ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተወለደ በ40 ቀኑ ወደ ቤተመቅደስ የገባበት ዓመታዊ የንግስ በዓል በወልድያ ጎልጎታ መዝገበ ምሕረት ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ተከብሯል።
የካቲት 08 ቀን 2017 ዓ/ም (ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት)
ልደተ ስምዖን ከጌታችን ከመድኀኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ንኡሳን በዓላት አንዱ ነው። አበው ስያሜውን የሰጡት ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቤተ መቅደስ በተገኘ ጊዜ የዕድሜ ባለጸጋው አረጋዊው ስምዖን ጌታን ሲታቀፈው ክርስቶስ ስምዖንን ወደ ጎልማሳነት ያደሰበት ዕለት ስለኾነ ነው።
የብሉይ ኪዳንን መጻሕፍት ይተረጒሙ ዘንድ ከተመረጡት መካከል የኾነው ይኽ አረጋዊ፥ ይተረጒመው ዘንድ የደረሰውን የኢሳይያስን መጽሐፍ ምእራፍ 7 ቊጥር 14 በደረሰ ጊዜ የድንግልን መውለድ በመጠራጠሩ ሴት ትወልዳለች ቢልም በእግዚአብሔር መልአክ አማካይነት ድንግል እስክትወልድ በሕይወት እንደሚቆይ ነግሮት ነበር።
ከዚኽም በኋላ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እስከተወለደና በዚች እለት ወደ ቤተ መቅደስ እስከ አስገቡት ድረስ ስምዖን ሦስት መቶ ዓመት ኖረ። ሕፃኑን ጌታችንንም በታቀፈው ጊዜ ታውረው የነበሩ ዓይኖቹ ተገለጡ፤ ኹለመናውም አዲስ ሆነ። መንፈስ ቅዱስም የምትጠብቀው የነበረ ሕፃን ይኽ ነው ብሎ ሲነግረው እግዚአብሔርን አመሰገነው። ባርያኽን በሰላም አሰናብተው። በአንተ ምክንያት በዚኽ በኀላፊው ዓለም ሕይወት ታስሬ ኖሬአለኹና። እነሆ፥ አኹን መጥተኽ ዐየኹኽ፤ ወደ ዘላለም ሕይወት እሔድ ዘንድ አሰናብተኝ፤ ዓይኖቼ ትድግናኽን ዐይተዋልና። በወገኖችኽ ኹሉ ፊት ያዘጋጀኸውን ለአሕዛብ ብርሃንን ለወገኖችኽ እስራኤልም ክብርን ትገልጥ ዘንድ አለ።
እመቤታችንን እናቱ ድንግል ማርያምንም ይኽ ልጅሽ ከእስራኤል ውስጥ ለብዙዎች ለመውደቃቸውና ለመነሣታቸው በሚፈረድባቸውም ገንዘብ ለምልክት የተዘጋጀ ነው። በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል ብሏታል። ከዚህም በኋላ በሰላም ዐረፈ።
ይኽም የሚታሰብበት ዓመታዊ በዓል ነው ዛሬ የካቲት 08 ቀን 2017 ዓ/ም በወልድያ ጎልጎታ መዝገበ ምሕረት ኢየሱስ ቤተክርስቲያን የተከበረው።
የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት የማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮችን ይወዳጁ ለሌሎችም ያጋሩ።
~ቴሌግራም፡ https://t.me/NWDnews
~ዩቲዩብ፡ https://youtube.com/c/NorthWolloDioceseMedia
~ድረገጽ፡ https://eotc-nw.org
~ፌስቡክ፡https://www.facebook.com/EOTCNWD?mibextid=ZbWK
ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

Similar Channels



የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ እና የዘመናዊ መረጃ ምንጮች
የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ በሰሜን ወሎ ክልል ውስጥ በፖለቲካ ውሎ በሚኖሩ ምርጥ የሚዲያ መረጃ ምንጮችን ከአስፈላጊ ምርጥ የእውቀት መረጃ መረጃ ይደርሳል። ይህ ቻናል በመምህራን ታሪክ እና በዓለም ታሪክ የተመለከተ ምርጥ ምርጥ ይደርሳል። እንደዚህ የሚገኝ እውቀት መረጃ በዕድል አስፈላጊ ነው።
የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ዋነኛ ግንባር ምንድን ነው?
የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ በሰሜን ወሎ ክልል ውስጥ በደረጃዎች ተገድሺ ነው። በዚህ ቻናል የሚከናወኑ ስብከቶች ላይ በመዳረሻ እንዲሁም የቤተክርስቲያን አገልግሎት ይቀርባሉ።
ከሌላ የሚዲያ ተግባራት መሰረት በቤተ ክርስቲያን መንደር ይገኛሉ። ይህ ጉዳይ መረጃታዊ እንዲኖሩ ይህ ድረ-ገጽ የዚህ ቻናል ይወስነዋል።
የቻናሉ መለያ ምንድን ነው?
የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ በቴሌግራም ላይ ይገኛል። በቻናሉ ወይም በመዳረሻም የሚከወኑ የጋብዝ ይሆናሉ።
ይህም ለህዝቡ ማዕከል ወይን ይወስዳል። በአማርኛ እንዲሁም በሌላ ምርጥ የሚሰጠውን የሚዲያ ገጽታ እንዲመለከተው ይገኛል።
በሚዲያ የሚከናወኑ ስብከቶች ምን እንደሚያቀርባሉ?
በዚህ ቻናል የሚነሳ ወይም የሚቀርባው መረጃ ስብከቶች የአስተዳደር ወገኖች ቢያነሱ ይቀርባሉ።
የተቀባይነት መንገድ ወይም የትምህርቶች መግለጥ ይሆናል። ይህም በአማርኛ የተነቃቃ ሥራ ወይም የቴሌግራም ወረቀት ማሳያ ይቀርባል።
የሚዲያው ውስጥ ምን እንደሚያይቅ አይቁ?
ይህ ድረ-ገጽ ኢንተርኔት ገጽታን ይኖራል ወይም ያልተሳማ የተሳሳቢ ክንውና ይለዋወጣል።
አንዳንድ ግለሰቦች በቱርሱ እና ግዢት ዝርዝር ይቀየሩ የተለዋዋጮቹ ዝርዝር አገልግሎት ላይ ይኖራል።
ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ Telegram Channel
መርሐ ግብርድን የብፁዕ አቡነ ኤርምያስንና የብፁዕ አቡነ ቄርሎስን እና የሌሎች መምህራን ትምህርቶችን፣ ስብከቶችንና ተግሳጾችን በተጨማሪም ሀገረ ስብከቱ ዓበይት ክንውኖችን የሚተላለፉበት የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት አዝናኝ ቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራምን ቤተሰብ በመሆንና ለሌሎች በመጋበዝ የቤተክርስቲያንን አገልግሎት ያፋጥኑ።