ካህሊል ጂብራን !
የጥበብ - መንገድ 📖 በእንግሊዝኛ እና አሠሪና ከተማ መጽሀፍ ያግኙ ነው። ይህ መንገድ የጥበብን ወንድምን ወንድሜን እና ወንድሜን ልጅን እንዲሁም የሴቶችን እንስሃሎችን የማስመልከት ያልነበር መጽሀፍያን በነቃነን ፍላጎቴን በማሳደግ ላይ ምክንያት እንዲያስተውሉ ውይይት ያግኙ። የአሮጌ ብክል እና ፕሮፌሰር ልዩ እና ተከታዮች በአዲሱ መጽሀፍ መተሳየታቸውን ተጨማሪ ይሆናል። እናም በእንግሊዝኛ በማንበብ መንገድ በተመሳሳይ አልባ እንዲለያይ ላኩል።
21 Nov, 05:11
ሙላ ናስሩዲን ፍቅር ያዘው።ጨርቅ የሚያስጥል ፍቅር።እናም በፍቅር ያሳበደችውን ሴት ለማግባት ወሰነ።ለእናቱ ነገራቸው። እናት ግን የወደድካት ሴት እምነት ስለሌላት ከሷ ጋር መጋባት አትችልም አሉት።
"ምን ይሻላል ሁለታችንም እኮ እንዋደዳለን" አለ ናስሩዲን።
"ከወደደችህ የምትላትን ትቀበላለች፤ስለ እምነት በደንብ አስረዳት፤አማኝ ትሆናለች" አሉ እናት።ሙላ በዚህ ተስማምቶ ወደ ፍቅረኛው ቤት ሄደ። ሰበካት ስለ ፈጣሪም ነገራት።ስለ እምነት አስረዳት።
፡
ከቀናት በኋላ ናስሩዲን እያለቃቀሰ እናቱ ወዳሉበት ማድቤት ገባ።ክንዳቸውን ተደግፎ እየየውን አስነካው
፡
"ምን ሆንክ ልጄ እቅዳችን አልሰራም?" እናት ጠየቁ።
"መስራት እንኳን ሰርቷል፤ ስለ እምነት ሰበኳት አመነችኝ"አለ።
ታዲያ ምን ተፈጠረ የምታለቅሰው?እናት ጠየቁ።
፡
አያ ሙላ እያለቃቀሰ ምን አለ …
"ልትመንን ነው መነኩሴ ልትሆን ነው
20 Nov, 16:25
20 Nov, 05:19
ሕልምን አጥብቀህ ያዝ፤ ምክንያቱም ሕልሞች ከሞቱ፡ ሕይወት መብረር የማትችል ክንፍ ያለው የተሰበረ ወፍ ናትና ።
©ላንግስተን ሂዩዝ
19 Nov, 15:05
🌸 ስለ ሃይማኖቶች መለያየት !
ሌላ ትልቅ ምርመራ አለ፡፡ ሰዎች ሁሉ በእግዚአብሔር ዘንድ ትክክል ናቸው፡፡ እርሱም አንድ ህዝብ ለሕይወት አንድ ህዝብ ለሞት አንድም ለምህረት አንድም ለኩነኔ አልፈጠረም፡፡ ይህም አድሎ በስራው ሁሉ ፃድቅ በሆነ በእግዚአብሔር ዘንድ እንደማይገኝ ልቦናችን ያስተምረናል፡፡ ሙሴ ግን አይሁድን ለብቻቸው እንዲያስተምራቸው ተላከ፡፡ ለሌሎች ሕዝቦች ፍርዱ አልተነገረም፡፡ እግዚአብሔር ስለምን ለአንድ ህዝብ ፍርድ ሲነግር ለሌላው አልነገረም፡፡ በዚህ ጊዜ ክርስቲያኖች የእግዚአብሔር ትምህርት ከኛ ጋር ካልሆነ በስተቀር አይገኝም ይላሉ፡፡
አይሁድና እስላም የህንድ ሰዎችም ሌሎችም ሁሉ እንደነሱ ይላሉ፡፡ እንዲሁ ደግሞ ክርስቲያኖች እርስ በርሳቸው አይስማሙም፡፡ ካቶሊኮች እግዚያብሔር ከኛ ጋር ነው ያለ እንጂ ከናንተ ጋር አይደለም ይሉናል፡፡ እኛም እንዲሁ እንላለን፡፡ ሰዎች እንደምንሰማቸው ግን የእግዚአብሔር ትምህርት እጅግ ጥቂቶች ወደሆኑት እንጂ ለብዙዎቹ አልደረሰም፡፡ ከእነዚህ ሁሉ ደግሞ ወደ ማን እንደደረሰ አናውቅም፡፡ እግዚያብሔር ከፈቀደ ቃሉን በሰው ዘንድ ማፅናት ተስኖት ነውን? ሆነም ግን የእግዚያብሔር ጥበብ በመልካም ምክር ይህ ነገር እውነት እንዳይመስላቸው ሰዎች በሐሰት ሊስማሙ አልተወም፡፡ ሰዎች ሁሉ በአንድ ነገር በተስማሙ ጊዜ ይህ ነገር እውነት ይመስላል፡፡ ሰዎች ሁሉ በሃይማኖታቸው ምንም እንደማይስማሙ በሃሳብም ሊስማሙ አይችሉም፡፡ እስኪ እናስብ ሰዎች ሁሉ ሁሉን የፈጠረ እግዚያብሔር አለ በማለታቸው ስለምን ይስማማሉ? ፍጡር አለ ፈጣሪ ሊገኝ እንደማይችል፤ ስለዚህም ፈጣሪ እንዳለ እውነት ነውና ነው፡፡ ይህ የምናየው ሁሉ ፍጡር እንደሆነ የሰው ሁሉ ልቦና ያውቃል ፡፡ ሰዎች ሁሉ በዚህ ይስማማሉ፡፡ ነገር ግን ሰዎች ያስተማሩትን ሃይማኖት በመረመርን ጊዜ በውስጡ ሐሰት ከእውነት ጋር ተቀላቅሎበታል፡፡ ስለዚህ እርስ በርሱ አይስማማም፡፡ ሰዎች እርስ በርሳቸው አንዱ ይህ እውነት ነው ሲል፡፡ ሁለተኛው አይደለም ሐሰት ነው ሲል ይጣላሉ፡፡ ሁሉም የእግዚያብሔርን ቃል የሰው ቃል እያደረጉ ይዋሻሉ፡፡ እንደገናም የሰው ሃይማኖት ከእግዚያብሔር ብትሆን ክፉዎችን ክፉ እንዲያደርጉ እያስፈራራች መልካም እንዳያደርጉ ትፈቅድላቸው ነበር፡፡ ደጎችንም በትዕግስታቸው ታፀናቸው ነበር፡፡
ሃይማኖት ባሏ ሳያውቅ በምንዝርና
የወለደች ሴትን ትመስለኛለች፡፡ ባሏ ግን ስለመሰለው በሕፃኑ ይደሰታል፡፡ እናቲቱንም ይወዳታል፡፡ በዝሙት እንደወለደችው ባወቀ ጊዜ ግን ያዝናል፡፡ ሚስቱንም ልጅዋንም ያባርራል፡፡
እንዲሁም እኔም ሀይማኖቴን አመንዝራና ዋሾ መሆኑዋን ካወኩ በኋላ ስለርሷ በዝሙት ስለተወለዱ ልጆቿ አዘንኩ ፡፡ እነሱ በጠብ፣ በማሳደድ፣ በመማታት፣ በማሰር፣ በመግደል ወደዚህ ዋሻ ያባረሩኝ ናቸው፡፡ ነገር ግን የክርስቲያን ሃይማኖት እውነት ናት እንዳልል በዘመነ ወንጌል እንደተሰራ ክፉ አልሆነችም፡፡ የምህረትን ሥራ በሙሉ እርስ በርስ መፋቀርን ታዛለች፡፡ በዚህ ዘመን ግን የሀገራችን ሰዎች የወንጌልን ፍቅር ወደ ጠብና ሃይል ወደ ምድራዊ መርዝ ለወጡት፡፡ ሃይማኖታቸውን ከመሰረቱ አመፃ እየሰሩ ከንቱ ያስተምራሉ፡፡ በሐሰትም ክርስቲያኖች ይባላሉ፡፡
© ሐተታ ዘርዓ ያዕቆብ
19 Nov, 05:16
18 Nov, 05:29
አያ ሙላ ከንግድ ማከል ዕቃ ገዝቶ አሸክሞ እየሄደ ፣ የተሸከመው ሰውዬ በሰዉ መሃል ተሽሎክሉኮ ጠፋበት ፡፡
ከሳምንት በኋላ ሌላ ዕቃ ለመግዛት ከጓደኛው ጋር ወደ ንግድ ማከል የሄደው ሙላ ዕቃውን ይዞበት የጠፋውን ልጅ ከቅርብ ርቀት እንዳየው፣ “ያውልህ ያልኩህ
ልጅ..እቃዬን ይዞ የጠፋዉ...ቶሎ እንደበቅ” አለ !
“ለምንድነው የምንደበቀው - አንቀን ዕቃውን እንቀበለዋለን” እንጅ አለ
ጓደኛዬው
“ሞኝ አትሁን” አለ ሙላ ዓይኑ አፈጥጦ ፣ “እሺ ዕቃውን ሰጠኝ እንበል፡፡ ሳምንት
ሙሉ የተሸከምኩበትን ክፈል ቢለኝስ ? ”
መልካም~ ሰኞ 🙏
17 Nov, 16:31
<<…ልጅ ሆኜ ነብሴን እጅግ ደስ የሚላት ጢቢ፣ ጢቢ ስጫወት ነበር። ጎረምሳ ሆኜ ነብሴን እጅግ ደስ የሚላት ሴት ልጅን ሳቅፍ ነበር። ዛሬ አርጅቼ ነብሴን እጅግ ደስ የሚላት ልጄ ስትስቅ ሳይ ነው። አሁን እነዚህን ሶስት እኔዎች ሳስተያያቸው አንድ ሰው ናቸው? እርግጠኛ መሆን ያስችላል። እኔ ሽማግሌውስ አንድም፣ አራትም ብሆን ይኸው እዚህ አለሁ። ያ እኔ የምለው ልጅና ያ እኔ የምለው ጎረምሳ ግን የት ሄዱ? የኔ ትውስታ ውስጥ ከልጅየውም ከጎረምሳውም ከብዙ በጥቂቱ እንደ ፊልም ተቀርፆ ይገኛል እንጂ እነሱ ግን የሉም። እኮ እንዴት እኔ ውስጥ ተቀርፀው ሊገኙ ቻሉ? ያን ጊዜ ልጅየው ሆነ ጎረምሳው ሲኖሩ እኔ እዚያ አልነበርኩም'ኮ። ገና አልመጣሁም ነበራ። ያን ጊዜ ያልነበርኩ ሰውዬ ትውስታ ውስጥ አሁን የሌሉ ያን ጊዜ የነበሩ ሰዎች ተቀርጸው ይገኛሉ። ይሄ እንዴት ሊሆን ቻለ? የጊዜና የትውስታ ምስጢራዊ ምትሀት ነው። ለመሆኑ ጊዘና ትውስታ ምንና ምን ናቸው?...>>
-- --
ምንጭ ፦ እግረ-መንገድ፣ ስብሃት ገብረእግዚአብሔር ...ገጽ 206-207
16 Nov, 16:54
በእግዚአብሔር ሞቷልና በእግዚአብሔር የለም መካከል ያለው ፍልስፍናዊ ልዩነት
ጀርመናዊው ድንቅ ፈላስፋ ፍሬድሪክ ኒቼ "the gay science" በሚለው መፅሐፉ ውስጥ ተከተዩን ቃል ይላል:- God is dead. God remains dead. And we have killed him. How shall we, murderers of all murderers, console ourselves? That which was the holiest and mightiest of all that the world has yet possessed has bled to death under our knives. Who will wipe this blood off us? With what water could we purify ourselves? What festivals of atonement, what sacred games shall we need to invent? Is not the greatness of this deed too great for us? Must we not ourselves become gods simply to be worthy of it? There has never been a greater deed; and whosoever shall be born after us - for the sake of this deed he shall be part of a higher history than all history hitherto."
በአጭሩ ኒቼ በ "the gay science" ስራ ውስጥ የሰውልጅ through the rise of rationalism and science ቀድሞ የነበረውን ሀይማኖታዊና እግዚአብሔራዊ ጥገኝነት ገድሎቷል ጥሎታል ይላል.....እግዚአብሔርን ገድለነዋል በሳይንስ እና በአመክንዮ
እንግዲህ god is dead የሚለው ሐረግ ብዙ ሰው እንደሚመስለው(ለፍልስፍና ቤተኛ በሆኑት ወገኖች ዘንድ) existence of god ላይ ያተኮረ ሳይሆን በጊዜ የነበረውን የ moral decay ለማሳየት የተጠቀመው ነው....ሀይማኖት የስነምግባርና የትርጉም ምንጭ መሆኑ ያበቃበትና nihilism የታወጀበት መፈክር ነው....god is dead
እግዚአብሔር የለም'ስ
እግዚአብሔር የለም በatheism የአስተሳሰብ ጎራ ውስጥ የሚቀነቀን ፍልስፍናዊ ሀሳብ ነው....ይህ ነገር ትኩረቱ ከላይ እንዳየነው የ morality ጉዳይ ሳይሆን existence of creator ነው....ማለትም አለም ከየት መጣ?! ማን አስገኘን?! ለምን ተገኘን?! ከሚሉት metaphysical ጥያቄዎች የሚነሳ ነው.....የዘርፉ ፈላስፋዎች እግዚአብሔር የሚባል አካል የሰውልጅ ተፈጥሮ ነግሳበት በነበረ ጊዜ በአእምሮ እንደ አፅናኝ እንደ ጠባቂ የሚያየውን አባታዊ ምስል ፈጥሮ ማምለክ እንደጀመረ ያስረዱናል....መፅሐፈ ክህደት ላይ ኦሪት ዘምልኪ 1÷26 ላይ "ኑ እግዚአብሔርን በመልካችን እንደምሳሌያችን እንፍጠር" ብለው የሰውልጆች ሲማከሩ እናነባለን(postmodernism ስልት)
ኢትዮጵያዊ የቅኔ ሊቅ ተዋነይ ይችን ሀሳባችንን በቀጣዩ ቅኔ ያጠናክርልናል
የአምን ወይገኒ
ኵሉ ዓለም በዘፈጠረ ለሊሁ
ብዙኃን እንዘ ይገንዩ ይስግዱ ቅድሜሁ
ለነጽሮ ዝኒ ነገር እሥራኤል ከመይፍርሑ
ሙሴ ፈጠረ ፈጣሪሁ
ወ ፈጣሪ ፈጠረ ኪያሁ
ትርጉም
ዓለም ኹሉ እርሱ ራሱ በፈጠረው ያምናል፣ ይገዛልም
ብዙዎች በፊቱ እየተገዙ ይሰግዱለት ዘንድ፣
ይኽንን ነገር ለመመልከት እሥራኤላውያን እንዲፈሩ
ሙሴ ፈጣሪውን ፈጠረ፣
ፈጣሪም እርሱን ፈጠረ”
አዩልኝ:- እስራኤላውያን እንዲፈሩ(ስርዓት እንዲገቡ) ሙሴ ፈጣሪ የሚባል ነገር ፈጠረ....እንዲህ የሚል ጂኒየስ የቅኔ ሊቅ እናንት ኢትዮጵያዊያን በጉያቹ ታቅፋቹ አሁንም ሙሴ ለገዛ ህዝቡ የሰራውን እግዚአብሔር የሚባል የውሸት ፈጣሪ ላይ ተቸንክራቹ ታላዝናላቹ ምስኪናት
አዲዮስ
🔯שלום
16 Nov, 15:15
15 Nov, 06:08
☯የማንነት እውነት !
“You’ll never know who you are unless you shed who you pretend to be. ” ― Vironika Tugaleva
⚡️በዙሪያችን ያለው ደመና በውስጣችን ያለውን ጸሐይ ከልሎታል… የየዕለታችን አመድ የመነሻችንን ፍም አዳፍኖታል… የአስተዳደጋችን ቅኝት የዕይታ አድማሳችንን ኮድኩዶታል፣ የአስተምሯችን ስሪት፣ የየቤተእምነታችን መሰረት፣ የአካባቢ፣ የሃገር፣ የሚዲያና የአብሮ ውሎ ሸንጓችን ጨለማ የማንነታችንን ግዝፈት ውጦታል… ትልቁን ምስል ለማየት ስለተሳነን ባየነው ልክ ራሳችንን ሰርተናል… በምልዓት ማየት ስላልጀመርን ለሽንቁር ማንነት ራሳችንን አሳልፈን ሰጥተናል… ነባሩን ዘዬ ስላልፈተሽን አዲስ መንገድ ማየት አቅቶናል… የነገሩንን ስላመንን የሆነውን መጠየቅ ትተናል… አይቻልም ስላሉን አለመደፈሩን ተቀብለናል… እናም ዛሬ ራስዳሽኑ ማንነት በኮረት ጥላ ውስጥ ተጨልሟል…
⚜የማንነትን ጉዳይ… እንደየ ጥናት መስኩ ሃቲት፣ እንደየ መንግስታቱ ውልደት፣ እንደየ ማሕበረሰቡ ነባር ትውፊት፣ እንደየ ሐይማኖታቱ መፃሕፍት እንጂ እንደ ጥልቁ ማንነታችን ምንነት ለመተንተን ሞክረን አናውቅም… ለኛ ማንነት ማለት ብዙዎች የሚያቀነቅኑት ምንነት ነው – ከየልባችን የምንመክረው ዘላለማዊ ወግ አይደለም… ማንነት ለኛ ከመሰሎቻችን የተዋስነው የአደራ ዕቃ ነው – በነፍሳችን ሹክሹክታ ስምረት የሚሰራ ሁሉአዊ መልክ አይደለም… ማንነት ለኛ ከመሆን በኋላ በሆነ ሁነት ውስጥ የሚቀነበብ ወቅታዊ ነው – ከመሆን በፊት በነበረ፣ ባለና በሚኖር ምንጭ ላይ የቆመ ዘላለማዊ አይደለም…
🔆የልኬታችንን ምልዓተ ዓለምነት እንዳናይ አዚም ያደረገብን ማነው?… የምንጫችንን አልፋ እንዳናውቅ ነገር የሰራብን ማነው?… ከጥልቅነታችን የመሰረት ወለል የነቀለን ማነው?… በአንድነት አውድማችን ላይ እልፍነትን ያበራየው ማነው?… በስክነት ጉባኤያችን ውስጥ ጩኸት የዶለው ማነው?… እውነትን ከምናይበት ማማ ላይ ጽልመት የጋረደብን ማነው?…
⚜‘አንተ ማነህ?’ ላለን ሁሉ ማንነት ያልሆነ ማንነት ስንነግር ቆይተናል… ስማችን ያልሆነ ስም፣ ሃገር ያልሆነ ሃገር፣ ቀለም ያልሆነ ቀለም፣ ልክን የማይገልጽ ልኬት፣ ተናጥሎን የሚሰብክ ማንነት፣ ብስለትን የማይገልጽ ዕድሜ፣ ምንምነትን የሚያረቅ ታሪክ፣ … ወዘተ… በቀቀናዊ ኑረት…
⚡️ከመሆን በፊት የሆንከው መሆን ዘላለማዊ፣ ከመሆን በኋላ የሆንከው ሁነት ጊዜያዊ ነው… ዜግነትህ፣ ብሔርህ፣ የትምህርት ደረጃህ፣ ስራህ፣ መደብህ፣ የትውልድ ቦታህ፣ ቤተሰብህ፣ ሐይማኖትህ… ማናቸውም በ ‘እኔ’ ና ‘የኔ’ ቁናነት የሚሰፈሩ ነገሮችህ ማንነትህ አይደሉም… የትኛውም፣ ከእስከ አልባው ሕዋ በተናጥሎ የሚያስቀምጥህ ሃሳባዊውም ሆነ ቁሳዊ ምንትስ ማንነትህ አይደለም… ያንተ ማንነት የሌላውም ማንነት ነው… የእኔ፣ የእርሱ፣ የእነርሱ የሚባል ማንነት የለም… ማንነት አንድና ዘላለማዊ ነው… ዘላለማዊ ማንነት ስላለህ ዘላለምህ ውስጥ ሞት እንኳ የለም…
🌺 በ’እኔታ’ እና ‘አንተታ’ መገለጥ /Subjective manifestation/ ውስጥ እንመላለስ እንጂ የምንጫችን አንድነት /Oneness/ የሁለንተናችን አንድነት ነው… ይህም በሰው፣ በእንስሳ፣ በተክል፣ በፕላኔት፣ በጠፈር፣ በሕዋ… በሚታየውና በማይታየው ዓለም ውስጥ ባሉ መገለጦች ውስጥ ሁሉ ያለ አንድነት ነው… ሕብረት፣ ጋርዮሽ፣ ጥምረት፣ ሕብራዊነት፣ ትብብር አይደለም አነድ-ነት ነው… አንድ ላይ መሆን አይደለም አንድ ብቻ መሆን ነው… Self ውስጥ ቁጥር የለም… በቃ ‘መሆን’ Being ብቻ ነው ያለው…
💫 ራማና ማሀርሺ እንደነገረን “The Self is beyond duality. If there is one there will also be two. Without one there are no other numbers. The truth is neither one nor two. It is as it is.”
🔆 ማንነት አለኝ የምትለው አይደለም – የሆንከው እራሱ ነው… Possession በማንነት ውስጥ ቦታ የለውም… አንተነትህ ከማንነትህ የተነጠለ አይደለም – ማንነትህ ነው አነተነትህ… ማንነትህ ቅርጽ፣ ቀለም፣ መስፈሪያ፣ ድንበር አልያም ጠገግ የለውም – በሁሉ ያለ፣ በሁሉም የሚኖር ነው…
💫“All that we have to do is to give up identifying the Self with the body, with forms and limits, and then we shall know ourselves as the Self that we always are.” Ramana Maharshi
🌼 አንተ ውስጥ ‘ሌላው’ አለ – ‘ሌላው’ ውስጥም አንተ አለህ… “Quantum Physics reveals thus reveals a basic oneness of the universe” – Erwin Schrödinger
💫 አንስታይን በበኩሉ ይህን ይላል … “A human being is part of the whole, called by us ‘Universe’; a part limited in time and space. He experiences himself, his thoughts and feelings as something separated from the rest—a kind of optical delusion of his consciousness. This delusion is a kind of prison for us, restricting us to our personal desires and to affection for a few persons nearest us. Our task must be to free ourselves from this prison.”- Albert Einstein
🔆 ስለማንነትህ እንዲገባህ ማንንም አትጠይቅ… የማንነትህን ልኬት በሌሎች ግንዛቤ ውስጥም አትሻ… ከራስህ ጋር አውጋ! ወደውስጥህ ተመልከት…
⚡️ ከውጭ የምታየው ሁሉ የውስጥያህ ነጸብራቅ ነው… አንተ ሕዋ ውስጥ ሳይሆን ሕዋው ነው አንተ ውስጥ ያለው እንደማለት…
💫“You are not IN the universe; you ARE the universe, an intrinsic part of it. Ultimately you are not a person, but a focal point where the universe is becoming conscious of itself. What an amazing miracle.” ― Eckhart Tolle, ‘A New Earth’
🔆ነፍስህ እስካላዜመችው ማንነት አይገባም… ከአዕምሮ ባርነት እስካልተላቀቅህ መሆን አይገለጽም… ወደ ውስጥ እስካልዘለቅህ ከራስህ ጋር አትገናኝም
ልብህን ጠይቅ ይመለስልሃል!! የማንኛውም ጥያቄህ መልስ ማንነትህ ውስጥ አለ… ማንነትህን የማወቅህ ቅጽበት ውስጥ ደግሞ ደስታ – ዘላለማዊ ደስታ… እ-ፎ-ይ-ታ!!!
መልካም አሁን
©ደምስ ሰይፉ
15 Nov, 04:30
ከእለታት አንድ ቀን ሙላ ናስሩዲን በሰፈሩ ከሚገኝ ሱቅ በመሄድ ባለሱቁን ፦ " ቆዳ ይኖርሃል?" ሲል ጠየቀው
ባለሱቁም ፦ "አለኝ" አለ
ናስሩዲንም ፦ "ሚስማርስ አለህ?"ሲል ጠየቀ
ባለሱቁም ፦" አዎ አለኝ "ሲል ድጋሜ መለሰ
ናስሩዲንም አሁንም ጠየቀ ፦"ክርስ አለህ?"አለው
ባለሱቁም ፦"ክር አለኝ" አለ
ናስሩዲን ፦"መርፌስ አለህ?" ሲል ጠየቀ
"አዎ አለኝ " አለ ባለሱቁ
ናስሩዲን አንዲህ ሲል ተናገረ ፦ " ታድያ ጫማ እየሠፋህ ለምን አትሸጥም?" በማለት እየሳቀ ጥሎት ሄደ ።
መልካም - ቀን 🌻
14 Nov, 16:51
13 Nov, 10:19
12 Nov, 13:38
12 Nov, 04:16
11 Nov, 16:24
11 Nov, 13:33
10 Nov, 12:54
ድብብቆሽ እንጫወት?! እኔ ልብ ውስጥ ከተደበቅሽ አንቺን ማግኘት አይከብድም ። ከራስሽ ቅርፊት ጀርባ ከተደበቅሽ ግን ማንም አንቺን በመፈለግ አይጠቀምም።
©ካህሊል ጅብራን ❤️
09 Nov, 15:58
ጥንቆላ፡ አምልኮት እና ስርአት
Based on Philosophical Point of views
በሰውልጅ ቀደመት ታሪክ ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ ይዘው የሚገኙ ሦስት ኃይላተ ሰብ ናቸው ጥንቆላ ፡አምልኮ እና ስርአት[ስርየት]።ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ የሰው ልጅ ከነበረው አጠቃላይ የመረዳት ንቃት ማነስ እንዲሁም ለማይታዩ አካላት[መለኮታዊ ለሚላቸው(Superstition)] ከፍተኛ ቦታን ሰጥቷ ሲራቀቅበት እንዲሁም ሲያመልክበት እዚህ ያለንበት ደረጃ ደርሷል።
ብዙ ሰዎች በትረ ኃይሉን ኃይማኖት የጨበጠ ጊዜ¹ እነዚህ ነገሮች እንደጀመሩ ያስባሉ።እውነታው ግን ይሄ ነው! የሰውልጅ ታሪክ «ሀ» ብሎ የጀመረ ሰአት የጀመሩ ናቸው።እንደውም በተቃራኒው በዘመነ ጽልመት እየተዳከሙ የመጡትንም እንዲሁም የሮማን ካቶሊክ ቸርች አብዛኞቹን በፀረ ክርስትናዊ ምልከታ ግድያ የፈረደችባቸው ጊዜያት ናቸው።
በመጀመሪያ ሀሳቤን ለማስረዳት በእነዚህ ሶስት ተመሳሳይ የሚመስሉን ነገርግን የተለያዩ ቃላት ውቅርን በመፍታት ልጀምር፥
ጥንቆላ[Witch]: ጥቁር አስማት[Black Magic] እና መናፍስት መጥራት[Summoning spirits] ላይ ያተኮረ በሰውልጅ የህይወት ዳራ ውስጥ ጣልቃ ገብነት በመፍጠር ለውጥ ለማምጣት የሚደረግ ነገር።
አምልኮ[occult]: ስለመናፍስት፡የሰውልጅ እውነተኛ መንፈሳዊ ማንነት እንዲሁም ስለተለያዩ ኃይላተ ተፈጥሮ[ነጭ አስማት እና ጥቁር አስማት] የሚያጠና ሳይንስ ነው።ከሜታፊዚክሱ እና ፓራሳይኮሎጂ ጋር ከፍተኛ ተመሳስሎ አለው[በዚህ አጋጣሚ! ዘመናዊው ሳይንስ በራሱ በዚህ ስር የሚመደብ ነው]
ስርአት[Ritual]:ማንኛውም የታቀደ ተግባር ለማንኛውም ነገር ሊደረግ የሚችል በሰዎች መሰባሰብ የሚከውን ነጭ አስማታዊ ስርአት። ባህላዊ፡ ሊሆን አልያ ፖለቲካዊ[የምርጫ ሂደት Ritual ነው!]ወይም ኃይማኖታዊ ሊሆኑ ይችላል በዚህ ይካተታሉ።
እዚህ ላይ እርቅ ከፈጠረን ፍልስፍና በእነዚህ ሶስት ኃይላተ ንቃት ላይ የነበሯት ጉልህ ሚና እንመልከት።
Philosophy And Witch Teaching
በየትኛውም ሰይጣናዊ አምልኮ[Black Magic] ውስጥ ወይም አስተሳሰብ ውስጥ የምናገኘው ነገር እጅግ የተዳከመ የፍልስፍ እንቅስቃሴ ሲሆን አምልኮቱ ካረቀቁት በቀር ተከታዮች ስራቸው በሙሉ ድምፅ ልምምዱን ማፅደቅ ብቻ ነው።በርግጥ ከቀደምት አባቶቻቸው የተማሩን ነገር ነበር እነሱ የሚተገብሩት አንዳንዶቹ ግን ፍልስፍናን እንደመራቀቂያ መሳሪያ በመጠቀም ሌላ ታሪክ ውስጥ ገብተው ነበር።ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚነሳው ነገር የእነቶማስ ሆብስ እና አርስቶትል ፍልስፍና ሀሳብ እና አንድምታ ከጥንቆላ አስተምህሮ ጋር ንክኪ የነበረው መሆኑ ነው።የፕሌቶን ፍልስፍና[በተለይ Existence of the two worlds] አጥብቀው ይወዱታል።አንዴ ከተነሳ ላይቀር በአለም ላይ እጅግ ተፈላጊ ስለነበረው የሰለሞን ቀለበት(✡️) ማንሳቱ እጅግ አስፈላጊ ይሆናል። ሰለሞን ከእግዚአብሔር ከተቀበለው ጥበብ መብዛት የተነሳ ሰባ ሁለት[72] ዋና ዋና የመናፍስት ገዢ መሪዎች ላይ ስልጣን በቀለበቱ በኩል ያገኘ እና ቀለበቱ የመናፍስቱን መሳቢያ ጠልሰም[በእኛ አጠራር መርብበተ-ሰለሞን] በምልክትነት እንደያዘ ይታመናል።ይሄን ቀለበት ማግኘት ዋንኛ የጥንቆላ Objective Goal ነበር።
Philosophy Science $ Occult
እመኑኝ! ሳይንስ የሚመስጣቹ ሰዎች ይሄኛውን ዘርፍ ትወዱታላቹ።በአይሁድ እምነት ውስጥ በነበረው ሚስጥራዊ ትምርህት ካባላ[Kabbalah]፤በግሪክ:በግብፅ እንዲሁ ሀገራችንን ጨምሮ አጠቃላይ የአለም እምነቶች ውስጥ የገባው ሄርሜቲዝም [ኢትዮጵያዊው ሄኖክ] እና በስነ-ቅመማው ወይም አልኬሚ [Alchemy] ሚስጥራዊ አስተምሮች በሙሉ በከፍተኛ መልኩ ፍልስፍና የተጠቀሙ ሲሆን በአልኬሚው እንደነዚሞስ በሄርሜቲዝ ሙሉ በሙሉ Philosophical Aspect of Natural Existence ስለነበረ በሙሉ።
በካባላው ውስጥ የአይሁድ ጠቢባን ፍልስፍና የአፍ መቻቸው ነበረ።ከእነ ዲሞክራተስ:ፕሌቶ:ታለስ:አንክሲማንደር አናክሲማነሳ:ፓራሜንደስ ወደኢል ደግሞ ዜኖ[Zeno of Elie] ከመሳሰሉትን ጋር ከፍተኛ ተመሳሳይ ነጥቦች ነበሯቸው። ዘመናዊ ሳይንስ አብዛኛው ምርምር እና ጥናት የወሰደው ከካባላ ትምህርቶች ነው።
አንደሰ ሁለቱን ለመጥቀስ ያህል፥
1]Concept of Atom[የአተም ምንነት]
2]የተፈጥሮ ህግ እና የሰው ልጅ ምንነት[ከሳይንስ አንፃር]
3]የአንስታይን አንፃራዊ ህግ[Relativity Theory]
4]የኳንተም ፊዚክስ ምርምሮች
ካባላ[Kabbalah] ወደእኛ ሀገር አስተምህሮቱን ስናመጣው ከ«ባህረ ሀሳብ» ጋር አንድ ነው[ማን ከማን ወሰደ ነጥቤ አይደለም!]
Philosophy Under Alchemy
ይሄ ዘርፍ ላይ ደግሞ የኬሚካል ቅመማ፣ብረትን ወደ ወርቅ የመቀየር ሂደት ሌሎች የእፀዋት እና የከበሩ ዲንጋዮች ምርምር በዋናነት መርሁ ያደረ ሲሆን በግብፅ መነሻውን አድርጎ በግሪክ በኩል ቻይና፡ህንድ እና አረብ እንዲሁም ሌሎች ጋር የደረሰ አለምአቀፋዊ ሚስጥራዊ አስተምህሮ ነው።አልኬሚ ብረትን ወደ ወርቅ የመቀየሩ ነገር በቀጥታ የሚፈታ አደለም።ፍልስፍና በሙስሊም ኡለማዎች[Golden Age of Islamic] ዘንድ እና በህንድ መንፈሳዊ እምነቶች[Hinduism,Zen Buddhism]በኩል ሞገስ ያገኘች ሰሞን ነበር አልሜኬ ከፈጣሪ የተበረከተላቸው። አልኬሜ እንደፍልስፍና የተፈጥሮ ንጥረ አካላት እና ሰው እንዴት እንደሚተሳሰሩ ስራዬ ብሎ ያጠናል።ሰው የንቃቱ እና የመረዳቱ ደረጃው ከዴካርት በላይ ያስጨንቀዋል።
በዘመነ ዳግም ውልደት ታዋቂ የነበሩ አልኬሚስቶች ኒውተን እና ተከታዮቹ[Calculase Based Universe] ፣ከአረብ ሒሳብ እና አስትሮኖሚ ምሁራን አቬሴናን እና ጅላል አል-ሩሚ እንዲሁም አቡ ሙሳ፣ ወደ ህንድ በዋናነት ኒታይኒታ ሲድሀ እና ዮጊ ቬማናን ፣ወደ ቻይና ሰን ፑ-ሂ[Sun Pu-Eh] እና ኮ-ሆንግ[Ko Hong] ወደ ግብፅ ፈላስፎቹ በሙሉ በዚህ ተጠምደው ነበር ፤ወደ ግሪክ በዋናነት ዞሲሞስ እና አርስቶትል ወደእኛም ሀገር ደግሞ ሙሉበሙሉ በሚባል ደረጃ የነበረ ነገርግን ብረትን ወደ ወርቅ ከመቀየሩ በላይ ዋና ማእከሉ የእፀዋት መሰል ቅመማ ላይ ትኩረቱ ያደረገ ሆነ።
የአብርሃም ኃይማኖቶችን ጨምሮ ሌሎች ጥንታዊው ሆነ ዘመናዊ ኃይማኖት ነገረ መለኮታ ከእነዚ በመነጨ አስተምህሮ የተቀረፀ ነው።ኒቺ በOn the Genealogy of Morality² መፅሀፉ በኩል አጠቃላይ እነዚህ ዳራ ለመጥቀስ ሞግሯል።የአምልኮ እና የፍካሬ ከዋክብ ተመራማሪ የሆነው ማንሊ ፒ.ሆል «The Secret Teaching of All Religion³» መፅሀፉን እንድታነቡ እየጋበዝኩ ሀተታዬን እቋጫለሁ።
___
© ዋቢ መጽሐፍት 📚
¹ Dark Age[When Christianity of Thinking Mainly Dominants]
² On the Genealogy of Morality
Book by Friedrich Nietzsche
³ The secret Teaching of All Religion By Manly P.Hall
© ፍልስፍና
05 Nov, 05:12
04 Nov, 17:04
04 Nov, 17:04
04 Nov, 06:48
03 Nov, 16:04
03 Nov, 10:41
03 Nov, 08:22
ሙላ ነስሩዲን ትዳር ይይዝና መኖር እንደ ጀመረ ፡ አንድ ጓደኛው ወደሱ በመምጣት..
« ሙላ ነስረዲን ይለዋል አቤት በማለት ሲመልስለት ሰዎች ያሙሀል አለው ።
«ሙላ ነስረዲንም ጉዳዩን ለማጣራት ምን ብለው ነው፡ የሚያሙኝ ሲል ሰውየውን ይጠይቀዋል? »
« ሙላ ነስሩዲን ሚስት ካገባ በኋላ ሀይማኖተኛ ሆኗል እያሉህ ነው »
«ሙላ ነስሩዲንም ልክ እኮ ናቸው ፡ እሷን ካገባው በኃላ ነው በገሀነም መኖር ማመን የጀመርኩት »
02 Nov, 05:22
01 Nov, 17:29
የመኖር ትርጉም ጠፍቶኝ ስጨናበስ
የክዋኔ ጉልበት አጥሮኝ ስልፈሰፈስ
የፍቅር ስሜት ትርጉሙ ሲነፍስ'ሲፈስ
ሞትን በፅኑ ናፈኩ
ያልታጎለ ዝምታን አሰስኩ
የምንምነት መገኛ የት ይሆን ብዬ ፈለኩ
ፈለኩ
ፈለኩ
ፈለኩ
ግና
የህይወት ቋንቋው ይህ ነውና
ምን እላለሁ ዝምብዬ ዝም አልኳ
©ROHHA
01 Nov, 05:17
31 Oct, 15:56
31 Oct, 15:56
31 Oct, 05:37
30 Oct, 15:51
29 Oct, 16:24
29 Oct, 15:13
28 Oct, 05:26
27 Oct, 12:34
26 Oct, 05:28
“Art is to console those who are broken by life.”
« ኪነት በህይወት የተሰበረውን ማጽናናት ነው »
― Vincent van Gogh
24 Oct, 15:01
24 Oct, 03:56
23 Oct, 16:21
23 Oct, 13:39
23 Oct, 09:15
22 Oct, 03:59