ሰውና ~ ፍልስፍናው @philoso_phy Channel on Telegram

ሰውና ~ ፍልስፍናው

@philoso_phy


☞የዕውቀት መጀመሪያ አለማወቅን ማወቅ ነው፠ ~ማወቅ ደግሞ ከማሰብ ይጀምራል✔️
#የፍልስፍና_ስራ_ሰውን ለተፈጠረበትየሰውነትአላማ ማብቃትነው
❖ ጥንታዊ ፍልስፍናዎች<
❖ አስገራሚ አውነታዎች<
❖ ሳይኮሎጂ<
❖ አስደማሚ ታሪኮች<
❖ መፅሀፍ ቅዱሳዊ አስተንትኖት<
☞ጠቅልሎ የያዘ ለነፍስና ለስጋ የሚበጁ ለሰላማዊ ህይወትም ሆነ ለምድራዊ ቆይታ መሠረት የሚሆኑ አጅግ በረካታ ሀሳቦችን ለናንተ ያደርሳል

ሰውና ~ ፍልስፍናው (Amharic)

ይህ ሰውና ~ ፍልስፍናው ታሪክ እና ፍልስፍና ገንዘብ ነው። ይህ ለነፍስና ፣ ለስጋ ፣ ለስላማዊ ህይወት፣ እና ለምድራዊ ቁይታ መሰረት የሚሆኑ ሰውኖችን ለናንተ የሚያደርሱትን እና ጠቅላላ መረጋገጫዎች በታካክ ሀሳቦች እናድርገማለን። የሰውና ~ ፍልስፍናው ታሪክ እና ፍልስፍና ገንዘብ መሳሪያዎች ሰፍቶ አገልግሎት እና ሥራ ተሰጠን። ሳይኮል ለመሆናቸው የተሳካ፣ ከትርጉም እና መረጋ እንዲሆን አስተውሉን።

ሰውና ~ ፍልስፍናው

25 Jan, 14:24


7ቱ 🌿የጃፓኖች ዐይን-ገላጭ የሕይወት መርሆዎች !

1⃣ IKIGAI

፨ በሕይወት ውስጥ ዓላማህን ድረስበት።
፨ ሰርክ ማለዳ የመንቃትህን ምክንያት እወቅ።
፨ አስፈላጊነትህን (ለዓለም)፣ ጥንካሬህን፣ ዝንባሌህን የተወዳጀ የሆነ ነገር አስስ። ይሄ ነው ለሕይወትህ ትርጉም የሚሰጣት።

2⃣ SHIKITA GA NAI

፨ መለወጥ የማይቻልህን ነገር ተወው፣ ልቀቀው።
፨ ካንተ ቁጥጥር ውጪ አንዳንድ ነገሮች መኖራቸውን እና ያም ያለ መሆኑን ተረዳ። ሂድ እና መቀየር በምትችለው ነገር ላይ ትኩረት አድርግ።

3⃣ WABI-SABI

፨ በጎዶሎነት ውስጥ ሠላምን አግኝ።
፨ ራስህ እና ሌሎችን ጨምሮ በሕይወት ውስጥ ምንም ነገር ፍፁም አለመሆኑን ተገንዘብ።
፨ ለእንከን-የለሽነት ከመትጋት ይልቅ ሕይወትን ልዩ በሚያደርጋት ጎዶሎነት ውስጥ ደስታን አጣጥም።

4⃣ GAMAN

፨ በፈታኝ ጊዝያቶች ክብርህን ጠብቅ።
፨ ፈተና ውስጥ እንኳ ብትሆን የሥሜት-ብስለትህን እና ራስ-ገዝነትህን አሳይ።
፨ ታጋሽ፣ ፅኑ፣ ተረጂ ለመሆን እንዳትዘነጋ።

5⃣ OUBAITIORI

፨ ራስህን ከማንም ጋር እንዳታወዳድር።
፨ ሁሉም የተለየ ጊዜ-ቤት እና ልዩ ጎዳና አለው።
፨ ራስህን በሌላው ለመለካት ከመሞከር ይልቅ በራስህ መሻሻሎች ብቻ ማተኮርህ አስፈላጊ ነው።

6⃣ KAIZEN

፨ ሰርክ በሁሉም የሕይወትህ ክፍል ውስጥ መሻሻሎችን ፈልግ!
፨ ጥቃቅን ለውጦች እንኳ መጠራቀም ችለው በጊዜ ሂደት ውስጥ ግዙፍ ለውጥ ያመጣሉ።

7⃣ SHU-HA-RI

"ተማሪዎቹ ሲዘጋጁ መምህሩ ይገኛል።"
―Teo Te Ching

👉 (እንዴት) ስለመማር እና በዘዴው ስለመጠበብ ማወቂያ መንገድ ነው። ከዕውቀቱ ለመድረስ ሶስት ደረጃዎች አሉት።

፨ SHU: የአንዱን አዋቂ (master) ትምህርት በመከታተል መሰረቶቹን መቅሰም!
፨ HA: ከአዋቂው የተቀሰመውን ትምህርት ከሙክረት በማዋሃድ የተግባር ልምምድ መጀመር።
፨ RI: ይሄ ደረጃ የሚያጠነጥነው ፈጠራዎች ላይ እና ትምህርቶቹን በተለያዩ መስኮች የመተግበር ችሎታ ላይ ነው።

ሰውና ~ ፍልስፍናው

22 Jan, 14:47


🌿"ምን ሆኛለሁ?"

የግድ ሊያነቡት የሚገባ የስነልቦና መፅሀፍ!

ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በስነልቦና ሳይንስ ተመርቃ የእርቅ ማዕድ ኘሮግራም መሰራች እንዲሁም እንመካከር የEBS ኘሮግራም ከዛም ባለፈ የአእምሮ ቁስለት (trauma) ላይ ለ17 አመታት የስነ ልቦና ሕክምና ስትሰጥ በቆየችው በ ትዕግስት ዋልተንጉስ እና ከዛዉ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በትያትር ጥበባት የመጀመሪያ ዲግሪውን አግኝቶ በተለያዩ የመንግስትና የግል ኘሬሶች ከሪፖርተርነት እስከ ዋና አዘጋጅነት እንዲሁም ሦስተኛው አይን፣ ሰዓት እላፊ፣ ሩብ ጉዳይ እና ከትዳር በላይ ትያትሮችን "ፍልስምና" በሚል ርዕስ 6 መፅሀፍትን በማሳተም ለተደራሲያን እንዲደርስ ባደረገው በቴዎድሮስ ተክለአረጋይ የተዘጋጀ እንደ ሀገር ፈር ቀዳጅ የሆነ መፅሀፍ ነው።

በታመመ ቤተሰብ ውስጥ ማደግ ፈተና ነው፡፡ ፍቅር፣ ትኩረት፣ መደመጥ የምግብ ያህል ይርበናል፡፡ ቤተሰብ ለእኛ ጊዜ የለውም፤ ምናልባት በአደንዛዠ እፅ ተይዟል፤ ቤት ውስጥ ቀን ተቀን የሚደበድብ ወንድም ወይም እህት፣ አክስት ወይም አጎት ይኖራሉ፡፡አንደኛው ወይም ሁለተኛው ወላጅ የአዕምሮ እክል ሊኖርበት ይችላል፡፡ እንደ ችግሩ አይነት ስሜትም ይቀያየራል፡፡ አሳዳጊ ራሱ የተሸከመው የልጅነት የአዕምሮ ቁስል ይኖረዋል፡፡ ወላጆች ከመጠን ባለፈ በሀይማኖት ውስጥ ጠልቆ በመቅረት የልጆችን ፍላጎት ከፈጣሪ አይበልጥም በማለት ረስቷል፡፡ እዚህ ቤተሰብ ውስጥ የልጅ አካላዊ እና ስሜታዊ ፍላጎቶች አይሟሉም ፡፡ በታመመ ቤተሰብ ውስጥ ቤተሰብ ለልጁ እንዴት ማሰብ፣ ፍላጎቶቹን ማስተናገድ፣ ከሰዎች ጋር መቀላቀል እንዳለበት ሚና ተሰጥቶታል፡፡ ልክ እንደ መድረክ ወይም ቴሌቪዥን ድራማ በዚሀ ቤተሰብ ውስጥ ሚና አለን፡፡ አንድ ድራማ ውስጥ የሚጫወት ተዋናይ የተሰጠውን ሚና በደንብ ካልተጫወተ ቦታውን ሊነጠቅ እንደሚችል ሁሉ በታመመ ቤተሰብ ውስጥም ልጆች ሚናቸውን ካልተወጡ ከባድ ችግር ይፈጠራል፡፡

ይህ መጽሐፍ ለየትኛውም አይነት የባህሪ አለመረጋጋት በራሱ መድሀኒት አይደለም። ችግሩን ማወቅ እና መረዳት ለችግሩ መድሀኒት እንዳለውና መድሀኒቱ የት እንደሚገኝ ነው የሚጠቁመው፡፡ ዛሬ ላይ የምናየው ችግር ከአሁን ይልቅ የትናንት የዞረ ድምር ውጤት እንደሆነ ማወቅ በራሱ ለመፍትሔው አንድ መንገድ ነው፡፡ ይህን መንገድ ነው መጽሐፉ የሚያሳየው፡፡ በዚህ መጽሐፍ ማሳየት የፈለግነው ሰዎች ለገጠማቸው ችግር መፍትሔውን የማይገኝበት ቦታ ላይ እንዳይፈልጉ ለማስቻል ነው፡፡ የሰዎች ትናንትና ከዛሬያቸው ጋር እንዲታረቅ (ትናንትናቸው ከዛሬያቸው ጋር እንዲጨባበጥ) ለማስቻል ነው ።

              ትዕግስት ዋልተንጉስ

ሁላችሁም ገዝታችሁ አንብቡት ታተርፋበታላቹ።

ሰውና ~ ፍልስፍናው

22 Jan, 14:42


#ደሃ_ስትሆን

ደሃ ስትሆን ማንም አይፈልግህም
ደሃ ስትሆን ማንም አያዳምጥህም
ደሃ ስትሆን ማንም አይወድህም
ከእናትህ እና ከፈጣሪ ውጪ
ድህነት ዝም እንድትል
የሚያደርግህ ነገር ነው
ድህነትን ለማሸነፍ ደሞ.....

ሰውና ~ ፍልስፍናው

13 Jan, 20:32


እንደዛሬው ዘመን “ሰዎች ስለኛ ምን ይላሉ?” የሚለው ጭንቀት ጎልቶ የታየበት ወቅት የለም🌿


ከሚከተሉት መካከል የትኛውን ትመርጣለህ? በዓለም ላይ አንደኛ ጎበዝ ሆነህ እንደ አንደኛ ደደብ መታየት ወይስ የመጨረሻ ደደብ ሆነህ እንደ አንደኛ ጎበዝ መታየት?

ዋረን ቡፌት በሌላ አገላለፅ እንዲህ ያስቀምጠዋል። “ዓለም ሁሉ ማፍቀር የማይችል እያለህ ጎበዝ - አፍቃሪ መሆን ይሻልሃል ወይስ አንተ ፍቅር የማይገባህ ሰው ሆነህ - እያለ ዓለም በሙሉ ጎበዝ አፍቃሪ ቢልህ?” ይህንን በመመርመር ውስጥ ቡፌት ለጥሩ ሕይወት አንጓ ከሆኑ ነገሮች መካከል የሆነውን አንድ ነጥብ ያነሳል፡፡ ይህም በውስጥ ግምገማ (inner scorecard) እና በውጪ ግምገማ (outer scorecard) መካከል ያለው ልዩነት ነው፡፡

ላንተ ወሳኙ የትኛው ነው? “አንተ ራስህን እንዴት ነው የምታየው” የሚለው ነው። ወይስ “ሌሎች ሰዎች አንተን እንዴት ነው። የሚያዩህ” የሚለው?.. ትኩረትህ አንተ በራስህ ምን እንደምታደርግ በማስብ ፈንታ “ዓለም ስለኔ ምን ይላል” በሚለው ላይ ከሆነ የውጪ ግምገማ(outer scorecard) አፍቃሪ መሆንህ ይታወቃል፡፡ ይህም ጥሩ ሕይወትን የማበላሻ አንዱ መንገድ ነው፡፡

የሌሎች ሰዎች አስተያየት ያለው ጥቅም አንተ “አለው” ብለህ ከምታስበው በታች የወረደ ነው። ይህ በድንጋይ ዘመን የቀረ ነገር ነው፡፡ ሰዎች አንተን በአድናቆት ሰማይ ቢያስነኩህ ወይም በትችት ከትቢያ ቢደባልቁህ ይህ በሕይወትህ ላይ የሚኖረው እውነተኛ ተፅዕኖ አንተ ለራስህ ከሚሰማህ ኩራትና ሀፍረት አንፃር በጣም ዝቅተኛ ነው፡፡

ስለዚህ ራስህን ነፃ አውጣ፡፡ ይህንን ማድረግ ያለብህ ደግሞ ስለ ሶስት ምክንያቶች ነው፡፡ አንደኛ ይህ በስሜት የመዘፈቅ ሕይወት በአግባቡ እየመራህ የምትቀበለው አይሆንም፡፡ ወደድክም ጠላህም በጊዜ ሂደት ክብርና ዝናህን በአግባቡ መቆጣጠር አትችልም፡፡ ጂያኒ ኢጅኔሊን እንዲህ ይላል፡- “እያረጀህ ስትሄድ የሚገባህንና ትክክለኛውን ክብር (reputation) ታገኛለህ፡፡ ሰዎችን ለጊዜው ልታታልል ትችላለህ፤ በሕይወት ዘመን ሁሉ እንደሸወድክ መኖር ግን አትችልም፡፡”

ሁለተኛ በክብርና በዝና (prestige and reputation) ላይ ትኩረት ማድረግ (በትክክል ደስተኛ የሚያደርገን ነገር ምንድን ነው?› - የሚለውን አረዳዳችንን ይረብሻል፡፡ ሶስተኛ ያስጨንቀናል፡፡ ስለሆነም ይህ ለጥሩ ሕይወት ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው ነገር ነው፡፡

- እንደዛሬው ዘመን “ሰዎች ስለኛ ምን ይላሉ?” የሚለው ጭንቀት ጎልቶ የታየበት ወቅት የለም፡፡ ዴቪድ ብሩክስ እንዲህ ይላል  “ማህበራዊ የመገናኛ ብዙሃን ሰዎችን ወደ ትንንሽ የብራንድ አስተዳዳሪነት ቀይሯቸዋል። ሰዎች ዛሬ ፌስ ቡክን፣ ቲውተርን፣ አጭር መልዕክትን እና ኢንስታግራምን እየተጠቀሙ የተጋነነ ውጫዊ ማንነትን ለመፍጠር ሲታትሩ ይውላሉ፡፡” ብሩክ
  በፌስቡክ ላይ የምናገኛቸው የመጋራት (share) የመውደድ (like) እና ሌሎችም ግብረ መልስ መስጫዎች ሰዎች ለሰዎች ያላቸውን አረዳድ እንዲያንፀባርቁ የተቀረፁ ናቸው፡፡ በዚህ መንገድ ለሰዎች የምንሰጣቸው ግብረ መልሶች ደግሞ ፌስ ቡክ ላይ ባየነው መጠን እንጂ እውነተኛ ማንነታቸውን አውቀን የማይሆንበት እድል ሰፊ ነው፡፡ አንድ ጊዜ በዚህ መረብ ከተጠለፍክ ጥሰህ ለመውጣትና ጥሩ ሕይወትን ለመምራት ቀላል አይሆንልህም፡፡

#ትምህርት፡- ጭብጡ ምንም ይሁን ምን ሰዎች ስላንተ ሊፅፉና ሊያወሩ ይችላሉ። ከኋላህ እየተከታተሉ የሚያንሾካሹኩ ሰዎችም አይጠፉም። በውዳሴ ሊያሞካሹህ ወይም በትችት ሊኮንኑህ ይችላሉ። አንተ ይህንን መቆጣጠር አትችልም። ጥሩው ነገር ደግሞ መቆጣጠርም የሌለብህ መሆኑ ነው፡፡ ፖለቲከኛ ወይም ዝነኛ ሰው ካልሆንክ በስተቀር ገቢህ በማስታወቂያ ላይ የተመሰረተ አይሆንም፡፡ እንደዚህ ከሆነ ደግሞ ስለዝናና ክብር (reputation) አትጨነቅ፡ ከመወደድና ከመውደድ ውጣ። ራስህን ጎግል ላይ አትፈልግ። ከዚያ ይልቅ የሆነ ነገር ሥራ።

ቡፌት እንዲህ ይላል- “እኔ ደስ የሚለኝን ነገር ግን ሌሎች ሰዎች የማይወዱትን ነገር ባደርግ ደስተኛ ነኝ፡፡ ነገር ግን እኔ የሰራሁትን ነገር ሌሎች ሰዎች ቢያደንቁልኝም፣ እኔ ግን የማልረካበት ከሆነ ደስተኛ አልሆንም።” ይህ የውስጥ ግምገማ (inner scorecard) ትክክለኛ አገላለፅ ነው። ስለዚህ በዚህ ላይ አተኩር። የውጪ አድናቆቶችንና ወቀሳዎችን ዝቅ ባለ ስሜት እያችው።

✍️ሮልፍ ዶብሊ

ሰውና ~ ፍልስፍናው

13 Jan, 20:18


ሰውና ~ ፍልስፍናው pinned «ኤለን መስክ እንዲህ ይላል፦ “ከቀድሞዬ ፍቅረኛዬ አምበር ሄርድ ጋር በተለያየንበት ጊዜ ላደረኩላት ነገር ሁሉ ሒሳብ ጠየቅኳት እና ሁሉንም ነገር ሙሉ በሙሉ ከፍላለች:: በሴቶች ላይ በጣም ስስታመ ነኝ 💸:: አምበር ሄርድ የእኔ ገንዘብ እስከሆነ ድረስ በግዴለሽነት ገንዘብ ማውጣት ትወድ ነበር። በዚህም ለብዙ የበጎ አድራጎት ስራ የሚውል ገንዘብ እያለችኝ መቀበል ታዘወትር ነበር። ትዊተርን የገዛሁት ለፖለቲካዊ…»

ሰውና ~ ፍልስፍናው

13 Jan, 20:18


ኤለን መስክ እንዲህ ይላል፦

“ከቀድሞዬ ፍቅረኛዬ አምበር ሄርድ ጋር በተለያየንበት ጊዜ ላደረኩላት ነገር ሁሉ ሒሳብ ጠየቅኳት እና ሁሉንም ነገር ሙሉ በሙሉ ከፍላለች:: በሴቶች ላይ በጣም ስስታመ ነኝ 💸::

አምበር ሄርድ የእኔ ገንዘብ እስከሆነ ድረስ በግዴለሽነት ገንዘብ ማውጣት ትወድ ነበር። በዚህም ለብዙ የበጎ አድራጎት ስራ የሚውል ገንዘብ እያለችኝ መቀበል ታዘወትር ነበር።

ትዊተርን የገዛሁት ለፖለቲካዊ ወይም ለንግድ ዓላማ ሳይሆን ለአምበር ነው። እንደ ቫለንታይን ቀን ስጦታ ልሰጣት ፈልጌ ነበር። ነገር ግን ከቫላንታይን አንድ ቀን በፊት በትዊተር ላይ አዲስ የወንድ ጓደኛ ስታገኝ ከእኔ ጋር ተለያየች።

ከእኔ ጋር ከተለያየች በኋላ ከትዊተር አገድኳትና ስሙን ወደ
X ቀየርኩት። ነገር ግን አዲሱ ፍቅረኛዋን በቴስላ ድርጅት ውስጥ ቀጠረችው። እና ከጥቂት ቆይታ በኋላ እኔ  አለቃው ላይ እንዲህ ማድረግ ስላልፈለገ ተለያት።

ከዚያም በግንኙነታችን ወቅት ለምታጠፋው ለእያንዳንዱ ሳንቲም ደረሰኝ ሰጠኋት። እና ሙሉውን ገንዘብ መልሳ ከፈለችኝ። ምክንያቱም ግንኙነታችንን ከመጀመራችን በፊት አብረን ካልሆንን ትከፍለኛለች የሚል ሰነድ እንድትፈርም አድርጊያለሁ። በሴቶች ጋር በጣም ንፉግ ነኝ እና ለዚህም ይመስለኛል እስካሁን ያላገባሁት”
✌🏼😌

ሰውና ~ ፍልስፍናው

04 Dec, 19:16


ክፍል ሁለት 2

"ምን? ማለት? እንዴት ሊሆን ይችላል? ለምን? የሚሉ ቃላት ከአፌ በድንጋጤና በብስጭት ይወጡ ነበር። ምንም ሳልላት ወዴት እንደምሄድ ሳላውቅ እየሮጥኩ ወጣሁ። ጓደኛዬን በጣም ነበር የምወዳት። እሷ ለኔ ከእህትም በላይ ነበረች:: ያለምንም ምክንያት እንዲህ ልታደርግብኝ አትችልም። ማሰብ ያቆምኩኝ ያክል ተሰማኝ። እሺ ምንድነው የማደርገው? ያለኝ አማራጭ ደግሜ እውነቱን መንገር ነው። "

" ' እግዚአብሔር መልካም ነው። እኛ የምንችለውን ሁሉ እናደርጋለን እንፀልያለን ደግሞም ዳኑን እኛ እራሳችን እናናግረዋለን። አሁን ፈተና ስለደረሰ ራስሽን አረጋግተሽ ለማጥናት ሞክሪ።' ብለው እኔን ማረጋጋቱ ተያይዘውታል አብረውኝ የሚያገለግሉ ጓደኞቼ። እኔ ግን ማረጋጋትም ቀስ ብሎ ማሰብም አልቻልኩኝም።  ዳኒ እኔን አለማመኑ ቢያበሳጨኝም በተደረገው ክፉ ስራ  ማዘኑን ሳስብ ያሳዝነኛል። እሱም እውነት አለው። ስለዚህ የቻልኩትን ማድረግ አለብኝ ብዬ ወሰንኩኝ። የመጨረሻ ምርጫዬ ጓደኛዬ ኤልሳ ናት። ያኔ ሆስፒታል ተኝቼ 'ጥፋቱ የኔ ነው' ያለችኝ ምክንያት በመጠየቅ ሰበብ እሷን አግኝቼ ለዳኒ የተደረገው ሁሉ እንድትነግረውና እኔ ምንም ነገር እንዳላደረኩኝ እንድታስረዳው ልጥይቃት ስልክ ደወልኩላት። እያለቀሰች እናገረችኝ። እኔ ግራ የገባኝና ያናደደኝ የሷ ማልቀስ ነው።የምንገናኝበትንና ሰዓት ወስነን ስልኩ ተዘጋ!"

"ከእሷ ቀድሜ ስለነበር የተገኘሁት እሷ ስትመጣ ሳያት መሆን የሌለብኝ ስሜት ተሰማኝ...ጥላቻ...። ' ማርቲ ማድረግ የሌለብኝን ነገር አድርጌያለሁ። ይቅር በይኝ!' ብላ ንግግሯን ስትጀምር በቅድሚያ ትክክለኛውን ነገር ንገሪኝ ቀጥሎም እንዴት ልትረጂኝ እንደምትችዪ አሳውቂኝ። ብዬ ተቆጣዋት! ኤልሳም እሷ እክክለኛውን ነገር እንደምትነግረው ቃል ገባችልኝ። እኔም ድጋሚ ልታገኘኝ ከፈለገች ይህን ካደረገች በኋላ እንደሆነ ነግሬያት ተለያየን።"

"እኔ ምንም ነገር ውስጤ አልከበደብኝም። እኔ ጋ እውነት አለ። ጥፋት አላጠፋሁም። ቢሆንም ግን ዳኒ እውነቱን ካወቀ በኋላ ብንለያይም አይጨንቀኝም።" ትላለች ማርታ። በዚህ ሰዓት በራስ መተማመንም የዳኒ ናፍቆትም በንግግሯ ውስጥ ይነበባል።

"ከሁለት ቀናት በኋላ የእጅ ስልኬ ጮኸ" ትለናለች ማርታ....እስቲ እንከታተላት

"ሄለው ማን ልበል? ስል 'ማርቲዬ ደህና ነሽ? ሔለን(የተቀየረ ስም) ነኝ' ሔለን አብራኝ የተማሪዎች ህብረት የምትመራ መልካም እህት ናት። 'ዛሬ ዳኒን አግኝተን አውርተን ነበር ሀሉን ነገር በስርዓት ተነጋግረናል። ለዕረፍት ቤተሰብ ጋ ስለሄደ ከሁለት ቀን በኋላ ተመልሶ እንደሚመጣና እንደሚያገኝሽ ተስማምተናል። ስለዚህ ጠብቂው። ሁሉም ነገር ተስተካክሏል እሺ ማርቲ አታስቢ። በቃ እንገናኛለን' ብላኝ ስልክ ዘጋን። የሆነ ደስታ ተሰማኝ ትላንት የሆነውን ነገር ረሳሁት።ዳኒ መጥቶ እውነትም እስከምንነጋገርና ወደ ቀድሞ ፍቅራችን እንደምንመለስ ናፍቄያለሁ።"

"ቀኑ አልፎ በሦስተኛው ቀን በአካል ተገናኘን። ውስጤን ናፍቆት ንዴት ሃዘን ይሰማኛል።ምክንያቱ ብዙ ነው። የመጀመሪያ ጥያቄዬ የነበረው የሱን ደህንነትና ለምን ስልኬ እንዳላነሳ ነበር የጠየኩት። ዳኒም ' ማርቲ ሁሉንም ነገር ደርሼበታለሁ ኤልሳም ነግራኛለች። አንቺን አለማመኔ አሳፍሮኝ ነው ስልክ ያላነሳሁት። አሁን ምንም ነገር ልታስረጂን አልፈልግም ሁሉን አውቄያለሁ። ምንም ወሬ ሳላበዛ ይቅርታ ብቻ አድርጊልኝና ፍቅራችንን እንቀጥል።' ሲለኝ ምንም ማውራት አልፈለኩም ምክንያቱም ራሱ ጥፋቱን አምኗል። ኤልሳንም ደውዬ ይቅር ብዬሻለሁ አልኳት። "

"ከብዙ ቀናት በኋላ ዳኒ 'እራት ካልጋበዝኩሽ' አለኝ። እኔም ደስ አለኝ። እሺ አልኩት። ነገር ግን የእራቱ ግብዣ ጓደኛው በተከራየው ቤት ውስጥ እንደሆነ ሲነግረኝ ውስጤ መሄድ እንደሌለብኝ ቢነግረኝም መጥፎ ነገር ሊፈጠር  አይችልም በሚል የእራት ግብዣውን 12:00 ለማድረግ ተስማማን።ነገር ግን ማንም ሰው አብሮሽ እንዳይማጣ ሲለኝ ተጠራጥሬ ነበር።"

12:00 ላይ ጓደኛው ቤት ጋ ስደርስ ወጥቶ ወደቤት አስገባኝ። ቤቱ በሚያምር ሁኔታ አድምቆታል። ሰላም ተባብለን አንድ ወንበር ነበረች እሷ ላይ ልቀመጥ ስል 'በፍፁም አይሆንም እዚ ጋ ነው መቀመጥ ያለብሽ' ብሎ አልጋው ላይ አስቀመጠኝ። እሱም ተቀመጠ። የተዘጋጀውንም እራብ በላን። ከምሽቱ 1:00 ላይ እጄን መንካትና ሰውነቴ ማሸት ሲጀምር ብድግ ብዬ ተንሳሁ። ምን እያደረክ ነው እዚ'ኮ ብቻችንን ነን። ጌታን መበደል የለብንም በቃ እራት በላን አይደል እንሂድ ስለው እጄን ስቦ አስቀመጠኝና 'የምነግርሽ ነገር አለ' አለኝ። እሺ ምንድነው ዳኒ የምትነግረን? '  ትወጂኛለሽ' ብሎ ሲጠይቀኝ ተናደድኩኝ። 'በእርግጥ ድንግል ነሽ? እኔ እስካሁን ማመን አልቻልኩኝም። እዛ እላጋ ላይ አብሮሽ የተቀመጠው ወንድምሽ ነው ብዬ ለማመን እስካሁን ከብዶኛል። ስለዚህ #ድንግልናሽን_ካልሰጠሽኝ_እጣላሻለው ደግመንም አብረን አንሆንም። አንቺ በእርግጥ ድንግል ከሆንሽ ይኸው ዛሬ አይቼ ልመን' ሲለኝ ፈራሁኝ። ሁለት ፍርሃት። አንደኛ ጌታን ልበድል መሆኑ ሁለተኛ ዳኒን ላጣው በመሆኔ። ግራ ገባኝ። ትሰማለህ ዳኒ? በጣም እወድሃለሁ አፈቅርሃለሁ ታምኜልሃለሁ። ድንግል ነኝ ስልህ ልታምነኝ ይገባ ነበር። ነገር ግን አላመንከኝም። እንድታምነኝ #ዝሙት ሰርቼ አላሳምንህም! ስለዚህ በጣም አዝናለሁ። ድንግልናዬን እንዳላጣ ብዬ ሳይሆን ዋጋ ከፍሎ ያዳነኝና የራሱ ማደሪያ ያደረገኝን ጌታ አልጋ ላይ ተኝቼ ዝሙት ሰርቼ አልበድለውም። ቅድስናዬ አስጠብቄ ጌታን አስደስቼው ክብረ ንፅህናዬ ጠብቄ እስከትዳር እኖራለሁ። ለአንተ ይቅርታ አድርጌልሃለሁ። ከዚህ በኋላ ግን እኔና አንተ ማቼውም ፍቅረኛሞች መሆን አንችልም። ብዬው ልወጣ ስል እጄን ያዘኝና አልጋው ላይ ጣለኝ። እፍን አድርጎ ያዘኝ። ነገር ግን እንዴትም ብዬ ያለ የሌለ ኃይሌን ተጠቅሜ እጁን ንክስ አድርጌው በአንድ እግር ጫማ ከዛ ቤት እየሮጥኩኝ ወጣሁ። ጌታ ታደገኝ።" በማለት እንባና ሲቃ በተሞላ መልኩ ታሪኳን አጫወተችኝ። እንዲህ ያስለቀሰኝ በእንደዚህ አይነት ህይወት ያለፈች እህቴ ትዝ ብላኝ ነው። የሷ ታሪክ ሌላ ጊዜ እነግርሃለሁ" ብላ ሌላ ታሪክ ልትነግረኝ ቃል ገብታልኝ ታሪኳን ቀጠለች።

በመጨረሻም ትለናለች ውድ እህታችን "  እሱም ሌላ ሱስ ውስጥ ገብቶ ከጓደኛዬ ኤልሳ ጋር አብረው ጓደኝነት ጀመረው ነበር እኔም በሰላም ተመረኩኝ። ከምርቃቴ ሦስት አመት በኋላ በጣም የምወደውና የሚወደኝ ውድ ባል አገባሁኝ። #ድንግልናዬን_ለባሌ ሰጠሁት ቆንጆም ልጅ ወለድን። የዳንኤል  ታሪክ ስሰማ ከኤልሳ ጋር አብረው እንዳልቀ ጠሉና ሌላ ሴት እንዳገባ ነው"

" ስለዚህ #ድንግል_ለባል_እንጂ_ለጓደኛ_አይሰጥም" በማለት ማርቲ ታሪኳን በዚህ አጠናቀቀች። እኛም እሷ ከተነገርችው ንግግር አንዱን ወስደን የታሪኩ መቋጫ እናድርግ......

💢 #ድንግልና_ለባል_እንጂ_ለጓደኛ_አይሰጥም! 💢

💍 @Biblicalmarriage 🌷

ሰውና ~ ፍልስፍናው

02 Dec, 07:19


🌿#ድንግልናሽን_ካልሰጠሽኝ_እጣላሻለሁ

አንድ ማርታ(የተቀየረ ስም) የምትባል ልጅ ነበረች። እድሜዋ 20 ሲሆን 2ኛ አመት የምህንድስና ተማሪና የተማሪዎች ህብረት መሪ ነች።ዳንኤል(የተቀየረ ስም) ከሚባል ልጅ ጋር ከተዋወቀች 1 ዓመት ከ 2 ወራት አልፏል! በነዚህ ጊዜያት ከዚህ በፊት አይታው የማታውቀው እንክብካቤ ያሳያታል እሷም በጣም ትወደዋለች! ታምነዋለች። ሁልጊዜ መንፈሳዊ ነገር ያስተምራታል። ይህ ልጅ ለእሷ የሚያስብና የሚሳሳ ሰው ነው። ያስጠናታል። እሷም በነዚህ ጊዜያት ባየችው ፍቅርና እንክብካቤ ተማርካ ሙሉ ልቧን ሰጥታዋለች!ከባለታሪካችን ጋር ቆይታ እናድርግ...."ይህማ የወደፊት ባሌ ነው ብዬ አስብ ነበር" ትላለች ባለታሪኳ! "ነገር ግን ይህንን ፍቅርና እንክብካቤ ማጣጣም በጀመርኩበት ወቅት ዳኒ እጅጉን ነጭናጫና ብስጩ ሆነ። ቃሎቹም እኔን እየከበዱኝ ይመጡ ጀመር። እኔ ግን ከሱ ውጭ ማሰብ አልቻልኩኝም! ትምህርቴንም በተወሰነ መልኩ ችላ አልኩኝ። ዳኒ ምን ሆኗል ብዬ ማሰብ ሆነ ስራዬ። ዳኒ ጓደኞቹም ላይ ተቀይሯል!" እያለች ታሪኳን ትቀጥላለች።በዚህ መሃል ነበር እንባዋል መቆጣጠር አቅቷት አይኗ በእምባ ተሞላ። እኔም ታሪኩን እንድትጨርስ አደረኳት ታሪኩም እንዲህ ይቀጥላል..." ዳኒ 'ዛሬ በጣም እፈልግሻለሁ' ብሎ Text አደረገልኝ። እኔም ላለፈው ሳምንት ድምፁንም ስላልሰማሁ በአካልም ስላላገኘሁት ከግቢ ውጭ ወደ ቀጠረኝ ካፌ በፍጥነት ሄድኩኝ። ዳኒም ሰላም ካለኝ ካለኝ በኋላ ቀጥሎ 'አንቺ ግን ትወጂኛለሽ?' የሚል ጥያቄ ነበር የጠየቀኝ።እኔም ውስጤን ስለማውቀው ለእርሱ ያለኝን ከፍተኛ ፍቅር እንባ እየተናነቀኝ ነገርኩት። እርሱም 'ዛሬ ግቢ አንገባም ውጭ ነው የምናድረው!' ሲለኝ ይህ እንደማይሆን አጥብቄ ብነግረውም ይባስ ይጮህብኝ ጀመር እኔም በፍቅር ለምን ውጭ እንደማናድር ደጋግሜ ብነግረውም ጭራሽ ተቆጥቶኝ ጥሎኝ ሄደ። እንደዛ ይሳሳልኝ የነበረው ዳኒ ምን ሆኗል ብሎ ማሰብ ሆነ ስራዬ።" በማለት ምሬትም ንዴትም ጭንቀትም በሞላበት ስሜት ሃሳቧን ቀጠለች።"ጓደኞቼም 'ዳኒ የሆነ ነገር ሳይሆን አይቀርም!' ሲሉኝ ምን ሁኔታ ላይ እንዳለ የማወቅ ጉጉቴ የበለጥ ጨመረ። እንደወትሮዬም ከዚህ በፊት አብረን የምንቀመጥበትና የምንገናኝበት ቦታ እሱን ፍለጋ ስሄድ ያየሁትን ነገር ማመን አቃተኝ።ደነገጥኩኝ! ከዛ በኋላ የሆንኩትን ነገር አላውቅም። ከ30 ደቂቃ ቆይታ በኋላ ስነቃ ራሴን ያገኘሁት ሆስፒታል አልጋ ላይ ነበር። 'ማርቲዬ አይዞሽ እኔን..ምክንያቱ እኔ ነኝ' የሚል ድምፅ ሰማሁኝ። ይህን ድምፅ በደንብ አውቀዋለሁኝ። የራሴ የልብ ጓደኛዬ የሆነችው ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ጀምሮ አብረን የተማርን እንደ እህቴ የማያት ጓደኛዬ ነበረች። ይህንን ድምፅ ስሰማ ይባስ ተበሳጨሁ ተናደድኩኝ ተለዋወጥኩኝ። 'አንቺ ነሻ የኔ የምለውን ዳኒን የቀየርሽብኝ። እያመንኩሽ ጉድ የሰራሽኝ ከሃዲ' ብዬ መጮህ ጀመርኩኝ። ዳኒን ፍለጋ ስሄድ እዛ ቦታ ያየሁት ሲሳሳሙ ነበር።ከዚህ በኋላ አይንሽን ማየት አልፈልግም ብዬ ከዛ ሆስፒታል ብቻዬን ወደ ግቢ ሄድኩኝ። አሁንም ግን ዳኒን ይፈልጋል ልቤ። አሁን ባየሁትና እሱ እየሆነ ያለው ነገር ትላንትን ሊሸፍንብኝ አልቻለም። ድንገት የእጅ ስልኬ ላይ Text ገባ። ክፍቼ ሳነበው 'እባክሽ ሚስጥር ለንገርሽ ስለምፈልግ ማታ 12 ሰዓት ላይ ግቢ ፊት ለፊት ያለው ካፌ እንገናኝ' ይላል። እቺ ልጅ ጉድ የሰራችኝ ጓደኛዬ ጓደኛ ናት። ይህንንማ ማወቅ አለብኝ ብላ ቀጠለች። ሰዓቱን መጠበቅ ስላልቻልኩኝ እባክሽ ከቻልሽ አሁን እንገናኝ ብዬ ላኩላት። 'የኔ እህት አሁን Class ሳላለኝ 10 ሰዓት ላይ እንገናኝ'ብላ መለሰችልኝ። 10 ስዓት ላይ ይችን ልጅ አገኘዋት። የምትነግረኝን ለማንም እንዳትናገር ቃል አስገብታኝ ሁኔታውን ትነግረኝ ጀመር። ' ያንቺና የዳኒ ፍቅር የግቢ ተማሪ ሁሉ የሚያውቀውና የሚቀናበት እንደሆነ አውቃለሁ። ኤልሳ ዳኒን ስለምትፈልገው ማርታ ከሌላ ወንድ ጋር ሆቴል ገብታ አድራለች ከዛም ድንግል ነኝ ብላ የምትዋሽህም ውሸቷን ነው ብላ ስለነገርችው ነው ዳኒ አንቺ ላይ የተቀየረው።' ብላኝ 'ከዚህ በላይ መቆየት አልችልም ብላኝ ሌላ የአዕምሮ ስራ ሰጥታኝ ትታኝ ሄደች።ሰማይ ምድሩ ዞረብኝ። እኔ'ኮ አይደለም ከሌላ ወንድ ጋር ልተኛ ይቅርና ሌላ ወንድ ሊያቅፈኝ ሲሞክር እንኳን የምጣላ ሴት ነኝ። ሳላገባ አይደለም ድምግልናዬ ከንፈሬን እንኳን አላስነካም ብዬ ለራሴም ለእናቴም ጋር ቃል ገብቻለሁ።" በትካዜ ጭልጥ ብላ ሄደች ንግግሯም ለተወሰኑ ሰከንዶች ተቋረጠ። "ዳኒ አያምነኝም ነበር ማለት ነው። እንዴት ከእኔ ሌላ  ሰው አመነ። ብለየው እንኳን እውነቱን ነግሬው መሆን አለበት ብዬ ስላመንኩኝ ደውዬለት ላገኘው  እንደምፈልግ ነግሬው በቀጠሮውም ሰዓት ወደምንገናኝበት ቦታ አመራው። እሱም ቀድሞኝ ተገኝቷል።ሰኣት አክባሪነቱን እወድለታለሁ።ነገር ግን ሳየው የተደበላለቀ ስሜት ተፈጠረብኝ። ንዴት ፍቅር ናፍቆት ጥላቻ...ብዙ ብዙ። ተጨባብጠን ተቀመጥን። ስለ እኔ ማንነት ከመጀመሪያው ጀምሮ ከነገርኩት በኋላ አስደንጋጭ ቃል ከአንደበቱ አወጣ። 'አሁንም ትዋሻለሽ እኔ'ኮ ከራሴ ይልቅ ነበር ያመንኩሽም የወደድኩሽም። አንቺ ግን አሁንም ድንግል ነኝ ስትዪ አታፍሪም? ውሸታም ነሽ' ብሎኝ ከደብተሩ ውስጥ አንድ ፎቶ አውጥቶ አሳየኝ። ደነገጥኩኝ...እኔ ነኝ ፎቶው ላይ ያለሁት። የሆነ ወንድ እኔን ሲስመኝ የሚያሳይ። ከሆነ ወንድ ጋር ተቀምጬ የሚያሳይ። ይህ ወንድ ደግሞ ግቢ ውስጥ እኔን የሚፈልገኝና ከዚህ በፊት ከዳኒ ጋር የተጣለ ልጅ ነው። አዕምሮዬ ማሰብ እንዲሁም ይህ መች እንደሆነ ሊያውቅ አቃተው። ዳኒም ጥሎኝ ሄደ።


እኔና ፎቶው ተፋጠጥ። እኔ ነኝ ልጁም እራሱ ነው። ነገር ግን ይህንን ነገር አላደረኩትም። ከዚህም ልጅ ጋር እንዲህ ባለ አስነዋሪ ድርጊት የትም አልተገናኘንም። ዞረብኝ። መሳቅ ጀመርኩኝ። ጥንቃቄ በተሞላው መልኩ በሚያሳምን ሁኔታ በPhotoshop የተሰራ ፎቶ ነው! አልጋው ላይ ተቀምጫለሁ። እዛ አልጋ ላይ የተቀመጠው ግን እኔን ሊጠይቀኝ የ መጣው ወንድሜ ነበር። እንዴት እንዱህ እንደተደረገ ለማወቅ የሴት ጓደኛዬ ጋር ደውዬ ማግኘት እንዳለብኝ አመንኩ። ልጅቷንም አገኘዋት። እንዴት እንደሆነም በዘርዝር ነገረችኝ። ዳኒዬ አሳዘነኝ። ፎቶው ተሰርቆ ተወስዶ ነው እንዲህ የተሰራው። ይህንን ተንኮል ያሰራው ከምወዳት ጓደኛዬ ጋር ተመሳጥሮ ያ ይፈልገኝ የነበረው ልጅ ነው። ይህ ቀላል ስለሆነ ለዳኒብትክክለኛውን ፎቶ አሳይቼው አሳምነዋለሁ! ብዬ አሰብኩኝ። በፍጥነት ወደቤት ሄጄ ስፈልገው ፎቶው የለም። ኤልሳ ጋር ደውዬ እባክሽ እኔ ከአንቺ ምንም አልፈልግም ተንኮል የተሰራበትን ትክክለኛውን  ፎቶዬ ስጪኝ አልኳት። ይቅርታ አድርጊልኝ ማርቲ ፎቶውን ልጁ ቀዳዶ ጥሎታል አለችኝ።"

ታሪኩ ይቀጥላል......

እራሶን በማርታ ቦታ ያድርጉና በቀጣይ ምን ያደርጋሉ? መልስዎትን  ይላኩልን!

ሰውና ~ ፍልስፍናው

13 Oct, 06:21


🌿Good Morning እጅግ የምወዳችሁና መልካምን ነገር የምመኝላችሁ የሃገሬ ሰዎች!

እንኳን በሰላም ለዛሬዋ ቀን አበቃችሁ!

እስቲ የዛሬዋን ቀን አርፋችሁ ጀምሯት!

ቀንን አርፎ መጀመር ማለት እረፍትና እርካታ ፍለጋ ምንም ነገር ለማድረግ ከመታገል መረጋጋት ማለት ነው፡፡

ውስጣችሁ እርፍ እንዲል ማንም ሰው ሊቀባለችሁ አይገባም፣ ማንንም ሰው ማስደሰትም የለባችሁም፡፡ ስላረፋችሁ ግን ከሰዎች ጋር ያላችሁን ግንኙነት ሚዛነዊ አድርጋችሁ የመያዝ መረጋጋት ታገኛላችሁ፡፡

ውስጣችሁ እርፍ እንዲል የትኛውም ስራ ስኬታማ መሆን የለበትም፡፡ ውስጣችሁን አሳርፋችሁና አረጋግታችሁ የምትሰሩት ስራ ራሱ መነሻው ስኬታማነት መሆኑን አስታውሱ፡፡

ከእነዚህ ሁለት ምሳሌዎች ተነስቼ ከጀመርላችሁ ሌሎቹን እናንተው አስቧቸው፡፡

ምንም ነገር ስታደርጉ፣ የውስጣችሁን እረፍት ነገሩ እስከሚሳካ አታዘግዩት፡፡

መጀመሪያውኑ ፈጣሪ በሰጣችሁ ማንነት፣ ባላችሁ የሕይወት ራእይና አጠገባችሁ ካለምንም ቅድ-ሁኔታ በሚወዷችሁ ሰዎች እርፍ በሉ፡፡

ከዚህ አይነቱ ሁኔታ ስትነሱና ስትጀምሩ ሰዎችም ሆኑ ሁኔታዎች የእናንተን ስሜት እንደፈለጉ አያደርጉትም፡፡



Dreyob

ሰውና ~ ፍልስፍናው

08 Oct, 10:13


🌿#እንዳታስቡ_ማሰብ_የተከለከለ_ነው!!!

ታላቅ መሆን የሚቻለው ታላላቅ ሀሳቦችን በቋሚነት በማሰብ ነው!

በውስጣዊ ስብእናው ታላቅ እስኪሆን ድረስ ማንም ሰው በውጫዊ ስብእናው ታላቅ መሆን አይችልም፡፡ እስኪያስብ ድረስ ደግሞ ማንም ሰው በውስጣዊ ስብእናው ታላቅ መሆን አይችልም፡፡ የትኛውም ዓይነት ትምህርት፣ ንባብ ወይም ጥናት ሳታስቡ ታላቅ ሊያደርጋችሁ አይችልም፤
ሀሳብ ግን በጥቂት ቀናት ታላቅ ያደርጋችኋል!

በጣም በርካታ ሰዎች ማሰብን ሳይለማመዱ፣ ማሰብ የተከለከለ ነው የተባሉ ይመስል ብዙ መጽሐፍን በማንበብ ብቻ ታላቅ ነገርን ለማድረግ ሲሞክሩ ይስተዋላል፡፡ እንደዚህ አይነቶቹ ሰዎች አይሳካላቸውም፡፡ በምታነቡት ነገር ሳይሆን በምታነቡት ነገር ላይ በምታስቡት ሀሳብ ነው አእምሯችሁን የሚገነባው፡፡

ማሰብ ከየትኛውም አይነት ስራ ከባዱና አድካሚው ነው፡፡ ስለዚህም ብዙ ሰዎች ከማሰብ መራቅን ይመርጣሉ፡፡ ብዙ ሰዎች የእረፍት ጊዜያቸውን በሙሉ የሚያሳልፉት ያለማቋረጥ ደስታን በማሳደድ፣ ማሰብን ለማምለጥ በሚደረግ ጥረት ብቻ ነው፡፡ ብቻቸውን ከሆኑ ላለማሰብ ወደ ጌም፣ ወይም እንደ አስቂኝ ትዕይንት ያላቸው ነገሮች ይጓዛሉ፡፡ ብዙ ሰዎች ብዙ ጊዜያቸውን የሚያሳልፉት ከሃሳብ በመሸሽ ነው፤ ለዛም ነው ባሉበት ቦታ ሆነው የሚቀሩት፡፡

ማሰብ እስካልጀመርን ድረስ በጭራሽ ወደ ፊት አንሄድም!

ማሰብ ስብእናን ይሰራል፡፡ ማሰብ እድገት ነው፡፡ ሳታስቡ ማደግ አትችሉም፡፡ ሳታስቡ ሀብታምም መሆን አትችሉም፡፡

ማንኛውም ሰው ሁለትና ሁለትን አባዝቶ አራትን አለማግኘት እንደማይችለው ሁሉ፣ ማንኛውም ሰው ለሀብት ሳይንሳዊ ህጎች እስከተገዛ ድረስ ሀብታም አለመሆን አይችልም፡፡

ከሀሳብ ውጪ ታላቅ ሊያደርጋችሁ የሚችል ነገር የለም! ከሀሳብም ውጪ ሀብታም ሊያደርጋችሁ የሚችል ነገር የለም!!

ሰውና ~ ፍልስፍናው

27 Sep, 10:01


🌻እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሳችሁ!🌻
በዓሉ የሰላም ፣ የደስታና የፍቅር እንዲሆንላችሁ እንመኛለን፡፡

ሰውና ~ ፍልስፍናው

13 Sep, 10:57


👉 🌻#አዲስ_አመት🌻

- አዲስ ተስፋ
- አዲስ ዕድል
- አዲስ ታሪክ
- አዲስ ቢዝነስ
- አዲስ አእምሮ
- አዲስ ፍቅር
- አዲስ ለውጥ

ይዞልን መጥቷልና እስቲ እንኳን ደህና መጣህ እንበለው በኮመንታችን
🌻

ሰውና ~ ፍልስፍናው

11 Sep, 13:24


🌼🌼 #2017_ያንተ_አመት_ነው 🌼🌼

👉 ምክንያቱም ቲቪ ላይ ተጥደህ አትውልም
👉 ሶሻል ሚዲያም ትቀንሳለለህ
👉 ንባብ ታበዛለህ
👉 አማራጭ ቢዝነስ ታያለህ
👉 ራስህን ታስተምራለህ
👉 የሚያሳድጉህ ጓደኞች ታፈራለህ
👉 በእምነት ትንቀሳቀሳለህ

= ስኬት ያንተ ይሆናል።

መልካም አዲስ አመት

ሰውና ~ ፍልስፍናው

28 Aug, 07:16


መደሰት እና ማስደሰት

ማንም ሰው ለእናንተ ደስተኛነት የሃላፊነት ሸክም እንደሌለው አምናችሁ ስትቀበሉ እና እናንተም ብትሆኑ ለማንም ሰው ደስተኛነት የሃላፊነት ሸክም እንደሌለባችሁ ሲገባችሁ፣ እናንተ ነጻ ሆናችሁ፣ ሰዎችንም ነጻ አድርጋችሁ ትኖራላችሁ፡፡

ሰዎች ደስ እንዲላቸው ማድረግ የምትችሉትን አድርጉ፡፡ ሁለት ነገሮችን ግን አትርሱ፡-

1. ምንም አደረጋችሁ ምንም የሰዎቹ ደስተኛነት በእነሱው እጅ እንደሆነ በመገንዘብ የምትችሉትን ካደረጋችሁ በኋላ ደስተኛነቱን ለእነሱ ተውላቸው፡፡ ደስተኛነቱን ለእነሱ መተው ማለት፣ ገና ለገና ተደስተውና አልተደሰቱ እንደሆነ በመጨነቅ ሁኔታቸውን እያያችሁ የበለጠ ለማስደሰት ከመታገል ራስን መጠበቅ ማለት ነው፡፡

2. ሰዎችን ለማስደሰት ማድረግ የምትችሉትና የምትሄዱት ርቀት ገደብ ሊኖረው እንደሚገባ በማወቅ የእናንተን ሕልውና የሚነካ ርቀት ድረስ ከመሄድ ተቆጠቡ፡፡ የእናንተን ሕልውና የሚነካ ርቀት ድረስ ከመሄድ መቆጠብ ማለት ሰዎችን ለማስደሰት በምታደርጉት ጥረት የስሜትና የስነ-ልቦና ቀውስ ውስጥ ከመግባት ራስን መጠበቅ ማለት ነው፡፡

ሰዎች እናንተን ለማስደሰት የሚችሉትን ቢያደርጉ መልካም ነው፡፡ ሁለት ነገሮችን ግን አትርሱ፡-

1. ሰዎች በሚያደርጉላችሁ መልካም ነገር ተደሰቱ፣ ሆኖም ሁል ጊዜ ያንን ያደርጉልኛል ብላችሁ ከመጠበቅና ያንን ስታጡ ከመጎዳት ራሳችሁን ጠብቁ፡፡ ይህ ማለት፣ በሰዎች ሁኔታ መደሰት የመፈለጋችሁ ትክክለኛነት እንደተጠበቀ ሆኖ፣ እንደሰዎቹ ተለዋዋጭ ሁኔታ የስሜት ውጣውረድ ውስጥ ከመግባት ራስን መጠበቅ ማለት ነው፡፡

2. ሰዎች ባደረጉላችሁ ነገር ደስተኛ ብትሆኑም፣ እነሱ ወደው ካደረጉት ነገር የተነሳ ግዴታ እየተሰማችሁ ለዚያ ምላሽ ለመስጠት የማታምኑበትን ሕይወት እንድትኖሩ የመገደድ ስሜት ውስጥ ከመግባት ተጠበቁ፡፡ ይህ ማለት፣ ሰዎች ለእናንተ ደስተኛነት የሚያደርጉትን ነገር እንደሸክም ከመቁጠር ራስን መጠበቅ ማለት ነው፡፡

መልካም ቀን!🌿
/Dreyob

ሰውና ~ ፍልስፍናው

19 Aug, 07:55


#ምስጢር_ልነግርህ_ነው 

አንብብና ተግብረው!

አንድ ነገር ላሳይህ ነው፤ ተከተለኝ. . .

1- የ'ኖኪያ/Nokia' የመጀመሪያ ምርት ምን ይመስልሃል?

👉  የሽንት ቤት ወረቀት ነበር

2- የ'ሳምሰንግ/SAMSUNG' የመጀመሪያ ምርትስ?

👉 ግሮሰሪ ነበር

3- 'ላምበርጊኒ/ Lamborghini' እጅግ ውድና ቅንጡ መኪና አምራች ነው፤ የመጀመሪያ ምርቱ ግን ምን ነበር?

👉 የእርሻ ትራክተር ነበር

4- 'አይኪያ/Ikea'ን ታውቀዋለህ፤ ሃብታምና ዝነኛ ድርጅት ነው፤ ግን በምን ምርት ጀመረ?

👉 በእስክርቢቶ ነበር የጀመረው

5- የ'ኤል ጂ/LG'ስ የመጀመሪያ ምርት ምን ነበር?

👉 የፊት ቅባት/cream ነበር

ይህ የሚነግርህ የመጀመሪያ ምርትህ መነሻ ከየትም ሊሆን እንደሚችል ነው፤ ዋናው መጀመርህ ነው። የመጀመሪያ ምርት ወይም አገልግሎት ውጤታማ ላይሆን ይችላል። የቢሊየነሩ ቢልጌትስ አጀማመርም በውጤታማ ምርት አልነበረም።

ይህንን ግን ማንም አልነገረንም! ለምን?

ሰውና ~ ፍልስፍናው

17 Aug, 09:53


#አምላክህ_ስለ_አንተ_ምን_ይላል?

1-ውብ ነህ!
2-የምትወደድ ነህ!
3-ተመርጠሀል!
4-ልዩ ነህ!
5-በአምሳሌ ተፈጥረሀል!
6-ጠንካራ ነህ!
7-ውድ ነህ!
8-ጠቃሚ ነህ!
9-ይቅር ተብለሀል!
10-ለዓላማ ተፈጥረሀል

👇🎀👇

👉 #ጠይቁ_ይመለስላችኋል 4ተኛ ዕትም
👉 #ሰይጣንን_አስርቡት 2ተኛ ዕትም
👉 #የነፍስ_ምግብ 2ተኛ ዕትም
👉 #ኦርቶጵያ 4ተኛ ዕትም
👉 #እስከማዕዜኑ 3ተኛ ዕትም
👉#የተሰቀለው_ንጉሥ (በአማርኛ)

ሰውና ~ ፍልስፍናው

14 Aug, 21:56


🌿ሲፈልጓችሁና ሳይፈልጓችሁ

ሰዎች ደግመውና ደጋግመው እንደሚፈልጓችሁ ከነገሯችሁ፣ በተቻላችሁ መጠን ለመስማት እድል ስጧቸውና ከዚያም ፍጎታችሁንና ውሳኔያችሁን ንገሯቸው፡፡ ይህ ተግባር፣ “ለሰዎች ተገቢውን ዋጋ መስጠት” ተብሎ ይጠራል፡፡

ሰዎች ደግመውና ደጋግመው እንደማይፈልጓችሁ ከነገሯችሁ፣ ዛሬ ነገ ሳትሉ ከሕይወታቸው ውጡላቸው፡፡ ይህ ተግባር፣ “የራስን ዋጋ ማወቅ” ተብሎ ይጠራል፡

ሰውና ~ ፍልስፍናው

12 Aug, 08:31


#ወዳጄ_ሆይ

💥ፍቅር ከእግዚአብሔር ነውና
👉ሁሉን ውደድ!
💥 በቃል የተሰበረ በመረቅ አይድንምና
👉 ለቃልህ ተጠንቀቅ!
💥 ለክረምት በጋ፣ ለሌሊት ቀን እንዳለው
👉 ላንተም ጊዜ አለህ! በርታ!
💥 ቀን የሚያመጣው ምን እንደሆነ አታውቅምና
👉 ነገ በሚሆነው አትመካ!
💥 ከትላንት ተማር፣ ዛሬን ኑር፣ ነገን ተስፋ አድርግ!
👉 እግዚአብሔር ከጎንህ አለ!

ሰውና ~ ፍልስፍናው

07 Aug, 14:09


አታድርጉት!

• ገንዘብን ለማግኘት ብላችሁ ጤንነታችሁን አትሰው!

• ሰዎችን ላለማጣት ብላችሁ ከራሳችሁ ጋር አትለያዩ!

• ስልጣንን ለመጨበጥ ብላችሁ ከሕብረተሰብ ጋር አትጣሉ!

• አጉል ልማዳችሁን ላለመልቀቅ ብላችሁ ከሕይወት መስመር አትውጡ!

• ላለመሸነፍ ብላችሁ ቤተሰባችሁን አታፈራርሱ!

ይቅርባችሁ!

ሰውና ~ ፍልስፍናው

27 May, 10:58


#ሳይኮሎጂ_እንዲህ_ይላል

አእምሯችን አደጋን የማወቅና የመለየት አቅም አለው።

ደመ ነፍስህ የሆነ የተሳሳተ ነገር እንዳለ ከነገረህ፣ ያንን ስሜት ችላ አትበለው።


ትስማሙበታላችሁ? ሀሳብ አስተያየቶቻቹሁን አካፍሉን።

ሰውና ~ ፍልስፍናው

22 May, 12:00


🌿#6ቱ_የቅናት_ምልክቶች

#አንድ
አንተን የማክበር ወይም ላንተ እገዛ የማሳየት ጊዜ ሲሆን ጊዜ የለንም ይላሉ።

#ሁለት
አንተን ወይም እንቅስቃሴህን ይኮርጃሉ

#ሶስት
የምታደርገውን ሁሉ ያያሉ ግን አንተ እንድታይ አይፈልጉም።

#አራት
ራሳቸውን እንደ ጓደኛ ወይም እንደ ቤተሰብ ይቆጥራሉ። ድርጊታቸው ግን ያን አያሳይም።

#አምስት
እነሱን የሚጠቅም ሲሆን ብቻ ይፈልጉሃል።

#ስድስት
ትልልቅ ስኬቶችህን እንደ ትንሽ ይቆጥራሉ።

ሰውና ~ ፍልስፍናው

16 May, 18:32


የምድር ውበት ሰው ነውየሰውም ውበት አስተሳሰቡ ነው።

ሰውና ~ ፍልስፍናው

05 May, 06:10


ክርስቶሰ ከሙታን ሁሉ ተለይቶ ተነስቷል። መልካም የትንሣኤ በዓል ይሁንላችሁ ። ለአገራችን ኢትዮጵያ ትንሳኤውን ያቅርብልን !!!

ሰውና ~ ፍልስፍናው

26 Apr, 00:52


🌿ሳይኮሎጂ_እንዲህ_ይላል፦

ሰዎች ሲወዱህ ብዙ አትደሰት።

እውነተኛው ጥያቄ "እስከ መቼ?" የሚለው ነው።


ስለ እውነተኛው ጥያቄ ምን ትላላችሁ እናንተስ?  እስከመቼ ያላችሁበትን ገጠመኝ አካፍሉን እስቲ ...

ሰውና ~ ፍልስፍናው

22 Apr, 05:53


🌿ህይወት ቀጥላለች እዚህ ሰአት ላይ ደርሳለች በእያንዳንዱ ሰከንድ መንቀሳቀስ ደሞ ወደ ሞታችን እየቀረብን ነው ።
እናም በሞታችን ስራችንን እንድናስቀጥል በእያንዳንዱ ሰከንድ ልክ መንቀሳቀስ አለብን ተማሪ ከሆንክ ጥናት ሰራተኛ ከሆንክ ስራህን ምክንያቱም ያንተ እረፍት ስራህ እንዲሆን ሁሌ መሞከር አለብህና ያለፈውን ስህተትህን መልሰህ ማስተካከል ትችላለህ ግን ያለፈህን ጊዜ መመለስ አትችል።


💫 መልካም ቀን ይሁንላችሁ።

ሰውና ~ ፍልስፍናው

21 Apr, 07:43


መልካም ዝልፈተ ሰንበት !🌿
መልካም ዝልፈተ ሰንበት !🌿
መልካም ዝልፈተ ሰንበት !🌿

ሰውና ~ ፍልስፍናው

21 Apr, 07:41


ሰውና ~ ፍልስፍናው pinned «ኃዘንተኛ ለመሆን ከፈለጋችሁ . . .  ሃዘንተኛ ሰው ሆናችሁ መኖር ከፈለጋችሁ ቀላሉ መንገድ ሁልጊዜ፣ በሁሉም ቦታና በሁሉም ሁኔታ፣ ሁሉንም ሰው ለማስደሰት ሲጦዙ መኖር ነው፡፡ ማንም ሰው እንዳያዝንባችሁ፣ ቅር እንዳይሰኝባችሁን ሁል ጊዜ ሁሉም ሰው በእናንተ ሃሳብም ሆነ ተግባር ደስተኛ እንዲሆን የምትፈልጉ ከሆነ የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ አደገኛ የስሜት ቀውስ ውስጥ መግባታችሁ አይቀርም፡፡ ጉዳዩ ግን…»