አንዴ ዝቅ አንዴ ከፍ
የተከታይ ነገር ይበዛዋል ወልከፍ።
ተከታይ ገለባ ቀልቡ ወኔው ስሱ
የትሁት ተከታይ አንካሳ ነው ነፍሱ።
ጥያቄው? "አብሬህ ባረጀሁ" እያልኩኝ የዋጀሁ ተፈተነ እምነቴ ጠፋብኝ
ስብከቴ ዕምነቴ ታለለ
ነኝ ያልኩት የታለ?
ግን ማረኝ::
ሰው ምን ቢበድል
ትንሽ ትንሽ ገድል። (ያጣል?)
ሰው ምን ቢሳሳት
ንዋየ ቅድሳት።
(አይደለም?)
ሰው ምን ቢከፋ
ጳውሎስ ቢሆን ኬፋ
ዘሩ ትሁት አንተ ግንደወይን ጽድቁ
ሲያፈሩ ተገኙ ወዳንተ ሲወድቁ።
የማያገኙትን እያሰላሰሉ ኖሮ ከመቀጨት
ወዳንተ በጣለኝ እንደደመራ እንጨት።
እኔማ
እያደነቀፈኝ
እኔማ
ኃጢያት እያቀፈኝ
እኔማ
ሰይጣን ቢገዛኝም ከእግር እስከራሴ
እከተልሀለሁ በቁርጥራጭ ነፍሴ።
አንተ ብቻ ማረኝ።
✍ኤልያስ ሽታሑን
@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gitim
#Join_and_share