╔═══❖•ೋ° °ೋ•❖═══╗
....... የቁማር ፍቅር ......
✎ ፀሐፊ፦ ሀፍሳ
╚═══❖•ೋ° °ೋ•❖═══╝
┎━─━─━─━─━─━─━─━─━┒
በ @Loveis_one የተዘጋጀ
┖━─━─━─━─━─━─━─━─━┚
╔════•| ✿ |•════╗
#ክፍል_አንድ [፩]
╚════•| ✿ |•════╝
"እንዴ አባ 4 ሰአት ሞላኮ...."ከተኛችበት ዘላ ተነሳች።"መድረሳ እንደሚረፍድብኝ እያወቅክ በአላህ..."አጉረመረመች።አባቷ አደለም እሷን ለመቀስቀስ ቀርቶ ራሱ እንኳን አለመነሳቱን ስታይ ተገረመች።
"እንዴ አባ ያለመደብህን"ብርድ ልብሱን ገለበችው "አንተም ስራ መቅረትህ ነው እንግዲ ተነስ...ዛሬ ቤት መዋላችን ነው..."ፀጉሯ ላይ የጠቀለለችውን ሻሽ ፈታ አጠር ለስለስ ያለ ፀጉሯን ፈትታ በታተነችው።"እርቦኛል ደሞ ቁርስ እንብላ..."ብላ የፈታችውን ፀጉር መልሳ እያስያዘች ወደ ጠባቡ እቃ ክፍል ገባች።የሚሞቀውን አሟሙቃ ለራት የተረፈውን ዳቦ ይዛ ቁርስ አቀራረበች።አባቷ አልተነሳም።
"ኡፍ ደሞ ችግር አለብህ..."ጎኑ ቁጭ አለች።"ተነስ..."ነቀነቀችው።መልስ አልሰጣትም
"አባ ተነስ ለስሙስ እኔን ሬሳ መይት ትለኛለህ ከመቼ ወዲ ነው እንደዚ መተኛት የጀመርከው?"ትኮረኩረው ጀመር።
"ይኸው መድረሳ አስቀረኸኝ አንተም ስራ መቅረትህ ነው ቢያንስ ሌላው ቢቀር ቶሎ ቁርስ እንብላ...."የምትችለውን ያህል ነቀነቀችው።
መልስ የለም..... ደንገጥ አለች
"በማይቀለደው እየቀለድክ ባልሆነ...ኡፍ ርቦኛል ወላሂ ከፈለክ በልተን ስንጨርስ ትቀልዳለህ..."
ፀጥ...
"አባ..."በጀርባው ገልበጥ አረገችው።ልብ ምቱን ለማዳመጥ ፈልጋ ፈራች።ባይኖርስ??ቁሞ ቢሆንስ? እናት አባት እህት ወንድም ሆኖ ያሳደጋት ሚስኪኑ አባቷ ልቡ ደም መርጨት አቁሞ ቢሆንስ?? "ማይሆነውን"አለች በውስጧ።የአባቷ እዚ ሰአት ድረስ መተኛት ስጠራው አለመስማት ለጤና አለመሆኑ ገባት።ከሱብሂ ቡኋላ ቁርስ ሲሰራ ሲያዘገጃጅ ሲያብቃቃ እንጂ አንድ ቀን ተኝቶ ነግቶበት አያቅ።ምን ነካው??ማመን ግን አልፈለገችም።ቀስ ብላ ተነስታ ወደ ውጪ ወጣች።ወፍራሟ ጎረቤታቸው ደጅ እየጠረገች ነበር
"አሰሌ ተመድረሳቹ ዛሬም ቀረሽ ወይ?"
"አው እቴቴ አባ አልቀሰቀሰኝም ነበር እስካሁን ተኝቷል"አለች መሬት መሬቱን እያየች
"ምን ትያለሽ?እሱ የጧትም ሰው አደል እንዴ?ተንቅልፍ ጋር ይተዋወቃል ብለሽ ነው?"
"አላውቅም ስጠራውም አይሰማም ገብተሽ እይው"እምባዋ ወረደ
ወፍሯሟ ዝናሽ በአሰል ንግግር ደንግጣ መጥረጊያዋን ጥላው ወደ ውስጥ ገባች።አሰል በሩ ጋር ግድግዳውን ተደግፋ አቀርቅራ እጇን እያፍተለተለች መጠባበቅ ጀመረች
"ምን ትላለች እየተነፈሰም አደል?ሟርተኛ"ሚለውን ቃል ለመስማት የቋመጠች ቢሆንም ከጆሮዋ ሊጠፋ የማይችል የዘላለመም ጩኸት ተሰማት..
"ኡኡኡኡኡኡ አፈር ስሆን አፈር ስሆን...."የዝናሽ ጩኸት ሰፈሩን አመሰው።አሰል ሰማይ ምድሩ ቅብዥር አለባት።የተደገፈችውን ግድግዳ ታካ መሬቱ ላይ ቁጭ አለች አብሯት እምባዋ ተንሸራተተ።ከአይኖቿ የሀምሌ ዝናብ የሚያስንቅ እምባ ቡልቅ ቡልቅ ማለቱን ቀጠለ.... በየመሀሉ
"ለምን??"ትላለች።አባትም እናትም ሆኖ ያሳደጋት አባቷ አሁን ሞተ ብላ መቀበል ጭራሽ የማትችለው ነገር ሆነባት።የወደፊት ህይወት ያለሱ ጭራሽ የማይታሰብ ሲኦል ሆኖ ተገለጠላት።የዝናሽ አሰቃቂ ዋይታ መንደርተኛውን የሰበሰበ ቢሆንም ለአሰል ግን ቅስም ሰባሪ የህይወት ጣዕም መራራ መሆን እንደሚጀመር ሚያሳይ ማንቂያ ደውል ነበር።ደጋግሞ አስተጋባባት...."ለኔ ባረገው ለኔ ባረገው...."ዝናሽ ሰፈሩን ማደባለቅ ተያያዙት
"ያረብ ህልም አርገው"ተንሰቀሰቀች።መንደርተኛው ከየቤቱ እየተሯሯጠ መጣ።ለጊዜው የሷ እኩዬች መድረሳ ስላሉ እናቶች የሷን መኖር አላስተዋሉም ሁሉም ያለቅሳል ይጮሀል።የሰው መብዛት ሀዘኗን አባሰው።በህይወት ሳለ የሚገለምጡት ሚያጉረጠርጡበት ሁሉ ዛሬ ሲያለቅሱ ውስጧ ንዴት ተቀጣጠለበት።ያለችው ህልም ላይ እንጂ እውነት ሆኖ አልታይሽ አላት....
"አባትሽ እየጠራሽ ነው..."፣"አባትሽ ሽንኩርት ግዢ ብሎሻል..."እያሉ በሩቁ ትዕዛዝ ሚያስተላልፉላት ዛሬ ላይ ራሱን ከአደጋ እንደሚጠብቅ ትል ከተጠቀለለችበት ቦታ እየመጣ
"ጀናዛ ተሰናበቺ..."እያለ ናላዋን አዞረው።ከአባትነት ወደ ጀናዛነት።ሽንኩርት በውሀ በጥብጠው የበሉት ሽሮ ናፈቃት።ሶስት አራት ቀን ያደረውን ዳቦ ከአባቷ ጋር በፍቅር እንዳልበሉት ዛሬ ትኩስ ዳቦ ከጉሮሮዋ አልወርድ አለ።
ከሳምንት ቡኋላ.....
ያላቸው ብቸኛ ቤተሰብ የአባቷ እህት ሂዳያ ብቻ ናት።እሷም ቢሆን ክረምት እነሱ ጋር ታሳልፍ ስለነበር ትወዳታለች።የወንድሟን ልጅ ለማሳደግ በአደራ ተቀብላ አሰልን ተወልዳ ካደገችበት ጎጃም ወደ አዲስ አበባ ወሰደቻት።ያለቀሰችው ማልቀስ... "ህልሜ ነው" ብላ በጉጉት "ከዛሬ ነገ ከእንቅልፌ ይቀሰቅሰኛል...ውሀ በሽሮ በጥብጠን አንድ ዳቦ ለሁለት ተካፍለን ሻይ በሳምንት አንዴ እያፈላን በፍቅር...በአሳማሚ ድህነት ማንም በማይሽረው ጥልቅ መዋደድ መኖር እንቀጥላለን..."ብላ የቃዠችው መቃዠት ሁሉ መና ሲሆን ታያት።
አክስቷ ወይዘሮ ሂዳያ ከባለቤቷ ከድር እና ከሁለት ልጆቿ ጋር ነው የምትኖረው።የመጀመሪያ ልጇ የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ 3ተኛ አመት ፍልስፍና ተማሪ ነው።ሁለተኛ ልጇ ከአሰል በእድሜ አንድ አመት የምትበልጥ ጠይም ቆንጆ ናት።
ተወልዳ ከኖረችበት ጎጃም አዲስ አበባ መምጣቷ አባቷን በማጣት ሀ ብሎ የጀመረውን የጨለማ ህይወት ሁ ብሎ የሚያስቀጥለውን መንገድ መክፈት ጀመረ.....
...... ይቀጥላል ......
ይቀጥል የምትሉ??👍
ቻናላችንን ለወዳጅ ዘመዶ ሼር በማድረግ ስራዎቻችንን ያበረታቱ። ስለምትከታተሉን ከልብ እናመሰግናለን!
↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴↴
╬╬═════════════╬╬
@Loveis_one
@Loveis_one
╬╬═════════════╬╬