ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ @nwdnews Channel on Telegram

ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
የብፁዕ አቡነ ኤርምያስ እና የብፁዕ አቡነ ቄርሎስ እንዲሁም የሌሎች መምህራን ትምህርቶች፣ ስብከቶችና ተግሳጾች በተጨማሪም በሀገረ ስብከቱ የሚከወኑ ዓበይት ክንውኖች የሚተላለፉበት የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት የቴሌግራም ቻናል ነው። የቻናሉ ቤተሰብ በመሆንና ለሌሎች በመጋበዝ የቤተክርስቲያንን አገልግሎት ያፋጥኑ።
5,932 Subscribers
2,745 Photos
8 Videos
Last Updated 17.02.2025 22:36

የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ እና የዘመናዊ መረጃ ምንጮች

የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ በሰሜን ወሎ ክልል ውስጥ በፖለቲካ ውሎ በሚኖሩ ምርጥ የሚዲያ መረጃ ምንጮችን ከአስፈላጊ ምርጥ የእውቀት መረጃ መረጃ ይደርሳል። ይህ ቻናል በመምህራን ታሪክ እና በዓለም ታሪክ የተመለከተ ምርጥ ምርጥ ይደርሳል። እንደዚህ የሚገኝ እውቀት መረጃ በዕድል አስፈላጊ ነው።

የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ዋነኛ ግንባር ምንድን ነው?

የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ በሰሜን ወሎ ክልል ውስጥ በደረጃዎች ተገድሺ ነው። በዚህ ቻናል የሚከናወኑ ስብከቶች ላይ በመዳረሻ እንዲሁም የቤተክርስቲያን አገልግሎት ይቀርባሉ።

ከሌላ የሚዲያ ተግባራት መሰረት በቤተ ክርስቲያን መንደር ይገኛሉ። ይህ ጉዳይ መረጃታዊ እንዲኖሩ ይህ ድረ-ገጽ የዚህ ቻናል ይወስነዋል።

የቻናሉ መለያ ምንድን ነው?

የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ በቴሌግራም ላይ ይገኛል። በቻናሉ ወይም በመዳረሻም የሚከወኑ የጋብዝ ይሆናሉ።

ይህም ለህዝቡ ማዕከል ወይን ይወስዳል። በአማርኛ እንዲሁም በሌላ ምርጥ የሚሰጠውን የሚዲያ ገጽታ እንዲመለከተው ይገኛል።

በሚዲያ የሚከናወኑ ስብከቶች ምን እንደሚያቀርባሉ?

በዚህ ቻናል የሚነሳ ወይም የሚቀርባው መረጃ ስብከቶች የአስተዳደር ወገኖች ቢያነሱ ይቀርባሉ።

የተቀባይነት መንገድ ወይም የትምህርቶች መግለጥ ይሆናል። ይህም በአማርኛ የተነቃቃ ሥራ ወይም የቴሌግራም ወረቀት ማሳያ ይቀርባል።

የሚዲያው ውስጥ ምን እንደሚያይቅ አይቁ?

ይህ ድረ-ገጽ ኢንተርኔት ገጽታን ይኖራል ወይም ያልተሳማ የተሳሳቢ ክንውና ይለዋወጣል።

አንዳንድ ግለሰቦች በቱርሱ እና ግዢት ዝርዝር ይቀየሩ የተለዋዋጮቹ ዝርዝር አገልግሎት ላይ ይኖራል።

ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ Telegram Channel

መርሐ ግብርድን የብፁዕ አቡነ ኤርምያስንና የብፁዕ አቡነ ቄርሎስን እና የሌሎች መምህራን ትምህርቶችን፣ ስብከቶችንና ተግሳጾችን በተጨማሪም ሀገረ ስብከቱ ዓበይት ክንውኖችን የሚተላለፉበት የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት አዝናኝ ቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራምን ቤተሰብ በመሆንና ለሌሎች በመጋበዝ የቤተክርስቲያንን አገልግሎት ያፋጥኑ።

ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ Latest Posts

Post image

ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተወለደ በ40 ቀኑ ወደ ቤተመቅደስ የገባበት ዓመታዊ የንግስ በዓል በወልድያ ጎልጎታ መዝገበ ምሕረት ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ተከብሯል።

የካቲት 08 ቀን 2017 ዓ/ም (ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት)

ልደተ ስምዖን ከጌታችን ከመድኀኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ንኡሳን በዓላት አንዱ ነው። አበው ስያሜውን የሰጡት ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቤተ መቅደስ በተገኘ ጊዜ የዕድሜ ባለጸጋው አረጋዊው ስምዖን ጌታን ሲታቀፈው ክርስቶስ ስምዖንን ወደ ጎልማሳነት ያደሰበት ዕለት ስለኾነ ነው።

የብሉይ ኪዳንን መጻሕፍት ይተረጒሙ ዘንድ ከተመረጡት መካከል የኾነው ይኽ አረጋዊ፥ ይተረጒመው ዘንድ የደረሰውን የኢሳይያስን መጽሐፍ ምእራፍ 7 ቊጥር 14 በደረሰ ጊዜ የድንግልን መውለድ በመጠራጠሩ ሴት ትወልዳለች ቢልም በእግዚአብሔር መልአክ አማካይነት ድንግል እስክትወልድ በሕይወት እንደሚቆይ ነግሮት ነበር።

ከዚኽም በኋላ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እስከተወለደና በዚች እለት ወደ ቤተ መቅደስ እስከ አስገቡት ድረስ ስምዖን ሦስት መቶ ዓመት ኖረ። ሕፃኑን ጌታችንንም በታቀፈው ጊዜ ታውረው የነበሩ ዓይኖቹ ተገለጡ፤ ኹለመናውም አዲስ ሆነ። መንፈስ ቅዱስም የምትጠብቀው የነበረ ሕፃን ይኽ ነው ብሎ ሲነግረው እግዚአብሔርን አመሰገነው። ባርያኽን በሰላም አሰናብተው። በአንተ ምክንያት በዚኽ በኀላፊው ዓለም ሕይወት ታስሬ ኖሬአለኹና። እነሆ፥ አኹን መጥተኽ ዐየኹኽ፤ ወደ ዘላለም ሕይወት እሔድ ዘንድ አሰናብተኝ፤ ዓይኖቼ ትድግናኽን ዐይተዋልና። በወገኖችኽ ኹሉ ፊት ያዘጋጀኸውን ለአሕዛብ ብርሃንን ለወገኖችኽ እስራኤልም ክብርን ትገልጥ ዘንድ አለ።

እመቤታችንን እናቱ ድንግል ማርያምንም ይኽ ልጅሽ ከእስራኤል ውስጥ ለብዙዎች ለመውደቃቸውና ለመነሣታቸው በሚፈረድባቸውም ገንዘብ ለምልክት የተዘጋጀ ነው። በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል ብሏታል። ከዚህም በኋላ በሰላም ዐረፈ።

ይኽም የሚታሰብበት ዓመታዊ በዓል ነው ዛሬ የካቲት 08 ቀን 2017 ዓ/ም በወልድያ ጎልጎታ መዝገበ ምሕረት ኢየሱስ ቤተክርስቲያን የተከበረው።

የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት የማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮችን ይወዳጁ ለሌሎችም ያጋሩ።

~ቴሌግራም፡ https://t.me/NWDnews

~ዩቲዩብ፡ https://youtube.com/c/NorthWolloDioceseMedia

~ድረገጽ፡ https://eotc-nw.org

~ፌስቡክ፡https://www.facebook.com/EOTCNWD?mibextid=ZbWK

15 Feb, 09:32
320
Post image

የሰማዕቱ የቅዱስ መርቆሬዎስ ዓመታዊ በዓል ተከብሮ ውሏል።

ጥር ፳፭ ቀን ፳፻፲፯ ዓ/ም (የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት)

ጥር ኻያ ዐምስት ቀን በዓሉ የሚከበርለት የሰማዕቱ ቅ/መርቆሬዎስ ዓመታዊ በዓል በሰሜን ወሎ መንበረ ጵጵስና ሀገረ ስብከት በጉባላፍቶ ወረዳ ቤተክህነት ስር በሚገኘው ገዶ ቅ/መርቆሬዎስ ቤተክርስቲያን ተከብሮ ውሏል።

ይኽች እለት ሰማዕቱ #ቅዱስ_መርቆሬዎስ በሥዕሉ ላይ አድሮ ቅዱሳን ባስልዮስንና ጎርጎርዮስን የረዳበት እለት ናት፡፡

መርቆሬዎስ ማለት የአብ ወዳጅ ወይም የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ማለት ሲኾን መርቆሬዎስ ተብሎ ከመጠራቱ በፊት ፒሉፓዴር እንደነበር ገድሉ ይናገራል።

በዓሉ የተከበረው በዋዜማው ከመንበረ ክብሩ ተነሥቶ በታቦት ማደሪያው ካደረ በኋላ ዛሬ ጥር ፳፭ ቀን ፳፻፲፯ ዓ/ም ወደመንበረ ክብሩ በመመለስ ነው።

የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት የማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮችን ይወዳጁ ለሌሎችም ያጋሩ።

~ቴሌግራም፡ https://t.me/NWDnews

~ዩቲዩብ፡ https://youtube.com/c/NorthWolloDioceseMedia

~ድረገጽ፡ https://eotc-nw.org

~ፌስቡክ፡https://www.facebook.com/EOTCNWD?mibextid=ZbWK

02 Feb, 13:10
533
Post image

በወልድያ ከተማ ውስጥ የሚገኙ የሰንበት ትምህርት ቤቶች የጥምቀት በዓል አከባበርን ገመገሙ።

ጥር 23 ቀን 2017 ዓ.ም (ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት)

በሰሜን ወሎ መንበረ ጵጵስና ሀገረ ስብከት ቤተክህነት የወልድያ ከተማ አስተዳደር የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥራ አስፈጻሚዎችና የወረዳው ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ተወካዮች የከተራ፣ የጥምቀትና የቃና ዘገሊላ በዓላት አከባበርን ዛሬ በሀገረ ስብከቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ገምግመዋል።

በሀገረ ስብከቱ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ ዋና ክፍል አዘጋጅነት በተደረገው በዚሁ የምክክር መርሐ ግብር የሰንበት ትምህርት ቤቶች አባላት በአገልግሎት ላይ ያሳዩት መልካም እንቅስቃሴዎችና በቀጣይ መስተካከል የሚገባቸው ክፍተቶች መነሳታቸውን የክፍሉ ኀላፊ መ/ር ኤርምያስ አዳነ ተናግረዋል።

የሰንበት ትምህርት ቤቶችን በማሠልጠንና በመከታተል ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ጠብቀው እንዲያስጠብቁና መንፈሳዊ ኀላፊነታቸውን እንዲወጡ ለማድረግ ክፍሉ በእቅድ እየሠራ ነው ተብሏል።

የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት የማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮችን ይወዳጁ ለሌሎችም ያጋሩ።

~ቴሌግራም፡ https://t.me/NWDnews

~ዩቲዩብ፡ https://youtube.com/c/NorthWolloDioceseMedia

~ድረገጽ፡ https://eotc-nw.org

~ፌስቡክ፡https://www.facebook.com/EOTCNWD?mibextid=ZbWK

31 Jan, 19:37
707
Post image

ሃይማኖታችኹን በልጆቻችኹ ልብ ላይ ዝሩ || ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ

ሙሉውን በዚኽ ሊንክ ገብተው ያድምጡ!

https://youtu.be/n-s-KbVliqY?si=MKiXhzF-wD3fSF2d

31 Jan, 11:27
1,699