለም፡፡ ዳግመኛም በሕያዋንና በሙታን ለመፍረድ ለሁሉም እንደየሥራው እከፍለው ዘንድ እመጣለሁ፡፡ ያችንም ሰዓት የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ የአዳም ልጆችም ቢሆኑም ከእኔና ከአባቴ ከመንፈስ ቅዱስም በቀር የሚያውቃት የለም፡፡ ያንጊዜ ‹ዐመፅን የሚናገር አንደበት ሁሉ ይዘጋል› ብሎ አባትሽ ዳዊት እንደተናገረ እከራከራለሁ የሚል አንደበት እንደድዳ ምላሽ ያጣል›› አላት፡፡
ክብርት እመቤታችን ማርያምም ይህንን ሁሉ ምሥጢር የተወደደ ልጇ የነገራትን ታስተውለው በልቧም ትጠብቀው ነበር፡፡ ጌታችንም አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ለክብርት እናቱ ይህንን ከነገራት በኋላ ቀኝ እጁን ዘርግቶ ከወንዙ ማዶ ጢር በሚባል ተራራ ያሉትን ድንጋዮች ጠቀሳቸው፡፡ ያንጊዜም እነዚህ ድንጋዮች እየተገለባበጡ መጥተው እንደ ጀልባ ሆነው በወራጁ ወንዝ ላይ ተንሳፈፉ፡፡ ከዚያም እመቤታችንን ከሕፃኑ ጋር ከነቤተሰቧና ከነጓዟ አሻገረሯት፡፡
እነዚህንም ድንጋዮች ያዩ ሰዎች ሁሉ እጅግ አድንቀው ‹‹ብቻውን ድንቅ ተአምራት ያደረገ፣ እስራኤልን የፈጠረ እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን የጌትነቱም ስም የተመሰገነ ነው›› እያሉ አመሰገኑ፡፡ እነዚህም የተባረኩ ሰዎች ወንዙን ከተሻገሩ በኋላ በዚህች አገር ለስምንት ቀን ተቀመጡ፡፡ ከዚህም በኋላ አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች ክብርት እመቤታችን ስለደረገላት መልካም ሥራ ሁሉ እግዚአብሔርን ፈጽማ እያመሰገነች ወደ አባቷ ወደ ዳዊት አገር ተመለሰች፡፡
ዳግመኛም በኋለኛው ዘመን ጌታችን በዚህ በደብረ ቍስቋም ቅዱሳን ሐዋርያቶቹን ሰበሰባቸውና ታቦትንና ቤተ ክርስቲያንን አክብሮ የቍርባን መሥዋዕትንም ሠርቶ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለወገኖቹ ሰጣቸው፡፡ ለዚህም ነገር የእስክንድርያ አገር ሊቃነ ጳጳሳት ቅዱሳን አባቶቻችን ቄርሎስና ቴዎፍሎስ ምስክሮቹ ሆኑ፡፡
ክብርት እመቤታችን ከስደቷ በረከት ትክፈለን!
+ ዳግመኛም በዚህች ዕለት አባ ፊልክስ ዐረፈ፡፡
አባ ፊልክስ፡- ይኸውም ቅዱስ ምግባር ሃይማኖቱ፣ ትሩፋት ተጋድሎው ያማረ ሆኖ ቢያገኙት በእግዚአብሔር ፈቃድ የሮሜ አገር ሊቀ ጳጳሳት አድርገው ሾሙት፡፡ በዘመኑም ከሃዲው ቴዎስድሮስ ቄሳር ነግሦ ምእመናንን ሲያሠቃያቸውና ሲገድላቸው ሊቀ ጳጳሳት አባ ፊልክስንም ብዙ አሠቃጥቷቸዋል፡፡ አባ ፊልክስም በክርስቲያኖች ላይ እየደረሰ ያለው ጽኑ መከራ እንዲቆም ወደ እግዚአብሔር በጸለየ ጊዜ ይህን ከሃዲ ንጉሥ በነገሠ በ2ኛ ዓመቱ አጠፋው፡፡
ከዚህም በኋላ የክርስያኖችን ደም እንደውኃ ያፈሰሰው ከሃዲው ዲዮቅልጥያኖስ ነገሠና ክርስቲያኖችን በዓለም ላይ እያደነ ማሠቃየትና መግደል በጀመረ ጊዜ ይህ አባት አባ ፊልክስ የክርስቲያኖችን ሥቃይ እንዳያሳየው ወደ እግዚአብሔር በጸለየ ጊዜ ወዲያው በመጀመሪያው ዓመት ዐረፈ፡፡ ይህም አባ ፊልክስ ለክርስቲያን ወገኖች እጅግ ጠቃሚ የሆኑ ብዙ ድርሳናትንና ትግሣጻትን የጻፈ ነው፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!
ከገድላት አንደበት

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

14 Nov, 08:38


በተፈጥሮአዊ አቀማመጡ እጅግ ድንቅ የሆነው ደብረ ዓሣ አባ ዮሐኒ ገዳም!
በዛሬዋ ዕለት ኅዳር 5 ቀን በሞት ፋንታ የተሰወሩት አባ ዮሐኒ የእናታቸውን ጡት ፈጽሞ ጠብተው አያውቁም ይልቁንም የታዘዘ ንስር አሞራ በክንፎቹ ጋርዶ እያለበሳቸው እና ቶራ (ሰሳ) እያጠባቻቸው ነው ያደጉት፡፡ አባታችን ስለጽድቅ ብለው 500 ሜትር ርዝመት ካለው ከዚህ ትልቅ ተራራ ላይ ራሳቸውን ቁልቁል ቢወረውሩ መሬት ሳይደርሱ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በአየር ላይ እንዳሉ ተቀበላቸው፡፡ ወዲያውም አባ ዮሐኒ ክንፍ አውጥተው ከቅዱስ ገብርኤል ጋር ጎን ለጎን ሆነው በዛሬው ዕለት ኅዳር 5 ቀን ወደ ብሔረ ሕያዋን ይዟቸው ገባ።ብሔረ ሕያዋን ያሉ እነ ሄኖክና ኤልያስም ‹‹ሰው ከሚሞትበት ሀገር ሞት ወደሌለበት አገር ማን አመጣው?›› አሉ፡፡ መልአኩም በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር ባዘዘኝ ጊዜ እኔ ገብርኤል ነኝ ያመጣሁት›› አላቸው፡፡ ቀጥሎም መልአኩ ‹‹አንተ ሄኖክ ምንም ንጹሕ ብትሆን በሥርዓተ ሥጋ ተወልደህ በሥርዓተ ሥጋ አድገህ ሚስት አግብተህ ወልደሃል፣ እግዚአብሔርም እዚህ ያደረሰህ በንፅህናህ ነው፤ አንተም ኤልያስ ምንም ድንግል ብትሆን በሥርዓተ ሥጋ ተወልደህ በሥርዓተ ሥጋ አድገህ ከዚህ ደርሰሃል፤ ይህ አባ ዮሐኒ ግን ከተወለደ ጀምሮ የእናቱን ጡት አልቀመሰም፣ ቀን ቀን ሰሳ እያጠባችው ሌሊት ሌሊት ንስር አሞራ በክንፎቹ እያለበሰው አድጓል እንጂ›› ብሎ ነገራቸው፡፡ ቀጥሎም መልአኩ የአባ ዮሐኒን ገድል ዘርዝሮ ከነገራቸው በኋላ ሊሞት ያለበትንም የአሟሟቱን ነገር ከነገራቸው በኋላ ‹‹ታዲያስ እንዲህ ያለውን አምጥቼ ከብሔር ሕያዋን ባስገባው ፍርዴ እውነት አይደለምን?›› አላቸው፡፡ ሄኖክና ኤልያስም ይህን ጊዜ ‹‹ይገባዋል›› ብለው አባ ዮሐኒን በምስጋና ተቀበሉት፡፡ ገዳሙ ውስጥ ሦስት ቤተ መቅደሶች ያሉ ሲሆን አንዱን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ይቀድሱበት የነበረው ነው፡፡ ገዳሙ ደብረ ዓሣ እየተባለ ይጠራል፡፡ ምክንያቱም ቤተ ክርስቲያኑ በመሬት መንቀጥቀጥ ከመፍረሱ በፊት ጣራው የዓሣ አንበሪ ቅርጽ ነበረው፡፡ ዐፄ ገብረ መስቀልም በወቅቱ በዚህ ዓሣ ምስል ያሠሩት ቅዱስ መስቀል በገዳሙ ውስጥ ይገኛል፡፡ አንድም ደግሞ በመጀመሪያ ዐፄ ገብረ መስቀል እና ሌሎቹም ቅዱሳን አበው በገዳሙ ውስጥ ሱባኤ ገብተው ሳለ ቅዱሳን በዓሣ ተመስለው ሲወጡና ሲገቡ በማየታቸው ነው ገዳሙ ‹‹ደብረ ዓሣ አባ ዮሐኒ›› የተባለው ሌላው በተፈጥሮአዊ አቀማመጡ እጅግ ድንቅ በሆነው በዚህ ገዳም ውስጥ አስገራሚ የመቃብር ጉድጓዶች አሉት፡፡ መቃብሮቹ የተፈለፈሉ ዋሻዎች ናቸው፡፡ አንዱ ዋሻ በአንድ ጊዜ ከ6 ሰዎችን ጎን ለጎን አስተኝቶ መያዝ አይችልም ነገር ግን በጣም የሚገርመው የመቃብር ጉድጓዶቹ እስከዛሬም ድረስ አልሞሉም፡፡ አንድ ሰው ከተቀበረ ከዓመት በኋላ አስክሬኑ ይጠፋል፣ አጥንቱም አይገኝም፡፡ ሰሌኑ ግን እስከ ሁለት ዓመት ይቀመጣል፡፡ ለአባ ዮሐኒ ለዚህ ገደማቸው ዕጣን ጧፍ ዘቢብ የሰጠ ሰው ቢኖር ስጦታውን እንደ አቤል መሥዋዕት አድርጎ ጌታችን እንደሚቀበልለት ለጻድቁ ቃልኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡
ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን!
ከገድላት አንደበት
✞ ✞ ✞

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

11 Nov, 14:26


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን!
ኅዳር 3-አፈር ከኢየሩሳሌም አምጥተው ዋልድባ ሲደርሱ መነኮሳቱ ‹‹ገዳሙን በአህያ አታስረግጥ›› ቢሏቸው አህዮቹን ክንፍ አውጥተው እንዲበሩ ያደረጉት አቡነ ፍሬ ካህን ዕረፍታቸው ነው፡፡
+ እነ አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባን አስተምረው ያመነኮሱትና ውኃ ይቀዳላቸው የነበረውን አህያቸውን አንበሳ ቢበላባቸው በአህያው ምትክ አንበሳውን 7 ዓመት ለገዳማቸው ውኃ ያስቀዱት የደብረ በንኮሉ ታላቁ አባት አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ዕረፍታቸው ነው፡፡
+ ጻድቁ ንጉሥ ቅዱስ ነዓኵቶ ለአብ የተሰወረበት ዕለት ነው፡፡
+ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ሰማያዊ መና ሲመግባቸውና የጌታችንንም ቅዱስ ሥና ደም በሰንበት እያመጣለቸው ያቆርባቸው የነበሩት ሰማዕቱ አቡነ ዓምደ ሚካኤል ዕረፍታቸው ነው፡፡
+ አባ አትናቴዎስና እኅቱ ቅድስት ኢራኢ በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡
+ ከቆሮንቶስ አገር የተገኙት ቅዱስ አባ ኪርያቆስ ዕረፍታቸው ነው፡፡

አባ አትናቴዎስና እኅቱ ቅድስት ኢራኢ፡- እነዚህንም ቅዱሳን ከሃዲው ንጉሥ መክሲምያኖስ ይዞ ጽኑ ሥቃይን አሠቃያቸው፡፡ ንጉሡም ቅዱሳኑ ጌታችንን በማመን እስከመጨረሻው መጽናታቸውን ባየ ብዙ መከራ አደረሰባቸው፡፡ በመጨረሻም ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ ራቁታቸውን ከጉድጓድ ውስጥ በመጨመር በላያቸው ላይ የጉድጓዱን አፍ ዘግቶ ደፈነው፡፡ አባ አትናቴዎስና እኅቱ ቅድስት ኢራኢም በዚያው የሰማዕትነታቸው ፈጻሜ ሆኖ የክብር አክሊልን ተቀዳጁ፡፡ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን!

+ + +
አቡነ ዓምደ ሚካኤል፡- ትውልዳቸው ወሎ ቦረና ነው፡፡ ወላጆቻቸው ገላውዲዮስና ኤልሳቤጥ ሁለቱም በሃይማኖትና በዓለም ገንዘብ የበለጸጉ ናቸው፡፡ ይህንንም ጻድቅ ልጃቸውን የአርባዕቱ እንስሳ በዓል ዕለት ወለዱትና ስሙን ዓምደ ሚካኤል ብለው ጠሩት፡፡ ለዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ፣ ለዐፄ በእደ ማርያምና ለዐፄ እስክንድር የሠራዊት አለቃ የነበረ ጻድቅ ነው፡፡ በአንድ ዓመቱ ወላጆቹ ወደ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ይዘውት እንደሄዱ ከወላጆቹ ተለይቶ ጠፍቶ ሳይገኝ ቀረ፡፡ መልአክም ከቤተ መቅደስ አግብቶ እየመገበው 3 ቀን አቆይቶታል፡፡ በ3ኛው ቀን ቄሱ ሊያጥን ሲገባ በከርሰ ሐመሩ ውስጥ ሕፃኑን አገኘውና ወስዶ ለወላጆቹ ሰጣቸው፡፡

ባደገም ጊዜ በመመጽወትና አብያተ ክርስቲያናትን በማደስ የሚተጋ ሆነ፡፡ ለድኆችም በቅንነት በመፍረድ በታላቅ ተጋድሎ የሚኖር ሆነ፡፡ ለነገሥታም ገዥ ከሆነ በኋላ በጸሎቱና በበረከቱ በሀገራችን ላይ ሁሉ ሰላም ሆነ፡፡ ጠላቶችም ሁሉ ለነገሥታቱ ተገዝተው ይገብሩ ነበር፡፡ በበጎ ምግባሩ የቀኑ ዐመፀኞችም በክፋ ተነሡበት፡፡ ጻድቁ በመንፈስ አድጎ መንኩሶ በታላቅ ተጋድሎ ሲኖር ነገር ሠሪዎች በሐሰት ወንጅለው ከሰሱት፡፡ ንጉሡም እጅግ ስለሚወደው የራራለት ቢሆንም በነገራቸው ባስጨነቁት ጊዜ ወደ ሩቅ አገር አስሮ አጋዘው፡፡ አባታችንም በግፍ ታስረው ሳሉ በእስር ቤቱ ውስጥ ብርሃን ወረደላቸው፣ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤልም ሰማያዊ መና እያመጣ ይመግባቸው ነበር፡፡ የጌታችንንም ሥና ደም በሰንበት እያመጣለቸው ያቆርባቸው ነበር፡፡ ነገረ ሠሪዎቹ ይገድሏቸው ዘንድ ንጉሡን ለመኑት፡፡ በዓመፃቸውም ብዛት ወደ ፍርድ ሸንጎ አምጥተው ገደሏቸው፡፡

አንድ ጻድቅ መነኩሴ የቅዱስ ዓምደ ሚካኤልን ሥጋ ሦስት ቅዱሳን መላእክት ሲያጥኑ አገኛቸውና ያየውን ለሕዝቡ ተናገረ፡፡ በሌላም ጊዜ የብርሃን ፋና ከሰማይ ሲወርድላቸው ብዙ ቀን የተመለከቱ ብዙ ቅዱሳን ምስክርነታቸውን ሰጡ፡፡ ንጉሡም ይህንን ሁሉ ሲሰማ በአሳቾቹ ልበ ደንዳናነትና ክፋት እጅግ ተጸጽቶ በሞት ቀጣቸው፡፡ ቅዱስ ዓምደ ሚካኤልንም በአባቶች መቃብር በክብር አስቀበራቸው፡፡ ስማቸውንም በበጎ እንጂ በክፋ ማንም እንዳያነሳቸው በአዋጅ አስነገረ፡፡ መታሰቢያም አቆመላቸው፡፡
ከዚህም በኋላ ዐፄ ልብነ ድንግል በነገሠ ጊዜ የአባቱን የበእደ ማርያምን ቃል ኪዳን ሰምቶ ዐፅማቸውን አፍልሶ ወደ አትሮንስ ማርያም ወሰደውና በቅዱሳን ነገሥታት መቃብር በክብር አኖረው፡፡ ሊቀ ብርሃናት መርቆሬዎስ አረጋም ጻድቁ ሲያርፉ በደብረ ሊባኖስ ገዳም የተቀበሩ ቢሆንም ከብዙ ዘመን በኋላ ዐፅማቸውን አፍልሰው በተድባበ ማርያም እንደቀበሯቸው ጽፈዋል፡፡
የአቡነ ዓምደ ሚካኤል ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን!
+ + +
አባ ኪርያቆስ፡- ወላጆቹ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት እያስተማሩ አሳደጉት፡፡ የቆሮንቶስ አገር ኤጲስቆጶስ የሆኑት አባ ጴጥሮስ አናጉስጢነት ሹሙት፡፡ (አናጉስጢስ ማለት መጽሐፍን ለሕዝቡ እንዲያነቡ የሚሰጥ የቤተ ክርስቲያን ማዕረግ ነው፡፡) አባ ኪርያቆስ ቅዱሳት መጻሕፍትን ዘወርት የሚመረምር ሆነ፡፡ ትርጓሜያቸውንና ምሥጢራቸውንም በመመርመር የቤተ ክርስቲያንን ሥርዓትና ሕግ አጸና፡፡ በትምህርቱና በዕውቀቱም ከሁሉም ይልቅ ከፍ ከፍ አለ፡፡ ዕድሜውም 18 ዓመት በሆነው ጊዜ ሚስት ያጩለት ዘንድ ወላጆቹ ግድ አሉት ነገር ግን አባ ኪርያቆስ ፈጽሞ እምቢ አለ፡፡ ይልቁንም ከገዳማት ወደ አንዱ ይሄድ ዘንድ እንዲያሰናብቱት ወላጆቹን ለመናቸው፡፡ ወደ ኢየሩሳሌሙ ኤጲስቆጶስ አባ ቄርሎስ ዘንድ በመሄድ መመንኮስ እንደሚፈልግ ነገራቸው፡፡ እርሳቸውም በአባ ኪርያቆስ አማካኝነት የብዙዎች ነፍሳት ብሩሃን እንደሚሆኑ ትንቢት ተናገሩለትና የመነኮሳት አባት ወደሚሆን ወደ ክቡር አባ ሮማኖስ ላኩት፡፡ አባ ሮማኖስም በደስታ ተቀብለው አመነኮሱትና የሰይጣንን የማሰናከያ መንገዶች ሁሉ ዘርዝረው አስተማሩት፡፡ አባ ኪርያቆስም በጸም በጸሎት በስግደት ተወስኖ እየተጋደለ በገዳሙ አባቶችን እያገለገለ ተቀመጠ፡፡ ከብዙ ተጋድሎውም በኋላ እግዚአብሔር የመፈወስን ሀብት ሰጠውና ብዙ ድውያንን የሚፈውሳቸው ሆነ፡፡ የትሩፋቱና የቅድስናው ዜና በሁሉም ቦታ በተሰማ፡፡

ከዚህም በኋላ ኢየሩሳሌሙ ኤጲስቆጶስ አባ ቄርሎስ የክብር ባለቤት የሆነ መንፈስ ቅዱስን መቅዶንዮስ ስላቀለለ አባ ቄርሎስ 150 እጅግ የከበሩና ቅዱሳን የሆኑ ሊቃውንት ኤጲስቆጶሳትን አንድነት ወደሚሰበስብበት ወደ ቁስጥንጥንያ በሚሄድ ጊዜ ይህን አባ ኪርያቆስን አስከትሎት ሄደ፡፡ እነርሱም በላያቸው ባደረ መንፈስ ቅዱስ ስም ተከራክረው ከሃዲ መቅዶንዮስን ረቱት፣ አስተምረው መክረው ዘክረው የማይመለስ ሆኖ ቢያገኙት አውግዘው ረግመው ለዩት፡፡ አባ ኪርያቆስም እግዚአብሔርን ሲያገለግል ኖሮ በመልካም ሽምግልና ሆኖ በዚህች ዕለት በሰላም ዐረፈ፡፡ ከዕረፍቱም በኋላ ከሥጋው ብዙ ድንቅ ድንቅ ተአምራት ተፈጽመው ታዩ፡፡ ቅዱስ ሥጋው በኢየሩሳሌም ካሉ ገዳማት በአንደኛው በክብር ይኖራል እርሱም በሕይወት ያለ ይመስላል እንጂ የሞተ አይመስልም፡፡ እስከዛሬ ድረስ ሥጋው አልተለወጠም ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄዱ ሁሉ ያዩታል፡፡ የሚያዩትም ሁሉ በቅርብ ቀን ያረፈ ይመስላቸዋል ነገር ግን አባ ኪርያቆስ ያረፈው ለደጋጎቹ ነገሥታት ለአኖሬዎስና ለአርቃዴዎስ አባታቸው በሆነ በታላቁ ንጉሥ በቴዎዶስዮስ ዘመን ነው፡፡ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

11 Nov, 14:26


+ + +
አቡነ መድኃኒነ እግዚእ፡- ከደጋግ ክርስቲያኖች ከቀሲስ ሰንበት ተስፋነ እና ከኅሪተ ማርያም በ1180 ዓ.ም በሥዕለት የተወለዱት አቡነ መድኃኒነ እግዚእ እጅግ አስደናቂ ገድልና ትሩፋት ያላቸው ጻድቅ ቢሆኑም ብዙው ሕዝበ ክርስቲያን እንደሚገባቸው መጠን ያላወቃቸው ታላቅ አባት ናቸው፡፡ መዘንጋታቸው እጅግ ከሚያስቆጩን አባቶች መካከል ትልቁን ድርሻ የሚወስዱት የደብረ በንኮሉ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ናቸው፡፡ እስቲ ቀጥሎ ስማቸውን የጠቀስኳቸውን እነዚህን ቅዱሳን አባቶች ታሪካቸውንና የጽድቅ ሕይወታቸውን አስታውሱት፡- እነርሱም አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ፣ አቡነ ያሳይ ዘማንዳባ፣ አቡነ ሳሙኤል ዘቆየፃ፣ አቡነ ሳሙኤል ዘጣሬጣ፣ አቡነ ታዴዎስ ዘባልታርዋ፣ አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ ዘጉጉቤ እና አቡነ ዮሐንስ ዘጉራንቄ እነዚህን የመላእክትን ሕይወት በምድር የኖሩ ታላላቅ የሀገራችንን ቅዱሳን አስተምረውና አመንኩሰው ለጽድቅ ያበቋቸው አባት አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ናቸው፡፡

አቡነ መድኃኒነ እግዚእ እነዚህን ሰባቱን ቅዱሳን በአንድ ጊዜ ሲያመነኩሷቸው በዚያው ቅጽበት መንፈስ ቅዱስ ወርዶ ገዳሙን ደብረ በንኮልን በብርሃን አጥለቅልቆት ታይቷል፡፡ ከሰማይም የምስክርነት ድምፅ ተሰምቷል፡፡ በዚህም ምክንያት አንድ ላይ የመነኮሱት እነዚህ ሰባቱ ቅዱሳን ‹‹ሰባቱ ከዋክብት›› እየተባሉ ይጠራሉ፡፡ እነዚህም ሰባቱ ከዋክብት የጣናን ባሕር በእግራቸው ጠቅጥቀው ተሻግረው ብዙዎቹን ደሴቱ ላይ ያሉ አስደናቂ የጣና ገዳማትን የመሠረቱት ናቸው፡፡ ከእነርሱም ውስጥ ትልቅ ጠፍጣፋ ድንጋይን እንደጀልባ ተጠቅመው በእርሱ ላይ ሆነው ወደ ደሴት የገቡ አሉ፡፡ በእግራቸውም እየረገጡ ባሕሩን የተሻገሩ አሉ፡፡ በሌላም ቦታ በየብስ የተሰማሩትም ቢሆኑ መጻሕፍቶቻቸውን በአንበሳ ጭነው የተጓዙ አሉ፡፡

በደብረ ሊባኖሱ ሐዲስ ሐዋርያ የኢትዮጵያ ብርሃኗ በሆኑት በአቡነ ተክለ ሃይማኖት እጅ ከመነኮሱ በኋላ አቡነ መድኃኒነ እግዚእም በተራቸው ያስተማሯቸውና ያመነኮሷቸው መነኮሳት ቁጥራቸው በውል አይታወቅም፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖትም ለአቡነ መድኃኒነ እግዚእ ‹‹ስፍር ቁጥር የሌላቸው ከዋክብት ቅዱሳንን›› በመንፈስ ቅዱስ እንደሚወልዱ ትንቢት ተናግረውላቸው ነበር፡፡ የተንቤኑን አቡነ ዐቢየ እግዚእን፣ የዞዝ አምባውን አቡነ አብሳዲን ጨምሮ አባታችን መድኃኒነ እግዚእ ብርሃን ሆነው በጣም ብዙ ቅዱሳንን የለኮሱ ታላቅ ጻድቅ ናቸው፡፡ በዚህም ምክንያት ‹‹ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን›› ይባላሉ፡፡

የአቡነ መድኃኒነ እግዚእ ልጆች ዛሬ ግሸን ላይ በክብር ተቀምጦ ሀገራችንን ከመዓት እየጠበቀ ያለውን የጌታችንን ቅዱስ መስቀል ያመጡትም እነርሱ ናቸው፡፡ ዐፄ ዳዊት በዘመናቸው ረኃብ ስለነተሳ የደብረ ቢዘኑን አቡነ ፊሊጶስን ከገዳማቸው አስጠርተው ‹‹ምን ባደርግ ይሻለኛል?›› ብለው አማከሯቸው፡፡ አቡነ ፊሊጶስም ‹‹የጌታችንን መስቀል ያስመጡ›› ብለው መከሯቸው፡፡ ንጉሡ ዐፄ ዳዊትም ከኢየሩሳሌም፣ ከቍስጥንጥንያና ከእስክንድርያ መንግሥታት ጋር ተጻጽፈው ዓሥሩን ታላላቅ ቅዱሳን መርጠው ይዘው ሄደው መስቀሉን መስከረም 10 ቀን አምጥተውታል፡፡ በጽድቅ ሥራቸውና ተአምራትን በማድረግ በወቅቱ ታዋቂ የነበሩትና ቅዱስ መስቀሉን ያመጡት ዐሥሩ ቅዱሳንም የደብረ ቢዘኑ አቡነ ፊሊጶስ፣ የጣና ደሴቱ አቡነ ኂሩተ አምላክ፣ የጣና ደሴቱ አቡነ እንድርያስ፣ አቡነ በትረ ማርያም፣ አቡነ ዮሐንስ፣ አቡነ ታዴዎስ፣ አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ፣ አቡነ ዘካርያስ፣ አቡነ ያሳይና አቡነ ቶማስ ናቸው፡፡

የአቡነ መድኃኒነ እግዚእ ተአምራታቸው እጅግ ብዙ ነው፡፡ አራዊት ሁሉ እንደሰው ያገለግሏቸው የነበር፡፡ ውኃ የሚያመላልስላቸውንና የሚያገለግላቸውን አህያ አንበሳ ቢበላባቸው በአህያው ምትክ አንበሳውን ድፍን 7 ዓመት ለገዳማቸው ውኃ አስቀድተውታል፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው፡- ለአባታችን ውኃ የሚያመላልስላቸውና የሚያገለግላቸው አንድ አህያ ነበራቸው፡፡ ውኃው የሚገኘው እርሳቸው ካሉበት በጣም እርቆ በእግር የ3 ሰዓት መንገድ ከተሄደ በኋላ ነው፡፡ ነገር ግን አህያቸው እንደ ሰው እየተላላካቸው ይቀዳላቸው ነበር፡፡ አንድ ግን ከመንገድ አንበሳ አግኝቶት ግማሽ አካሉን በልቶት ሄደ፡፡ አባታችንም የአህያቸውን ተረፈ በድን አግኝተው በማዘን ‹‹ውኃ የሚያመላልስልኝ ረዳቴ ይህ አህያ ብቻ ነበር፣ አሁንም አህያዬን የበላህ አውሬ እንድታነጋግረኝ እፈልጋለሁ›› ቢሉ በአንበሳ ተበልቶ የሞተው የአህያው ግማሽ አካል አፍ አውጥቶ አንድ አንበሳ እንደበላው ነገራቸው፡፡ አቡነ መድኃኒነ እግዚእም በዚህ እጅግ ደስ ተሰኝተው ፈጣሪያቸውን ካመሰገኑ በኋላ አህያቸውን የበላውን አንበሳ ከጫካው ውስጥ ጮኸው ጠሩት፡፡ አንበሳውም ከሌሎቹ አንበሳ ተለይቶ ወደ እርሳቸው በመምጣት እግራቸው ሥር ወድቆ ሰገደ፡፡ አባታችንም ‹‹አህያዬን የበላኸው አንተ ነህን?›› ብለው ሲጠይቁት አንበሳውም በሰው አንደበት ‹‹አዎ እኔ ነኝ›› አላቸው፡፡ እርሳቸውም ፈጣሪያቸውን በድጋሚ ካመሰገኑ በኋላ አንበሳውን ‹‹በል ና ተከተለኝ በአህያዬ ምትክ ታገለግለኛለህ›› አሉት፡፡ አንበሳውም ተከትሏቸው ወደ በዓታቸው በመግባት ለ7 ዓመታት እንደ አህያቸው ውኃ እየቀዳ አገልግሏቸዋል፡፡ የአንበሳው ቆዳ ዛሬም በገዳማቸው ደብረ በንኮል በክብር ተቀምጠቷል፡፡

አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባንም አመንኩሰው መርቀው ሲሸኟቸው እንዲያገለግሏቸው አንበሶችን ከጫካ ጠርተው ያዘዙላቸው አባታቸው አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ናቸው፡፡ የዋልድባው አቡነ ሳሙኤል አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ከመነኮሱ በኋላ በደብረ በንኮል 12 ዓመት አባታችንን ሲያገለግሉ ከቆዩ በኋላ እሳት እስከማያቃጥላቸው ድረስ ከብቃት ደረጃ ላይ ሲደርሱ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ መርቀው በማሰናበት በዓት እንዲያጸኑ ሲያደርጓቸው አቡነ ሳሙኤል በቅዱስ ሚካኤል መሪነት ጣና ደሴት ገብተው ሱባኤ ያዙ፡፡ በዚያም ሳሉ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ማረፋቸውን በመንፈስ ዐውቀው ሲያለቅሱ ጌታችን የአቡነ መድኃኒነ እግዚእን ነፍስ በእቅፉ አድርጎ ወደ ገነት ሲያሳርጋት አሳያቸው፡፡ ወዲያውም ጌታችን በብርሃን ሰረገላ አድርጎ አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባን ደብረ በንኮል አድርሷቸዋል፡፡ በዚያም እስከ 40ኛው ቀን ከቆዩ በኋላ በዚሁ ዕለት ሲቀድሱ ክንድ ከስንዝር ከመሬት ከፍ ብለው ቅዱሳን ሐዋርያት እየተራዱዋቸው ከቀደሱ በኋላ ወደነበሩበት መልሷቸዋል፡፡ የጻዲቁ የአቡነ መድኃኒነ እግዚእ ዕረፍታቸው ኅዳር 3 ቀን 1360 ዓ.ም ሲሆን ጠቅላላ ዕድሙያቸውም 180 ዓመት ነው፡፡

ዐፄ ፋሲል ጻድቁ የተከሏቸውን የጥድ ዛፎች በሙሉ ተቆርጠው የአክሱም ቤ/ክ እንዲሠራበት አዋጅ አወጁና መልእክተኞች መጥተው ዛፎቹን ሲቆርጡ መነኮሳቱ ግን ‹‹ጻድቁ አባታችን የተከሏቸው የጥድ ዛፎች መቆረጥ የለባቸውም›› ብለው ቢከራከሩም ሰሚ አላገኙም፡፡ መነኮሳቱም ወደ እግዚአብሔር ቢያመለክቱ ጩኸታቸው ተሰምቶላቸው ወዲያው እየተቆረጡ ያሉት የጥድ ዛፎች በሙሉ በተአምራት ወደ ወይራ ዛፍነት ተለወጡ፡፡ የወይራ ዛፎቹም ለዐፀድ እንጂ ለሕንፃ የማይመቹ ጎባጣ ሆኑ፡፡ የዚህም ምልክቱ ዛሬም ድረስ አለ፡፡ ግንዱ ጥድ ዛፉ ግን ወይራ የሆነ ትልቅ ዛፍ ‹‹ወይራ ዘገብረ ተአምር›› በሚባል ቦታ አሁንም ድረስ ቆሞ ይታያል፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

11 Nov, 14:26


ጻድቁ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ በ1312 ዓ.ም የመሠረቱት ገዳማቸው ደብረ በንኮል ከአክሱም በእግር ሦስት ሰዓት ያስኬዳል፡፡ ይኸውም በንግሥተ ሳባ ቤተ መንግሥት አድርጎ የቀዳማዊ ሚኒሊክን መቃነ መቃብር አልፎ በመሄድ ነው፡፡ ወይም በመኪና ለመጓዝ አክሱም ጉበዱራን አቋርጦ ውቅሮ ማራይ ከተማን አልፎ በስተ ሰሜን አቅጣጫ 10 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ በስተ ምዕራብ የአቡነ አላኒቆስ ዘማይበራዝዮን ገዳም፣ በስተ ምሥራቅ የአቡነ ሰላማን ገዳም እየተለመከቱ እንደተጓዙ ጥቅጥቅ ባለ ደን የተሸፈነውን ደብረ በንኮልን ያገኙታል፡፡ ኅዳር 20 ጻድቁ ስለሚነግሱ ገዳሙም ለአክሱም ቅርብ ስለሆነ ይህ ለአክሱም ጽዮን ተጓዦች ተጨማሪ ትልቅ በረከት ነው፡፡
ደብረ በንኮል ማለት ‹‹ሙራደ ቃል›› ማለት ነው፡፡ ትርጉሙም የምሥጢር መውረጃ ማለት ነው፡፡ በቦታው ላይ ሱባኤ ለያዘ ሰው እንደ ቅዱስ ያሬድና እንደ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ምሥጢር እንደሚገለጥለት የሚጠቁም ነው፡፡ በ14ኛው መ/ክ/ዘ የነበሩት ደጋግ መነኮሳት ሕይወታቸውን በሙሉ በምንኩስና፣ በጸሎትና በታላቅ ተጋድሎ መኖር ሲፈልጉ ከደብረ ዳሞ፣ ከሐይቅ እስጢፋኖስ፣ ከደብረ ሊባኖስና ከሌሎቹም የሀገራችን ክፍሎች እየተነሡ ወደ ደብረ በንኮል አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ገዳም ነበር የሚሄዱት፡፡
የአቡነ መድኃኒነ እግዚእ ቃልኪዳን፡- ጻድቁ ባርከው ያፈለቁት ጸበላቸው ላበደ ሰው መድኃኒት ነው፡፡ ከመቃብራቸው ላይ የሚነሣውን አፈር ጻድቁ ባርከው ባፈለቁት ጸበላቸው ታሽቶ በእጃቸው መስቀል ተባርኮና ታሽቶ የሚዘጋቸውን የአቡነ መድኃኒነ እግዚእን እምነታቸውን በእምነት ሆኖ የያዘን ሰው ንብረቱን ሌባ ቀማኛ ዘራፊ አይሰርቀውም፤ የመኪና አደጋ አይደርስበትም፤ ጥይት አይመታውም፡፡ ‹‹በእምነት ሆኖ የያዘን ሰው›› መባሉን ልብ ይሏል፡፡ ይኸውም ለጻድቁ የተሰጣቸው ታላቅ ቃልኪዳን ነው፡፡
የአቡነ መድኃኒነ እግዚእ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን!

+ + +
አቡነ ፍሬ ካህን፡- ጻድቁን በመጀመሪያ ከጎጃም ተነሥተው በታዘዘ መልአክ መሪነት ትግራይ ደብረ በንኮል አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ገዳም ሄደው መንነው መነኮሱ፡፡ ጻድቁ ስድስት ክንፍ የተሰጣቸው ሲሆኑ በታላቅ መንፈሳዊ ተጋድሎ ይታወቃሉ፡፡ አቡነ ፍሬ ካህን ወንጌልን ሲሰብኩ ሙታንን እያስነሡ በሲኦል ውስጥ ስላለው መከራና ሥቃይ እንዲመሰክሩ ያደርጓቸው ነበር፡፡ ጻድቁ ሐይዳ ገዳም ታቦት ተቀርጾላቸው ገድል የተጻፈላቸው ቢሆንም ሙሉ ገድላቸው ታትሞ ለምእመኑ አልተዳረሰም፡፡ አቡነ ቶማስ ካረፉ በኋላ አቡነ ፍሬ ካህን ገዳማቸውን ተረክበው በጽድቅ መንገድ መነኮሳቱን አስተዳድረዋል፡፡ አቡነ ፍሬ ካህን አፈር ከኢየሩሳሌም አምጥተው ዋልድባ ሲደርሱ መነኮሳቱ ‹‹ገዳሙን በአህያ አታስረግጥ›› ቢሏቸው አህዮቹን ክንፍ አውጥተው እንዲበሩ አድርገዋቸዋል፡፡

አባታችን ሽሬ ደብረ ሐይዳ አቡነ ፍሬ ካህን የተባለ ትልቅ ገዳም አላቸው፡፡ ገዳሙ ከአቡነ ቶማስ ዘሐይዳ ገዳም ጋር አንድ ነው፡፡ ወደዚህ ገዳም ውስጥ ሥጋና ቅቤ ተበልቶም ሆነ ተይዞ መውጣት ፈጽሞ አይቻልም፡፡ አልታየሁም ተብሎ በድብቅ ሥጋ ተይዞ ቢገባ ሥጋው ይተላል፡፡ ሥጋና ቅቤ የበላ ሰውም ዕለቱን በድፍረት ወደ ገዳሙ ቢገባ ሆዱ በኃይል ይነፋል በዚህም ይታወቅበታል፡፡ ከብቶችም ቢሆኑ ወደ ገዳሙ አይወጡም፣ ማንም ሳይመልሳቸው ራሳቸው ይመለሳሉ፡፡ የአቡነ ፍሬ ካህን ዕረፍታቸው ኅዳር 3 ነው፡፡
የአቡነ ፍሬ ካህን ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን!

+ + +

ጻድቁ ንጉሥ ቅዱስ ነዓኵቶ ለአብ፡- ከላስታ (ከዛጉዌ) ነገሥታት መካከል ቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ፣ ቅዱስ ገብረ ማርያም፣ ቅዱስ ላሊበላና ቅዱስ ነአኵቶለአብ እነዚህ አራቱ ነገሥታት እንደ መልከጼዴቅ (ዘፍ 14፡18) ክህነትን ከንግሥና፣ ቅድስናን ከንጽሕና ጋር አንድ አድርገው በመያዝ እግዚአብሔርንም ሰውንም በቅድስና አገልግለው አልፈዋል፡፡ በንግሥናቸው አገርን በመልካም ሥራና በቅድስና ከማስተዳደራቸው በተጨማሪ ቅዱሳን ጻድቃን ሆነው እግዚአብሔርን በብዙ ድካም በመልካም ተጋድሎአቸው ያገለገሉና አገልግሎታቸውም ሆነ ቅድስናቸው በእግዚአብሔር ዘንድ የተመሰከረላቸው ቅዱሳን ናቸው፡፡ ከእነርሱም ውስጥ ሞትን ሳያይ እንደነ ሄኖክና ኤልያስ የተሰወረ አለ፤ ከእነርሱም ውስጥ በባሕር ላይ ቤተ መቅደሱን ያነጸ አለ፤ ከእነርሱም ውስጥ የታዘዘ መልአክ መጥቶ ወደ ሰማይ ነጥቆ ወስዶት የቤተ መቅደሶቹን አሠራር ራሱ ጌታችን በቃሉ ያስረዳው አለ፡፡ ከእነርሱም ውስጥ በክህነቱ ሲቀድስ 40 ዓመት ሙሉ ቅዱስ ቁርባኑን መላእክት ከሰማይ እያመጡለት የነበረ አለ፡፡ እነዚህ ቅዱሳን ነገሥታት ገድላቸውና ትሩፋታቸው፣ ምግባር ሃይማኖታቸው እጅግ ድንቅ ነው፡፡
የእነዚህ ቅዱሳን ነገሥታቱን የዘር ሐረጋቸው ከሰሎሞን ዘር ሲያያዝ የመጣ ነው፡፡ ከ10ኛው እስከ 13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን (920-1253 ዓ.ም ገደማ) በላስታ ቡግና ምድር የነገሡ የላስታ ቡግና ተወላጅ የሆኑ የኢትዮጵያ ቅዱሳን ነገሥታት የንግሥናቸው መጠሪያ ‹‹የዛጉዌ ሥርወ መንግሥት›› ወይም ‹‹የላስታ መንግሥት›› በመባል ይታወቃል፡፡ ከዛጉዌ ነገሥታት ውስጥ የመጀመሪያው ንጉሥ መራ ተክለሃይማኖት የዐፄ ድልነአድን ልጅ መሶበወርቅን አግብቶ አራት ልጆችን ወልዷል፡፡ ሦስቱ ወንዶች ጠንጠውድም፣ ግርማ ስዩምና ዣን ስዩም ይባላሉ፡፡ ጠንጠውድም ገብረ መስቀልን ወለደ፣ ግርማ ስዩም ቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ ወለደ፣ ዣን ስዩም ደግሞ ቅዱስ ገብረማርያምንና ቅዱስ ላሊበላን ወለደ፡፡ ገብረ መስቀልም ጣራው ክፍት ሆኖ ዝናብ የማያስገባውን ገዳም መሠረቱትን የዘመቄቱን ታላቁን አባት አቡነ አሮንን ወለደ፡፡ ቅዱስ ገብረማርያም ደግሞ ቅዱስ ነዓኵለአብን ወለደ፡፡ ይኸውም ቅዱስ ነዓኵ ለአብ በዛሬዋ ዕለት ሞትን ሳያይ እንደነ ሄኖክና ኤልያስ የተሰወረ ነው፡፡
‹‹ነዓኵቶ ለአብ›› ማለት የስሙ ትርጓሜ ‹‹እግዚብሔር አብን እናመስግነው›› ማለት ነው፡፡ የቅዱስ ላሊበላ የወንድም ልጅ ሲሆን ከ11ዱ የዛጉዌ ነገሥታት ውስጥ 10ኛው ነው፡፡ አባቱ ቅዱስ ገብረ ማርያም ሥልጣኑን ለወንድሙ ለቅዱስ ላሊበላ ትቶ በመመንኮስ በበዓት ተወስኖ በጾም በጸሎት ሲጋደል ጌታ ተገልጾለት ‹‹ክብሩ እንደ መላእክት የሆነ ልጅ ትወልዳለህና ወደቤትህ ተመለስ›› ብሎ አዘዘው፡፡ ንጉሡ ገብረማርያምም ‹‹40 ዓመት ስነግሥ ያልወለድኩትን አሁን ዓለም በቃኝ ስል ትወልዳለህ የተባልኩት ልጅ ምን ዓይነት ልጅ ይሆን!›› እያለ ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡ ሚስቱን መርኬዛንም መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ካበሰራት በኋላ ነአኵቶለአብ ጌታ በተወለደበት ዕለት ታኅሳስ 29 ቀን ተወለደ፡፡ ቅዱስ ላሊበላም ቀደም ብሎ የተወለደው እንዲሁ በጌታ የልደት ቀን ታኅሳስ 29 ቀን 1101 ዓ.ም ነው፡፡

መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ነአኵቶ ለአብ እንደሚወለድ ቀድሞ ለንጉሥ ላሊበላ ነግሮት ነበርና እንደነገረውም እርሱ ሲወለድ ‹‹ያ የነገርኩህ ሕፃን ተወልዷልና ወስደህ በሃይማኖት አንጸህ አሳድገው›› ብሎታል፡፡ ቅዱስ ላሊበላም ሃይማኖቱን ጠንቅቆ እያስተማረ በእንክብካቤ አሳደገው፡፡ ግብፅ ሄዶ ከአቡነ ቄርሎስ ዲቁናን ተቀበለ፡፡ በኋላም ቅስናን ተቀበለ፡፡ ቅዱስ ላሊበላ ቤተ መቅደሶቹን ሠርቶ ከጨረሰ በኋላ በሕይወት ሳለ መንግሥቱን ስላወረሰው ከላሊበላ በኋላ ነግሦ ኢትዮጵያን ለ40 ዓመት (ከ1197 ዓ.ም-1237 ዓ.ም) ድረስ መርቷል፡፡ ዕድሜው ሲደርስ መልአኩ ሚስት እንዲያጭለት ለቅዱስ ላሊበላ ነግሮት ሲያጭለት እግዚአብሔርን በድንግልና ማገልገል ይፈልግ ነበርና በዚህም እጅግ ሲያዝን

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

11 Nov, 14:26


የዐባይን በጸሎቱ ገዝቶ ያቆመው ጻድቁ ንጉሥ ቅዱስ ነአኵቶ ለአብ!

ረድኤት በረከቱ ይደርብንና በዛሬዋ ዕለት እንደነሄኖክና ኤልያስ ከሞት የተሰወረው ጻድቁ ንጉሥ ቅዱስ ነዓኵቶ ለአብ ከኢትዮጵያ ወጥቶ እንዳይሔድ የዓባይን ወንዝ በጸሎቱ በማቆም ያደረገው ድንቅ ተአምር ይህ ነው፡- ‹‹ግብፃውያን ለአባቱ ለቅዱስ ላሊበላ ለመንግሥቱ እጅ መንሻ ግብር ብዙ ወርቅና ብር እያመጡ ይሰጡት ነበር፡፡ ነገር ግን ቅዱስ ላሊበላ በሕይወት ሳለ መንግሥቱን ለቅዱስ ነዓኵቶ ለአብ ካወረሰው በኋላ በቅዱስ ነዓኵቶ ለአብ ዘመን ለኢትዮጵያ መንግሥት ያስለመዱትን እጅ መንሻ ማምጣትን አቋረጡ፡፡ የገድሉን ማማርና ጽድቁን ሳያውቁ እጅ መንሻውንና ግብሩን ከለከሉ፣ ለመንግሥቱም አልተገዙ፡፡ በእርሱም ላይ ያመጹ እነዚህ የግብፅ ሰዎች ከዓባይ ወንዘ ውሃ በቀር ዝናብን አያውቁም፡፡

ቅዱስ ነዓኵቶ ለአብም የአባቱን ልማድ ስላስቀሩና ክብሩንም ስላቃለሉ 3 ዓመት ከ3 ወር ያህል የዓባይን ወንዝ በጸሎቱ ኃይል አቆመው፡፡ ግብፃዊያንም የሚጠጡትና የሚዘሩበት ውሃን ፈጽመው አጡ፡፡ እህልና ውሃም በማጣት በድርቅ ተመቱ፡፡ ሰዎቻቸውና እንስሶቻቸውም አለቁ፡፡ በዚህም ጊዜ እርስ በእርሳቸው ‹‹…ይህ የከፋ መቅሰፍት ያጋጠመን በምንድነው?›› ብለው ሲመካከሩ በዚያ የሚኖር አንድ ሰው ስሙ ማማስ የሚባል ‹‹ይህች የከፋች መከራ ያገኘችን የዚያን የሕፃኑን የቅዱስ ላሊበላን ልጅ የቅዱስ ነዓኵቶ ለአብን እጅ መንሻውን ስለከለከልነው ለመንግሥቱም ስላልተገዛን ነው›› አላቸው፡፡ ግብፃዊያኑም ‹‹ምን ብናደርግ ከዚህ ረኀብና መከራ እንድናለን?›› አሉት፡፡ ማማስም ‹‹እጅ መንሻውን ስጡ፣ ለመንግሥቱም ተገዙ፣ በከተማውም ውስጥ ገብታችሁ ለፈጣሪው ስገዱ›› አላቸው፡፡ እነርሱም በወርቅ የተለበጡ ልዩ ልዩ ስጦታዎችን የመንግሥቱንም እጅ መንሻ የ6 ዓመቱንም ጨምረው ይዘው ወደ ቅዱስ ነዓኵቶ ለአብ መጥተው ሰግደው ስጦታቸውን ሰጥተው ይቅር ይላቸው ዘንድ እያለቀሱ ለመኑት፡፡ እርሱም ‹‹የሠራችሁትን በደላችሁን ክፉ ሥራችሁን ሁሉ እግዚአብሔር ይቅር ይበላችሁ›› አላቸው፡፡ በወንጌል ቃል ጨውነት የጣፈጠ የተባረከ አንደበቱ ይህን በተናገረ ጊዜ ለ3 ዓመት ከ3 ወር ቆሞ የነበረው የዓባይ ወንዝ ከግዝቱ ተፈቶ በሰላም መፍሰስ ጀመረ፡፡ በአገራቸውም ንውጽውጽታ ሆነ፣ ልቅሶአቸውም ወደ ደስታ ተቀየረ፡፡ ረኀብና ችግራቸውም ወደ ጥጋብ ተለወጠ፡፡ ግብፃዊያኑም በቅዱስ ነዓኵቶ ለአብ በጸሎቱ ኃይል አመኑ፡፡ መንፈስ ቅዱስን የተመላ ዳግማዊ ኤልያስን ሆኖ አግኝተውታልና፡፡

ቅዱስ ነአኵቶ ለአብ ክህነትን ከንግሥና ቅድስናን ከንጽሕና ጋር አስተባብረው ይዘው ኢትዮጵያን ከመሩ ከአራቱ የዛጉዌ ነገሥታት አንዱ ሲሆን በነገሠበት 40 ዓመት ሙሉ ዓርብ ዓርብ ቀን የክርስቶስን ሕማም እያሰበ በዕንቁና በወርቅ በተሽቆጠቆጠው ዘውዱ ፈንታ የእሾህ አክሊልን ደፍቶና በአምስቱ ቅንዋተ መስቀሎች ምሳሌ አምስት ጦር ዙሪያውን ተክሎ እያለቀሰ ይጸልይና ይሰግድ ነበር፡፡

ጌታችንም በመጨረሻ ለቅዱስ ነአኵቶ ለአብ ተገልጦለት ‹‹...እውነት እልሃለው 40 ዓመት ሙሉ እንባህን ያፈሰስክባት ይህች ምድር እስከ ዕለተ ምጽአት እያነባች ትኖራለች፣ ይኸውም የእኔን መከራ እያሰብክ ከዐይንህ ዕንባ ሳይቋርጥ እንዳለቀስክልኝ ሁሉ ከቤተ መቅደስህ በእንባ መልክ የሚንጠባጠብ ጠበል ይፍለቅልህ፣ ይህም የዕንባህ ምሳሌ ነው፤ ከዚህ ለሚጠጡ ለሚጠመቁ ድኅነት ይሁናቸው›› የሚል የምሕረት ቃልኪዳን ሰጥቶታል፡፡ ጌታችን ይህን አስገራሚ ቃልኪዳን ከሰጠው በኋላ ቅዱስ ነአኵቶ ለአብን በሞት ፈንታ እንደነ ሄኖክና ኤልያስ ኅዳር 3 ቀን ሰውሮታል፡፡ በቃልኪዳኑም መሠረት ብዙ ፈውስን የሚሰጠው ጠበሉ ዛሬም ድረስ ልክ እንደሰው ዕንባ ቤተ መቅደሱ ካለበት ዋሻ ላይ እየተንጠባጠበ ወደ ታች ይወርዳል፣ ምንም እንኳን ከዋሻው በላይ ያለው መሬት ሜዳ ቢሆንም ቃልኪዳኑ ነውና የጠበሉ መጠን ክረምት ከበጋ አይጨምርም አይቀንስም፡፡ ይልቁንም በሰው ዕንባ መጠን ጠብ ጠብ እያለ በመውረድ ከእርሱ ለሚጠመቁት ፈውስን እየሰጠ ይገኛል፡፡
ጌታችን በዛሬው ዕለት ከሞት ለሰወረው ለቅዱስ ነአኵቶ ለአብ "በንግሥና ሳለህ 40 ዓመት ሙሉ የእኔን መከራ አስበው እንባህን ያፈሰስክባት ይህች ምድር እንደ አንተ እስከ ዕለተ ምጽአት እያነባች ትኑር፣ ከቤተ መቅደስህ በእንባ መልክ የሚንጠባጠብ ጠበል ይፍለቅልህ" ባለው አምላካዊ ቃሉ መሠረት የእንባው አምሳያ የሆነው ፈዋሽ ጠበል በዚህ በፎቶው ላይ በሚታየው ማጠራቀሚያ ላይ እንደ እንባ ጠብ ጠብ እያለ ይወርዳል፡፡
የቅዱስ ነአኵቶ ለአብ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!

ዳግመኛም በዚኽች ዕለት ኅዳር 3 ቀን፡-
+ እነ አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባን አስተምረው ያመነኮሱትና ውኃ ይቀዳላቸው የነበረውን አህያቸውን አንበሳ ቢበላባቸው በአህያው ምትክ አንበሳውን 7 ዓመት ለገዳማቸው ውኃ ያስቀዱት የደብረ በንኮሉ ታላቁ አባት አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ዕረፍታቸው ነው፡፡
+ አፈር ከኢየሩሳሌም አምጥተው ዋልድባ ሲደርሱ መነኮሳቱ ‹‹ገዳሙን በአህያ አታስረግጥ›› ቢሏቸው አህዮቹን ክንፍ አውጥተው እንዲበሩ ያደረጉት አቡነ ፍሬ ካህን ዕረፍታቸው ነው፡፡
+ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ሰማያዊ መና ሲመግባቸውና የጌታችንንም ቅዱስ ሥና ደም በሰንበት እያመጣለቸው ያቆርባቸው የነበሩት ሰማዕቱ አቡነ ዓምደ ሚካኤል ዕረፍታቸው ነው፡፡

ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

11 Nov, 14:26


እመቤታችን ተገልጻለት ጋብቻው ከእግዚአብሔር መሆኑን ነግራ አጽናንታዋለች፡፡ ‹‹የጌታህ ፈቃድ ነውና አትዘን ይልቁንም አግባ፣ ክብርህም ከደናግላን አያንስም›› ብላ ስለነገረችው ሚስት ቢያገባም ልክ እንደ ቅዱስ ዲሜጥሮስና ልዕልተወይን ንጽሕናቸውንና ድንግልናቸውን ለመጠበቅ በመማከር በግብር ሳይተዋወቁ ለ25 ዓመታት በድንግልና ሆነው በትዳር ኖረዋል፡፡ እህት ወንድሞች ሆይ እስቲ ልብ በሉ! በሕግ ካገባት ሚስቱ ጋር ለዚያውም በእመቤታችን ትእዛዝ አግብቶ ሳለ በግብር ሳያውቃት አብሮ ከድንግል ሴት ጋር በትዳር 25 ዓመት መኖር ይህ እንዴት ያለ ቅድስና ነው በእውነት!!!
ከዚህ በኋላ መልአክ መጥቶ ‹‹በንጽሕና የተጋባችሁት ልትወልዱ ነው እንጂ ዝም ብላችሁ ልትኖሩ አይደለም›› ብሏቸው አንድ ቀን ብቻ በግብር ተዋወቁና እጅግ የሚያምርና የሚያሳሳ ልጅ ወለዱ፡፡ ልጁም እጅግ የሚያምርና የሚያሳሳ ቢሆንም ንጉሡ ቅዱስ ነአኵቶለአብ ግን በእግዚአብሔር መንፈስ የወደፊቱን ያውቅ ነበርና ሱባኤ ገብቶ ‹‹በእኔ እግር ተተክቶ ሲነግሥ ፍርድ አጣሞ አንተንም ሰውንም ከሚበድል ይህን ልጄን ቅሰፍልኝና ሄሮድስ ካስፈጃቸው ሕፃናት ጋር ደምርልኝ›› በማለት ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፡፡ እንደጸሎቱም ጌታችን የካቲት 16 ቀን ልጁን በሰላም አሳርፎለት ሄሮድስ ካስፈጃቸው ሕፃናት ጋር ደምሮለታል፡፡ በዚህም ጊዜ መኳንንቶቹ፣ መሳፍንቶቹና ሕዝቡ ሁሉ ለልቅሶ ቢመጡ እርሱ ግን በቤተ መንግስቱ በልቅሶ ፈንታ ታላቅ የደስታ ድግስ አድርጎ ስለጠበቃቸው ‹‹የንጉሡ ልጅ ሞተ የተባለው ውሸት ነው›› ብለዋል፡፡

ቅዱስ ነአኵቶ ለአብ ክህነትን ከንግሥና ቅድስናን ከንጽሕና ጋር አስተባብረው ይዘው ኢትዮጵያን ከመሩ ከአራቱ የዛጉዌ ነገሥታት አንዱ ሲሆን በነገሠበት 40 ዓመት ሙሉ ዓርብ ዓርብ ቀን የክርስቶስን ሕማም እያሰበ በዕንቁና በወርቅ በተሽቆጠቆጠው ዘውዱ ፈንታ የእሾህ አክሊልን ደፍቶና በአምስቱ ቅንዋተ መስቀሎች ምሳሌ አምስት ጦር ዙሪያውን ተክሎ እያለቀሰ ይጸልይና ይሰግድ ነበር፡፡ በዙፋኑም ላይ ለፍርድ በተቀመጠ ጊዜ ከንግሥና ልብሱ ውስጥ በስውር ማቅ ለብሶና ሰውነቱን በሰንሰለት አስሮ ከላይ ግን በክብር ልብሱ ተሸፍኖና በወርቅ ወንበር ተቀምጦ ይፈርድ ነበር፡፡ ፍርድ ሲሰጥም ሁሉንም ነገር በመንፈስ ቅዱስ እያውቅ ነበር፡፡ ምስክሮችን አይሻም ይልቁንም ሰዎቹ ገና ሳይመጡ ሌሊት በምን ወንጀል ተካሰው እንደሚመጡ በመንፈስ ይገለጽለት ነበር፡፡ ወደ እርሱም በመጡ ጊዜ እነርሱ ጉያቸውን ከመናገራቸው በፊት እርሱ አቀድሞ አስማምቶ በጽድቅ ፈርዶላቸው ወደየመጡበት ይመልሳቸዋል፡፡ ሰዎቹም ‹‹…ይህስ በእውነት የመንፈስ ቅዱስ ፍርድ እንጂ የሰው ፍርድ አይደለም›› እያሉና እያደነቁ ይመለሳሉ፡፡

ጻዲቁ ቅዱስ ነአኵቶ ለአብ በዘመኑ ግብፆች ‹‹ግብር አንሰጥም›› ብለው ስላመፁበት የዓባይን ወንዞች በጸሎቱ ወደ ሌላ ቦታ እንዲፈስ ስላደረገባቸው ግብፆች ከበፊቱ ጨምረው ግብራቸውን አምጥተው ሰጥተውት ግዝቱን አንስቶላቸዋል፡፡

ቅዱስ ነአኵቶ ለአብ መላ ዘመኑን ሁሉ የክርስቶስን መከራ እያሰበ ያለቅስ ስለነበር የመድኃኔዓለምን መራራ ሐሞት መጠጣት እያሰበ ሁልጊዜ ዓርብ ዓርብም ኮሶ ይጠጣ ነበር፡፡ በመጨረሻም ውለታን የማይረሳ አምላክ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ተገልጦለት እንዲህ አለው፡- ‹‹ወዳጄ ነአኵቶ ለአብ ሆይ! እኔ ለዓለም ደሜን ያፈሰስኩት አንድ ቀን ነው፤ አንተ ግን 40 ዓመት ሙሉ ስለ እኔ ብለህ ደምህንንና እንባህን ስታፈስ ኖርክ፣ ይበቃሃል አሁን ወደ እኔ ልወስድህ ነው›› አለው፡፡ ቅዱስ ነአኵቶ ለአብም ጌታችንን ‹‹ጌታዬ ሆይ! እዚህ ቦታ እኔን ብለው የሚመጡ ወገኖቼን ማርልኝ›› አለው፡፡ ጌታችንም ‹‹እውነት እልሃለው ከተፀነስክበት ቀን ጀምሮ እስካሁን ድረስ ያለውን ገድልህን እያነበበ ዝክርህን የዘከረውን፣ በዓልህን ያከበረውን፣ ለቤተ ክርስቲያንህ መባ ያገባውን ሁሉ ኃጢአቱ ቢበዛም ‹ቅዱስ ነአኵቶ ለአብ አማልደኝ› ያለውን ኃጢያቱ ምን ቢበዛ እምርልሃለው፤ ዳግመኛም እልሃለው 40 ዓመት ሙሉ እንባህን ያፈሰስክባት ይህች ምድር እስከ ዕለተ ምጽአት እያነባች ትኖራለች፣ ይኸውም የእኔን መከራ እያሰብክ ከዐይንህ ዕንባ ሳይቋርጥ እንዳለቀስክልኝ ሁሉ ከቤተ መቅደስህ በእንባ መልክ የሚንጠባጠብ ጠበል ይፍለቅልህ፣ ይህም የዕንባህ ምሳሌ ነው፤ ከዚህ ለሚጠጡ ለሚጠመቁ ድኅነት ይሁናቸው›› የሚል የምሕረት ቃልኪዳን ሰጥቶታል፡፡ ጌታችን ይህን አስገራሚ ቃልኪዳን ከሰጠው በኋላ ቅዱስ ነአኵቶ ለአብን በሞት ፈንታ እንደነ ሄኖክና ኤልያስ ኅዳር 3 ቀን ሰውሮታል፡፡ በቃልኪዳኑም መሠረት ብዙ ፈውስን የሚሰጠው ጠበሉ ዛሬም ድረስ ልክ እንደሰው ዕንባ ቤተ መቅደሱ ካለበት ዋሻ ላይ እየተንጠባጠበ ወደ ታች ይወርዳል፣ ምንም እንኳን ከዋሻው በላይ ያለው መሬት ሜዳ ቢሆንም ቃልኪዳኑ ነውና የጠበሉ መጠን ክረምት ከበጋ አይጨምርም አይቀንስም፡፡ ይልቁንም በሰው ዕንባ መጠን ጠብ ጠብ እያለ በመውረድ ከእርሱ ለሚጠመቁት ፈውስን እየሰጠ ይገኛል፡፡

የቅዱስ ነአኵቶ ለአብ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

10 Nov, 15:41


ከገድላት አንደበት-ke gedilat andebet
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ኅዳር 1- ክህነትን ከንግስና ቅድስናን ከንጽሕና ይዞ ኢትዮጵያን ለ40 ዓመት
በቅድስና ያስተዳደረ ጻድቁ ንጉሥ ቅዱስ ነአኵቶ ለአብ ልደቱ ነው፡፡
+ ከአፍራቅያ አገር የተገኙ መክሲሞስ፣ ማንፍዮስ፣ ፊቅጦርና ፊሊጶስ የተባሉ
ቅዱሳን በከሃዲው ንጉሥ በዳኬዎስ ዘመን በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡
ቅዱሳን ሰማዕታት መክሲሞስ፣ ማንፍዮስ፣ ፊቅጦርና ፊሊጶስ፡- ከአፍራቅያ አገር
የተገኙት እነዚህ ቅዱሳን በከሃዲው ንጉሥ በዳኬዎስ ዘመነ መንግሥት
ሰማዕትነታቸውን የፈጸሙ ናቸው፡፡ በዚህም ከሃዲ ንጉሥ በዳኬዎስ ዘመን ሰባቱ
ደቂቅ 372 ዓመት አንቀላፍተው የነቁት ከእርሱ በሸሹ ጊዜ ነው፡፡ እርሱ እጅግ
ክፉ ነበርና፡፡
ለስም አጠራሩ ክብር ይግባውና ንጉሥ ዳኬዎስ ጌታችንን ክዶ ጣዖትን
ማመለክና የክርስቲያኖችን ደም እንደ ውኃ ማፍሰስ በጀመረ ጊዜ እነዚህ ቅዱሳን
መስተጋድላን የክርስቲያኖቹን መከራ ሲያዩ እነርሱም ስለ ሃይማኖታቸው
መስክረው ሰማዕት ይሆኑ ዘንድ በምክር ተስማሙ፡፡ በአንድነትም ተሰብስበው
ወደ ንጉሥ ዳኬዎስ ዘንድ በመሄድ ‹‹እኛ በግልጽ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ
የምናምን ክርስቲያኖች ነን ለእርሱም እንሰግዳለን እናመልከዋለንም›› አሉት፡፡
ንጉሥ ዳኬዎስም ይህን ቃል ከቅዱሳኑ በሰማ ጊዜ እጅግ ተቆጣ፡፡ ወስዶም
በጅራፍ ታላቅ ግርፋንት አስገረፋቸው፡፡ ዳግመኛም በእሳት የጋሉ የብረት
በትሮችን ወስደው እንዲደበድቧቸው አዘዘ፡፡ እንዳዘዘውም በእሳት በጋሉ በትሮች
ደበደቧቸው፡፡ ከዚህም በኋላ በበርኖስ እላቂ ጨርቅ ከመጻጻና ከጨው ነክረው
ቁስላቸውን አሹዋቸው፡፡ ሰማዕታቱም በዚህ እጅግ ተሠቃዩ፡፡ ነገር ግን አሁንም
የንጉሡን ትእዛዝ ባልሰሙ ጊዜ ሥቃዩንም ፈርተው ከእምነታቸው ፈቀቅ እንዳላሉ
ባየ ጊዜ ንጉሡ ቁጣን በማብዛት ጽኑ በሆኑ ልዩ ልዩ ሥቃዮች አሠቃያቸው፡፡
ሕዝቡም የሰማዕታቱን ትዕግስታቸውን ባዩ ጊዜ ‹‹እኛም በእነዚህ ቅዱሳን
አምላክ አምነናል›› እያሉ በጌታችን እየታመኑ በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡ ከሃዲው
ንጉሥ ዳኬዎስም በመጨረሻ የእነዚህንም ቅዱሳን ራስ ራሶቻቸውን በሰይፍ
አስቆረጣቸውና የሰማዕትነታቸው ፍጻሜ ሆነ፡፡
+ + +
ቅዱስ ነአኵቶ ለአብ፡- ‹‹ነአኵቶለአብ›› ብሎ ስሙን ያወጣለት መልአኩ ቅዱስ
ገብርኤል ነው፡፡ ዕድሜው ከፍ ሲል ጌታችን ለላሊበላ ተገልጦለት ሚስት
እንዲያጭለት ነግሮት ሚስት የታጨለት ቢሆንም ቅዱስ ነአኵቶ ለአብ ግን
እግዚአብሔርን በድንግልና ማገልገል ይፈልግ ነበርና ሚስት ካገባም በኋላ
ከሚስቱ ጋር ተማክሮ ሁለቱም ድንግልናቸውን ጠብቀው 25 ዓመት ሙሉ
በትዳር ውስጥ አብረው ነገር ግን በድንግልና ሆነው ኖረዋል፡፡
ከዚህም በኋላ መልአክ ተገልጦ ‹‹በንጽሕና የተጋባችሁት ልትወልዱ ነው እንጂ
ዝም ብላችሁ ልትኖሩ አይደለም›› ብሏቸው እነርሱም ፈቃደ እግዚአብሔር ከሆነ
ብለው አንድ ቀን ብቻ በግብር ተዋወቁና ልጅ ወለዱ፡፡ ልጁም እጅግ
የሚያምርና የሚያሳሳ ቢሆንም ንጉሡ ቅዱስ ነአኵቶለአብ ግን በእግዚአብሔር
መንፈስ የወደፊቱን ያውቅ ነበርና ሱባኤ ገብቶ ‹‹በእኔ እግር ተተክቶ ሲነግሥ
ፍርድ አጣሞ አንተንም ሰውንም ከሚበድል ይህን ልጄን ቅሰፍልኝና ሄሮድስ
ካስፈጃቸው ሕፃናት ጋር ደምርልኝ›› በማለት ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፡፡
እንደጸሎቱም ጌታችን የካቲት 16 ቀን ልጁን በሰላም አሳርፎለት ሄሮድስ
ካስፈጃቸው ሕፃናት ጋር ደምሮለታል፡፡
ይህ ጻዲቅ ንጉሥ በወርቅ ዘውዱ ፈንታ የእሾህ አክሊልን ደፍቶና በአምስቱ
ቅንዋተ መስቀሎች ምሳሌ አምስት ጦር ተክሎ ይሰግድና ሰውነቱን ይጎዳ ነበር፣
መላ ዘመኑንም የክርስቶስን መከራ እያሰበ ያለቅስ ነበር፡፡ በመጨረሻም ጌታችን
ተገልጦለት አስገራሚ ቃልኪዳን ሰጥቶት በሞት ፈንታ እንደነ ሄኖክና ኤልያስ
ሰውሮታል፡፡ ሙሉ ገድሉን አምላኩ ከጊዜው ያድርሰንና ጻድቁ በተሰወረበት ዕለት
ኅዳር 3 ቀን በስፋት እናቀርበዋለን፡፡
የጻድቁን ንጉሥ የቅዱስ ነአኵቶ ለአብን እና የቅዱሳን ሰማዕታቱ ረድኤት
በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን!
(ገድለ ቅዱስ ነአኵቶ ለአብ፣ ስንክሳር ዘወርሃ ኅዳር)

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

10 Nov, 15:41


ከገድላት አንደበት-ke gedilat andebet
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ኅዳር 2-ርኅራሄን የተመላች ክብርት እመቤታችን በስደቷ ወራት መጥምቁ
ዮሐንስ ገና የ7 ዓመት ሕፃን ሳለ በበረሃ እናቱ ኤልሳቤጥ በሞት ዐርፋበታለችና
በዚህ ጊዜ እመቤታችን የተወደደ ልጇን መድኃኔዓለምን ‹‹ጌታዬ ሆይ! ስለምን
ዮሐንስን ብቻውን ከበረሃ ውስጥ ትተወዋለህ?›› በማለት ለመጥምቁ ዮሐንስ
ምልጃን አቅርባለች፡፡
+ አረማውያን ስለቀናች ሃይማኖቱ ብዙ መከራ ያደረሱበት ለአባቶች ሊቃነ
ጳጳሳት 27ኛው የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳስ አባ ጴጥሮስ ዕረፍቱ ነው፡፡ እርሱም ቤተ
ክርስቲያንን የጠበቀ፣ ምእመናንን በሃይማኖት ያጸና ዘወትር መልአክትንም
ይጽፍላቸው የነበረ ነው፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!
+++
ርጉም ሄሮድስ ከሞተ በኋላ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ ከድንግል ማርያም
ጋር ከምድረ ግብፅ ተመልሶ በናዝሬት ተቀምጦ ሳለ እነሆ የዕድሜ ባለፀጋ
የሆነችው የዮሐንስ እናት ክብርት ኤልሳቤጥ ልጇን ዮሐንስን ይዛው ወደ
ደብረሲና በረሃ ከገቡ ከአምስት ዓመት በኋላ ዐረፈች፡፡ ዮሐንስም በእናቱ
አስክሬን አጠገብ ተቀምጦ በእጅጉ እያዘነ መሪር ልቅሶንም እያለቀሰ ሳለ
የተሸሸገውን ሁሉ የሚያውቅ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
የኤልሳቤጥን መሞት፣ እናቱም ስለሞተችበት ዮሐንስ ብቻውን ከበረሃ ውስጥ
ተቀምጦ እያለቀሰ መሆኑን ዐወቀ፡፡
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የኤልሳቤጥን መሞት፣ የወዳጁ ዮሐንስ
ኃዘንና ማልቀስ ባወቀ ጊዜ እርሱም በናዝሬት ሆኖ ያለቅስ ጀመር፡፡ እመቤታችን
ቅድስት ድንግል ማርያምም ልጇ ወዳጅዋ ሲያለቅስ ባየችው ጊዜ ‹ልጄ ወዳጄ
ሆይ! ምን ሆንክ? ስለምንስ ታለቅሳለህ?› ብላ ጠየቀችው፡፡ ጌታችንም ለቅድስት
እናቱ እንዲህ በማለት መለሰላት፡- ‹እነሆ ወገንሽ የሆነችው ኤልሳቤጥ ዐረፈች፤
ዮሐንስንም ብቻውን ከበረሃ ውስጥ ተወችው፡፡ ዮሐንስም ሕፃን ስለሆነ
የሚያደርገውን አጥቶ በእናቱ አስክሬን አጠገብ ከፊት ለፊቷ ተቀምጦ በመረረ
ኃዘን ያለቅሳል፡፡ እናቴ ሆይ እኔም ዘመድሽ የሆነ የዮሐንስን ልቆሶ ስላወቅሁኝና
የእርሱም ኃዘን ስለተሰማኝ የማለቅሰው ስለዚህ ነው› አላት፡፡ በድንጋሌ ሥጋ
በድንጋሌ ነፍስ የፀናች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም የኤልሳቤጥን
መሞት በሰማች ጊዜ በጣም ምርር ብላ አለቀሰች፡፡ ያንጊዜም ብርሕት ደመና
መጥታ ከፊታቸው ቆመች፤ ፈጥናም ተሸከመቻቸውና ኤልሳቤጥ ከሞተችበት
ዮሐንስም ካለበት ቦታ ከደብረሲና በረሃ ውስጥ ወስዳ አደረሰቻቸው፡፡ ዮሐንስም
ባያቸው ጊዜ ደነገጠ፡፡ ከዚያ በፊት ሰው አይቶ ስለማያውቅ የእናቱን አስክሬን
ብቻውን ትቶ ወደ ጫካ ሸሸ፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም የዮሐንስን ፍርሃት
አራቀለትና እንዲህ አለው፡- ‹እኛን ከማየትህ የተነሣ አትፍራ፣ አትደንግጥም፤
አይዞህ እነሆ የእናትህ ዘመዶች ማርያምና ሰሎሜ በእናትህ አስክሬን ላይ
መልካም ነገር ሊያደርጉ መጥተዋልና ና ወደ እኛ ቅረብ› አለው፡፡ ዮሐንስም
ይህን ቃል ከጌታችን አንደበት በሰማ ጊዜ ወደኋላው ተመለሰ፡፡ ከመሬትም ላይ
ወድቆ ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ሰገደለት፡፡
ጌታችንም እመቤታችን ማርያምንና ሰሎሜን እንዲህ ብሎ አዘዛቸው፡-
‹በጠማው ጊዜ ለእርሷ ይጠጣ ዘንድ ለዮሐንስ በፈለቀችለት ውኃ የኤልሳቤጥን
ሥጋ አጥባችሁ ገንዙ› አላቸው፡፡ እንዳዘዛቸውም የኤልሳቤጥን አስክሬን አጥበው
ገነዙት፡፡ ጌታችንም ቅዱስ ሚካኤልንና ቅዱስ ገብርኤልን ይመጡ ዘንድ
አዘዛቸው፡፡ እነርሱም ፈጥነው እንደ ዐይን ጥቅሻ ከሰማይ ወርደው መጡና
ከጌታችን ፊት ቆሙ፡፡ ጌታችንም ‹የኤልሳቤጥን ሥጋ የሚቀበርበትን መሬት
ቆፍሩ› አላቸው፡፡ ቅዱስ ሚካኤልንና ቅዱስ ገብርኤልንም መቃብሩን ይቆፍሩ
ዘንድ ጀመሩ፡፡ ጌታችን ዘካርያስንና ስምዖንን በአካለ ነፍስ ከሰማይ መጥተው
በኤልሳቤጥ አስክሬን ላይ ጸሎተ ፍትሐቱን ያደርሱ ዘንድ አዘዛቸው፡፡ እነርሱም
የኤልሳቤጥ አስክሬን ካለበት ቦታ ላይ ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል፣
እመቤታችን ማርያምና ሰሎሜ ከጌታችን ፊት ቆመው ሳለ ስምዖንና ዘካርያስ
በአስክሬኑ አጠገብ ቆመው ጸሎተ ፍትሐቱን ያደርሱ ጀመር፡፡ ጸሎተ ፍትሐቱንም
በጨረሱ ጊዜ መላእክት በቆፈሩት መቃብር ውስጥ ቀበሩዋትና የስምዖንና
የዘካርያስ ነፍስ ወደነበረችበት ቦታዋ ተመለሰች፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም
የኤልሳቤጥን መቃብር በትእምርተ መስቀል አምሳል ደፈነው፡፡ ኤልሳቤጥም
ያረፈችበት ዕለት የካቲት አሥራ ስድስት ቀን ሆነ፡፡
ከዚህ በኋላ ዮሐንስን ብቻውን ከበረሃ ውስጥ ትተውት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
ከእመቤታችን ጋር ወደ ናዝሬት ለመመለስ ከደመናዋ ላይ ተሣፍሮ ተነሣ፡፡
ያንጊዜም ክብርት እመቤታችን ልጇን እንዲህ አለችው፡- ‹ጌታዬና አምላኬ
ፈጣሪዬ ሆይ! ስለምን ዮሐንስን ብቻውን ከበረሃ ውስጥ ትተወዋለህ? እንዴትስ
ትተነው እንሄዳለን? ወደዚህ ቦታ ይዛው የሸሸችው እናቱ ጥላው ሞታ በመቃብር
ውስጥ ተቀብራለች ከእኛ ጋር ይዘነው እንሂድ እንጂ› አለችው፡፡ ዳግመኛም
እመቤታችን እንዲህ አለችው፡- ‹ነፍስ ያለወቀ ሕፃን ስላሆነ አራዊት ይበሉታልና
ይዘነው መሄድ አለብን› አለችው፡፡ ጌታችንም ለቅድስት እናቱ እንዲህ በማለት
መለሰላት፡- ‹በመምህርነት ወጥቶ ለእስራኤል ታይቶ እስከሚያስተምር ድረስ
የሰማያዊው አባቴ ፈቃድ በበረሃ ውስጥ ብቻውን እንዲኖር ነው፡፡ አንቺ ብቻውን
እንዴት ከበረሃ ይኖራል ትያለሽ፤ አራዊቶች እንዳይጣሉት ሊቀ መላእክት ቅዱስ
ገብርኤል ከእርሱ አይለይም፡፡ በፈለገው ነገር ሁሉ እንዲራዱትና እንዲታዘዙለት
መላእክተ ብርሃንን አዝለታለሁ፡፡ ብርሃናዊው መልአክ ገብርኤልም ሰማያዊ
ሕብስትን ለምግቡ ያመጣለታል፤ በጠማውም ጊዜ እንደ ወተት የነጣችውን፣
እንደ ወለላ ማርም የጣፈጠችውን ውኃ ከኤዶም ገነት ያመጣለታል፡፡ ይህችንም
እርሱ ካለበት ድንጋይ ሥር የምትፈልቀውን ውኃ እንደ እናቱ ጡት ለአፉ
የጣፈጠች አደርግለታለሁ፡፡ አንቺ ብቻውን እንዴት በበረሃ ውስጥ ይኖራል
ትያለሽ፤ እስከ ዛሬ ድረስም የጠበቅሁት እኔ ነኝ፣ ሌላ ማን ጠበቀው ብለሽ ነው?
እኔ አይደለሁምን? ወዳጄ ዮሐንስን ሰማያዊው አባቴ ከዚህ ዓለም ፍጥረት ሁሉ
በጣም አብልጦ ይወደዋል፡፡ አባቱ ዘካርያስም በሥጋው ቢሞት በነፍሱ ሕያው
ስለሆነ ዮሐንስን ለማጽናናት በአካለ ነፍስ ከእርሱ እንዳይለየው አደርጋለሁ፡፡
እናቱ አልሳቤጥም በሥጋዋ ብትሞት በነፍሷ ሕያዊት ስለሆነች ታጽናናው ዘንድ
በነፍሷ በፍጹም ከእርሱ እንዳትለየው አደርጋለሁ፡፡ ዮሐንስን የተሸከመች ማኅፀን
ንዕድ፣ ክብርት ስለሆነች በሥጋዋ ውስጥ መጥፎ ሽታ፣ ክፉ መዓዛ አይገኝባት፣
በመቃብሯም ውስጥ ትሎች አይገኙበት፡፡ ድንግል እናቴ ሆይ! አንቺ እኔን ፀንሰሽ
ሳለሽ ወደ ኤልሳቤጥ በሄድሽ ጊዜ በእጇ ይዛ ጨብጣ፣ በአፏ በሳመችሽ ጊዜ
እንዲህ ብላ ትንቢት ተናግራለች፡፡ ‹አንቺ ከሴቶች ሁሉ ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ፤
የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው፤ የጌታዬ እናቱ ወደ እኔ ትመጪ ዘንድ እኔ
ምንድነኝ? ከእግዚአብሔር አግኝተው የነገሩሽን ቃል ይደረጋል ብለሽ የተቀበልሽ
አንቺ ብፅዕት ነሽ፣ ክብርት ነሽ› ብላ ስላመሰገነችሽ እንኳን ሥጋዋ ሊፈርስ
ይቅርና መግነዟም አይለወጥም፤ መቃብሯም አይጠፋም፤ ነፍሷንም ከሥጋዋ ጋር
እንድትኖር አደርጋታለሁ፡፡› ይህን የመሰለ ነገር ስለ ወዳጁ ዮሐንስ ለድንግል
እናቱ ነግሯት ለጨረሰ በኋላ ዮሐንስን ከበረሃ ውስጥ ትተውት በደመና ላይ
ተጭነው ወደ ናዝሬት ተመለሱ፡፡››
ክብርት እመቤታችን ለእኛም በመከራ ጊዜ ትለመነን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

09 Nov, 07:14


በሀገራችን በቅዱስ ማርቆስ ስም የታነጹ አብያተ ክርስቲያናት!
ወንጌላዊው ሰማዕት የሆነው ማር ቅዱስ ማርቆስ ከዕረፍቱም በኋላ በዐፀደ ነፍስ በረድኤት እየተገለጠ ካደረጋቸው ድንቅ ድንቅ ተኣምራት ውስጥ አንዱ ይኽ ነው፡- ‹‹ታላላቅ ተኣምራትን የሚያደርግ ቅዱስ ማርቆስ ካረፈ በኋላ በኹለተኛው ዓመት ከእስክንድርያ ወደ ግብጽ ከተማ ይሔዱ ዘንድ ደቀ መዛሙርቱ ተነሡ፡፡ ወደ ባሕር ወደብ በደረሱም ጊዜ የሚያሻግራቸው ባለመርከብ አላገኙም፤ ያንጊዜም ባለመርከብ ያገኙ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸለዩ፣ ወዲያውም የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመርከብ አዛዥ ተመስሎ መምህራቸው ቅዱስ ማርቆስ ደግሞ በመርከበኛው አምሳል ተመስለው ወደእነርሱ ዘንድ መጥተው ሰላምታ ሰጧቸው፤ በመርከብም ይወስዷቸው ዘንድ ጠየቋቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም አላወቋቸውም ነበር፡፡

ደቀ መዛሙርቱም ምድራዊ መርከብ መስሏቸዋልና ኹለቱም ሰዎች ምድራዊ መስለዋቸዋልና ፈጽመው እየተደሰቱ እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ተጓዙ፡፡ ባሕሩንም ተጉዘው ወደሚፈልጉት ደረቅ ምድር ከደረሱ በኋላ መርከበኞቹ ከመርከባቸው ጋር ተሠወሩ፡፡ የቅዱስ ማርቆስ ደቀ መዛሙርትም ፈጽመው በማድነቅ እግዚአብሔርን አመሰገኑ፡፡

በዚያችም ሌሊት የተመረጠ ቅዱስ ማርቆስ በራእይ ወደ እነርሱ መጥቶ ‹‹የክርስቶስ ባለሟሎች ሆይ! ሰላም ለእናንተ ይሁን›› አላቸው፡፡ ዳግመኛም ‹‹ባሕሩን ያሻገራችሁ ፈጣሪያችሁ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፣ በመርከበኛው አምሳያ የነበርኩትም እኔ አባታችሁ ማርቆስ ነኝ፤ አሁንም እላችኋለሁ ከባድ ጭንቅ ቢያገኛችሁ አይዟችሁ አትደንግጡ፣ በሃይማኖት ጽኑ እንጂ›› አላቸው፡፡ እነርሱም እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር እንዳለ ዐውቀዋልና በደስታ ወደ ግብጽ ከተማ አደባባዮች ኹሉ ሔደው በግልጽ አስተማሩ፤ ድንቅ ድንቅ ተኣምራትንም እያደረጉ ወንጌል ሰብከው ብዙዎችን አሳምነው አጠመቁ፣ አብያተ ክርስቲያናትን አነጹ፣ አገልጋይ ቀሳውስትን ሾሙ፡፡

ቅዱስ ማርቆስ የእምነት አባታችን ስለሆነ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ‹‹ማርቆስ አባቴ እስክንድርያ እናቴ›› ብላ ለዘመናት በመንበረ ማርቆስ ሥር ቆይታለች፡፡
በሀገራችን በርካታ አብያተ ክርስቲያናት በቅዱስ ማርቆስ ስም የታነጹ ሲሆን ዋና ዋናዎቹ፡-
1. በዐፄ ምኒልክና በአቡነ ማቴዎስ በ1875 ዓ.ም የታነጸው በሰሜን ሸዋ ተጉለት ሰላ ድንጋይ የሚገኘው ደብረ ኅሩያን ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን፣
2. ከመናገሻ ማርያም ዝቅ ብሎ የሚገኘው መንበረ መንግሥት መናገሻ ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን፣
3. ጎጃም ደብረ ማርቆስ የሚገኘው በንጉሥ ተክለ ሃይማኖት የታነጸው ምልዕተ አድባራት ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን፣
4. አዲስ አበባ በቀድሞው ገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት በአሁኑ ስድስት ኪሎ ዩኒቨርሲቲ ግቢ በግርማዊ ጃንሆይ የታነጸው መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ይጠቀሳሉ፡፡

በእነዚኽና በሌሎቹም በስሙ በታነጹና ታቦቱ ባለቤት አብያተ ክርስቲያናት የቅዱስ ማርቆስ ዓመታዊ በዓላት (ጥቅምት 30 እና ሚያዝያ 30) በድምቀት ይከበራሉ፡፡

ሰላ ድንጋይ ደብረ ኅሩያን ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ሰሜን ሸዋ ሰላ ድንጋይ ከተማ የሚገኘዉ ደብረ ኅሩያን ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን የታነጸው በግብጹ ሊቀ ጳጳስ
በብፁዕ አቡነ ማቴዎስ እና በዐፄ ሚኒልክ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ትእዛዝ ነው፡፡ የተሠራውም በ42 ዓምድ ሲሆን የተመሠረተውም በ1875 ዓ.ም ነው፡፡ ውስጡ በጥንታዊ ዕደ ጥበብ የታነጸ እጅግ ውብ ከመሆኑም በላይ በጉልላቱና በሴቶች መግቢያ በር በኩል ግርግዳውን ቦርቡሮ በተከማቸ ንብ ይጠበቃል፡፡ ማሩ እምንት ሆኖ ለምችመናንንም እየተሰጠ ብዙዎች ተፈውሰውበታል፡፡

በንጉሡ ትእዛዝ መንበረ መንግሥት መናገሻ ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያንንም ያሠሩት በብፁዕ አቡነ ማቴዎስ ናቸው፡፡ የሰላ ድንጋዩ ማርቆስ አሁን ያለው ገጽታ የመጀመሪያው
አይደለም፣ የመንበረ መንግሥት መናገሻ ማርቆስ ግን የጥንቱን ይዘት ሳይለቅ እስካሁን አለ፡፡

ዐፄ ሚኒልክ የሰላ ድንጋይ ቅዱስ ማርቆስን ቤተ ክርስቲያን ለማሠራት ሲሉ እዚያው ሰላ ድንጋይ በምትገኘዉ የሸዋ ንጉሥ ከነበሩት የንጉሥ ሳህለ ሥላሴ እናት ወ/ሮ ዘነበ ወርቅ
ሰገነት ላይ በመቀመጥ ቤተ ክርስቲያኑ እስኪያልቅ ድረስ መንግሥታዊ ሥራቸዉን እዚያው ሰገነት ላይ እያከናወኑ ለ6 ወራት እንደቆዩ የቦታው ታሪክ ያስረዳል፡፡ ብፁዕ አቡነ
ማቴዎስም ሰገነቷ ላይ ክህነት እንደሰጡባት ይነገራል፡፡ በዐፄ ኀይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥትም ሰገነቷ የግብር መሰብሰቢያ፣ በደርግ ጊዜ ደግሞ አብዮት አደባባይ በመሆን አገልግላለች፤ በአሁኑ ጊዜ ደግሞ ሰገነቷ በአካባቢዉ የሚገኙ ቅርሶችን በውስጧ በማሰባሰብ እንደሙዚየም እያገለገለች ትገኛለች፡፡

መልዕልተ አድባራት ደብረ ፀሓይ ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን የሚገኘው በምሥራቅ ጎጃም ዞን ዋና ከተማ ደብረ ማርቆስ ሲሆን የተመሠረተውም 1874 ዓ.ም በንጉሥ ተክለ
ሃይማኖት ነው፡፡

አዲስ አበባ ስድስት ኪሎ የሚገኘው መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን የታነጸው በ1916 ዓ.ም ነው፡፡ ዐፄ ኀይለ ሥላሴ ከቤተ መንግሥታቸው ላይ ቦታ ቀንሰው ያነጹት ቤተ ክርስቲያን ነው፡፡

ወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ ከበዓሉ ረድኤት በረከት ይክፈለን! ቤተ ክርስቲያናችንን እና ሀገራችንን በጸሎቱ ይጠብቅልን።
✞ ✞ ✞

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

08 Nov, 17:25


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ጥቅምት 30-በግብፅ ምድር ያሉ ጣዖታትን ፈጽሞ ያጠፋ እስከ ኢትዮጵያም ድረስ መጥቶ ወንጌልን ያስተማረ በመጨረሻም አረማዊያን አካሉን በበሬ አስጎትተው ሥጋው ተበጣጥሶና ተቆራርጦ እስኪያልቅ ድረስ ያሠቃዩት፣ የቀረውንም አካሉን ሰብስበው በእሳት ያቃጠሉት፣ የከበረች ወንጌልን የጻፈ፣ ሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ ልደቱ ነው፡፡
+ የመጥምቁ ዮሐንስ አንገት በግፍ በሰማዕትነት ከተቆረጠች በኋላ በግልጽ የታየችበት ዕለት ነው፡፡ ይኸውም የመጥምቁ ዮሐንስ ቅድስት ነፍሱ ከተቆረጠች ራሱ ጋራ በአየር ውስጥ እየበረረች 15 ዓመት ስታስተምር ከኖረች በኋላ በዚህች ዕለት በዐረቢያ ምድር በግልጽ ታይታለች፡፡
+ መኑፍ ከሚባል ሀገር የተገኙት ጻድቁ አባ አብርሃም ዕረፍታቸው ነው፡፡
አባ አብርሃም፡- ይኸውም ቅዱስ በሚባል ሀገር እግዚአብሔርን ከሚፈሩና እጅግ ባለጸጎች ከሆኑ ደጋግ ወላጆቹ ተወለደ፡፡ ባደገ ጊዜም የምንኩስናን ልብስ ይለብስ ዘንድ ወዶ ወደ ላዕላይ ግብፅ ተሳፍሮ ሄዶ በታላቁ አባት በአባ ጳኩሚስ እጅ መነኮሰ፡፡ እሳቸውንም እያገለገለ በገድል ተጠምዶ እየኖረ 23 ዓመት ተቀመጠ፡፡ ከዚህም በኋላ አባ ጳኩሚስን አስፈቅዶ ብቻውን በዋሻ ውስጥ መኖር ጀመረ፡፡ ለዕለት ጉርሱ ጥሬ መግዣ ይሆነው ዘንድ ዓሣ ማጥመጃ መረብም ይሰፋ ነበር፡፡ ጌታችንም መረቦቹን የሚሸጥለት ሰው ላከለት፡፡ እርሱም መረቦቹን ሸጦ ምግቡን አተር ይገዛለታል፡፡ ከእርሷም አንድ እፍኝ ብቻ አስቀርቶ በውኃ አርሶ ይመገብና የቀረውን ለሌሎች ይሰጣል፡፡
አባ አብርሃም በእንዲህ ዓይነት ጽኑ ተጋድሎ 17 ዓመት ኖረ፡፡ በየሁለት ዓመቱ ወደ መነኮሳቱ እየተመለሰ ሥጋውን ደሙን እየተቀበለ ወደ በዓቱ ይመለስ ነበር፡፡ ዕረፍቱም በደረሰ ጊዜ የአባ ጳኩሚስን ረድእ አስጠርቶት አብረው ጸሎት ካደረጉ በኋላ አባ አብርሃም በዚያው ጥቅምት 30 ቀን በሰላም ዐረፉ፡፡ መነኮሳቱም መጥተው ከሥጋው በረከትን ተቀብለው አስክሬኑን ወስደው ከቅዱሳን ጋር አኖሩት፡፡ ከሥጋውም ብዙ ተአምራት ተፈጽመው ታዩ፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!
+ + +
ዳግመኛም በዚህች ዕለት ወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ ልደቱ ነው፡፡ (የዕረፍቱን ዕለት ሚያዝያ ሠላሳን ይመልከቷል፡፡)
ማርቆስ ማለት ‹‹አንበሳ፣ ንብ›› ማለትነው፡፡ የቀድሞ ስሙ ዮሐንስ ነው፡፡ እናቱ ማርያም ቅዱሳን ሐዋርያትን ታገለግል ስለነበር ቤቷንም ለጸሎት እንዲሆን አደረገች፡፡ ቅዱስ ማርቆስ በትውልዱ ዕብራዊ ሲሆን ቤተሰቦቹ ግን ይኖሩ የነበሩት በሰሜን አፍሪካ ቀሬና በተባለችውና በዛሬዋ ምዕራባዊ ሊቢያ ጠረፍ አካባቢ ነበር፡፡ ነገር ግን የሰሜን አፍሪካ ዘላን ጎሳዎች የሆኑት በርበሮች በየጊዜው ከተማቸውን እየዘረፉና ጥቃት እየሰነዘሩ ሲያስቸግሯቸው እናቱ ማርያምና አባቱ አርስጦቡሎስ ወደ ትውልድ ሀገራቸው ኢየሩሳሌም በመመለስ በዚያው መኖር ጀመሩ፡፡ ቅዱስ ማርቆስም በዚያው ስላደገ በዘመኑ ይሰጥ የነበረውን ትምህርት ተምሯል፡፡ የላቲን፣ የግሪክና የዕብራይጥ ቋንቋዎችን በደንብ ያውቅ ነበር፡፡
ወንጌልን መጀመሪያ ከጌታችን በኋላም ከቅዱሳን ሐዋርያት እየዞረ ስለተማረ ንብ ተብሏል፣ አንበሳ የተባለበትም ምክንያት አንበሳ ላምን እንደሚሰብር ማርቆስም እንዲሁ በላም አምሳል ተሠርተው ሲመለኩ የነበሩ የግብፅ ጣዖታትን ሰባብሮ አጥፍቷልንና ነው፡፡
ጌታችን በይሁዳ አውራጃዎች እየተዘዋወረ ሲያስተምር ቅዱስ ማርቆስ ያንጊዜ ገና ሕፃን ነበር፡፡ ለዚህም ነው ጌታችን መከራ መስቀሉን እየተቀበለ ወደ ቀራንዮ ሲሄድ ማርቆስ ዕርቃኑን በነጠላው ሸፍኖ ሲከተለው አይሁድ ሊይዙት ባሰቡ ጊዜ ጨርቁን ጥሎ ራቁቱን የሸሸው፡፡ ሐዋርያት ዓለምን ዕጣ በዕጣ ተከፋፍለው ሲወጡ ቅዱስ ማርቆስ በበርናባስ አቅራቢነት ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር በመጀመሪያ ጉዞው በ46 ዓ.ም ለስብከተ ወንጌል ወጥቶ ነበር፡፡ ነገር ግን ጵንፍልያ በምትባል ከተማ ላይ ‹‹እናቴ ናፈቀችኝ›› ስላለ በርናባስ ይዞት ወደ ኢየሩሳሌም ተመልሷል፡፡ ሐዋ 13፡13፡፡ ነገር ግን ሐዋርያት ከሄዱበት ተመልሰው ስላደረጓቸው ተአምራት ሲናገሩ ሲሰማ ተጸጸተ፡፡ ድጋሚም ከበርናባስ ጋር ሄደ፡፡ በርናባስም ካረፈ በኋለ ወደ ሮሜ ሄዶ ቅዱስ ጴጥሮስን ተቀላቅሎ ደቀ መዝሙሩ ሆነ፡፡ በዚያም ቅዱስ ጴጥሮስ የተረጎመለትን ወንጌል ጻፈ፡፡ በሮሜ ሀገርም አስተማረበት፡፡
ከዚህም በኋላ በጌታችንም ትእዛዝ በ60 ዓ.ም ወደ ሰሜን አፍሪካ መጥቶ እስክንድርያ ደረሰ፡፡ በሀገሪቱም አምልኮተ ጣኦት በስፋት ተንሰራፍቶ ስለነበር ወንጌልን እንዴት አድርጎ መስበክ እንዳለበት እያሰበ በከተማ ሲዘዋወር የእግሩ የጠፈር ጫማው ተበጠሰና ለአንድ ሰፊ ሰጠው፡፡ ጫማ ሰፊውም ሲሰፋ እጁን ስለወጋው ‹‹ኤስታኦስ›› ብሎ በዮናናውያን ቋንቋ ጮኸ፡፡ ትርጉሙም አንድ አምላክ ማለት ነው፡፡ ያን ጊዜም ቅዱስ ማርቆስ ጫማ ሰፊውን ‹‹ለመሆኑ አሁን የጠራሃውን አምላክ ታውቀዋለህን?›› ብሎ ጠየቀው፡፡ ጫማ ሰፊውም ‹‹ሲሉ እሰማለሁ እንጂ አላውቀውም›› አለው፡፡ ቅዱስ ማርቆስም የቆሰለች እጁን በተአምራት ፈወሰውና ወንጌልን ሰበከለት፡፡ እርሱም ወደ ቤቱ ወሰደውና ለቤተሰቡም ጭምር ወንጌልን ይሰብክ ዘንድ ጋበዘው፡፡ ቅዱስ ማርቆስም ወደ ጫማ ሰፊው (ስሙ አንያኖስ ይባላል) ሄዶ ወንጌልን ሰበከ፡፡ በግብፅም የመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን በአንያኖስ ቤት ተመሠረተች፡፡
ቅዱስ ማርቆስም በእስክንድርያ ወንጌልን ሰብኮ አገልጋዮችን ሾሞ ወደ ሰሜን አፍሪካና ሌሎች አምስት ሀገሮች ሄዶ ወንጌልን ሰበከ፡፡ ወደ ትውልድ ሀገሩ ቀሬናም ሄዶ ሰብኳል፡፡ ከ2 ዓመትም በኋላ ወደ እስክንድርያ ቢመለስ ክርስቲያኖችን ጸንተው ቤተ ክርስቲያን ሠርተው አገኛቸው፡፡ ከሀዲዎችም ሊገድሉት ሲሞክሩ እየተሰወረባቸው እየወጣ ወደ አምስቱ ሀገራት እየደረሰ ይመለስ ነበር፡፡ ነገር ግን የትንሳኤን በዓል ለማክበር ወደ እስክንድርያ መጥቶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ገብቶ እየቀደሰ እያለ ጣዖት አምላኪዎች ሰብረው ገብተው ይዘውት አንገቱን አሥረው ቀኑን ሙሉ ከተማውን እየጎተቱት ሲያዞሩት ዋሉ፡፡ በቀጣዩም ቀን እንዲሁ አስረው መሬት ለመሬት ሲጎትቱት ስለዋሉ በዚያው ዐረፈ፡፡ እሳት አንድደው ሥጋውን ሊያቃጥሉት ሲሉ ኃይለኛ ዶፍ ዝናብ ስለወረደ ጨረቃና ፀሐይም ስለጨለሙ አረማውያኑ ፈርተው ሸሹ፡፡ ቅዱስ ማርቆስ ሰማዕትነቱን የፈጸመው በ68 ዓ.ም ሚያዝያ 30 ቀን ነው፡፡
የቅዱስ ማርቆስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!
+++
የመጥምቁ ዮሐንስ አንገት ከተቆረጠች በኋላ 15 ዓመት በአየር እየበረረች ስታስምር እንደኖረች፡- የመጥምቁ ዮሐንስ ቅድስት ነፍሱ ከተቆረጠች ራሱ ጋራ በአየር ውስጥ እየበረረች 15 ዓመት ስታስተምር ከኖረች በኋላ ጥቅምት 30 ቀን በዐረቢያ ምድር በግልጽ ታይታለች፡፡ ይኸውም የሆነው እንዲህ ነው፡- ሄሮድያዳ ልጅ ርጉም የሆነ ንጉሥ ሄሮድስን በዘፈኗ በጣም አድርጋ ስላስደሰተችው እርሱም በተራው ሊያስደስታት ፈለገና እስከ መንግሥቱ እኩሌታ ድረስም ቢሆን የለመነችውን ይሰጣት ዘንድ በሕዝቦቹና በመኳንንቱ ሁሉ ፊት እንዳይከዳት በፅኑ ቃልኪዳን ማለላት፡፡ እርሱም አስቀድሞ ‹‹የፈለግሽውን ጠይቂኝ፣ የመንግሥቴንም እኩሌታ ቢሆን እሰጥሻለሁ ምን ላድርግልሽ?›› እያለ በመሐላ ባላት ጊዜ በእናቷ ምክር የዮሐንስን አንገት ቆርጦ ይሰጣት ዘንድ ለመነችው፡፡ እርሱም ስለማሐላው የዮሐንስን አንገት እንድትቆረጥ አደረገ፡፡ በመጀመሪያም የሄሮድስ ወታደሮች ሠይፍ ይዘው የዮሐንስን አንገት ይቆርጡ ዘንድ ወደ መኅኒ ቤት ሲሄዱ ቅዱስ ዮሐንስም

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

08 Nov, 17:25


የሄሮድስ ጭፍሮች ሊገድሉት እንደመጡ በመንፈስ ቅዱስ ፀጋ ስላወቀ ከጨለማው ቤት ውስጥ አንገቱን በመስኮት አውጥቶ እንደሚመቻቸው አድርጎ ጠበቃቸው፡፡ የንጉሡም ጭፍሮች የመጥምቁን ራስ በወጪት አድርገው ለንጉሣቸው ሄሮድስ ሰጡት፡፡ ሄሮድስም ለሄሮድያዳ ልጅ ሰጣት፡፡ የመጥምቁ ዮሐንስ ግን በወጪት ላይ ሆና ሕዝቦቹና የመንግሥቱ ታላላቅ ሰዎች እየሰሟት በየመኳንንቱ ፊት ንጉሥ ሄሮድስን ‹‹የወንድምህን የፊሊጶስን ሚስት ማግባት አይገባህም›› እያለች መጀመሪያ ትዘልፈው እንደነበረው ሁሉ አሁንም ዘለፈችው፡፡ መዓዛዋም እጅግ ደስ የሚያሰኝ ነበር፣ ዐይኖቹም እንደፀሐይ ያበሩ ነበር፡፡
የሄሮድያዳም ልጅ የመጥምቁን ራስ ወስዳ ለእናቷ ልትሰጣት ስትል ዐይኖቹ እንደፀሐይ ሲያበሩ ብታየው ‹‹ንጉሡን አትፈራውምን?›› በማለት ተቆጣች፡፡ በመቀጠልም ‹‹እነዚህን ዐይኖቹን በወስፌ እያወጣሁ እጥላቸዋለሁ፣ ምላሱንም ደግመኛ እንዳይገሥጽ ቆርጨ እጥላቸዋለሁ›› በማለት ፊቱን በጥፊ ለመምታት እጇን ስታነሣ ያንጊዜ የዮሐንስ ራስ ክንፍ አውጥታ በረረች፡፡ በአየር ላይ ሳለችም ዳግመኛ ‹‹የተረገምሽ ሄሮድያዳ የባልሽን ወንድም ሄሮድስን ማግባት አይገባሽም፣ ቀድሞ የምዘልፍሽ አሁንም የምዘልፍሽ እኔ ነኝ›› እያለች የዮሐንስ ራስ የቤቱን ጣሪያ ሰንጥቃ እንደንሥር በአየር በራ ሄደች፡፡
ከዚህም በኋላ ለጥፊ የዘረጋቻቸው የሄሮድያዳ እጆቿ ከትከሻዋ እየተቆረጡ መሬት ላይ ወደቁ፤ እውነቷንም መሬት አፏን ከፍታ ዋጠቻት፡፡ ዘፋኟ ልጇም አብዳ የቤተ መንግሥቱን ዕቃ ሁሉ መሰባበር ጀመረች፡፡ የንጉሡ አንዱ ጭፍራም የሄሮድያዳን በእሳት እንደተለበለበ የግንድ እሳት የመሰለና የተቆረጠ እጇን አምጥቶ ለሄድሮስ ሰጠውና የሆነውን ነገረው፡፡ ንጉሡም ነገሩ እውነት መሆኑን ሄዶ ባየ ጊዜ በሀፍረት እጅግ ተሸማቀቀ፡፡ ዘፍና በማስደሰት የዮሐንስን ራስ እንዲያስቆርጠው ያደረገችው የሄሮድያዳ ሴት ልጅም አብዳ በቤተ መንግሥቱ ስትለፈልፍ አገኛት፡፡ ሄሮድስም መኳንንቶቹን ‹‹በቤተ መንግሥቴ የተደረገውን ይህን ነገር ለማንም አትንገሩ›› ብሎ አማላቸው ነገር ግን ያበደችው የሄሮድያዳ ሴት ልጅ ራሷ ሄዳ ሄሮድስን ‹‹የወንድምህን የፊሊጶስን ሚስት ማግባት ፈጽሞ አይገባህም›› እያለች በመኳንንቶቹ ፊት ገሠጸችው፡፡ ንጉሥ ሄሮድስም ይህን ቃል ከእርሷ በሰማ ጊዜ እጅግ ተናደደና ‹‹ቀደሞ ያልሆነ ሥራ ታሠራ በኋላ ደግሞ ምሥጢር ታወጣ ንሣ በሰይፍ ቁረጣት›› ብሎ አንገቷን በሰይፍ አስቆረጣት፡፡ ሥጋዋንም ዓሣ አንበሪ ተቀብሎ ዋጣት፡፡ ሄሮድም የወንደሙን ሚስት ሲያገባ አስቀድሞ አግብቷት የነበረችውን ሚስቱን በግፍ አባሯት ነበር፡፡ እርሷም ይህንን ሄሮድስ ያደረሰባትን ግፍ ለአባቷ አርጣ ብትነግረው አባቷ ብዙ ጦር ሰብስቦ መጥቶ ምድረ ገሊላን በኃይል አፈራረሳት፡፡ የበላዩ ንጉሥ ቄሳርም የገሊላን መፍረስና መውድም ሲሰማ ምክንያቱን ቢጠይቅ ሄሮደስ ባደረገው ግፍ ምክንያት መሆኑን ነገሩት፡፡ ቄሳርም ሄሮድስን ከሥልጣኑ ሽሮ አጋዘውና በወህኒ ጣለው፡፡ ሄሮድስም በወህኒ ቤት ሳለ አብዶ ራሱን ስቶ የገዛ አካሉን እየነጨ እየበላ ቷ ብሎ ፈንድቶ ተልቶ ሸቶ እጅግ ክፉ አሟሟት ሞተ፡፡
ከዚህም በኋላ ጌታችን ወደ ቅዱስ ዮሐንስ ራስ መለስ ብሎ እንዲህ በማለት ሥልጣን ሰጣት፡- ‹‹እነሆ መንፈስሽን በራስሽ ውስጥ አድርጌልሻለሁ በሰማይም የምትበሪበት እንደ ንሥር ክንፍ ሰጥቼሻለሁና እንደንስር በሰማይ እየበረርሽ በዓለም ሁሉ እየዞርሽ የሄሮድስንና የሄሮድያዳን ኃጢአት ግለጭባቸው፤ እስከ 15 ዓመት ድረስ ገቢረ ተአምራት የምታደርጊበት ኃይሌን መንፈሴን በእራስሽ ውስጥ አድርጌልሻለሁ›› አላት፡፡ ዳግመኛም ጌታችን ዮሐንስን ‹‹እኔም ከ3 ዓመት በኋላ ለአዳም የሰጠሁትን ተስፋ ፈጽሜ በሞቴ ወደ ሲኦል ወርጄ ነፍሳትን ከዲያብሎስ እጅ ማርኬ በ3ኛው ቀን ከሙታን ተለይቼ ተነሥቼ ወደ ባሕርይ ክብሬ ተመልሼ ወደ ሰማይ አርጌ ባባቴ ቀኝ በተቀመጥኩኝ ጊዜ ከ15 ዓመት በኋላ ርጉም ሄሮድስ ካስፈጃቸው ከትንንሾቹ ሕፃናት ጋራ ትሆን ዘንድ በአባቴ ፈቃድ እራስህን ተሸክመው ወደ አባትህ ወደ ዘካርያስ ያመጧት ዘንድ እኔ መላእክትን አዛቸዋለሁ፡፡ ዛሬ ግን ነፍስህን በእኔ ቀኝ ባባትህ በዘካርያስ አጠገብ አኑሬያታለሁ መንፈስህንም እስከ 15 ዓመት በእራስህ ውስጥ እንድትኖር አዝዣታለሁ፣ ሥጋህም ከነቢዩ ከኤልሳዕ ጋር እንዲቀመጥ አድርጌያለሁ›› አለው፡፡
ከዚህም በኋላ ጌታችን እንዳዘዛት የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስ እራስ እንደንስር በአየር ላይ እየበረረች የምታስተምር ሆነች፡፡ በምሥራቅ በኩል ሄዳ በዐረብ አገር ውስጥ በሰማይ ላይ ስታስተምር በዚህች ዕለት ጥቅምት 30 ቀን በግልጽ ታየች፡፡ ነጋዴዎች ድምጹዋን ሰምተውና አይተዋት እጅግ ተደስተው ገንዘባቸው ሁሉ ጥለው የቅዱስ ዮሐንስን እራስ ለመያዝ ሰውነታቸውን ብዙ አደከሙ፡፡ ነገር ግን ለመያዝ አልተቻላቸውም፡፡ ከዚህም በኋላ ከሰማይ ‹‹የምትያዝበት ጊዜ ስላልደረሰ ሰውነታችሁን አታድክሙ›› የሚል ድምጽ ከሰማይ መጣላቸው፡፡ መፈለጋቸውንም ተው፡፡ የቅዱስ ዮሐንስም እራስ 15 ዓመት ስታስተምር ኖራ ሚያዝያ 15 ቀን በዐረብ ሀገር ዐረፈች፡፡ የታዘዙ ቅዱሳን መላእክትም መጥተው ከቅዱስ ዮሐንስ እራስ ከተባረኩ በኋላ በታላቅ ዝማሬ እያመሰገኑ የቅዱስ ዮሐንስን አንገት ወስደው በነቢዩ ኤልሳዕ መቃብር ውስጥ አብረው ቀበሯት፡፡ ቅድስትን ነፍሱንም እያመሰገኑ ወደ ሰማይ አሳረጓት፡፡ በዚያም በሥሉስ ቅዱስ ዙፋን ፊት ወድቃ ከሰገደች በኋላ አባቷ ዘካርያስንና እናቷ ኤልሳቤጥን እጅ ነሳቻቸው፡፡ ከዚህም በኋላ በ3ኛው ሰማይ ውስጥ ተቀመጠች፡፡ ጌታችን ሦስቱን ሰማየ ሰማያት ርስት ጉልት አድርጎ ሰጥቶታልና፡፡
የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!
(ገድለ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ-ሚጣቅ አማኑኤል እትም፣ ገድለ ሐዋርያት፣ የጥቅምት ወር ስንክሳር)

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

02 Nov, 11:32


ውራ ኢየሱስ ገዳምን የመሠረቱትና ጌታችን ከገነት ዕንጨቶች የተሠሩ ታቦታት አምጥቶ የሰጣቸው ታላቁ ጻድቅ አቡነ ዮሐንስ ዘውራ ኢየሱስ ጥቅምት 22 ቀን ዕረፍታቸው ነው።
+ + + + +
አቡነ ዮሐንስ ዘውራ ኢየሱስ:-የአባታቸው ስም የማነ ብርሃን የእናታቸው ስም ሐመረ ወርቅ ይባላል።በመጀመሪያ እናታቸው ሐመረ ወርቅን ወላጆቿ ያለ ፈቃዷ ሊድሯት ሲሉ እርሷ ግን “ደብረ ሊባኖስ ሔጄ ከአባታችን ተክለ ሃይማኖትና ከሌሎቹም ቅዱሳን መቃብር ሳልባረክ አላገባም በማለት ነሐሴ 16 ቀን ወደ ደብረ ሊባኖስ ሔደች። በዚያም ሳለች አቡነ ተክለ ሃይማኖት በራእይ ተገለጡላትና የብርሃን ምሰሶ አሳይተዋት ይኸ ለአንቺና ለባልሽ ለየማነ ብርሃን ነው› አሏት። ይኽንንም ራእይ ለሰባት ቀን የገዳሙ አባቶችና አበ ምኔቱ አባ ዳንኤል አዩት። ከዚኸም በኋላ ባለጸጋውና ሃይማኖትን ከምግባር አስተባብሮ የያዘው የማነ ብርሃን ከዘርዐ ያዕቆብ ሀገር በእመቤታችን ትእዛዝ ወደ ደብረ ሊባኖስ ሲመጣ አበ ምኔቱ አባ ዳንኤል የማነ ብርሃንን እና ሐመረ ወርቅን ኹለቱ ተጋብተው የተባረከ ልጅ እንደሚወልዱ በራእይ ያዩትን ነገሯቸው፤ ከዚኽም በኋላ በአባታችን በተክለ ሃይማኖት የዕረፍታቸው በዓል ዕለት ነሐሴ 24 ቀን ተጋቡ። እነርሱም በሃይማኖት በምግባር እግዚአብሔርን ደስ አሰኝተው ሲኖሩ እግዚአብሔር ልጅ ሰጣቸውና አቡነ ዮሓንስ ነሐሴ 24 ቀን ተፀንሰው ግንቦት 24 ቀን ተወለዱ።

የፈለገ ብርሃን ናዳ ማርያም እና የክብረ ደናግል ናዳ ቅዱስ ላሊበላ አንድነት ገዳም አበምኔት፣ የቅኔ፣ የትርጓሜ መጻሕፍት፤ የፍትሐ ነገሥት እና የባሕረ ሐሳብ መምህር የሆኑት ሊቀ ብርሃናት ቆሞስ ይባቤ በላይ ከግእዝ ወደ አማርኛ የተረገሙት የአቡነ ዮሐንስ ዘውራ ኢየሱስ ገድል እንደሚናገረው ጻድቁ በሰባት ዓመታቸው ይኸችን ዓለም ንቀው የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ኹለተኛ ልጅ ወደሆነው አባ ጸጋ ኢየሱስ ዘንድ ሔደው 5 ዓመት እየተማሩ ተቀምጠው በ12 ዓመታቸው መነኰሱ። ከዚኽም በኋላ አቡነ ዮሐንስ ወደ ዋልድባ በመሔድ አባቶችን ማገልገል ጀመሩ። መነኰሳቱም ሌሊትና ቀን እንዲገለግሏቸው በሥጋ ቍስል ሁለንተናው
ለተላና ለሸተተ ግብሩ ለከፋ ለአንዲ መነኵሴ ሰጧቸው። በሽተኛውም መነኵሴ አቡነ ዮሐንስን ይረግማቸው አንዳንድ ጊዜም ይደበድባቸው ነበር፣ ነገር ግን አቡነ ዮሐንስ በዚህ ከማዘን ይልቅ ደስ እያላቸው ያንን ሊቀርቡት የሚያሰቅቅ በሽተኛ በማገልገል ለዓመታት አስታመመ።

እንዲሁም የዋልድባ መነኰሳትን መኮሪታ በማብሰል፣ ቋርፍ በመጫር እና ዕንጨት በመልቀም፣ ውኃ በመቅዳት ገዳማውያንን ያገለግሉ ነበር። ከዕለታትም በአንደኛው ቀን በዋልድባ የሚኖር በክፉ በሽታ ተይዞ የሞተ አንድ መነኩሴ ሞቶ ሣለ ሽታውን ፈርተው መነኰሳቱ ለመገነዝ ፈሩ፡ ነገር ግን አበ ምኔቱ ለመገነዝ ወደ ውስጥ ሲገባ አቡነ ዮሐንስ አብረው ገቡ። አቡነ ዮሐንስም ወደሞተው መነኵሲ ቀርበው አቀፉት፣ በዚኸም ጊዜ ጥላቸው ቢያርፍበት ያ የሞተው መነኵሴ አፈፍ ብሎ ከሞት ተነሣና ከሞትሁ 3ኛ ቀኔ ነው አይቶ የጎበኘኝ የለም፣ ዛሬ ግን የእግዚአብሔር ሰው የገዳማት ኮከብ የቅድስት ውራ ገዳም መነኰሳት አባት፣ የማይጠልቅ ፀሓይ፣ የማይጠፋ ፋና ወደ ሰባቱ ሰማያት ወጥቶ ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ ጋር የሥላሴን ዙፋን የሚያጥን አባታችን ዮሐንስ ባቀፈኝ ጊዜ ነፍሴ ከሥጋዬ ጋር ፈጽማ ተዋሐደች፤ አምላክን የወለደች እመቤታችን ማርያምም ንዑድ ክቡር ቅዱስ በሆነ በዮሐንስ ጸሎት ከሞት አስነሥቶ ሕያው አደረገህ አለችኝ› ብሎ ተናገረ። ዳግመኛም እመቤታችን አባ ዮሐንስን ወደ ኢየሩሳሌም ሔደው እርሳቸውን ሲጠብቁ የኖሩትን ሦስት ታቦታት ያመጡ ዘንድ አቡነ ዮሐንስን እንዳዘዘቻቸው ተናገረ። በዚኽም ጊዜ የዋልድባ መነኰሳትና የገዳሙ አለቃ ለፍላጎታችን አገልጋይና ታዛዥ አደረግንህ ይቅር በለን ብለው ከእግራቸው ሥር ወድቀው ለመኗቸው። አባታችንም ‹‹አባቶቼ ሆይ! እናንተ ይቅር በሉኝ፡ ይህ የሆነው ስለ እኔ አይደለም፡ ስለ ክብራችሁ ነው እንጂ አሏቸው። መነኰሳቱም በትሕትናቸው ተገርመው እያለቀሱ ወደ ኢየሩሳሌም ሸኟቸው። በዚኸም ጊዜ አባታችን ዕድያቸው ገና 19 ነበር።

አባታችን ዮሐንስም ጎልጎታ ደርሰው ከቅዱሳት ቦታዎች ተባርከው ወደ አስቄጥስ ገዳም ሔዱ። በዚያም 500 ዓመት የኖረ ኹለተኛ እንጦንስ የተባለ አንድ ባሕታዊ ኣገኙ። እመቤታችንም አባ እንጦንስን ታቦተ ኢየሱስን፣ ታቦተ ኪዳነ ምሕረትን እና ታቦተ ጽዮንን እያስጠበቀችው ይኖር ነበር። አባ እንጦንስም ኣቡነ ዮሐንስን ባገኛቸው ጊዜ በልቡ ተደስቶ በመንፈሱ ረክቶ በዐይኖቼ አንተን ያሳየኝ በጆሮዎቹም ቃልህን ያሰማኝ የአባቶቻችን አምላክ እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን፤ እመቤታችን ማርያም ከልጇ ከወዳጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር በእጇ የሰጠችኝን ያስጠበቀችኝን እነዚኽን ታቦታት ተቀበለኝ›› ብለው ሦስቱን ጽላት ‹‹ወደ ሀገርህ ይዘህ ሒድ›› ብለው ሰጧቸው። አባታችን ዮሐንስም ‹‹…እኔ እርሱ አይደለሁም እንዴት አወከኝ?› ሲሏቸው አባ እንጦንስም ፈገግ ብለው ከሞተ ሦስት መዓልትና ሦስት ሌሊት የሆነውን ሰው በጸሎትህ ከሞት ካስነሣኸው በኋላ ከሀገርሀ ከኢትዮጵያ ከዋልድባ ገዳም ከተነሣኽ ዘጠኝ ወር ነው፤ ይኸንንም የእግዚአብሔር መላእክት ነገሩኝ መምጣቱን ተስፋ የምታደርገው ኢትዮጵያዊው ጻድቅ ከሀገሩ ዛሬ ተነሣ አሉኝ አሏቸው። አባታችን ዮሐንስም እመቤታችን ማርያምን እንዴት አገኘሃት? አሏቸው። አባ እንጦንስም ከልጇ ከወዳጇ ጋር በብርሃን መርከብ ላይ ተቀምጣ መላእክት፣ ነቢያት፣ ሐዋርያት ጻድቃን፣ ሰማዕታት ሲከቧትና በክብር በምስጋና ሲሰግዱላት ግንቦት 21 ቀን በደብረ ምጥማቅ አገኘኋት አሏቸው። እመቤታችንም ልጇን ኢየሱስ ክርስቶስን ፈቃድህን ለሚያደርጉ ለኢትዮጵያ ሕዝብና ለዓለሙ ሁሉ የመዳን ተስፋ ስጠኝ አለችው። ጌታችንም ያንጊዜ መላእክትን ከገነት ዕንጨትና ዕብነ በረድ፡ ከጎልጎታ መቃብሩና ከጌቴሴማኒ አፈር እንዲያመጡ አዘዛቸው። መላእክትም የታዘዙትን አምጥተው በሰጡት ጊዜ ጌታችን ከገነት የመጡትን ዕንጨትና ዕብነ በረድ ሦስቱን ታቦታት አድረጋቸው በማለት አባ እንጦንስ ለአባ ዮሐንስ ነገሯቸው።

አቡነ ዮሐንስም ሦስቱን ጽላት ይዘው አንዲት እንደፀሓይ የምታበራ ድንጋይ እየመራቻቸው ሰኔ 12 ቀን ጎጃም ደረሱ። ድንጋዩዋንም መንገድ እንድትመራቸው የሰጣቸው ጌታችን ነው። ከዚያም ውሮ ተብሎ የሚጠራ አንድ ባላባት ቤት ገብተው አድረው በሚገባ ተስተናግደው በቀጣዩ ቀን ድንጋዩዋ እየመራቻቸው ቅዱሳን ከነበሩበት ጫካ ወስዳ አገናኘቻቸው። ቅዱሳኑም ለአቡነ ዮሐንስ የጠበቅንልህን ይኸችን ቦታ ተረከበን የዘለዓለም ማረፊያህ ናትና› ብለው እነርሱ ወደ ኢየሩሳሌም ሔዱ። አባታችንም ታቦተ ኢየሱስን በዚኽች ገዳም ተክለው ቦታዋን መጀመሪያ በተቀበላቸው ሰው በውሮ ስም "ውራ ኢየሱስ ብለው ሰየሟት።

ከዘጠኝ ዓመትም በኋላ መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል እየመራቸው ወደ ጣና ወስዶ ዘጌ አደረሳቸውና ታላቋን ዑራ ኪዳነ ምሕረትን ተከለ።

ከዚያ ቀጥለው ታቦተ ጽዮንን አዴት አካባቢ ተከሉ። እነዚህን ሦስት ገዳማት አቅንተው ከኖሩ በኋላ መልካም የሆነውን ተጋድሏቸውን ፈጽመው ጥቅምት 22 ቀን ዐርብ በ9 ሰዓት ዐረፉ። ከማረፋቸውም በፊት ጌታችን እመቤታችንን፣ መላእክትን፣ ቅዱሳንን ሰማዕታትን አስከትሎ መጥቶ “…ጸሎት አድርጎ መልክህን የደገመ እባብ አይነድፈውም፤ መብረቅ አይገድለውም የሚል ድንቅ የምሕረት ቃልኪዳን ገባላቸው። ዳግመኛም ስምህን የጠራውን መታሰቢያህን ያደረገውን፤ በበዓልህ ቀን ማኅሌት የቆመውን የገድልህን መጽሐፍ የጻፈውን ያጻፈውን

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

02 Nov, 11:32


ያነበበውን የሰማውን፣ እጅ መንሻ ለቤተ ክርስቲያን የሰጠውን እምርልሃለሁ፤ ልጆቹንም እስከ 15 ትውልድ እባርክልሃለሁ፤ በገዳምህ በውራ መብረቅ ነጎድጓድ፣ እባብ ሰውን አይገድልም የማይጸድቅ ሰው ወደ ገዳምህ አይመጣም" አላቸው።

አባታችንም ካረፉ በኋላ መነኰሳት ልጆቻቸው ሥጋቸውን ተሸክመው ከደብረ ጽዮን ኮቲ ተነሥተው ወደ ውራ ኢየሱስ ለመውሰድ ሲጓዙ በበረሓ ሣሉ መሸባቸውና ፀሓይ ገባች፣ ወዲያውም ሰባት አንበሶች መጥተው እንዳይፈሯቸው መነኰሳቱን በሰው አንደበት ካናገሯቸው በኋላ የአቡነ ዮሓንስን ዐፅም ተሸክመው ሰባት ምዕራፍ ያህል ወሰዱት። ወቅቱ ቢመሽባቸውም በእግዚአብሔር ፈቃድ ፀሓይ ግን በተኣምራት ወጣችላቸውና ውራ ኢየሱስ ገዳም በሰላም ደረሱ። ያንጊዜም ፀሓይ ገባች፤ አንበሶቹም እጅ ነሥተው ወደ ቦታቸው ተመለሱ።

አቡነ ዮሐንስ መላ ዘመናቸውን የማያዩ ዐይነ ሥውራንን እንዲያዩ፣ የማይሰሙ እንዲሰሙ፣ የማይራመዱ እንዲራመዱ በማድረግ፤ ሕሙማንን በመፈወስ፣ ሙታንን በማስነሣት በርካታ ተኣምራትን በማደረግ ወንጌልን በመስበክ ያገለገሉ ሲሆን ከዕረፍታቸውም በኋላ በርካታ ድንቅ ድንቅ ተኣምራትን አድርገዋል። ከተኣምራታቸውም አንዱ ይኸ ነው፡- ንዑድ ክቡር ልዩ በሚሆን በአባታችን ዮሐንስ የዕረፍታቸው ቀን ጥቅምት 22 ቀን አንድ ዐረማዊ እስላም ሰው ለተሳልቆና ለመዘባበት ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ቈረበ። በአባታችን በዓል ዕለትም ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀብሎ ወጥቶ እየተቻኮለ ሔዶ ከእስላሞች መስጊድ ገብቶ በአባታችን በዮሐንስ በዓል ምክንያት የቆረበውን ቍርባን ተቀብሎ በወገኖቹ በከሃዲያኑ እስላሞች ፊት ተፋው። ወዲያውም የዚያ እስላም ሰው መላ ሰውነቱ አበጠ በንፋስ ገመድነትም ታንቆ ሰዎች እስኪያዩት ድረስ በሰማይና በምድር መካከል ተሰቀለ።

በተሰቀለበትም ቦታ ወፎችና አሞራዎች ይበሉት ጀመር፤ ሥጋውንም በሉት። በዚኽም ጊዜ ያ እስላም ድምፁን ከፍ አድርጎ ‹‹እኔ ንዑድ ክቡር ልዩ በሆነ በአባታችን በዮሐንስ አምላክ አምኛለሁ ብሎ መሰከረ። እግዚኣብሔርም የገዳማት ኮከብ በሆነው በብፁዕ ዮሓንስ ልመናና ጸሎት ፈጽሞ ይቅር አለው። ከዚኽም በኋላ ለብቻው ቀኖና ገባ የቀኖና ሥርዓቱንም ጨርሶ ንስሓ ገብቶ ከባለቤቱ ከልጆቹ ከቤተሰቦቹና ከዘመዶቹ ከጎረቤቱቹ ሁሉ ጋር የክርስትና ጥምቀትን ተጠመቀ ስሙንም ገብረ ዮሐንስ አሉት ትርጓሜውም የዮሐንስ ባለሟል ማለት ነው።

የአቡነ ዮሐንስ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን።

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

02 Nov, 11:32


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ጥቅምት 23 ልመናው ጸሎቱ በረከቱ በሁላችን ይደርብንና የልዳው ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ያደረገው ተአምር ይህ ነው፡- አግበራ በምትባል አውራጃ በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም የታጸች አንዲት ቤተ ክርስቲያን ነበረች፡፡ በድላይ የተባለ አንድ አረማዊ ገዥ ወደ እርሷ በደረሰ ጊዜ ወደ ቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ በአመጽ ገብቶ ከሚስቱ ጋር ከሴሰነ በኋላ በእሳት አቃጠላት፡፡ ዳግማዊ ቆስጠንጢኖስ የተባለ ንጉሣችን ዘርዐ ያዕቆብም ይህን በሰማ ጊዜ በሰማዕቱ፣ በእመቤታችንና በተወዳጅ ልጇ ኃይል ይህን አረመኔ በድላይን ለመውጋት ተዘጋጀ፡፡

ከሃዲው በድላይም በበኩሉ ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብን ለመውጋት ተነሣ፡፡ ውጊያውንም ለመጀመር በተነሡ ጊዜ በነጭ ፈረስ ላይ የተቀመጠ ፈረሰኛ ሰው በበድላይ የጦር ሠራዊት ውስጥ ታየ፡፡ ከኋላ ሆኖ ይነዳቸዋል፣ በሌላ ጊዜም ከፊት ሆኖ ይመራቸው ነበር፡፡ ከንጉሥ ዘርዐ ያዕቆብ አጠገብ ባደረሳቸው ጊዜ ግን ያ ነጭ ፈረሰኛ ከበድላ ሠራዊት ተለይቶ የበድላይን ጦር ለመውጋት ከንጉሣችን ዘርዐ ያዕቆብ ሠራዊት ጋራ ተቀላቀለ፡፡ በክርስቲያኖቹና በአረማውያኑ መካከል ጦርነቱ በበረታ ጊዜ አረማውያኑ ተሸነፉ፡፡ አለቃቸው በድላይም በጦርነቱ መካከል በጦር ተወግቶ ወድቆ ሞተ፡፡

በድላይም ክፉ አሟሟት ሲሞት ባዩት ጊዜ ከሠራዊቱም መካከል ብዙዎቹ ‹‹በድላይ ከልቡ ትዕቢት የተነሣ ክፉ አሟሟት ሞተ፣ እግዚአብሔር ለእሥራኤል ይዋጋለቸው ነበርና በንጉሥ ሕዝቅያስ ዘመን ሰናክሬም እንደተዋረደ፣ በዮዲትም ዘመን ሆሎፎርኒስ እንደተዋረደ በድላይም ዛሬ ክፉኛ ተዋረደ›› ተባባሉ፡፡ ንጉሥ ዘርዐ ያዕቆብም በእመቤታችንና በሰማዕቱ በቅዱስ ጊዮርጊስ ተራዳኢነት የአረማውያንን ሬሣ ምድርን እስኪሸፍናት ድረስ በጦርነቱ አሸናፊ ሆነ፡፡ የሞቱትና ተማረኩትም ብዛታቸው በቁጥር አይታወቅም ነበር፡፡ ዘመናዊ የሆኑት የጦር መሣሪያዎቻቸውም እጅግ ብዙ ነበሩ፡፡ ራሱ ንጉሡ በድርሳኑ እንደገለጸው ‹‹ወደ ቤተ መግሥቴ የገባው የራሳቸው የሰዎቹና የፈረሶቻቸው ጌጥ በያይነቱ ሊናገሩት የማይቻል እጅግ አስደናቂ ነበር›› አለ፡፡ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስም አረማውያንን ስለመውጋቱ አረማውያኑ ራሳቸው ሲመሰክሩ ‹‹በነጭ ፈረስ ላይ ተቀምጦ በግልጽ ሲዋጋን የነበረው ቅዱስ ጊዮርጊስ ነበር›› አሉ፡፡ ክርስቲያኖቹም ‹‹ሰማዕቱ እረዳን›› በማለት ተደሰቱ፡፡

በዚያም የጦርነቱ ቀን ሌሊቱን ቅዱስ ጊዮርጊስ በስሙ በታነጸች ወደ አንዲት ሌላ ቤተ ክርስቲያን ሄደና የጦር መሣሪያ በታጠቀ አርበኛ ወይም ወታደር ተመስሎ ለአንድ ቄስ ተገለጠለት፡፡ ጦሩን በእጁ ይዟል፣ ፈረሱም በጣም አልቦት ነበር፡፡ የጦር መሣሪያ በታጠቀ አርበኛ አምሳል ለቄሱ የተገለጠለትም ‹‹ዛሬ ከበድላይ ጋር ጦርነት ውዬ መጣሁ›› አለው፡፡ ስለዚህም እኛ የክርስቶስ ወገኖች የቅዱስ ጊዮርጊስን የተአምራቱን ማረጋገጫ ምስክር ከራሱ አገኘን፡፡ የቅዱስ ጊዮርጊስ ጸሎቱ በረከቱ የረድኤቱም ሀብት የተዋሕዶ ልጆች የሆንን ሁላችን ይጠብቀን፡፡ የዓሥራት ሀገሩን ቅድስት ኢትዮጵያን ይጠብቅልን!!!
✞ ✞ ✞

ዳግመኛም ዛሬ ለአባቶች ሊቃ ጳጳሳት 52ኛ የሆኑት የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሴፍ ዕረፍታቸው ነው፡፡ ይኸውም በዘመናቸው ከነበረው ከኢትዮጵያው ንጉሥ ጋር ለየት ያለ አስገራሚ ታሪክ የነበራቸውና ብዙ ተአምራትን ያደረጉ ናቸው፡፡

እንዲሁም በዚህች ዕለት የቆሮንቶስ አገር ኤጲስቆጶስ ዲዮናስዮስ በዐላዊው ነገሥታት በዲዮቅልጥያኖስና በመክሲምያኖስ ዘመን በሰማዕትነት ዐርፈዋል፡፡ እኚህንም ቅዱስ ከሃድያኑ ነገሥታት በያዟቸው ጊዜ ጽኑ በሆኑ ልዩ ልዩ ሥቃዮች አሠቃዩአቸው፡፡ ማሠቃየትም በሰለቻቸው ጊዜ በዚህች ዕለት የአቡነ ዲዮናስዮስን ራስ በሰይፍ አስቆረጡት፡፡ የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበሉ፡፡
✞ ✞ ✞

ዳግመኛም በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ተተክለው በደብረ ሊባኖስ የተሾሙት አቡነ ኤልሳ ዕረፍታቸው ነው፡፡ ጻድቁ ሀገራቸው ሸዋ ነው፡፡ በዐፄ ይኩኖ አምላክ ዘመን የነበሩ ሲሆን ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት ቀጥለው በደብረ ሊባኖስ ገዳም በእጨጌነት የተሾሙ የመጀመሪያ ዕጨጌ ናቸው፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከማረፋቸው በፊት ‹‹በእኔ ወንበር ኤልሳዕ ይሾም ነገር ግን ዘመኑ ትንሽ ስለሆነ ከእርሱ ቀጥሎ ፊሊጶስን ትሾማላችሁ›› ብለው ለቅዱሳን ተከታይ ሐዋርያቶቻቸው ተናግረው ነበር፡፡

በዚህም መሠረት አቡነ ኤልሳዕ ተሹመው ብዙም ሳይቆዩ አንድ ዲያቆን ሞተና ሊቀብሩት ሲወስዱት በመንገድ ላይ ሳለ ድንገት ከሞት ተነሥቶ ‹‹አባቴ ተክለ ሃይማኖት ኤልሳዕ አሁን ወደኔ ስለሚመጣ ፊሊጶስን ሹሙት ብለህ ተናገር ብለውኝ ነው›› ብሎ ከተናገረ በኋላ ተመልሶ ዐርፎ ተቀበረ፡፡ አቡነ ኤልሳዕም ወዲያው ዐርፈው አቡነ ፊሊጶስ 3ኛ ሆነው ተሾሙ፡፡ አቡነ ኤልሳዕ ከተጋድሎአቸው ብዛት የተነሣ በሕይወት ዘመናቸው ሁሉ ጎናቸውን አሳርፈው ተኝተው አያውቁም ነበር፡፡ ነገር ግን ማረፍ ሲኖርባቸው በወንበር ላይ ተደግፈው ትንሽ ብቻ ያርፉ ነበር፡፡ አቡነ ኤልሳዕ በሞት ያረፉትም እንደልማዳቸው ጎናቸውን ሳያሳርፉ በወንበር ላይ እንደተደገፉ ነበር፡፡ አባታችን ስለዚህም ጉዳይ ሲናገሩ እንዲህ ይሉ ነበር፡- ‹‹ነፍስ ትጋትን ትወዳለች፣ ሥጋ ግን ይደክማል፡፡ ለመነኮሳትና ለእግዚአብሔር አገልጋዮች ሁሉ መኝታ ማብዛት አይገባቸውም፡፡ መኝታ ማብዛት ሕልምን ያመጣል፣ ነፍስን ይጎዳል፣ ሰውነትንም ያደክማል፡፡››

አቡነ ኤልሳዕ በዘመናቸው ወንጌልን በማስተማርና ድንቅ ድንቅ ተአምራትን በማድረግ ይታወቁ ነበር፡፡ እንደ ነቢዩ ኤልሳዕ እሳቸውም ሙት አስነሥተዋል፡፡ ባሕር እየከፈሉ ቀደ መዛሙርቶቻቸውን ያሻግሩ ነበር፡፡ በጸሎታቸው የዠማን ወንዝም ለሁለት የከፈሉ ታላቅ አባት ናቸው፡፡ የአባቶቻችን በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

02 Nov, 11:32


ከአባታችን ይባረኩ፤ እጅ ይነሡም ዘንድ አርባ አራት ቅዱሳን በደመና ተጭነው አባታችን ካለበት ቦታ ወደ ዐደል መጡ፡፡ ሶምሶን ከአህያ መንጋጋ፤ ሙሴ ከዐለት ውሃ እንዳፈለቁ ሁሉ ለሚያስፈልጋቸው ነገር ይጠቀሙበት ዘንድ አባታችንም በጸሎቱ በአንድ ጊዜ አርባ አራት የውሃ ምንጮችን አፍልቆ ሰጣቸው፡፡ እነርሱም ይህን አይተው አደነቁ፤ ስምህ ዘግሩም ይሁን አሉት፤ ስለዚህም አባታችን አባ ዘግሩም ተባለ፤ ምንጮቹም ድውያንንና ሕሙማንን የሚፈውሱ ሆኑ፡፡
ዳግመኛም ለአባታችን የሚገለገልበት አንድ አህያ ነበረው፤ የሚጭነው ሰው ሳይከተለው ለሁለት ቀናት ሔዶ ወደ ጫነው ሰው ቤት ይመለስ ነበር፤ የአገሩ ሰዎችም ይህን አይተው ያላቸውን ሁሉ ይጭኑትና ብቻውን ሔዶ ወደ አባታችን ይመለስ ነበር፡፡

የአቡነ ብርሃነ መስቀልን ተአምራቱን ዜናውን በሰማ ጊዜ ከንጉሡ ባለሟሎች አንዱ መጣ፡፡ ሌላም በቤቱ አጠገብ የሚኖር አንድ ሰው መጣና ‹‹ጨው ጭኜ ወደ ገበያ እወስድበት ዘንድ አህያህን ስጠኝ›› ብሎ ለመነው፡፡ የተቸገሩትን ለመርዳት የሚልከው አንድ አህያ ነበረውና አባ አብርሃምም ‹‹የጨው መጠን ምን ያህል ነው?›› አለው፡፡ ያ ሰውም ‹‹በሰቅል ስሳ ይሆናል›› አለው፡፡ አባታችን አብርሃምም ‹‹ውሰደው ከተናገርኸው በላይ ግን አትጫነው›› አለው፡፡ ሰውየውም አህያውን ወስዶ አባታችን እንዳለው ጫነው፤ ለአባታችን ያልነገረውን በቤቱ የተረፈውን ግን ያ ሰውና ወንድሙ ተሸከሙት፡፡

እነርሱም ተካፍለው ተሸክመው መንገዳቸውን እየሄዱ ሳለ ከአገር ብዙ በራቁ ጊዜ ወንድሙን ‹‹ና አህያውን እንጫነውና እንደፈቀድነው እንሒድ የሚያየን የለምና›› አለው፡፡ በዚሀመ ምክራቸው መሠረት ተሸክመውት የነበረውነ በአህያው ላይ ጫኑት፡፡ ነገረ ግን አህያው መንቀሳቀስን ፈጽሞ እምቢ አለ፤ ወደ ቀኝም ወደ ግራም አላለም፤ ሲገፉትና ሲደበድቡት ብዙ ደከሙ፤ እንዲህ እያደረጉ ሳሉ አንድ አገልጋይ የንጉሥ መልእክት ይዞ መጣ፡፡ እኒህን ስሕተተኞችም አገኛቸውና ‹‹ጌቶቼ ለምን ትደክማላችሁ?›› አላቸው፡፡

እነርሱም ‹‹ይህ አህያ አልሄድም አለን›› አሉት፤ የንጉሡ መልእክተኛም መንፈስ ቅዱስ አነሳሳውና ከፊታቸው ቆመና ‹‹የዚህ ነገር ምክንያቱ ምንድን ነው?›› አላቸው፡፡ እነርሱም ‹‹ይህን አህያ ከአንድ መንፈስ ቅዱስ ካደረበት ቀሲስ አመጣነው፤ በዚህ ቀሲስ ቃል ላይ በጨመርን ጊዜ መሔድን እምቢ አለን›› በማለት የሠሩትን ነገሩት፡፡ ‹‹እስኪ የጨመራችሁትን ቀንሱለት›› አላቸው፤ ቀነሱለትና ያን ጊዜ አህያው ተነሥቶ እነርሱም ወደሚፈልጉበት ቦታ ሔዱ፡፡ ይህንንም ሁለት ጊዜ ሦስት ጊዜ ደጋግመው አደረጉ እምቢም አላቸው፡፡ ይህ ሁሉ የሆነው የቅዱሱን ቃል በመተላለፋቸው እንደሆነ አወቁ፤ ያም የንጉሡ አገልጋይ ተደንቆ ‹‹ኑ ይህ ቅዱስ ካለበት አድርሱኝ›› አላቸው፡፡ አባታችን ካለበት ቦታም ደርሶ ከእርሱ ዘንድ ተባረከ፡፡
ያም አህያውን የወሰደው ሰው ከአቡነ ብርሃነ መስቀል እግር ሥር ተንበርክኮ ‹‹በፊትህ በድያለሁና ቃልህንም አሳብያለሁና አባቴ ሆይ ይቅር በለኝ፤ አህያውም መሄድን እምቢ አለ፤ የጨመርንበትን ሸክም በቀነስንለት ጊዜ ግን ይሄዳል›› አለው፡፡ ዳግመኛም ‹‹…እኔ ግን እንደ እኔ አይነት ሰው ነህ መስሎኝ ቃልህን አፈረስሁ፤ አንተ ግን በፍቅርህ ገመድ ሳብኸኝ›› አለው፡፡ አባታችን ብርሃነ መስቀልም ‹‹ለምን ሐሰት ተናገርህ? መጽሐፍ ‹ሐሰት የኀጢአት መጀመሪያ ናት፤ ሐሰተኞችም የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም› ይል የለምን?›› በማለት ከመከረው በኋላ በሰላም ወደቤቱ እንዲሔድ ነገረው፡፡

ያም ሰው ከአቡነ ብርሃነ መስቀል ዘንድ ወጥቶ መንገዱን ሔደ፤ ያ የንጉሡ መልእክተኛም አብርሃም ከተባለ ከአቡነ ዘግሩም ዘንድ ተባርኮ ወጣ፤ የቤተ ክርስቲያኗንም አሠራር አይቶ የአባታችን የአብርሃምን ተአምር አደነቀ፤ የንጉሡን ትእዛዝ ይፈጽም ዘንድም መንገዱን ሄደ፡፡ ከብዙ ቀናት በኋላ ያ መልእክተኛ ከንጉሡ ዘንድ ደረሰ፤ ስመ መንግሥቱ ቆስጠንጢኖስ ለተባለ የእግዚአብሔር ወዳጅ ለሆነ ለንጉሥ ዳዊት ነገሩን ነገረው፡፡ ‹‹ጻድቅ ንጹሕ የሆነ ቀሲስ አለ፤ በዚህ ዘመን በመንግሥትህ ሀገር ሁሉ እንደርሱ ያለ ሰው የለም፤ ሥራው ሁሉ እንደቀደሙት አባቶች ነውና›› አለው፡፡
በዐይኑ ያየውን፤ በጆሮው የሰማውን ሁሉ ስለሠራት ቤተ ክርስቲያንም ነገረው፤ ንጉሡም ይህን ሁሉ በሰማ ጊዜ በልቡ ተደሰተ፤ በመንፈሱም ሐሴትን አደረገ፤ እግዚአብሔርንም አመሰገነው፤ እንዲህም አለ፡- ‹‹በዘመነ መንግሥቴ የተሰወረውን የሚያውቅ፤ ተአምራትን የሚያደርግ እንዲህ ያለ ጻድቅ ሰውን የሰጠኝ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ስሙ ይክበር፡፡ አባቴ ቤተ ክርስቲያን ማነጽ በፈለግህ ጊዜ ወደ እኔ ለምን አልላክህም ብሎ ላከበት፤እኔ ከደቀ መዛሙርትህ እንደ አንዱ አይደለሁምን በረከትህን በተቀበልሁ ነበር አለ፡፡ በዚህ የመንግሥት ዙፋን ላይ ያለሁ በእግዚአብሔር ፈቃድ ነው እንጂ በራሴ ፈቃድ ይመስልሃልን በእስረኞች መካከል ሳለሁ ከእስረኞች መካከልም ተኝቼ ሳለ ከዚያ አውጥቶ በአባቶቼ በሰይፈ አርዕድና በዐምደ ጽዮን ዙፋን ላይ አስቀመጠኝ፡፡ አንተ ግን በኀጢአቴ አትናቀኝ፤ ለቤተ ክርስቲያን የምትፈልገውን ይህን ገንዘብ ውሰድ፡፡›› ዳግመኛም ለአባታችን ልብስ ላከለት፤ ሚስቱም እንዲሁ ላከች ‹‹በጸሎትህ አትርሳን›› አሉት፡፡

ከዚህም በኋላ ይመነኩስ ዘንድ ወደደ፤ የመላእክትና የቅዱሳን ልብስ የምትሆን የምንኩስና ልብስን ያለብሰው ዘንድ የአቡነገብረ መንፈስ ቅዱስ ረድእ ወደ ሆነው ወደ አባ ብሶይ መጣ፡፡ ወደ እርሱ ደርሶ ሥርዐተ ምንኩስና ከፈጸመለት በኋላ አባታችን አብርሃም ‹‹የቀድሞ ስሜን ተውልኝ›› አለው፤ አባ ብሶይም ‹‹ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የደቀ መዛሙርቱን ስም እንደ ለወጠላቸው ስምህን እለውጣለሁ እንጂ አይሆንም›› አለው፡፡ ‹‹ስምህንም አብርሃም፣ ጳውሎስ፣ ዮሐንስ ከሚሉት መካከል ዕጣ በማጣጣል እሰይምሃለሁ›› አለው፡፡
ሦስት ጊዜም ዕጣ ጣሉ፤ አብርሃም የሚለውም ስም ወጣ፤ ይህ ነገር ከእግዚአብሔር እንደሆነ አወቀ፡፡ከታናሽነቱ ጀምሮ የአብርሃም ምግባር የሆነውን እንግዳ መቀበልን፣ እግር ማጠብንና የተራበውን ማብላት ጀመረ፤ ስለዚህ አብርሃም መባል ተገባው፡፡ ‹‹ከታናሽነቴ ጀምሮ የአብርሃምን ሃይማኖት እንደወደድሁ፣ እንግዳ በመቀበል እንደ ኖርሁ ይህን ስም የሰጠኝ እግዚአብሔር ይመስገን›› አለ፡፡ መንኩሶ በፈቃዱ አብርሃም ተብሎ ተጠርቷልና በብዙ ገድልና በትሕርምት በዚያች ቦታ ኖረ፡፡

የነዳያን ፍቅር በልቡ ውስጥ አለ፤ ሁል ጊዜ ስለ ምግባቸውና ስለ ልብሳቸው ያስብ ነበር፤ ለሚያስፈልጋቸው ነገርም ገንዘብ ይሰጣቸው ነበር፡፡ ለድኆች ልብሱን ያካፍላል፤ ለእነርሱም ሰጥቶ እርሱ ራቁቱን ይቆማል፤ ልጆቹም ይመጣሉ፤ ‹‹ልብስህ ወዴት ነው?›› ይሉት ነበር፤ እርሱም ‹‹ሌቦች በማያገኙበት ቦታ አለ›› ይላቸው ነበር፡፡ ልጆቹ ግን ሥራውን አያውቁም ነበር፤ ውዳሴ ከንቱ እንዳይሆንበት ሁሉን ይሠውር ነበር፤ አይገልጥላቸውም ነበር፤ ድኃ ባየ ጊዜ አጽፉን ይሰጥ ነበር፤ አጽፉን ይቅርና ምንም ልብስ አያስቀርም ነበር፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

02 Nov, 11:32


አንድ ቀን አንድ ድኃ መጥቶ ስለ እግዚአብሔር ስም ምግብና ልብስ ለመነው፡፡ አባታችን ያን ድኃ ባየው ጊዜ አጽፉን ሰጠው፤ ዳግመኛ አንድ ድኃ መጣ፤ በቤቱም የሚሰጠውን አጣ፤ መጠምጠሚያውን አውርዶ እርሷንም ለድኃው ሰጠውና በቤቱ ተቀመጠ፡፡ አንድ ደቀ መዝሙሩ ወደ ቤቱ መጥቶ ራቁቱን አገኘውና ተቆጣበት፤ ‹‹ክቡር አባቴ ሆይ! ለምን እንዲህ ትሆናለህ? አለው፡፡ ‹‹ለምትበላውና ለምትለብሰው ሳታስቀር ያለ አቅምህ ለምን ምጽዋት ትሰጣለህ? ልብስህንና መጎናጸፊያህን ሰጥተህ አንተ ራቁትህን ትሆናለህ፡፡›› አባታችንም ‹‹ልጄ ሆይ! ፈጽሞ ስለሚያረጅና ስለሚጠፋ የዚህ ዓለም ልብስ ፈንታ የብርሃን መጎናጸፊያ የሚያለብሰኝ አምላኬ አለልኝ›› አለ፤ ልጆቹም ሌላም ልብስ አምጥተው አለበሱ፡፡ ‹‹ይህንም እንደ ቀደመው አታድርግ›› አሉት፤ እርሱ ግን ስለ ድኆችና ስለ ችግረኞች ፍቅር ብዙ ጊዜ ምጽዋት ያደርግ ነበር፤ ቅብዓት በሰውነት፣ ውሃ በአንጀት እንዲገባ የነዳያን ፍቅር ወደ ልቡ ገባ፡፡
የነዳያንን የጩኸት ድምፅ በሰማ ጊዜ ከልቡ ደስታ የተነሣ ለመነሣት ይፈልጋል፤ ከማእድ ላይ ቢሆንም እንኳን ድምፃቸውን ከሰማ እጁን ወደ ማእድ አያወርድም ነበር፤ ይሰጣል እንጂ ምንም ነገር አያተርፍም ነበር፡፡ ነዳያን ግን ዘወትር ጩኸትና ልመናን አያቋርጡም ነበር፤ አባታችን ስለ ምግባቸውና ስለ ልብሳቸው እንደሚያስብ አውቀው ከቤቱ አይርቁም ነበር፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን ወደ አንዲት ታላቅ ሀገር ሔዶ ከዚያ ደረሰ፤ በሰንበት ምሽት ለእሑድ አጥቢያ ከዚያ አደረ፤ ሥርዓተ ቁርባን ከተፈጸመ በኋላ ደቀ መዝሙሩን ‹‹ልጄ የምንበላው ነገር አለህ ወይስ የለህም?›› አለው፤ ያ ደቀ መዝሙርም ‹‹አባቴ አዎን አለኝ›› አለው፡፡ በቤተ ክርስቲያን ያያቸውን ታላላቅ መነኮሳት ሰበሰበ፤ ቁጥራቸውም ዐራት መምህራን ነበሩ፡፡ የተዘጋጀ ምግብና ጠላ ያን ጊዜ እነርሱም ከቤታቸው እንጀራ አመጡ፤ ሁለት ያመጣ አለ፤ ሦስትም ያመጣ አለ፤ ሁላቸውም እንደ አቅማቸው አመጡ፤ አባታችንም ጸሎት ያደርግ ዘንድ ተነሣ፤ ባረከላቸውም፡፡
ደቀ መዝሙሩንም ‹‹ጠላውን አምጣው›› አለው፤ ሁለት መነኮሳትም እንሥራውን አመጡት፤ ከመካከላቸው አንዱን ጠጣ አለው፤ ቀምሶም ለአባታችን ሰጠው፤ ጣዕሙ ደስ ባሰኘው ጊዜ አባታችን ከሩቅ ሀገር የመጡ የተራቡ ሰዎች ከቤቱ ደጃፍ እንዳሉ አወቀ፡፡ መነኮሳቱንም ‹‹አባቶቼ፣ ወንድሞቼና ልጆቼ ፈቃዳችሁ ከሆነስ ለክርስቶስ እንሰጠው ዘንድ ለነዳያንና ለችግረኞች እንስጣቸው›› አላቸው፡፡
በቤተ ክርስቲያን የተሰበሰቡ ወንድሞች መነኮሳት፣ ክቡራን ካህናት፣ ዲያቆናትና ሕዝቡ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ የሆነ፣ በወንጌል ወተት ያደገ፣ የእግዚአብሔር ሰው የሆነ የአባታችንን ትሕትና፣ ትሩፋትና ቅድስና ባዩ ጊዜ አዘኑበት፡፡ ምንም ቃል አልመለሱለትም፤ በቦታቸው ወይም በቤታቸው አልነበሩምና፤ በልባቸው ‹‹እኛስ ከሩቅ ሀገር የመጣን አይደለምን?›› አሉ፡፡ እነርሱ ግን ከዚያው ይኖሩ ነበር፤ አባታችን ግን ነዳያንን ሰብስቦ ያንን ምግብ ሰጣቸው፡፡
ወደ ቤቱ ተጠርተው የመጡ እነዚያ መነኮሳትም አንዲት ቃል አልተናገሩም፤ ነገር ግን በልባቸው ተቆጡ፤ በጣምም አዘኑ፤ አባታችን ግን ደቀ መዛሙርቱን ሌላ ማእድ ያቀርቡ ዘንድ አዘዘ፤ ከመንገድ ስንቅ ይመገቡ ነበርና ጥቂት አመጡ፡፡ ገና ሳይቀምሱም ከሕዝብ አንዱ ‹‹አባቴ ሆይ! ጸልይልኝ፤ ይህን ጥቂት በረከትም ተቀበል›› ብሎ ብዙ ጠላ ላከ፤ እነዚህ መነኮሳት ግን ይህን ባዩ ጊዜ ፈጽመው ተደነቁ፤ ፈጽመው ፈሩ፤ ተንቀጠቀጡም፡፡ አባታችንም ተነሥቶ ለክርስቶስ ሰጠሁት፤ ለተራቡትም አስቀደምሁ፤ ለድኆች የሚሰጥ ለእግዚአብሔር ያበድራል የሚል ተጽፏልና አላቸው፡፡
እነዚህ መነኮሳትም ‹‹አባታችን መምህራችን ሆይ! ይቅር በለን አንተ ብዙ ሐዘንን ታውቃለህና፤ እኛ ስለሆዳችንና ስለልብሳችን አዘንን፤ አንተ ግን እንደ ጌታህ ክርስቶስ የድኆችና የችግረኞች ወዳጅ ነህና›› አሉት፡፡ ‹‹አላወቅንምና አባታችን ይቅር በለን፤ አንተ ፈቃደ እግዚአብሔርን ትፈጽማለህ፤ እርሱም ልመናህን ይሰማልና›› አሉት፡፡ ‹‹እንዲሰጥህ አላወቅንም፤ ነገር ግን ጎተራህን ሁሉ እንደሚሞላልህ ሰምተን ነበር፤ የተዘጋጀ ምግብንም እንዳወረደልህ ሰምተን ረሳን፤ አሁንም አባታችን ይቅር በለን፤ ባንተ ላይ ተቆጥተን ነበር፤ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር እንደሆነ አላወቅንም፤ አንተ ግን አስቀድመህ ለተራቡት ሰጠህ፤ ቀጥሎም ከአምላክህ በረከት ለእኛ ለመብላት ለተዘጋጀን ሰጠኸን›› አሉት፡፡ አባታችን ዘግሩምም ‹‹ወንድሞቼና ልጆቼ ይህን የማደርገው ለሰው ልታይ ብዬ አይደለም፤ ለትምክህትም አይደለም፤ እግዚአብሔር የሰጠኝ ሀብት ነው እንጂ›› አላቸው፡፡ ‹‹እኔ እሰጣለሁ፤ እርሱም የሚያስፈልገኝን ነገር አላሳጣኝም›› አላቸው፤ እነርሱም ከእርሱ ተባረኩ፤ ከዚህም በኋላ ታላላቅ ተአምራትና ድንቅ ነገርን የሚያደርግ የእግዚአብሔርን ገናናነት ተነጋገሩ፡፡
ከዕለታት አንድ ቀንም አባ ዘግሩም ቆሞ ሳለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ እርሱ መጣ፤ ቅድስት የሆነች የጎኑን መወጋትና ቁስሎቹን ሁሉ አሳየው፡፡ በደሙ መፍሰስም ተደሰተ፤ ሰግዶም እንዲህ አለ፤ ‹‹ጌታየ የሚፈሰውን ደምህን እዳስስ ዘንድ ፍቀድልኝ›› አለው፤ ጌታችንም ቅዱስ የሆነ ደሙን ይዳስስ ዘንድ ፈቀደለት፤ እንደ ቶማስም ጎኑን ዳሰሰ፤ ቶማስስ ደቀ መዛሙርቱን ስላላመነ ነበር፤ ይህ አባታችን ግን ጌታችን ‹‹ሳያዩኝ የሚያምኑኝ ብፁዓን ናቸው›› ብሎ እንደተናገረው ሳያይ ያመነ ነው፡፡ ይህ አባታችን ግን ሳያይ አመነ፤ በቅዱስ ደሙ መፍሰስም ደስ አለው፤ ወንድሞቼ ሆይ ለአባታችን የተሰጠውን ጸጋ ተመልከቱ፤ የመድኃኒታችንን ቁስሎች ዳስሷልና፤ ለድኆች የማዘን ፍሬው ይህ ነው፤ ‹‹ለድኆች የሚራራ ለእግዚአብሔር ያበድራል›› ተብሏልና፡፡
ለሰው ልጅ የሚሰጥ ታላቅ ጸጋን አገኘ፤ ከሀገሮች ሲመለስም ወደ ደብረ ጽዮን ለመሄድ ግባ ከተባለ ታላቅ ወንዝ ደረሰ፤ ከፈሳሹ ብዛት የተነሣ ስትበረታታ አገኛት፡፡ ብዙ ሰዎች ከእርሱ ጋር ነበሩ፤ የሚያደርጉትንም አጡ፤ ብፁዕ አባታችን ግን ከወንዙ ዳር ቆመ፤ በምርጉዙም በባሕሩ ላይ አማተበ፤ ያን ጊዜ ወንዙ ወዲያና ወዲህ ተከፈለ፤ በዚያ የነበሩ ሰዎች ሁሉ ተሻገሩ፡፡ ነቢዩ ሙሴ የኤርትራን ባሕር በከፈላት ሕዝቡንም በመራ ጊዜ እንደ ተሻገሩ ሁሉ ተሻግረዋልና እግዚአብሔርን አመሰገኑ፡፡ ይህም አባታችን ባሕርን በየብስ አሻገራቸው፤ ከዚህ በኋላ በሰላም ወደ ቤቱ ደረሰ፡፡ እንዲሁ እግዚአብሔር ሁላችንን ይጠብቀን፤ የአባታችን የአባ ዘግሩም ጸሎቱና በረከቱ በቃል ኪዳኑ የምንታመን የወንጌል ልጆች ሁላችንን ሕዝበ ክርስቲያኑን ይጠብቀን ለዘለዓለሙ አሜን፡፡

(ምንጭ፡- ገድለ አባ ዘግሩም)

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

02 Nov, 11:32


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ጥቅምት 24-ጌታችን ተገልጦላቸው በፍቅር የተወጋ ጎኑን በእጃቸው እንዲዳስሱ የፈቀደላቸው እርሳቸውም ያላቸውን ሁሉ አውጥተው ለድኆችና ለችግረኞች፤ ለባልቴቶችና እናት አባት ለሌላቸው ምጽዋትን ከሰጡ በኋላ ሌላ የሚመጸውቱት ቢያጡ እርቃናቸውን እስኪቀሩ ድረስ የለበሱትን ልብሳቸውን እያወለቁ ለነዳያን ይሰጡ የነበሩት መፍቀሬ ነዳያን አባ ዘግሩም ዓመታዊ መታሰቢያ በዓላቸው ነው፡፡ ይኸውም በዚህች ዕለት መልአክ ከሰማይ ታቦተ መድኃኔዓለምን አምጥቶ ሰጥቷቸዋል፡፡
+ ዳግመኛም በዚህች ዕለት መስተጋድል መነኮስ አባ አብላርዮስ ዕረፍቱ ነው፡፡
+ ቅድስት ጸበለ ማርያም ተሐራሚት የዕረፍቷ መታሰቢያ በዓል መሆኑን ስንክሳሩ በስም ይጠቅሳታል፡፡
አባ አብላርዮስ፡- ይህም ቅዱስ ጋዛ ከሚባል አገር የተገኘ ሲሆን ወላጆቹ አረማውያን ናቸው፡፡ የዮናናውያንን ትምህርታቸውንና ፍልስፍናቸውን ሁሉ አስተምረው አሳደጉት፡፡ በዚህም የአብላርዮስ ሰውነቱ ለጥበብ ማደሪያዋ እስከሆነ ድረስ በዕውቀት ከሁሉም በላይ ሆነ፡፡ ከዚህም በኋላ ከሀገሩ የሌለ ሌላ ጥበብን ከውጭ አገር ይማር ዘንድ ወደ እስክንድርያ አገር ሄደ፡፡

በእስክንድርያም መምህራን ሁሉ ከሚገኖሩበት ቦታ ገብቶ ከእነርሱ ብዙ ትምህርትን ተማረ፡፡ በዚያም የቤ ክርስቲያንን መጻሕፍትን አግኝቶ ማንበብ ጀመረ፡፡ የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳሳት አባ እለ እስክንድሮስም መጻሕፍትን ይተረጉምለትና ያስረዳው ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ ክብር ይግባውና አብላርዮስ በጌታችን አምኖ የክርስትና ጥምቀትን ተጠመቀ፡፡ ከዚያም መንኩሶ መንፈሳዊውን ገድል መፈጸም ጀመረና ብዙ ተጋደለ፡፡ ወደ አባ እንጦንዮስ ዘንድ ሄዶ መንፈሳዊ የሆኑ ብዙ ትሩፋቶችን እየሠራ ከእርሳቸው ብዙ ተማረ፡፡

ከዚሀም በኋላ አባ አብላርዮስ ወላጆቹ እንደሞቱ በሰማ ጊዜ ሄዶ የተውለትን ገንዘባቸውን ሁሉንም ወስዶ ለድኆችና ጦም አዳሪዎች መጸወተው፡፡ ከዚያም ወደ ሶርያ ገዳማት በመሄድ በአንዱ ገዳም ገብቶ ፍጹም የሆነውን ጽኑ ተጋድሎውን በዚያ ፈጸመ፡፡ ከጾም ጸሎት ስግደት ብዛት ሰውነቱ አልቆ ቆዳው ከአጥንቱ እስኪጣበቅ ድረስ ተጋደለ፡፡ እርሱም በሰባት ቀን አንድ ጊዜ ብቻ የሚመገብ ሆነ፣ ምግቡም የዱር ሣር ነው እንጂ የላመ የጣፈጠ ምግብን አይቀምስም ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ ልዩ ልዩ የሆኑ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን የማድረግና ሀብተ ትንቢትን ተሰጠው፡፡ ቅዱስ ኤጲፋንዮስን ያመነኮሰውና ለደሴተ ቆጵሮስ ኤጲስቆጶስ እንደሚሆን ትንቢትን የተናገረለት አባ አብላርዮስ ነው፡፡

አባ አብላርዮስም በምንኩስና እየተጋደለ 63 ዓመት ኖሮ አጠቃላይ በ80 ዓመቱ ተጋድሎውን ፈጽሞ በዚህች ዕለት በሰላም ዐርፏል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅና ቅዱስ ባስልዮስ አባ አብላርዮስን በየድርሣኖቻቸው ደጋግሞ አመስግነውታል፡፡
+ + +

መፍቀሬ ነዳያን አባ ዘግሩም፡- አባታቸው ገርዜነ ጸጋ የተባለ ደገኛ ካህን ሲሆን እናታቸው ደግሞ ነፍስተ እግዚእ ትባላለች፡፡ እነዚህም ደገኛ ክርስቲያኖች በእግዚአብሔር ሕግ ጸንተው ብዙ ዘመን ሲኖሩ የተባረከ ልጅ ይሰጣቸው ዘንድ እግዚአብሔርን ይለመኑት ነበር፡፡ ልዑል እግዚአብሔርም መልአኩን ልኮ የተባረከ ልጅ እንደሚወልዱ አበሰራቸው፡፡ አባ አብርሃምም በመልአኩ ብሥራት ግንቦት ሃያ አራት ቀን በተወለዱ ጊዜ ወላጆቻቸው ብርሃነ መስቀል ብለው ጠሩት፡፡ በኋላ የተጠራበት ስመ ጥምቀቱ ግን ማኅፀንተ ሚካኤል ነው፡፡ ወላጆቹም በመንፈሳዊ አስተዳደግ ስላሳደጉት ከልደቱ ጀምሮ ጸጋ እግዚአብሔር አደረበት፡፡ በመንፈስ ቅዱስ አደገ፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያንም መሄድን አላስታጎለም፡፡ እንደ ነቢዩ ሳሙኤል ከታናሽነቱ ጀምሮ በእግዚአብሔር ቤት አድጓልና፡፡
አድጎ ለትምህርት በደረሰ ጊዜ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን፣ መጻሕፍተ ነቢያትን፣ መዝሙረ ዳዊትን ይማር ዘንድ አባቱ ለመምህር ሰጠው፡፡ ሕፃኑም በትምህርቱ አስተዋይ ሆነ፡፡ ሳያቋርጥ ሁልጊዜ ከመምህሩ መረዳትን ያበዛ ነበር፡፡ በመንፈስ ቅዱስም ኃይል የጸና ሆነ፡፡ ዲቁናም ከተሾመ፡፡
ከዚህም በኋላ እናቱና አባቱ ያለ ፈቃዱ ሚስት ያጩለት ዘንድ ወደዱ፡፡ በመጽሐፍ ‹‹የልጅ ልጅህን ታያለህ፣ አንተ ብፁዕ ነህ፣ መልካምም ይሆንልሃል›› የሚል በመጽሐፍ ተጽፏልና፡፡ ስለዚህም ያጋቡት ዘንድ አቻኮሉት፤ እርሱ ግን ዓለመን ፍጹም ንቆ በምንኩስና በተጋድሎ መኖርን ወደደ፡፡

ለምንኩስናም ስሙ አባ ክርስቶስ ይባርከነ ወደተባለ አንድ መነኩሴ ወዳለበት ገዳም ሲሄድ በመንገድ መደራ በተባለች ቦታ በታላቅ ገዳም ውስጥ ከእንግዶች ጋር አደረ፤ በሌሊት በነቃ ጊዜ አንድ ድኃ በዚያች ቤት ውስጥ አገኘ፤ የድኃውን ልብስ ወስዶ የእርሱን ልብስ ሰጥቶተ በሌሊት ወጥቶ መንገዱን ሔደ፡፡ በነጋም ጊዜ ያ ድኃ ያደረገለትን ለሰዎቹ ተናገረ፡፡ ‹‹በእንግዳ ማደሪያ ከእኔ ጋር አብሮ ያደረ አንድ ሰው እኔ የለበስሁትን ልብስ ወስዶ የእርሱን መልካም ልብስ ተወልኝ›› አላቸው፡፡ እነርሱም ‹‹… የእግዚአብሔር ሰው ነውና መልካም ሥራ አደረገልህ አንተ ግን ሔደህ ስለ እርሱ ጸልይለት›› አሉት፡፡

አባ አብርሃም ግን ከአባ ክርስቶስ ይባርከነ ከቀድሞ ቤቱ በደረሰ ጊዜ በዚያም አላገኘውም፤ ውኃ ከሌለበት፤ ፀጥታ ከሰፈነበት ምድረ በዳም ሔደ፡፡ የፀሐይ ወቅት ነበረና በዚያ ሲመላለስ ሳለ ውኃ ጥም ያዘው፡፡ ያን ጊዜም በገዳሙ ውስጥ ባዶ ወጭት አገኘና በፊቱ አስቀምጦ ወደ እግዚአብሔር በጸለየ ጊዜ ወዲያው ብዙ ዝናም ዘነመ፤ በወጭቷም አጠራቀመና እስኪበቃው ድረስ ከእርሷ ጠጣ፡፡ ከዚያም አባታችን ክርስቶስ ይባርከነን አገኘውና ሊያደርግ የሚፈልጋቸውን ምሥጢሩን ሁሉ ነገረው፡፡

የእግዚአብሔር መልአክ መጥቶ አባታችንን ‹‹…በደመና ተጭነህ ወደ ዳሞት አገር ሂድ›› አለው፤ አባታችንም በደመና ተጭኖ ፍራጽ ከተባለ ገዳም ደረሰ፤ በዚያም ምድርን ባረኮ ውሃ አፈለቀ፤ መልአኩም ወደ ቀኝህ ተመልከት አለው፡፡ ወደ ቀኙ ሲያይ ዐደልን ብርሃን ከቧት ተመለከተ፤ ዕፅዋትም ጭፍቅ ያሉ ነበሩ፤ አባ ዘግሩምም ይህች ቦታየ ናት አለ፤ የጻሕናንን ምድር እየባረከም ይሄድ ዘንድ ወደደ፡፡ ብዙ ውሃ አፈለቀ፤ ዐደልም ደረሰ፤ በዚያም ውሃ አፈለቀ፤ አባታችን ዘግሩም ወደ ውስጧ ገባ በዚያም ተቀመጠ፣ የገዳሙ አራዊትም በዚህ ተደሰቱ፡፡ ሙሴ ጽላትን እንደተቀበለ ሁሉ ጥቅምት ሃያ አራት ቀን የእግዚአብሔር መልአክ ከሰማይ አመጥቶ የብርሃን መስቀልና የመድኃኔዓለምን ታቦት ሰጠው፡፡ ዳግመኛም የእግዚአብሔር መልአክ የተዘጋጀ ኅብስትና የተቀዳ ጽዋን፤ ለመሥዋዕት የሚሆነውንም ሁሉ ሰጠው፤ አባታችንም ከካህናት ጋር በዚያች ቤተ ክርስቲያን ቀድሶ ሥጋውንና ደሙን ሰጣቸው፡፡

በቤተ ክርስቲያን አጠገብ አንዲት የዋንዛ ዛፍ ነበረች፤ ሕዝቡም ይሰበሰቡባትና በሥሯ ተቀምጠው ክፉ ሥራ ይሠሩ ነበር፤ አባታችንም ‹‹ለምን እንዲህ የማይገባ ሥራ ትሠራላችሁ? ሲላቸው እነርሱ ግን አልሰሙም፡፡ በዚህም ጊዜ አባታችንም ያቺን ዛፍ ‹‹ከበታችሽ ካሉት ሕዝብ ጋር ተነሥተሽ ሒጂ›› ብሎ በቃሉ አዘዛት፡፡ ያን ጊዜም ያች ዛፍ ከሕዝቡ ጋር ተነሥታ የሁለት ጦር ውርወራ ያህል ሔደች፡፡ ጌታችን በቅዱስ ወንጌሉ ‹‹የሰናፍጭ ቅንጣት ታህል እምነት ቢኖራችሁና ይችን ሾላ ተነስተሽ ወደዚህ ነይ ብትሏት ትመጣለች፤ ይህን ተራራ ከዚህ ሂድ ብትሉት ይሄዳል›› እንዳለ አባታችን አባ ዘግሩምም ይህንን አደረጉ፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

02 Nov, 11:32


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ጥቅምት 22-ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ሀገሩ አንጾኪያ ሲሆን ቁጥሩ ከ72ቱ አርድእት ነው፡፡ ከአቴናና ከእስክንድርያ ሊቃውንት የሕክምና ሙያን አጥንቷል፡፡ ከሕክምና መያው በተጨማሪ የሥዕል ሙያም ነበረው፡፡ በይህ ምክንያት በወንጌሉና በሐዋርያት ሥራ መጽሐፉ ላይ ከሌሎቹ በተለየ ሁኔታ ሥዕላዊ አገላለጽን ሲጠቀም ተስተውሏል፡፡ በእጁ የሣላቸው ቅዱሳት ሥዕላትም በተለያዩ ሀገራት ይገኛሉ፡፡
ቅዱስ ሉቃስ የሣላቸው የእመቤታችን ሥዕላት በእኛም ሀገር እንደ ደብረ ዠመዶ፣ ዋሸራና ተድባበ ማርያም፣ ደብረ ወርቅ ማርያም… ባሉ ታላላቅ ቅዱሳት ገዳማት ውስጥ ይገኛሉ፡፡ ቅዱስ ሉቃስ የከበሩ ቅዱሳን ሐዋርያትን ጴጥሮስንና ጳውሎስን ያገለግላቸው ነበር፡፡ ለታኦፊላም ወንጌልንና የሐዋርያትን ዜና የጻፈው እርሱ ነው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ጴጥሮስና ጳውሎስ በሰማዕትነት ካረፉ በኋላ በሮሜ ወንጌልን በሰፊው ሰብኳል፡፡ መልእክቶችንም ይጽፍላቸው ነበር፡፡ ጣዖት አምላኪዎችም ከክፉዎቹ አይሁድ ጋር ተማክረው በሐሰት ከሰውት በንጉሥ ኔሮን ፊት አቆሙትና ‹‹ብዙ ሰዎችን በሥራዩ ወደ ክርስትና እምነት አስገብቷልና በሞት ይቀጣ›› ብለው ጮኹ፡፡ ቅዱስ ሉቃስም በሰማዕትነት እንደሚሞት አስቀድሞ ዐውቆ ወደ ባሕር ዳርቻ በመሄድ ዓሣ የሚያጠምድ አንድ ሽማግሌ ሰው አገኘና ወንጌልን ከሰበከው በኋላ መጻሕፍቶቹንና ደብዳቤዎቹን ‹‹ወደ እግዚአብሔር መንገድ ያደርሱሃልና እነዚህን መጻሕፍት ጠብቀቸው›› ብሎ በአደራ ሰጠው፡፡ ሽማግሌውም በክብር በዕቃ ቤቱ አስቀምጦአቸው ለቀጣዩ ትውልድ አስተላልፏቸዋል፡፡
ቅዱስ ሉቃስ በንጉሡ ኔሮን ፊት በቀረበ ጊዜ ንጉሡ ‹‹በሥራይህ ሕዝቡን ሁሉ የምታስት እስከመቼ ነው?›› አለው፡፡ ቅዱስ ሉቃስም ‹‹ለሕያው እግዚአብሔር ልጅ ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ ነኝ እንጂ እኔስ ሥራየኛ አይደለሁም›› አለው፡፡ ንጉሡም ‹‹እየጻፈች ሰዎችን የምታስት ይህችን እጅህን እቆርጣታለሁ›› ካለው በኋላ ቀኝ እጁን አስቆረጠው፡፡ ቅዱስ ሉቃስም የጌታችንን ኃይሉን ያሳየው ዘንድ ወደደና የተቆረጠች የቀኝ እጁን በግራ እጁ አንሥቶ ከተቆረጠችበት ቦታ ላይ በማገናኘት እንደ ድሮው ደኅነኛ እጅ አደረጋት፡፡ በዙሪያውም የነበሩ ሰዎች ሁሉ የንጉሡም የሰራዊት አለቃ ከነሚስቱ በአጠቃላይ ቁጥራቸው 477 ሰዎች ሁሉም በጌታችን አመኑ፡፡ ንጉሡም እጅግ ተናዶ ከቅዱስ ሉቃስ ጋር ራሶቻቸውን ይቆርጧቸው ዘንድ አዘዘ፡፡ እነርሱም ሰማዕት ሆነው የክብር አክሊልን ተቀበሉ፡፡ የቅዱስ ሉቃስንም ሥጋ በአሸዋ በተመላ ከረጢት ውስጥ አስገብተው ወደ ባሕር ጣሉት ነገር ግን በእግዚአብሔር ትእዛዝ ወደ አንድ ደሴት ደረሰና ምእመናን አግኘተውት ወስደው በክብር አኖሩት፡፡
የቅዱስ ሉቃስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

31 Oct, 13:21


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ጥቅምት 22-ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ ዕረፍቱ ነው፡፡
+ ውራ ኢየሱስ ገዳምን የመሠረቱትና ጌታችን ከገነት ዕንጨቶች የተሠሩ ታቦታት አምጥቶ የሰጣቸው ታላቁ ጻድቅ አቡነ ዮሐንስ ዘውራ ኢየሱስ ዕረፍታቸው ነው።
+ + +
ቅዱስ ሉቃስ:-ሀገሩ አንጾኪያ ሲሆን ቁጥሩ ከ72ቱ አርድእት ነው፡፡ ከአቴናና ከእስክንድርያ ሊቃውንት የሕክምና ሙያን አጥንቷል፡፡ ከሕክምና መያው በተጨማሪ የሥዕል ሙያም ነበረው፡፡ በይህ ምክንያት በወንጌሉና በሐዋርያት ሥራ መጽሐፉ ላይ ከሌሎቹ በተለየ ሁኔታ ሥዕላዊ አገላለጽን ሲጠቀም ተስተውሏል፡፡ በእጁ የሣላቸው ቅዱሳት ሥዕላትም በተለያዩ ሀገራት ይገኛሉ፡፡
ቅዱስ ሉቃስ የሣላቸው የእመቤታችን ሥዕላት በእኛም ሀገር እንደ ደብረ ዠመዶ፣ ዋሸራና ተድባበ ማርያም፣ ደብረ ወርቅ ማርያም… ባሉ ታላላቅ ቅዱሳት ገዳማት ውስጥ ይገኛሉ፡፡ ቅዱስ ሉቃስ የከበሩ ቅዱሳን ሐዋርያትን ጴጥሮስንና ጳውሎስን ያገለግላቸው ነበር፡፡ ለታኦፊላም ወንጌልንና የሐዋርያትን ዜና የጻፈው እርሱ ነው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ጴጥሮስና ጳውሎስ በሰማዕትነት ካረፉ በኋላ በሮሜ ወንጌልን በሰፊው ሰብኳል፡፡ መልእክቶችንም ይጽፍላቸው ነበር፡፡ ጣዖት አምላኪዎችም ከክፉዎቹ አይሁድ ጋር ተማክረው በሐሰት ከሰውት በንጉሥ ኔሮን ፊት አቆሙትና ‹‹ብዙ ሰዎችን በሥራዩ ወደ ክርስትና እምነት አስገብቷልና በሞት ይቀጣ›› ብለው ጮኹ፡፡ ቅዱስ ሉቃስም በሰማዕትነት እንደሚሞት አስቀድሞ ዐውቆ ወደ ባሕር ዳርቻ በመሄድ ዓሣ የሚያጠምድ አንድ ሽማግሌ ሰው አገኘና ወንጌልን ከሰበከው በኋላ መጻሕፍቶቹንና ደብዳቤዎቹን ‹‹ወደ እግዚአብሔር መንገድ ያደርሱሃልና እነዚህን መጻሕፍት ጠብቀቸው›› ብሎ በአደራ ሰጠው፡፡ ሽማግሌውም በክብር በዕቃ ቤቱ አስቀምጦአቸው ለቀጣዩ ትውልድ አስተላልፏቸዋል፡፡
ቅዱስ ሉቃስ በንጉሡ ኔሮን ፊት በቀረበ ጊዜ ንጉሡ ‹‹በሥራይህ ሕዝቡን ሁሉ የምታስት እስከመቼ ነው?›› አለው፡፡ ቅዱስ ሉቃስም ‹‹ለሕያው እግዚአብሔር ልጅ ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ ነኝ እንጂ እኔስ ሥራየኛ አይደለሁም›› አለው፡፡ ንጉሡም ‹‹እየጻፈች ሰዎችን የምታስት ይህችን እጅህን እቆርጣታለሁ›› ካለው በኋላ ቀኝ እጁን አስቆረጠው፡፡ ቅዱስ ሉቃስም የጌታችንን ኃይሉን ያሳየው ዘንድ ወደደና የተቆረጠች የቀኝ እጁን በግራ እጁ አንሥቶ ከተቆረጠችበት ቦታ ላይ በማገናኘት እንደ ድሮው ደኅነኛ እጅ አደረጋት፡፡ በዙሪያውም የነበሩ ሰዎች ሁሉ የንጉሡም የሰራዊት አለቃ ከነሚስቱ በአጠቃላይ ቁጥራቸው 477 ሰዎች ሁሉም በጌታችን አመኑ፡፡ ንጉሡም እጅግ ተናዶ ከቅዱስ ሉቃስ ጋር ራሶቻቸውን ይቆርጧቸው ዘንድ አዘዘ፡፡ እነርሱም ሰማዕት ሆነው የክብር አክሊልን ተቀበሉ፡፡ የቅዱስ ሉቃስንም ሥጋ በአሸዋ በተመላ ከረጢት ውስጥ አስገብተው ወደ ባሕር ጣሉት ነገር ግን በእግዚአብሔር ትእዛዝ ወደ አንድ ደሴት ደረሰና ምእመናን አግኘተውት ወስደው በክብር አኖሩት፡፡
የቅዱስ ሉቃስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!
+ + + + +
አቡነ ዮሐንስ ዘውራ ኢየሱስ:-የአባታቸው ስም የማነ ብርሃን የእናታቸው ስም ሐመረ ወርቅ ይባላል።በመጀመሪያ እናታቸው ሐመረ ወርቅን ወላጆቿ ያለ ፈቃዷ ሊድሯት ሲሉ እርሷ ግን “ደብረ ሊባኖስ ሔጄ ከአባታችን ተክለ ሃይማኖትና ከሌሎቹም ቅዱሳን መቃብር ሳልባረክ አላገባም በማለት ነሐሴ 16 ቀን ወደ ደብረ ሊባኖስ ሔደች። በዚያም ሳለች አቡነ ተክለ ሃይማኖት በራእይ ተገለጡላትና የብርሃን ምሰሶ አሳይተዋት ይኸ ለአንቺና ለባልሽ ለየማነ ብርሃን ነው› አሏት። ይኽንንም ራእይ ለሰባት ቀን የገዳሙ አባቶችና አበ ምኔቱ አባ ዳንኤል አዩት። ከዚኸም በኋላ ባለጸጋውና ሃይማኖትን ከምግባር አስተባብሮ የያዘው የማነ ብርሃን ከዘርዐ ያዕቆብ ሀገር በእመቤታችን ትእዛዝ ወደ ደብረ ሊባኖስ ሲመጣ አበ ምኔቱ አባ ዳንኤል የማነ ብርሃንን እና ሐመረ ወርቅን ኹለቱ ተጋብተው የተባረከ ልጅ እንደሚወልዱ በራእይ ያዩትን ነገሯቸው፤ ከዚኽም በኋላ በአባታችን በተክለ ሃይማኖት የዕረፍታቸው በዓል ዕለት ነሐሴ 24 ቀን ተጋቡ። እነርሱም በሃይማኖት በምግባር እግዚአብሔርን ደስ አሰኝተው ሲኖሩ እግዚአብሔር ልጅ ሰጣቸውና አቡነ ዮሓንስ ነሐሴ 24 ቀን ተፀንሰው ግንቦት 24 ቀን ተወለዱ።

የፈለገ ብርሃን ናዳ ማርያም እና የክብረ ደናግል ናዳ ቅዱስ ላሊበላ አንድነት ገዳም አበምኔት፣ የቅኔ፣ የትርጓሜ መጻሕፍት፤ የፍትሐ ነገሥት እና የባሕረ ሐሳብ መምህር የሆኑት ሊቀ ብርሃናት ቆሞስ ይባቤ በላይ ከግእዝ ወደ አማርኛ የተረገሙት የአቡነ ዮሐንስ ዘውራ ኢየሱስ ገድል እንደሚናገረው ጻድቁ በሰባት ዓመታቸው ይኸችን ዓለም ንቀው የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ኹለተኛ ልጅ ወደሆነው አባ ጸጋ ኢየሱስ ዘንድ ሔደው 5 ዓመት እየተማሩ ተቀምጠው በ12 ዓመታቸው መነኰሱ። ከዚኽም በኋላ አቡነ ዮሐንስ ወደ ዋልድባ በመሔድ አባቶችን ማገልገል ጀመሩ። መነኰሳቱም ሌሊትና ቀን እንዲገለግሏቸው በሥጋ ቍስል ሁለንተናው
ለተላና ለሸተተ ግብሩ ለከፋ ለአንዲ መነኵሴ ሰጧቸው። በሽተኛውም መነኵሴ አቡነ ዮሐንስን ይረግማቸው አንዳንድ ጊዜም ይደበድባቸው ነበር፣ ነገር ግን አቡነ ዮሐንስ በዚህ ከማዘን ይልቅ ደስ እያላቸው ያንን ሊቀርቡት የሚያሰቅቅ በሽተኛ በማገልገል ለዓመታት አስታመመ።

እንዲሁም የዋልድባ መነኰሳትን መኮሪታ በማብሰል፣ ቋርፍ በመጫር እና ዕንጨት በመልቀም፣ ውኃ በመቅዳት ገዳማውያንን ያገለግሉ ነበር። ከዕለታትም በአንደኛው ቀን በዋልድባ የሚኖር በክፉ በሽታ ተይዞ የሞተ አንድ መነኩሴ ሞቶ ሣለ ሽታውን ፈርተው መነኰሳቱ ለመገነዝ ፈሩ፡ ነገር ግን አበ ምኔቱ ለመገነዝ ወደ ውስጥ ሲገባ አቡነ ዮሐንስ አብረው ገቡ። አቡነ ዮሐንስም ወደሞተው መነኵሲ ቀርበው አቀፉት፣ በዚኸም ጊዜ ጥላቸው ቢያርፍበት ያ የሞተው መነኵሴ አፈፍ ብሎ ከሞት ተነሣና ከሞትሁ 3ኛ ቀኔ ነው አይቶ የጎበኘኝ የለም፣ ዛሬ ግን የእግዚአብሔር ሰው የገዳማት ኮከብ የቅድስት ውራ ገዳም መነኰሳት አባት፣ የማይጠልቅ ፀሓይ፣ የማይጠፋ ፋና ወደ ሰባቱ ሰማያት ወጥቶ ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ ጋር የሥላሴን ዙፋን የሚያጥን አባታችን ዮሐንስ ባቀፈኝ ጊዜ ነፍሴ ከሥጋዬ ጋር ፈጽማ ተዋሐደች፤ አምላክን የወለደች እመቤታችን ማርያምም ንዑድ ክቡር ቅዱስ በሆነ በዮሐንስ ጸሎት ከሞት አስነሥቶ ሕያው አደረገህ አለችኝ› ብሎ ተናገረ። ዳግመኛም እመቤታችን አባ ዮሐንስን ወደ ኢየሩሳሌም ሔደው እርሳቸውን ሲጠብቁ የኖሩትን ሦስት ታቦታት ያመጡ ዘንድ አቡነ ዮሐንስን እንዳዘዘቻቸው ተናገረ። በዚኽም ጊዜ የዋልድባ መነኰሳትና የገዳሙ አለቃ ለፍላጎታችን አገልጋይና ታዛዥ አደረግንህ ይቅር በለን ብለው ከእግራቸው ሥር ወድቀው ለመኗቸው። አባታችንም ‹‹አባቶቼ ሆይ! እናንተ ይቅር በሉኝ፡ ይህ የሆነው ስለ እኔ አይደለም፡ ስለ ክብራችሁ ነው እንጂ አሏቸው። መነኰሳቱም በትሕትናቸው ተገርመው እያለቀሱ ወደ ኢየሩሳሌም ሸኟቸው። በዚኸም ጊዜ አባታችን ዕድያቸው ገና 19 ነበር።

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

31 Oct, 13:21


አባታችን ዮሐንስም ጎልጎታ ደርሰው ከቅዱሳት ቦታዎች ተባርከው ወደ አስቄጥስ ገዳም ሔዱ። በዚያም 500 ዓመት የኖረ ኹለተኛ እንጦንስ የተባለ አንድ ባሕታዊ ኣገኙ። እመቤታችንም አባ እንጦንስን ታቦተ ኢየሱስን፣ ታቦተ ኪዳነ ምሕረትን እና ታቦተ ጽዮንን እያስጠበቀችው ይኖር ነበር። አባ እንጦንስም ኣቡነ ዮሐንስን ባገኛቸው ጊዜ በልቡ ተደስቶ በመንፈሱ ረክቶ በዐይኖቼ አንተን ያሳየኝ በጆሮዎቹም ቃልህን ያሰማኝ የአባቶቻችን አምላክ እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን፤ እመቤታችን ማርያም ከልጇ ከወዳጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር በእጇ የሰጠችኝን ያስጠበቀችኝን እነዚኽን ታቦታት ተቀበለኝ›› ብለው ሦስቱን ጽላት ‹‹ወደ ሀገርህ ይዘህ ሒድ›› ብለው ሰጧቸው። አባታችን ዮሐንስም ‹‹…እኔ እርሱ አይደለሁም እንዴት አወከኝ?› ሲሏቸው አባ እንጦንስም ፈገግ ብለው ከሞተ ሦስት መዓልትና ሦስት ሌሊት የሆነውን ሰው በጸሎትህ ከሞት ካስነሣኸው በኋላ ከሀገርሀ ከኢትዮጵያ ከዋልድባ ገዳም ከተነሣኽ ዘጠኝ ወር ነው፤ ይኸንንም የእግዚአብሔር መላእክት ነገሩኝ መምጣቱን ተስፋ የምታደርገው ኢትዮጵያዊው ጻድቅ ከሀገሩ ዛሬ ተነሣ አሉኝ አሏቸው። አባታችን ዮሐንስም እመቤታችን ማርያምን እንዴት አገኘሃት? አሏቸው። አባ እንጦንስም ከልጇ ከወዳጇ ጋር በብርሃን መርከብ ላይ ተቀምጣ መላእክት፣ ነቢያት፣ ሐዋርያት ጻድቃን፣ ሰማዕታት ሲከቧትና በክብር በምስጋና ሲሰግዱላት ግንቦት 21 ቀን በደብረ ምጥማቅ አገኘኋት አሏቸው። እመቤታችንም ልጇን ኢየሱስ ክርስቶስን ፈቃድህን ለሚያደርጉ ለኢትዮጵያ ሕዝብና ለዓለሙ ሁሉ የመዳን ተስፋ ስጠኝ አለችው። ጌታችንም ያንጊዜ መላእክትን ከገነት ዕንጨትና ዕብነ በረድ፡ ከጎልጎታ መቃብሩና ከጌቴሴማኒ አፈር እንዲያመጡ አዘዛቸው። መላእክትም የታዘዙትን አምጥተው በሰጡት ጊዜ ጌታችን ከገነት የመጡትን ዕንጨትና ዕብነ በረድ ሦስቱን ታቦታት አድረጋቸው በማለት አባ እንጦንስ ለአባ ዮሐንስ ነገሯቸው።

አቡነ ዮሐንስም ሦስቱን ጽላት ይዘው አንዲት እንደፀሓይ የምታበራ ድንጋይ እየመራቻቸው ሰኔ 12 ቀን ጎጃም ደረሱ። ድንጋዩዋንም መንገድ እንድትመራቸው የሰጣቸው ጌታችን ነው። ከዚያም ውሮ ተብሎ የሚጠራ አንድ ባላባት ቤት ገብተው አድረው በሚገባ ተስተናግደው በቀጣዩ ቀን ድንጋዩዋ እየመራቻቸው ቅዱሳን ከነበሩበት ጫካ ወስዳ አገናኘቻቸው። ቅዱሳኑም ለአቡነ ዮሐንስ የጠበቅንልህን ይኸችን ቦታ ተረከበን የዘለዓለም ማረፊያህ ናትና› ብለው እነርሱ ወደ ኢየሩሳሌም ሔዱ። አባታችንም ታቦተ ኢየሱስን በዚኽች ገዳም ተክለው ቦታዋን መጀመሪያ በተቀበላቸው ሰው በውሮ ስም "ውራ ኢየሱስ ብለው ሰየሟት።

ከዘጠኝ ዓመትም በኋላ መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል እየመራቸው ወደ ጣና ወስዶ ዘጌ አደረሳቸውና ታላቋን ዑራ ኪዳነ ምሕረትን ተከለ።

ከዚያ ቀጥለው ታቦተ ጽዮንን አዴት አካባቢ ተከሉ። እነዚህን ሦስት ገዳማት አቅንተው ከኖሩ በኋላ መልካም የሆነውን ተጋድሏቸውን ፈጽመው ጥቅምት 22 ቀን ዐርብ በ9 ሰዓት ዐረፉ። ከማረፋቸውም በፊት ጌታችን እመቤታችንን፣ መላእክትን፣ ቅዱሳንን ሰማዕታትን አስከትሎ መጥቶ “…ጸሎት አድርጎ መልክህን የደገመ እባብ አይነድፈውም፤ መብረቅ አይገድለውም የሚል ድንቅ የምሕረት ቃልኪዳን ገባላቸው። ዳግመኛም ስምህን የጠራውን መታሰቢያህን ያደረገውን፤ በበዓልህ ቀን ማኅሌት የቆመውን የገድልህን መጽሐፍ የጻፈውን ያጻፈውን ያነበበውን የሰማውን፣ እጅ መንሻ ለቤተ ክርስቲያን የሰጠውን እምርልሃለሁ፤ ልጆቹንም እስከ 15 ትውልድ እባርክልሃለሁ፤ በገዳምህ በውራ መብረቅ ነጎድጓድ፣ እባብ ሰውን አይገድልም የማይጸድቅ ሰው ወደ ገዳምህ አይመጣም" አላቸው።

አባታችንም ካረፉ በኋላ መነኰሳት ልጆቻቸው ሥጋቸውን ተሸክመው ከደብረ ጽዮን ኮቲ ተነሥተው ወደ ውራ ኢየሱስ ለመውሰድ ሲጓዙ በበረሓ ሣሉ መሸባቸውና ፀሓይ ገባች፣ ወዲያውም ሰባት አንበሶች መጥተው እንዳይፈሯቸው መነኰሳቱን በሰው አንደበት ካናገሯቸው በኋላ የአቡነ ዮሓንስን ዐፅም ተሸክመው ሰባት ምዕራፍ ያህል ወሰዱት። ወቅቱ ቢመሽባቸውም በእግዚአብሔር ፈቃድ ፀሓይ ግን በተኣምራት ወጣችላቸውና ውራ ኢየሱስ ገዳም በሰላም ደረሱ። ያንጊዜም ፀሓይ ገባች፤ አንበሶቹም እጅ ነሥተው ወደ ቦታቸው ተመለሱ።

አቡነ ዮሐንስ መላ ዘመናቸውን የማያዩ ዐይነ ሥውራንን እንዲያዩ፣ የማይሰሙ እንዲሰሙ፣ የማይራመዱ እንዲራመዱ በማድረግ፤ ሕሙማንን በመፈወስ፣ ሙታንን በማስነሣት በርካታ ተኣምራትን በማደረግ ወንጌልን በመስበክ ያገለገሉ ሲሆን ከዕረፍታቸውም በኋላ በርካታ ድንቅ ድንቅ ተኣምራትን አድርገዋል። ከተኣምራታቸውም አንዱ ይኸ ነው፡- ንዑድ ክቡር ልዩ በሚሆን በአባታችን ዮሐንስ የዕረፍታቸው ቀን ጥቅምት 22 ቀን አንድ ዐረማዊ እስላም ሰው ለተሳልቆና ለመዘባበት ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ቈረበ። በአባታችን በዓል ዕለትም ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀብሎ ወጥቶ እየተቻኮለ ሔዶ ከእስላሞች መስጊድ ገብቶ በአባታችን በዮሐንስ በዓል ምክንያት የቆረበውን ቍርባን ተቀብሎ በወገኖቹ በከሃዲያኑ እስላሞች ፊት ተፋው። ወዲያውም የዚያ እስላም ሰው መላ ሰውነቱ አበጠ በንፋስ ገመድነትም ታንቆ ሰዎች እስኪያዩት ድረስ በሰማይና በምድር መካከል ተሰቀለ።

በተሰቀለበትም ቦታ ወፎችና አሞራዎች ይበሉት ጀመር፤ ሥጋውንም በሉት። በዚኽም ጊዜ ያ እስላም ድምፁን ከፍ አድርጎ ‹‹እኔ ንዑድ ክቡር ልዩ በሆነ በአባታችን በዮሐንስ አምላክ አምኛለሁ ብሎ መሰከረ። እግዚኣብሔርም የገዳማት ኮከብ በሆነው በብፁዕ ዮሓንስ ልመናና ጸሎት ፈጽሞ ይቅር አለው። ከዚኽም በኋላ ለብቻው ቀኖና ገባ የቀኖና ሥርዓቱንም ጨርሶ ንስሓ ገብቶ ከባለቤቱ ከልጆቹ ከቤተሰቦቹና ከዘመዶቹ ከጎረቤቱቹ ሁሉ ጋር የክርስትና ጥምቀትን ተጠመቀ ስሙንም ገብረ ዮሐንስ አሉት ትርጓሜውም የዮሐንስ ባለሟል ማለት ነው።

የአቡነ ዮሐንስ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን።
(ምንጭ በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን መጽሐፍ ገጽ 472-477)

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

30 Oct, 19:15


ለውጣዋለች ።እናም

ብዙ ልጆችን (መነኮሳያት) አፍርታ እነርሱም እንደእርሷ የበቁ ለመሆን
ችለዋል፡፡መሞት አይቀርምና ገዳሙን በደንብ ካስተዳደረች በኋላ በክብር አርፋች፡፡ጸሎትና በረከቷ ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በታላቋ ቅድስት ጻድቅ ታማቭ ኢሪኒ ጸሎት ይማረን።
✞✞✞
ነቢል ጂንዲ የተባለ በግብጽ ካይሮ የሚኖር የKLM COMPANY ፊልድ መካኒክ ነበር ።ይህ ሰው የጻድቋ እማሆይ የጣማፍ ኡምና ኤሬን (ሔራኒ) የዘወትር ጠያቂና መንፈሳዊ ልጅ ነበር።ይህ ሰው ቅድስት ሔራኒ አጊባ (AGIIBA) ወደ ተባለ ቦታ ስትሔድ እሷን ለመሸኘትና በረከቷን ለመቀበል የመጣ ሰው ነበር።ተጓዦቹ ሶስት መነኮሳት ሔራኒ ና ይህ ሰው ነበሩ።የሚጓዙትም በሁለት ጉዞ መጀመሪያ ወደ ማርሳ መጥሩህ ወደሚባል ትንሽዬ ኤርፖርት ከዛ ወደ አጊባ ነበር ።እናም አቶ ነቢል ያጋጠመውን ነገር እንዲህ ይመሰክራል።
"በጊዜው ኤር ሲናይ የተባለ ከግብጽ አየር መንገድ ጋር በትብብር የሚሰራ ድርጅት ነበር።ይህ ድርጅት የሀገር ውስጥ በራራ ብቻ የሚሰራ ሲሆን 3 foker-27 የተባሉ ፕሌኖች ነበሩት።በእለቱ እኛ ከነዚህ በአንዱ የተሳፈርን ሲሆን
ጉዞውም ከካይሮ-እስክንድርያ-ማርሳ መጥሩህ ነበር። ፕሌኖቹ ደካማ እና ትናንሽ ስለሆኑ ወደላይ ከፍ ብለው ብዙም አይሄዱም ነበር።ፕሌኑ ከተሳፈርን በሁዋላ ለመነሳት በሚያኮበኩብበት ጊዜ የሆነ ችግር እንዳለው ጠርጥሬ ነበር።ወደ ካፒቴኑ (አብራሪው) ሒጄ ስለጉዳዩ ብጠይቀውም "ተሳፋሪዎች ይረበሻሉ"በሚል ምክንያት ምንም መልስ ሊሰጠኝ አልፈለገም።ትንሽ እንደሔደ ግብጽ ዴልታ አከባቢ ሲደርስ አውሮፖላኑ አቅጣጫውን ቀይሮ ወደ ካይሮ እየተመለሰ እንደሆነ አስተዋልኩ ነገሩንም ስረዳው አደገኛ ሁኔታ ውስጥ ነን አውሮፖላኑ እንደተነሳ ጎማዎቹ በሙሉ መሰብሰብ ነበረባቸው በርግጥ የኋላ ጎማዎች በትክክል
ቢገቡም የፊቶቹ ግን የሆነ ስታክ አርጎ የያዛቸው ነገር ነበር። ዞሮ ዞሮ ወደተነሳበት ኤርፖርት ቢመለስም ማረፍ አይችልም ምክንያቱም ጎማዎቹ በሆነ ነገር ስታክ ስላደረጉ መዘርጋት አይችሉም።ባጭሩ ጎማዎቹ ለመብረርም ለማረፍም
በማይቻልበት ሁኔታ ተይዘዋል ማለት ነው።ፕሌኑ ወደ ካይሮ ተመልሶ ዝም ብሎ ሰማዩን ይዞር ነበር ምክንያቱ ደግሞ ነዳጁን ለመጨረስ እና በሚያርፍ ጊዜ የሚፈጠረውን እሳት አደጋ ለመቀነስ ነው። እኔም እንደባለሙያ እንደማንተርፍ
ባውቅም ጻድቋ እማሆይ ጣማፍ ከኛ ጋር ስላለች ምንም አንሆንም ብዬ እራሴን አሳመንኩ። ሁኔታውን የተረዳው ተሳፋሪም በመንጫጫት እና ድንጋጤ እየጮኸ ያያት ነበር በርግጥ ሁሉም ክርስቲያን ባይሆን ተአምር ሰሪነትዋን በዝና
የማያውቅ ግን አልነበረም።እሷም ከተነሱ ይወድቃሉ በማለት በእጇ እንዲቀመጡ መንገር ጀመረች።እየጮኸችም ቁጭ በሉ አይዞአችሁ ምንም አትሆኑም እያለች ልታረጋጋቸው ትሞክር ነበር።በአውሮፖላኑም የድርሱልኝ መልእክት 7 የእሳት አደጋና 8 አምቡላንስ ምድር ላይ ሆነው የሚሆነው ይጠባበቁ ነበር። ጣማፍም ወደ እኔ ዞር አለችና "ስለተፈጠረው ነገር ያረጋገጥከው ነገር አለ?? "አለች እኔም
በድንጋጤ አዎ እናታችን ያረጋገጥኩት ነገር አለ እሱም " ድንግል ማርያም በዚህ በኩል ያለውን ክንፍ ትደግፍልናለች፣ አቡ ሰይፊን (መርቆሬዎስ) በፈረሱ የፊቱን በኩል ይደግፍልናል፣ ጻድቁ አቡነ ቄርሎስ ፓትርያርኩ በዛኛው በኩል ይይዙልናል " እያልኩ ስርበተበት እሷ ኮስተር ብላ ቅዱስ ሩፋኤልስ ? ስትለኝ ክንፉ ከአውሮፖላኑ በታች ዘርግቶ እንዳይወድቅ ያደርገዋል ከዛ አውሮፖላኑ በሰላም ያርፍና ሁላችንም እንወርዳለን ብዬ ምኞቴን ስጨርስ።አዎ እንደዚህ ነው የሚሆነው አለችኝ።የተነጋገርነው የእምነት ንግግር እንጅ እየተደረገ ነበር ለማለት አልነበረም። ጣማፍ ግን በመስኮት እያየች የጠራናቸው ቅዱሳን መጥተው የቱን የቱን ቦታ እንደደገፉ ስትነግረን መደነቅ ጀመርን ።በሚገርም ሁኔታ አውሮፖላኑ በትክክል መጓዝ ጀመረና ወደ መሬት ተጠጋ ይህ እንዴት እንደሆነ በጣም ገርሞኝ ነበር ወደ መሬት እየተጠጋ መጥቶ ማኮብከቢያ አስፋልትን ሊይዝ ሲል ነዳጅ አለቀ ይህም ካፒቴኑ አየር ላይ እያዞረ ስለጨረሰው ነበር እናም ፕሌኑ ሚዛኑን ስለሳተ በአፍንጫው ወደ መሬት ተቀረቀረ ይህ ሁሉ ሲሆን ግን ተሳፋሪው ሁሉ በትክክል እንደሚሔድ እንጅ ምን እንደተፈጠረ መረዳት እስከማይችል ድረስ ምንም አይሰማውም ነበር።አውሮፕላኑ መሬት ላይ ቢወድቅም ማንም ተሳፋሪ ምንም የአደጋ ስሜት አልተሰማውም ደግሞ
ከካፒቴኒ ጀምሮ አንድም ሰው ምንም አደጋ አልደረሰበትም ነበር።ካፒቴኑም በፍጥነት ወደ ወስጥ መጥቶ የጣማፍን እጅ እየሳመ እናቴ ያንቺ ጸሎት ነው ያዳነን ይላት ነበር።እሷም ከሰዎች ሁሉ ጋር በሰላም ከፕሌኑ ወጣች አውሮፕላኑም ከውጭ ስናየው አፍንጫው ሙሉ ወደ መሬት ውስጥ ገብቶ ነበር።በተፈጠረውም ሀገር ሁሉ ተደንቆ እንዲያውም በታዋቂው አል አሕራም ጋዜጣ ወጥቶ ነበር "ብሏል።
(ምንጭ የእግዚአብሔር ዙፋን The Throne of God)
የቅድስት ኢሪን ረድኤት በረከት ይደርብን።

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

27 Oct, 16:18


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ጥቅምት 18-ቅዱስ ሮማኖስ በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡
የታላቁ ሊቅ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ደቀ መዝሙር የሆነውና የመጥምቁ ዮሐንስንና የነቢዩ ኤልሳዕን ዐፅም ያፈለሰው አቡነ ቴዎፍሎስ ዐረፈ፡፡
ሰማዕቱ ቅዱስ ሮማኖስ፡- ይኽም ቅዱስ መነኮስ ከሃዲ የሆነው የሀገራቸው ገዥ ክርስቲያኖችን ማሠቃየትና ማሳደድ በጀመረ ጊዜ ቅዱስ ሮማኖስ ቀሳውስትንና ዲያቆናትን ሕዝቡንም ሁሉ ሰብስቦ ክርስቶስን በማመን በሃይማኖት እስከመጨረሻው ይጸኑ ዘንድ መከራቸው፡፡ ከቅዱሳት መጻሕፍትም እየጠቀሰ የቀደሙ ሰማዕታትን ሕይወት አብነት እያደረገ ብዙ አስተማራቸው፡፡
ከሃዲው መኮንን አስቅልጵያኖስ ይህንን በሰማ ጊዜ ቅዱስ ሮማኖስን አስመጣውና ‹‹በወገን የከበርክ ሮማኖስ አንተ ነህን?›› አለው፡፡ ቅዱሱም ‹‹የወገን ክብር ምን ይጠቅመኛል? ለእኔስ ክብሬ ክርስቶስ ነው›› አለው፡፡ በዚህም ጊዜ መኮንኑ ተናዶ ሰቅለው ጉንጮቹን እንዲሰነጣጥቁትና እንዲያሠቃዩት አዘዘ፡፡ እንደ ትእዛዙም ባደረጉበት ጊዜ ቅዱስ ሮማኖስ ምንም አልተናገረም ነበርና መኮንኑ ትእግስቱን አደነቀ፡፡
ከዚህም በኋላ ቅዱስ ሮማኖስ መኮንኑን ‹‹ስንፍናህን እገልጥ ዘንድ ፈጣሪዬ አፌን ከፈተ፣ ዕውነት ነገርን ብታውቅ ለእግዚአብሔር ወይም ለአንተ አማልክት እንሰግድ ዘንድ ይገባ እንደሆነ እንዲነግረን ሕፃን ልጅ እንዲያመጡ እዘዝ›› አለው፡፡ መኮንኑም ታናሽ ሕፃን ልጅ አስመጣና ‹‹ስግደት ለማን እንዲገባ ዕውነቱን ንገረን›› አለው፡፡ ሕፃኑም በኮልታፋ አንደበቱ ‹‹ልብ የሌለህ ደንቆሮ መኮንን ሆይ! በአንዲት ቃል ዓለሙን ሁሉ ለፈጠረ ለሕያው እግዚአብሔር ስግደትና አምልኮ እንዲገባ አታውቅምን?›› አለው፡፡ በዚህም ጊዜ መኮንኑ እጅግ አፈረና ሕፃኑን ይሠቅሉት ዘንድ አዘዘ፡፡ ሕፃኑም ተሰቅሎ ሳለ እናቱን ‹‹ተጠምቻለሁና ውኃ አጠጪኝ›› አላት፡፡ እናቱም ‹‹ልጄ ሆይ! ከዚህ ውኃ የለም ነገር ግን ወደ ሕይወት ውኃ ሂድ›› አለችው፡፡ ወዲያውም የሕፃኑን ራሱን ቆረጡትና የሰማዕትነት አክሊልን ተቀዳጀ፡፡
ከዚህም በኋላ መኮንኑ የቅዱስ ሮማኖስን ምላሱን ከግንዱ አስቆረጠው፡፡ ነገር ግን መኮንኑን ይዘልፍ ዘንድ ለቅዱስ ሮማኖስ ረቂቅ ምላስ ተሰጠውና መኮንኑን ስለ ከንቱ እምነቱ በሕዝቡ ሁሉ ፊት ዘለፈው፡፡ በዚህም ጊዜ ምላሱ እንዳልተቆረጠች ተጠራጥሮ ከወታደሮቹ አንዱን ጠርቶ ‹‹ምላሱን ከግንዱ ያልቆረጥከው ለምንድነው?›› ሲለው ወታደሩም የቅዱስ ሮማኖስን የተቆረጠች ምላሱን አምጥቶ ለሞኮንኑ ሰጠው፡፡ ከዚህም በኋላ መኮንኑ በታላቅ ንዴት ሆኖ ቅዱስ ሮማኖስ በእሥር ቤት ውስጥ ሳለ አንቀው እንዲገድሉት አዘዘ፡፡ ቅዱሱም ሰማዕትነቱን በዚሁ ፈጸመ፡፡
የሰማዕቱ ቅዱስ ሮማኖስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!
አቡነ ቴዎፍሎስ፡- ይኸውም ቅዱስ ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት 23ኛ የሆነ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ሲሆን በማርቆስ ወንበር 28 ዓመት የኖረ ብዙ ተአምራትን ያደረገ ጻድቅ ነው፡፡ እርሱም ንጉሥ ቴዎዶስዮስ ከተሾመ ከ6 ዓመት በኋላ የተሾመ ሲሆን በዘመኑም ከዋክብት የሆኑ ታላላቆቹ ሊቃውንት ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅና ቅዱስ ኤጲፋንዮስ ነበሩ፡፡ ዳግመኛም በዘመኑ ከሞቱ ከ372 ዓመት በኋላ ሰባቱ ደቂቅ ከሞት ተነሥተዋል፡፡ አቡነ ቴዎፍሎስ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ደቀ መዝሙር ስለሆነ ቅዱሳት መጻሕፍትን ሁሉ አስተምሮታል፡፡ አቡነ ቴዎፍሎስም በመንፈሳዊ ተጋድሎ ያሸበረቀ፣ ምግባር ሃይማኖቱ የቀና፣ ትሩፋቱ የሰመረ ሆኖ ቢያገኙት ቅዱሳን አባቶች በእግዚአብሔር ፈቃድ በማርቆስ ወንበር ላይ ሊቀ ጳጳሳት አድርገው ሾሙት፡፡ በዕውቀቱና በአስተዋይቱም እጅግ ተመሰገነ ነውና ብዙ ጠቃሚ ድርሳናትንና ተግጻሣትን ደርሷል፡፡ ቅዱስን በመጀመሪያ ያሳደገው ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ቄርሎስ ነው፡፡ እርሱም የእኅቱ ልጅ ነውና የቤተ ክርስያንን ትምህርት እያስተማረ ካሳደገው በኋላ ወደ ቅዱስ ሰራብዮን እንዲሄድ ነገረው፡፡ ቅዱስ ሰራብዮንም መንፈሳዊ ተግባርን ሁሉ አስተማረው፡፡
በቅዱስ አትናቴዎስም ዘመን እንዲህ ሆነ፡- ቅዱስ አትናቴዎስ ‹‹በጎ ዘመን ባገኝ ይህን ኮረብታ ባስጠረግሁትና ለከበሩ ለመጥምቁ ዮሐንስና ለነቢዩ ኤልሳዕ ቤተ ክርስቲያን ባሠራሁ›› እያለ ሲመኝ አቡነ ቴዎፍሎስ ይሰማው ነበር፡፡ አቡነ ቴዎፍሎስም በሹመቱ ወቅት ይህንን የቅዱስ አትናቴዎስን ምኞት አስታውሶ የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሆን ዘንድ ያዝንና ይጸልይ ጀመር፡፡ በዚያም ወራት ባሏ ብዙ ገንዘብ ትቶላት የሞተ አንዲት ሴት ከሮሜ አገር ሁለት ልጆቿን ይዛ መጣች፡፡ ሊቀ ጳጳሳት አቡነ ቴዎፍሎስን ሲያዝን ቢታየው ‹‹ክቡር አባት ሆይ! ምን ያሳዝንዎታል?›› አለችው፡፡ እርሱም ‹‹ብዙ ወርቅ በዚህ ኮረብታ ውስጥ እያለ ድኆች ይራባሉ›› አላት፡፡ እርሷም ‹‹እርስዎ ስለእኔ ይጸልዩ እኔ አስጠርገዋለሁ›› አለችው፡፡
ሴትዮዋም ያን ኮረብታ አስጠረገችውና በውስጡ በድንጋይ ሰሌዳ የተከደኑ ወርቅ ተሞላባቸው ሦስት ሣጥኖች ተገኙ፡፡ በላያቸውም ሦስቱም ላይ ‹‹ቴዳ ቴዳ ቴዳ›› የሚል ተጽፎባቸዋል፡፡ እነርሱም በንጉሥ እስክንድር ዘመን የተቀበሩ እንደሆኑ የዘመን ቁጥር ማረጋገጫ ተገኘ፡፡ ይህም ከ700 መዘናት በፊት ነው፡፡ አቡነ ቴዎፍሎስም የጽሕፈቱን ምሥጢር በመንፈስ ቅዱስ ዐወቀ፡፡ ቴዳ ማለት የጌታ ስም ነው ይህም ማለት ለድኆች ይገባል ማለት ነው አለ፡፡ ሁለተኛውም ላይ ቴዳ የተባለው የንጉሡ ቴዎዶስዮስ ነው፡፡ ሦስተኛውም ቴዳ ቴዎፍሎስ ማለት ነው፡፡ ከዚህም በኋላ አባታችን ‹‹የእኔ በሆነው ገንዘብ አብያተ ክርስቲያናትን እሠራለሁ›› አለ፡፡
የወርቅ ሣጥኑንም ለንጉሥ ቴዎዶስዮስ ላከለት፡፡ እንዴት እንደተገኘ ካስረዳው በኋላ ቦታውንም መጥቶ እንዲጎበኘው ነገረው፡፡ ንጉሡም መጥቶ ሁሉን ባየ ጊዜ ወርቁን እኩሌታ ለአቡነ ቴዎፍሎስ መለሰለት፡፡ አቡነ ቴዎፍሎስም በዚያ ወርቅ ብዙ አብያተ ክርስያናትን ሠራ፡፡ ከሁሉ አስቀድሞ ግን በመጥምቁ ዮሐንስና በነቢዩ ኤልሳዕ ስም ሠራ፡፡ ሥጋቸውንም በእግዚአብሔር ፈቃድ በተአምር ከእስራኤል አገር አፍልሶ አምጥቶ በውስጧ በክብር አኖረ፡፡ ንጉሡም አቡነ ቴዎፍሎስ አብያተ ክርስያናትን ለማሳነጽ ያለውን ፍቅር አይቶ በግብፅ ያሉ የጣዖታት ቤቶችን ሁሉ አሳልፎ ሰጠው፡፡ አቡነ ቴዎፍሎስም አፈራርሶ በምትካቸው አብያተ ክርስቲያናትን አነጸ፡፡ የእንግዶች ማረፊያ የሆኑ ቤቶችንም ሠራ፡፡ አቡነ ቴዎፍሎስ የክርስትና ጥምቀትን በሚያጠምቅ ጊዜ የብርሃን በትረ መስቀል በሚጠመቁት ሰዎች ላይ በመስቀል ምልክት ሲያማትብ ያይ ነበር፡፡
አቡነ ቴዎፍሎስና ንጉሡ ቴዎዶስዮስ በልጅነታቸው ሲጫወቱ ዕንጨት እየለቀሙ ራእይ አይተው በኋላ አንደኛው ሊቀ ጳጳሳት አንደኛው ንጉሥ እንደሚሆን ተረድተው ነበርና አሁንም እንዳዩት ራእይ ዕውን ሆነና ቤተ ክርስቲያንን በጋራ አከበሯት፡፡ በአቡነ ቴዎፍሎስ በመጀመሪያ የሹመት ዘመን ንጉሥ ቴዎዶስዮስ ሃይማኖትን እናስተማራለን የሚሉትን ሁሉ ሰብስቦ ሃይማኖታቸውን በመጽሐፍ ጽፈው ወደ እርሱ እንዲያመጡ አዘዛቸው፡፡ እንዳዘዛአውም አደረጉ፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሡና አቡነ ቴዎፍሎስ እነዚያን ጽሑፎች በመሠዊያው ላይ አድርገው ወደ እግዚአብሔር በጸለዩ ጊዜ ጌታችን ወልድ በመለኮቱ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ ትክክል ነው ብሎ ከሚያምን በቀር ሌላው የከሃዲዎች መሆኑን ገለጠላቸው፡፡ በዚህም ጊዜ ንጉሡ እነዚያን የመናፍ*ቃኑን መጻሕፍት ሰብስበው እንዲያቃጥሏቸው አዘዘ፡፡ ዳግመኛም መናፍ*ቃኑን እርሱ በሚገዛበት አገር እንዳይገኙ አዘዘ፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም ቅዱሳት መጻሕፍትን አብዝቶ

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

27 Oct, 16:18


ይመረምር ነበርና የአውጋርዮስን መጻሕፍት አወገዛቸው፡፡ ያወግዟቸውም ዘንድ ወደ እስክንድርያው አቡነ ቴዎፍሎስና ወደ ቆጵሮሱ ወደ አቡነ ኤጲፋንዮስ ወደ ሌሎቹም ኤጲስቆጶሳት ሁሉ ዘንድ ላከ፡፡ አቡነ ቴዎፍሎስም አገልግሎቱን ፈጽሞ በሰላም ዐረፈ፡፡
የአቡነ ቴዎፍሎስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

26 Oct, 19:06


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ጥቅምት 17-ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ የተሾመበት ዓመታዊ በዓሉ ነው፡፡
+ ቅዱስ ፊልያስ በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡
+ አቡነ ዲዮስቆሮስ 2ኛ በዓለ ዕረፍታቸው ነው፡፡
+ የነቢዩ ሳሙኤል እናት ቅድስት ሐና ልደቷ ነው፡፡
+ የቅዱስ ባስልዮስ ወንድም ቅዱስ ጎርጎርዮስ የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው፡፡
ሰማዕቱ ቅዱስ ፊልያስ፡- እኚህም ቅዱስ የሀገረ ቀምስ ኤጲስቆጶስ ናቸው፡፡ በዘመናቸው ቍልቍልያኖስ የተባለ ከሃዲ መኮንን ነበረና አባታችንን ወደ ፍርድ አደባባይ አቀረባቸውና ‹‹ለአማልክቶቼ ሠዋ›› አላቸው፡፡ አቡነ ፊልያስም ‹‹እኔ ሰማይንና ምድርን ፈጥሮ ለሚገዛ ለልዑል እግዚአብሔር ብቻ ነው የምሠዋው›› አሉት፡፡ መኮንኑ ቍልቍልያኖስም ‹‹እግዚአብሔር ምን ዓይነት መሥዋዕት ይሻል?›› አላቸው፡፡ አባታችንም ‹‹ቅን ትሑት የሆነ ንጹሕ ልቡናን፣ ዕውነተኛ ፍርድን፣ ቁም ነገርንና እንዲህ የመሰለውን መሥዋዕት እግዚአብሔር ይወዳል›› አሉት፡፡
ቍልቍልያኖስም አቡነ ፊልያስን ‹‹የምትጋደለው ስለ ነፍስህ ነው ወይስ ስለ ሥጋህ?›› ሲላቸው ‹‹ስለ ነፍስና ስለ ሥጋ ነው፣ እነርሱ በአንድነት ይነሣሉና›› አሉት፡፡ ከዚህም በኋላ ቍልቍልያኖስ ‹‹የምትወዳት ሚስትና የምትወዳቸው ልጆች ወይም ዘመድ አለህን?›› አላቸው፡፡ አቡነ ፊልያስም ‹‹ከሁሉም የእግዚአብሔር ፍቅር ይበልጣል›› አሉት፡፡ ከሃዲውም መኮንን ‹‹እግዚአብሔር ከበጎ ሥራ የሠራው ምንድነው?›› አላቸው፡፡ አቡነ ፊልያስም እንዲህ አሉት፡- ‹‹እግዚአብሔር ያደረገልን ይህ ነው፡- ሰማይንን ምድርን በውስጣቸው ያሉትን ሁሉ ፈጠረልን፡፡ ዳግመኛም ከጠላታችን ከሰይጣን እጅ ያድነን ዘንድ ከሰማያት ወርዶ ከቅድስት ድንግል ማርያም ሰው ሆኖ ተወለደ፤ የሕይወትንም መንገድ በዓለም ውስጥ ተመላልሶ አስተማረ፣ መከራንም በሥጋው ተቀብሎ ተሰቅሎ ሞተ፣ በሦስተኛውም ቀን ከሞት ተነሥቶ በ40 ቀን ወደ ሰማይ ዐረገ፣ ዳግመኛም ለፍርድ ይመጣል፡፡ ይህንንም ሁሉ ስለእኛ አደረገ›› አሉት፡፡ ቍልቍልያኖስም ይህን በሰማ ጊዜ ‹‹አምላክ ይሰቀላልን?›› ብሎ ጠየቃቸው፡፡ አባታችንም ‹‹አዎን የዘላለም ሕይወትን ይሰጠን ዘንድ ስለእኛ ፍቅር ሞተ›› አሉት፡፡
ከዚህም በኋላ ከሃዲው መኮንን ቍልቍልያኖስ አባታችንን ‹‹አንተ የከበርክ እንደሆንህ ዐውቃለሁና እኔ እንዳከበርኩህ ልጣላህም እንዳልፈለግሁ ዕወቅ፡፡ አሁን ለአማለክቶቼ ሠዋ፣ እምቢ ካልክ ግን በክፉ አሟሟት ትሞታለህ›› አላቸው፡፡ አቡነ ፊልያስም ‹‹እኔንስ ደስ ማሰኘት ከወደድህ እንዲያሠቃዩኝና እንዲገድሉኝ እዘዝ›› አሉት፡፡ ቍልቍልያኖስም በዚህ ንግግራቸው በጣም ተቆጥቶ የአባታችንን ራሳቸውን በሰይፍ ይቆርጧቸው ዘንድ አዘዘ፡፡
አባታችንንም ሊገድሏቸው ሲወስዷቸው ዘመዶቻቸውና የሀገሩ ታላላቅ ወገኖች ወደ እርሳቸው መጥተው ለመኮንኑ በመታዘዝ ለአማልክቶቹ እንዲሠው አባታችንን እጃቸውንና እግራቸውን እየሳሙ ለመኗቸው፡፡ አባታችንም ይህን ጊዜ ‹‹የጌታዬን የኢየሱስ ክርስቶስን መከራ መስቀል ልሸከም እሄዳለሁና እናንተ አሳሳቾች ከእኔ ወግዱ›› ብለው ገሠጹዋቸው፡፡ ከመገደያቸውም ቦታ በደረሱ ጊዜ ፊታቸውን ወደ ምሥራቅ መልሰው በመጸለይ ምእመናንንም ለጌታችንን በአደራ አስጠብቀውና ተሰናብተዋቸው አንገታቸውን ለሰያፊዎቹ አሳልፈው ሰጧቸው፡፡ ሰያፊዎቹም የአባታችንን ራስ ቆረጡትና የሰማዕትነትን አክሊልን ተቀዳጁ፡፡
የቅዱስ ፊልያስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!
+ + +
ቅዱስ ዲዮስቆሮስ 2ኛ፡- ይህም ቅዱስ አባት በዘመኑ ካሉ ትውልድ እርሱን የሚመስል ያልተገኘ በጠባዩ ቅን፣ የዋሕ፣ በዕውቀቱም አስተዋይ በበጎ ሥራው ሁሉ ፍጹም የሆነ ነው፡፡ በመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ 31ኛው የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ሆኖ በማርቆስ መንበር ላይ ተሾመ፡፡ ከሹመቱም በኋላ መልእክትን ጽፎ ለአንጾኪያው ሊቀ ጳጳሳት ለአቡነ ሳዊሮስ ላከለት፡፡ መልአክቱም ስለ ሥሉስ ቅዱስ አንድነትና ሦስትነት የሚያስረዳ ነው፡፡ እንዲሁም ስለ ምሥጢረ ሥጋዌና ስለ እመቤታችን ንጽሕና ጽፎ ለአቡነ ሳዊሮስ ላከለት፡፡ አቡነ ሳዊሮስም መልእክቱን ተቀብሎ ባነበባት ጊዜ ፈጽሞ ደስ ተሰኘባትና ለአንጾኪያ ሕዝቦች አስተማረባት፡፡ ሁሉም በዚህ ደስ አላቸው፡፡
አቡነ ሳዊሮስም በመልሱ መልእክት ጻፈለትና ‹‹በኒቅያ ከተማ ተሰብስበው ሃይማኖታቸው የቀና 318 ቅዱሳን አባቶቻችን በቀናች ሃይማኖት አጽንተው የሠሯትን ቤተ ክርስቲያን እንድትጠብቅ ለዚህች ለከበረች አገልግሎት የመረጠህ እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ›› በማለት በሃይማኖት እስከመጨረሻው ጸንቶ ምእመናንንም እንዲያጸና አስገነዘበው፡፡ ብዙ ድርሳናትንም ጨምሮ ላከለት፡፡ አቡነ ዲዮስቆሮስ ሁለተኛም መልአክቱን ተቀብሎ ለሕዝቡ አስተማረባት፡፡ ሁልጊዜም ቅዱሳት መጻሕፍትን በማስተማር ምእመናንን በሃይማኖት እንዲጸኑ በማስተማር ብዙ ካገለገለ በኋላ መልካም አገልግሎቱን ፈጽሞ በሰላም ዐረፈ፡፡ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!
+ + +
ዳግመኛም ይህች ዕለት ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ የተሾመባት ዕለት ናት፡፡ እስጢፋኖስ ማለት ‹‹መደብ›› ማለት ሲሆን በግሪክ ቋንቋ ‹‹አክሊል›› ማለት ነው፡፡ በግብሩ የቀን ሃሩር የሌሊት ቁር የማይለውጠው፣ መብራት ማለት ነው፡፡ ትውልዱ ከነገደ ብንያም ሲሆን አባቱ ስምዖን እናቱ ሐና ይባላሉ፡፡ እነርሱም እግዚአብሔርን ከሚፈሩ ከነቢያትና ከጻድቃን ወገን ናቸው፡፡ በመጀመሪያ ሁለት ወንድ ልጆችን ወለዱ፡፡ አንዱ ይሁዳ ሲባል ሁለተኛውም ቅዱስ እስጢፋኖስ (አስተፓኖስ) ነው፡፡ እስጢፋኖስ የተወለደው ጥር 1 ቀን በእስራኤል ሃገር ውስጥ ልዩ ስሟ ሐኖስ በተባለች ቦት ነው፡፡ የተወለደውም በስለት ነው፡፡ እርሱም ከመጥምቁ ዮሐንስ እግር ሥር በመሆን ተምሯል፡፡ በኋላም ወደ ቅዱሳን ሐዋርያት በመሄድ ይላላካቸውና ያገለግላቸው ነበር፡፡ በኢየሩሳሌም ቤተ ክርስቲያን ከተሾሙት ከ7ቱ ዲያቆናት አንዱ ሲሆን የዲያቆናት አለቃ እርሱ ነው፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ ወንጌልን በማስተማሩና ብዙዎችን ክርስቶስን ወደማመን ስለመለሳቸው ክፉዎች አይሁድ በጠላልትነት ተነስተውበት ጥር 1 ቀን በ34 ዓ.ም ከጌታችን ቀጥሎ ከምእመናን ወገን የመከራውን ገፈት ስለተቀበለ (በድንጋይ ተወግሮ በሰማዕትነት ስላረፈ) ‹‹ቀዳሜ ሰማዕት›› ተሰኘ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ‹‹ሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስ›› እየተባለ ይጠራል፡፡ ይኸውም የከበሩ ቅዱሳን ሐዋርያት በሰባቱ ዲያቆናት ላይ አለቃ አድርገው በሾሙት ጊዜ የተሰጠው ስያሜ ነው፡፡
የመጀመሪያ ክርስቲያኖች የአማኞች ቊጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ በሄደ ጊዜ የማኅበራዊው ኑሮ አስተዳደር ማለትም የምግብንና የመሳሰሉትን ቁሳቁሶች (ገንዘብም ጭምሮ) በትክክልና በእኩልነት የማከፋፈሉ ሥራ በሐዋርያት ዘንድ አስቸጋሪ ሆኖ ተገኘ፡፡ እነርሱም ደግሞ ዋና ተግባር አድርገው በትጋት ለመያዝ የፈለጉት ማስተማርን ነበር፡፡ ስለዚህም አማኞችን ሁሉ ሰብስበው ከመካከላቸው በመልካም ጠባያቸው የተመሰገኑ በመንፈስ ቅዱስና በጥበብ የተሞሉ ሰባት ሰዎችን እንዲመርጡ አሳስቧቸው፡፡ አማኞችንም ነገሩ አስደስቷቸው ሰባት ሰዎችን መረጡ፡፡ እነርሱም፡- ቅዱስ እስጢፋኖስ (ዕረፍቱ ጥር 1)፣ ቅዱስ ጵሮኮሮስ (ሰኔ 8)፣ ቅዱስ ጢሞና (ሚያዝያ 16)፣ ቅዱስ ፊልጶስ (ጥቅምት 14)፣ ቅዱስ ጰርሜና (መስከረም 1)፣ ቅዱስ ኒቃሮና (3 ጊዜ ሞቶ የተነሣ)፣ ቅዱስ ኒቆላዎስ (ሚያዝያ 15) ናቸው፡፡ ሐዋ 6፡5፡፡

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

26 Oct, 19:06


አክሊላት ተቀዳጅቷል፡፡
ቅዱስ እስጢፋኖስ አምላኩን ክርስቶስን በብዙ ነገር መስሏል፡፡ በመጨረሻዋ የመሞቻው ሰዓት ላይ እንኳን ሆኖ አምላኩን አብነት አድርጎ ተገኝቷል፡፡ ጌታችን ‹‹ነፍሴን ተቀበላት›› እንዳለ ሁሉ ቅዱስ እስጢፋኖስም ‹‹አቤቱ ጌታ ሆይ ነፍሴን ተቀበላት›› ብሏል፡፡ ጌታችን ‹‹አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው›› እንዳለ እስጢፋኖስም ‹‹ጌታ ሆይ ይህን ኃጥአት አትቁጠርባቸው የሚያደርጉትን አያውቁምና›› በማለት ለገዳዩቹ ምሕረትን ለምኗል፡፡ በጌታችን ጸሎት እነ ፊያታዊ ዘየማንን ጨምሮ እልፍ ነፍሳት ወደ ንስሐ ተመልሰው ገነት መንግስተ ሰማያትን እንደወረሱ ሁሉ በቅዱስ እስጢፋኖስም ጸሎት ብዙ ነፍሳት ድነው ገነት መንግስተ ሰማያትን ወርሰዋል፡፡ የጌታችን ቅዱስ መስቀል እልፍ ሙታንን ያስነሣ ድውያንን ይፈውስ እንደነበር ሁሉ የቅዱስ እስጢፋኖስም ዐፅም ሙታንን ያስነሣ ድውያንን ይፈውስ ነበር፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ የተወገረበት ድንጋይ ሰባት አብያተ ክርስቲያናት ታንጸውበታል፡፡
የቅዱስ እስጢፋኖስ ልደቱና ዕረፍቱ ጥር 1 ቀን ነው፡፡ መእመናንም ሥጋውን ወስደው በክብር ቀበሩት፡፡ ጥቅምት 17 የተሾመበት ነው፡፡ መስከረም 15 ቀን ፍልሰተ ሥጋው ነው፡፡ የቅዱስ እስጢፋኖስ ቅዱስ ዐፅሙ ሙትን ያስነሣ ድውይን ይፈውስ ነበርና አይሁድ በቅናት ተነሥተው እንደ ጌታችን ቅዱስ መስቀል የቅዱስ እስጢፋኖስን ዐፅም አርቀው በመቆፈር ቀብረው በላዩም ቆሻሻ በመጣል ለ300 ዓመት ያህል ተቀብሮ ኖሮ በመጨረሻ በፈቃደ እግዚአብሔር እንደ ቅዱስ መስቀሉ ተቆፍሮ በመውጣት መስከረም 15 ቀን ቅዱስ ዐፅሙ ወጥቶ በክብር በስሙ በታነጸው ቤተ ክርስቲያን በክብር ተቀምጧል፡፡ ይኸውም የሆነው እንዲህ ነው፡- ሰማዕቱ ቅዱስ እስጢፋኖስ ካረፈ ከ300 ዓመት በላይ በሆነ ጊዜ ጻድቁ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ሲነገሥና ሃይማኖትን በመላው ዓለም አቀና፡፡ ተዘግተው የነበሩ ገዳማትና አብያተ ክርስያናት ተከፈቱ፡፡ በዚህም ወቅት የቅዱስ እስጢፋኖስ ሥጋው በሚገኝበት በኢየሩሳሌም አካባቢ ሉክያኖስ ለሚባል ሰው ቅዱስ እስጢፋኖስ በራእይ ተገለጠለትና ‹‹እኔ እስጢፋኖስ ነኝ፣ ሥጋዬ በዚህ ቦታ ተቀብሯል›› በማለት ሥጋውን ያወጡ ዘንድ አዘዘው፡፡ ሉክያኖስም ለኢየሩሳሌሙ ኤጰስ ቆጶስ ሄዶ ነገረውና ወደ ቦታው ሄደው ሲቆፍሩ ታላቅ ንውጽውጽታ ሆነና ሳጥኑ ተገኘ፡፡ ከሳጥኑ እጅግ ደስ የሚል በዓዛ ወጣ፡፡ በዚያ ቦታም ቅዱሳን መላእክት ሲያመሰግኑ ተሰሙ፡፡ ኤጲስ ቆጶሳቱና ካህናቱም የቅዱስ እስጢፋኖስን ሥጋ በክብር በታላቅ ዝማሬ ወስደው አስቀመጡት፡፡
ከዚህም በኋላ እንዲህ ሆነ፡- በኢየሩሳሌም የሚኖር የቁስጥንጥንያ ተወላጅ የሆነ ስሙ እለእስክንድሮስ የሚባል ሰው ነበር፡፡ እርሱም ለቅዱስ እስጢፋኖስ ውብ የሆነች ቤተ ክርስቲያን ሠርቶለት ሥጋውን አፍልሰው በዚያ በክብር አኖሩት፡፡ ከ5 ዓመት በኋላም እለእስክንድሮስ ዐረፈና ሚስቱ በቅዱስ እስጢፋኖስ አስክሬን ጎን ቀበረችው፡፡ ከሌሎች ከ5 ዓመቶችም በኋላ ሚስቱ የባሏን አስክሬን ወደ ቁስጥንጥንያ አገር ይዛ ልትሄድ አስባ ወደ መቃብሩ ስትሄድ የባሏን አስክሬን የወሰደች መስሏት በእግዚአብሔር ፈቃድ የቅዱስ እስጢፋኖስን ሣጥን ወስዳ እስከ አስቃላን ከተማ ድረስ ተሸከመችውና በመርከብ ተሳፍራ ወደ ቁስጥንጥንያ ሄደች፡፡
የእለእስክንድሮስም ሚስት በመርከብ ስትጓዝ ጣዕም ያለው የመላእክትን ዝማሬ ሰማች፡፡ ልታየውም በተነሣች ጊዜ ሣጥኑ የቅዱስ እስጢፋኖስ ሥጋ ያለበት መሆኑን ዐወቀቸ፡፡ ወደ ኢየሩሳሌምም ለመመለስ አልተቻላትም ይልቁንም ይህ እንዲሆን የእግዚአብሔር ፈቃድ መሆኑን ዐውቃ ለዚህ ክብር ስላበቃት አመሰገነች፡፡ ቁስጥንጥንያም እንደደረሰች ለሊቀ ጳጳሱ በእግዚአብሔር ፈቃድ የቅዱስ እስጢፋኖስብ ሥጋ ይዛ እንደመጣች ላከችበት፡፡ ካህናቱና ሕዝቡም ሁሉ በታላቅ ደስታ ወጥተው በክብር ተቀበሏት፡፡ ከሥጋውም ብዙ ተአምራት ተገልጠው ታዩ፡፡ ከዚህም በኋላ ሥጋውን በበቅሎ ጭነው ሲጎትቱ ቁስጣንጢኖስ ከሚባል ቦታ ሲደርሱ የቅዱስ እስጢፋኖስን ሥጋ የያዘችው በቅሎ አልንቀሳቀስ አለች፡፡ እግዚአብሔር የቅዱስ እስጢፋኖስ ሥጋው በዚህ ቦታ እንዲኖር የፈቀደ መሆኑን ዐወቁ፡፡ ሥጋውን የተጫነው በቅሎም በሰው አንደበት ‹‹የቅዱስ እስጢፋኖስን ሥጋ በዚህ ሊያኖሩ ይገባል›› ብሎ ተናገረ፡፡ ይህንንም ያዩና የሰሙ ሁሉ እጅግ አደነቁ፡፡ የበለዓምን አህያ ያናገረ አምላክ አሁንም የቅዱስ እስጢፋኖስን ሥጋ የተሸከመችውን በቅሎ እንዳናገራት ዐውቀው ደስ አላቸው፡፡ የሀገሪቱም ንጉሥ በቦታው ላይ ውብ ቤተ ክርስቲያን ሠርተውለት ሥጋውን በውስጧ በክብር አኖሩ፡፡ ከሥጋውም ብዙ አስገራሚ ተአምራት ተፈጽመው ታዩ፡፡
የቅዱስ እስጢፋኖስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

26 Oct, 19:06


ግራኝን ከእነ ሰራዊቱ ያሳደደው የቅዱስ እስጢፋኖስ ሰራዊት!

ግራኝ የተባለው አሕዛባዊ ዓመፀኛ በተነሣና በክርስቲያኖች ላይ ጦርነትን በዐወጀ ጊዜ በየአውራጃውና በየመንደሩ ፍጅትና ሁከት ሆነ።

ግራኝም የረከሰች ሃይማኖታቸውን ያልተቀበለውን ኹሉ እንዲገድሉ ለሰራዊቱም ኹሉ ትእዛዝ ሰጠ። ብዙዎች ክርስቲያኖችም በግፍ በጭካኔ በሰይፍ ተገደሉ። በእሳትም የተቃጠሉ አሉ፤ በመጋዝ የተሰነጠቁ አለ፤ ወደጥልቅ ጉድጓድ ተጥለው የሞቱ አሉ፤ ከየመንደራቸውም ወጥተው ወደተራራዎችና ዋሻዎች የተሰደዱ አሉ። ጠንበላ በምትባል የቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን ባለችበት አውራጃም የግራኝ ሰራዊቶች ደርሰው ይኽችን የጠንበላን አውራጃ ከበቧት። የሀገሪቱም ሰዎች ወደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን ገብተው ሰማዕቱን ይማጸኑት ጀመር። የግራኝም የወታደሮች አለቃ ለመሸመቅ አስቦ ወደ አንድ ዋሻ ሲገባ ዋሻው በተአምር ተደርምሶ ገደለው፣ በውስጡም ቀበረው። ርጉም ግራኝም እሳት ይዞ ጠንበላ አውራጃ የምትገኘውን የቅዱስ እስጢፋኖስን ቤተ ክርስቲያን ሊያቃጥላት ቀረበ። ነገር ግን ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤቱን እንዲያቃጥል አልፈቀደለትምና ሊያቃጥላት አልቻለም። ይልቁንም በቅዱስ እስጢፋኖስ ትእዛዝ በቤተ ክርስቲያኑ ጠፈር ላይ የነበሩ ንቦች ተነሥተው ከነሰራዊቱ እስከሩቅ አውራጃ ድረስ አሳደዱት። ግራኝም ከነሰራዊቱ በፍርሃትና በመንቀጥቀጥ ፈጥኖ ሸሸ። የጠንበላ ሀገር ሰዎችም ከግራኝ ያዳናቸውን የቅዱስ እስጢፋኖስን አምላክ ልዑል እግዚአብሔርን አመሰገኑ።

ሊቀ ዲያቆናት ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ ከዘመኑ ግራኞች ሀገራችንን ይታደግልን።
✞ ✞ ✞

ዳግመኛም ሊቀ ዲያቆናት ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ በአንድ አሕዛብ ላይ ያደረገው ተኣምር ይኽ ነው፡- ከዕለታት በአንደኛው ቀን ከአሕዛብ ወገን የኾነ አንድ ሰው "የክርስቲያኖች አምላካቸው ምን ያደርገኛል?" ብሎ ታበየ። "ክርስቲያኖች ወደሚያምኑበት የጠበል ሥፍራ ብገባስ መግባቴን ያውቅ ዘንድ ማን ይቻለዋል?" ብሎ እግዚአብሔርን ተፈታተነ። ይኽንንም ብሎ ክርስቲያን መስሎ ወደ ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ መካነ ጠበል በድፍረት ገባ።

ይኽም ደፋር አሕዛብ ወደ ጠበሉ በድፍረትና በመታበይ በገባ ጊዜ ሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስ ተገልጦ ይዞ ያንፈራግጠው ወደታችና ወደላይ ያንከባልለው ጀመር። ያም ሰው በታላቅ ቃል "የክርስቲያኖች ወዳጅ ቅዱስ እስጢፋኖስ ሆይ! እባክህ እዘንልኝ፣ እንደዚህ መድፈርን አልደግምም፣ በአምላክህ እግዚአብሔር ስም እምላለሁ። ከእንግዲህም ክርስቲያን እሆን ዘንድ እጠመቃለሁ...." እያለ ጮኸ። በዚያ የነበሩ ካህናትም ይነግራቸው ዘንድ ሲጠይቁት እርሱም አንድ ቀይ ሰው ተገልጦ በምድር ላይ ጥሎ እንደገሠፀውና እንደቀጣው ከነገራቸው በኋላ "ከእንግዲህስ ሳልጠመቅ ያሳለፍኩት ያለፈው ዘመኔ ይበቃኛል" አላቸው። እንዲያጠምቁትም ጠየቃቸው። እነርሱም አስተምረው በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቁት። እርሱም ጽኑ ክርስቲያን ኾኖ ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስን ቤተ ክርስቲያንን የሚያገለግል ሆነ።

የሊቀ ዲያቆናት የቀዳሜ ሰማዕት የቅዱስ እስጢፋኖስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን።

(ምንጭ፦ ሞረትና ጅሩ ወረዳ የሚገኘው ጠንበላ ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን ያሳተመው ገድለ ቅዱስ እስጢፋኖስ)
✞ ✞ ✞

(ፎቶው፦ የመስከረም 15 ቀን 2015 ዓ.ም የፍልሠተ ዐፅሙ ክብረ በዓል በታላቁ ሐይቅ ቅዱስ እስጢፋኖስ ገዳም ሲከበር የሚያሳይ ነው።
+ + +

ተአምር ከእግዚአብሔርና ከሰይጣን ሲሆን ልዩነቱ !
ይኸውም የቀዳሜ ሰማዕት የቅዱስ እስጢፋኖስ ተአምርና በሬውን በጆሮው እፍ ብሎ ቢተነፍስበት በምትሃት ለሁለት የሰነጠቀውና በተአምር ወደ አየር የበረረው የጠንቋዩ ናኦስ ተአምር ነው።
ቀዳሜ ሰማዕት ሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስ በአህዛብ ፊት ያደረጋቸው ተአምራት እጅግ ድንቅ ናቸው፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ በአህዛብ መካከል ቆሞ ሲያስተምር ከቆየ በኋላ አንድ አንደበቱ ዲዳ የሆነ ሰው አጠገቡ ቢመጣ በጆሮው የሕይወት እስትንፋስ እፍ ቢልበት መስማት የማይችለው መስማት ቻለ፡፡ በዚህም ጣኦት አምላኪው ናኦስ እና ተከታዮቹ ሁሉ ወደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ተመለሱ፡፡ ጣኦት አምላኪው ናኦስ በድርጊቱ በጣም ከመናደዱ የተነሣ በአጠገቡ የቆመውን በሬ ጠንቋዩ ናኦስ በጆሮው እፍ ብሎ ቢተነፍስበት በሬው በምትሃት ለሁለት ተሰንጥቆ በመሞቱ ወደ ቅዱስ እስጢፋኖስ የተመለሱት በናኦስ ምትሃታዊ ድርጊት በመሳባቸው እንደገና ወደ ናኦስ ተመለሱ፡፡
ቅዱስ እስጢፋኖስም በዚህ ጊዜ የአህዛብ ልቡና ወላዋይ እንዳይሆንና እንዳይጠፉም በማሰብ ናኦስ እፍ ብሎ ለሁለት ሰንጥቆ የገደለውን በሬ መልሶ በሕይወት እንዲያስነሣው ናኦስን ጠየቀው፡፡ ነገር ግን ናኦስ ያንን ማድረግ አልቻለም፡፡ ከዚህም በኋላ ቅዱስ እስጢፋኖስ ‹‹ናኦስ ዳግመኛ ሕይወት ዘርቶ ማስነሣት ካልቻለ እኔ ነገሩ ሀሰተኛ ነው ማለት ነው፣ እኔ ግን በእግዚአብሔር ኃይልና ድንቅ ሥራ ይህን ለሁለት ተሰንጥቆ የሞተውን በሬ ዳግመኛ ሕይወት ዘርቶ እንዲነሣ አደርገዋለሁ›› በማለት ወደ እግዚአብሔር ከጸለየ በኋላ በሬውን አስነሣው፡፡ ይህንንም ተአምር አድርጎ በማስተማር ልቦናቸው ተጠራጥሮ ወደ ናኦስ የተመለሱትን አህዛብ ገንዘቡ እንዲሆኑ በእግዚአብሔር ኃይልነት እንዲያምኑ አድርጓል፡፡ ናኦስ በአልሸነፍ ባይነትና በአጋንንት ረዳትነት ራሱን ወደ ላይ እንዲንሣፈፍ አድርጎ በአየር ላይ ቢወጣ ቅዱስ እስጢፋኖስ የእግዚአብሔርን ተአምር በማሳየት በትዕግስት ጠብቆ በአጋንንት ረዳትነት ወደ ላይ የተነሳውን ናኦስ በትምዕርተ መስቀል ቢያማትብበት ይዘውት የነበሩት አጋንንት ሁሉ ለቀውት ሲበተኑ ናኦስም ምድር ደርሶ ተንኮታኩቶ በመውደቁና ክፉ አሟሟት በመሞቱ በጣኦት አምላኪነት የነበሩ ሁሉ ዳግም ወደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ተመልሰዋል፡፡

ዛሬ ድረስ ተአምር በሚመስል ከንቱ ማታለል ሕዝቡን ከቤተክርስቲያን የሚለዩ በግብር ናኦስን የሚመስሉ በርካታ ሐሳውያን ተአምር ማድረግ የሚችሉ በመምሰል፣ መልእክት ከእግዚአብሔር ወይም ከእመቤታችን የመጣላቸው በማስመሰል፣ እውቀት ከማጣት የተነሣ የጠፋውን ብዙውን መንጋ ምእመን በፈውስና በጥምቀት ስም ወደ ሞት ይነዱታል!

ከቀዳሜ ሰማዕት ሊቀ ዲያቆናት ከቅዱስ እስጢፋኖስ ከበዓለ ዕረፍቱ በረከት ይክፈለን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

26 Oct, 19:06


እነዚህንም ቅዱሳን በከበሩ ሐዋርያት ፊት ባቆሟአቸው ጊዜ ጸልየው እጃቸውን በራሳቸው ላይ ጭነው ሾሟቸው፡፡ በከበሩ ሐዋርያት ጫንቃ ላይ ተጭኖ የነበረው ከባድ ሸክም ባሎቻቸው የሞቱባቸውን ሴቶችና ወላጆቻቸው የሞቱባቸውን ደሀ አደጎች በመርዳት ችግሮቻቸውን አቃለሉላቸው፡፡ በከበሩ ሐዋርያት ከተመረጡት ሰባቱ ዲያቆናት መካከል ሊቀ ዲያቆናት ተደረጎ የተመረጠው ቅዱስ እስጢፋኖስ ሲሆን ሌሎቹም ዲያቆናት እስከ ሕይወታቸው ፍጻሜ ወንጌልን በማስተማርና የመጀመሪያ ክርስቲያኖች በማስተዳደር በጽናት ተጋድለዋል፡፡
እነዚህም ሰባቱ ዲያቆናት ከአባቶቻቸው ከከበሩ ሐዋርያት አይተው የእነርሱንም መንፈስ ተቀብለው ያልተማሩ አህዛብን ልቡናቸውን ለመስበርና የእግዚአብሔርን ኃይልነት ተረድተው እንዲገነዘቡ በማሰብ ብዙ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን ያደርጉ ነበር፡፡ ከእነርሱም ውስጥ በዋነኛነት ቅዱስ እስጢፋኖስ በአህዛብ ፊት ያደረጋቸው ተአምራት እጅግ ድንቅ ናቸው፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ በአህዛብ መካከል ቆሞ ሲያስተምር ከቆየ በኋላ አንድ አንደበቱ ዲዳ የሆነ ሰው አጠገቡ ቢመጣ በጆሮው የሕይወት እስትንፋስ እፍ ቢልበት መስማት የማይችለው መስማት ቻለ፡፡ በዚህም ጣኦት አምላኪው ናኦስ እና ተከታዮቹ ሁሉ ወደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ተመለሱ፡፡ ጣኦት አምላኪው ናኦስ በድርጊቱ በጣም ከመናደዱ የተነሣ በአጠገቡ የቆመውን በሬ ጠንቋዩ ናኦስ በጆሮው እፍ ብሎ ቢተነፍስበት በሬው በምትሃት ለሁለት ተሰንጥቆ በመሞቱ ወደ ቅዱስ እስጢፋኖስ የተመለሱት በናኦስ ምትሃታዊ ድርጊት በመሳባቸው እንደገና ወደ ናኦስ ተመለሱ፡፡
ቅዱስ እስጢፋኖስም በዚህ ጊዜ የአህዛብ ልቡና ወላዋይ እንዳይሆንና እንዳይጠፉም በማሰብ ናኦስ እፍ ብሎ ለሁለት ሰንጥቆ የገደለውን በሬ መልሶ በሕይወት እንዲያስነሣው ናኦስን ጠየቀው፡፡ ነገር ግን ናኦስ ያንን ማድረግ አልቻለም፡፡ ከዚህም በኋላ ቅዱስ እስጢፋኖስ ‹‹ናኦስ ዳግመኛ ሕይወት ዘርቶ ማስነሣት ካልቻለ እኔ ነገሩ ሀሰተኛ ነው ማለት ነው፣ እኔ ግን በእግዚአብሔር ኃይልና ድንቅ ሥራ ይህን ለሁለት ተሰንጥቆ የሞተውን በሬ ዳግመኛ ሕይወት ዘርቶ እንዲነሣ አደርገዋለሁ›› በማለት ወደ እግዚአብሔር ከጸለየ በኋላ በሬውን አስነሣው፡፡ ይህንንም ተአምር አድርጎ በማስተማር ልቦናቸው ወላውሎ ወደ ናኦስ የተመለሱትን አህዛብ ገንዘቡ እንዲሆኑ በእግዚአብሔር ኃይልነት እንዲያምኑ አድርጓል፡፡ ናኦስ በአልሸነፍ ባይነትና በአጋንንት ረዳትነት ራሱን ወደ ላይ እንዲንሣፈፍ አድርጎ በአየር ላይ ቢወጣ ቅዱስ እስጢፋኖስ የእግዚአብሔርን ተአምር በማሳየት በትዕግስት ጠብቆ በአጋንንት ረዳትነት ወደ ላይ የተነሳውን ናኦስ በትምዕርተ መስቀል ቢያማትብበት ይዘውት የነበሩት አጋንንት ሁሉ ለቀውት ሲበተኑ ናኦስም ምድር ደርሶ ተንኮታኩቶ በመውደቁ በጣኦት አምላኪነት የነበሩ ሁሉ ዳግም ወደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ተመልሰዋል፡፡
የሰማዕታት መጀመሪያ የሆነው ቅዱስ እስጢፋኖስ በትምህርቱና በተአምራቱ ብዙዎችን ወደቀናች ሃይማኖት ስለመለሰ ክፉዎች አይሁድ ቀኑበትና የሐሰት ምስክር አዘጋጁበት፡፡ ‹‹በእግዚአብሔርና በሙሴ ላይ የስድብን ቃል ሲናገር ሰምተነዋል›› ብለው በሐሰት ከሰሱትና በሸንጎአቸው አቆሙት፡፡ ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስም ከአብርሃም ጀምሮ እስከ ጌታችን ያለውን ሁሉንም እየጠቀሰ የሃይማኖትን ነገር አስተማራቸው፡፡ ነቢያትን ስለማሳደዳቸውና ስለመግደላቸው እየወቀሰ ሲናገራቸው በትምህርቱ ተናደው ጆሮአቸውን ይዘው በመጮህ በድንጋይ ወግረው ይገድሉት ዘንድ እየጎተቱ ከከተማው ውጭ አወጡት፡፡ ቅዱሱም በድንጋይ ወግረው ሲገድሉት ከጌታችን የተማረውን ‹‹አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይህን ኃጢአት አትቁጠርባቸው›› እያለ ስለገዳዮቹ ምሕረትን ይለምን ነበር፡፡ ሰማይም ተከፍቶ የእግዚአብሔርን ክብር ተመለከተ፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ ይኸውም የቀድሞው ሳውል ቅዱስ እስጢፋኖስን በድንጋይ ሲወግሩት የገዳዮቹን ልብስ ይጠብቅና ድንጋይ ያቀብል ነበር፡፡ ‹‹የሰማዕትህንም የእስጢፋኖስን ደም ባፈሰሱ ጊዜ፥ ራሴ ደግሞ በአጠገባቸው ስቆም ተስማምቼ የገዳዮችን ልብስ እጠብቅ ነበር አልሁ›› ብሎ ራሱ ቅዱስ ጳውሎስ መስክሯል፡፡ ሐዋ 22፡20፡፡ የቅዱስ እስጢፋኖስ መምህር የነበረው ምሑረ ኦሪቱ ገማልያልና ልጁ አቢብ በእስጢፋኖስ ትምህርትና የሞቱ ሰዎች የሰጡትን ምስክርነት አይተው ከይሁዲነት ተመልሰው በክርስቶስ አምነው ተጠምቀዋል፡፡ ስለ ሰማዕቱ ቅዱስ እስጢፋኖስ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ እንዲህ ተብሎ ነው የተጻፈው፡- ‹‹እስጢፋኖስም ጸጋንና ኃይልን ተሞልቶ በሕዝቡ መካከል ድንቅንና ታላቅ ምልክትን ያደርግ ነበር፡፡ የነፃ ወጪዎች ከተባለችው ምኵራብም ከቀሬናና ከእስክንድርያም ሰዎች ከኪልቅያና ከእስያም ከነበሩት አንዳንዶቹ ተነሥተው እስጢፋኖስን ይከራከሩት ነበር፤ ይናገርበት የነበረውንም ጥበብና መንፈስ ይቃወሙ ዘንድ አልቻሉም፡፡ በዚያን ጊዜ በሙሴ ላይ በእግዚአብሔርም ላይ የስድብን ነገር ሲናገር ሰምተነዋል የሚሉ ሰዎችን አስነሡ፡፡ ቀርበውም ያዙት ወደ ሸንጎም አመጡትና ‹ይህ ሰው በዚህ በተቀደሰው ስፍራ በሕግም ላይ የስድብን ነገር ለመናገር አይተውም፤ ይህ የናዝሬቱ ኢየሱስ ይህን ስፍራ ያፈርሰዋል ሙሴም ያስተላለፈልንን ሥርዓት ይለውጣል ሲል ሰምተነዋልና› የሚሉ የሐሰት ምስክሮችን አቆሙ፡፡ በሸንጎም የተቀመጡት ሁሉ ትኵር ብለው ሲመለከቱት እንደ መልአክ ፊት ሆኖ ፊቱን አዩት፡፡›› 6:8-15፡፡
የአይሁድ በቅዱስ እስጢፋኖስ ላይ ያቀረቡት የክሳቸው ምክንያት ጌታችንን ከከሰሱት ክስ ጋር በሁለት ነጥቦች ይመሳሰላል፡፡ የመጀመሪያው ክሳቸው ‹‹የሙሴን ሕግ ሽሯል›› የሚል ነው፡፡ ‹‹የሙሴን ሕግ በመሻር ኦሪት አትጠቅምም አትመግብም አታድንም፤ ሐዲስ ኪዳን (ወንጌል) ግን ትመግባለች ታድናለች›› ብሏል ብለው ከሰሱት፡፡ ሐዋ 6፡13፡፡ ሁለተኛው ክሳቸው ‹‹እግዚአብሔርንም ይሰድባል›› የሚል ነው፡፡ ሐዋ 7፡50፡፡ አይሁድም የቅዱስ እስጢፋኖስን የወንጌል ቃል ንግግሮች በእግዚአብሔር ላይ እንደተሰነዘሩ ስድቦች በመቁጠር ነበር የወነጀሉት፡፡ የኦሪት የካህናት አለቃውም ቅዱስ እስጢፋኖስ ለተከሰሰበት መልስ ይሰጥ ዘንድ ሲጠይቀው እርሱ ግን ለተከሰሰበት መልስ ከመስጠት ይልቅ ከአብርሃም ጀምሮ እስከ ክርስቶስ ድረስ ያለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ጽሑፍ በዝርዝር በሚገባ ተረከላቸው፡፡
ቅዱስ እስጢፋኖስም እንዲህ አላቸው፡- ‹‹ከነቢያትስ አባቶቻችሁ ያላሳደዱት ማን ነው? የጻድቁንም መምጣት አስቀድሞ የተናገሩትን ገደሉአቸው፤ በመላእክት ሥርዓት ሕግን ተቀብላችሁ ያልጠበቃችሁት እናንተም አሁን እርሱን አሳልፋችሁ ሰጣችሁት ገደላችሁትም፡፡ ይህንም በሰሙ ጊዜ በልባቸው በጣም ተቈጡ ጥርሳቸውንም አፋጩበት፡፡ መንፈስ ቅዱስንም ተሞልቶ ወደ ሰማይ ትኵር ብሎ ሲመለከት የእግዚአብሔርን ክብር ኢየሱስንም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አየና፡፡ እነሆ ሰማያት ተከፍተው የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አያለሁ አለ፡፡ በታላቅ ድምፅም እየጮኹ ጆሮአቸውን ደፈኑ፣ በአንድ ልብ ሆነውም ወደ እርሱ ሮጡ፤ ከከተማም ወደ ውጭ አውጥተው ወገሩት፡፡ ምስክሮችም ልብሳቸውን ሳውል በሚሉት በአንድ ጎበዝ እግር አጠገብ አኖሩ፡፡ እስጢፋኖስም ‹ጌታ ኢየሱስ ሆይ ነፍሴን ተቀበል› ብሎ ሲጠራ ይወግሩት ነበር፡፡ ተንበርክኮም ‹ጌታ ሆይ ይህን ኃጢአት አትቍጠርባቸው› ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ፡፡ ይህንም ብሎ አንቀላፋ፡፡ ሳውልም በእርሱ መገደል ተስማምቶ ነበር፡፡ 7:52-60፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ ስለንጽሕናው ስለድንግልናው፣ ስለሰማዕትነቱ ስለተጋድሎው እና ስለስብከቱ ስለተአምራቱ ሦስቱ

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

25 Oct, 15:15


አሁንም ድረስ ዋርካው በሥፍራው ላይ ሕያው ማስረጃ ሆኖ ይገኛል።

ገዳሙ ከአቡነ ኢያሱ ዕረፍት ከዘመናት በኋላ በግራኝ አህመድ ወረራ ጥቃት ደርሶበት መነኰሳቱም ተበታትነው ለ247 ዓመት ጠፍ ሆኖ ከቆየ በኋላ በ1747 ዓ.ም አቡነ ዮሴፍ የተባሉት ጻድቅ በሊቀ መላእክት በቅዱስ ሚካኤል መሪነት ከአምባሰል ተነሥተው መጥተው ገደሉን ቦርቡረው ቅኔ ማሕሌት፣ ቅድስትና ቅዱሳንን ያሟላ ቤተ መቅደስ በማነጽ ዳግም ገዳሙን በማቅናት የቀደመውን የአባቶችን ታሪክ ማስቀጠል ችለዋል። በግራኝ አህመድ ወረራ ወቅት ቅርሶቹና ነዋየ ቅዱሳቱ አደጋ እንዳይደርስባቸው አባቶች ሰብስበው በስውር ከተቀበሩ ከረጅም ጊዜ በኋላ የቀበሩበት ቦታ ጠፍቶባቸው ነበር ነገር ግን የወንዙ ውኃ አቅጣጫውን ቀይሮ ሽቅብ ፈስሶ ቅርሶቹ ያሉበትን ቦታ አመላክቷል።

መካነ ሱባኤ ወተመስጦ ጀር ቅድስት ሥላሴ አቡነ ኢያሱ ገዳም የበርካታ መናንያን አበው በኣት ከመሆኑም ባሻገር የወንዶች ብቻ ገዳም ሲሆን መናንያኑ ከአራዊት ጋር ተስማምተው የሚኖሩበት ነው። ዙሪያው በገደል የተከበበ ሲሆን ወደ ገዳሙ ለመውረድ የዕንጨት መሰላልን ተጠቅሞ መጓዝ ግድ ይላል። ወደ ገዳሙ መግቢያ የሚያስወርደው መሰላል ደቡብ ወሎ ከሚገኘው ከታላቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ገዳም መግቢያ ጋር ይመሳሰላል። የመሰላሉ ርዝመት ከ15 ሜትር በላይ ይሆናል።

ገዳሙ ከእግዚአብሔር ጋር በሱባዔ ለመገናኘት ፍጹም ጸጥታ የሰፈነበት ከመሆኑም በላይ ረድኤተ እግዚአብሔር ያለበት ቅዱስ ቦታ ነው። ዋሻው የሚከፈተው ዐቢይ ጾም ላይ እና በእመቤታችን የፍልሰታ ጾም ወቅት ነው። በዋሻው ውስጥ ሱባዔ የሚያዘው በደረቅ ሽምብራ ቆሎ እና በአንድ ኩባያ በሶ ብቻ ነው። አባቶች በኣት ዘግተው ጾመ ፍልሰታን፣ ጾመ ነቢያትን፣ ጾመ ሐዋሪያትን በይበልጥ በምነና ሕይወት የሚያሳልፉበት የበረከት ገዳም ነው።

በጀር ሥላሴ የሚገኘው ታሪካዊ ታላቅ ተራራ በልበሊት ኢየሱስን ግራኝ አሕመድ ሲያቃጥል ሁለት በወርቅ የታነጹ አብያተ ክርስቲያናት በፍቃደ እግዚአብሔር እንደሰወረ አባቶች ይናገራሉ። ይኸም ጥንታዊና ታሪካዊ ተራራ አሁንም በቦታው የሚገኝ ሲሆን በዋሻው ውስጥ የክብር ባለቤት ጌታችን በስደቱ ወራት ከእናቱ ድንግል ማርያም፣ ከዮሴፍና ከሰለሜ ጋር ለጥቂት ጊዜ የተቀመጠበት ሲሆን አቡነ ዜና ማርቆስና አቡነ ተክለ ሃይማኖትም በምነና የተጋደሉበት ታላቅ ዋሻ ነው። ዋሻው እስከ ኢየሩሳሌም ድረስ ውስጥ ለውስጥ የሚያስኬድ ሲሆን በውስጡ ከ40 በላይ አብያተ ክርስቲያናት እንደተሰወሩበት አባቶች ይናገራሉ።

በግራኝ አሕመድ ወረራ ወቅት የግራኝ ሠራዊት አብያተ ክርስቲያናቱን እናጠፋለን ብለው ሲመጡ በተኣምራት ሰምጠው እንደጠፉ አባቶች ያስረዳሉ። አዛዦቹንም በዋሻ ውስጥ የሚገኙት ወፍ የሚያህሉ ተርቦች ነድፈው ጨርሰዋቸዋል። እነዚያ ተርቦች አሁንም ድረስ በገዳሙ ውስጥ ያልተፈቀደ ነገር ሲደረግ በመናደፍና በመከልከል ዋሻውን የሚጠብቁ ሲሆኑ አንዱ ተርብ ከነደፈ ሕይወት ሊያጠፋ እንደሚችል የገዳሙ አባቶች ይናገራሉ። ከዚኸም በላይ ዋሻው በነብርም ይጠበቃል።

ገዳሙ ባለብዙ ቃልኪዳን ሲሆን ብዙ ስውራን አበው ዛሬም የሚኖሩበት ትንቢታቸው የማይነጥብ ብዙ ግሁሳን የከተሙበት ነው። ስውራኑ አበው ዛሬም እግዚአብሔር ለፈቀደለት ሰው ይገለጣሉ። ደገኞቹ የኢትዮጵያ ቀደምት ነገሥታት የገዳሙን ክብር በመረዳት ቦታው ድረስ በመሔድ በረከት ይቀበሉ ነበር። ዳግማዊ ምኒሊክ ለጀር ሥላሴ ገዳምና ለገዳማውያኑ አለኝታ ስለነበሩ በገዳሙ የታሪክ መዝገብ ስማቸው ዘወትር ይነሳል። ግርማዊ ዐፄ ኀይለ ሥላሴ ቦታውን ይንከባከቡት የነበረ ሲሆን ለገዳሙ መርጃ የሚሆን አዲስ አበባ ላይ የሚከራይ ቤት አሠርተው በኪራዩ ገቢ ገዳሙ እንዲጠቀም አድርገው ነበር። በአካልም ገዳሙ ድረስ በመሔድ በረከትን ይቀበሉ ነበር።
የአቡነ ኢያሱ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

25 Oct, 15:15


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ጥቅምት 16 የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ያቃቱ ዕረፍቱ ነው።
ጀር ሥላሴ ገዳምን የመሰረቱትና የጻድቁ አቡነ ሀብተማርያም እረድዕ የነበሩት አቡነ ኢያሱ ዘጀር ሥላሴ ዕረፍታቸው ነው።
ጥቅምት 16-የብርሃን እናቱ ድንግል ወላዲተ አምላክ በስደቷ ወራት ያደረገችው ተአምር ይህ ነው፡- ክብርት እመቤታችን ከተወደደ ልጇ ከአምላካችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር በስደታቸው ወራት ከአንዱ ሀገር ወደ ሌላው ሀገር እየተዘዋወሩ ወደታችኛው ግብጽ ቤጎር ቆላ ደረሱ፡፡ በዚያም ግብፃውያን እንደ ሕጋቸው ለአማልክቶቻቸው ላሞችን አርደው ሠውላቸው፡፡ በጎሽ፣ በአውራሪስ፣ በነጭ ዝንጀሮ የሚመሰሉ አጋንንትም መጡ፡፡ እመቤታችንም ከሩቅ ሆና ተመልክታቸው እነዚያን አጋንንት በጸሎቷ እንደጢስ በተነቻቸው፡፡ ግብፃውያንም ፈርተው እየጮኹ ሸሹ፡፡ በዚያም ወራት ‹‹ረዳት አማልክቶቻችንን ጠፉብን›› ብለው እያዘኑ ሳለ ዮሴፍን ሲጸልይ አግኝተውት አስረው በምድር ላይ አስተኝተው 40 ግርፋት ገረፉት፡፡ እርሱም በዚህ ጊዜ ‹‹እመቤቴ ሆይ ስለ አንቺና ስለ ልጅሽ ይህ መከራ አግኝቶኛልና እርጂኝ›› ብሎ በኀይል ጮኸ፡፡ እመቤታችንም ድምጹን ስትሰማ የሄሮድስ ጭፍሮች የመጡ መስሏት እጅግ ደነገጠች፡፡ ቅዱስ ገብርኤልም ተገልጦ ካረጋጋት በኋላ ዮሴፍን በኀይል ይደበድቡ የነበሩትን በእሳት ሰይፉ ጨረሳቸው፡፡ ዮሴፍንም በእጆቹ ዳሰሰውና ፈወሰው፡፡ እመቤታችንም ዮሴፍን ባየችው ጊዜ ‹‹ይህ ሁሉ መከራ ያገኘህ በእኔና በልጄ ምክንያት ነው›› ብላው አንገት ለአንገት ተቀቅፈው ተላቀሱ፡፡ መልአኩም ‹‹ይሄ ሀዘናችሁ በደስታችሁ ጊዜ ይረሳል…›› እያለ አረጋጋቸውና ዐረገ፡፡ የሀገሩ ሰዎችም ይወጓቸው ዘንድ ወጡና ክፉ ውሾችን ለቀቁባቸው፡፡ ነገር ግን ውሾቹ በሰው አንደበት እመቤታችንን እያነጋገሯት ሰግደው የእግሯን ትቢያ ልሰው በመመለስ ባለቤቶቻቸውን መልሰው መናከስ ጀመሩ፣ ብዙዎቹንም ገደሏቸው፡፡ አረጋዊ ዮሴፍም ‹‹እመቤቴ ሆይ በዚህ ሀገር ከምንኖርስ በዱር በበረሀ ብንኖር ይሻለናል›› ብሏት ወደለ ሌላ ትርጓሜዋ የሰላም ሀገር ወደሆነች ዲርዲስ ሀገር ደረሱ፡፡ ሰዎቹም ‹‹ይህችስ የነገሥታት ወገን ትመስላለች በላያችን ላይ ትነግሥብናለች›› ብለው በክፉ ሲነሱባቸው በማግስቱ ደመና ነጥቃ ወስዳ ኤልሳቤጥ በሞት ካረፈችበት በረሀ አደረሰቻቸው፡፡ ዮሐንስ በእናቱ በድን ላይ ሆኖ እያለቀሰ ሳለ ዮሴፍንና ሰሎሜን ባያቸው ጊዜ ደነገጠ፡፡ ጌታችንም አረጋጋው፡፡ እመቤታችንም ስለ ኤልሳቤጥ ሞት እጅግ መሪር የሆነ ልቅሶን ስታለቅስ ልጇ ድንቅ ምሥጢርን ከነገራት በኋላ አረጋጋት፡፡ እመቤታችንም ‹‹እናቱ ሞታበታለችና በዚህም በረሀ ማንም የለውምና ዮሐንስን ከእኛ ጋር እንውሰደው›› ስትለው ጌታችን ‹‹ዕድሉ በዚህ በረሀ ነው›› ብሎ አረጋጋት፡፡

ከዚህም በኋላ ደመና ነጥቃ ወስዳ ወደ ጋዛ ምድር አደረሰቻቸውና በዚያ አተር የሚያበራዩ ሰዎችን አግኝታ እመቤታችን ‹‹ለልጄ አተር ስጡኝ›› አለቻቸው፡፡ እነርሱም ክፉዎች ነበሩና ‹‹ይህ አተር ሳይሆን ድንጋይ ነው›› አሏት፡፡ ሕፃኑ ልጇም ‹‹እናቴ ሆይ እንደቃላቸው ይሁንላቸው ተያቸው›› አላት፡፡ ያንጊዜም አተሩ ድንጋይ ሆነ፣ ይህም እስከዛሬም ድረስ አለ፡፡
አባ ያቃቱ:- ከእርሱ በፊት የነበረው አቡነ ብንያሚን በሞት ባረፈ ጊዜ ይህን ቅዱስ አባት መርጠው በእስክንድርያ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት፡፡ እርሱም ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት 49ኛ ነው፡፡ በዘመኑ ከሃዲያን ብዙ ያሠቃዩት አባት ነው፡፡ ስሙ ቴዎዶስዮስ የሚባል መለካዊ ካሃዲ ሰው ነበር፡፡ እርሱም ወደ ደማስቆ ንጉሥ ዘይድ ዘንድ ሄዶ ብዙ እጅ መንሻን ሰጥቶ ለእስክንድርያ አገረ ገዥ ሆኖ ተሾመ፡፡ ከተሾመም በኋላ አባ ያቃቱንን ማሠቃየት ጀመረ፡፡ በየዓመቱ ግብር እያለ ሰባት ሺህ የወርቅ ዲናር ከአባታችን እየተቀበለ እግዚአብሔር እስካጠፋው ድረስ አባታችንን እጅግ አሠቀያቸው፡፡

በአባታችን ዘመን የብዙዎች ቅዱሳን አባቶች አባት የሆነው የአባ መቃርስ ቤተ ክርስቲያን ሕንፃዋ ተፈጸመ፡፡ በአንዲት ሌሊት ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ለአቡነ ያቃቱን ተገለጠላቸውና ፍዩጥ በሚባል አገር በአባ መቃርስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚያገለግል ዮሐንስ የሚባል ጻድቅ መነኮስ እንዳለ ነገራቸው፡፡ ዳግመኛም መልአኩ ዮሐንስን አስመጥተው በእሳቸው ቦታ እንዲሾሙት ነገራቸው፡፡ አባታችንም ሰዎችን ልከው ቅዱስ ዮሐንስን ካስመጡት በኋላ ሥራቸውን ሁሉ አስረክበውት በዚህች ዕለት በሰላም ዐርፈዋል፡፡
የአባ ያቃቱ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን

አቡነ ኢያሱ ዘጀር ሥላሴ:-አቡነ ኢያሱ በ15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በሰሜን ሸዋ የተነሡ ሲሆን ምንኵስናቸውን ከደብረ ሊባኖሱ ከዕጨጌ አቡነ መርሐ ክርስቶስ እንደተቀበሉ ታሪካቸው ያስረዳል። ትውልዳቸው አምሐራ ሳይንት ሲሆን መካነ ሱባኤ ወተመስጦ ጀር ቅድስት ሥላሴ ገዳምን የመሠረቱ ታላቅ ጻድቅ ናቸው።

እርሳቸው የመሠረቱት ጀር ቅድስት ሥላሴ ገዳም በግራኝ ወረራ ሳይወድም ስለቀረ ጥንታዊነቱን እንደጠበቀ ስለሚገኝና ታላቅ የበረከት ቦታ የቅዱሳን መናኸሪያ ስለሆነ ብዙዎች ነገሥታት ገዳሙን እየሔዱ ተሳልመው በረከት አግኝተውበታል። የአቡነ ኢያሱን ገድላቸውን ከአቡነ ሀብተ ማርያም ገድል ጋር ጣልያናዊው ራይኔሪ በሀገሩ ሮም እንዳተመው ቀሲስ ዶ/ር አምሳሉ ተፈራ ጽፈዋል። (0s valdo Raineri, Atti di Habta Māryam (†1497) e.di Iyasu (†1508), Santi Monaci Etiopici, Roma 1990 (Or ChrA 235), 165-265.)

የጻድቁ በዓለ ዕረፍታቸው ጥቅምት 16 በገዳሙ በታላቅ ድምቀት የሚከበር ሲሆን ስለ ጻድቁ ገድል በዝርዝር ተጽፎ አላገኘንም፣ ይልቁንም አቡነ ኢያሱ ስለገደሙት ታላቁ ጀር ቅድስት ሥላሴ ገዳም ነው በብዛት የሚነገረው።

አቡነ ኢያሱ ጀር ስላሴ ከመምጣታቸውም በፊት አስቀድመው በአቡነ ዜና ማርቆስ ገዳም፣ በደብረ ሊባኖስ እና በሌሎችም ገዳማት እየተዘዋወሩ በተጋድሎ ሲቀመጡ ‹‹ቦታህ ይኸ አይደለም›› ተብለው በሊቀ መላእክት በቅዱስ ሚካኤል መሪነት ነው ወደ ጀር ሥላሴ የመጡት። ወደ ቦታው ከመምጣታቸው በፊት አካባቢው ባእድ አምልኮ የተስፋፋበት ነበር፣ ነገር ግን ጻድቁ ሕዝቡን ክርስትናን አስተምረው ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር መልሰውታል። የምንኵስናን መሠረት ጥለውበታል። የአቡነ ኢያሱ የዕረፍታቸው ቦታ ደብረ ሊባኖስ ቢሆንም መታሰቢያቸው በመራቤቴ በሚገኘው አስደናቂ ገዳማቸው ይታሰባል። በገዳሙ በክብረ በዓሉ ወቅት ታቦት አይወጣም፣ ከበሮ አይመታም። ምክያቱም ፍጹም የጸሎት የጽሞና ቦታ ስለሆነ ነው።

መካነ ሱባኤ ወተመስጦ ጀር ቅድስት ሥላሴ አቡነ ኢያሱ ገዳም በተፈጥሮአዊ አቀማመጡ እጅግ አስደናቂ ሲሆን በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን እንሳሮ ወረዳ በደንቢ ግራርጌ ቀበሌ ጀር በሚባል ስፍራ የሚገኝ ታላቅ ገዳም ነው። ገዳሙ ከአዲስ አበባ 137 ኪ.ሜ ከደብረ ብርሃን 91 ኪ.ሜ ከለሚ ከተማ 4 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኝ ከጥንት ጀምሮ ስዉር ገዳም ሆኖ የቆየ ነው። ገዳሙ በ1495 ዓ.ም በዐፄ ናኦድ ዘመነ መንግሥት በቅዱስ ሚካኤል መሪነት ጻዲቁ አቡነ ኢያሱ ወደዚህ ቦታ መጥተው መሥርተውታል። በጅረት ታጂቦ ስለሚገኝ ነው ጀር ሥላሴ የተባለው። የክብር ባለቤት ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በራእይ አስመልክቶ ከመሠረታቸው ገዳማት አንዱ ነው። አቡነ ኢያሱም በገዳሙ በሚገኘው አንድ ትልቅ ዋርካ ሥር ቆመው ይጸልዩ እንደነበር አባቶች ያስረዳሉ።

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

24 Oct, 15:27


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ጥቅምት 15-ይኽቺ ዕለት የቅዱሳን ሐዋርያት የዕረፍታቸው መታሰቢያ ትሆን ዘንድ አባቶቻችን ሥርዓት ሠሩ፡፡
ከኒቆምድያ አገር ቅዱስ ቢላሞን በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡
ቁጥራቸው 158 የሆኑ የቅዱስ ቢላሞን ማኅበርተኞችም አብረውት በሰማዕትነት ተሰይፈዋል፡፡
ሰማዕቱ ቅዱስ ቢላሞን፡- ይህም ቅዱስ አባቱ ጣዖት አምላኪ ነው እናቱ ግን ክርስቲያን ናትና ልጇን ቢላሞንን በጥበብ አሳደገችው፡፡ ቢላሞንም ስሙ አርማላስ ከተባለ ቄስ ጋር ተገናኘና በጌታችን ማመንን አስተማረው፡፡ አስተምሮትም ሲጨርስ የክርስትናን ጥምቀት አጠመቀው፡፡ ቢላሞንም ከተጠመቀ በኋላ በጾም በጸሎት በእጅጉ ይተጋ ጀመር፡፡ ታላላቅ የሆኑ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን እስኪያሳይ ድረስ በመንፈሳዊ ተጋድሎ ኖረ፡፡ በአንዲት ዕለትም ለዐይኖቹ መድኃኒት እንዲያደርግለት አንድ ዐይነ ሥውር ሰው ወደ ቅዱስ ቢላሞን መጣ፡፡ ይህን ጊዜ ቅዱስ ቢላሞን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያለ በዐይነ ሥውሩ ዐይኖች ላይ የመስቀል ምልክት ሲያደርግ ያንጊዜ የዐይነ ሥውሩ ዐይኖች በሩ፡፡
ከሃዲና አረመኔ የሆነው የአገሪቱም ንጉሥ ዐይኖቹ የበሩለትን የዚያን ሰው ዜና በሰማ ጊዜ ሰውየውን ወደ እርሱ አስቀረበውና ‹‹ዐይኖችህን ማን አዳነህ?›› አለው፡፡ ሰውየውም ‹‹ቅዱስ ቢላሞን ፈወሰኝ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ እያለ በመስቀል ምልክት አማተበብኝ ያንጊዜም ማየት ቻልኩ›› ብሎ ከነገረው በኋላ ‹‹እኔም ክርስቲያን ነኝ፣ በቅዱስ ቢላሞን አምላክ አምኛለሁ›› ብሎ መሰከረ፡፡ ንጉሡም በዚህ በጣም ተቆጥቶ የሰውየውን ራስ በሰይፍ አስቆረጠውና የሰማዕትነትን የድል አክሊል እንዲቀዳጅ አደረገው፡፡
ከዚህም በኋላ ንጉሡ ወታደሩን ልኮ ቅዱስ ቢላሞንን አስመጣውና ለ ሃይማኖቱ ጠየቀው፡፡ ቅዱስ ቢላሞንም ‹‹እኔ መድኃኒትና ሕይወት በሆነ ሰማይንና ምድርንም በፈጠረ በኢየሱስ ክርስቶስ የማምን ክርስቲያን ነኝ›› ብሎ በከሃዲውና አረመኔው ንጉሥ ፊት ታመነ፡፡ ንጉሡም ብዙ ሽንገላዎችን በመሸንገል ከእምነቱ ሊያስወጣው ብዙ አባበለው፡፡ ብዙ ቃልኪዳንም ገባለት፡፡ ነገር ግን ቅዱስ ቢላሞን ቃሉን እንዳልሰማው ሲያውቅ በእርሱ ላይ ተቆጥቶ ድምጹን ከፍ አድርጎ ‹‹የምነግርህን ምክሬን ካልሰማኸኝ ጽኑ በሆኑ ልዩ ልዩ ሥቃዮች አሠቃይሃለሁ›› አለው፡፡ ቅዱሱም ይህን ጊዜ ‹‹እኔ አንተ ከምታሠቃየኝ ሥቃይ ፈርቼ ሃይማኖቴን ለውጬ ፈጣሪዬን አልክድም›› አለው፡፡ ንጉሡም በታላቅ ቁጣ ሆኖ ለብዙ ቀናት ሲያሠቃየው ቆየ፡፡ ጽኑ የሆነ ግርፋትን አስገረፈው፣ በስቅላትም አሠቃየው፣ በባሕር ውስጥ አሰጠመው፣ በሚነድ እሳት ውስጥ ወረወረው ነገር ግን ቅዱስ ቢላሞንን ጌታችን በመከራዎቹ ሁሉ ጽናትንና ብርታትን ይሰጠው ቁስሎቹንም ይፈውስለትና ጤነኛ ያደርገው ነበር፡፡
በመጨረሻም ቅዱስ ቢላሞን በታላቅ ሥቃይ ውስጥ ሳለ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ቢላሞንን ባጠመቀው ቄስ አምሳል ተገለጠለትና ‹‹የመረጥኩህ ቢላሞን ሆይ! ደስ ይበልህ እነ ሰማያዊ መንግሥትን አዘጋጅቼልሃለሁና›› አለው፡፡ የንጉሡ ጭፍሮችም ይህንን የደስታ ቃል በሰሙ ጊዜ ክብር ይግባውና በጌታችን አመኑ፡፡ በንጉሡም ፊት የጌታችንን ክብር ሲመሰክሩ ንጉሡ በቁጣ በሰይፍ ራስ ራሶቻቸውን አስቆረጣቸው፡፡ ቁጥራቸው 158 የሆኑ ሰዎች ከቅዱስ ቢላሞን ጋር ተሰይፈው የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ፡፡
ቅዱስ ቢላሞን ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!
ዳግመኛም ይህቺ ዕለት የቅዱሳን ሐዋርያት የዕረፍታቸው መታሰቢያ ትሆን ዘንድ አባቶቻችን ሥርዓት ሠሩ፡፡ የእነዚህም የከበሩ ቅዱሳን ሐዋርያት የዕረፍታቸው በዓል በአጭሩ እንደሚከተለው ነው፡-
የዐሥራ ኹለቱ ሐዋርያት ሰማዕትነት፡- ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ምስክሮች (ሰማዕትታ) የሚለውን ስያሜ መጀመሪያ የተጣቸው ለሐዋርያቱ ነው፡፡ ‹‹በኢየሩሳሌም፣ በይሁዳ፣ በሰማርያ እስከ ዓለም ዳርቻ ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ›› ብሏቸዋልና፡፡ ሐዋ 1፡8-22፡፡ በዚኽም አምላካዊ ቃል መሠረት ሁሉም ሐዋርያት ወንጌልን የሰበኩት በብዙ ሰማዕትነት ነው፡፡ ዐሥራ ኹለቱም ሐዋርያት ሰማዕታት ናቸው፡፡ 36ቱ ቅዱሳት አንስት፣ 72ቱ አርድእት በአጠቃላይ የሐዲስ ኪዳንን ክርስትና በዓለም ያስፋፉት መቶ ሃያውም ቤተሰብ ሰማዕትነትን ተቀብለዋል፡፡ በዚኽም መሠረት፡-
1. ቅዱስ ጴጥሮስ፡- ገዳዮቹን ‹‹እኔ እንደጌታዬ ልሰቀል አይገባኝም እንደ ጌታዬ ሳይሆን ቁልቁል ዘቅዝቃችሁ ስቀሉኝ›› ብሎ በመለመን ሐምሌ 5 ቀን 67 ዓ.ም ቁልቁል ተሰቅሎ ሰማዕትነቱን በድል ፈጽሟል፡፡
2. ቅዱስ ዮሐንስ፡- ጣዖት አምላኪዎች በፈላ ውኃ እያቃጠሉ ብዙ ካሰቃዩትና በፍጥሞ ደሴት ካጋዙት በኋላ ጥር 4 ቀን ወደ ብሔረ ሕያዋን ሔደ፡፡
3. ቅዱስ እንድርያስ፡- ከክብሩና ከፍቅሩ አንጻር ‹‹ጌታዬ በተሰቀለበት ዐይነት መስቀል አትስቀሉኝ›› ብሎ ገዳዮቹን ለምኖ የእንግሊዝኛው ኤክስ (X) ፊደል ቅርጽ ባለው መስቀል ላይ ተሰቅሎ ታኅሣሥ 4 ቀን በክብር ዐረፈ፡፡
4. ቅዱስ ፊሊጶስ፡- ኅዳር 18 ቁልቁል ተሰቅሎ ሰማዕትነቱን ፈጽሞ የድል አክሊልን ተቀዳጀ፡፡
5. ቅዱስ በርተሎሜዎስ፡- መስከረም 1 ቀን አሸዋ በተሞላ ትልቅ ከረጢት ውስጥ ታሥሮ ከነሕይወቱ ባሕር ውስጥ ተጥሎ በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡
6. ቅዱስ ቶማስ፡- እጅና እግሩን ታሥሮ ቆዳው እንደፍየል ቆዳ ተገፎ ስልቻ ተስፍቶበት በውስጡም አሸዋ ተሞልቶ ራሱን ቶማስን አሸክመውት ገበያ ለገበያ ሲያዞሩት ከዋሉና ቁስሉንም በጨው እያሹ ብዙ ካሠቃዩት በኋላ በመጨረሻ በ72 ዓ.ም ግንቦት 26 ቀን አንገቱን በሰይፍ ቆርጠውት ሰማዕተነቱን በድል ፈጽሟል፡፡
7. ቅዱስ ማቴዎስ፡- ጥቅምት 12 ቀን አንገቱን ተሰይፎ ሰውነቱም ብዙ ቦታ ተቆራርጦ ሥጋው ለሰማይ ወፎች ተሰጥቶ በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡
8. ቅዱስ ያዕቆብ ወልደ እልፍዮስ፡- በንጉሥ ቀላውዴዎስ ትእዛዝ ክፉዎች አይሁድ በድንጋይ ወግረው ገድለውት ሰማዕትነቱን የካቲት 10 ቀን በድል ፈጸመ፡፡
9. ቅዱስ ያዕቆብ ወልደ ዘብዴዎስ፡- ንጉሥ ሄሮድስ ሰይፍ መዞ አንገቱን ቆርጦት ሚያዝያ 17 በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡
10. ቅዱስ ናትናኤል፡- አረማውያን ሐምሌ 10 ቀን አንገቱን በሰይፍ ቆርጠውት ሰማዕትነቱን በክብር ፈጸመ፡፡
11. ቅዱስ ማትያስ፡- አረማውያን በብረት አልጋ ላይ አስተኝተው ከሥሩ 24 ቀን ሙሉ እሳት አንድደው ካቃጠሉት በኋላ መጋቢት 8 ዐረፈ፡፡
12. ቅዱስ ታዴዎስ፡- ክፉዎች አረማውያን በብዙ አሠቃቂ መከራዎች ካሰቃዩት በኋላ ሐምሌ 2 ቀን በሰማዕትነት ገድለውታል፡፡
የከበሩ ቅዱሳን ሐዋርያት ከዕረፍታቸው መታሰቢያ በዓል ረድኤት በረከት ይክፈሉን

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

24 Oct, 05:11


በሀገራችን የሚገኘው የረድኡ ሐዋርያ የቅዱስ ፊሊጶስ ካቴድራል-
"ደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል!"
ይኸውም ሐዋርያ ቅዱስ ፊሊጶስ እግዚአብሔር ልኮት ኢትዮጵያዊውን ጃንረባ ባኮስን ያጠመቀው ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ታረክ፣ ምስረታ እና ልደት የሚያወሳ የታሪክም ሆነ የቤተክርስቲያን ምሁር ሐዋርያው ቅዱስ ፊልጶስን እና ቅዱስ ባኮስን ሳያነሳ ማለፍ አይቻለውም፡፡ ምክንያቱም በኢትዮጵያ የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል እንዲሰበክ መነሻ የሆኑ ለእኛ ለኢትዮጵያውያን የወንጌል አባታቶቻችን ስለሆኑ ነው፡፡

ከሰባቱ ሊቀ-ዲያቆናት አንዱ ሆኖ የተሾመው ቅዱስ ፊልጶስ ትውልዱ ኢሲዶር ከምትባል የቄሳሪያ የወደብ ከተማ ሲሆን በቅዱስ እስጢፋኖስ ሞት ምክንያት ደቀመዛሙርት ከኢየሩሳሌም እስከተበተኑ ድረስ በኢየሩሳሌም ከሐዋርያት እግር ስር ሆኖ ተምሯል፡፡ ከመንፈስ ቅዱስ መገለጥ በኋላ ሐዋርያት በኢየሩሳሌም ባደረጉት የመጀመሪያ የስብከት አገልግሎት በርካታ ምዕመናን አምነው ተጠመቁ፤ የምዕመናኑ ቁጥር እጅግ በመጨመሩ እና የአገልግሎቱ ዘርፉም እየበዛ በመሄዱ አገልጋዮችን መጨመር አስፈላጊ መሆኑን በአመኑ ጊዜ ሐዋርያት ቀደም ሲል በአእርድትነት ሲያገለገሉ ከነበሩት መካከል ሰባቱን ሊቀ-ዲያቆናት ለመጋቢነት መረጡ፡፡ ምዕመኑን በመጋቢነት እንዲያገለግሉ ከተመረጡት ሰባቱ ሊቀ-ዲያቆናት መካካል አንዱ ቅዱስ ፊልጶስ ሐዋርያ ዘሰማርያ ወኢትዮጵያ ነው፡፡ በ35ዓ.ም. ቅዱስ እስጢፋኖስ በአይሁድ እጅ በሰማዕትነት ማለፉ ተከትሎ በኢየሩሳሌም የነበሩት ማኅበረ ምዕመናን ተበተኑ፤ ቅዱስ ፊልጶስም ጊቶን ወደ ምትባል የስሞን መሠርይ የትውልድ ስፍራ ወደሆነች የሰማርያ ከተማ ሄደ፡፡ በዚህያም ሐዋርያዊ አገልግሎቱን በማጠናከር በእርካታ ምዕመናን በኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነት አምነው እንዲጠመቁ አስችሏል፡፡ በተለይ በጥንቆላ ግብሩ የሚታወቀውን ሲሞን መሠርይን በማሳመን ማጥመቁን ቅዱስ መጽሐፍ ዘግቦለታል፡፡ ሐዋ 8፡13።

በሰማርያ ሳለ የጌታም መልአክ ፊልጶስን ተነሥተህ በደቡብ በኩል ከኢየሩሳሌም ወደ ጋዛ በሚወርደው በምድረ በዳው መንገድ ሂድ አለው፡፡ እርሱም ተነሥቶ ሂደ፡፡ እነሆ የኢትዮጵያ ንግሥት የህንደኬ ባላሟል እና የሀብት ንብረቷ ሁሉ አዛዥ የሆነ አንድ ኢትዮጵያዊ ጃንደረባ አገኘ፡፡ ይህም ሰው ሊሰግድ ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ ነበር፡፡ ሲመለስም በሠረገላ ተቀምጦ የነቢዩን የኢሳይያስን መጽሐፍ ያነብ ነበር፡፡ መንፈስም ፊልጶስን “ሂድ ወደዚህ ሠረገላ ቅረብ” አለው፡፡ ፊልጶስም ፈጥኖ ወደ ሠረገላው ሂደ፤ ጃንደረባውም የነቢዩን የኢሳይያስን መጽሐፍ ሲያነብ ሰምቶ “ለመሆኑ የምታነበውን ታስተውለዋለህን?” አለው፡፡ ጃንደረባውም “የሚያስረዳኝ ሰው ሳይኖር እንዴት አድርጌ አስተውለዋለሁ” አለው፤ ቅዱስ ፊልጶስም ስለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል ሰበከለት፡፡ በመጓዝ ላይ ሳሉም ውሃ ካለበት ስፍራ ደረሱ ጃንደረባውም “እነሆ ውሃ እዚህ አለ ታዲያ እንዳልጠመቅ የሚከለክለኝ ምን ነገር አለ?” አለው፡፡ ፊልጶስም “በፍጹም ልብህ ካመንህ መጠመቅ ትችላለህ” አለው፡፡ ጃንደረባውም ‹‹ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ አምናለሁ›› ሲል መለሰለት፤ ሠረገላውም እንዲቆም አዘዘ፡፡ ከዚያም ሁለቱም አብረው ወደ ውሃው ወረዱ፤ ፊልጶስም ጃንደረባውን አጠመቀው፡፡ ከውሃውም በወጡ ጊዜ የጌታ መንፈስ ፊልጶስን ነጥቆ ወደ አዛጦን ወሰደው። ሐዋ 8፣ 26-39። ወደ ቂሣርያ እስኪመጣ ድረስም በእየከተሞቹ ሁሉ እየተዘዋወረ ወንጌልን ሰብኳል፡፡ በቂሳርያ ሳለ ሚስት አግብቶ 4 ሴቶች ልጆችን ወለደ፤ እነርሱም ሀብተ ትንቢት የተሰጣቸው ደናግናል ነበሩ፡፡ ሐዋ 21፣8። በረጅም የወንጌል አገልግሎቱ ብዙ አይሁድን እና ሳምራዊያንን ወደ ክርስትና መልሶ ጥቅምት 14 ቀን በሰላም ማረፉን የታረክ መዛግብት ይናገራሉ፡፡
✞ ✞ ✞

አ.አ ኮልፌ አጠናተራ የሚገኘው የቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ሊመሠረት የቻለው በወቅቱ በአዲስ አበባ አድባራት ከፍተኛ የሆነ የቀብር ቦታ እጥረት ስለነበር 700 የሚደርሱ እድርተኞች መዘጋጃ ቤት በመሄድ ቀብር ቦታ ይሰጠን በማለት በማመልከታቸው ምክንያት ኮልፌ አጠናተራ እስላም መቃብር ፊት ለፊት ያለው ባዶ መሬት እንዲወስዱ ተፈቀደላቸው፡፡ ነገር ግን የተፈቀደላቸው ቦታ አቶ ስፍር መዝጊያ የሚባሉ ግለሰብ ይኖሩበት ስለነበር እድርተኞቹ ቦታውን ለቀብር ቦታ እንደሚፈልጉት ገለጹላቸው፡፡ አቶ ስፍርም በህልሜ እዚህ ቦታ መኖር እንደማልችል ታይቶኝ ነበር በማለት በ45,000 ብር በመሸጥ ለቀቁላቸው፡፡ ከዚህም በመቀጠል ፍቃድ ለማግኘት ወደ ቤተክህነት የእድሩ ሊቀመንበር አቶ አበባው ግዛው እና አቶ ወልደ ሚካኤል እና ሌሎችም በመሆን በጊዜው የኢ/ኦ/ተ ፓትርያርክ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ተክለሃይማኖት በመሄድ ስለሁኔታው በግልጽ ቦታውን እንዲባርኩላቸው ጠየቁ፡፡ አባታችንም ክርቲያን ቤተክርስቲያን በሌለበት ቦታ አይቀበርም ብለው በመመለሳቸው የእድሩ አባላት በአማኑኤል ቤተክርስቲያን ተሰብስበው ተወያዩ፡፡ በውይይታውም አቶ ስፍር ይኖሩበት የነበረውን ቤት እንደቤተክርስቲያን ለመጠቀም በመነጋገር ወደ አቡነ ተክለሃይማኖት ሄደው ሀሳባቸውን ገለፁላቸው፡፡ ብፁእ አባታችንም ፈቃዳቸው ሆኖ ጊዜያዊ ወደፊት ግን ቤተክርስቲያን ስሩለት በማለት ቤተክርስቲያን ለመሆን የሚያባውን ጸሎት በማድረግ ከመኖርያ ቤተ ወደ ቤተክርስቲያን የካቲት 20 ቀን 1978 ዓ.ም ሃያ አራት ሊቃነ ጳጳሳት በማስከተል የዲያቆኑን የቅዱስ ፊልጶስ ታቦትን አምጥተው ቤተከልርስቲያኑን መሠረቱት፡፡ ቤተክርስቲያኑን እንዲያስተዳድሩ ለሊቀ ካህናት ክፍሌ ገ/መስቀል ጽላቱን ደግሞ ለጳውሎስ ካህን ለነበሩት ለቄስ ዘመንፈስ በአደራ አስረከቧው፡፡ በዕለቱም ጥቅምት 14 እረፍቱ፣ የካቲት 20 ቅዳሴ ቤቱ በጋራ እንዲያከብሩ በማሳሰብ ተናገሩ፡፡ ከተወሰነ ጊዜ በኃላም በቆርቆሮ የተሰራ መቃኞ በማዘጋጀት ታቦቱ ወደዚያ ገባ፡፡ አሁን ላይ በዚህ መልኩ በሚያምር ሁኔታ የተሠራው የደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል ተሠርቶ አልቆ የተመረቀው ጥቅምት 14 ቀን 2000 ዓ.ም ሲሆን አሁን ላይ ካቴድራሉ 34 ዓመት ሆኖታል፡፡

የቅድስት ሀገራችን ኢትዮጵያ ባለውለታ የሆነው የጥምቀት የክርስትና አባታችን የሐዋርያው የቅዱስ ፊልጶስ በዓለ ዕረፍት ጥቅምት 14 ቀን አዲስ አበባ ኮልፌ አጠና ተራ በሚገኘው በደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል በደመቀ ሁኔታ ይከበራል። እርስዎም ከቦታው ተገኝተው የበረከቱ ተሣታፊ ይሆኑ ዘንድ በአምላከ ቅዱስ ፊልጶስ ስም በክብር ጠርተንዎታል።
(የካቴድራሉ ሰንበት ት/ቤት)

የሐዋርያ የቅዱስ ፊሊጶስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!

አምላከ አቡነ አረጋዊ፣ አምላከ ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ
አምላከ ቅዱስ ፊሊጶስ፣ በሰማዕትነት ያረፉትን ወገኖቻችንን ከሰማዕታት ማኀበር ይደምርልን! እኛንም እስከመጨረሻው እርሱን በማመን ያጽናን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

24 Oct, 05:11


ደብረ ዳሞ ላይ አቡነ አረጋዊ በዚኽች ዕለት የተሰወሩበት ቦታ ላይ የተሠራው ቤተ መቅደስ!
"እግዚአብሔር ደብረ ሃሌሉያ የተባለች ደብረ ዳሞን መርጧታልና ለአቡነ አረጋዊ ማደሪያው ትሆን ዘንድ ወዷታልና እርሷ ለዘለዓለሙ ማደሪያውና መሠወሪያው ናት" ቅዱስ ያሬድ ለደብረ ዳሞ የዘመረላት ዝማሬ ነው።

አቡነ አረጋዊ፣ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ብርሃኗ የሆነ ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ እና ንጉሥ በዐፄ ገብረ መስቀል ሦስቱ ቅዱሳን አብረው ብዙ ታሪኮችን ፈጽመዋል፡፡ ገዳማትን ላይ በመዟዟር ቅዱስ ያሬድ ዜማን ሲያስተምር ንጉሡ ደግሞ የቤተ ክርስቲያንን ይዞታ ያስፋፉና ቋሚ መተዳደሪያ ይሰጡ ገዳማቱን ያጠናክሩ ነበር፡፡ አቡነ አረጋዊ ደግሞ አብረው ምኩስናን ያስፋፉ ነበር፡፡ ሦስቱም ይህን ተግባራዊ እንዳደረጉ ለማሳያ ይሆን ይሆን ዘንድ ቅዱስ ያሬድ 3 ዓመት ዝማሬ መዋሥዕት ያስተማረባትንና ዛሬም ድረስ ማስመስከሪያ የሆነችውን እጅግ ጥንታዊቷን ዙር አባ ጽርዓ አርያም አቡነ አረጋዊ ገዳምን እንደምሳሌ ማየት እንችላለን፡፡ አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ያሬድ በዘንዶ ታዝለው ዓምባው ላይ ከወጡ በኋላ ለንጉሡ ለዐፄ ገብረ መስቀል ደግሞ አቡነ አረጋዊ ተራራውን ባርከው ከፍለው መንገድ አበጅተውላቸው ወደ ዓምባው ወጥተው ሦስቱም በዚያ በጋራ ኖረው ብዙ መንፈሳዊ ሥራን ሠርተዋል፡፡

ረድኤት በረከታቸው ይደርብንና አቡነ አረጋዊ ያደረጉት ተአምር ይህ ነው፡- ከዕለታት በአንደኛው ቀን የክቡር አባታችን የአረጋዊ በዓል በሚከበርበት ዕለት መነኮሳቱ ከተራራው ግርጌ ወይም ከገመዷ ሥር ለተሰበሰቡት ሰዎች የዝክር ጠላ ሲያወርዱ የጠላው እንስራ ከላይ ወደታች ወደቀ፡፡ ነገር ግን የእንስራው ክዳኗ እንኳን ሳይከፈት ከወደቀችም በኋላ 50 ክንድ ያህል መሬት ለመሬት ከተንከባለለች በኋላ በስተመጨረሸ ልክ ሰው እንዳስቀመጣት ሆና ተቀመጠች፡፡ ያችም የጠላ ማድጋ ከዚያ ትልቅ ገደል ላይ ወድቃ ምንም መሰበር እንዳልደረሰባት ጠላውም ምንም ጠብ እንዳላለ ባዩ ጊዜ በዚያየተሰበሰቡ ሁሉ ይህን አይተው በእጅጉ አደነቁ፡፡ አባታችን አቡነ አረጋዊ የባረከው የዝክሩ በረከት ነው በማለት ሁሉም ክዳኑን ከፍተው ከመጠጣት ይልቅ እንደቀባ ቅዱስ ሰውነታቸውነ ተቀቡት፡፡ ብረት እንኳን ከከፍታ ቦታ ላይ ወደ መሬት ቢወድቅ ይጣመማል የዚህ ማድጋ ነገርስ ድንቅ ነው እያሉ አደነቁ፡፡ የዝክሩንም ጠላ የቀመሱት ድውያን ተፈወሱበት፡፡ ሕዝቡም የአቡነ አረጋዊንም ዝክር በይበልጥ ማዘከር ጀመሩ፡፡ እኅት ወንድሞች አስተውሉ! የቅዱሳን አባቶች ገድላቸው የተነበበት ውሃ፣ ለዝክራቸው የተዘጋጀው ጠላ ድኅነተ ሥጋን ድኅነተ ነፍስን ያስገኛል፡፡

የአባታችን የአቡነ አረጋዊ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

23 Oct, 12:32


እየበተነ ሰው ወርቁን ለማንሳት ሲሄድ በፍጥነት ወደ ቤተ ክርስቲያን አድርሰውታል፡፡
የቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!
+ + +
ሰማዕቱ ቅዱስ ሙሴ፡- ሙሴ የተባለው ይህ ጻድቅ ታሪኩ ከሙሽራው ገብረ ክርስቶስ ታሪክ ጋር ይመሳሰላል፡፡ ዕረፍታቸውም በአንድ ቀን ነው፡፡ የሙሴ ወላጆቹ ከሮም ሀገር የሆኑ እግዚአብሔርን የሚያመልኩና የሚፈሩ ደጋግ ባለጸጎች ናቸው፡፡ በጾም በጸሎት የታወቁ ለድኆችና ጦም አዳሪዎችም የሚመጸውቱ ነበሩ፡፡ ልጅ ግን አልነበራቸውምና ተስለው ልጅ ሲወልዱ ስሙን ሙሴ አሉት፡፡ ጥበብ መንፈሳዊና ጥበብ ሥጋዊ እያስተማሩ አሳደጉትና ከሮም አገር ታላላቅ ወገን የሆነችን ልጅ በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት አጋቡት፡፡
በጫጉላ ቤትም ሳለ የልጅቱን እጅግ ያማረ ውበት አይቶ ይህ ሁሉ ነገር ጠፊ ነው ብሎ አሰበ፡፡ የሁለቱንም ድንግልና እንደጠበቁ ሚስቱንም ‹‹በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እስከምንገናኝ ድረስ ደህና ሁኚ›› ብሎ ከጫጉላ ቤቱ ወጥቶ ሄደ፡፡ የለበሰውንም የክብር ልብስ ሸጠውና ለድኆችና ጦም አዳሪዎች መጸወተው፡፡ እርሱም ፍጹም ድኃ ሆኖ ቁራሽ እየለመነ እርሱን እየተመበገ እስከ ሀገረ ሮሀ ድረስ ሄደ፡፡ ሀገረ ሮሀ በደረሰም ጊዜ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ለንጉሡ አቃርዮስ የተላኩለትን ቅዱሳት ሥዕላት ተሳለመና ወጥቶ ኑሮውን ከድኆችና ለምስኪኖች ጋር አደረገ፡፡ እስከ ምሽት ድረስም እየጾመ በጸሎት ይተጋ ነበር፡፡ ለምኖ የሚያገኘውን ለራሱ ትንሽ ብቻ አስቀርቶ ብዙውን ይመጸውተዋል፡፡
አባቱ አውፊምያኖስ መጥፋቱን ሲሰማ ብዙ ገንዘብ በመስጠት ባሮቹን ሁለት ሁለት አድርጎ በየሀገሩ በመላክ አስፈለገው፡፡ ሁለት የአባቱ አገልጋዮችም ቅዱስ ሙሴን አግኝተውት ነበር ነገር ግን አላወቁትም፡፡ ይልቁንም አባቱ በመንገድ ለምታገኙት ድኆች ሁሉ ስጡ ብሎ ያዘዛቸውን ገንዘብ ሰለድኆች ሲሰጡ ለሙሴም አብረው ሰጥተውት አለፉ፡፡ ሙሴ ግን የአባቱ አገልጋዮች መሆናቸውን ዐውቆ ከአባቱ ባሮች ምጽዋትን ስለመቀበሉ ፈጣሪውን አመሰገነ፡፡ ከዚህም በኋላ ተጋድሎውን በማብዛት እስከ ሦስት ቀን ድረስ ይጾም ጀመር፡፡ እመቤታችንም ለአንድ አገልጋይ ካህን ተገልጣ የቅዱስ ሙሴን ታሪክና ጽድቁን ነግራቸው ከነዳያኑ ለይተው ወደ ቤተ ክርስቲያኑ እንዲያስገቡት ነገረቻቸው፡፡ ካህኑም ሄደው እመቤታችን እንደላከቻቸው ነግረውት ወደ ውስጥ አስገብተው በዓት ሰጡት፡፡ ቅዱስ ሙሴም ‹‹ማንነቴ ከታወቀብኝ ከዚህ አገር አልኖርም›› በማለት ወደ ቅዱስ ጳውሎስ ሀገር ጠርሴስ ሊሄድ አስቦ በሌሊት ተነሠቶ በመርከብ ተሳፈረ፡፡
ነገር ግን መርከቢቷን ታላቅ ማዕበል አናወጣትና ወዴት እንደሄዱ ሳያውቁት ሮም ሀገር ወደብ ደረሱ፡፡ ቅዱስ ሙሴም ‹‹ፈቃደ እግዚአብሔር ከአባቴ ደጅ ካመጣኝ ማንነቴ ለማንም ሳልገልጥ በአባቴ ደጅ ተጥዬ ድኃ ተመጽዋች ሆኜ ለመኖር በሕያው ክርስቶስ ስም እምላልሁ›› ብሎ በአባቱ ደጅ እየለመነ ተቀመጠ፡፡ አባቱም አንድ ቀን በብዙ በአገልጋዮቹ ታጅቦ ወደ ቤቱ ሲገባ አገኘውና ከፈረሱ ላይ እንዳለ አባቱን በደጁ ላይ መጠለያ እንዲያሠራለትና የአገልጋዮቹን ትራፊ ፍርፋሪ እንዲመገብ ለመነው፡፡ አባቱም የልጁን መሰደድ አስታውሶ በተቃጠለ ልብ ሆነ አለቀሰና ፈቃዱን ፈጸመለት፡፡ ሁለተኛም ከአገልጋዮቹ አንዱን ጠርቶ ‹‹ለዚህ ምስኪን ድኃ ሰው በሚያስፈልገው ነገር ሁሉ እርዳው›› ብሎ አዘዘለት፡፡ ቅዱስ ሙሴም ያንን የታዘዘለትን አገልጋይ ‹‹ከቅዳሜና እሁድ ውጭ ምግብ አታምጣልኝ›› ብሎት በሰንበት ቀናት ብቻ ትንሽ እየተመገበ በእንደዚህ ያለ ተጋድሎ በአባቱ ደጅ ወድቆ ለ12 ዓመት ተቀመጠ፡፡
ጌታችንም ተገልጦለት ትልቅ ቃልኪዳን ሰጠውና ከአራት ቀን በኋላ ከቅዱሳኑ ሁሉ ጋር ተመልሶ መጥቶ እንደሚወስደው ነግሮት ዐረገ፡፡ ቅዱስ ሙሴም ያገለግለው የነበረውን የአባቱን አግልጋይ ወረቀትና ቀለም እንዲያመጣለት ነግሮት አመጣለትና ታሪኩን ሁሉ ራሱ ጽፎ በእጁ እንደያዘው በዕለተ እሁድ ዐረፈ፡፡ ሊቀ ጳጳሳቱና ኤጲስ ቆጶሳቱ ሕዝቡም ሆነው ከቅዳሴ በኋላ ከሰማይ ድምፅ ሰምተው ተሸበሩ፡፡ ከብዙ ምህላ በኋላ ወደ አውፊምያኖስ ደጅ እንዲሄዱና የቅዱስ ሙሴን አስክሬን በክብር እንዲያኖሩ ተነገራቸው፡፡ ሊቀ ጳጳሳቱም የቅዱስ ሙሴን አባት አውፊምያኖስን ጠርቶ ‹‹ከእርሱ እንባረክ ዘንድ በሕይወት እያለ ለምን አልነገርከንም?›› አሉት፡፡ አባቱም እጅግ ደንግጦ እንዲህ ዓይነት ሰው በቤቱ እንደሌለ ነገረው፡፡ እቤቱ ሄደውም የቅዱስ ሙሴን ሥጋ ባረፈበት መጠለያ አገኙት፡፡ ስለራሱ የጻፈውንም ጽሕፈት ሊቀ ጳጳሳቱ በሕዝቡ ሁሉ ፊት አነበባት ሁሉም ታላቅ ልቅሶን አለቀሱ፡፡ ሊቀ ጳጳሳቱም ቅዱስ ሥጋውን በክብር ገንዘውት ወደ ጴጥሮስና ጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን ወሰዱት፡፡ ሥጋውን የተሣለሙ ብዙ ደውያን ተፈወሱ፡፡ እጅግ ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራቶችም ተፈጸሙ፡፡ የቅዱስ ሙሴ ዕረፍቱ ታሪኩ አንድ ዓይነትና ተመሳሳይ ከሆነለት ከቍስጥንጥንያው ሰማዕት ከሙሽረው ከቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ዕረፍት ጋር ጥቅምት 14 ቀን ሆነ፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!
+ + +
አቡነ አረጋዊ፡- በምንኩስና ስማቸው ዘሚካኤል ተብለው የሚጠሩትና ከተሰዓቱ ቅዱሳን ውስጥ አንዱ የሆኑት አቡነ አረጋዊ አባታቸው ይስሃቅ የሮም ነገሥታት ወገን ስለሆኑ ከነገሥታት ወገን የምትሆን ሚስት ቢያጩለትም እምቢ ብሎ ወደ ታላቁ አባት አባ ጳኩሚስ ገዳም ገባ፡፡ አቡነ አረጋዊም እንዲያመነኩሰው ቢጠይቀው መጀመሪያ ላይ ‹‹አንተ የንጉሥ ልጅ ስለሆንክ የአባትህ የመንግሥቱ ወራሽ መሆን ነህና መመንኮስ ትችላለህን?›› በማለት ዓለምን ንቆና ቆርጦ የመጣ መሆኑን በተለያዩ ፈተናዎች ካረጋገጠ በኋላ አመነኮሰው፡፡ በመነኮሰበትም ጊዜ ዕድሜውም 14 ዓመት ነበር፡፡ በዚህም ዘሚካኤል (አቡነ አረጋዊ) ከእንጦንስና ከመቃርስ ከጳኩሚስም የምንኩስና ወይም መንፈሳዊ ሐረግ 4ኛ ትውልድ ሆኑ፡፡
የአባ ዘሚከኤል እናት ንግሥት ዕድና የልጇን ዜና ሰምታ ወደ ገዳሙ መጥታ እርሷም አባ ጳኩሚስ ግንቦት 12 ቀን ከዓረፈ በኋላ በእርሱ ተተክቶ ገዳሙን ያስተዳድር በነበረው በአባ ቴዎድሮስ እጅ መንኩሳ የእርሱ እናትና የጳኩሚስ እኅት ካሉበት ከሴቶች ገዳም ገባች፡፡ የንጉሡ ልጅ በሕጻንነት ምንኩስና መቀበሉን የሰሙ 8 ደጋግ ቅዱሳን ከያሉበት ተሰባስበው አባ ጳኩሚስ ገዳም ገብተው ከአባ ዘሚካኤል ጋር ተገናኙ፡፡ አባ ጳኩሚስን ‹‹እኛንም እንደዚህ ሕፃን አመንኩሰን›› አሉትና አመንኩሶ ባረካቸው፡፡ ሁሉንም ነገር ከአባ ጳኩሚስ ጠንቅቀው እየተማሩ ለብዙ ዓመታት ከእርሱ ጋር ተቀመጡ፡፡ እነዚህም ቅዱሳን የቁስጥንጥንያው አባ ሊቃኖስ፣ የሀገረ ቁስያው (ኢጣሊያ) አባ ይምአታ፣ የአንጾኪያው (ሶሪያ) አባ ጽሕማ፣ የቂልቅያው (ግሪክ) አባ ጉባ፣ የእስያው አባ አፍጼ፣ የሮምያው ጰንጠሌዎን፣ የቂሣርያው አባ አሌፍ ናቸው፡፡
እነዚህ ቅዱሳን ወደ ትውልድ ሀገራቸው ሮም ተመልሰው ሮምን ወደ ቀናች ሃይማኖት መለሷት፡፡ በዚያም ሳሉ በምድረ አዜብ ብሔረ ኢትዮጵያ ስለሚኖሩ ሰዎች ዝና ስለ ነገሥታቶቻቸውም ቅድስናና ሀገሪቱም የእመቤታችን አሥራት መሆኗን ከመጻሕፍት ተረዱ፡፡ አባ ዘሚካኤልም ከሁለቱ ደቀ መዛሙርቶቹ ጋር በሌሊት ወጥቶ ወደ ኢትዮጵያ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል እየመራው መጥቶ አክሱም ደረሰ፡፡ በዚያም ጥቂት ጊዜ በመቀመጥ ተመልሶ ወደ ሮምያ ሄዶ ስለ ኢትዮጵያ ያየውንና የሰማውን በሙሉ ሁሉ ለሌሎቹ ቅዱሳን ሲነግራቸው እነርሱም ‹‹ይህችን ሄደን ማየት አለብን›› ተባበብለው ያላቸውን ሁሉ ይዘው ታቦቶቻቸውን፣ ካህናቶቻቸውን፣ ንዋየ ቅድሳቶቻቸውን፣

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

23 Oct, 12:32


መጻሕፍቶቻቸውን ሁሉ ይዘው በዘሚካኤል መሪነት በመምጣት በ460 ዓ.ም ጳጳሱና ንጉሡ ካሉበት አክሱም ከተማ ገቡ፡፡
ተሰዓቱ ቅዱሳን ከአብርሃ ወአጽብሐ 6ኛ ንጉሥ በሚሆን በአልሜዳ ዘመነ መንግሥት ከአውሮፓና ከእስያ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው አክሱም ከተማ ካረፉ በኋላ ሀገረ ስብከታቸውን ተከፋፍለው ገዳም እየገደሙ፣ በዓት እያበጁ፣ ከሣቴ ብርሃን አባ ሰላማ የመሠረተውን የክርስትና ሃይማኖት በከፍተኛ ሁኔታ አስፋፍተዋል፡፡ ገዳማትን አስፋፍተው የወንጌልን ብርሃን በሀገራችን ላይ አብርተዋል፡፡
እነዚህ ቅዱሳን የነገሥታት ወገን ስለሆኑ በሮም ነግሦ የሚገኘውን ወንድማቸውን ይስሐቅን ላኩበት፡፡ ንጉሡ ይስሐቅ ለአባ ዘሚካኤል የእኅት ልጅ ነው፡፡ እርሱም መልእክቱ እንደደረሰው 7 ዓመት በሮም ከነገሠ በኋላ መንግሥቱን ትቶ በሌሊት ተነሥቶ በመውጣት ወደ ሀገራችን በመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል መሪነት መጣና ከወንድሞቹ ጋር ተቀላቀለ፡፡ እነርሱም አመነኮሱትና ስሙን ገሪማ አሉት፡፡ ሁሉም በአንዲት የጸሎት ቤት በምንም ሳይለያዩ በአንድነት እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ፣ እንደ አንድ ልብ መካሪ ሆነው ለጸሎት ቆመው ውለው ያድሩ ነበር፡፡ የአባ ዘሚካኤልም እናት ወደ ሀገራችን ኢትዮጵያ መጥታ ከሴት መነኮሳት ጋር እነርሱ ባሉበት አካባቢ ትኖር ነበር፡፡ አባ ዘሚካኤልን የበላይ አድርገው ሾሙትና ስሙንም አረጋዊ አሉት፡፡ እነዚህ ቅዱሳን ድውያንን እየፈወሱና ሙታንን እያስነሱ እጅግ በጣም አስገራሚ የሆኑ ድንቅ ድንቅ ብዙ ተአምራትን ያደርጉ ነበር፡፡ ተአምራቶቻቸውን በኋላ እናየዋለን፡፡ ከሰንበት በቀር እህል የሚባል ነገር የማይቀምሱት እነዚህ ቅዱሳን ኢትዮጵያን በኪደተ እግራቸው ባርከዋታል፣ ጌጦቿ ሆነውላታል፣ በትምህርታቸው የእምነቷን መሠረት አጽንተውታል፣ የልዕልናዋንም ታሪክ ለዓለም መስክረውላታል፡፡
ለ12 ዓመታትም በፍጹም አንድነት አብረው ከተቀመጡ በኋላ ‹‹እርስ በራሳችን እየተያየን ብንኖር ተድላ ደስታ ይሆንብናልና ተለያይተን እንቀመጥ›› ብለው ተማከረው በተለያየ በዓት አባ ሊቃኖስ በደብረ ቁናጽል፣ አባ ጰንጠሌዎንም በእርሱ ትይዩ በሆነ ቦታ፣ አባ ገሪማ በደብረ መደራ፣ አባ ጽሕማ በደብረ ጸድያ፣ አባ ይምአታ በደብረ ገረዓልታ፣ አባ አፍጼ በደብረ ይሐ፣ አባ አሌፍ በደብረ አኅድአ መኖር ጀመሩ፡፡ አባ አረጋዊ ደግሞ በጣም ርቀው በመሄድ በደብረ ዳሞ በዋሻና በፍርኩታ ውስጥ በተራራም ላይ መኖር ጀመሩ፡፡ አባችን አቡነ አረጋዊ ከደብረ ዳሞ ተራራ ስር ባለችውና አሁንም ድረስ ማየ ምርቃይ (መጠመቂያ) በምትባለው ምንጭ እጅግ ብዙ መነኮሳትን በዚያ አጥበው ካመነኮሱ በኋላ ሴቶቹን ቅድስት ዕድና ካሉበት ቤተክርስቲያን ያስገቧቸው ነበር፡፡ የአቡነ አረጋዊም እናት ቅድስት ዕድና በጥር 4 ቀን በክብር ዐርፋች፡፡ አባታችን ለመጀመሪያ ጊዜ ዘንዶው አስወንጭፏቸው ደብረ ዳሞ ላይ ሲወጡ መስቀላቸው ያረፈበት የመስቀሉ ቅርጽ ዛሬም ድረስ በጠፍጣፋ ድንጋይ ላይ ምልክቱ በግልጽ ይታያል፡፡ የአጽፋቸውም ቅርጽ እንዲሁ የሚታይ ሲሆን እነ አቡነ ተክለሃይማኖት የጸለዩበት ዋሻም በቦታው ላይ ይገኛል፡፡
አባ ጰንጠሌዎን ምንም ውኃና እንጨት ከሌለባት በአንድ ትንሽ ተራራ ላይ ወጥቶ በዚያም 5 ክንድ ቁመት ብቻ ያላት ከመቃብር ያልተሻለች ትንሽ የድንጋይ ዋሻ ቆፍሮ በእርሷ ውስጥ መኖር ጀመረ፡፡ ከአንዲትም ቀዳዳ በቀር መስኮት አልነበራትም፡፡ አባ ጰንጠሌዎንም በውስጧ ሳይቀመጥ ሳይተኛ በእግሩ ቆሞ 45 ዓመት ጸለየ፡፡ ምድራዊ ወይም ሥጋዊ የሆኑ ፍትወታት ፈጽመው ጠፍተውለታልና ከመላእክትም ማኅበር ጋር አንድ ሆኗልና ከፍጹም ምስጋና በቀር እህል ወይም ውኃ ወይም ቅጠል እንኳ አይቀምስም ውኃም አይጠጣም ነበር፡፡ እናንተ ቅዱሳን ሆይ! የነገሥታት ልጆች ስትሆኑ ላባችሁን እያንጠፈጠፋችሁ በዱር በገደል መንከራተታችሁ፣ በቀበሮም ጉድጓድ መቀመጣችሁ፣ የምትለብሱት ሳታጡ በበርድ በቁር መራቆታችሁ ምንኛ ድንቅ ነው!? የምትበሉት የምትጠጡት ሳታጡ የነገሥታት ልጆች ስትሆኑ መራብ መጠማታችሁስ እንደምን ያለ ነው!?
‹‹ተሰዓቱ ቅዱሳን ብዙ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን ያደረጉ ነበር፣ መላእክትም ዘወትር ባለመለየት ይጎበኙዋቸው ነበር፡፡ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስም ዘወትር እየተገለጠላቸው ይባርካቸውና ቃልኪዳን ይሰጣቸው ነበር፡፡ በጸሎታቸውም አጋንንትን ያስወጣሉ፣ ድውያንን ይፈውሳሉ፣ ዕውራንን ያበራሉ፣ ሙታንን ያስነሣሉ፡፡ ለእያንዳንዳቸውም የሃይማኖታቸውን ኃይል አሳዩ፡፡ ከእነርሱ መካከል ተራራ ያፈለሱ አሉ፣ ባሕሩን ከፍለው ደረቅ መንገድ ያደረጉ አሉ፣ ጠዋት ዘርተው ማታ ሰብስበው የሚያጭዱ አሉ፣ ይኸውም የስንዴውን ነዶ በግራር ዛፍ ላይ አበራይተው የዛፉ ቅጠል ሳይረግፍ በሬዎቹም ከዛፉ ላይ ሳይወድቁ ምርቱ ብቻ እየወረደ በአውድማው ላይ እንዲከማች ያደረጉ አሉ፣ ወዲያውም ስንዴውን ለመገበሪያ ሠይመው ለዘጠኝ ሰዓት መሥዋዕተ ቊርባን ያደረሱ አሉ፡፡››
‹‹በዓለት ድንጋይ ላይ የወይራ ተክል ተክለው በዚያኑ ጊዜ ጸድቆ ለምልሞ ታላቅ ዛፍ ከሆነ በኋላ በእግዚአብሔር ፈቃድ ግንዱ ደርቆ ቆርጠውና ፈልጠው እንጨቱን አንድደው እሳቱ ፍም ከወጣው በኋላ ፍሙን በቀጭን ሻሽ ወስደው ለዘጠኝ ሰዓት የቅዳሴ ማዕጠንት ያደረሱ አሉ፡፡››
‹‹ለቤተክርስቲያን አገልግሎት የሚውልና ለሥርዓተ ቊርባን ማከናወኛ የሚሆን ውኃው ሳይፈስ በወንፊት ውኃ የሚቀዱ አሉ፡፡››
‹‹ከእነሱም አንዱ በዐረፈ ጊዜ የሥጋው ሥርዓተ ግንዘት በመላእክት እጅ የተከናወነ አለ፡፡ ይልቁንም ቁመቱና ርዝመቱ ከታላላቅ ገደል እጅግ በጣም የሚበልጥ የድንጋይ ዓምድ ከወንዝ ማዶ ዘንበል ብሎ መጥቶ ሥጋቸውን በክብር ተቀብሎ በተራራው ጫፍ ላይ እስከዛሬም ድረስ ፈጽሞ ሳይነቃነቅና ሳይናወፅ ቀጥ ብሎ ቆሞ ይገኛል፡፡ የሰዎቹም የመግነዝ ምልክት ጥበበኛ እንደሣለው ሥዕል በድንጋዩ ዓምድ ላይ ተስሎ ወይም ተቀርፆ ይታያል፡፡››
‹‹ቆመው ጸሎት በሚጸልዩበት ጊዜ ዓሥሩ የእጆቻቸው ጣቶችና ዓሥሩ የእግሮቻቸው ጣቶች እንደፋና የሚያበሩበትና እንደመብረቅ የሚብለጨልጩበት ጊዜ አለ፡፡››
‹‹ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለአንዳች ሐዋርያ ስብከት አስቀድማ በክርስቶስ እንዳመነችና በዚህም ምክንያት የልዕልናዋን ታሪክ ለዓለም ለማሳወቅ ፈጥነው የሄዱ አሉ፡፡ የኢትዮጵያ ምድር በእነዚህ የቅዱሳን ኪደተ እግር ተቀደሰች፣ በውስጧም በመመላለሳቸው አውራጃዎቿና አደባባዮቿ ሁሉ ታደሱ፡፡ መዓዛ ትምህርታቸውና ተአምራቶቻቸው በሁሉም አውራጃዎች ተሠራጨ፣ የእምነቷንም መሠረት አጸኑ፡፡››
የተሰዓቱ ቅዱሳን በዓለ እረፍታቸው እንደሚከተለው ነው፡- አባ ገሪማ (ሰኔ 17 ቀን ተሰወሩ)፣ አባ አሌፍ (መጋቢት 11)፣ አባ ጰንጠሌዎን (ጥቅምት 6)፣ አባ ጽሕማ (ጥር 19)፣ አባ ይምአታ (ጥቅምት 29)፣ አባ አፍጼ (ግንቦት 29 ተሰወሩ)፣ አባ ጉባ (ግንቦት 29)፣ አባ ሊቃኖስ (ህዳር 28 ተሰወሩ)፣ አባ አረጋዊ ጥቅምት 14 ተሰወሩ፡፡
ለአቡነ አረጋዊ በደብረ ዳሞ ሰማያዊ የመሥዋዕት ኅብስትና ንዋያተ ቅድሳት ከሰማይ ወርደውላቸዋል፡፡ ‹‹ብፁዕ አባታችን በደብረ ዳሞ መጠነኛ ቤትን ሠራና ይዞት የመጣውን ታቦት በውስጡ አስገባው፡፡ ስለ ቊርባኑም ነገር ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፡፡ መላእክትም ለመሥዋዕቱ ሥርዓተ ዝግጅት የሚያስፈልጉትን የወርቅ ጻሕል፣ የብር ጽዋ፣ ለልብሰ ተክህኖ የሚያገለግሉ የወርቅ ላንቃ፣ ካባ፣ በውስጧ ትኩስ ኅብስት ያለባት መሶበ ወርቅ ለመሠዊያው የሚያስፈልገውን ሁሉ ከሰማይ ይዘውለት ወርደዋል፡፡››

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

23 Oct, 12:32


ኢትዮጵያዊው ንጉሥ ዐፄ ካሌብ ከ24 ሺህ በላይ የሚሆኑ የናግራን ሰማዕታትን ደም ሊበቀልላቸው ሲያስብ መጀመሪያ በጸሎታቸው እንያስቡትና እንዲመክሩት አቡነ አረጋዊንና አቡነ ጰንጠሌዎንን ጠይቋቸዋል፡፡ በመጀመሪያ የቊስጥንጥንያው ሊቀ ጳጳስ ጢሞቴዎስ በናግራን አገር ስለተፈጁት የክርስቲያን ወገኖች በግፍ የተጨፈጨፉበትን መልእክት የያዘች ደብዳቤ ወደ ኢትዮጵያው ንጉሥ ወደ ዐፄ ካሌብ ላከ፡፡ ዐፄ ካሌብም መልእክቱን ከተረዳ በኋላ ወደ ብፁዕ አቡነ አረጋዊ እንዲህ ሲል መልእክት ላከ፣ ‹ፊንሐስ የተባለ አረማዊ የናግራን ክርስቲያኖችን ደም በከንቱ ያፈሰሰ፣ ቤተክርስቲያንን የመዘበረና ያጠፋ ፍጹም የእግዚአብሔር ጠላት ወደሚሆን ሄጄ እዋጋው ዘንድ ተዘጋጅቻለሁ፡፡ ስለዚህ አባቴ ሆይ! አንተም በበኩልህ ጸሎት አድርግልኝ፣ የጻዲቅ ጸሎት ትራዳለች፣ ኃይልንም ታሰጣለች፣ በጠላት ላይ ድልንም ታቀዳጃለችና› ሲል ላከበት፡፡ አባታችን አቡነ አረጋዊም ለንጉሡ ጭፍሮች ‹ወደ ጦሩ ግንባር ሂድ፣ እግዚአብሔር ጠላቶችህን ከእግርህ በታች ያስገዛልህ፣ ለአንተም ግርማ ሞገስ ይስጥህ፣ በሰላም ይመልስህ› ብለው መርቀው ሸኝተውታል፡፡ ዐፄ ካሌብም ወደ ናግራን ዘምቶ ከሃዲውን የአይሁድ ንጉሥ ፊንሐስን ከገደለውና ጦሩን ሁሉ ደምስሶ በማጥፋት የክርስቲያኖቹን ደም በሚገባ ተበቀለ፡፡ በአንጾኪያ፣ በእስክንድሪያ፣ በሮም፣ በቊስጥንጥንያና በዓለም ላይ ያሉ ክርስቲያኖች ሁሉ ይህን ሲሰሙ በእጅጉ ተደሰቱ፡፡ ይህም የሆነው በ525 ዓ.ም ነው፡፡ ንጉሡ ዐፄ ካሌብ የናግራን ሰማዕታት ደም ተበቅሎላቸው ሁሉንም ነገር አስተካክሎላቸው በደስታ ወደ አክሱም ከተመለሰ በኋላ ‹ይህን ያደረገልኝን አምላኬን በምን ላስደስተው?› ሲል አሰበና ተድላውን፣ ደስታውን ዓለምን ንቆ፣ ልብሰ መንግሥቱን አውልቆ አንዲት የውኃ መንቀልና አንዲት ምንጣፍ ብቻ ይዞ በአባ ጰንጠሌዎን እጅ መንኩሶ አጠገባቸው ከሚገኝ አንድ ዋሻ ውስጥ ገባ፡፡ ዋጋው እጅግ የከበረውንና በነገሠ ጊዜ የጫነውን ዘውዱን ከጌታችን መካነ መቃብር ወይም በር ላይ ይሰቀልለት ዘንድ ከአደራ ደብዳቤ ጋር ለኢየሩሳሌሙ ሊቀ ጳጳሳት ለአባ ዮሐንስ ላከለት፡፡ ወደ አቡነ አረጋዊም እንዲህ ሲል መልእክት ላከ፡- ‹አባቴ ሆይ በአንተ ጸሎት በእግዚአብሔር ቸርነት ከጦርነቱ በሰላም ተመልሻለሁ፣ አሁንም የክርስቶስን አርዑተ መስቀል ተሸክሜአለሁና እግዚአብሔር ለፍጻሜው ያብቃህ እያልህ ስለ እኔ ጸልይልኝ› ብሎ ወደ አባታቸን ወደ አቡነ አረጋዊ ላከበት፡፡ ስለዚህም ነገር አባታቸን ወደ አቡነ አረጋዊ በጣም ተደሰቶ ‹ልጄ ሆይ! መልካሙንና የበለጠውን አድርገሃል፣ አሁንም እግዚአብሔር የፈቀደከውን ነገር ሁሉ ይፈጽምልህ› ብለው መረቁት፡፡ ንጉሥ ዐፄ ካሌብም በዋሻ 12 ዓመት በጾም በጸሎት በብዙ ተጋድሎ ሲኖር ቆይቶ በግንቦት 20 ቀን ዐርፎ እስከ ዘለዓለሙ ድረስ የማያልፍ ሰማያዊ ክብርን ወረሰ፡፡››
የአቡነ አረጋዊ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

23 Oct, 12:32


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ጥቅምት 14-አቡነ አረጋዊ የተሰወሩበት ዕለት ነው፡፡
+ እግዚአብሔር ልኮት ወደ ጋዛ በመውረድ ኢትዮጵያዊውን ጃንረባ ባኮስን ያጠመቀው ረድኡ ሐዋርያ ቅዱስ ፊሊጶስ ዕረፍቱ ነው፡፡
+ ገድሉ በሀዘን የሚያስለቅሰው ሙሽራው ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ዕረፍቱ ነው፡፡
+ ገድሉ ከሙሽራው ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ታሪክ ጋር ተመሳሳይ የሆነው ቅዱስ ሙሴ ዕረፍቱ ነው፡፡
+ የቅዱስ መራክዋ እና ከእርሱ ጋር ያሉ ሰማዕታት የዱማቴዎስ፣ የእምራይስና የ431 ሰማዕታት መታሰቢያ በዓላቸው መሆኑን ስንክሳሩ በስም ይጠቅሳቸዋል፡፡
ረድኡ ሐዋርያ ቅዱስ ፊሊጶስ፡- ‹‹ሐዋርያው ፊሊጶስ›› ተብለው የሚጠሩት ሁለት ሐዋርያት ስለሆኑ የስም መምታታትና የታሪክ መፋለስ እንዳይኖር ሁለቱን በደንብ ለይቶ ማወቅ ያስፈልጋል፡፡ ይኸኛው ረድኡ ሐዋርያ ፊሊጶስ ቁጥሩ ከ12ቱ ሐዋርያት ውስጥ አይደለም፡፡ ቁጥሩ ከ72ቱ አርድእት ውስጥ ነው፡፡ ቁጥሩ ከ12ቱ ሐዋርያት ውስጥ የሆነው ‹‹ሐዋርያው ፊሊጶስ›› ከዚህኛው የተለየ ነው፡፡ ይሄኛው ሐዋርያ ቁጥሩ ከ12ቱ ሐዋርያት ውስጥ የሆነው በማቴዎስ ወንጌል 10፡3 ላይ እንተጠቀሰው ከ12ቱ ሐዋርያት ውስጥ በ5ኛ ደረጃ የተጠቀሰው ነው፡፡ ከገሊላ የተገኘ የቤተ ሳይዳ ሰው ሲሆን የግሪክ ሰዎችን ወደ ጌታችን ያቀረባቸው እርሱ ነው፡፡ ዮሐ 12፡20-22፡፡ ፊሊጶስ ሐዋርያው ቅዱስ ናትናኤልን ‹‹የናዝሬቱን ኢየሱስን አግኝተነዋል መጥተህ እይ…›› በማለት ወስዶ ከጌታችን ጋር አገናኝቶታል፡፡ ዮሐ 1፡44-52፡፡ ጌታችንን ‹‹አብን አሳየንና ይበቃናል›› ብሎ የጠየቀውም ይኸው ሐዋርያ ፊሊጶስ ነው፡፡ ይህም ጥያቄው ለእኛ ለሁላችን መሠረታዊውን የክርስትና እውቀት እንድናገኝ እረድቶናል፡፡ ጌታችንም ‹‹እኔን ያየ አብን አይቷል፣ እኔ በአብ እንዳለሁ አብም በእኔ እንዳለ እመኑኝ›› በማለት ነው መልስ የሰጠው፡፡ ዮሐ 14፡8-14፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ፊሊጶስ ብዙዎች ጣዖት ማምለካቸውን ትተው በክርቶስ እንዲያምኑ በማድረጉ ጣዖት አምላኪዎች ቁልቁል ሰቅለው ነው በሰማዕትነት የገደሉት፡፡ ዕረፍቱም ኅዳር 18 ነው፡፡
ዛሬ የዕረፍቱን በዓል የምናከብርለት ይሄኛው ረድኡ ሐዋርያ ቅዱስ ፊሊጶስ ቁጥሩ ከ72ቱ አርድእት ሲሆን በኢየሩሳሌም ቤተ ክርስቲያን ከሰማዕቱ ቅዱስ እስጢፋኖስ ጋር ከተሾሙት ከሰባቱ ዲያቆናት መካከል አንዱ ነው፡፡ ሐዋ 6፡3-5፡፡ ጌታችን በቂሳርያ ባለፈ ጊዜ በውስጧ ሲያስተምር ሰምቶ ነው ጌታችንን አምኖ የተከተለው፡፡ ጌታችን ወንጌልን ይሰብኩ ዘንድ ሁለት ሁለት አድርጎ ከላካቸው ሐዋርያት ውስጥ አንዱ ነው፡፡
ረድኡ ሐዋርያ ቅዱስ ፊሊጶስ በበዓለ ሃምሳ ዕለት የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ ከተቀበለና ከጌታችን ዕርገት በኋላ ወደ ሰማርያ ወርዶ አስተምሮ ብዙዎችን አጥምቋቸዋል፡፡ በሥራዩ የሚታወቀውን ሲሞን መሠሪን አስተምሮ አጥምቆት ነበር፡፡ እርሱ ግን የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ በገንዘብ ሊገዛ አሰበ፡፡ ጌታችን ከሕማሙና ከሞቱ በፊት ለ72ቱ አርድእት ድውይ የመፈወስ ሙት የማስነሳት ሥልጣን ስለሰጣቸው ፊሊጶስም ይህንን በማድረግ ተልእኮውን ተወጥቷል፡፡ ወንጌላዊው ፊሊጶስም እየተባለ ይጠራል፡፡ ከእስጢፋኖስ ሞት በኋላ ወደ ሰማርያ ወርዶ ከብዙ ተአምራት ጋር አስተምሯል፡፡ ዮሐ 8፡5-13፡፡ በኋላም በመንፈስ ቅዱስ መሪነት የእግዚአብሔር መልአክ ልኮት ወደ ጋዛ በመውረድ ኢትዮጵያዊውን ጃንረባ ያጠመቀው ይኸኛው ሐዋርያ ነው፡፡ ጃንደረባውንም አጥምቆት ከውሃው ከወጡ በኋላ ፊሊጶስን መንፈስ ቅዱስ ነጥቆ ስለወሰደው ጃንደረባው ዳግመኛ አላየውም፡፡ ሐዋ 8፡26-40፡፡
ከዚህም በኋላ ሐዋርያው በቂሳርያ ትንቢት የሚናገሩ አራት ሴቶች ልጆችን አስከትሎ እዝዱድ ከምትባለው ሀገር ገብቶ የክርስቶስን ወንጌል በመስበክ ብዙዎችን አሳምኖ አጥምቋል፡፡ ሐዋ 21-8፡፡
የሐዋርያ የቅዱስ ፊሊጶስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!
+ + +
ሙሽራው ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ፡- ሙሽራው ገብረ ክርስቶስ ወላጅ አባቱ የቍስጥንጥንያው ንጉሥ ቴዎዶስዮስና እናቱ ንግሥት መርኬዛ በስለት ያገኙት ብቸኛ ልጃቸው ስለሆነ ሃይማኖትን እያስተማሩት በምግባር በእጅጉ ተንከባክበው አሳድገውታል፡፡ የአባቱን ንግሥና በመውረስ ቍስጥንጥንያን እንዲገዛላቸው በመፈለግ ወላጆቹ ለአካለ መጠን ሲደርስ የሮሙን ንጉሥ ሴት ልጅ አጋቡት፡፡ እርሱ ግን ዓለምን ፍጹም በመናቅ የክርስቶስን መስቀል ለመሸከም የተዘጋጀ ነበርና የሠርጉ ዕለት ሌሊት የእርሱንም ሆነ የሙሽይቱን ድንግልና እንደጠበቀ ከጫጉላ ቤት ወጥቶ በመርከብ ተሳፍሮ ሩቅ ሀገር በመሄድ በቤተክርስቲያን ተቀምጦ ከነዳያን ጋር ተደባልቆ በመለመን ለምኖ ያገኘውንም ለሌሎች እየመጸወተ በጾም በጸሎት ተጠምዶ 15 ዓመት ኖረ፡፡
እመቤታችን ተገልጻ ለአንድ የቤተክርስቲያኑ አገልጋይ የገብረ ክርስቶስን ጽድቅ ብትነግረው ምሥጢሩን ለሀገሩ ሁሉ አዳረሰበት፡፡ ሙሽራው ገብረ ክርስቶስም ‹‹ግብሬ ታወቀ፣ ከዚህ ውዳሴ ከንቱ ልሽሽ›› በማለት ወደሌላ ሀገር በመርከብ ሲጓዝ ፈቃደ እግዚአብሔር መርከቢቱን ያለ አቅጣጫዋ ወስዶ አባቱ ደጅ አደረሰው፡፡ ማንነቱን እንደደበቀና ዓለምን ምን ያህል እንደናቃት ይረዳ ዘንድ በአባቱና በንጉሡ ደጅ የኔ ቢጤ ለማኝ ሆኖ ለአባቱ ውሾች የሚሰጠውን ፍርፋሪ እየተመገበ አሁንም 15 ዓመት ሙሉ በትዕግስት ተቀመጠ፡፡
የአባቱ አሽከሮች እንኳን እጣቢና ቆሻሻውን ሁሉ እየደፉበት ሲያሠቃዩት የአባቱ ውሾች ግን የእግሩን ቁስል ይልሱለት ነበር፡፡ በአጠቃላይ ገብረ ክርስቶስ እጅግ የተከበረ የታላቅ ንጉሥ ልጅ ሲሆን ነገር ግን ዓለምን ፍጹም በመናቅ ስለ ጽድቅ ተሰዶ እየለመነ ያገኘውን እየመጸወተ በጾም በጸሎት እየተጋደለ 30 ዓመት ሙሉ ተቀመጠ፡፡ በመጨረሻም ጌታችን እመቤታችንን፣ ቅዱሳን መላእክትን ሁሉ፣ ከገብረ ክርስቶስ በፊት የነበሩ ነቢያትን ሁሉ፣ ሐዋርያትን፣ ጻድቃንን፣ ሰማዕታትን ሁሉ አስከትሎ መጥቶ ቃልኪዳን ከገባለት በኋላ ከጌታችን ጋር አብረውት የመጡት ሁሉ በታላቅ ክብርና ምስጋና እያመሰገኑት ጌታችን ክብርት ነፍሱን በእቅፉ ተቀብሎ አሳርጓታል፡፡
የቁስጥንጥንያው ሊቀ ጳጳሳት አባ ቴዎፍሎስ በቅዳሴ ላይ ሳሉ ከንጉሡ ቤት ሄደው የገብረ ክርስቶስን ሥጋ እንዲያመጡ የእግዚአብሔር ድምፅ ከሰማይ በትእዛዝ መጣላቸውና ሄደው ቢያዩ የገብረ ክርስቶስን ሥጋ በንጉሥ አባቱ ደጅ ወድቆ አገኙት፡፡ በገብረ ክርስቶስም እጅ ላይ በጥቅል ወረቀት የተጻፈ ደብዳቤ ነበርና ወስደው ሊያነቡት ሲሞክሩ ወረቀቱ አልላቀቅ ብሎ ፈጽሞ እምቢ አላቸው፡፡ ብዙ ምሕላና ጸሎት ከተደረገ በኋላ ወረቀቱ ከእጁ ላይ ተላቀቀና ሲነበብ ገብረ ክርስቶስ ስለ አምላኩ ፍቅር ብሎ ለ30 ዓመታት ያሳለፈውን እጅግ አሠቃቂ መከራ በተለይም በአባቱ ደጅ ማንም ሳያውቀው ያሳለፈውን እጅግ አሳዛኝ መከራና በኀዘን የሚያስለቅሰውን ታሪኩን በራሱ እጅ በዝርዝር ጽፎት ተገኝቷል፡፡ ንጉሡ አባቱና ንግሥት እናቱም ይህንን ልጃቸው የጻፈውን መልእክት ባነበቡ ጊዜ የሚሆኑት ጠፋቸው፡፡ በጣም የሚገርመው ደግሞ መጀመሪያ ላይ ወላጆቹ ሚስት አድርገው ያመጡለት የሮሙ ንጉሥ ሴት ልጅ ለባሏ ታማኝ ሆና 30 ዓመት ሙሉ በእናት አባቱ ቤት በትዕግስት ስትጠብቀው መኖሯ ነው፡፡ እርሷም ታሪኩ ሲነበብ ብትሰማ እንደ ዕብድ ሆነች፡፡ የቅዱስ ገብረ ክርስቶስን ሥጋውን ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲወስዱ እጅግ አስገራሚ ተአምራት በድውያን ሕመምተኞች ላይ ተፈጽሟል፡፡ ከተአምራቱ የተነሣ መንገዱ በሕዝብ ተጨናንቆ አላሳልፍ ቢላቸው ንጉሡ በመንገድ ዳር ወርቅ

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

22 Oct, 18:03


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ጥቅምት 13-መስተጋድል መነኮስ አቡነ ዘካርያስ ዕረፍቱ ነው፡፡
ስንክሳሩ ‹‹ቀሲስ አብጥልማኮስና ወንድሞቹ በሰማዕትነት ዐረፉ›› በማለት ስማቸውን የጠቀሳቸው ሰማዕታት ዕረፍታቸው ነው፡፡

አቡነ ዘካርያስ ኃያል መነኮስ፡- ይኸውም ቅዱስ ገና በጨቅላ ዕድሜው በ7 ዓመቱ ወደ ገዳም ገብቶ መላ ዘመኑን በታላቅ ተጋድሎ የኖረ ነው፡፡ አቃርዮስ የተባለው አባቱም መስተጋድል የሆነ መነኮስ ነው፡፡ ቅዱስ አቃርዮስ አስቀድሞ ወደአስቄጥስ ገዳም ገብቶ በተጋድሎ ይኖር ነበር፡፡ ልጁን ቅዱስ ዘካርያስም 7 ዓመት በሆነው ጊዜ እናቱ ወደ አስቄጥስ ገዳም አምጥታ ለአባቱ ሰጠችው፡፡
ቅዱስ አቃርዮስም ልጁን ዘካርያስን ወደ አረጋውያን መነኮሳት አባቶች ዘንድ ወሰደውና ቅዱሳኑ በላዩ ጸለዩበት፡፡ ቅዱሳኑም ዘካርያስን ከባረኩት በኋላ ‹‹ይህ ሕፃን ፍጹም መነኩሴ ይሆናል›› ብለው ትንቢት ተናገሩለት፡፡ ከዚህም በኋላ ዘካርያስ መነኮሳቱን እያገለገለ በጾም በጸሎት እየተጋ በተጋድሎ በገዳሙ ውስጥ አደገ፡፡ መልኩም እጅግ ያማረ ስለነበር ስለ እርሱ በገዳሙ ውስጥ አንዳንዶች አጉረመረሙ፡፡ ‹‹ይህን ያህል መልከ መልካም ሲሆን በገዳም ውስጥ በመነኮሳት መካከል እንዴት ይኖራል›› እየተባባሉ አንዳንዶች ሐሜት ውስጥ ገቡ፡፡

ዘካርያስም በመልኩ ማማር የተነሣ አንዳንዶች በእርሱ ላይ ማጉረምረማቸውን በሰማ ጊዜ ከአስቄጥስ ገዳም ወጥቶ በመሄድ ናጥራን ወደሚባል ተራራ ሥር ወዳለች አንዲት አዘቅት ሄደ፡፡ ልብሱንም አውልቆ በረግረጉ ውስጥ ብዙጊዜ ተኛ፡፡ ሥጋውም ፍጹም ጠቆረ፡፡ ሰውነቱ ተመላልጦ ቆሰለ፡፡ ብዙ ዘመንም በደዌ ተይዞ እንደኖረ ሆነ፡፡ ከዚህም በኋላ ልብሱን ለብሶ ወደ አስጥስ ገዳም ተመልሶ ገባ ነገር ግን አሁን ማንም ያወቀው የለም፡፡ ከብዙ ቀናት በኋላ አባቱ አቃርዮስ አስተውሎ ልጁ እንደሆነ ዐወቀውና ‹‹መልክህን የለወጠው ምንድነው?›› ብሎ ጠየቀው፡፡ ቅዱስ ዘካርያስም ያደረገውን ሁሉ ለአባቱ ነገረው፡፡ እርሱም በእሁድ ቀን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ሊቀበል ወደ ቤተ ክርስቲያን ገባ፡፡ እግዚአብሔርም ያንጊዜ የቅዱስ ዘካርያስን ሥራውን ሁሉ ለታላቁ አባት ለኤስድሮስ ገለጸለት፡፡ አቡነ ኤስድሮስም ቅዱስ ዘካርያስ ያደረገውን ነገር ለመነኮሳቱ አስረዳቸው፡፡ እነርሱም በጋራ ሆነው ‹‹አስቀድሞ እንደ ሰው ሁነህ መጣህ፣ ዛሬ ግን እንደ እግዚአብሔር መላአክ ሁነህ መጣህ›› አሉት፡፡

ከዚህም በኋላ ቅዱስ ዘካርያስ በብዙ ገድል ተጠምዶ ኖረ፡፡ ትሕትናን፣ ቅንነትን፣ ያማረ የትሩፋትን ሥራ ሁሉ ገንዘብ አደረገ፡፡ አባቱ ቅዱስ አቃርዮስም ስለ ልጁ ቅዱስ ዘካርያስ ሲናገር ‹‹እኔ በገድል ብዙ ደክሜያለሁ ነገር ግን ከልጄ ሥርዓተ ገድል ገና አልደረስኩም›› ብሎ ይናገር ነበር፡፡ ቅዱስ ዘካርያስ ጽኑ በሆነ ተጋደሎው በገዳም 45 ዓመት በመኖር እግዚአብሔርን ሲያገለግል ከኖረ በኋላ በሰላም ዐርፏል፡፡ መላ ዘመኑም 52 ዓመት ሲሆን ከዚህም ሰባቱን ዓመት በወላጆቹ ቤት 45 ዓመት ደግሞ በገዳም በታላቅ ተጋድሎ ኖረ፡፡
ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!

ስንክሳር (ገድላት) ዘዕለታት

22 Oct, 05:34


በሀገራችን ማኅበረ ዶጌገዳ ገዳም የሚገኘው
የቅዱስ ማቴዎስ የእጅ መስቀልና መቋሚያ!

በዚኽች ዕለት በዓመታዊ የዕረፍት በዓሉ ታስቦ የሚውለው ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ በ40 ዓ.ም ወደ አገራችን ኢትዮጵያ በመጣ ጊዜ ማኅበረ ደጌ ወንጌልን ሰብኮ ብዙዎችን ያጠመቀ ሲሆን በኢትዮጵያ ለመጀመሪያው ጊዜ የማኅበር ማኅበር ማኅበረ ደጌን መሥርቷል። በወቅቱ የነበረችው ንግሥትም በቅዱስ ማቴዎስ እጅ ተጠምቃለች፡፡ ቅዱስ ማቴዎስም ንግስቲቱን ካጠመቀ በኋላ ቀጥሎ መኳንንቱን፣ መሳፍንቱንና የጦር ሠራዊቱን ሁሉ አጥምቋቸዋል፡፡

ከዚህም በኋላ የጻድቃንን ማኅበር አቋቁሞ በጌታችን ስም በየወሩ በ29 ቀን እየተሰበሰቡ ጽዋ እንዲጠጡ አድርጓቸው ወደ ኢየሩሳሌም ሄዷል፡፡ ጥር 29 ቀን በዓመታዊ በዓላቸው ታስበው በሚውሉት በሦስት ሺህ ቅዱሳን (ማኅበረ ደጌ) መካከል ጌታችንም በአካል ተገልጦ የጽዋ ማኅበራቸውን አብሯቸው ጠጥቷል፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአምሳለ ነዳይ ድሀ መስሎ በመካከላቸው ይገኝ ነበር። ይኸውም "ሁለትም ሦስትም ሆነው በስሜ በሚሰበሰቡበት በዚያ እኔ በመካከላቸው እሆናለሁ" ያለውን የወንጌሉን ቅዱስ ቃል ያጠይቃል፡፡ ማቴ 18:20፡፡

ቅዱስ ማቴዎስ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ለመጀመሪያው ጊዜ የመሠረተው የጽዋ ማኅበር (ማኅበረ ደጌ) የሚገኘው ከአክሱም ከተማ ወደ ደቡብ በሚወስደው መንገድ 12 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ነው። በዚህ ቦታ ላይ የቅዱስ ማቴዎስ የእጅ መስቀልና መቋሚያው ይገኛሉ።

የወንጌላዊው የቅዱስ ማቴዎስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!

1,233

subscribers

2,126

photos

2

videos