ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌 @rihu_islamic_post Channel on Telegram

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

@rihu_islamic_post


ከናንተም ወደ በጎ ነገር የሚጠሩ በመልካም ሥራም የሚያዙ ከክፉ ነገርም የሚከለክሉ ሕዝቦች ይኑሩ፡፡ እነዚያም እነሱ የሚድኑ ናቸው፡፡[3:104]

ስህተቶች ስታገኙ አስታከክሉን በረከሏሁ ፊኩም
GP @Rihu_islamic_Discussion

ከናንተም ወደ በጎ ነገር (Amharic)

እንኳን ለእናንተም እና ለበጎ ነገር የምልክበት ወደ በጎ ነገር ሜዳተ ሥራ እንዲሆን ብዙ ትእዛዝ ከናንተም በትር ወደ በጎ ነገር የመረጃዋን ይከታተሉ፡፡ ከክፉ ነገር ላይ ወደ በጎ ነገር ሜዳተ ሕጋም የምንያዙ ሕዝቦችን በመልኩ ይበልጥል፡፡ የፖስት ማስታወቂያዎችን ለማግኘት የሚየተዘምናና ምሳሌና እንዘምንዎትን ወደ በጎ ነገር እንደሚያሰፋል በመሆኑ እነዚያ ሌሎች የእስላም ተባንኖች ናቸው፡፡ በበዎ አባላትና በበዝነኝ ተመሷሷል፡፡፡ እባኮት በ@Rihu_Tube_bot ያስሩት፡፡ በተጨማሪ አገባብ ወደ @Rihu_islamic_Discussion እንቀርባለን፡፡

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

20 Feb, 15:16


🌷ጥያቄ

🌹ጾም በኛ ላይ እንደተደነገገዉ ከኛ በፊት በነበሩ ህዝቦችም ላይ ተደንግጎ ነበር?


🍓 ከትክክለኛው መልስ ጀርባ የሚመጣላቹን  በመንካት  ተጠቀሙ

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

17 Feb, 14:51


👾ነቢዩ 〽️🤍〽️በሂወት ዘመናቸዉ ስንት የረመዷን ወሮችን ጹመዋል?
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

😈〽️አስር

🥶〽️ስምንት

⚡️〽️ዘጠኝ

🌼〽️አስራ አንድ


መልሱን በመንካት ጠቃሚ ነገር ያግኙ 😋

✅ ትክክል ከሆናቹ ▫️Add ˢᵘⁿᵃʰ ʷᵃᵛᵉ ▫️የሚል ይመጣላቹሃል 🎴

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

16 Feb, 06:41


📚ሴቶች ላይ ያተኮሩ ምክሮች


ፀሃፊ ፦ አል ሸይኽ አብዱረዛቅ አል በድር

ክፍል........ስድስት


🔘የሴት ልጅ መረጋጋት ቤቷ በመርጋቷ ነው

እናንተ የሙስሊሞች ስብስብ ሆይ ፦አላህ ለዚህ ቀጥ ላለ ሃይማኖት እኛን በመምራቱ የዋለልን ውለታ እና ፀጋ እጅግ ግዙፍ ነው።

ዲነል ኢስላም አላህ የሰዎችን እምነት፣ ባህሪ እና ስራ ያስዋበበት የሰውን ውጫዊም ውስጣዊም አካልን ያስተካከለበት የሆነ ሃይማኖት ነው ።
ይሄን ሃይማኖት አጥብቆ የያዘ ነጻ ይወጣል እሱን የተወ ደግሞ ካማረ እና ብልጫ ካለው ስራ እና ባህሪ ያገለለ ይሆናል ።
እውነት መፈክሩ እና መዞሪያው፣ ፍትህ መቆሚያው፣ እዝነት መገንቢያው፣ መልካም ነገር ተቆራኙ ፣ መስተካከል እና ማስተካከል ግቡ የሆነ ድንቅ ሃይማኖት ነው ።

አላህ ለዚህ ታላቅ ዲን ስለመራን እና ከባልተቤቶቹም ስላደረገን ጠዋት ማታ ልናመሰግነው እና በዚህ ዲን ላይ እንዲያጸናን ዘወትር ልንማጸነው ይገባል ።

ይህ ሃይማኖት በመልካም እና ቀጥ ባሉ መንገዶች እና ህግጋቶች መጥቷል ።ህግጋቱም ባሮቹን ለማስተካከል፣ ደስታቸውን እና እድለኝንታቸውን ለማረጋገጥ እና የፈተና እና ጥፋት በሮችን ለመዝጋት የመጡ የተጠኑ እና የረቀቁ ህግጋት ናቸው ።
ታዲያ ሴት ልጅ እሷን በመነጠል የመጡ የአላህ እና የመልዕክተኛውﷺ ትዕዛዛት እና ህግጋትን አጥብቃ ከያዘች በደስታ ጥቡቅነት እና የበላይነት የተሞላ ህይወትን በሁለቱም አለም ትኖራለች።
አላህ አንድ ሙስሊም ሴትን የእስልምና ህግጋትን እና ስርአቶች እንድትይዝ ከገጠማት እና ልቧን ክፍት ካደረገላት ደስተኛ ትሆናለች እራሷንም ማህበረሰቡንም ከፈተናዎች ታድናለች። ምክኒያቱም ሴት ልጅ ፈተና ናትና
የሴት ልጅ ፈተና እጅግ ከባድ ነው የፍጡራን አይነታ የሆኑት ሙሃመድﷺ በህዝቦቻቸው ላይ የፈሩት ፈተናም ነው ።
ታዲያ አንዲት ሴት የእስልምና ስርአቶችን እና ማመላከቶችን ከያዘች እራሷንም ማህበረሰቡንም ከፈተናዎች እና ጥፋቶች ትጠብቃለች ።
አንድ ሙስሊም ሴት ቁርአንን ልታነብ እና ልታስተነትን የመልክተኛውን ንግግሮች ልትማር እና የተማረቻቸውን ህግጋት እና ስርአቶች ያለመወላወል እና ቸልተኝነት ልትፈጽም ይገባታል።
እነዚህ ህግጋት ደግሞ የሁለቱም አለም ህይወቷ እንዲስተካከል እና በደስታ እና እርጋታ እንድታሳልፋቸው ምክንያት ናቸው ።

አላህ ይጠብቀንና ከፊል ሙስሊም ሴቶች ከእስልምና ህግጋት እና ትእዛዛት አፈንግጠው በውዳቂ ቦታዎች እና ጥፋት ላይ ናቸው።
አብዛኞቹ ከእድሜያቸ አብዛኛውን ያሳለፉት ከእስልምና ህግጋት እና ስርአቶች ርቀው ነው ።
እነዚህንም ህግጋት እና ስርአቶች ችላ በማለታቸው ትልቅ ሽንፈት እና ውድቀት እንደደረሰባቸው ሲናገሩ ይደመጣሉ። እድለኛ ማለት በሌሎች የተመከረ እድለቢስ ደግሞ ሌሎች በሱ የተመከሩበት ነው ።

ሙስሊም ሴት የ እስልምና ህግጋትን እና ስርአቶች ስታስተነትን ህግጋቶቹ ከፊል የ ኢስላም ጠላቶች እንደሚሞግቱት እሷን ለማጨናነቅ እና ነጻነቷን ለማሳጣት እና ለመገደብ የመጡ እንዳልሆኑ ትረዳለች።
እንደውም ሴትን ከፈተና አደጋ እና ጥፋት አርቆ የተከበር እና የተረጋጋ ህይወት እንድትኖር የሚያደርጋት ነው ።

አላህ በተከበረዉ ቃሉ እንዲህ ይላል :-

وَقَرْنَ فِى بُيُوتِكُنَّ وَلَا تَبَرَّجْنَ تَبَرُّجَ ٱلْجَٰهِلِيَّةِ ٱلْأُولَىٰ
👇👇

ሴት ልጅ ቤቷ ውስጥ ከረጋች እርጋታ እና ሰላም ይረጋገጥላታል ግን ዝም ብሎ ያለምክንያት እና ጉዳይ ወጣ ገባ የምታበዛ ከሆነች ግን ከእርጋታ እና ሰላም ትርቃለች ።
ሴት ልጅ ቤቷ ውስጥ የራሷ የሆነ ሃላፍትና አላት ቤቷን መያዝ መጠበቅ እና ቤቷ ውስጥ መርጋት እና ማዘውተር ከሷ የሚጠበቅ እና የሚፈለግ ነገር ነው ከቤቷ ከወጣችም ደግሞ ያለ ጉዳይ እና ምክንያት ሊሆን አይገባም።
ለአሳሳቢ ጉዳይ ከቤቷ ከወጣች የ እስልምና ስርአትን በጠበቀ መልኩ ሊሆን ይገባል የተገላለጠች ፣የተጋጌጠች ፣ውበቷን ግልጽ አድርጋ ፣ሽቶ ተቀብታ እና የተዋበች ሆና ልትወጣ አይገባትም ።
ቤቷ ረግታ ጥቡቅነቷን ያስጠበቀችን ሴት ደግሞ ወንድ ልጅ ክብሯን እና ብልጫዋን ሊጠብቅ እና ሊንከባከብላት ግድ ይለዋል። በወንድ እና ሴቶች መካከል መደባለቅ እና መገለልም ሊኖር አይገባም።

ከኡቅበት ቢን አምር እንደተወራው የአላህ መልዕክተኛﷺ እንዲህ ብለዋል "ሴቶች ጋር መግባትን ተጠንቀቁ "
ሴት ልጅ ቤቷ እንድትረጋ ታዛለች ወንድ ደግሞ ሴቶች ባሉበት ቦታ ላይ ዝም ብሎ እንዳይገባ ተከልክሏል ። ይህም ተከትሎ የሚመጣውን ፈተና እና ጥፋት ለመከላከል ነው ።
የአላህ መልዕክተኛ ﷺ ወንዶችን ሴቶች ጋር እንዳይገቡ ሲከለክሉ አንድ ከአንሷር የሆነ ሰው ጠየቃቸው ፦
"አንቱ የአላህ መልዕክተኛ ሆይ የ ባል ዘመድ እንደ
የባል ወንድም የባል አጎት እና የባል የአጎት ልጅንም ያካትታል? "

(እንደዚህ ቅርበት ያላቸውም ቢሆኑም ሴቶች ጋ መግባት ለነሱም ይከለከላል እነሱንም ያካትታል?)

መልዕክተኛውም ﷺ "እሱማ ሞት ነው " ብለው መለሱ

ይሄን ትልቅ ማንቂያ እና ማስጠንቀቂያን እናስተንትን ፦
መልዕተኛውﷺ "ሞት ነው " ብለው በሞት መስለው እንደማይቻል እና እንደውም ትልቅ አደጋ እምደሆነ የገለጹት ቅርብ የሆነን የባል ወንድም፣ የባል አጎት አሊያም የባል የአጎትን ልጅ ነው ታዲያ ምንም ቅርበት የሌለው ሩቅ የሆነ ባዕድ ወንድስ እንዴት ሊሆን ነው?

መልዕክተኛውﷺ "ሞት ነው " ብለው በሞት የገለፁት፦
ስርአትን ማጣት ከሞት የማይተናነስ በመሆኑ ነው
አዎ በእርግጥም አደብን ያጣ ሰው ሊራመድ፣ ሊበላ፣ ሊጠጣ፣ ሊናገር ይችላል ግና በእውነታው የሞተ እንጂ ሌላ አይደለም። ምክንያቱም ክብር እና ጥቡቅነት ከሱ ላይ ሞተዋልና ።

ክብር ይሞታል ጥቡቅነት እና መልካም ስነ ምግባርም ይሞታል ለመሞታቸውም ምክንያት አላቸው ዲነል ኢስላም ደግሞ ሰዎችን ከክብር ጥቡቅነት እና መልካም ስነምግባር ሞት ሊጠብቃቸው ነው የመጣው ።

በዚህ ፈተናው በየአቅጣጫው በተንሰራፋበት ዘመን ሙስሊም ሴት የከሃዲያንን ውዳቂ የሆነ የጥፋት መንገድ በመከተል ለውድቀት ጥፋት እና መዘናበል ተጋልጣለች። በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች በምትመለከታቸው ነገሮች ተታላ ክብር እና ጥቡቅነቷን እያጣች ትገኛለች ።

በአሁን ሰአት በጣም ከባድ የፈተና ወቅት ላይ እንገኛለን ታዲያ ክብራችንን ለመጠበቅ እና ለማስጠበቅ በየአቅጣጫው ልንታገል ግድ ይለናል ።

ሴት ልጅ በ እስልምና ስርአት ስር ከኖረች የተከበረ እና የተረጋጋ ህይወት ትኖራለች ማህበረሰቧንም ታስከብራለች ግን የኢስላም ጠላቶችን ጥሪ ሰምታ ከተዘናበለች እራሷንም ማህበረሰቧንም ጥፋት እና ፈተና ላይ ትጥላለች

አንድ ሙስሊም ሴት አሁን ያላት ውበት እራሷ የምትደነቅበት እና ሌሎችን ደግሞ የምትፈትንበት ውበቷ ከእለታት በአንዱ ቀን እንደሚጠፋ መሬት ስር ገብቶ አፈር እንደሚደፋበት እና የተለያዩ ትላትሎችም እንደሚበሉት እና እንደሚበሰብስ ልትዘነጋ አይገባም ።
ያኔ በዛች ጠባብ ቤት ውስጥ ውበቷ ረግፎ ከስራዋ ጋር ትገናኛለች

አንቺ ሙስሊሟ እህቴ ሆይ ፦አላህን ተጠንቀቂ ጥፍጥናን ቆራጭ ለሆነው ለሞት ጊዜ ለዛ ጨለማ ቤት እና የሰራሽውን ሁሉ ለምትጠየቂበት አስፈሪ ቀን የሚሆንሽ ስራ አዘጋጂ!!!!!!!!!

ይቀጥላል………………

منقول

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

16 Feb, 06:41


ሴቶች ላይ ያተኮሩ ምክሮች

ፀሃፊ ፦ አል ሸይኽ አብዱረዛቅ አል በድር

ክፍል........ስምንት

🔘የልብስ ጸጋ እና ፈተናዎቹ

የአላህ ጸጋዎችን ማስታወስ ሃያሉን እና ሁሉን ቻይ የሆነውን ጌታ አላህ ለማመስገን ታላቅ ሰበብ ነው
ማመስገን ደግሞ የተሰጠን ጸጋ ላይ እንዲጨመርልን ሰበብ ነው

አላህ ለባሮቹ ከዋላቸው ታላላቅ ጸጋዎች መካከል አንዱ ሃፍረተ ገላቸውን የሚሸፍኑበት ንጹህ እና የተዋቡ ሆነው የሚቀርቡበት ልብስን መስጠቱ ነው
ለዚህም ነው አላህ በሱረቱ አል ነህል ላይ ይሄን ታላቅ ጸጋ እንዲ ሲል የገለጸው እና የቆጠረው

وَٱللَّهُ جَعَلَ لَكُم مِّنۢ بُيُوتِكُمْ سَكَنًۭا وَجَعَلَ لَكُم مِّن جُلُودِ ٱلْأَنْعَٰمِ بُيُوتًۭا تَسْتَخِفُّونَهَا يَوْمَ ظَعْنِكُمْ وَيَوْمَ إِقَامَتِكُمْ ۙ وَمِنْ أَصْوَافِهَا وَأَوْبَارِهَا وَأَشْعَارِهَآ أَثَٰثًۭا وَمَتَٰعًا إِلَىٰ حِينٍۢ
አላህም ከቤቶቻችሁ ለእናንተ መርጊያን አደረገላችሁ፡፡ ከእንስሳዎችም ቆዳዎች በጉዟችሁ ቀን በመቀመጫችሁም ቀን የምታቀልላቸውን ቤቶች ለናንተ አደረገላችሁ፡፡ ከበግዋ ሱፎች፣ ከግመልዋም ጠጉሮች፣ ከፍየልዋም ጠጉሮች የቤት ዕቃዎችን እስከ ጊዜም ድረስ መጠቃቀሚያን (አደረገላችሁ)፡፡
وَٱللَّهُ جَعَلَ لَكُم مِّمَّا خَلَقَ ظِلَٰلًۭا وَجَعَلَ لَكُم مِّنَ ٱلْجِبَالِ أَكْنَٰنًۭا وَجَعَلَ لَكُمْ سَرَٰبِيلَ تَقِيكُمُ ٱلْحَرَّ وَسَرَٰبِيلَ تَقِيكُم بَأْسَكُمْ ۚ كَذَٰلِكَ يُتِمُّ نِعْمَتَهُۥ عَلَيْكُمْ لَعَلَّكُمْ تُسْلِمُونَ
አላህም ከፈጠረው ነገር ለእናንተ ጥላዎችን አደረገላችሁ፡፡ ከጋራዎችም ለእናንተ መከለያዎችን አደረገላችሁ፡፡ ሐሩርንም (ብርድንም) የሚጠብቋችሁን ልብሶች የጦራችሁንም አደጋ የሚጠብቋችሁን ጥሩሮች ለእናንተ አደረገላችሁ፡፡ እንደዚሁ ትሰልሙ ዘንድ ጸጋውን በእናንተ ላይ ይሞላል፡፡
فَإِن تَوَلَّوْا۟ فَإِنَّمَا عَلَيْكَ ٱلْبَلَٰغُ ٱلْمُبِينُ
(ከኢስላም) ቢሸሹም ባንተ ላይ ያለብህ ግልጽ ማድረስ ብቻ ነው፡፡
يَعْرِفُونَ نِعْمَتَ ٱللَّهِ ثُمَّ يُنكِرُونَهَا وَأَكْثَرُهُمُ ٱلْكَٰفِرُونَ
የአላህን ጸጋ ያውቃሉ፡፡ ከዚያም ይክዷታል፡፡ አብዛኞቻቸውም ከሓዲዎቹ ናቸው፡፡

አላህ እዚህ የቁርአን አንቀጽ ላይ ለባሮቹ ከተለያዩ ነገራት የሚሰሩ ከሃሩርም ሆነ ብርድ የሚጠብቋቸው የሚዋቡባቸው እና ሃፍረተ ገላቸውንም የሚሸፍኑበት ልብስን መስጠቱ ከታላላቅ ጸጋዎቹ እንደሆነ ገለጸ

ልብስ አንድ ሙስሊም ባሪያ ሊያመሰግንበት የሚገባ ግልጽ እና ታላቅ ጸጋ ለመሆኑ ጥርጥር የለውም
አላህ ባዘዘው እና በሚወደው ነገር ላይ ሊጠቀመውም ይገባል
ሸሪአ ካስቀመጠው የአለባበስ መስፈርት የወጣ እና ስርአቱን እና የአለባበስ ሁኔታውን በተጻረረ መልኩ ከመጠቀምም መጠንቀቅ አስፈላጊ ነው

አንድ ሙስሊም በአለባበሱ ላይ ሸሪአን የተጻረረ እንዲሆን የሚያደርገውን የሸይጣንን ተንኮል እና የተደበቀ ሴራ ሊጠነቀቅ ይገባዋል
አላህም ሸይጣን ከሰው ልጅ ጋር ያለው ጠላትነት የቀደመ እና የቆየ እንደሆነ ገልጾልናል

ሸይጣን አባታችን አደምን እና እናታችን ሃዋን ሃፍረተገላቸው እንዲገለጽባቸው የተጠቀመውን ዘዴ እና ጥሩ አሳቢ እና መካሪ መስሎ እየማለ እንዴት እንዳሳሳታቸው እና ከነበሩበት ታላቅ ደረጃ እንዴት እንዲወርዱ እንዳደረጋቸው አላህ በተከበረው ቃሉ እንዲህ ገልጾታል

وَيَٰٓـَٔادَمُ ٱسْكُنْ أَنتَ وَزَوْجُكَ ٱلْجَنَّةَ فَكُلَا مِنْ حَيْثُ شِئْتُمَا وَلَا تَقْرَبَا هَٰذِهِ ٱلشَّجَرَةَ فَتَكُونَا مِنَ ٱلظَّٰلِمِينَ
«አዳም ሆይ! አንተም ሚስትህም በገነት ተቀመጡ፡፡ ከሻችሁትም ስፍራ ብሉ፡፡ ግን ይህችን ዛፍ አትቅረቡ፡፡ ራሳቸውንከሚበድሉት ትኾናላችሁና» (አላቸው)፡፡

فَوَسْوَسَ لَهُمَا ٱلشَّيْطَٰنُ لِيُبْدِىَ لَهُمَا مَا وُۥرِىَ عَنْهُمَا مِن سَوْءَٰتِهِمَا وَقَالَ مَا نَهَىٰكُمَا رَبُّكُمَا عَنْ هَٰذِهِ ٱلشَّجَرَةِ إِلَّآ أَن تَكُونَا مَلَكَيْنِ أَوْ تَكُونَا مِنَ ٱلْخَٰلِدِينَ
ሰይጣንም ከሐፍረተ ገላቸው የተሸሸገውን ለእነርሱ ሊገልጽባቸው በድብቅ ንግግር ጎተጎታቸው፡፡ «ጌታችሁም መልኣኮች እንዳትኾኑ ወይም ከዘላለም ነዋሪዎች እንዳትኾኑ እንጂ ከዚህች ዛፍ አልከለከላችሁም» አላቸው፡፡

وَقَاسَمَهُمَآ إِنِّى لَكُمَا لَمِنَ ٱلنَّٰصِحِينَ
«እኔ ለእናንተ በእርግጥ ከሚመክሩዋችሁ ነኝ» ሲልም ማለላቸው፡፡

فَدَلَّىٰهُمَا بِغُرُورٍۢ ۚ فَلَمَّا ذَاقَا ٱلشَّجَرَةَ بَدَتْ لَهُمَا سَوْءَٰتُهُمَا وَطَفِقَا يَخْصِفَانِ عَلَيْهِمَا مِن وَرَقِ ٱلْجَنَّةِ ۖ وَنَادَىٰهُمَا رَبُّهُمَآ أَلَمْ أَنْهَكُمَا عَن تِلْكُمَا ٱلشَّجَرَةِ وَأَقُل لَّكُمَآ إِنَّ ٱلشَّيْطَٰنَ لَكُمَا عَدُوٌّۭ مُّبِينٌۭ

በማታለልም አዋረዳቸው፡፡ ከዛፊቱም በቀመሱ ጊዜ ኀፍረተ ገላቸው ለሁለቱም ተገለጠችላቸው፡፡ ከገነት ቅጠልም በላያቸው ላይ ይደርቱ ጀመር፡፡ ጌታቸውም «ከዚህ ዛፍ አልከለከልኋችሁምን᐀ ሰይጣንም ለእናንተ ግልጽ ጠላት ነው አላልኳችሁምን᐀» ሲል ጠራቸው፡፡

قَالَا رَبَّنَا ظَلَمْنَآ أَنفُسَنَا وَإِن لَّمْ تَغْفِرْ لَنَا وَتَرْحَمْنَا لَنَكُونَنَّ مِنَ ٱلْخَٰسِرِينَ
«ጌታችን ሆይ! ነፍሶቻችንን በደልን፡፡ ለእኛ ባትምር ባታዝንልንም በእርግጥ ከከሳሪዎቹ እንኾናለን» አሉ፡፡
👇👇👇👇👇

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

16 Feb, 06:41


ታዲያ ሸይጣን አሁንም በዚያ ጥመቱ እና እምቢ ባይነቱ እንደቀጠለ ነው ልክ እነሱንም እንዳሳሳተው ዝርያቸውንምንም ለማሳሳት ቆርጦ እንደተነሳ እና እየለፋ እንዳለ ነው ለዚያም ነው አላህ እነሱን እንዴት እንዳሳሳተ ከገለጸ ብኋላ ለነሱ ዝርያዎችም እንዲህ ሲል ያስጠነቀቀው፦

يَٰبَنِىٓ ءَادَمَ قَدْ أَنزَلْنَا عَلَيْكُمْ لِبَاسًۭا يُوَٰرِى سَوْءَٰتِكُمْ وَرِيشًۭا ۖ وَلِبَاسُ ٱلتَّقْوَىٰ ذَٰلِكَ خَيْرٌۭ ۚ ذَٰلِكَ مِنْ ءَايَٰتِ ٱللَّهِ لَعَلَّهُمْ يَذَّكَّرُونَ
የአዳም ልጆች ሆይ! ኀፍረተ ገላችሁን የሚሸሽግን ልብስ ጌጥንም በእርግጥ በናንተ ላይ አወረድን፡፡ አላህን የመፍራትም ልብስ ይህ የተሻለ ነው፡፡ ይህ ከአላህ ታምራቶች ነው፡፡ ይገሠጹ ዘንድ (አወረደላቸው)፡፡

يَٰبَنِىٓ ءَادَمَ لَا يَفْتِنَنَّكُمُ ٱلشَّيْطَٰنُ كَمَآ أَخْرَجَ أَبَوَيْكُم مِّنَ ٱلْجَنَّةِ يَنزِعُ عَنْهُمَا لِبَاسَهُمَا لِيُرِيَهُمَا سَوْءَٰتِهِمَآ ۗ إِنَّهُۥ يَرَىٰكُمْ هُوَ وَقَبِيلُهُۥ مِنْ حَيْثُ لَا تَرَوْنَهُمْ ۗ إِنَّا جَعَلْنَا ٱلشَّيَٰطِينَ أَوْلِيَآءَ لِلَّذِينَ لَا يُؤْمِنُونَ
የአዳም ልጆች ሆይ! ሰይጣን አባትና እናታችሁን ኀፍረተ ገላቸውን ሊያሳያቸው ልብሶቻቸውን ከነሱ የገፈፋቸው ሲኾን ከገነት እንዳወጣቸው ሁሉ እናንተን አይሞክራችሁ፡፡ እነሆ እርሱ ከነሰራዊቱ ከማታዩዋቸው ስፍራ ያዩዋችኋልና፡፡ እኛ ሰይጣናትን ለእነዚያ ለማያምኑት ወዳጆች አድርገናል።

እዚህ ቦታ ላይ አላህ ሁለት አይነት ልብሶችን ገልጾ እነሱም ታላቅ ጸጋ መሆናቸውን አወሳ ፦

♦አንደኛው ልብስ ውስጣዊ የሆነ የተቅዋ ልብስ ሲሆን እሱም ባለቤቱ እንከጠበቀው እና እስከተንከባከበው ድረስ የማይጠፋ እና የማያረጅ የመንፈስም የልብም ውበት ነው ።
♦️ ሁለተኛው የልብ አይነት ደግሞ ውጫዊ ይሆነ ሃፍረተ ገላን የሚሸፍን ልብስ ሲሆን እሱም ለሰው ልጅ ውበት እና ሞገስ የሚሰጥ ነው ።

አንድ ሰው ውጫዊ የሆነ ልብሱን ካወጣው እና ከጣለው አፍረተ ገላው ይገለጣል ።
የውስጣዊ ልብሱን ተቅዋን ካጣ  ደግሞ ውርደት እና የበታችነት ይገጥመዋል ከሃያዕ እና  ከጥቡቅነት ያገለለ የጥፋት ህይወትን ይኖራል።

ታዲያ አንዲት ሴት በነፃነት ስም እና ለሷ አሳቢ መስለው ጥቡቅነቷን እንድታጣ ፣ ልብሷን መሸፈኛዋን እንድትጥል ፣ እንድትገላለጥ የሚገፋፏትን ሴረኞች ችላ ብላ ሴራቸውን ልታከሽፍባቸው ይገባል ።

ሰውነትን የሚገላልጡ ልብሶችን እንድትለብስ እና እንድትወድ ፣ ሙስሊም ያልሆኑ ለእራሳቸው ጠፍተው ሊሎችንም አጥፊ የሆኑ ሴቶችን መንገድ እንድትከተል እና አርአያ አድርጋ እንድትይዛቸው የሚገፋፏትን አካላት በዲኗ በሃያእዋ እና በሂጃቧ ተውባ ተስፋ ልታስቆርጣቸው ቆርጣ መነሳትም አለባት።

ይቀጥላል …………

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

16 Feb, 06:41


ሴቶች ላይ ያተኮሩ ምክሮች


ፀሃፊ ፦ አል ሸይኽ አብዱረዛቅ አል በድር

ክፍል........ሰባት

🔘[وَقُل لِّلْمُؤْمِنَٰتِ يَغْضُضْنَ مِنْ أَبْصَٰرِهِنَّ وَيَحْفَظْنَ فُرُوجَهُنَّ………]
ሚለውን የቁርአን አንቀፅ ማስተንተን


🔻وَقُل لِّلْمُؤْمِنَٰتِ يَغْضُضْنَ مِنْ أَبْصَٰرِهِنَّ وَيَحْفَظْنَ فُرُوجَهُنَّ وَلَا يُبْدِينَ زِينَتَهُنَّ إِلَّا مَا ظَهَرَ مِنْهَا ۖ وَلْيَضْرِبْنَ بِخُمُرِهِنَّ عَلَىٰ جُيُوبِهِنَّ ۖ وَلَا يُبْدِينَ زِينَتَهُنَّ إِلَّا لِبُعُولَتِهِنَّ أَوْ ءَابَآئِهِنَّ ..............

ከፍ ያለው እና የላቀው አላህ በዚህ ታላቅ የቁርአን አንቀጽ ውስጥ አማኝ ሴቶችን አይናቸውን እንዲሰብሩ እና ብልቶቻቸውንም እንዲጠብቁ አዟል። እንዲሁም ሌሎችም ሴት ልጅ ላይ የተንጠለጠሉ ህግጋቶችንም አውስቷል ።
አላህ ይሄን ትዕዛዝ እና ህግጋት ያወሳው በዚህ ዙሪያ ከወንዶችም ጋር የሚገናኝን አንቀፅ ካወሳ ብኋላ ነው።
ከዚህ አንቀጽ በፊት አላህ ወንድ አማኞችንም በተመለከተ እንዲህ ብሏል፦
📌قُل لِّلْمُؤْمِنِينَ يَغُضُّوا۟ مِنْ أَبْصَٰرِهِمْ وَيَحْفَظُوا۟ فُرُوجَهُمْ ۚ ذَٰلِكَ أَزْكَىٰ لَهُمْ ۗ إِنَّ ٱللَّهَ خَبِيرٌۢ بِمَا يَصْنَعُونَ
ለምእመናን ንገራቸው፡- ዓይኖቻቸውን (ያልተፈቀደን ከማየት) ይከልክሉ፤ ብልቶቻቸውንም ይጠብቁ፤ ይህ ለነሱ የተሻለ ነው፤ አላህ በሚሠሩት ሁሉ ውስጥ ዐዋቂ ነው፡፡

እይታን መስበር ወንዶችም ሴቶችም የታዘዙበት ነገር ነው። የተከለከለን መመልከት ደግሞ ወደ ዝሙት እና ጸያፍ ነገሮች ከሚያዳርሱ መዳረሻዎች ውስጥ ዋነኛው ነው ። እይታውን ልቅ የሚያደርግ ፣እዚህም እዚያም የሚመለከት እና የአላህን ክልከላት የማይከለከል ሰው ሃራም ላይና ጸያፍ ነገር ላይ ለመውደቅ የቀረበ ነው ።
📌 [وَقُل لِّلْمُؤْمِنَٰتِ]
አላህ እዚህ ቦታ ላይ ለምዕመናት ንገራቸው ሲል "ምዕመናት" የሚለውን ታላቅ አጠራር ተጠቀመ ይሄም በዚህ አገላለፅ የምትገለጽ የሆነች እውነተኛ አማኝ ሴት የአላህን ህግጋት ይሄ ይሆናል ይሄ አይሆንም ፣ ይሄ ይመቸኛል ፣ይሄ አይመቸኝም ሳትል ምንም ሳትወላውል የምትቀበል ለአላህ ህግጋት እጅ እግሯን የምትሰጥ ስለሆነች ነው ።
📌 [وَقُل لِّلْمُؤْمِنَٰتِ يَغْضُضْنَ مِنْ أَبْصَٰرِهِنَّ]
አላህ እይታን መስበርን ባዘዘባቸው ቦታዎች ላይ እይታን መስበር አስፈላጊ ነው ።
ከዚህም ጋር አንድ ወንድን በቀጥታ መመልከትም ሆነ ፎቶውን መመልከት እኩል ናቸው ።ሁለቱም አይነት ሁኔታዎች ላይ መጨረሻቸው አንድ እና የሚታወቅ ነገር በመሆኑ የተከለከለ ይሆናል።
እይታዋን የማትሰብር ሴት እራሷን ለበርካታ አደጋዎች ያጋለጠች ናት። ሸይጣንም ቀስ በቀስ በማዘናጋት መጠቀሚያ ያደርጋታል ።
ከባድ ፈተና እና ፀያፍ ነገር ላይ ወድቀው የምናያቸው ሴቶችን ሁኔታ ብናጤን ጅማሮው እይታን ልቅ መማድረግ፣ አጥፊ የሆኑ ፎቶግራፎችን እና ሚዲያዎችን በመመልከት እና በማዘውትር አሊያም ዘፈኖችን በማዳመጥ ነው።
ለዚህም አላህ እይታን በመስበር ጀመረ
ይህም ወደ ጸያፍ ነገር የሚያዳርስ የመጀመሪያም መዳረሻ በመሆኑ ነው። ከዚህም ጋር የተከለከሉ የሆኑ ወደ ሃራም የሚያዳርሱ ዘፈኖችን ማድመጥ ፣የተከለከሉ የሆኑ ፎቶግራፎችን መመልከት ፣ ባዕድ ከሆኑ ወንዶች ጋር ማውራት አሊያም በዚህ ፀያፍ ነገር ያሉ ሴቶች ጋር ንግግርን ማብዛትም የተከለከሉ እና የተጠሉ ተግባራት ናቸዉ
📌 [وَيَحْفَظْنَ فُرُوجَهُنَّ]
አንድ ሙስሊም ሴት ብልቷን ለመጠበቅ የሚረዷትን ሰበቦች በሙሉ ልትይዝ ይገባታል። ይህንም በማድረጓ ታላቅ ክብር እና ልቅዕናን ታገኛለች ።
📌[وَلَا يُبْدِينَ زِينَتَهُنَّ إِلَّا مَا ظَهَرَ مِنْهَا ۖ]
ሴት ልጅ ሙሉ ሰውነቷን የሚሸፍን ልብስ በመልበስ እሷ መሸፈን ከማትችለው እና ግልፅ ከወጣው በስተቀር ሙሉ ሰውነቷን መሸፈን አለባት ። የምትለብሰው ልብስ እራሱ ፈታኝ የሆነ ልብስ ሊሆን አይገባም ።
ከፊል ሴቶች ብዙ ጌጣጌጦች ያለበት እና ለወንዶች ፈተና የሚሆኑ ልብሶችን ይለብሳሉ በዚህ ተግባራቸው እዚህ ቦታ ላይ ያለውን የአላህን ትዕዛዝ እየተጻረሩ መሆኑን ተገንዝበው ሊመለሱ ይገባል። ሊለበስ የሚገባው ልብስ የጥቡቅነት መገለጫ የሆነ ልብስ እንጂ ፈተናን የሚያመጣ ሊሆን አይገባም።
📌 [وَلْيَضْرِبْنَ بِخُمُرِهِنَّ عَلَىٰ جُيُوبِهِنَّ]
ሴት ልጅ ሙሉ ሰውነቷን የሚሸፍን ልብስ መልበስ አለባት
ባዕድ ወንዶች ባሉበት ቦታ ላይ መከናነቢያዋን ከላይ ጀምራ ልትለቅ ይገባል ፊቷን ፣እጇን ሙሉ ሰውነቷንም ልትሸፍን ይገባል ።
📌 [وَلَا يُبْدِينَ زِينَتَهُنَّ إِلَّا لِبُعُولَتِهِنَّ .........]
አላህ ሴቶችን መሸፈን ሲያዛቸው እና ጌጦቻቸውን እንዳይከፍቱ ሲከለክላቸው እንደ ፊት፣ እጅ ያሉ አካሎቻቸውን ሊከፈቱላቸው እና ጌጦቻቸውንም ግልጽ ሊያደርጉላቸው የሚፈቀድላቸውን የተወሰኑ አካላን ጠቀሰ ከነሱም ውስጥ ፦
📌[وَلَا يُبْدِينَ زِينَتَهُنَّ إِلَّا لِبُعُولَتِهِنَّ ]
ሴት ልጅ ለባሏ መከፈት እና ጌጧን እና ውበቷ ግልጽ ማድረግ ይፈቀድላታል ።
እንደውም ሴት ልጅ ሙሉ ውበቷን እና መልካም ገፅታዋን ከባሏ ውጪ ለሌላ ለማንም ግልጽ እንድታደርግ አልታዘዘችም። ነገር ግን ከፊል ሴቶች በተቃራኒው ባሎቻቸው ጋር ጌጦቻቸውን ግልጽ የማያደርጉ እና ያልተዋቡ ሆነው ውጪ መውጣት በፈልጉ ጊዜ ግን ተውበው ተጋጊጠው እና ሙሉ ውበታቸውን ግልፅ አድርገው ይወጣሉ ።

በተጨማሪም:-👇

📌"ለአባቶቻቸው ወይም ለባሎቻቸው አባቶች ወይም ለወንዶች ልጆቻቸው ወይም ለባሎቻቸው ወንዶች ልጆች ወይም ለወንድሞቻቸው ወይም ለወንድሞቻቸው ወንዶች ልጆች ወይም ለእህቶቻቸው ወንዶች ልጆች ወይም ለሴቶቻቸው ወይም እጆቻቸው ለያዙት (ባሪያ) ወይም ከወንዶች ለሴት ጉዳይ የሌላቸው ለኾኑ ተከታዮች ወይም ለነዚያ በሴቶች ሐፍረተ ገላ ላይ ላላወቁ ሕፃኖች ካልኾነ በስተቀር አይግለጹ"
ሲል መከፈት የሚፈቀድላቸውን አካላቶች ዘርዝሯል

📌[وَلَا يَضْرِبْنَ بِأَرْجُلِهِنَّ لِيُعْلَمَ مَا يُخْفِينَ مِن زِينَتِهِنَّ ۚ]
እዚህ ውስጥም ሴቶችን መጠበቅ እና ጥቡቅነታቸውን ማስጠበቅ አለበት
ሴት ልጅ የእግር ጌጦችን አድርጋ ስትራመድ የወንዶችን እይታ ለመሳብ ብላ እግሯን መምታት አይፈቀድላትም ።ከዚህም ጋር ድምጽ ያለው እና ከፍታ ያለው ጫማም ልትለብስ አይገባም።

በስተመጨረሻ አላህ ይሄን የቁርአን አንቀጽ በአስፈላጊ እና አሳሳቢ ነገር ዘጋው
📌 [وَتُوبُوٓا۟ إِلَى ٱللَّهِ جَمِيعًا أَيُّهَ ٱلْمُؤْمِنُونَ لَعَلَّكُمْ تُفْلِحُونَ]
ትድኑ ዘንዳ ሁላችሁም ወደ አላህ በመመለስ ተጸጸቱ
ጥፋት ላይ ያለች እና የአላህን ህግጋት ሳትጠብቅ የቆየች ሴት ነጻ ከሚወጡት ከአላህ ባሮች ትሆን ዘንዳ ወደ አላህ በመመለስ ትቻኮል

ይቀጥላል................

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

16 Feb, 06:41


📚ሴቶች ላይ ያተኮሩ ምክሮች


ፀሃፊ ፦ አል ሸይኽ አብዱረዛቅ አል በድር

ክፍል........ሁለት

🔘 ቁርአን ለሙስሊም ሴት የሰጣት ስጦታዎች እና ማመላከቶች

የተከበረው ቁርአን ሃያል ከሆነው እና ላቅ ካለው ጌታ የተወረደ ፣ሰዎችን ወደ ቅኑ መንገድ የሚመራ ፣ትክክኛ ደስታን በሁለቱም አለም የሚያረጋግጥ መፅሃፍ ነው ።
ይህ መጽሃፍ የሰው ልጆች መመሪያ ከበሽታዎችም መፈወሻ እና መዳኛ ነው።
ከዚህ መጽሃፍ ውጪ የበላይነት እና ልቅዕናን የሻ ሰው መዋረዱ እና ማነሱ አይቀሬ ነው ።
አላህ ለባሮቹ ብርሃን እና ወደ ቀጥተኛ መንገድ የሚመራቸውን መመሪያ እና ማመላከቻን አድርጎበታል ።

ይህች አጭር መልዕክት በቁርአን ውስጥ ያሉ ሴትን ልጅ ብቻ የነጠሉ እና ያተኮሩ ነጥቦችን የያዘች ናት ።
ታዲያ አንዲት ሴት በነዚህ ህግጋት ከተመራች እና አጥብቃ ከያዘች በሁለቱም አለም ደስተኛ ትሆናለች የበላይነቷንም አረጋግጣ ታላቅ ድልን ትጎናጸፋለች ።

ከነዚህ ህግጋት ካፈገፈገች እና ችላ ካለች ግን ለ እራሷ ጠፍታ ብዙዎችን ታጠፋለች

ይሄ ነጥብ የሙግት እና የመከራከሪያ ነጥብ አይደለም አንዲት ሴት የአላህን ንግግር እና ህግጋት ስትሰማ ከመቀበል ልታመነታ እና በውስጧ ላይ ያለመቀበል ስሜት ሊኖር አይገባል። እንዲህ አይነቱ ማመንታትም ፍጹም የሙስሊም ባህሪ እና መገለጫ አይደለም ።

ታዲያ አንዲት ሴት ደስታዋን የምታገኘው በአላህ ዲን ላይ ቀጥ ስትል እና በቁርአን ስትመራ ብቻ እንደሆነ በሚገባ ልታውቅ ይገባል ።
ቁርአን ለሴት ልጅ ከሰጣት ታላቅ ስጦታዎች እና ያማሩ ማመላከቶች ውስጥ ሴትን ልጅ አላህን በመገዛት ፣ያዘዛትን በመታዘዝ እና የከለከላትንም በመከልከል ውስጥ ጀነትን እንደሚሸልማት ቃል መግባቱ ነው ።

♦️ክቡር እና ውድ መሆንዋን ሲገልጽላት ከባዕድ አካላት እይታ እንድትሸፈን በሂጃብ አዘዛት
ከሂጃቧ ጋርም በእርጋታ ፣በሃያዕ እና በሌሎችም ምስጉን ባህሪያት እንድትዋብ አደራ አላት ከዚህም ጋር ልክ እንደ በፊት መሃይማን ህዝቦች ከመገላለጥ እና ተጋጊጦ ከመውጣት አስጠንቅቋታል ።

♦️ በአንድ በተገለለ ስፍራ ከባዕድ ወንድ ጋር ብቻዋን እንዳትገናኝ ፣እንዳትቀመጥ እና እንዳታወራ አስጠንቅቋታል ።
በጉዳይ እና አሳሳቢ በሆነ ነገር እንኳ ከወንዶች ጋር ካወራች ልቡ ላይ በሽታ ያለበት እንዳይከጅላት በንግግሯ እንዳትለሳለስ ከለከላት ይህም ደግሞ የተከበረ እና ምስጉን ባህሪዋ ከእሷ እንዳይገፈፍ ጸያፍ እና አስቀያሚ ወደሆነው ዝሙት ላይም እንዳትወድቅ ሊጠብቃት እና ክብሯን ያስጠበቀች ሆና እንድትቆይ ሊያደርጋት ነው ።

♦️በአስፈላጊ እና አስቸኳይ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ከቤታ እንዳትወጣ እና በቤቷ ውስጥ መቀመጥን እንድታዘወትርም አዘዛት
በጉዳይም በወጣች ጊዜ አይኗን እንድትሰብር እና የወንዶችን እይታ በምንም አይነት ሁኔታ እንዳትስብም አስጠንቅቋታል ።

አንድ ሙስሊም የሆነች ሴት አላህ በዚህ ውብ ሃይማኖት ላይ የዋለላትን ትልቅ ውለታ ተገንዝባ ባስቀመጠላት ደንቦች ልትመራ እና ያዘዛትንም ነገሮች ልትፈጽም ግድ ይላታል።
አላህን የምትፈራ አላህ ፊት መቆም ፣መጠየቅ፣ጀነት ፣ጀሃነም አለብግኝ ብላ የምታስብ እና ለሱም የምትዘጋጅ ሴት ከአላህ ህግጋት ዞር ሊያደርጋት የሚመጣን አካል የማትሰማ እና ከቁብ የማትቆጥር ናት

ይቀጥላል……………

منقول

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

16 Feb, 06:41


📚ሴቶች ላይ ያተኮሩ ምክሮች

ፀሃፊ ፦ አል ሸይኽ አብዱረዛቅ አል በድር

ክፍል........አንድ

🔘መግቢያ፦

ምስጋና ለዚያ በቁርአን ትልቅ ውለታን ለዋለልን፣ ወደ እስልምና ለመራን፣ ከፍጡራኖች አይነታ የሆኑት መሃመድﷺ ኡመት ላደረገን ጌታ የተገባ ይሁን። ከአላህ ውጪ በ እውነት ሊገዙት የሚገባ አምላክ እንደሌለ እና ሙሃመድም ﷺመልዕክተኛው መሆናቸውን እመሰክራለው። በመልዕተኛው በቤተሰባቸው እና ባልደረቦቻቸውም ላይ የአላህ ውዳሴ እና ሰላም ይስፈን።
በመቀጠል ፦
ይህች አጭር መልዕክት ሴቶችን የሚነጥሉ እና ሴቶች ላይ ብቻ ያጠነጠኑ ምክሮች እና ማመላከቶችን አካታ የያዘች ናት።
ሙስሊም እህቶችን የሚጠቅም እና ወደ መልካም እንዲገጠሙ ሰበብ እንዲያደርገው ከአላህ እንከጅላለን መገጠም ከአላህ ነውና ጉዳያችንን ሁሉ ወደእርሱ እናስጠጋለን ።

✨ አንቺ ለዚህ ድንቅ እና ውብ ሃይማኖት የተገጠምሽዋ እህቴ ሆይ ፦
አላህ በእውቀት እና ኢማን ህይወትሽን ያሳምርልሽ ውጫዊ አካልሽንም በመሸፈን እና በሃያዕ ያስውብልሽ እና ይህ መልዕክት ትጠቀሚበት ዘንድ እና በአላህ ዲን ላይ ቀጥ እንድትዪ እና ትዕዛዛቱን በመጠበቅ ላይ እንድትቆሚ ከአላህ በመከጀል ያበረከትኩልሽ ስጦታ ነው ።

አንቺ የተከበርሽዋ እህቴ ሆይ፦ አላህ በዚ ውብ ሃይማኖት ውስጥ የዋለልሽ ውለታዎች ተቆጥረው የማይዘለቁ ናቸው ።
ከህግጋቶች ውስጥ ያማረው እና ቀጥ ያለው ህግ አሸናፊ እና ጥበበኛ የሆነው የአለማት ጌታ አላህ ህግጋት መሆኑን ከልብሽ አረጋግጠሽ ልታምኚ ይገባል።
እድለኝነት፣ብልጫ፣ደስታ ልታገኚ የምትችይው ይሄንን ዲን አጥብቀሽ፣ በመያዝ የአላህን ትዕዛዝ በመጠበቅ እና መልዕተኛውﷺ በመከተል መሆኑን በደምብ ተገንዝበሽ ከዚህ ዲን እና የተከበረ መንገድ ሊያርቅሽ የሚመጣን ሁሉ ችላ ልትዪ እና ጀርባ ልትሰጪ ይገባል ።
ክብሽ ፣ ልቅዕናሽ ፣ ደስታሽ ሁሉ በአላህ እጅ እንደሆነ አምነሽ ከጌታሽ ጋር ያለሽን ግንኙነት ልታጠነክሪ ፣ ሁሌም ወደ እርሱ ልትዞሪ እና ልትጠጊ ይገባል ።
የጠያቂን ጥያቄ የማይመልሰውን ጌታሽን ሁሌም ቅናቻውን መንገድ እንዲመራሽ እና እንዲገጥምሽ ፣ በሱ ዲን ላይ እንዲያጸናሽ እና ከፈተናዎች እና ጥፋቶች እንዲጠብቅሽ መለመንሽ ሁሌ ከጌታሽ ጋር ቅርብ እንድትሆኚ ያደርግሻል ።
የተከበርሽው እህቴ ሆይ በዚህች አጭር የህይወት ጉዞ ትልቁ ጭንቀትሽ እና ሃሳብሽ የአላህን ውዴታ ማግኘት እና ለተከበሩት ባሮቹ ያዘጋጃትን ጀነት መውረስ ብቻ ይሁን ።

🔻እንዲሁም አላህ በሴት ልጅ ዙሪያ ያስቀመጣቸው ህግጋት ልክ እንደ ሌሎች የእስልምና ህግጋት ጥግ በደረሰጥበብ የተቀመጡ ጉድለትም ግድፈትም የሌለባቸው በደልንም ያልያዙ መሆናቸውን ልታውቂ ይገባል

ባሮቹን ተመልካች ፣ በማስተናበር ሃይሉ ጥበበኛ እና ለባሮቹ በሁለቱም አለም የሚበጃቸውን አዋቂ ከሆነው ከአለማቱ ጌታ የተወረደ ሆኖ እንዴት ጉድለት እና በደል ያለው ይሆናል ??

ሂጃብን መልበስ ፣ ቤት ውስጥ መርጋት፣ ሃያዕን መላበስ፣ ከወንዶች ጋር አለመደባለቅ እና ሌሎችም ሴቶችን ነጥለው የመጡ ህግጋቶች የመጡት ሴትን ልጅ ለመጠበቅ ፣ ደረጃ እና ክብሯን ለማስጠበቅ ከጥፋት እና መበላሸት እሷን ለመጠበቅ እና የንጽህና እና ጥቡቅነት ጌጥን ለማልበስ ነው ።
ሴት ልጅ በእስልምና እይታ ሊጠብቋት እና ሊንከባከቧት የምትገባ ውድ የሆነች አልማዝ የተከበረች ጌጥ እና ሃብት ናት ።
ይሄን ዲን አጥብቆ ለመያዝ እና ትዕዛዛቱን ለመጠበቅ አላህ የገጠመው ሰው ምንኛ ያማረ እድል እና ጸጋ ተሰጥቶታል !!
በተቃራኒው ግን በእነዚህ ህግጋት ውስጥ መበደል፣ ማጨናነቅ ፣ነጻነትን መግፈፍ አለበት ብሎ የሞገተ እና ህግጋቱንም ከመተግበር የተዘናበለ በእርግጥም በአላህ ላይ በህግጋቱ እና ንግግሩም ላይ ያለ እውቀት ተናግሯል ከትላልቅ ክልከላዎች እና ወንጀሎች ውስጥም በአላህ ላይ ያለ እውቀት መናገር ነው ።
አላህ በተከበረው ቃሉ እንዲ ይላል:-
[وَأَن تَقُولُوا۟ عَلَى ٱللَّهِ مَا لَا تَعْلَمُونَ]
[በአላህም ላይ የማታውቁትን መናገራችሁ ብቻ ነው]

አንቺ ለዚህ ውብ ሃይማኖት የተገጠምሽዋ እህቴ ሆይ አንቺን የተመለከቱ እና ባንቺ ላይ ያተኮሩ የአላህ እና የመልዕክተኛውን ﷺንግግር በምታደጪ ጊዜ በማስተንተን እና በእርጋት አድምጪ ልብሽንም ክፍት አድርገሽ ተቀበይ ምክንያቱም የምትሰሚው ንግግር የዚያ ካለ ምንም አስገኝቶ መስሚያ፣ መመልከቻ፣ጥንካሬ፣ሃይል ሌሎችንም ብዙ ፀጋዎች የሰጠሽ ታላቅ ጌታ ንግግር ነው።
አደራሽን አሁንም አደራሽን በውስጥሽ ለአላህ ህግጋት ጥላቻ ፣ የአለመቀበል እና ያለመውደድ ስሜት ፣ከመተግበርም ማመንታት እና መዘናጋት እንዳይኖር ተጠንቀቂ ።
አንቺ የተከበርሽው እና ታላቅ ብልጫ ያለሽ እህቴ ሆይ፦
ደስታሽ እና እድለኛነትሽ ከዚህ ዲን ጋር የተቆራኘ ነው ።ይሄን ዲን አጥብቆ በመያዝ እና ስርአቱን በመጠበቅ የተገባም ነው ።
እውነተኛ የሆነን ውበት ሙሉ የሆነን ጌጥ የምትፈልጊ ከሆንም ይሄን የአላህን ንግግር በደምብ አስተንትኚ.፦
[وَلِبَاسُ ٱلتَّقْوَىٰ ذَٰلِكَ خَيْرٌۭ ۚ ]
[አላህን የመፍራትም ልብስ ይህ የተሻለ ነው፡፡]

ተቅዋን በመላበስ በአላህ ህግጋት እና ፍርዶች ላይ ቀጥ በማለት እና ወዶ መበቀበል ውስጥ እንጂ ትክክለኛ ውበት እና ደስታ የለም።

ይቀጥላል.............

منقول

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

16 Feb, 06:41


📚ሴቶች ላይ ያተኮሩ ምክሮች


ፀሃፊ ፦ አል ሸይኽ አብዱረዛቅ አል በድር

ክፍል........ሶስት


🔘 የሴት ልጅ ፈተና እና ሴቶች ከወንዶች ጋር የመደባለቅ አደጋ

ሙስሊም ሴት በእልምና ክንፍ ስር የተከበረ ህይወትን ትኖራለች በትዕዛዛቱ እና ስርአቱም ስር በደስታ እና በእርጋታ የተሞላ ህይወትን ትኖራለች ።

ሙስሊም ሴት የጌታዋን ትዕዛዝ እስከጠበቀች የመልዕተኛዋንﷺ መንገድ እስከተከተለች እና ለአላህ ህግጋት እጅ እግሯን እስከሰጠች ድረስ ጎኗ የተጠበቀ የተከበረች እና በመልካም ስነምግባር የተዋበች ሆና ትቀራለች።

ታዲያ አንዲት ሴት በደስታ እና በእርጋታ ትኖር ዘንድ ከዲኗ ዞር ሊያደርጋት የሚመጡ ማንኛውም ነገሮች ልትሰማ እና ቦታ ልትሰጥ አይገባም ።

የሴት ልጅ ፈተና ከተከሰተ መጨረሻው የሚያሰጋ እና የማይታወቅ ጥፋት እና ጉዳት እንደሚያስከትል የሚያመላክቱ ብዙ መረጃዎች አሉ ።
ለዚህም ነው መልዕክተኛው ﷺ በኡመታቸው ላይ የሴቶችን ፈተና እንደሚፈሩ የገለጹት

ቡኻሪና ሙስሊም በዘገቡት ሃዲስ የአላህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል "ከኔ ቡሃላ በወንዶች ላይ ከሴቶች የበለጠ ፈተናን አልተውኩም

ሙስሊም ከ አቢ ሰዕድ አል ኹድሪይ በዘገበው ሃዲስም "ዱንያን ተጠንቀቁ ሴቶችንም ተጠንቀቁ የበኒ ኢስራኢሎች የመጀመሪያ ፈተና እኮ በሴቶች ነበር "ብለዋል

በዚህ ዙሪያ የተወሩ ሃዲሶች በርካታ ናቸው ይህም ደግሞ ማህበረሰቡን ለመጠበቅ እና የሴትን ልጅ ክብር ለማስጠበቅ ነው ።

ሴት ልጅ እራሷን ከጠበቀች እና ክብሯን ካስጠበቀች ቤተሰቦቿ እና ማህበረሰቡ ላይ መጥፎ እና ጸያፍ ነገር እንዳይወድቅባቸው ጥፋት እና መጥፎ ነገርም በመካከላቸው እንዳይሰራጭ ምክንያት ትሆናለች ።

ሴት ልጅ የእስልምና አስተምህሮትን አጥብቃ ከያዘች በሁለቱም አለም ደስተኛ ትሆናለች ንጹህ እና በጥቡቅነት የተሞላ ጠንካራ ማህበረሰም ለመገንባትም ታግዛለች ነገር ግን ከእስልምና አስተምህሮት ችላ ካለች ትጠፋለች፣ እራሷን ጸያፍ ነገሮች ላይ ትጥላለች ፣የላቀ ደረጃ እና ክብሯንም ታጣለች፣ እራሷን በቆሻሻ ነገር ትለውሳለች ፣ዝሙት ላይ ትወድቃለች በዚህን ጊዜም ለራሷ በቤተሰቦቿ እና አቅራቢያዋ ላይ ላሉት ሁሉ ውርደት እና ሰቀቀን ታመጣለች የቤተሰቦቿን አንገት ታስደፋለች እራሷን እና ቤተሰቦቿን የሰው መጠቋቆሚያ ታደርጋለች በዚህም ሁኔታ ካረገዘች ልጇን ትገድላለች ይሄኔ በጣም ከባባድ ወንጀል የሚባሉትን ዝሙት እና ነፍስን ማጥፋት እራሷ ላይ ትሰበስባለች ልጁን ከወለደች ደግሞ ቤተሰቦቿ ላይ ባዕድ የሆነ ያልተፈቀደላቸውን አካል ታስገባለች ወደነሱ የሚጠጋ ግን ከነሱ ያልሆነን አካል ታመጣባቸዋለች ከዚህ ውጪ የበርካታ ጥፋቶች መከሰተ ምክንያት ትሆናለች።


የሴት ልጅ መገላለጥ ፣ተጋጊጦ እና ተውቦ መውጣት ፣ከወንዶች ጋር መደባለቅ፣ከወንዶች ጋር መገለል የስልጣኔ ማሽቆልቆል የማህበረሰብ መለያየት የመልካም ስነምግባር መነሳት የጥፋት እና ወንጀሎች መስፋፋት እና መሰራጨት የከተማዎች መውደም ለመከሰት ዋና ሰበብ ነው ።

ኢብኑል ቀዪም رحمه الله እንዲህ ይላሉ "ሴት ልጅ ከወንድ ጋር መደባለቅ የጥፋቶች ሁሉ መነሻ እንዲሁም የከባባድ ቅጣቶች መውረጃ ምክንያት ለመሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም። ሴቶች ከወንዶች ጋ ልቅ ሆነው መደባለቃቸው ዝሙት እና ጸያፍ ነገሮች እንዲበዙ እና አጠቃላይ የሆነ ሞት እና ወረርሽኝ መስፋፋት ምክኒያት ነው "


♦️እስልምና ለሴት ልጅ መሸፋፈንን ሲያዛት ፣ ተገላልጦ እና ተጋጊጦ ከመውጣት እና ከወንዶች ጋር መደባለቅን ሲከለክላት ክብሯን ለመጠበቅ ከጥፋቶች ሊያድናት የጥቡቅነት እና የንፅህናን ጌጥ ሊያለብሳት እንጂ ለሌላ አይደለም።

የአላህ መልዕተኛ ﷺ ሴት ልጅ ቤቷ የምትሰግደው ሰላት መስጂድ ከምትሰግደው የበለጠ እንደሆነ አስተምረዋል ይህም ደግሞ የሴቶች እና ወንዶችን መደባለቅ ለመከላከል እና እሷን ለመጠበቅ ነው ።
በአምልኮ ቦታ እና የሸይጣን ጉትጎታ ደካማ በሚሆንበት ቦታ እንኳን የሴቶች ከወንዶች ጋር መደባለቅ ከተሰጋ እና ከተከለከለ አሁን ላይ በየመንገዱ በየአዳራሹ በየገበያው እና በየፕሮግራሙ እንዲሁ ተደባልቀው የሚታዩት ሴቶች የእለት ተእለት ውሎዋቸውን ከወንድ ጋር ተደባልቀው የሚያሳልፉ ሴቶች ምን ነክቷቸው ነው ? የአላህን ህግ ጥሰው እንዲሁ ልቅ በመሆናችው አላህ ተቆጥቶባቸው እንዳያጠፋቸው አይሰጉም ? አላህ ይጠብቀን እና በዘግናኟ እና አስፈሪዋ ጀሃነም መካከል መገላበጥስ አያስፈራችውም???

ይቀጥላል …………

منقول

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

16 Feb, 06:41


📚ሴቶች ላይ ያተኮሩ ምክሮች


ፀሃፊ ፦ አል ሸይኽ አብዱረዛቅ አል በድር

ክፍል........አራት


🔘ታላቅ ተግሳጽ ከተከበረች ሰሃቢት ታሪክ


ይህ ታሪክ ታላቅ ተግሳጽን ያዘለ እና ትልቅ ቁምነገርን የሚያስጨብጥ የአንዲት ሰሃቢት ታሪክ ነው።
አላህ መልካም ስራዋን ይውደድላት እና ቀይለት ቢንት መኽረማህ ትባላለች በታሪኳ ላይ ወደ እስልምና የገባችበትን ፣ወደዚህ ያማረ ዲን የተቀላቀለችበትን እና ወደ መዲና ስትገባ የነበረን ሁኔታ ታወጋለች ።
ታሪኳ ረዘም ያለ ቢሆንም ከታሪኳ ውስጥ ወደ መዲና ገብታ የመልዕክተኛው ﷺ መስጂድ ስትገባ የነበረውን ሁኔታ አጠር አድረጌ አቀርባለው

ታሪኳን ስትናገር እንዲህ ትላለች ፦

" የአላህ መልዕክተኛﷺ መስጂድ ውስጥ የፈጅር ሰላት ወቅት ላይ ደረስኩ ከጽልመቱ የተነሳ በዙሪያዬ ያሉት ወንዶች ይሁኑ ሴቶች መለየት አይቻልም ነበርና ከወንዶች ጋር ሰፍ ሰርቼ ለመስገድ ቆምኩ በወቅቱ አዲስ ሰለምቴ ነበርኩ"

በደምብ እናስተንትን አንዲት ሴት መስጂድ ውስጥ የፈጅር ሰላት ወቅት ላይ ከአንድ ወንድ ጎን ሰፍ ላይ ቆማለች

" ሰፉ ላይ አጠገቤ ቆሞ የነበረው ወንድ እንዲህ አለ "ሴት ነሽ ወይንስ ወንድ " እኔም አይ ሴት ነኝ እንጂ ብዬ መለስኩ ከዚያም እንዲህ አለኝ "አንቺ በእርግጥም ልትፈትኚኝ ቀርበሻል ከሴቶች ጋር ስገጂ "
ለካ እኔ ያላየሁት ወደጓዳ የሴቶች ሰፍ ኖሯል …ወደ ሴቶቹ ሰፍ ሂጄ ተቀላቅዬ ሰገንድኩ" ትላለች

ይህቺ ሰሃቢት አዲስ ሰለምቴ ገና የእስልምና ህግጋት እና ስርዓቶች በዝርዝር ያልተገነዘበች ነበረችና ይሄን ስህተት ተሳሳተች ።

አንቺ ሙስሊሟ እህቴ ሆይ በደምብ ልብ በይ፦ ቦታው መስጂድ ነው ዘመኑ ደግሞ የአላህ መልዕክተኛ ﷺ ወርቃማ ዘመን ሁኔታው እና ጊዜው ደግሞ የተከበርው የሰላት ወቅት ከዚህ ሁሉ ጋር ግን ያ ታላቅ ሰሃባ አላህ መልካም ስራውን ይውደድለት እና " አንቺ በእርግጥም ልትፈትኚኝ ቀርበሻል" አለ

ይህም የአላህ መልዕክተኛውﷺ " ከኔ በኋላ በወንዶች ላይ ከሴት ልጅ የበለጠን ፈተና አልተውኩም" በሚለው ኡሳማ ቢን ዘይድ ባስተላለፈው ሃዲሳቸው ግልጽ ያደረጉት ነው

አቢ ሰዕድ አል ኹድሪይ ባወራው ሃዲስም " ዱንያን ተጠንቀቁ ሴቶችንም ተጠንቀቁ የበኒ ኢስራኢሎች የመጀምውሪያ ፈተና እኮ በሴቶች ነበር " ብለዋል

ይህ ሰሃቢይ በራሱ ላይ ፈተናን የፈራው መስጂድ ውስጥ በሰላት ወቅት ጨለማ ሆኖ ሳለ ነበር ታዲያ ጨለማ ባልሆነበት በግልፅ ብርሃን በየገብውያው እና አዳራሹ ሴቶች በሙሉ ውበታቸው ከወንዶች ጋር ሲደባለቁስ ፈተናው እንዴት ሊሆን ነው !! ???

አዎ ይሄ ትልቅ አደጋ አስፈሪ ፣አጥፊ እና አውዳሚ ፈተና ነዉ!!!!

የአላህ መልዕክተኛ ﷺ በበርካታ ሃዲሳቸው በአምልኮ ቦታ፣ ኢማን፣ እርጋታ በሚኖርበበት እና ወደ አላህ የበለጠ ቅርብ በሚሆንበት ቦታ እራሱ ሴቶች ከወንዶች ጋር መደባለቅ እንደማይገባቸው አስተምረዋል።
ቡኻሪና ሙስሊም በዘገቡት ኡሙ ሰለማ እንዲህ ትላለች
"የአላህ መልዕክተኛ ﷺ ሰግደው ካጠናቀቁ በኋላ ሴቶች ቶሎ ተነስተው ይወጣሉ እሳቸውም ከባልደረቦቻቸው ጋር በተቀመጡበት ትንሽ ይቆያሉ "
ዙህሪይ እንዲህ ይላሉ "ይህም ሴቶች ሲወጡ ከአንድም ከወንድ ጋር ሳይገጣጠሙ ወተው እንዲያልቁ ነው "

አንቺ ሙስሊሟ ሴት ሆይ ሃያሉን እና ከፍ ያለውን ጌታ ፍሪ ተጠንቀቂው
በተማርሻቸው ባወቅሻቸው ባደመጥሻቸው የ እስልምና አስተምህሮቶች የአላህ እና የመልዕተኛውﷺ ንግግሮች በምን ያክሉ ምን ያክል እንደሰራሽ መጠየቅሽ የማይቀር ነው ።
አላህን መፍራት እና መጠንቀቅ ህግጋቱን አጥብቆ መያዝ ደግሞ ሙስሊሞችን በሁለቱም አለም ስኬታማ የሚያደርግ እና ታላቅ የሆነ የበላይነትን የሚያጎናፅፍ ነው።

ከዚህ ጋር ደግሞ ሁሌ ልናዘወትረው የሚገባ ዱአ የሚከተልው ነው ፦

አቡ ዳዉድ እና ሌለችም በዘገቡት ሃዲስ አብደላህ ኢብኑ ኡመር እንዲህ ይላል የአላህ መልዕክተኛﷺ ዘወትር ጠዋት እና ማታ ይሄንን ዱአ ይሉ ነበር

اللَّهُمَّ إِنِّي أسْأَلُكَ العَفْوَ وَ العَافِيَةَ في الدُّنْيَا وَالآخِرَةِ، اللّهُمَّ إِنِّي أسْأَلُكَ العَفْوَ وَ العَافِيَةَ في دِيْنِي وَدُنْيَايَ وَأهْلي وَمالي، اللَّهُمَّ اسْتُرْ عَوْرَاتي، وَآمِنْ رَوْعَاتي، اللَّهُمَّ احْفَظْني مِنْ بَيْنِ يَدَيَّ، وَمِنْ خَلْفِي، وَعَنْ يَمِيْنِي وَعَنْ شِمَالي، وَمِنْ فَوْقي ، وَ أعُوذُ بِعَظَمَتِكَ أنْ أُغْتَالَ مِنْ تَحْتِي.


አላህ ሆይ በዚህችም ሆነ በቀጣዩ ዓለም ይቅርታንና ጤንነትን እጠይቅሃለሁ፡፡ አላህ ሆይ በሀይማኖቴ፥ በዚህች አለም ህይወቴም፥ በቤተሰቦቼም፥ በንብረቴም ደህንነትን እጠይቅሃለሁ፡፡ አላህ ሆይ ነውሬን ሸፍንልኝ፡፡ አላህ ሆይ ከፊት ለፊቴ ፥ ከኃላዬም፥ ከቀኜም፥ ከግራዬም፥ ከበላዬም ጠብቀኝ፡፡ ከበታቼም እንዳልጠቃ በአንተ እጠበቃለሁ፡፡

ታዲያ አንድ ሙስሊም ይሄንን ዱአ ሊያዘወትር ቤተሰቦቹን ልጆቹን ጓደኞቹንም ይሄን ዱአ እንዲይዙ እና እንዳይተዉ አደራ ሊል ይገባል።

መገጠም ከሱ ውጪ በ እውነት የሚመለክ አምላክ በሌለው በአላህ እጅ ብቻ ነው

ይቀጥላል ……………


منقول

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

16 Feb, 06:41


📚ሴቶች ላይ ያተኮሩ ምክሮች


ፀሃፊ ፦ አል ሸይኽ አብዱረዛቅ አል በድር

ክፍል........አምስት


🔘ከጀነት ሰዎች ዉስጥ የሆነች ሴት ታሪክ


ይህ ታሪክ እጅግ የሚገርም እና ታላቅ ምክርን ያዘለ ነው። ታሪኩ ከጀነት ሰዎች መካከል ስለሆነችዋ ድንቅ ሴት ይተርካል፦

ቡኻሪና ሙስሊም በዘገቡት ሃዲስ አጣዕ ኢብኑ አቢ ረባህ እንዲህ ይላል፦ ኢብኑ አባስ እንዲህ አለኝ ፦
"ከጀነት ሰዎች ውስጥ የሆነችን ሴት አላመላክትህን?"
"እንዴታ አመላክተኝ እንጂ" ብዬ መለስኩለት

"ይህቺ ጥቁሯ ሴት ከእለታት በአንዱ ቀን ወደ መልዕክተኛው ﷺ ዘንድ መጣችና
"አንቱ የአላህ መልዕክተኛ ሆይ እኔ የአውድቅ በሽታ አለብኝ ስወድቅ ደግሞ ሰውነቴ ይከፋፈትብኛል አላህ ከዚህ በሽታዬ እንዲፈውሰኝ ዱአ አድርጉልኝ" አለቻቸው ረሱልﷺ " ከፈልግሽ ከዚህ በሽታሽ ታገሺ ትግስት ካደረግሽ ደግሞ ጀነት አለልሽ ከፈለግሽ ደግሞ አላህ ከበሽታሽ እንዲያድንሽ ዱአ አደርግልሻለው ? "ብለው ምርጫ ሰጧት እሷም "በዚህ በሽታዬ ላይ እታገሳለው ግን በምወድቅበት ጊዜ ሰውነቴ ይከፋፈታልና ስወድቅ ሰውነቴ እንዳይከፋፈትብኝ ዱአ አድርጉልኝ" አለች
ረሱልምﷺ ዱአ አደረጉላት ።

የዚህችን ታላቅ ሴት ታሪክ እናስተንትን ይህቺ ሴት ውስጧ በኢማን ፣ በእውነተኝነትን፣ በንጽህና እና በሃያዕ የተሞላ ነው ።ከባድ ጭንቀት እና መከራ ነበረባት እሱም ያገኛት የአውንቅ በሽታ ነበር ይህ በሽታ ይጎዳት ፣ ያስጨንቃት እና ያሳስባት ነበር በዚህም ምክኒያት ከዚህ በሽታ ትድን ዘንዳ ወደ መልዕክተኛው ﷺ ዘንድ ዱአን ከጅላ መጣች ረሱልም ﷺ ከዚህ በሽታ ከመዳን የበለጠ ታላቅ ነገርን አመላከቷት እሱም ከዚህ ህመም እና ጭንቀት ሰብር አድርጋ የሰብሯም መጨረሻ ጀነት እንደሚሆን ነው እሷም ከምንም በላይ ታላቅ የሆነውን ነገር መረጠች ።
በረሱል ﷺ አረጋጋጭነት በዚህ በሽታዋ ላይ ታግሳ ከጀነት ሰዎች መካከል መሆንን መረጠች ።
አላህ መልካም ስራዋን ይውደድላትና መታገስን ከመምረጧ ጋር ግን በምትወድቅበት ጊዜ ከፊል የሰውነት ክፍሏ መከፈቱ አሳሰባት ።
ሰውነቷ የሚከፈተው በበሽታ ምክንያት ስትወድቅ ፈልጋው እና ወዳው ካለመሆኑ ጋር የሃያእዋ ጥንካሬ እና የልቧ ጽዱነት ይህን መገላመጥ እንድትጠላው እና እንዲያስጨንቃት አደረጋት ከበሽታዋ ታግሳ ጀነት ማግኘትን መረጠች ግና ከሱም ጋር ሳትፈልገውም ቢሆን የሚከፈተው ሰውነቷ አሳሰባት
የዚህች የተከበረች ሴት ታሪክ ታላቅ ተግሳጽን የያዘ ነው
ታላቅ ስነ ምግባር ! ያማረ መገለጫ !ውብ የሆነ ሃያእ! እና የልብ ፅዱነት እና ጥራት የሚንፀባረቅበት ድንቅ ታሪክ!!!!!!!

የዚህች ሴት ሁኔታ እንዲህ ከሆነ ባልፈለገችው በህመም ምክኒያት በመሆኑ የማያስጠይቃት እና ባልወደችው መገላመጥ እንዲህ ከተጨነቀች በምርጫዋ እና ፍላጎቷ ምንም ሳይመስላት ተገላልጣ እና ተጋጊጣ የምትወጣ ሴት ምን ነክቷት ነው??

የጌታዋን ቃል ታደምጣለች ፣የመልዕክተኛውንﷺ ትዕዛዛት ጠንቅቃ ታውቃለች ፣ተገላልጦ እና ተጋጊጦ በመውጣት ላይ የመጡ ዛቻ እና ማስፈራሪያ ያላቸውንም ሃዲሶች ትሰማለች ግን ይሄን ሁሉ ከቁብ አትቆጥረውም

ይህች የጀነት ሴት በነበራት የአውድቅ በሽታ ምክኒያት ነበር የምትገላለጠው ሆኖም እጅግ ትፈራው እና ያስጨንቃት ነበር በአሁን ሰአት ያሉ የበርካታ ሴቶች መገላለጥ እና ተጋጊጦ መውጣት ግን ከተጠያቂነት የማያድን አይነቱ ለየት ካለ የአውድቅ በሽታ የመነጨ ነው
እሱም ከሃያእ እና ኢማን ማነስ እና መድከም የመነጨ የስሜት አውድቅ በሽታ ነው። አው ይሄ በጣም አስከፊ በሽታ ነው።
በፈተና በሮች እና በስሜት ተጣሪዎች ምክኒያት በዚህ ዘመን የዚህ አይነቱ አውድቅ በሽታ እየተበራከተ መጥቷል።


አንቺ ሙስሊሟ ሴት ሆይ የዚህችን ድንቅ ሴት ታሪክ በደምብ አስተውዪ የኢማኗን ጥንካሬ እውነተኝነቷን እና የሃያእዋን ግዝፈት እና ውበት አስተንትኚ ካለባት በሽታ ጋር ለመገላለጥ የነበራት ፍራቻ በዚህ ደረጃ ከሆነ አንቺ አማኝ ሴት ሆይ ያንቺስ ሁኔታ እንዴት ነው ?

በአሁኑ ሰአት ከፊል ሴቶች ከባድ፣ ዘግናኝ እና አስፈሪ ለሆነ ወረራ ተጋልጠዋል።
"ዘመናዊነት" በሚባል ሸንጋይ እና ገዳይ ቃል ተሸንግለው አስፈሪ ሁኔታ ውስጥ ይገኛሉ ።
ሴቶች ዘመናዊ ናት ብለው በተደመሙባት አንዲት ሃያእዋን እና ስነብግባሯን ባጣች ሴት ተደንቀው የሷ አድናቂ ነን በሚል የሷን ተግባር ዱካ በዱካ ተከትለው ሲተገብሩ ይስተዋላሉ ።

ሙስሊም የሆነች ሴት አላህ ልትፈራ እና ልትጠነቀቅ ይገባል ጌታዋ ፊት እንደምትቆም ልትዘነጋ አይገባም አላህ ፊት ቆማ ስለ ሃያእዋ፣ ስለ ጥቡቅነቷ እና በጌታዋ እና በመልዕክተኛውﷺ ንግግሮች ላይ ስለመጡ ነገሮች ሁሉ እንደምትጠየቅ አውቃ ለዚህም እራሷን ልታዘጋጅ ይገባታል ።

በሙስሊሞች መካከል መገላመጥ ተጋጊጦ መውጣት ከወንዶች ጋር መደባለቅ እጅግ ተበራክቷል ይህ ደግሞ ከተከበሩ ሰሃቦች ዘመን ጀምሮ እነሱንም በመልካም የተከተሉ ሴቶች ጋር የማይታወቅ በሙስሊም ሴቶች ታሪክ ላይ ታይቶም ተሰምቶም የማይታወቅ ነው ።

በአሁን ሰአት ያሉ ሙስሊም ሴቶች ግን የስሜት ፣የሸይጣን ተገዢ እና የዘመናዊነት አታላይ ሰለባ ሆኑ እና መገላለጥ ምንም የማይመስላቸው ሆኑ አንዷ ደረቷን ከፍታ ስትሄድ አንዷ ደሞ እጅ እግሯምን ከፍታ ሌላኛዋ ደግሞ ጸጉሯን……… ሌሎችም ዘግናኝ እና አሳፋሪ የሆኑ የመገላለጥ ሁኔታዎች በየቦታው ሙስሊም ሴቶች ላይ ይስተዋላሉ ።

እነዚህ ሴቶች ግን አላህ ፊት መቆምን አያስታውሱም ? በእያንዳንዱ በሰሩት መጥፎ እና ጸያፍ ተግባር አላህ ፊት መተሳሰብ እና አሳማሚ ቅጣት እንዳላቸውስ አያውቁም ? ኢማናቸው እና ሃያአቸውን እንዲህ የገፈፈው ምንድነው ? በዚህ ደረጃ የወረደ እና የዘቀጠ ባህሪ ላይ እንዲሆኑስ ያደረጋቸው ምንድነው ?

አንድ ሙስሊም ሴት አላህ ፊት እንደምትቆም ልታስታውስ ይገባል በጌታዋ ታግዛ ፣ ዱአ ተቀባዩን ጌታዋን ሃያእአ እና ጥቡቅነት እንዲያላብሳት እየለመነች ፣ማድረስ ያለባትን ሰበቦች እያደረሰች፣ እራሷን እየጠበቀች እና የጌታዋን ትዕዛዛት እየጠበቀች እራሷን ልትታደግ እና ልታድን ይገባል።
መገጠም በአላህ እጅ ብቻ ነውና

ይቀጥላል……………

منقول

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

16 Feb, 03:29


📆 #በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
⏰#አልአሃድ 1⃣7⃣ #ሻዕባን 1⃣4⃣4⃣6⃣ ሂ

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

10 Feb, 19:06


مع القرآن الكريم

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

02 Feb, 07:25


. ስደት ወደ ሀበሻ

ያኔ ቢንገላቱ ነቢ በቁረይሾች
እረፍት እንዲያገኙ ከነዚያ ጨካኞች
ሰሀባው መርጠው ላኩ ወደ ሀበሻ
ጥሩ ንጉስ አለ እውነትን የሚሻ
ጃእፋር አስከትሎ ሰሀባው ዘለቀ
ወደ ሀበሻው ንጉስ ፍቅርን ካፈለቀ
መጡ ተከትለው የዛ አልበቃቸው
መከራ አደረሱ ስለሙ ቢሏቸው
ያኔ ምርጡ ንጉስ እፌቱ ቀረቡ
ሁለቱም ቅሬታ ሀሳብ ሊያቀርቡ
ጀመሩ ሠላምታ ኣንገታቸውን ሰብረው
ቁረይሾች ውሸት ጣኦት መምለክለምደው
ሙሥሊሞች ዝም አሉ አንገትምአልደፉ

ጠየቁ ነጃሺ !

ለምን አትሠግዱም ሠላምታ ሰጥታቹ
በንጉሡ ፊት እኔጋ ቆማችሁ
ቁረይሾች በመቅደም እንዲምተናገሩ
ንጉስ ሆይ ንቀት ነው ብለውአቃጠሩ

ጃእፋርም መለሠ በሠከነ አንደበት
እኛ የምንሠግደው አንገትምንደፋለት
ለአላህ ብቻ ነው ብሎምመለሠለት
ንጉሥ ተደነቀ በጃእፋር ንግግር
ለማወቅም ጓጓ የመጡበትን ነገር
ጠየቀ ነጃሺ ለምንስ መጣቹ?
ከኔሥ ዘንዳ ምንስ ፈለጋችሁ
ቀጣዪን ክፍል በጉጉት ጠብቁኝ

እስከምንገናኝ በዱአ አትርሱኝ

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

31 Jan, 18:21


♾ልዩ የዳዕዋ ፕሮግራም♾

💡 فضل  شهر شعبان🌙

🌙"የሻዕባን ወር ቱሩፋት" 💡🎴በሚል ርዕስ፡

🟢በወንድም አቡ ዑሰይሚን [حفظه الله] የዳዕዋ ፕሮግራም በአሏህ ፈቃድ ይቀርባል።

🔜ሰአት➡️ቅዳሜ ከምሽቱ 3️⃣🔤0️⃣0️⃣ጀምሮ።

            📌የሚተላለፍበት ቻናል፡
                  ⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️

🎴⏩  https://t.me/Yeselefoch

           🌹በሱና ቻናሎች ጀመዓ የተዘጋጀ🌹

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

30 Jan, 17:20


አላህ በተከበረው ንግግሩ እንዲህ ይላል፦
📖 {وَرَبُّكَ يَخْلُقُ مَا يَشَاءُ وَيَخْتَارُ}
{ጌታህ የፈለገውን ይፈጥራል (የፈለገውንም) ይመርጣል (ይሾማል)}


✍አላህ ሀገሮችን ፈጠረ። ከሀገሮች
    👉🏽መካን መረጠ

✍አላህ ቤቶችን ፈጠረ። ከቤቶች
    👉🏽መስጂደን መረጠ

✍አላህ ሌሊቶችን ፈጠረ። ከሌሊቶች
  👉🏽ለይለተል ቀድርን መረጠ

✍አላህ አጠቃላይ ቀናቶችን ፈጠረ። ከቀናቶች
  👉🏽የውሙል ነህር (ለኢደል አድሃ የሚታረድበትን ቀን) መረጠ

✍አላህ የሳምንት ቀናቶች ፈጠረ። ከሳምንት
👉🏽ጁምዓን መረጠ

✍አላህ መላኢካዎችን ፈጠረ። ከመላኢካዎች
  👉🏽ጅብሪልን መረጠ

✍አላህ ሰዎችን ፈጠረ። ከሰዎች መሃል
  👉🏽ነብያቶችን መረጠ
ከነብያቶች
  👉🏽መልዕክተኞችን መረጠ
ከመልዕክተኞች
👉🏽አምስቱ ኡሉል አዝም መረጠ
ከኡሉል አዝሞች
👉🏽ሁለቱ ኸሊሎቹ  መረጠ
ከኸሊሎቹ (ከወዳጆቹ)
👉🏽ነብዩ ሙሐመድን መረጠ

✍አላህ ወራቶን ፈጠረ። ከወራቶች
  👇🏾👇🏾👇🏾👇🏾👇🏾👇🏾
👉🏽ረመዷንን መረጠ👈🏿
👆🏾👆🏾👆🏾👆🏾👆🏾👆🏾


  ✍ረመዷን ማለት፦
👇🏾
  👉🏽ሸይጣን የሚታሰርበት፣
  👉🏽ነፍስያ የምትዳከምበት፣
  👉🏽ቀልብ የምትረጥብበት፣
  👉🏽የጀነት በሮች የሚከፈቱበት፣
  👉🏽የጀሀነም በሮች የሚዘጉበት፣
  👉🏽ወንጀልና በደል የሚቀንስበት፣
  👉🏽እዝነትና በረካ የሚሰፍንበት፣
  👉🏽ወንጀለኞች የሚፀፀቱበት፣
  👉🏽ታዛዦች የሚጠነክሩበት፣
  👉🏽ዝንጉዎች የሚነቁበት፣
  👉🏽ንቁዎች የሚሸምቱበት፣
  👉🏽ሸማቾች የሚያተርፉበት፣
በአጠቃላይ
👇🏾
👉🏽የጀነት ገበያ የሚፋፋምበት ወር ነው‼‼

✍እነሆ ይህ ወደ ተመረጡ ህዝቦች በተመረጠው መልዕክተኛ ላይ በተመረጠው መላኢካ አማካኝነት የተላለፈው የተመረጠውና ታላቁ የረመዷን ወር ሊገባ ☝️አንድ ✌️ሁለት 👌ሶስት እየተባሉ በጣት የሚቆጠሩ ቀናቶች ብቻ ቀርተውታል።

🌴ረመዷን አሁን ያለበት ሁኔታ ሲታይ👇🏾
👉🏽በቅርብ ርቀት ፊቱን ወደኛ በማቀጣጨት ፊት ለፊታችን ቆሞ ፈገግ እያለ "ልምጣ እንዴ? ምን ያህል ጓግታችሁ እየጠበቃችሁኝ ነው?" እያለ እያጓጓንና ፍቅሩን እየለቀቀብን ይመስላል‼

ታድያ
  አልጓጓህም❓
      አልጓጓሽም❓
          አልጓጓቹም❓
እኔ ግን "ጉግት" ብዬ ነው የጓጓሁት

🤲አላህ ደርሰው ከሚጠቀሙበት ያደርገን
አ ሚ ን!!

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

26 Jan, 03:02


የጧት ስንቅ____🌺✍️

ችግርን  መጋፈጥ የሚያመጣቸው በጎ ተፅዕኖዎች

ችግር  አንድን ሰው በመተናነስ  ወደ ጌታው እንዲዞር ያደርገዋል ።  ÂŤ  አሏህ ምንኛ የጠራ ጌታ ነው ። በችግር ውስጥ ዱዓ እንድታወስ  አደረገ ። አሏህ ባሪያውን  በአንዳንድ ነገሮች ይፈትንና  ለመላኢኮች ይህን ለምን እንዳደረገ ሲናገር  ÂŤ ድምፁን ለመስማት ነው»  ይላል Âť ።  ዱአውንና ልመናውን ማለት ነው ። ችግር በተጠቂው ልብ ውስጥ መተናነስን ያሰርፃል ።

ﻛَﻼَّ ﺇِﻥَّ اﻹِْﻧﺴَﺎﻥَ ﻟَﻴَﻄْﻐَﻰٰ

በእውነቱ ሰው ወሰንን ያልፋል፡፡
(አል_ዐለቅ 6)

♻️ሰዎች የተቸገረን ሰው ያስመቻሉ ። ለተቸገረ ሰው ዱዓ ያደርጋሉ ። ስለዚህ በችግር ወቅት ሙዕሚኖች  በወንድማማችነት መንፈስ አንድ ይሆናሉ ።

ችግር አንድን ሰው አመስጋኝ ሊያደርገው ይገባል ።  ምክንያቱም ከደረሰበት የባሰ ችግር ቢደርስበት ኖሮስ?  በተጨማሪም ችግር ኃጢያትን ያሰርዛል ።  የአሏህ ባሪያ እነዚህን እውነታዎች ሲረዳ አመስጋኝ ይሆናል ። 

ۗ ﺇِﻧَّﻤَﺎ ﻳُﻮَﻓَّﻰ اﻟﺼَّﺎﺑِﺮُﻭﻥَ ﺃَﺟْﺮَﻫُﻢ ﺑِﻐَﻴْﺮِ ﺣِﺴَﺎﺏٍ

« ታጋሾቹ ምንዳቸውን የሚሰጡት ያለግምት ነው»
(አዝ_ዙመር  10)

@Rihu_islamic_post

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

23 Jan, 11:31


كن سببًا في قضاء حوائج غيرك ،
يُسخر الله لك من يقضي حاجتك .

قال النبي ﷺ : ( من كان في حاجة أخيه ،
كان الله في حاجتِه ) رواه مسلم .

@Rihu_Tube

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

19 Jan, 14:00


🌻「 በአላህ መተማመን 」🪴
⊱⋅ ──────🌤────── ⋅⊰
(በአላህ መተማመን ሰበብ ከማድረስ ጋር)

🌴:አላህ ለፊዎችን ይወዳል ፣ የሠራተኞችን ዋጋ አይቆርጥም ይመነዳል ፣ ወደ ቀና መንገዱም የሚመራው ሌት ተቀን መንገዱን ፈላጊ የሆኑ ታጋዮችን ነው፡፡

🌿:ተስፋ ካደረግክ ፣ ሰበቡን ካደረስክ ፣ ዉጤቱን እንደሚሰጥህ አትጠራጠር
#በአላህ_ተማመን፡፡

➙ መድሃኒት በትክክል ዉስድ ትድናለህ፣
➙ጠንክረህ  ሼል ታገኛለህ፣
➙በርትተህ  አጥና ታልፋለህ፣
➙ ወጥረህ ታገል ነፃ ትወጣለህ፣
➙ አብዝተህ ታገስ ያሰብከዉን ታሳካለህ፣
➙ ተንቀሳቀስ ለውጥ ታመጣለህ፣
➙ ከልብህ ለምን ትመነዳለህ፡፡
➙አትስነፍ፣ አትድከም፣ አትታክት፣ ተስፋ አትቁረጥ፣  አትሰልች፣ አታቋርጥ፣

▫️ለመንኩ ለመንኩ ደከመኝ ብለህ እጅህን አታዉርድ፡፡  ያውልህማ . . . የስኬት ብርሃን ጭላንጭሉ እየታየ ነው፡፡ ፀሐይህ እየወጣች ነው፡፡

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

17 Jan, 10:18


ቀልባችን አላህን እንድፈራ ሊያግዙን ከሚችሉ ጉዳዮች ዉስጥ፦
1) የአላህን ዉለታዎች ማስታወስ
2) የአላህን ስሞችን እና ባህርያቶች ማወቅ
3) ሰለፎችን አላህን እንዴት እንደሚፈሩት ታሪካቸውን ማንበብ
4) ሞትን ማስታወስ
5) ምክሮችን ማዳመጥ
6) ሀላልን መመገብ
7) የቲሞችን መንከባከብ
8) ስለቂያማ ማስታወስ
9) ወንጀሎችን  መራቅ
10) ጥሩ ጓደኞችን መጎዳኘት
11) መቃብርን መዘየር
12) ዱዓእ ማድረግ
13) ማለቃቀስ ( አላህን ብቻ በማስታወስ እምባ ባይመጣም ለማልቀስ መታገል )
14) ቁርአንን መቆራኘት
15) ዚክርን ማብዛት
.
ይገኙበታል::

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

14 Jan, 19:23


ስልክህን ልትተኛ ስትል ፈትሸው። ምናልባት ጠዋት ስትነሳ አንተ ላታከፍተው ትችላለህ። አላህ የሚያውቀውና የሚያየው ከሰው የተደበቀ ብዙ ወንጀል ሊኖርበት ይችላልና ቀን ሙሉ ለሠራኸው ወንጀል ምህረት ጠይቀህ ተኛ።
Š

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

13 Jan, 16:55


ኒቃቡ ጅልባቡ አቤት ሲያምርብሽ
ተዋቢ ልበሽው ካፊሮች ይቅኑብሽ

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

11 Jan, 04:52


📲「 በስልክ መቅራት 」📖
▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬

📌: አንዲት ሴት
ሀይድ ላይ ባለችበት ወቅት ቁርአንን በእጇ ይዛ መቅራት ስለማይፈቀድላት በሞባይል ላይ በተጫነው ቁርአን ከፍታ ብትቀራ ይከለከላል እንዴ ⁉️

📜 ≠「
መልስ  」∬

✅:በውስጣቸው የቁርአን ቅጅ የተጫነባቸው
ሞባይሎች የመፅሀፉን ቁርአን አይነት ተመሳሳይ ፍርድ የላቸውም። ምክንያቱም የመፅሀፉ ቁርአን የሚታይ ፣ የሚዳሰስና የማይወገድ ፅሁፍ ሲሆን የስልኩ ግን ጨረር ስለሆነ የማይዳሰስና ወዲያውም በቀላሉ ማጥፋት የሚቻል እና ፊደላቶቹም እዛው ስልኩ ላይ ሁሌ የፀኑ ሳይሆኑ ሲያፈልግ ብቻ ግልፅ የሚሆኑ በመሆኑ ነው። በዛ ላይ ስልክ ቁርአን ብቻ ሳይሆን ሌላም ነገር የተጫነበት ነው።

✒️:ስለዚህ በሀይድ ላይ ያለችም ትሁን በጥቅሉ
ያለ_ጡሀራ በስልክ ላይ የሚገኘውን ቁርአን ማንበብ ይፈቀዳል። እንደውም አንዳንድ ኡለሞች ይህ ሀይድ ላይ ላሉ እንስቶች ሀይዳቸው እስኪጠናቀቅ ድረስ ሙሉ በሙሉ ከቁርአን እንዳይርቁ ሲባል አሏህ ያመጣላቸው ማግራት ነውና ሙሉ በሙሉ ቁርአንን ከመተው ቢጠቀሙት የተሻለ ነው ብለዋል።

•📗。*。📙。
📘。\|/。📒
        🔎{ምንጭ🗂}
📔。/|\。📕
•📓。*。🗃 °

🌐
https://www.almrsal.com/post/425653
🌐
https://islamqa.info/ar/answers/106961/قراءة-القران-من-الجوال-هل-يشترط-لها-الطهارة
🎙ፈታዊ ኑሩን ዓለድ–ደርብ ፣ ለኢብኑ ዑሰይሚን ፣ 309 ፣

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

10 Jan, 18:06


#የሰው_ልጅ 🔍

✅:በምድር ላይ ሲኖሩ የሰው ልጆች የአላህ ምስክሮች ናቸው፡፡ ባዩትና በሰሙት ነገር ይመሰክራሉ፡፡ ሰዎችን በሥራቸዉና በባህሪያቸው መሠረት ክፉዎችንና ደጋጎችን ይመድባሉ፡፡

📸:ሰዎች አንድን ሰው ሲያዩ እሱን /ሷን ባዩበት ቅጽበት የሆነ ነገር ስለሚያስታዉሱ ከዚያ ሰው አንፃር  የሚሉት ነገር አላቸው፡፡ ብዙዎቻችንም እንዲሁ ነን ፦

🔴አንዳንዱን ስናይ “ሱብሓነላህ!” እንላለን፡፡

🔴አንዳንዱን አይተን “አልሐምዱሊላህ!” እንላለን፡፡

🔴አንዳንዱን አይተን “አዑዙ ቢልላህ!” እንላለን፡፡

🔴አንዳንዱን አይተን “ሐስቢየላህ!” እንላለን፡፡

🔴አንዳንዱን አይተን “አላሁ አክበር!” እንላለን፡፡

🔴አንዳንዱን አይተን “አስተግፊሩላህ!” እንላለን፡፡

🔴አንዳንዱን አይተን “ማሻአላህ!” እንላለን፡፡

🔴አንዳንዱን አይተን  “ላ ሐውለ ወላ ቁውወተ ኢልላ ቢልላህ!” እንላለን፡፡ 
 
🔴አንዳንዱን አይተን   “ላ ኢላሀ ኢልለላህ!” እንላለን፡፡

📌:ታዲያ እኛስ ሰዎች እኛን ሲያዩ ምን እንዲሉ እንፈልጋለን? እኛን አይተው ከሚደነቁ ወይስ ከሚማረሩ ?
╭┈─────── ೄ🌹ྀ࿐ ˊˎ-

╰┈➤✅ᢀ  @Rihu_islamic_post 💌

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

09 Jan, 16:41


#ካስደነቁኝ_አባባሎች🔎

✅:ተምረናል እንጂ አላወቅንም *

✅:ተዋደናል እንጂ አልተፋቀርንም *

✅:እናወራለን እንጂ አልተገበርንም *

✅:እንሰብካለን እንጂ አልሰራንበትም *

✅:እንሞክራለን እንጂ አልፈፀምንም *

✅:እንስቃለን እንጂ አልተደሰትንም *

✅:እናለቅሳለን እንጂ አላዘንም *

╭┈─────── ೄ🌹ྀ࿐ ˊˎ-

╰┈➤🌗ᢀ
@Rihu_islamic_post 💌

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

09 Jan, 02:34


✅:አንድ ሰው ሱንና ሶላትን እየሰገድ ሳለ ኢቃማ ከተደረገና ሱናውን ሶላት ቢያጠናቅቅ የግዴታው ሶላት ተክቢረተል_ኢህራም ኢማሙን ተከትሎ ወዲያውኑ ማለት እችላለሁ ብሎ ካመነ ሱንናውን ያጠናቅቅ። ተክቢረተል ኢህራሙ የሚያመልጠው ከሆነ ግን የሱንናውን ሶላት ያቋርጠው።

ሸይኽ አልባኒ  رحمه الله ፈታዋ ራቢጝ

ይሄ ማድረግ ሶላትን ከማበላሸት ሳይሆን የተሻለውን መልካም ስራ ከመምረጥ ነው የሚቆጠረው።

╭┈─────── ೄ🌹ྀ࿐ ˊˎ-

╰┈➤✅ᢀ @Rihu_islamic_post 💌

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

08 Jan, 07:39


“በዚህ ዓለም እስካለህ በማንም ላይ ጥገኛ አትሁን፣ ጥላህ እንኳ በጨለመ ጊዜ ጥሎህ ይጠፋል።”

ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያህ

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

07 Jan, 17:47


➨እህቴ ለማን ነው የምትዋቢው ?
በጣም የሚያሳዝነው ብዙ እህቶቻችን መቆነጃጀት እራስን ማስዋብ ጥሩ ልብስ መልበስ የሚቀናቸው
ወደ ሰርግ ሊሄዱ ሲሉ
ወይም ጓደኛቸው ጋር ሲቀጣጠሩ
አንዳንዶች ደግሞ ወደ ሥራ ሲወጡ
ሌሎቹ ደግሞ የአላህ ባሮችን አሳስተው ወደ ሐራም ለመጥራት ያለ ምክንያት ሲወጡ
እና ለመሳሰሉት ነው
የባሎቻቸውን ሐቅ አሽቀንጥሮ ይጥላሉ።
🔅ከወጡበት ወደ ቤት ሲመለሱ ያ ሁሉ ያጌጡበት ነገር አውጥተው ይወረውራሉ
ባል ሲመጣ በማድ ቤት ልብስ በላብ ሽታ
በሊጥ እጅ በሽንኩርት ባለቀሰ ዐይን
በተንጨባረረ ፀጉር
በተዝረከረከ ገፅታ ከሷ እንዲርቅ በሚያደርግ ሁኔታ ትቀበለዋለች ተመልከቺ እህቴ ባለቤትሽ ላንቺ ምን አይነት ፍላጎት ይኖረዋል በዚህ ሁኔታሽ ምን አይነት የፍቅር ስሜትስ ያገኛል።
✔እንዴትስ ያንቺ ታደርጊዋለሽ
በተለይ ከቤት ወጥቶ አስከ ሚመለስ አላህን በማይፈሩ የለበሱ መስለው ራቁታቸውን ሆነው ወደ ጀሃነም በሚጣሩ ተከቦ ከሸይጣንና ነፍስያ ጋር ታግሎ ወዳንቺ ሲመጣ ያን በሚያብስ ገፅታና ሐላል ፍቅር ተቀብለሽ ማስተናገድ ካልቻልሽ በሌባ ላለመዘረፍሽ ምን ዋስትና አለሽ።
አው የቤት እመቤት ስትኾኚ እናት ነሽ።
♨ይህ ማለት መዝረክረክ ማለት አይደለም
♨ይህ ማለት እቤት ውስጥ እራስን መጣል ማለት አይደለም
✔አንቺ ለልጅሽም እናት ነሽ
✔ለፍቅርሽም እናት ነሽ
✔ለቤትሽም እናት ነሽ እናት በሁሉም የእናትነት ድርሻዋ የተዋጣላት ናት
እቤት ውስጥ ያለብሽን ሃላፊነት ከመወጣትሽ ዋናውና ትልቁ የትዳር አጋርሽን የፍቅር ቱኩሳት ሳይበርድ ጠብቀሽ ማቆየትሽ ነው
ይህ ደግሞ ውስጥሽን አላህን በመፍራት ላይሽን ባለሽ ልብስና ጌጥ በማስዋብ ነው ይህን ካላደረግሽ ስትወጪ የምትዋቢው ለማን ነው ??

***
╭┈─────── ೄ🌹ྀ࿐ ˊˎ-

╰┈➤✅ᢀ  @Rihu_islamic_post💌

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

06 Jan, 16:02


🌻「 አይገርምም ግን ? 」🔭
▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬
✅:ቢላዋ የተለመደው ጥቅሙ ለመቁረጥና ለመቅላት ነበር፡፡ በነቢዩ ኢብራሂም (ዓለይሂ ሰላም) እጅ ሆና በነቢዩ ኢስማዒል (ዓለይሂ ሰላም) አንገት ላይ ስታርፍ ግን የአላህ ትእዛዝ ነበረባትና ዶለዶመች::ለመቁረጥም ፈቃደኛ ሣትሆን ቀረች።(አስ ሷፋት፡103)

✅:እናት በልጇ ጉዳይ ከራሷ በቀር ማንንም የማታምን ከየትኛውም ፍጥረት በበለጠ ለልጇ አዛኝ እና እሩህሩህ ፍጥረት ናት:: የነቢዩ ሙሳ (ዓለይሂ ሰላም) እናት ግን ዐይኗ እያየ ልጇን በሣጥን አድርጋ ወደ ባህሩ ወረወረች:: በአላህ ላይ እምነቷ ከፍ ያለ ነበርና፡፡ ቃል የገባላት ጌታ ከልጇ መልሦ እንደሚያገናኛት ታውቅ ነበርና፡ (አል ቀሶስ ፡7)

✅:እሣት በባህሪዋ አቃጣይ ናት፡፡ የቀረባትን ሁሉ ትፈጃለች:: የደፈራትን ያለ ምህረት ትበላለች:: ይህም በመሆኑ ለአጥፊዎቹ የጀሀነም ሰዎች ተዘጋጀች፡፡ ነቢዩ ኢብራሂም (ዓለይሂ ሰላም) ግን ሙቀቷ ከሩቅ ቦታ በሚፋጀው በላይዋ ላይ የሚበረውን በራሪ ጭምር ስባ ወደራሷ ወደምትከተው እሣት ከሩቅ መንጀኒቅ በተባለ መሣሪያ ተስፈንጥረው መሃሏ ላይ ቢጣሉም የሰከነችና ሰላማዊ ሆነችላቸው:: ጌታዋ “ለወዳጄ ኢብራሂም ቀዘቃዛና ሰላማዊ ሁኚ ብሏታልና፡፡ (አል አንቢያእ ፡ 69)

✅:የባህርን ማዕበል ታላቅ ዋናተኛ አይደፍረውም::
ተራ መርከበኛም አይጋፈጠውም፡፡ ለነቢዩ ሙሳ (ዓለይሂ ሰላም) እና ለተከታዮቹ ግን ግዙፉ ባህር የአላህን ትእዛዝ መፈፀም ነበረበትና ለሁለት ተከፈለ፡፡ ውሃውም ደረቅ ሜዳ ሆነ::

🌿:አላህን የያዘ ትልቁን ገመድ ያዝ፡፡ በርሱ የተመካም እውነት መመካት በሚገባው ተመካ፡፡ ነቢዩ የዕቁብ (ዓለይሂ ሰላም) ልጃቸው በትንሽነቱ ከርሣቸው ከተለየ ጊዜ ጀምሮ ሙሉ ተስፋቸው በአላህ ላይ ነበር::አላህም(ሱብሃነሁ ወተዐላ)ተስፋቸውን በተስፋ አላስቀረም ፤ ከልጃቸው አገናኛቸው:: ለዘመናት ያለ ግድብ ሲፈስ የነበረ እንባቸውን አበሠ ፤ ሊጠፋ የተቃረበ ዐይናቸውንም ብርሃን መለሰ፡፡ (ሱረቱ ዩሱፍ ቁ፡96)

🔸:ﺇِﻧَّﻤَﺎ ﺃَﻣْﺮُﻩُ ﺇِﺫَا ﺃَﺭَاﺩَ ﺷَﻴْﺌًﺎ ﺃَﻥ ﻳَﻘُﻮﻝَ ﻟَﻪُ ﻛُﻦ ﻓَﻴَﻜُﻮﻥُ

🔹:ነገሩም አንዳችን በሻ ጊዜ ኹን ማለት ነው፡፡ ወዲያው ይኾናልም፡፡(ያሲን ፡ 82)


╭┈─────── ೄ🌹ྀ࿐ ˊˎ-

╰┈➤✅ᢀ @Rihu_islamic_post💌

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

06 Jan, 03:22


በነብዩ ﷺ ዘመን ⏳

✅:በነብዩ صل الله عليه وسلم ዘመን ሴቶች በቀጥታ ከወንዶች ኋላ ሆነው ነበር የሚሰግዱት:: መጋረጃ ማድረግ እየቻሉ ነገር ግን አላደረጉላቸውም:: ለሴቶች የተለየ ክፍልም ማዘጋጀት ሲችሉ ግን ደግሞ አላደረጉትም።

💡ዛሬ ላይ አንድት ሴት መስጅድ ሄዳ  ለሴቶች ተብሎ ታጥሮ የተዘጋጀውን መስገጃ  ቦታ በመተው ከወንዶች ኋላ ያለምንም መጋረጃ ብትሰግድ ሰዎች ምን ይሏታል ? እብድ ወይስ ጤነኛ ❓

🔖ለማንኛውም ለሴቶች የተለዬ መጋረጃ  ማድረግ፣ የተለየ ክፍል ማዘጋጀት ጥንት የማይታወቅ፣ በመልካሞቹ ትውልዶች ዘመን ያልተለመደ ተግባር መሆኑ ነው አይደል?

🚩:#የኢማማቸውን አሰጋገድ ብቻ ሳይሆን ኢማማቸው የት ቦታ እንደሆነም ጭምር እንዳያውቁት ነውኮ ያደረጋቸው። ኧረ አንዳንድ እህቶች የወንዶቹ መስጂድ ምን ምን ይኖረው ይሆን ብለው እስከማሰብም ይደርሳሉ።

✨✨✨✨✨✨✨✨

📍:በጆበርግ ከተማ ታላቁ ጁማ መስጂድ ሴቶች የወንዶቹን መስጂድ እንዲያዩት የተለዬ ፕሮግራም ተዘጋጅቶላቸው ፣ ገለጻ አድራጊ ተመድቦላቸው፣ በሰአቱም ወንዶች እንዳይገቡ ክልከላ ተደርጎ ነበር። በነብዩ صلى الله عليه وسلم ዘመን ግን ሴቶች ስለነብዩ መስጂድ ሁለነገር ያውቁ ነበር።

🖥:የመካ ክልሉ ሙፍቲ እንድሁም የኢብኑ ባዝ መስጂድ ኢማምና ኸጢብ ሸይኽ ሙሀመድ ዑመር ባዝሙል حفظه الله  ከአመታት በፊት በፌስቡክ ከለቀቁት ጽሁፍ ከተወሰኑ ማሻሻያዎች ጋር የተተረጎመ

منقول
╭┈─────── ೄ🌹ྀ࿐ ˊˎ-

╰┈➤✅ᢀ @Rihu_islamic_post💌

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

05 Jan, 18:00


#✉️

1️⃣መስጂድ ቁጭ ብለህ ሰላት በምትጠባበቅበት ወቅት ፣

2️⃣የታመመን ስትጠይቅ ፣

3️⃣በሰላት ላይ የመጀመሪያው ሰፍ ስትቆም ፣

4️⃣ሙስሊም ወንድምህን  ስትዘይር ፣

5️⃣በሩቅ ለወንድምህ ዱአ ስታደርግ ፣

6️⃣ሰዎችን መልካም ነገር ስታስተምር ፣

7️⃣ውዱእ አድርገህ ስትተኛ ፣

🔖በነዚህ ሁኔታዎች እስከሆንክ ድረስ መላኢካዎች ላንተ ዱዓ🤲 ከማድረግ አይወገዱም።

╭┈─────── ೄ🌹ྀ࿐ ˊˎ-

╰┈➤✅ᢀ @Rihu_islamic_post💌

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

03 Jan, 03:11


✅ከአንድ ሰው ጋር በሀሳብ ስላልተስማማን ብቻ ስሙን ለማጥፋት አንሩጥ። በስድብ፣ በሀሜትም ይሁን ዝናውን ለማፈራረስ አንድከም። ክብሩን ለማውረድ አናሲር። ሰላም ለማሳጣት አናውጠንጥን። ሙስሊም የሆነ ሰው ሁለመናው የተከበረ ነው። አላህ መልካም ባሮቹን ሲነኩበት በእጅጉ ይቆጣል። ከቁጣው ፊት ችሎ የሚቆም ካለ ደጋግ አማኞችን ይዳፈር። የአላህ መልዕክተኛ ﷺ በሀዲሳቸው አላህ(ሱብሃነሁ ወተዐላ) እንዲል ብሏል ብለዋል፦

🟠مَنْ عَادَى لِي وَلِيًّا فَقَدْ آذَنْتُهُ بِالْحَرْبِ

🔘አንድን የኔን ባሪያ ጠላቱ አድርጎ የያዘን ጦርነት አውጄበታለሁ

📚‌✿・⁺ [ ቡኻሪ ]


╭┈─────── ೄ🌹ྀ࿐ ˊˎ-

╰┈➤✅ᢀ @Rihu_islamic_post 💌

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

02 Jan, 07:43


➡️:ከጠፋህም ይጨነቃሉ ፣ ብዙ ከታየህም ይጨነቃሉ ፣ ችግር ላይ ነኝ ካልካቸዉም ይጨነቃሉ፣ አሞኛል  ስትላቸዉም ይጨነቃሉ ፣ ከተናገርክም ይጨነቃሉ ፣ ዝም ካልክም ይጨነቃሉ።  የአንዳንድ ሰው መጨነቅ ለተጨነቀ ወይም ችግር ላይ ላለ ሰው ተጨማሪ ጭንቀት ወይም ችግር ሊሆን ይችላል። አንዳንድ ጊዜ ሰዎችን ጭንቀታቸው እስኪያልፍላቸው ጠብቋቸው። በጥያቄም አታሰልቿቸው። ምን ሆና/ሆኖ ነው ብላችሁም እንደ እናት ሆድ አትንቦጅቦጁ።

🍀:የቀናት ማለፍ ብቻ የሚፈቷቸው ችግሮቻችን ብዙ ናቸው ወዳጆቼ። ዱንያ እንደሆነች ክብ ነች። ደስታና ሐዘን፣ ችግርና እፎይታ፣ ማግኘትና ማጣት፣ መውደቅና መነሳት ዞሮ መምጣት ልማዳቸው ነው። ዱንያ ጀነት አይደለችም፣ ዘወትር አንደላቃ አታኖርም።

منقول

╭┈─────── ೄ🌹ྀ࿐ ˊˎ-

╰┈➤✅ᢀ @Rihu_islamic_post 💌

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

02 Jan, 07:34


#✉️

🔺ሰዎችን ለማስረዳት ድምፅህን ሳይሆን አነጋገርህን ከፍ አድርግ፣ ተክሎችን የሚያጠጣው ዝናብ እንጅ መብረቅ አይደለም።

╭┈─────── ೄ🌹ྀ࿐ ˊˎ-

╰┈➤✅ᢀ @Rihu_islamic_post 💌

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

31 Dec, 18:29


💠አትኩሮትህን በሌለህ ነገር ላይ ሳይሆን ባለህ ነገር ላይ አድርገው። ደስተኛ ለመሆን ሁሉም ነገር ሊኖርህ አይገባም። በደንብ ካስተዋልከው አሁን ያለህ ነገር ደስተኛ ለመሆን በቂ ነው። ምክንያቱም አንተ ያለህን የሚመኙ ምስኪኖች ብዙ ናቸውና። የሰራኸውና የምትሰራው ነገር የሆነ ጊዜ ላይ ዞሮ ያገኝሃል ፣ መጥፎ ከሰራህ እንደስራህ ፣ መልካም ከሰራህም እንደዚያው ይገጥምሃል ። "ሰው የዘራውን ያጭዳል" የሚለውን ስታስታውስ ፣ ክፉ ነገር እየዘራህ መልካም ነገር አትጠብቅ ፣ ራስህን አትሸውድ ። ጤፍ ዘርተህ ባቄላ አትጠብቅ ። ጤፍ የዘራ ገበሬ ጤፍ እንደሚያጭድ ሁሉ፣ አንተም የዘራኸውን በእጥፍ ታጭዳለህ።

አላህ መልካም የምንስራ ያድርገን~🤲

╭┈─────── ೄ🌹ྀ࿐ ˊˎ-

╰┈➤✅ᢀ @Rihu_islamic_post

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

30 Dec, 14:48


ኑ ጌታችንን እንወቅ ❗️

✅:የሰው ልጅ አዕምሮ አስተሳሰቡ የተገደበ ነው ወይም limit አለው ሲባል አይገባኝም ነበር። ነገር ግን ይሄን ጉድ ስሰማ የአዕምሮ የማሰብ ገደቤን በሚገባ አውቄዋለሁ። እናንተም እዩት የአዕምሮ ገደባችሁን ታገኙበታላችሁ።

╭┈─────── ೄ🌹࿐ ˊˎ-

╰┈➤✅ᢀ
@Rihu_islamic_post💌

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

29 Dec, 12:51


የህሊና 🦋 ዕረፍት

✅:አቡ የዚድ አል በስጣኒ የተባሉ ሰለፍ:-

⬅️ጌታዬ ሆይ አንተን በመውደዴ አልገረምም ምክኒያቱም እኔ ተራ #ሰው ነኝና። ነገር ግን አንተ እኔን በመውደድህ በጣም #እገረማለው።ምክንያቱም አንተ የላቅክ ታላቅ ጌታ ስትሆን ተራ የሆነን ባሪያህን ወዳጅ ነህና➡️

💎:እንዴት የሚያምር ንግግር ነው! የእኛ አላህን መውደድ ሳይሆን የአላህ እኛን መውደዱ ነው ሊያስደንቀን የሚገባው።ምክንያቱም እኛ አላህን በመውደዳችን ለአላህ ልናበረክተው የምንችለው ነገር የለም።አላህ እኛን በመውደዱ ግን በርካታ ፀጋዎችን እናገኛለን።

╭┈─────── ೄ🌹ྀ࿐ ˊˎ-

╰┈➤✅ᢀ @Rihu_islamic_post 💌

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

27 Dec, 15:50


📨:ወደ መልካም ነገር ያመላከተ እንደ ሰሪው ነው። መሥራት ባትችሉ አመላክቱ ፣ መፃፍ ባትችሉ ሌሎች የፃፉትን አጋሩ።

↬ዱንያ ላይ የምንቆየው ለአጭር ጊዜ ነው። ምድር ላይ እንደሁለተኛ ዕድሜ ሆኖ የሚያገለግለን ዛሬ እዚህ የምንጽፈው ነገር ነው። ከሶላታችን ፣ ከፆማችን ምንም ምንዳ ላይኖረን ይችላል። መልካም ነገሮችን ማጋራት ወደ አኺራችን ከምናስቀድማቸው ጠቃሚ ስንቆች መካከል አንዱ ነው። ብልህ እንሁን። አላህ ያፅናን።

🔴 ዓለማዊ ጥቅም አለው ብዬ አልወተዉታችሁም፣ በስነልቦናም ሆነ በዲኑ ጉዳይ ሊጠቀምበት የሚችል ሰው ሊኖር ይችላልና ይህን #ቻናል አጋሩት። ╭┈─────── ೄ🌹࿐ ˊˎ-

╰┈➤✅ᢀ @Rihu_islamic_post 💌

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

27 Dec, 15:46


ጭንቀት

💥:በመጨነቅና በማማረር ያመጣነው ለውጥ የለም፡፡ ተነስቶ መንቀሳቀስ እንጂ ዘግቶ ማልቀስ የፈየደን ነገር አላየንም፡፡ በጭንቀት ስንዝር ያህል እንኳን ነገሮችን መግፋት አንችልም፡፡ የጎደለ ኑሮ የሚሞላው #በሥራ እንጂ በጭንቀት አይደለም፡፡ ተጨንቀን ብዙ አየን፡፡ ጭንቀትን ትተንም አየን፡፡ ሰፊ ልዩነቱን በርግጥም አስተዋልን፡፡ ዘና ብለን ስንስቅላቸው ረጃጅም ቀናቶች አለፉ፡፡ ትላልቅ ሸክሞች ረገፉ፡፡ ከባባድ ችግሮችም ተረሱ፡፡ እናም ፈታ በል ፤ ዘና በል፡፡ አትጨነቂ ፣ አትጨነቅ 🦋

✅:የነገሮች ዋና መሰረታቸው ቀደር ነው፡፡ ቀደር ማለት ደግሞ ቀድሞ የተላለፈ የአላህ (ሱብሃነሁ ወተዓላ) ውሳኔ ነው፡፡ ለተወሰነና ላለፈ ነገር "መዐልኤሽ!" ምንም ማለት አይደለም በል፡፡

❗️ብርጭቆ ሰበረ ብለህ ልጅህን ከቤት አታባርር፡፡

❗️እንጀራው አረረ ብለህ ከሠራተኛህ ጋር ቦክስ አትግጠም፡፡

🔎አንዳንድ ሰዎች ይገርሙኛል ፤ ሳይመቱ ከተመቱት በላይ ይጮሃሉ፡፡ መቶኝ ነበር ፈንክቶኝ ነበር ለጥቂት ነው የሳተኝ ብለው ቂያማ ያቆማሉ፡፡ እንኳንም የሳተህ ባይስትህ ኖሮ ጣጣህ ብዙ ነበር፡፡ ሳይፈነክትህ እንዲህ የሆነክ ቢፈነክትህ ኖሮ እንዴት ትሆን ነበር!፡፡ በዚህች ዓለም ላይ እየሆነ ያለው ነገር ሁሉ በርሱ ፈቃድ ነው፡፡ በፈቃዱ ተማረን ምን ልናመጣ ነው?፡፡ የወደደውን አንወድም ብለን ምን ልንሆን!፡፡ ፌንጣ ብትቆጣ ክንፏን ጥላ መብረር ካልሆነ ምን ልታመጣ!

🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥

💡:እስልምና አትጨነቁ ይላል፡፡ የፈጠረን ጌታ ‹እመኑ፣ በርቱ፣ ትጉ፣ ተስፋ አትቁረጡ፣ አትስነፉ፣ አትድከሙ፣ አትዘኑ፣ አይዟችሁ፡፡ …› ብሏል፡፡ በመልካም ትዕግስትና ተስፋ አደራ ይላል፡፡ በጥሩ መጨረሻና ስኬት ቃል ይገባል፡፡ ነቢዩ (ﷺ) ምንም ሊረዷቸው ባልቻሉ ጊዜ ‹የያሲር ቤተሰቦች ሆይ! ትእግስት አድርጉ ቀጠሮአችሁ ጀነት ነው፡፡› ብለዋቸዋል፡፡

✅:ሞኝ የሆነ ይጨነቅ፡፡ እኔ ሞኝ አይደለሁም አልጨነቅም፡፡ ዕድሜዬ አጭር መሆኗን አውቃለሁ፡፡ መሞቴ ላይቀር ለምን ቀድሜ እሞታለሁ፤ ለማንስ ለምንስ ብዬ እታነቃለሁ፡፡ መድረሱ ላይቀር ለምን ቀድሜ ፈግማለሁ፡፡ አልጨነቅም - ተጨንቄ ምን አገኘሁ! ተበሳጭቼስ ምን አተረፍኩ፡፡ ተናደውና ራሳቸውን መቆጣጠር አቅቶአቸው ሰው የደበደቡ እስር ቤት ናቸው፡፡ ተበሳጭተው የተሳደቡ ‹ምኑ ባለጌ ነው?› ተብለው በሰዎች ትዝብት ዉስጥ ገብተዋል፡፡ ስብእናቸውን አስንቀዋል፡፡ ምን አስጨነቀኝ፡፡ ቦታዬ አላህ ዘንድ የታወቀ ነው፡፡ አላህ ዘንድ አልጉደል እንጂ እዚህ ኪሎዬን ቢቀንሱ ስድባቸው አይለጠፍብኝም፡፡ ከአላህ ጋር እስካለሁ ዘና እላለሁ፡፡

✅:የደስታችን መሰረቱ አላህ ብቻ ይሁን፡፡ ከሁሉም በላይ ከርሱ ጋር የሚኖረንን ግንኙነት እናሳምር፣ እሱ እንዳለውና እንዳዘዘው ለመኖር እንሞክር፣ ህግጋቱን ከመጣስ እንጠንቀቅ፣ ድንበሩን አንጋፋ፡፡ ከአላህ ጋር ስንሆን አካላዊ ለውጥ ላይኖረን ይችል ይሆናል፣ ኪሎ ላንጨምር እንችላለን፡፡ ሆኖም ግን ዉስጣዊ ሰላምና የበዛ ደስታ ይኖረናል፡፡ በዚህ ደግሞ ሁሉንም ነገር ማሸነፍ እንችላለን፡፡ ጣሉት ጃሉድን ያሸነፈው፣ ሙሳ ፈርዐውንን የረታው፣ ኢብኑ መስዑድ አቡጀሀል አንገት ላይ የወጣው … በሥጋ ግዝፈት ሳይሆን በኢማን ጥንካሬ ነው፡፡ የኢብኑ መስዑድ እግር ቅጥነቱ ቢያስገርምም ‹የቂማ ቀን ሚዛን ላይ ከኡሑድ ተራራ በላይ ክብደት አለው፡፡› ብለዋል ነቢዩ (ﷺ)፡፡
╭┈─────── ೄ🌹࿐ ˊˎ-

╰┈➤✅ᢀ @Rihu_islamic_post 💌

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

26 Dec, 05:30


#ካገኘሁት 🖥

✅:መልካምነት ደግ መስራት ብቻ ሳይሆን ክፉም አለመስራት ነው።

✅:መኖርን እንደተቀበልቅ ፈተናዋንም ተቀበል።

✅:እየሳቀ ሀጢአት የሰራ እያለቀሰ ጀሀነም ይገባል።

✅:ለማወቅ ተቸገር ለማገኘት ጣር ከትልቅ ባህር ምርጥ አሳ ይገኛል።

✅;አጀማመርህን ካሳመርክ ከፊሉን ጨረስክ ማለት ነው።

✅:ለራበው ሰው ሁሉም ነገር ጣፋጭ ነው።

╭┈─────── ೄ🌹ྀ࿐ ˊˎ-

╰┈➤✅ᢀ @Rihu_islamic_post 💌

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

25 Dec, 07:08


አስገራሚ እውነተኛ ታሪክ " !!

ኢብኑ ዑሰይሚን እንዲህ አሉ ፡-

 đŸ”ť - አንድ የማምነው ሰው እንዲህ ሲል አወራኝ ፡
የሆነ ሰው ነበር ሚስቱ ለማንኛውም ቤት ቆርቁሮ ለሚለምን ሚስኪን ዳሀ ምንም አይነት ነገር እንዳትሰጭ ብሎ ይከለክላት ነበር ፡፡

🔻ከዕለታት አንድ ቀን የሆነ ዳሀ ሚስኪን ቤቱን ይቆረቁራል ፡ ከዚያ ሚስት ቤቱን ስትከፍት ይህ ሚስኪን እንዲህ አላት ፡ እመቤቴ እባክሽን የምለብሰው የሌለኝ እርቃን ነኝ ከብርድ ራሴን የምከላከልበት ልብስ የሌለኝ ሰው ነኝ ? ባላት ጊዜ ፡ ይች የዚህን ሚስኪን ሁኔታ ያየች ሚስት አላቻላትምና ከቤቷ ውስጥ በመመለስ ልብስ እና ሶስት ተምሮችንም ጭምር ሰጠችው እና ሄደ ፡፡

🔻የዚች ሴት ባለቤት መስጂድ ውስጥ ተኝቶ ነበር ፡ ይህ ባሏ በህልሙ ልክ ቂያማ ስትቆም ያያል ! ሰዎች ሁሉ ትርምስምሳቸው ወጥቷል ! ሰወች በጣም ብርቱ በሆነ የፀሃይ ቃጠሎ ውስጥ ናቸው ! ልክ ይሄን አስደንጋጭ ክስተት እየተመለከተ ሳለ ከበላዩ የሆነ ልብስ ከዚህ ከፀሃይ ቃጠሎ ይከልልለታል ፡ ግና ይህንን ልብስ ሶስት ቦታ ተሸነቋቁሮ ያየዋል ፡ ከዚያም የሆኑ ሶስት ተምሮች መጥተው እነዚህን ሶስት የሽንቁር ቀዳዳ ቦታወች ሲደፍኑት ተመለከተ ፡ በጣም ተገረመ ፣ ተደነቀ በዚህ ህልም ፡ ወዲያው ከእንቅልፉ ባነነ እና በድንጋጤ ወደ ቤቱ በፍጥነት በማምራት ያየውን ህልም ሙሉውን ለሚስቱ ተረከላት ፡  ሚስትም ይህ ህልም  በእነዚያ በሰጠቻቸው ልብስና ተምሮች ሰደቃ ምክኒያት መሆኑን ስለለተረዳች ፡ ያ ሚስኪን ዳሀ ቤት መጥቶ የሰጠችውን ልብስና ሶስት ፍሬ ተምሮች ነገረችው ለባሏ ፡

ከዚያም እንዲህ አላት ፡ አደራ ከዚህ ቡሀላ አንድንም ዳሀ ከደጄ እንዳትመልሽ ፡፡

☞ ይህ ሰው አሏህ አነቃው ፡ ይሄም ክስተት ነብዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) የተናገሩትን ሃዲስ ያስመሰክራል ፡

🔻ነብዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ይለሉ፡- የቂያማ እለት አሏህ በሰዎች መካከል ፍርድ እስኪሰጥ ድረስ ሁሉም ሰው ከሰደቃው ጥላ ስር ነው የሚጠለለው ፡፡

📚ምንጭ፡- ሸርሁ ኪታብ አል ረቃኢቅ ከሶሒህ አል ቡኻሪ (ገፅ/6)


✔ኢብነል ቀይም እንዲህ አሉ፡-

  ☞- ሰደቃ የአደጋ አይነቶችን የመከላከል ልዩና አስገራሚ ተፅዕኖ አለው ፡ ከአረመኔ ወንጀለኛ እና ከግፈኛና በደለኛ እንዲሁም ከካፊር ቢሆንም እንኳን ፡፡

 â˜ž አሏህ በዚች በሰደቃው አማካይነት ከተለያዩ አደጋወች ይከላከልለታል ፡፡

  📚ምንጭ፡- አል ዋቢሉ ሶይብ (50/49)
  
@Rihu_islamic_post
@Rihu_islamic_post

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

30 Nov, 06:45


የኔ ጀግና!
~
ሸይኽ ሙሐመድ ብኑ ዐብዲል ወሃብ ኢስላምን ያጠለሹ፣ ሙስሊሞችን በአጉል ኮተቶች ጠፍረው ያሰሩ የሱፊያ ኮተቶችን የበጣጠሰ አንበሳ ነው። በጀሊሉ፣ በወሃቡ ፈቃድ የተሃድሶ ንቅናቄው የቀብር አምልኮትን ግንድ ከምድረ ሰዑዲያ ገንድሶታል። በመላው የሙስሊሙ አለም ያለውን የበሰበሰ የሱፊያ ሸክም አነቃንቆታል። ኧረ ክፉኛ ወዝውዞታል።
በዚህ የተነሳ ሱፊዮች ዘንድ እንደሱ የተጠላ ፍጡር የለም። የተፃፈ ኹጥባ ለማንበብ ሚንበር ላይ ወጥቶ የሚንገዳገደው ሁላ እየተነሳ "ሙሐመድ ብኑ ዐብዲል ወሃብ ጃሂል ነው" ሲል የምንሰማው ያለ ምክንያት አይደለም። ይገባናል፣ የሚያስጮሃችሁ ህመማችሁ ነው። "አሶራኹ ዐላ ቀድሪል አለም" እንዲል ዐረብ። "ጩኸት በህመም ልክ ነው!"
ሙሐመድ ብኑ ዐብዲል ወሃብ እንዳንተ ሶደቃ ሲያባር እድሜውን አልፈጀም። ጋርዶ ጫት የሚቀረጥፍ ቦዘኔ አልነበረም። ሁሉን እንዳመጣጡ ያስተናገደ፣ ለቆመበት አላማ ቆርጦ የተነሳ፣ ከዚያም እስከ ደም ጠብታ የታገለ ቆራጥ ነበር፣ የጀግና ጀግና! የፅናት፣ የትጋት፣ የብቃት ተምሳሌት!
ዛሬ ግን ይሄ ነው የሚባል የዒልም ቅሪት የሌለው፣ ኢስላምን የግል ጥቅም መሸመቻ ያደረገ፣ ከሆዱ አሻግሮ መመልከት የማይችል ቦዘኔ ሁላ እየተነሳ "እሱ'ኮ ጃሂል ነበር" ይላል። እርሱ ጃሂል ከነበረ አንተ ጅህልና እራሱ ነህ!
•
"ወሃብዮች ዑለማእ አያከብሩም" የሚሉ አስመሳዮች ሁላ በሸይኹ ላይ ምላሳቸውን ሲያሾሉ ማየት በስፋት የተለመደ ነው። ግማሹ "ተ'ክ'ፊ'ር ነው" ይላል። ግማሹ "የሁዲ ነው" ይላል። ግማሹ "የእንግሊዝ ቅጥረኛ ነበር" ይላል። ሌላም ሌላም ለጆሮ የሚሰቀጥጡ ውንጀላዎች አሉ። እናንተ ናችሁ ስለ ዑለማእ ክብር የምታወሩት? በጀግኖቻችን ክብር ላይ እየተረማመዱ ከዚያ የነሱን የጥፋት ሰባኪዎች እንድናከብርላቸው ይፈልጋሉ።
በሃገራችን በመውሊድ ሰበብ ስማቸው ገኖ ከሚታወቁ ቦታዎች ጋር ተቆራኝቶ ዝናቸው ከናኘ መሻይኾች ውስጥ #ብዙዎቹ የእውነት እንደሚባለው በዒልም የላቁ እንደነበሩ የሚያሳይ ማስረጃ ብትጠይቁ አስቂኝ ነገር ነው የምትሰሙት። "እስኪ ኪታባቸውን አሳዩን?" ብትሉ "የመውሊድ መንዙማ ፅፈዋል" "ማዲሕ ነበሩ። መድሕ አዘጋጅተዋል" ብለው የግጥም መድብል ይነግሯችኋል። ዒልም ማለት ግጥም መፃፍ ነው እነዚህ የዞረባቸው ዘንድ! በዚህ የግንዛቤ አቅምህ ነው ሸይኽ ሙሐመድ ብኑ ዐብዲል ወሃብን በጅህልና የምትወርፈው?! አዎ መውሊድ ያገነናቸው ብዙ ስመ ገናናዎች አሉ። ከመውሊድ ጭፈራ ባለፈ ከነ ጭራሹ በቦታው ምንም አይነት የዒልም እንቅስቃሴ የሌለባቸው ብዙ ናቸው።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

28 Nov, 05:17


بسم الله الرحمن الرحيم

👉ነፍስህን ለማሻሻል አራት መንገዶች አሉ (ናፍስ)።  ናቸው: 👌

➤1. #በራስህ_ላይ_ግዴታ_ማድረግ (مُشَارَطَه) ፦ *ኃጢአት እንዳሠራ ለራስህ ቃል ግባ።  ቀኑን ሙሉ ማንኛውንም ኃጢአት ላለማስራት በየቀኑ ጠዋት ላይ ለነፍስህ ቃል ግባ። ይከብዳል አቃለው ግን ታደርገዋለህ። 💪

➤2.  #ክትትል_አላህ_ያየኛል_ማለት (مُرَاقَبَه) ፦     ኃጢአት ፈፀምክ? ምንም ኃጢአት እንዳሠራ ራስህን መከታተልህን ቀጥል።

➤3.  #ራስንህን_መመርመር (مُحَاسَبَه) ፦ ስንት  ኃጢአቶችን እንደሠራህ ከስንት መልካም ሥራዎች !!!! ...
ማታ ፣ ከመተኛትህ በፊት ፣ ብቻህን ስትሆን ፣ ቀኑን ሙሉ ምን እንደተሳሳትክ እና ምን እንደተ ፈጠረ ገምግመው።

➤4.  #እራስን_ማረም (مُوَاخَذَه) ፦ በቀን ውስጥ ለፈጸመከው አለመታዘዝ ነፍስህን ቅጣት ፣ እናም ቅጣቱ የአምልኮን ሸክም በላዩ ላይ ማድረግ ነው።  ለተሳሳቱት ነገሮች ንስሃ በመግባት እና ለተከናወኑት መልካም ሥራዎች አላህን ሱብሃነ ወተዓላ ማመስገን።

➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴
╭─┅───══───┅─╮
@Rihu_islamic_post
╰─┅───══───┅─╯
⤴️⤴️ሸር &ጆይን ይበሉ⤴️

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

24 Nov, 02:52


🌸🍃ደስተኛ ሁነህ መዋል ከፈለክ ፦

🌺 ሰላትን ከወቅቷ አታሳልፍ

🌺ቀንህን ስትጀምር በአላህ ላይ ጥሩ ግምት ይኑርህ በገመትከው ልክ ይገኝላሀልና

🌺 አላህም መሀርታ መጠየቅን አብዛ የሪዝቅ በር ይከፈትለሀል

🌺 በነብዩ ﷺ ሰለዋት ማውረድን አብዛ … አላህ ጭንቀትህን ያስወግድለሃል ወንጀልህንም ይምርልሀል

🌺 ለሰዎች ፈገግ በል ንግግርህንም ለዘብ አድርግ ውዴታቸውን ታገኛለህ

🌺በሀሳብህ ላይ የምትዘራውን በእርግጥም በህይወትህ ላይ የምታጭደው መሆንህን አትዘንጋ … ለዚህም ማጨድ የምትፈልገውን ብቻ እሰብ !


መልካም
ውሎ💐

@Rihu_islamic_post

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

24 Nov, 02:39


﴿يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا اتَّقُوا اللهَ وَابْتَغُوا إِلَيْهِ الْوَسِيلَةَ وَجَاهِدُوا فِي سَبِيلِهِ لَعَلَّكُمْ تُفْلِحُونَ﴾.

«اللَّهُمَّ اجْعَلْنَا من أفْضَلِ مَنْ تَوَجَّهَ إلَيْكَ وَأقْرَبِ مَنْ تَقَرَّبَ إلَيْكَ وَأنْجَحِ مَنْ سَألَكَ وَطَلَبَ إلَيْكَ».

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

22 Nov, 20:04


✅ የመኝታ ዚክር ...
       〰️〰️〰️
بسمك ربي وصعت جنبي وبك ارفعه فإن أمسكت نفسي فارحمها وإن أرسلتها فاحفظها بما تحفظ به عبادك الصالحين »

~ትርጉም፦(ጌታዬ ሆይ በስምህ ወገቤን አሳረፍኩ በስምህም አነሳዋለሁ፥ነፍሴ ከያዝካት እዘንላት፣ከለቀቅካትም መልካም ባሮችን በምትጠብቅባት ጠብቃት።

🔖መተኛትህን ካልቀረ በሱና ላይ ሁነህ ተኛ!

@Rihu_islamic_post

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

19 Nov, 16:40


📌ትክክለኛው ተወኩል📌
~~~~
✅:ግመልህን እሰር በአላህ ተወከል።
~~~~
✅:ጣር፣ልፋ ፣ አንብብ ለማለፍ ተዘጋጅ በአላህ ተወከል።
~~~~
✅:ተሯሯጥ፣ነግድ፣ ሰበቡን አድርስ በአላህ ተወከል።
~~~~
✅:ቆፍር፣ አለስልስ ፣ ጊዜውን ጠብቀህ ዝራ በአላህ ተወከል።
~~~~
✅:በአላህ የሚመካን አላህ በቂው ነው።

🔰:ተወከልቱ አለሏህ . . . . . . . . .

♻️ @Rihu_islamic_post
♻️ @Rihu_islamic_post
♻️ @Rihu_islamic_post

#SHARE_The_خير_

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

19 Nov, 15:49


🔸" ﻭﻟﻴﺲ ﺍﻟﺬﻛﺮ ﻛﺎﻷﻧﺜﻰ"
🔹“ወንድም ልጁ እንደ ሴት ልጁ አደለም»

♦️ሴት ልጅ በሕይወት ዘመኗ በተለያዩ አካላዊና፣ ሆርሞናዊ ሂደቶች ዉስጥ ታልፋለች፡፡ ለምሳሌ በወር አበባ፣ በእርግዝና፣ በወሊድ፣ በማጥባት፣ በወር አበባ መቋረጥ ወቅት ….  ከባባድ የሆርሞን ለውጦች የሚታዩባቸው ጊዜያቶች ናቸዉና በባህሪዋም ላይ ለውጥ ቢታይ የሚገርም አይሆንም፡፡ እነኚህን ጊዜያት በተለይ የሕይወት አጋራቸው የሆኑ ወንዶች በሚገባ ማስተዋል ይኖርባቸዋል፡፡ ይህን ማስተዋል ከሴት ልጅ አንፃር ለሚወስዱት እርምጃ ምክንያታዊና ትክክለኞች እንዲሆኑ ያስችላቸዋል፡፡ ብትነጫነጭ፣ ብትቆጣ፣ ብትበሳጭ፣ ሆድ ቢብሳት፣ ቢደብራት … ምን አባቷ! ብሎ ከመቆጣት  ይልቅ ምን ሆና ነው!? ብሎ ጠጋ ብሎ ነገሩን መመርመሊ ሳይሻል አይቀርም፡፡


❀ ✨                               
╠═══ •『 ﷽ 』• ═══╣
┣𝐆RP• @Rihu_islamic_Discussion   
┣━━━━╗ ❤️ ╔━━━━⎙
┣CHL• @Rihu_islamic_post
╠════•❁🎐❁•═════╣
🌐 #SHARE_The_خير

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

15 Nov, 08:00


ዱንያ አጠፋፋችን አይደል አህባቢ 😶‍🌫️
ምንም ይሁን ምንም ለዱንያ እጅ አንሰጥም . . .

✅:ዱንያ ላይ ያለነው ለመኖር ነው፡፡ እስከኖርንም እጅ አንሠጥም #እንታገላታለን፡፡ እጃችንን ሰብስበን ዱንያን በብርቱ እንፋለማታለን፡፡ እና አላህ የሚታገሉትን #ይረዳልና በቻላችሁ መጠን ሁሉ ታገሉ፡፡ ⚡️

➡️የሆነች ነገር ሞክሩና 'ጌታዬ ሆይ በዚህች ላይ ትንሽ ጨምርልኝ' በሉ፡፡ የአላህ ትንሽ ነገር ብዙ ናት፡፡ የሱ ጠብታ እዝነት ተራራ ናት፡፡

. . .

✨:የቻላችሁትን ያህል በአላህ ትዕዛዝ ሥር ተገኙ፡፡

✨:አቅማችሁ በፈቀደው መጠን መልካም ሥሩ፡፡

✨:አላስተዋላችሁም እንጂ ብዙ ነገር ተሠጥታችኋል፡፡

✨:አላህ ከሠጣችሁ መልካም ቃላት ይሁን ገንዘብ ወይም ከሌላ ነገር አትሰስቱ፡፡

✨:በቀን ይሁን በማታ ለችግረኞች እጃችሁን ዘርጉ፣

✨:የተጨነቁትን አብሽሩ በሉ፣

✨:የየቲሞችን እንባ አብሱ፣

✨:ተስፋ የቆረጡትን አጽናኑ፣

✨:ሐዘን ለገባቸው ፈገግ አሳዩ፣

✨:ግራ ለተጋቡት ያልፋል በሉ፣

✨ሀሳብ ካዳከማቸው አጠገብ ሁኑ፣

✨:የተሰበሩትን ጠግኑ፣

✨:የተጎዱትን አክሙ፣

✨:ሸክም ለከበዳቸው መከታ ሁኑ፡፡

✨✨✨✨✨✨✨✨

🫀:እንዲያ ስንሆን የዱንያን ፈተናዎች አብረን እንሻገራለን ። እንዲህ ጥሩ ስንሆን አላህ ይወደናል፤ ይቀበለናል፡፡ እሱ ከተቀበለን ሌላው ሁሉ ቢጥለንም ምንም አይደል፡፡  

🔥🔥🔥🔥🔥
✧╭┻┻┻┻┻┻┻┻┻┻╮✧
✧┃╱╲ 🍓╱╲🍒 ╱╲┃✧
╭┻━🍒━━━🍍━━━┻╮
┃╱╲╱╲ 🍈╱╲🍇 ╱╲ ┃
🎁━━━━━━━━━━━━🎁
✨💕 @Rihu_islamic_post 💕✨

🌐 #SHARE_The_خير🔺

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

15 Nov, 03:02


➥ወይ ምኞቴ‼️▯ﻳَﺎ ﻟَﻴْﺘَﻨِﻲ▯

. . . .▯ ﻳَﺎ ﻟَﻴْﺘَﻨِﻲ ﻛُﻨﺖُ ﻣَﻌَﻬُﻢْ ﻓَﺄَﻓُﻮﺯَ ﻓَﻮْﺯًا ﻋَﻈِﻴﻤًﺎ

🖱:▯. . . . . «ታላቅ ዕድልን አገኝ ዘንድ ከነሱ ጋር በኾንኩ ወይ ምኞቴ!» ይላል፡፡▯
●𝗤𝗨𝗥𝗔𝗡 4-73●

●ﻳَﺎ ﻭَﻳْﻠَﺘَﻰٰ ﻟَﻴْﺘَﻨِﻲ ﻟَﻢْ ﺃَﺗَّﺨِﺬْ ﻓُﻼَﻧًﺎ ﺧَﻠِﻴﻼً

🖱:▯«ዋ ጥፋቴ! እገሌን ወዳጅ ባልያዝኩ ኖሮ እመኛለሁ፡▯
●𝗤𝗨𝗥𝗔𝗡 25-28●

●ﻳَﻘُﻮﻝُ ﻳَﺎ ﻟَﻴْﺘَﻨِﻲ ﻗَﺪَّﻣْﺖُ ﻟِﺤَﻴَﺎﺗِﻲ

🖱:▯«ዋ እኔ! ምነው በሕይወቴ (መልካምን ሥራ) ባስቀደምኩ ኖሮ» ይላል፡፡▯
●𝗤𝗨𝗥𝗔𝗡 89-24●

●. . . . ﻳَﺎ ﻟَﻴْﺘَﻨِﻲ اﺗَّﺨَﺬْﺕُ ﻣَﻊَ اﻟﺮَّﺳُﻮﻝِ ﺳَﺒِﻴﻼً

🖱:▯. . .. «ከመልክተኛው ጋር ቀጥተኛን መንገድ ይዤ በኾነ ዋ ምኞቴ!»▯
●𝗤𝗨𝗥𝗔𝗡 25-27●

●. . . . ﻳَﺎ ﻟَﻴْﺘَﻨَﺎ ﺃَﻃَﻌْﻨَﺎ اﻟﻠَّﻪَ ﻭَﺃَﻃَﻌْﻨَﺎ اﻟﺮَّﺳُﻮﻻَ

🖱:▯«. . . . .ዋ ምኞታችን! አላህን በተገዛን መልክተኛውንም በታዘዝን ኖሮ». . . .▯
●𝗤𝗨𝗥𝗔𝗡 33-66●

●. . . ﻳَﺎ ﻟَﻴْﺘَﻨِﻲ ﻟَﻢْ ﺃُﻭﺕَ ﻛِﺘَﺎﺑِﻴَﻪْ

🖱:▯. . .. «ዋ ጥፋቴ! ምነው መጽሐፌን ባልተሰጠሁ». . . ።▯
●𝗤𝗨𝗥𝗔𝗡 69-25●

●. . . . ﻳَﺎ ﻟَﻴْﺘَﻨِﻲ ﻛُﻨﺖُ ﺗُﺮَاﺑًﺎ

🖱:▯. . . ዋ ምኞቴ! ምንነው ዐፈር በኾንኩ. . . .▯
●𝗤𝗨𝗥𝗔𝗡 78-40●

🪧:በመጨረሻው በጭንቁ ቀን እንዲህ ከማለታችን በፊት ኸይር ስራን ባገኘነው አጋጣሚ እናስቀድም ችላ አንበል ትልቁ ፀፀት ማለት ይህ ነው❕ወላሂ ከዚ በላይ ፀፀት የለም❗️
➠ነፍሳችን በሰውነታችን ውስጥ እስካለች ድረስ አላህ የሕይወታችንን አዲስ ቀን ሰጥቶናል። ጊዜው ሳይረፍድ እና ትልቁን ፀፀት ከመጸጸታችን በፊት አሁኑኑ በምርጥ አጋጣሚ ተጠቅመን (በረመዳን ወር) ወደ አላህ እንመለስ❗️

ﻭَﻣَﻦْ ﺃَﺣْﺴَﻦُ ﻗَﻮْﻻً ﻣِّﻤَّﻦ ﺩَﻋَﺎ ﺇِﻟَﻰ اﻟﻠَّﻪِ ﻭَﻋَﻤِﻞَ ﺻَﺎﻟِﺤًﺎ ﻭَﻗَﺎﻝَ ﺇِﻧَّﻨِﻲ ﻣِﻦَ اﻟْﻤُﺴْﻠِﻤِﻴﻦَ

➠ወደ አላህ ከጠራና መልካምንም ከሠራ፣ «እኔ ከሙስሊሞች ነኝ» ካለም ሰው ይበልጥ ቃሉ ያማረ ማን ነው?▯ፉሲለት-33▯

☑️:ይሄንኑ መልዕክት ሼር በማረግ በጎ ስራን ከአሁኑ እንጀምር።

@Rihu_islamic_post
@Rihu_islamic_post

#SHARE_The_خير

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

14 Nov, 09:43


አስሬ ማጉረሴ...

በህይወት መስመሬ እጅግ የሚነደኝ፡
እንቅልፍ እየነሳ ፀንቶ እሚያሳድደኝ፡

ተስፋ እያስቆረጠ ሁሌ የሚገድለኝ፡
ከውስጤ እማይጠፋ አንድ ብሶት አለኝ፡

ባስታወስኩት ቁጥር ሚያጣላኝ ከራሴ፡
አብሮኝ ለማይራብ አስሬ ማጉረሴ፡
@Rihu_Tube

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

12 Nov, 04:42


📐~በጥንቃቄ ይሁን~🖇
▱▰▱▰▱▰▱▰▱▰
➧ከሞኝ ጋር ስተከራከር~🪧
➧ከአዋቂ ጋር ስትከራከር~📕
➧ክብር ያለውን ሰው ማዋረድ ስትሞክር~🔎
➧ደካማን ሰው ስታከብር~📌
➧ከመጥፎ ጋር ስትወዳጅ~🖍 በጥንቃቄ ይሁን።

📍~ሞኝነት ነው~📌

➧ተውባን ማዘግየት~⏳
➧ሞትን መርሳት~🪔
➧ሚስጢርን ማባከን~🩸
➧አላማን መዘንጋት~💡
➧ግዴታን አለመወጣት~〽️
➧ጊዜን ማባከን~⏰
➧ወላጅን አለመታዘዝ~🎗
➧ሰውን መበደል~💢 ሞኝነት ነው።

@Rihu_islamic_post
@Rihu_islamic_post

#SHARE_The_خير

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

12 Nov, 02:31


➡️የጧት ዚክር

وَاذْكُرِ اسْمَ رَبِّكَ بُكْرَةً وَأَصِيلًا

▪️የጌታህን ስም በጧትና በማታ አውሳ!!

ውሎህን በዚክር ጀምር

@Rihu_islamic_post

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

10 Nov, 18:50


بسم الله

-ቂርዓት ላይ ያለሽ እህት ሆይ ኢልም መቅሰም ሂወትሽን ሙሉ የምትሰጭዉ ዉድ ነገር ይሁን እንጂ እስክታገቢ ወይም ሀገር ቤት እስክትገቢ ጊዜ ማሳለፊያ አታድርጊዉ ።

- ሴት መሆንሽ ኣሊማህ ከመሆን አያግድሽምና በኢልም ትልቅ ደረጃ እንደርሳለሁ ብለሽ ለነፍስሽ ንገሪያት ሂማሽን በጣም ከፍ አድርጊ ለዚህም የሴት ምሁራኖች ታሪክ ማንበብ ይረዳሻል ።

አንጋፋው የአል-ሃፊዝ ኢብኑ ሀጀር ተማሪ አል-ኢማም السخاوي ከ80 በላይ ሸይኻዎቹ ሴቶች ነበሩ بين فقهية ومسندة ታዉቂያለሽ ????

-ከአመት አመት አጫጭር ኪታቦች ብቻ አትቅሪ ይልቁን በቅደም ተከተል ከሙኽተር ኪታቦች አንስተሽ እስከ ሰፋፊ ኪታቦች መቅራት አለብሽ በዚህም ነዉ እዉቀትሽን የምታዳብሪዉ ብዙ እህቶችንም በፈትዋ ምታብቃቂዉ
ለምሳሌ ዘንድሮ ሰፊና እየቀራሽ ከሆነ የዛሬ 3 or 4 አመት ሚንሃጅ መጨረስ አለብሽ አቂዳም እንደዚሁ ፈትሁል መጂድ ምናምን ማጠናቀቅ አለብሽ ሌሎች ፈኖችም ላይ እንደዚሁ ።

በዚሁ አደራ ምልሽ ያለአቅምሽ ያለደረስሽበትን ፈን ወይም ኪታብ አትዳፈሪ فإنه من رام العلم جملة ذهب عنه جملة .

-ምንም ቢያነሳሱሽም በሱና ሰዎች መሀከል ባለ ልዩነት እራስሽ ቢዚ አታድርጊ ።

-ጎደኞችስ አንቺን የሚመስሉ ለቂርዓት ትኩረት የሚሰጡ እንጂ በተራ ወሬ ዉድ ጊዜያቸውን የሚያባክኑ አይሁኑ ።

بالله التوفيق

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

10 Nov, 16:32


⭕️ሐቢቢ‼️
✅:መልካም ነገር ማድረግ ቢያቅትህ እንኳ ክፉ ከመስራት ተቆጠብ።
✅:ሙስሊም ወንድምህን መጥቀም ባትችል እንኳ አትጉዳው።
✅:ወንድምህን ማስደሰት ባትችል እንኳን አታሳዝነው።
✅:የለመነህን መርዳት ባትችል አታሳጣው።
✅:ያገኘውን ባትጨምርለት አትቀንስበት።
✅:የተሳካለትን ባታግዘው እንኳ አትመቀኘው።
✅:ትልቅ ደረጃ ላይ የደረሰውን ለማክበር ባትታደል እንኳ አትናቀው።
✅;የበለጠህን ማድነቅ ባይሆንልህ እንኳ አትክሰሰው።
✅:የሰውን ስም ማጥፋት ፣ ማማትና መመቀኘት በራስ ላይ እዳ ማምጣት ነው።
✅:ባለዕዳ ከመሆን በዋናው መኖር ይሻላል።
✅:በዕዳ ከመታሰር ባዶ እጅ መሆን ይመረጣል❕

🔰 @Rihu_islamic_post
🔰 @Rihu_islamic_post
🔰 @Rihu_islamic_post

#SHARE_The_خير_

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

08 Nov, 16:56


🍂🍂...."ዙለይካ"


💫💫 ነብዩሏህ ዩሱፍን (አ.ሰ) ያፈቀረች ጊዜ እስር ቤት እያለ ሄዳ መጠየቅ ስለማትችል/ ስለተከለከለች ድምፁ በጣም ናፈቃት እና የእስር ቤቱን ገራፊ ጠርታ እንዲገርፈው አዘዘችው ሲገርፈው ድምፁን ለመስማት ገራፊውም ግራ ገባው በምን ሰበብ ይግረፈው

ሄዶ ለነብዩሏህ ዩሱፍ(አ.ሰ) አማከረው እና እንዲህ አለው እኔ መሬቱን ስመታ አንተ ትጮሃለህ አለው
በዚህ ተስማምተው መሬቱን ሲመታ ዩሱፍም ይጮሀል
ከዛን ወደ ዙለይካ ተመልሶ ሲመጣ

ዋሸኸኝ አለችው እሱም እንዴት አወቅሽ እመቤቴ አላት
እሷም አለች ዩሱፍን ብትመታው ኖሮ እኔንም ይሰማኝ ነበር /እኔን ያመኝ ነበር አለችው ::

አጂብ ልክ እንደ ዩሱፍ የአሏህን እውነተኛ ፍቅር በልቦናዎቻችን ላይ ያኑርልን.........አሚን🤲

🍃🍃 መልካም ለይል አህባቢ🍃🍃

@Rihu_islamic_post

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

07 Nov, 09:16


-"الْبَاقِيَاتِ الصَّالِحَاتِ.🤎

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

05 Nov, 16:24


🔎~ፈገግታ #ከኡለሞች ጋር~😄
▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬▭
📌:ሙጊራህ ኢብኑ ሹዕባህ ረዲየላሁ ዐንሁ እንዲህ ይላሉ➘

▮"አንድም ሰው #ሸውዶኝ አያውቅም ከአንድ ወጣት #በስተቀር። የሆነ ጊዜ አንዲት ሴት ላገባ አሰብኩኝና ሳማክረው:▮

📍"አሚራችን ሆይ! እኔ #ባታገባት ይሻላል እላለሁ" አለኝ።
🔎"ለምን❓" ስለው

🔎"የሆነ ሰው #ሲስማት አይቻለሁ‼️" አለኝ።

📯ከዚያ እሱ እራሱ እንዳገባት ሰማሁና👇
"የሆነ ሰው ሲስማት አይቻለሁ አላልክም ነበር⁉️" ስለው

📭;"አዎ ልጅ እያለች አባቷ ሲስማት አይቻለሁ" አለኝ።
【አልቢዳያ ወንኒሀያህ: 8/53】
📕ትርጉም❳ኢብኑ ሙነወር

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

04 Nov, 22:22


የፈጅር ሶላት ለሚከብዳችሁ ሰዎች የሸይኽ ሷሊህ ኢብኑ ዑሰይሚንን ምክር አዳምጡ፡

1ኛ፡ በጊዜ መተኛት።

2ኛ፡ ስንተኛ ለፈጅር እነቃለሁ የሚል ትክክለኛ/ቁርጥ ያለ ኒያ መነየት/ማሰብ።

3ኛ፡ አላርም መሙላት፡ አላርሙ ሲጮህ አጠፋዋለሁ ብለን ከሰጋን አላርሙን ራቅ ያለ ቦታ ማስቀመጥ።

4ኛ፡ ሰዎች ፈጅር ላይ እንዲያስታውሱን፡ እንዲደውሉልን ማናገር።

አሏህ ሰምተው ከሚጠቀሙት ያድርገን 🤲
@Rihu_islamic_post
@Rihu_islamic_post

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

03 Nov, 18:44


=
ነገ ሰኞ ነው የቻልን እንፁም

ያልቻልን share እናድርግ ።

🌴አንድን ስራ ያመላከተ ሰው ከሰራውሰው እኩል አጅር ያገኛል ።

  📣ጆይን @muslimstudents1

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

03 Nov, 18:31


3:30 ይጀመራል

حديث أبي الدرداء في طلب العلم

ገባ ገባ በሉ

https://t.me/SUHHAilEdu?livestream

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

01 Nov, 08:30


🌷"►አጠር ያለች ግጥም ለውዷ እህቴ"🌷

ትሸፈነው እንጂ በመላ አካላቷ
ሒጃቧ ነውና የሴት ልጅ ውበቷ

ጀነት እንዲያስገባሽ ነውና ምኞቴ
የአላህን  ትዛዝ  ጠብቂው እህቴ"

ክብሯን እዲጠብቅ ዱሪዬ እንዳይደፍራት
"ባለጌና አጃቢ በሩቁ እንዲፈራት"

ስሟን እንዲጠብቅ ሰውም እንዲያከብራት
በውበት ላይ ውበት እንዲጨምርላት"

ለሴት ልጅ መሸፈን ይህን መረጠላት"
ለማስቸገር ሳይሆን መልካም አስቦላት
ውዱ ወንድሜ አቡ/ ኣኢሻ አወል
   ••       •⊰✿🌹✿⊱•      ••
📚 @Rihu_islamic_post
📚 @Rihu_islamic_post
📚 @Rihu_islamic_post

#SHARE

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

30 Oct, 17:37


💢~መከራና ችግር~💥
▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬
✅:አትፍራ ወዳጄ! ልብ በል ሐቢቢ‥. አላህ (ሱብሃነሁ) ከዋለልን ፀጋዎች አንፃር ስናይ የመከራ ዕድሜ ትንሽ ነው፡፡ እድሜ ልኩን በምድር ላይ ሲንከራተት ኖሮ የሞተ ሰው የለም፡፡ ዱኒያ አንድ ቀን ብታስለቅሰን አንድ ቀን ልትስቅልን ግድ ነው።

🔎:የሚገርመው ፍፁም ፍትሃዊ የሆነ ጌታችን አላህ (ሱብሃነሁ ወተዐላ) በሷ ላይ በሚያገኘን ትንሽም ሆነ ትልቅ ችግር ምንዳ ለገሰን፡፡ የመከራ
#ምንዳው✨ #በጤናና #በድሎት ጊዜ ከሚያገኙት በላይ
ነው፡፡ ከሱ የሚገኘው ልምድም ከየትኛው የህይወት ትምህርት በላይ ነው፤ ጥቅሙም ከማንኛውም ሀብት የላቀ ነው~😌

🖍:አንድ ቀን የሆነ ሰው
#ኢማሙ_አሽሻፊዒን “ፈተና ከበዛበትና እርጋታ ከሞለበት ህይወት ለአንድ ሰው የትኛው ይሻለዋል?” በማለት ጠየቃቸው:: ኢማሙም እንዲህ በማለት መለሡ➘

▮ፈተና የበዛበት ህይወት ይሻለዋል: ምክንያቱም አላህ ነቢዩ ኑህን፣ ነቢዩ ኢብራሂምን፣ ነቢዩ ሙሣን፣ ነቢዩ ዒሣን እና ነቢያችን ሙሐመድን ﷺ ፈተናቸው። በመጨረሻም የተረጋጋ ህይወት ሠጣቸው▮
┊  ┊  ┊  ┊
┊  ┊  ┊  ✿
┊  ┊  ❀ 🍃
┊  ✿ ✨
❀ 📗               
╠═════ •『  』•   
┣━━━━━━╗ 🍀

┣𝐂𝐡𝐚𝐧𝐧𝐞𝐥• @Rihu_islamic_post
╠═══════•❁❀❁•══════
#SHARE_The_خير

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

30 Oct, 11:52


➪አግባ......
ዐብደሏህ ኢብኑ መስዑድ ረዲየሏሁ ዐንሁ
እንዲህ ይላል: -
🌹« ለመኖር አስር ቀናቶች ቢቀሩኝና ከአስር ቀናቱ እንዳለቁ እንደምሞት ባውቅ እናም (ሚስት) ለማግባት ጊዜ ባገኝ ፊትናን ፈርቼ አገባ ነበር ።»
[ሰዒድ ቢን መንሱር አስሱነን 493]
@Rihu_islamic_post
@Rihu_islamic_post

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

28 Oct, 13:58


✅:መንገድ የምታቋርጥ ጉንዳን አትርገጥ፣

✅:ጥሬ የምትለቅም ወፍ አታስደንግጥ፣

✅:ዉሃ የሚጠጣ ዉሻ አታባርር፣

✅:ርቦት የሚግጥ እንሠሣ አታስደንብር፣

✅:ተመቻችታ የተኛች ድመት አትቀስቅስ፣

✅:የሸረሪት መኖርያን አታፍርስ፡፡

➣ይላል #ኢስላም፡፡ ሱብሓነከ ረቢ!

🤔 እየኖርነው ነው ግን ❓

╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ-
@Rihu_islamic_post
@Rihu_islamic_post

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

26 Oct, 16:12


ትዝታ. . .
✅:የድሮ ልብሶችህን፣ ማስታወሻዎችህን፣ ጓደኞችህን እና ሌሎችንም ነገሮች እንደ ዋዛ አትጣላቸው። ያደግክባቸው መንደሮችና ቤቶች አትርሳቸው። ዛሬ ላይ ሆነህ መለስ ብለህ የበፊቱን ህይወትህን ትቃኝበታለህ። አላህ(ሱብሃነሁ ወተዐላ) ከየት አንስቶ የት እንዳደረሰህ፣ ከምን አንስቶ ወዴት እንደወሰደህ ታስተነትንበታለህ። ተሻሽለህ ከሆነ ይበልጥ የአላህን ፀጋ ታመሰግንበታለህ። ቀንሰህ ከሆነ ደግሞ በአዲስ እልህ ትነሳሳለህ። የሰው ልጅ በየቀኑ አይታወቀውም እንጂ ለውጥ ላይ ነው። የድሮ ቅሪቶቻችን ምላስ ኖሯቸው መናገር ባይችሉም እንኳ ስለኛ ብዙ ይናገራሉ። ለኛም ብዙ ትምህርትን ይሰጣሉ። #ትዝታ ወደኋላ ተመልሰን የድሮ ማንነታችንን የምንቃኝበት ፓስፖርታችን ነው።
──────⊱◈◈◈⊰──────
📚 @Rihu_islamic_post
📚 @Rihu_islamic_post
📚 @Rihu_islamic_post

#SHARE_The_خير_

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

26 Oct, 09:34


ሶላት አሰጋገዳችን ያማረ ሊሆን የሚችለው አላህን ስንፈራ ነው! አላህን የሚፈራ ሰው ቤትም ውስጥ ይስገድ መስጅና አደባባይም ላይ ይስገድ ለብቻው ጨለማ ላይም ይስገድ ነብያችን ስገዱ ባሉት መልኩ ረጋ ብሎ ልቡን ሰብስቦ መስፈርቱን መሰረቱን አሟልቶ ይሰግዳል አላህን የማይፈራና ፈራቻው የሚጐለው ሰው ግን ቢሰግድም ላይ ላዩን ነው ነካ ነካ የሚያደርገው የሙናፊቅ ሶላት ነው የሚሰግደው ልክ ዶሮ እህል እንደሚያነሳው ሩኩንም ሱጁዱንም አጣድፎ የሚወጣው/የምትወጣው። በምንኛውም ሁኔታችን ላይ አላህን የፈራን እንሁን።

የሶላታችንን ነገር አደራ! የማንሰግድም እንስገድ የምንሰግድም ሩህ ያለው ሶላት እንስገድ። ስንሰግድ ለመላቀቅ ሳይሆን ከሶላቱ ጥቅም ለማግኘት ይሁን።


የሙሂ ማስታወሻዎች

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

24 Oct, 16:23


🤲"አላህ ሆይ! ስጠን"🤲

💡#ደስታን፦ በየእለቱ ቀን በቀን፤ ከወንጀል ሀጢአት የሚያርቀን፤ በምድር ላይ በህይወት እስካለን።
💡#ጤናን፦ በጌታችን ኢባዳ እንድንበረታ፤ ለፆም ለፀሎቱ እንድንፍታታ።
💡#ሀብትን፦ የሰውን ልጅ ከማየት የምንብቃቃበት፤ ድሃ ችገረኛን የምናስታውስበት፤ ሀጅ ዚያራ የምንሄድበት።
💡#ጥንካሬን፦ በዱንያ ሙሲባዎች እንዳንፈታ፤ በሀዘን መከራ በበሽታ እንዳንረታ፤ በመሰናክሎች ከአላማችን እንዳንገታ።
💡#ቁርጠኝነትን፦ ዲናችንን የምንማርበት ፤ ያወቅነውን ላላወቁት የምናሳውቅበት፤ እራሳችንና ማህበረሰቡን የምንጠቀምበት።
💡#ልብን፦ ሀቅን በሀቅነቱ የምናውቅበት፤ መጥፎን መጥፎ መሆኑን ለይተን የምንሸሽበት፤ በጎ ነገርን የምንረዳበት፤ መልካም ነገርን ሁሉ የምናስብበት።
💡#ድፍረትን፦ ሀያሉን ጌታ አላህን የምንፈራበት፤ የምድር ላይ ሀላፊነታችንን የምንወጣበት፤ ኢስላምን ከጥቃት የምንከላከልበት።
💡#ወኔን፦ ከስንፍና አባዜ ለመውጣት፤ ለዚህች አለም የግምቷን ያህል ብቻ ዋጋ ለመስጠት።
🌷آمِينْ يَا رَبَّ الْعَالَمِين

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

24 Oct, 13:19


✅:በተግባር ባትችል ሀሳብ በመስጠት፣ በሀሳብ ባትችል በልቦናህ ለሰው በመጨነቅ ለሰው ጠቃሚ ሁን። አላህ መልካምነትህን ሲያይ እጅ እግርህን ጠፍሮ ባርያው ያደርግሃል፤ በበጎ ሥራዎች  ላይ ያሠማራሃል። መልካምን ነገር ሁሉ ያገራልሃል።

╭┈─────── ೄ🌹ྀ࿐ ˊˎ-

╰┈➤🌗ᢀ @Rihu_islamic_post

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

24 Oct, 12:52


#MoE

የ2017 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ ምደባ ይፋ ሆነ።

በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው በመደበኛው ፕሮግራም ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ለመከታተል የሚያስችል የማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ይፋ ሆኗል።

ተማሪዎች ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ምደባቸውን ማየት እንደሚችሉ ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።

በድረ-ገፅ 👇
https://placement.ethernet.edu.et
በቴሌግራም 👇
https://t.me/moestudentbot

የተቋም ይቀየርልኝ ጥያቄ የማያስተናግድ መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳውቋል

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

24 Oct, 11:58


እህቴ ሆይ አላህን ፍሪ!
~
እስኪ ውስጥሽን አዳምጪው። ለማን ነው ይህን ያደረግሽው? አላህ ምን ይለኛል ብለሽስ አስበሻል? ተይው አላህ ዘንድ ሰው ዘንድ ራሱ ያስንቅሻል። ከጌታሽ ተጣልተሽ፣ ሰዎች ዘንድ ትዝብት ላይ ወድቀሽ ምን ትርፍ ታገኛለሽ?

ለማንኛውም ነብያችን ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
" صِنْفَانِ مِنْ أَهْلِ النَّارِ لَمْ أَرَهُمَا ؛ قَوْمٌ مَعَهُمْ سِيَاطٌ كَأَذْنَابِ الْبَقَرِ يَضْرِبُونَ بِهَا النَّاسَ، وَنِسَاءٌ كَاسِيَاتٌ عَارِيَاتٌ، مُمِيلَاتٌ مَائِلَاتٌ، رُءُوسُهُنَّ كَأَسْنِمَةِ الْبُخْتِ الْمَائِلَةِ، لَا يَدْخُلْنَ الْجَنَّةَ، وَلَا يَجِدْنَ رِيحَهَا، وَإِنَّ رِيحَهَا لَيُوجَدُ مِنْ مَسِيرَةِ كَذَا وَكَذَا "
"ሁለት አይነት ሰዎች ከእሳት ጓዶች ውስጥ ናቸው። እኔ አላየኋቸውም (ወደፊት ይመጣሉ።)
* እንደ ከብት ጅራት ያለ መግረፊያ ይዘው ሰዎችን በነሱ የሚደብድቡ ሰዎች እና
* ለብሰው የተራቆቱ፣ ለሌሎች ጥፋታቸውን የሚያስተምሩ፣ ከአላህ ትእዛዝ ያፈነገጡ፣ ፀጉሮቻቸው እንዳዘነበሉ የተከመሩ የግመል ሻኛዎች የሆኑ ሴቶች ናቸው። እነዚህ ጀነትን አይገቡም። ሽታዋንም አያገኙም። ሽታዋ ከብዙ ርቀት የሚገኝ ነው።"

📚 ሙስሊም ዘግበውታል።

منقول

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

24 Oct, 08:25


የኢባዳ መስፈርቶች

☞ አንድ ሠው አንድ ኢባዳን ከመስራቱ በፊት ሶስቱ ነገሮችን ቀደም ብሎ ማስተካከል ይኖርበታል

① በአላህ ማመን

በአላህ ማመን ከ ኢማን መሰረቶች ሁሉ ወሳኙ የላቀ ደረጃ ያለውና የአእማዶች ዋና ምሰሶ ሲሆን የተቀሩት የኢማን መሰረቶች የእርሱ ቅርንጫፍና በርሱ ውስጥ ተካታቾች ናቸው፡፡ በአላህ ማመን አላህ በጌትነቱ ፣በአምላክነቱ ፣ በስሞቹና ባህሪያቱ ብቸኛ መሆኑን ማመን ሲሆን እነዚህ ሶስቱ በአላህ
ለማመን ዋና ዋና መሰረቶች ናቸው፡፡
እንዲያውም ከግድፈት የፀዳው የእስልምና ሃይማኖት “ተውሂድ ” የተሰኘበት ምክንያት አላህ በንግስናውና በጌትነቱ አጋር
የሌለው ፣ በአካሉ ፣በስሞቹና ባህሪያቱ አምሳያ የሌለውና እንዲሁም በአምልኮ ቢጤ የሌለው ብቸኛ መሆኑን በማመን
የተመሰረተ በመሆኑ ነው፡፡ በዚህ መሰረት የነብያትና የመልዕክተኞች ተውሂድ በሶስት
እንደሚፈልግ ግልፅ ይሆናል፡፡

አንደኛው ክፍል “ተውሂድ ሩቡብያ” ፡- አላህ የሁሉም ነገር ጌታ፣ ንጉስ፣ ፈጣሪና ሲሳይ ለጋሽ መሆኑን ፣ ህይወት ሰጭ ፣ ገዳይ ፣
ጠቃሚ፣ ጎጂ፣ በጭንቅ ጊዜ ሲጠራ አቤት ባይ ፣የነገሮች ሁሉ ገዥ ፣የመልካም ነገሮች ባለቤት ነገሮችን ሁሉ ወደርሱ መላሽና
በእነዚህ ነገሮች ሁሉ አጋር የሌለው መሆኑን ማመን ነው፡፡
ሁለተኛው ክፍል “ተውሂዱል ኡሉሂያ” ፡-ራስን ዝቅ ብሎበመተናነስ ፣ በመውደድ፣በመፍራት፣ በማጎንበስ፣በግንባር በመደፋት፣ በማረድ፣ስለትን በማቅረብና በሌሎችም የአምልኮ ዘርፎች አላህን ብቸኛ ማድረግና አጋር እንደሌለው ማመን ማለት ነው፡፡

ሶስተኛው ክፍል “ተወሂዱል አስማኢ ወሲፋት”፡- አላህን በቁርአኑና በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ሀዲሶች እራሱን በሰየመባቸውና
በገለፀባቸው ስሞችና ባህሪያት እርሱን ብቸኛ በማድረግ ፣ከጉድለት ፣ ከነውርና የእ
የእርሱ መለያ የሆኑትን ባህሪዎች
ከፍጡራን ጋር ከማመሳሰል መጠንቀቅ ፡፡ እንዲሁም አላህ ሁሉን ነገር አዋቂ፣ በሁሉ ነገር ላይ ቻይ ፣ህያው፣ ራሱን ቻቀይ፣
ማንጎላጀትም ሆነ እንቅልፍ የማይዘው፣ ተፈፃሚ የሆነ ፍላጎትና የላቀ ጥበብ ባለቤት፣ሰሚ፣ተመልካች፣አዛኝ እንደሆነ ፣ ከዐርሽ በላይ ስልጣኖችን ተቆጣጣሪ፣ ንጉስ፣ቅዱስ የሆነና ሌሎችም
እጅግ በጣም ያማሩ ስሞችና የላቁ ባህሪዎች ያሉት መሆኑን ማመን ማለት ነው

✔ በአላህ ሳይታመን የሚሠራ ኢባዳ ፋይዳ አይኖረውም ይህን አስመልክቶ አላህ እንዲህ ይላል "(ከሀዲያን) ከስራ ወደ ሚሠሩት ስራ አሰብን የተበተነ አብዋራም አደረግነው "

②(ኢኽላስ) ፍፁማዊነት ይህም ማለት የሚሠራውን ኢባዳ ፍፁም ለአላህ ብቻና ብቻ ማድረግ (ስራን ከእዩልኝ እናከይሰሙላ የፀዳ ማድረግ ማለት ነው)አላህ ሡብሀነሁ ወተአላ እንዲህ ይላል ፦ "ለሡ ሀይማኖትን ጥርት አድርገው እንዲገዙት እንጂ አልታዘዙም "

☞ ይህ ጉዳይ በርካታዎቻችን የምንፈተንበት ከባድ በሽታ ነው ። ወደ አንድ ሠው ልብ ዘልቆ ሲገባ ፍፁም ረቂቅ በሆነ መንገድ መሆኑ ነገሩን ከባድ ያደርገዋል ።

☞ በዚህ በሽታ የተለከፈ ሠው የሚሠራው ስራ ፈፅሞ ተቀባይነት አይኖረውም አላህ ሡብሀነሁ ወተአላ ይህን አስመልክቶ በሀዲሰ አል ቁድስ እንዲህ ይላል ። "ከኔ ጋር አጋርቶ አንድን ስራ የሠራ ሠው ስራውንም ሰውዬውንም እተወዋለሁ "

☞ እስቲ እራሳችንን እንፈትሽበት ዘንዳ እነዚህን ጥያቄዎች እራሳችንን እንጠይቅ

1) ፌስቡክ ላይ ስንፅፍ ምን ፈልገን ነው፡፡ የ ላይክ ብዛት ለመቁጠር ከሆነ አላህ ይጠብቀን መክሰራችንን አውቀን ዛሬውኑ ስራችንን እናስተካክል፡፡

2) ዳዕዋ ስናደርግ፤ ‹‹ብቃት አለው›› መባል ፈልገን ነው ወይንስ የአላህን ፊት ፈልገንበት??? ኢኽላሳችን ችግር ካለው አሁንም ቢሆን ሳይረፍድ ዛሬውኑ፤ አሁኑኑ ለአንድ አላህ ብቻ
ስራችንን እናጥራ፡፡

3) ለቤተሰባችንም ይሁን ለሌሎች መልካም ስንውል ምን ፈልገንበት ነው???

☞ የአላህ ፊት ያልተፈለገበት ኢባዳ ፋይዳ የለውም!!

③ ሙታበአ(ረሡል ሠለላሁ አለይሒ ወሠለምን መከተል) ፦ በአላህ ያመነ እንዲሁም ስራውንም አላህ ይመነዳኛል ሢል አስቦ ኢባዳ
የሚሠራ ሠው የሚሠራውን ኢባዳ ረሡል ሠለላሁ አለይሒ ወሠለም
ሠርተውታል አልሠሩትም ብሎ መፈተሽ ይኖርበታል አላህ ሡብሀነሁ ወተአላ እንዲህ ይላል ፦ ""መልዕክተኛው ያመጣላችሁን ያዙት ፣ ከከለከላችሁም ተከልከሉ ""

⇑ ከእነዚህ (ከላይ ከተጠቀሡት ሦስት መስፈርቶች) አንዱን ያጎደለ ኢባዳው
ተቀባይነት አይኖረውም!!!
☞ ሙስሊም ያልሆነ ሠው የሠራው ስራ ዋጋ የለውም
☞ ኢቲባእ የሌለው ስራ ቢድአ ነው
☞ የአላህ ፊት ያልተፈለገበት ስራ እዩልኝ እና ስሙልኝ ነው
(ትንሹ ሽርክ ነው)

@Rihu_islamic_post
@Rihu_islamic_post

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

23 Oct, 16:20


ነገ ሐሙስ ነው እንፁመው

መፆም ካልቻልን፡ ፆመኛን በማስፈጠር የፆመኛን አጅር እናግኝ

ይህንንም ካልቻልን ሌሎች እንዲፆሙ እናስታውስ

መልካም ምሽት
@Rihu_islamic_post

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

23 Oct, 02:37


🔅~የአላህ ፍራቻ~⚠️
▱▰▱▰▱▰▱▰▱
✅:የዲን ምሰሶዎች ሦስት(3) ናቸው:: ይላሉ አንድ ዓሊም:: ◈እነርሱም▽
➥:አላህን መውደድ▯➀▯
➥:እሱን መፍራት▯➁▯
➥:በሱ ላይ ተስፋን ማሣደር▯➂▯

❇️:ውዴታን ከአእዋፍ አንፃር ስናየው እንደ ጭንቅላት ነው:: ፍራቻና በአላህ ላይ ተስፋን ማሣደር ደግሞ እንደ ሁለት ክንፎች::

➥:አንድ በራሪ ጭንቅላቱ ከሌለ በህይወት ይኖራል ተብሎ አይታሠብም:: ሁለት ክንፎቹን ያጣ እንደሆነ ደግሞ ሚዛኑን ያጣል። የአዳኞች ሁሉ መሽቀዳደሚያ እና የጉልበተኞች ሁሉ መረባረቢያ ይሆናል❕

❉ ╤╤╤╤ ✿ ╤╤╤╤ ❉
◢◤◢◤◢◤◢◤◢◤◢◤◢◤
ᴄʜᴀɴɴᴇʟ• @Rihu_islamic_post
┗━━━━ • ✿ • ━━━━┛
#SHARE_The_خير

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

22 Oct, 03:12


🚨 እንተዋወስ 🚨

«ምኞትሽን ያሳካልሽ»

➪ልታይ ልታይ በበዛበት የኢስላምን ስም እያጠፉ እርቃናቸውን የሚሄዱ ሴቶች በበዙበት አንቺ የፀሀዩን መክበድ ሳይበግርሽ በሙሉ ሂጃብ ♕︎ክብርሽና እምነትሽ ለጠበቅሽው እህቴ አላህ በዱንያም በአኼራ ያሰብሽውን ኸይር ያሳካልሽ


@Rihu_islamic_post❤️
@Rihu_islamic_post💛
@Rihu_islamic_post💝

#SHARE

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

21 Oct, 03:35


📝~ፈተና ወይንስ እርጋታ❔~💎
▰▱▰▱▰▱▰▱▰▱▰
➥:አንድ ቀን የሆነ ሰው ኢማሙ አሽሻፊዒን
"ፈተና ከበዛበትና እርጋታ ከሞላበት ህይወት ለአንድ ሰው የትኛው ይሻለዋል?”በማለት ጠየቃቸው::
➯ኢማሙም እንዲህ በማለት መለሡ፦
✅:ፈተና የበዛበት ህይወት ይሻለዋል። ምክኒያቱም አላህ ነቢዩ ኑህን፣ ነቢዩ ኢብራሂምን፣ ነቢዩ ሙሣን፣ ነቢዩ ዒሣን እና ነቢያችን ሙሐመድንﷺ ፈተናቸው:: በመጨረሻም የተረጋጋ ህይወትን ሠጣቸው::😌
✅:አንድ ሷሊህ ሰው 'በሰላት ውስጥ ቁኑት ከሚያስረዝመውና
ሱጁድ ከሚያስረዝመው የትኛዉ የተሻለ ነው?:: ተብሎ ተጠየቀ፡፡ እሱም፦
"ኢኽላስ ያደረገው/ስራውን ጥርት አድርጎ ለአላህ ብቻ የሰራው /" ሲል መለሰለት።
▱▰▱▰▱▰▱▰▱▰▱
❉ ╤╤╤╤ ✿ ╤╤╤╤ ❉
ᴄʜᴀɴɴᴇʟ• @Rihu_islamic_post
┗━━━━ • ✿ • ━━━━┛
#SHARE_The_خير

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

19 Oct, 16:47


🚸ሰውና ዘመኑ⏳
🗣ዘመኑ ትላልቅና ያማሩ ህንፃዎች በብዛት የተገነቡበት ዘመን ነው።
👉ነገር ግን ቤተሰብ የፈራረሰና ፍቺ የበዛበት ዘመን።
🗣ዘመኑ ሀብትና ገንዘብ የተትረፈረፈበት ዘመን ነው።
👉🏼ነገር ግን ሀብታሞች ዘካን ማውጣት ትተው ድሆችም ከምንም ጊዜ በላዬ የተረሱበት ዘመን ነው።
🗣ዘመኑ ጨርቃጨርቅ እና የተለያዩ አልባሳት በብዛት የተመረቱበትና ገበያ ላይ የዋሉበት ዘመን ነው።
👉🏻ነገርግን የሰው ልጅ ልብስ አስጠልቶት እርቃኑን አሳይቶ የሚሄድበት ዘመን ነው።
🗣ዘመኑ ወፍራም እና ቦርጫም ሰዎች የሞሉበት ዘመን ነው።
👉🏻ነገርግን ውስጣቸው ከኢማን ባዶ የሆኑ ጉረኞች የሞሉበት ዘመን ነው።
🗣ዘመኑ ሁሉም ሰው አውቋል ተምሯል የተባለበት ዘመን ነው።
👉🏻ነገርግን የሰው ልጅ ዛሬም ከእንስሳ ያልተለየበት ዘመን ነው።
🗣ዘመኑ የሰው ልጅ መጥቆ ወደ ጠፈር ተጉዞ ጨረቃ ላይ ያረፈበት ዘመን ነው።
👉🏻ነገርግን እስካሁንም የሰው ልጅ ፈጣሪውን ያላገኘበትና ያላወቀበት ዘመን ነው።
🗣ዘመኑ ስለ ሰላም የሚለፈለፍበት ዘመን ነው።
👉🏻ነገረ ግን ጦርነትና ስደት የሰፈነበት ዘመን ነው።
🗣ዘመኑ ሙስሊሞች ከመቸውም ጊዜ በላይ ቁጥራቸው የበዛበት ዘመን ነው።
👉🏻ነገር ግን እስልምናቸው የስም ብቻ ሆኖ እነሱም የተዋረዱበት ዘመን ነው።
🗣ዘመኑ ዑለማዎችና የህግ ሰዎች የበዙበት ዘመን ነው።
👉🏻ነገርግን ሀቅን የሚናገር በአላህ ቃልም የሚፈርድ የጠፋበት ዘመን ነው።
🗣ዘመኑ አለማችን አንድ ለመሆን የተቃረበችበት /globalization/ ዘመን ነው።
👉🏻ነገር ግን የሰዎች የአመለካከት ልዩነት በእጅግ የተራራቀበት ዘመን ነው።
🗣ዘመኑ በርግጥ ሴቶች የበዙበት ዘመን ነው።
👉🏻ነገርግን ለሚስትነት ብቁ የሆኑ ሷሊህ ሴቶች የጠፉበት ዘመን ነው።
🗣ዘመኑ በእርግጥ ወንዶች የበዙበት ዘመን ነው።
👉🏻ነገርግን ለባልነት የሚመረጡ መልካም ባሎች የጠፉበት ዘመን ነው።
──────⊱◈◈◈⊰──────
@Rihu_islamic_post
@Rihu_islamic_post
@Rihu_islamic_post

#SHARE_THE_خير

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

19 Oct, 02:24


👉10 የልብ ህመሞች ✏️

1……✍ በአላህ (ሱብሀነ ወተአላ) እናምናለን እንላለን ነገር ግን ትዕዛዙን አንተገብርም።

2…..✍ ረሱልን (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ) እንወዳሉን እንላለን ግን የሳቸውን ፈለገ ሱናቸውን በመተግበር አልተከተልንም ።

3…..✍ ቁርዐን እንቀራለን ነገር ግን ወደተግባር አንለውጠውም።

4…..✍ የአላህ (ሱወ) ፀጋ ሁሌ ይደርሰናል ነገር ግን አመስጋኝ አልሆንም።

5….✍ ሸይጧን ጥላታችን እንደሆነ እንናገራለን ግን ከእርሱ ተቃራኒ አልቆምንም።

6….✍ ጀነት መግባትን እንፈልጋለን ነገር ግን ለመግቢያ የሚያግዘን ስራ እየስራን አይደለም።

7….✍ ጀሀንብ መግባትን አንፈልግም ነገር ግን ከሱ ለመራቅ ምንም አይነት ሙከራ አላደረግንም።

8….✍ ሁሉም ህይወት ያለው ነገር እንደሚሞት እናውቃለን ነገር ግን ለሞት እየተዘጋጀን አይደለም።

9….✍ ሰዎችን እናማለን ስህተታቸውን ለማውጣት እንጥራለን ነገር ግን የራሳችንን ጥፋትና ወንጀል እረስተናል።

10….✍ ሙታንን እንቀብራለን ነገር ግን ከዚህ ተግባራችን ትምህርት አንወስድም

«✆አንዲትም መልዕክት ብትሆን ከኔ አድርሱ» የሚለውን ነብያዊ ትዕዛዝ
ለማድረስ ብዮ ነው።

@Rihu_islamic_post

⬆️⬆️⬆️⬆️⤴️JOIN⤴️⬆️⬆️⬆️

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

18 Oct, 02:56


✅ ከጁመዓ ቀን ሱናዎች
➠➻➠➻➠➻➠➻➠➧
↩️‏ #سنن_يوم_الجمعة

➊ الغسل
➋ الطيب
➌ السواك
➍ لبس الجميل
➎ قراءة سورة الكهف
➏ التبكير لصلاة الجمعة
➐ الإكثار من الدعاء والصلاة على النبي ﷺ
🔹ገላን መታጠብ
🔹ሽቶ መቀባት
🔹ሲዋክ መጠቀም
🔹ጥሩ ልብስ መልበስ
🔹ሱረቱ ከህፍን መቅራት
🔹በጧት ለጁመዓ ሶላት መጣድ
🔹በነብዩ  ላይ ዱዓና ሰለዋት  ማብዛት

اللَّهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ، وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ كَمَا صَلَّيْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ، اللَّهُمَّ بَارِكْ عَلَى مُحَمَّدٍ، وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ، كَمَا بَارَكْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ، وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيد
      
الَّلهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى نَبَيِّنَا مُحَمَّد ٍﷺ 
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى نَبَيِّنَا مُحَمَّدٍ ﷺ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى نَبَيِّنَا مُحَمَّدٍ ﷺ


🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

17 Oct, 17:02


━━━━━━✦✿✦━━━━━━
ነብዩ ﷺ በመሰደባቸው የተቆጣው ውሻ
━━━━━━✦✿✦━━━━━━

☔: ከሞጎላዊያን አንድ ባለስልጣን የክርስትናን ሃይማኖት ከተቀበለ ጥቂት ጊዜያት በኋላ ሀይማኖቱን መቀበሉን አስመልክቶ በተዘጋጀ ድግስ ከተወሰኑ ቄሳውስቶች ጋር ሰብሰብ ብለው ተቀምጠዋል። ከአቅራቢያቸው አንድ ለአደን የተዘጋጀ ውሻ ታስሯል።
☔: በወቅቱ ከነበሩ ቄሶች አንዱ ለዓለማት እዝነት የተላኩትን ታላቁን ነቢ ሙሀመድ ﷺ በመጥፎ ማንሳትና መተቸት ብሎም መሳደብ ጀምሯል። ታዲያ ይህንን ሲሰማና ሲታዘብ የነበረው ውሻ እጅግ ተቆጣ ፤ ወዲያውኑ በከፍተኛ ድምፅ እየጮኸ ተሳዳቢውን ቄስ ዘሎ ነከሰውና አቆሰለው ፤ በአቅራቢያው የነበሩ ሰዎችም ተረባርበው አዳኑት ። ሰዎቹም፦ "ውሻው የምትናገረው ነገር አልተስማማውምና ሰለ ሙሀመድ (ﷺ) መጥፎ ከመናገር ተቆጠብ" ይሉታል ፤ ሰውየው ግን ፦ "አይ ችግሩ ከምናገረው አይመስለኝም ባይሆን በምናገርበት ወቅት እጄን ስዘረጋና ሳንቀሳቅስ ስለነበር እሱ ላይ የጠቆምኩበት መስሎት ነው" በማለት ስድብና ትችቱን ቀጠለ። ውሻው ግን ከመጀመሪያው በከፋ መልኩ በከፍተኛ ቁጣና ንዴት ዘሎ ጉሮሮውን በመንከስ ሰውየውን ገደለው።

➨ 👉 ይህ ክስተት በጊዜው የነበሩ ሰዎችን በከፍተኛ መልኩ አስገርሞ ነበር ፤ በዚህም ውሻ ምክንያት በወቅቱ ወደ 40 ሺህ የሚደርሱ ሰዎች እስልምናን ተቀበሉ።

➨ 👉 ክስተቱን ታላቁ አሊም ኢብኑ ሀጀር "አዱረሩል ካሚናህ" በተባለው መፅሃፋቸው አስፍረውታል።

✔የአላህን ሰራዊቶች እርሱ እንጂ ማንም አያውቃቸውም✔

━━━━━✦✿✦━━━━━
🦋 @Rihu_islamic_post
🦋 @Rihu_islamic_post
🦋 @Rihu_islamic_post

#SHARE

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

17 Oct, 08:57


የትዕግስት ደረጃ! አላህ በቁርዓኑ ደጋግሞ ያወሳው።

وَبَشِّرِ ٱلصَّٰبِرِينَ ﴿البقرة ١٥٥﴾


وَٱللَّهُ يُحِبُّ ٱلصَّٰبِرِينَ ﴿آل عمران ١٤٦﴾


وَٱصۡبِرۡ وَمَا صَبۡرُكَ إِلَّا بِٱللَّهِۚ ﴿النحل ١٢٧﴾


وَجَزَىٰهُم بِمَا صَبَرُواْ جَنَّةٗ وَحَرِيرٗا ﴿الإنسان ١٢﴾

إِنَّمَا يُوَفَّى ٱلصَّٰبِرُونَ أَجۡرَهُم بِغَيۡرِ حِسَابٖ ﴿الزمر١٠﴾

🌺https://t.me/Menehajselefiya
🌺https://t.me/Menehajselefiya

ŘïĤü🌺ÏSLÄMÏČ 🕋 PÖST🕌

17 Oct, 03:46


.


🌷تلاوة خاشعة


🌺 اللهم إجعل القرآن العظيم ربيع قلوبنا و نور صدورنا و جلاء همومنا و أحزاننا

7,146

subscribers

261

photos

149

videos