General Wingate Students Channel @gwstudent Channel on Telegram

General Wingate Students Channel

@gwstudent


ይህ የጄኔራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተማሪ ቻናል ነው። @Gw2016bot
This is the Student Channel of General Wingate Polytechnic College.

General Wingate Students Channel (Amharic)

ወደ ጄኔራል ዊንጌት ትምህርት ኮሌጁን ቻናል የተመዝገቡትን ቴክኒክ ኮለጠር እንዴት ያወቁን ማንኛውንም ዝግጅት፣ ትምህርት ወደጆንል ለመማር እና ለማስተዋወቅ እባኮችን ማሳየት ብለን የጄኔራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አዲስ አማርኛ ቴክኒክ ቻናል ተጠቃሚው በማየት ከሚሆነው ቴክን ተምሳሌ። @Gw2016bot

General Wingate Students Channel

09 Feb, 10:53


በኪነጥበብ ውስጥ ለመሳተፍ የተመዘገባችሁ እንዲሁም አዲስ መመዝገብ የምትፈልጉ ሰልጣኞች ነገ ሰኞ 3 / 06 / 2017 ዓ.ም ከ ቀኑ 7:00 ላይ አሮጌው አዳራሽ እንድትገኙ እናሳስባለን።

በሰልጣኝ ካውንስል የኮሚኒኬሽን ተጠሪ

General Wingate Students Channel

06 Feb, 18:16


Dear trainees of our college,
Thank you for your voluntary participation in today's blood donation program at our college. By donating your blood, you have made a big difference in the lives of others. This act not only saves lives, but also demonstrates our commitment to building a healthy community.
We are proud of your good deeds and your sense of compassion and responsibility. We would like to express our gratitude to all of you for your contribution to the success of this program. We believe that you will continue to participate in various charitable activities in the future.
Thank you again!

Trainees Council

General Wingate Students Channel

06 Feb, 09:19


Happening Now!

General Wingate Students Channel

05 Feb, 17:08


ማስታወቂያ

ለኮሌጁ ማህበረሰብ በሙሉ ነገ 29/05/2017 ዓ.ም ከረፋዱ 5:30 ጀምሮ በኮሌጁ ግቢ ውስጥ የደም ልገሳ ፕሮግራም ስለሚኖር ፈቃደኛ የሆናቹ ደም በመለገስ የወገናችንን ህይወት እንድንታደግ በአክብሮት እንጠይቃለን።


የሰልጣኝ ካውንስል የበጎ ፈቃድ ተጠሪ

General Wingate Students Channel

31 Jan, 05:38


ቀን 22/05/2017

የጄኔራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የስነምግባርና ጸረሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ከእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሰልጣኞች የስነምግባር ክበብ አባላት ጋር የልምድ ልውውጥ አደረገ ፡፡
የእንጦጦ የስነምግባርና ፀረሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ባለሙያ የሆኑት አቶ መክተው ሹመቴ እና የሰልጣኞች የስነምግባር መከታተያ ክበብ የህዝብ ግንኙነት ተጠሪ የሆነው ተማሪ አቤሴሎም ስለክበቡ የስራ እንቅስቃሴ ገለጻ አድርገዋል ፡፡
የጄ/ዊ/ፖ/ቴ/ኮ የስነምግባር ክበብ አባላትም የተለያዩ ጥያቄዎችን ያነሱ ሲሆን በክበቡ አባል ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶበታል ፡፡
ኮሌጁን ከሌሎች ኮሌጆች ለየት የሚያደርገው በሌሎች ቴክኒክና ሙያ ተቋማት የማይገኘው የሙዚቃና አርት ዲፓርትመንትን የያዘ ሲሆን የስልጠና ዘርፉን ሰልጣኞች በክበቡ በአባልነት በመያዝ የክበቡን የስራ እንቅስቃሴ በሙዚቃ፤ ግጥምና ጭውውት በማስደገፍ የስነምግባርን አስተምህርቶችን ለሰልጣኙ በማድረስ የብልሹ አሰራርና የሙስና መገለጫዎችን እያዝናና በማሳወቅ ረገድ ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ለመረዳት ችለናል ፡፡

General Wingate Students Channel

30 Jan, 09:10


Equatorial business group ሠራተኛ ስለሚፈልግ
የአውቶሞቲቭ ተመራቂዎችና ስራ ፈላጊ ለሆናችሁ በሙሉ እስከ 23/05/2017 ዓ.ም ሳሪስ አካባቢ በመሄድ ከዊንጌት ነው የመጣን በማለት ማመልከት ትችላላችሁ፡፡

General Wingate Students Channel

30 Jan, 08:47


ማስታወቂያ
በአውቶ መካኒክ፣በማሽኒግ፣በመካኒክስና በኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ የሙያ ዘርፍ በጀኔራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2016 ዓ.ም ተመራቂዎች በሙሉ Dodai Manufacturing plc የሚባል ድርጅት ስለሚፈልግ ከ22/05/2017- 24/05/2017 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ CV አዘጋጅታችሁ በስለክ ቁጥር 0968895418 በቴሌግራም በመላክ ማመልከትና ለስራ መወዳደር ትችላላችሁ፡፡


ለተጨማሪ መረጃ ከላይ ያለውን የድርጅቱን ደብዳቤ ማየት ትችላልችሁ

General Wingate Students Channel

28 Jan, 08:52


https://youtube.com/@bequelmis?si=m8s6ztkc7RiFZ9kN

General Wingate Students Channel

28 Jan, 08:52


ብቁ ሰራተኛ • ብቁ ቀጣሪ • ብቁ ውሳኔ ሰጪ
https://t.me/bequelmis1

General Wingate Students Channel

28 Jan, 08:52


የጀኔራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝና ሰልጣኝ መረጃዎችን በኢትዮጵያ የስራ ገበያ መረጃ ስርዓት (LMIS) እንዲመዘግቡ በፌዴራል ስራና ክህሎት ቢሮ አቅጣጫ የተሰጠ ስለሆነ ሁሉም የጀኔራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሰልጣኞች ከዚህ በታች ያለውን ሊንክና ቪዲዮ በመጠቀም በእጅ ስልካችሁ ወይም ኮምፒዩተር ላይ ኦን ላይን ሞልታችሁ ባስገባችሁት ስልክ የሚደርሳችሁን መዕልክት ይዛችሁ ወደ አስተዳድር ህንፃ የስራ ትስሰር ቢሮ ቁጥር 02 በመምጣት አሻራ መስጠት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡





ማሳሰቢያ፡- ሁሉም ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሰልጣኞች መዝገብ ግድ ነው

General Wingate Students Channel

18 Jan, 17:44


ቅዳሜ:- ጥር 10 ቀን 2017 ዓ.ም
                                               
‹ያን ጊዜ ኢየሱስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከዮርዳኖስ ወደ ገሊላ መጣ፡፡›› ማቴ 3፥13

ለኮሌጃችን የክርስትና እምነት ተከታይ ሰራተኞች፣ ሰልጣኞች እና የተቋማችን አጋሮች በሙሉ እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት በሰላም አደረሳችሁ!!

በዓሉ የሰላም፣ የአንድነት፣ የዕድገት እና የፍቅር ይሆንላችሁ ዘንድ እንመኛለን። መልካም በዓል ይሁንላችሁ፡፡

 የጀነራል  ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ

General Wingate Students Channel

15 Jan, 15:15


ቀን 7/05/2017
የአራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ ከጄኔራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሰልጣኞች የስነምግባር ክበብ አባላት ጋር የልምድ ልውውጥ አካሄደ ፡፡
በልምድ ልውውጡም የተማሪዎች የስነምግባርና ጸረሙስና ክበብ አባላት በስነምግባር ግንባታና በሙስና መከላከል ዙሪያ ፤በዋናነት ያከናወኗቸውን ተግባራት ገለጻ አድርገዋል ፡፡
የክበቡ ሰብሳቢ ሰልጣኝ አብርሀም እሸቱ እንደገለጸው መልካም ስነምግባርን ለማዳበር የሚያስችሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን በሾፖች አካባቢ የሚታዩትን የንብረት ብክነትና ስርቆትን ለመከላከል ከተማሪ ካውንስሉ ጋር በቅንጅት እየሰሩ እንደሚገኙና በስልጠና ሰዓት ወደ ክፍል የማይገቡና የተለያየ ችግር ያለባቸውን ተማሪዎች ቢሮ ጠርቶ በማነጋገር ችግሮችን የመፍታት እንቅስቃሴ እያደረግ እንደሚገኝ እንዲሁም ከአቅም በላይ የሆኑ ጉዳዮች ሲገጥሙ ከስነምግባርና ጸረሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬትና ከስልጠናና አካዳሚክ ጉ/ም/ዲን ጋር በመነጋገር እየፈቱ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡
የአለም የጸረሙስና ቀንን የተማሪዎች ጥያቄና መልስ ውድድር በማዘጋጀት ተማሪዎችን ያወዳደሩ ሲሆን ለተወዳዳሪዎችም ኮሌጁ የእውቅና ሰርተፍኬት አዘጋጅቶ የሰጠ መሆኑን ገልፀው በወቅቱም የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችም እንደሰሩ ተናግረዋል ፡፡
የክበቡ የሴት ተማሪዎች ተወካይ ሰልጣኝ ዲቦራ ክፍሉ እንደገለጸችው በተማሪዎች የምዘና አወሳሰድ ላይ የነበረውን የተሳሳተ ግንዛቤ ከተማሪዎች ጋር ባላቸው የውይይት መድረክ የተቀረፈበትና ሰልጣኞች ለምዘናው ራሳቸውን በእውቀት ብቁ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው በነበራቸው የእርስ በርስ ግንኙነት የአመለካከት ለውጥ መምጣቱን ገልጻ ጾታዊ ጥቃትን ከመከላከል አንጻርም ከሴት ተማሪዎች ጋር በቅርበት እየሰራች እንደሆነ ገልጻ የተማሪዎች የስነምግባር ክበብ የጥቆማ መቀበያ ሳጥን መኖሩ ግቢው ውስጥ የሚታዩ ኢ ስነምግባራዊ ተግባራትንና ብልሹ አሰራርን ለመጠቆም በአካል ለመምጣት ለማይደፍሩ ሰልጣኞች አመቺ ሁኔታ እንደፈጠረ አስረተድታለች ፡፡
የአራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ ሰልጣኞችም የተለያዩ ጥያቄዎችን ያነሱና ምላሽ ያገኙ ሲሆን ክበቡ ሰፊ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመው ከኮሌጁ ያገኙትን ተሞክሮ ወደ ተቋማቸው በመውሰድ እንደሚሰሩበት በመግለጽ ለነበራቸው ቆይታ አመስግነዋል ፡፡

General Wingate Students Channel

02 Jan, 12:26


https://t.me/GWIPTC

የስነምግባር እና የፀረሙስና ዳይሬክቶሬት ቢሮ የቴሌግራም ቻናል

General Wingate Students Channel

27 Dec, 14:50


የስልጠና ማስታወቂያ
          
  ለ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን የቀረበ የስልጠና ገጸ በረከት 

አጠቃላይ ለኮሌጁ ማህበረሰብ እና ለማህበራዊ ሚዲያችን ተከታታዮች በሙሉ ይህን የኮደርስ ስልጠና መሳተፍ እንደምትችሉ እያሳወቅን የኮደርስ ኢኒሼቲቭ ስልጠናን ሲያጠናቅቁ ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው ሰርተፍኬት ባለቤት እንደሚሆኑም ስንነግሮት በሙሉ እምነት ነው::

ስልጠናው የሚሰጠው በኦን ላይን /online/ ሲሆን ስልጠናውን ለመከታተል ኢተርኔት ባለበት ቦታ በላፕቶብ ወይም በእጅ ስልክ /ሞባይል/ በመጠቀም መውሰድ እንደምትችሉ ስናበስር ለእናንተ ቅርብ ሆነን ነው፡፡

የሚሰጡ የስልጠና ዓይነቶች:-
1.ዌብ ፕሮግራሚንግ /web programming/
2.ሞባይል ፕሮግራሚንግ /Mobile programming/
3.ዳታ ሳይንስ /Data science/
4. ሰው ሰራሽ አስተውሎት / Artificial Intelligence/ or AI

ማሳሰቢያ:-  ኦንላይን ስትሞሉ Institution የሚለው ላይ General Wingate Polytechnic College ብላችሁ መሙላት ይጠበቅባችኋል።
ትምህርቱ እድሜ፣ ፆታ እናቦታ አይገድበውም:: 

    📍 በዚህ ሊንክ   https://ethiocoders.et/

መረጃው የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ሲሆን ለተጨማሪ ማብራሪያ የኮሌጁን አይሲቲ /ICT/ ዲፓርትመንት መጠየቅ ትችላላችሁ ተብላችኋል፡፡

General Wingate Students Channel

27 Dec, 13:45


General Wingate Students Channel pinned «የ5 ሚሊየን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ስልጠና ሲጠናቀቅ አለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው ሰርተፍኬት ያገኛሉ::ትምህርቱ የሚሰጠው በኦን ላይን ሲሆን ከርሰዎ የሚፈልገው ሞባይል ወይ ላፕቶፕ እና ኢንተርኔት ብቻ ነው ::ትምህርቱን በኢንተርኔት ከቤተዎ ሁነው መማር ይችላሉ:: የሚሰጡ ትምህርቶች:- 1.ዌብ ፕሮግራሚንግ 2.ሞባይል ፕሮግራሚንግ 3.ዳታ ሳይንስ 4. AI 📍 በዚህ ሊንክ https://ethiocoders.et/…»

General Wingate Students Channel

27 Dec, 10:27


የ5 ሚሊየን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ስልጠና ሲጠናቀቅ አለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው ሰርተፍኬት ያገኛሉ::ትምህርቱ የሚሰጠው በኦን ላይን ሲሆን ከርሰዎ የሚፈልገው ሞባይል ወይ ላፕቶፕ እና ኢንተርኔት ብቻ ነው ::ትምህርቱን በኢንተርኔት ከቤተዎ ሁነው መማር ይችላሉ::

የሚሰጡ ትምህርቶች:-
1.ዌብ ፕሮግራሚንግ
2.ሞባይል ፕሮግራሚንግ
3.ዳታ ሳይንስ
4. AI
📍 በዚህ ሊንክ https://ethiocoders.et/
በኦንላይን ተመዝግባችሁ የመረጣችሁትን ኮርሰ ዲፓርትመንት እና ሙሉ ስም @eliaz_hussien ላይ ላኩልን።

ማሳሰቢያ: ኦንላይን ስትሞሉ Institution የሚለው ላይ General Wingate Polytechnic College ብላችሁ መሙላት ይጠበቅባችኋል።

እንዲሁም ማንኛውም ጥያቄ ካላችሁ መጠየቅ ትችላላችሁ።

General Wingate Students Channel

25 Dec, 17:47


ማስታወቂያ የእግርኳስ ውድድሩን የተመዘገባቹ  በተወሰኑ ዲፓርትመንቶች መዘግየት ምክንያት ውድድሩ ለ ቀጣይ ማክሰኞ ተዘዋውሯል ።
ስም ዝርዝር ያስገባቹ ዲፓርትመንቶች በ አካውንት 1000667783554 የመወዳደሪያ ብሩን አስገቡ ።
የውድድሩ አሸናፊ  የተዘጋጀለትን የገንዘብ ሽልማት ይወስዳል። መልካም እድል ።

General Wingate Students Channel

25 Dec, 07:15


ማስታወቂያ

የእግርኳስ ውድድር ላይ የምትሳተፉ ዲፓርትመንቶች ክፍያውን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000667783554 Yisak Seifu & Elias Mulugeta & Dibora Kiflu በሚለው አካውንት ገንዘቡን በማስገባት ደረሰኝ እና መታወቂያ በመያዝ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን።

General Wingate Students Channel

24 Dec, 17:15


ሀሙስ በ17 / 04 / 2017 ዓ.ም የሚካሄድ የእግርኳስ ጨዋታ Electrical vs Finishing 01 ከ ቀኑ 6:00 በትልቁ ሜዳ ጨዋታቸውን ያካሄዳሉ።

General Wingate Students Channel

23 Dec, 17:04


የጀነራል ዊንጌት ኮሌጅ የዲፖርትመንት እግር ኳስ ውድድር ድልድል

1,rood construction vs aluminum 1

2,electrical vs aluminum 2

3,ict night vs marketing

4,wood work vs web design

5,auto electrical vs data base

6,finising vs drafting

ነገ ማለትም እለተ ማክሰኞ 15/4/2017
6 ሰአት
             rood construction

                          Vs
                    
                   Aluminum

General Wingate Students Channel

21 Dec, 17:59


ማሳሰቢያ
በሰልጣኞች ካውንስል የተዘጋጀው የዲፓርትመንቶች የእግርኳስ ጨዋታ ውድድር በቅርቡ የሚጀመር ስለሆነ ዲፓርትመንታችሁን ወክላችሁ የምትወዳደሩ ሰልጣኞች በሙሉ ስም ዝርዝራችሁን አስገቡ።
👉🏽ጥብቅ ማሳሰቢያ: ዲፓርትመንቱን ወክለው በውድድሩ ላይ መሳተፍ የሚችሉት በጀኔራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ውስጥ የሚሰለጥኑ ሰልጣኞች ብቻ ነው።

👉🏽ከኮሌጁ ሰልጣኞች ውጪ በውድድሩ ላይ ሌላ ተጫዋች ማሳተፍ በጥብቅ የተከለከለ ነው። ሙሉ ለሙሉ ከውድድሩ ውጪ ይሆናሉ።
👉🏽ስትመዘገቡ ህጋዊ የሆነ የኮሌጁ መታወቂያ መያዛችሁን አትርሱ።
ጥያቄ ካላችሁ 0961358978 በመደወል መጠየቅ ትችላላችሁ።

የስፖርት ዘርፍ ተጠሪ

General Wingate Students Channel

20 Dec, 17:49


በድጋሚ የወጣ ማስታወቂያ

ውድ የጀነራል ዌንጌት ሰልጣኞች እንዲሁም የሚኒሚዲያ አባላት  አጠቃላይ ትውውቅ እና ልምምድ የተጀመረ ስለሆነ በ ሙዚቃ ,በስነ ፅሁፍ እንዲሁም ተያያዥ ዘርፎች የተመዘገባቹ ወይም አዲስ መመዝገብ እና አብራቹን መስራት የምትፈልጉ በሙሉ ሰኞ 14/4/2017 ዓ.ም ከቀኑ 7:00 ሠአት ላይ ከተማሪዎች ካፌ በላይ በሚገኘው አዳራሽ በመገኘት መሳተፍ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።

የኮሚኒኬሽን ዘርፍ ተጠሪ

General Wingate Students Channel

19 Dec, 18:14


ውድ የጀነራል ዌንጌት ሰልጣኝ እንዲሁም የሚኒሚዲያ አባላት  አጠቃላይ ትውውቅ እና ልምምድ ስለምንጀምር በ ሙዚቃ ,በስነ ፅሁፍ እና ተያያዥ ዘርፎች የተመዘገባቹ እንዲሁም አዲስ መመዝገብ እና አብራቹን መስራት የምትፈልጉ ነገ ማለትም አርብ 11/4/2017 ዓ.ም ከቀኑ 7:00 ሠአት ከተማሪዎች ካፌ በላይ በሚገኘው አዳራሽ በመገኘት መሳተፍ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።

General Wingate Students Channel

19 Dec, 17:20


ሰላም የጀነራል ዊንጌት ሰልጣኝ ተማሪዎች የእግር ኳስ ውድድር ሊደመር ስለሆነ ስም ዝርዝር ያላስገባቹ ዲፓርትመንቶች እስክ እሁድ ማለትም 13/04/17 ድረስ አጠናቃቹ የውድድሩ ተካፋይ እንድትሆኑ እንገልፃለን ።
ለበለጠ መረጃ :- 0961358978

General Wingate Students Channel

14 Dec, 04:45


አርብ:- ታህሳስ  4 ቀን 2017 ዓ∙ም

ፋዊ ድጋፍ ለሚያደርግላቸው ሰልጣኞችና ቤተሰቦቻቸው ስለ ፕሮግራሙ በኮሌጁ ገለፃ ሰጠ!!

የአፍሪካ ሴት የትምህርት ባለሙያዎች ፎረም /FAWE/ ከማስተር ካርድ ፋውንደሽን ጋር በመተባበር የትምህርትና ስልጠና ድጋፍ ለሚያደርግላቸው ሰልጣኞችና ቤተሰቦቻቸው ስለፕሮግራሙ ይዘት ግንዛቤ ሰጠ።

በዕለቱ የፋዊ ኢትዮጵያ ስራ አስኪያጅ እና የቦርድ ሰብሳቢ፣ የድርጅቱ ሰራተኞች፣ የኮሌጁ አመራሮችና ሰራተኞች ተገኝተዋል።

ፋዌ ኢትዮጵያ ቻፕተር እና ፋዌ አፍሪካ ከማስተር ካርድ ፋውንደሽን ጋር በመተባበር የሃርድ ስኪል ስልጠና ለሚከታተሉ ሰልጣኞች የትምህርትና ስልጠና ድጋፍ ፕሮግራም ተጠቃሚ እንዲትሆኑ አድርጓል፡፡

እንደ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፕሮጀክቱ የሚተገበርባቸው ጀነራል ዊንጌት እና አዲስ አበባ ተግባረ ዕድ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጆች ሲሆኑ በሁለቱ ተቋማት እየሰለጠኑ ለሚገኙ ሰልጣኞች ስለ ድርጅቱ ምንነት፣ የሚሰጣቸው ድጋፍ ዓይነቶች እና ከሰልጣኞችና ቤተሰቦቻቸው የሚጠበቅ ትጋት ምን እንደሆነ በመድረኩ ተገልጿል።

ፋዊ በምዕራፍ ሁለት ፕሮግራሙ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና /TVET/ ላይ ትኩረት አድርጎ ከ15 - 25 የዕድሜ  ክልል የሚገኙ ወጣቶችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው።

ፕሮግራሙ 80 ከመቶ ሴቶችን ተጠቃሚ ያደረገ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ ከ5 እስከ 10 ፐርሰንት ለአካል ጉዳተኛ ከ10 እስከ 15 ፐርሰንቱ ደግሞ ለሀገር ውስጥ ተፈናቃይ ዜጎች ዕድል መስጠቱ ታውቋል፡፡

General Wingate Students Channel

06 Dec, 15:45


አርብ፡- ህዳር 27 ቀን 2017 ዓ.ም

#ኮሌጁ_በ13ኛው_ዓለም_አቀፍ_የጥራት_ቀን_ኤግዚቢሽን_ላይ_ተሳተፈ!!                         

ኮሌጁ ለ13ኛ ጊዜ የሚከበረውን ዓለም አቀፍ የጥራት ቀን ምክንያት በማድረግ መገናኛ አምቼ አካባቢ በሚገኘው የጥራት መንደር ግቢ ውስጥ ኤግዚቢሽን ላይ  እየተሳተፈ ይገኛል።

በኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የምርት ጥራት እና የሥራ አመራር ሥርዓት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት የተሰጣቸው የግልና የመንግስት ድርጅቶች በተሳተፉበት ዓለም አቀፉ የጥራት ቀን ላይ የጀነራል ዊንጌት  ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅም የሚሰጠውን አገልግሎት በኤግዚቢሽኑ ላይ እያስተዋወቀ ይገኛል።

ኮሌጁ በጥራት መንደር ኢግዚቢሽን ላይ መገኘቱ ኢግዚቢሽኑ ላይ የሚሳተፉ ድርጅቶች እና ጎብኝዎች አብረውት እንዲሰሩ የመተዋወቅ ዕድል ይፈጥርለታል ተብሏል።

ኤግዚቢሽኑ “ጥራት፡ መስፈርቶችን ከማሟላት ወደ ላቀ የአፈጻጸም ብቃት” በሚል መሪ ቃል በኢትዮጵያ ለ13ኛ ጊዜ እየተከበረ ነው።

በኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የምርት ጥራት እና የሥራ አመራር ሥርዓት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ያገኙ ድርጅቶች የሚሳተፉበት ይህ ኤግዚቢሽን ዛሬ ሁለተኛ ቀኑን ያስቆጠረ ሲሆን ከህዳር 26-28/2017 ዓ.ም ለሦስት ተከታታይ ቀናት እንደሚከበር ታውቋል።

"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"

General Wingate Students Channel

06 Dec, 04:04


ሐሙስ፡- ህዳር 26 ቀን 2017 ዓ.ም

#የብሔር_ብሔረሰቦች_ቀን_በኮሌጁ_ተከበረ!!

19ኛው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን ሀገራዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አንድነት በሚል መሪ ቃል በኮሌጁ ተከበረ።

የኮሌጁ ሰራተኞች እና ሰልጣኞች በተገኙበት 19ኛው የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዛሬው ዕለት በኮሌጁ በድምቀት የተከበረ ሲሆን በመድረኩ ላይ ልዩ ልዩ አዝናኝ እና አስተማሪ ይዘት ያላቸው ዝግጅቶች ቀርበዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ ስለሕብረ ብሔራዊ ሥርዓታችንና እያጋጠሙት ስላሉት ተግዳሮቶች እንዲሁም የመፍትሔ ሀሳቦች የተካተቱበት ሰነድ የቀረበ ሲሆን ዓላማውም አገራዊ መግባባትን በመፍጠር ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን ለማጠናከር ታቅዶ መሆኑን ሰምተናል።

ከዚህ ባሻገር ስነ ጽሑፍና ሙዚቃ በሰልጣኞች እንዲሁም የሰርከስ ትርኢት በሰርከስ ዊንጌት አባላት ቀርቧል።

የበዓሉ ዝግጅት በድምቀት እንዲከበር በማድረግ ረገድ የኮሌጁ የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት እና የሰልጣኞች መማክርት የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳሉ።  

"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"

General Wingate Students Channel

02 Dec, 15:45


ሰኞ፡- ህዳር 23 ቀን 2017 ዓ.ም

        በኮሌጁ የፀረ  ሙስና ቀን ተከበረ!!

ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን ምክኒያት በማድረግ እንደ ተቋም ዛሬ ህዳር 23 ቀን 2017 ዓ.ም በኮሌጁ የፀረ ሙስና ቀን ተከበረ፡፡

በዓለም ለ21ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ20ኛ ጊዜ እየተከበረ የሚገኘውን የፀረ ሙስና ቀን በኮሌጁ የስነምግባር እና ፀረ ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት አስተባባሪነት "ወጣቶቸ" በሚል መሪ ቃል የኮሌጁ ሰራተኞች በተገኙበት ተከብሯል።

በዓሉ በፀረ ሙስና ትግሉ እየተሰሩ ያሉ ተግባራትን ለማስቀጠል፣ የትውልድ ስነ ምግባር ግንባታን ለማጠናከር፣ የፀረ ሙስና ትግሉን ህዝባዊ መሰረት በማስያዝ የጋራ ግንዛቤ ለመፍጠር እና መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ታቅዶ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ሙስና በስነ ምግባር ውድቀት፣ በቢሮክራሲ መብዛት፣ በተጠያቂነት መጓደል፣ በዜጎች ሁለንተናዊ ተሳትፎ ማነስ፣ ባልተማከለ የአሰራር ስርዓት እና መሰል መንስኤዎች የሚከሰት ሲሆን አፈፃፀሙ በጊዜ ሂደት እየሰፋ እና እየረቀቀ በመምጣቱ የሀገርን ሀብት ከዚህ አስከፊ ጥፋት ለመታደግ ሁሉም አካላት ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል ተብሏል፡፡

   "በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"

General Wingate Students Channel

02 Dec, 04:08


ማስታወቂያ ለኮሌጁ ሰልጣኞች
ኮሌጁ በሚያዘጋጀው እንዲሁም በሚሳተፍበት ፕሮግራሞች ላይ በሞዴሊንግ ዘርፍ ለመሳተፍ የተመዘገባችሁ በሙሉ ዛሬ ከሰዓት አጠቃላይ ገለፃ ስለሚሰጥ የተመዘገባችሁ በሙሉ ከሰዓት እንድትገኙ እናሳስባለን።


Announcement
Attention all models who have registered to participate in the college's upcoming programs! There will be a general briefing this afternoon for all registered models. Please make sure to attend.

General Wingate Students Channel

25 Nov, 11:59


ማስታወቂያ

የጀነራል ዊንጌት ሰልጣኞች በሙሉ በሰልጣኝ ካውንስል በስፖርት ክበብ አማካኝነት ከዚህ ቀደም እንደሚደረገው የዲፓርትመንት የእግርኳስ ውድድር በቅርቡ ይካሄዳል ስለሆነም በውድድሩ ላይ የምትሳተፉ ዲፓርትመንቶች የሰልጣኝ ካውንስል ቢሮ በአካል በመምጣት ስም ዝርዝራችሁን ማስገባት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
ማሳሰቢያ : ውድድሩ ነባር እና አዲስ ሰልጣኞችን ያካትታል።


የሰልጣኝ ካውንስል ቢሮ

General Wingate Students Channel

25 Nov, 06:03


ያለፈው ሳምንት ሲካሄድ የነበረው በአብዛኞቻችሁ ጥያቄ መሰረት በዚህ ሳምንት ከሰኞ እስከ አርብ ከ3:00 - 6:00 ድረስ በቤተመጻሕፍት በመገኘት የእድሉ ተጠቃሚ መሆን ትችላላችሁ።

General Wingate Students Channel

23 Nov, 08:28


ለኮሌጁ ሰልጣኞች

በኮሌጁ ግቢ ውስጥ የብሔራዊ መታወቅያ ምዝገባ እየተከናወነ ስለሆነ በፍጥነት በመመዝገብ የእድሉ  ተጠቃሚ እንድትሆኑ እናሳውቃለን።

ቦታ በኮሌጁ ግቢ ፔፕሲ ሱቅ አጠገብ።

General Wingate Students Channel

21 Nov, 17:54


ማስታወሻ
Aladi's Collection ከ General Wingate Polytechnic College Student Council ጋር በጋራ በመተባበር ለተከታታይ ሁለት ቀን ማንኛውንም አይነት የፈለጋችሁትን መፃሀፍቶች በኮሌጁ ላይብረሪ በመምጣት መቀየር እንደምትችሉ ገልፀን ነበር ፤ሆኖም በእነዚህ ሁለት ቀን መጥታችሁ መቀየር ያልቻላችሁ ነገ አርብ 13/03/2017 ዓ.ም በኮሌጁ ላይብረሪ በመገኘት የምትፈልጉትን አይነት መፅሀፍት መለወጥ እንደምትችሉ ለመግለፅ እንወዳለን።
ቦታ - የኮሌጁ ቤተ መፅሀፍት
ሰዓት - ከ3:00 -11:00 ድረስ

General Wingate Students Channel

19 Nov, 18:29


ለመፅሃፍት አንባቢያን በሙሉ

Aladi's Collection ከ General Wingate Polytechnic College Student Council ጋር በመተባበር ለመፅሀፍ አንባቢ ወዳጆች አዲስ ነገር ይዞ መጥቷል ። ከነገ ዕሮብ ህዳር 11 /2017ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ ሶስት ቀን እስከ አርብ 13/2017ዓ.ም ድረስ ከ3:00 ጀምሮ ያነበባችሁት እጃችሁ ላይ ያሉትን መፅሀፎች ይዛችሁ በመምጣት በምትኩ ማንበብ የፈለጋችሁትን ማንኛውንም መፅሀፍ መቀየር እንደምትችሉ ስንገልፅ በደስታ ነው።

👉 ከእናንተ የሚጠበቀው የምትቀይሩት መፅሀፍ የፊት ገፁ ያልተቀደደ እንዲሁም በውስጡ ያሉት ገፆች ያልጎደሉ ሙሉ መሆን አለባቸው።
👉 ከ ፖለቲካ ሀይማኖት እንዲሁም የትምህርት መፅሀፎች በስተቀር ሁሉንም አይነት የመፅሀፍ ዘውጎች ያካተተ ስለሆነ በፈለጋችሁት አይነት መቀየር ትችላላችሁ ።
📍ቦታ የኮሌጁ ላይብረሪ ውስጥ ከ 3:00 ጀምሮ

©️GWPTC Student Council

General Wingate Students Channel

19 Nov, 18:17


ICT night class.pdf

General Wingate Students Channel

18 Nov, 09:58


Do you like reading books? 📚📖📙

We invite you to bring your gently used books and exchange them for any books from Aladi's collection. This is a wonderful opportunity to refresh your personal library while sharing reading materials with others.
@addisamcenter                           register to attend: https://forms.gle/oDvSbGcESg6Jo61d8

General Wingate Students Channel

15 Nov, 15:02


ለሁሉም የቀን አዲስ ገቢ ሰልጣኞች

ከ16/03/2017 ዓ.ም ጀምሮ የስልጠና ልብስ(ጋወንና ቱታ) ሳይለብሱ ወደ ግቢም ሆነ ወደ ስልጠና ክፍል መግባት የማይቻል መሆኑን አውቃችሁ ከላይ በተገለፀው መሰረት አዘጋጅታችሁ በመልበስ የምትመጡ መሆኑን አውቃችሁ ከወዲሁ እንድትዘጋጁ እናሳውቃለን።

ኮሌጁ

General Wingate Students Channel

12 Nov, 10:13


የቀን ስልጠና ሚጀምረው

ረቡዕ 04/03/2017 ዓ.ም ጠዋት 2:45
መቅረት ፈፅሞ የተከለከለ ነው።

ኮሌጁ

General Wingate Students Channel

10 Nov, 10:09


ማስታወሻ
ነገ ማለትም ሰኞ 02/03/2017 ጋቢ Day ስለሚከበር ሁላችሁም ጋቢ ይዛችሁ በመምጣት የፕሮግራሙ ተሳታፊ መሆን ትችላላችሁ ።
ሰዓት ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በዕለቱ ዲኖች የአስተዳደር ሰራተኞች እንዲሁም የ2017ዓ.ም አዲስ ገቢ ሰልጣኞች ይገኙበታል።

General Wingate Students Channel

07 Nov, 09:54


📍Postponed
ነገ ሊካሄድ የነበረው የጋቢ ደይ በተለያዩ ምክኒያቶች ወደ ሰኞ ህዳር 2 / 2017 ዓ.ም ተዘዋውሯል።

General Wingate Students Channel

04 Nov, 17:21


    ከ3ሺ 300 በላይ አዳዲስ ሰልጣኞች በ2 ሳምንት ተመዘገቡ!!👏🏼👏🏼

ኮሌጁ የ2017 ዓ.ም አዳዲስ ሰልጣኞችን  ከጥቅም 15 ቀን 2017 ዓ∙ም ጀምሮ በበየነ መረብ /online/  እና በሀርድ ኮፒ ለ2 ሳምንታት የመዘገበ ሲሆን በዚህም 3365 የሚሆኑ አዳዲስ ሰልጣኞችን መዝግቧል።

ኮሌጁ አሁን ላይ በISO 9001:2015 የጥራት ማናጅመንት ስርዓት ሰርቲፋይድ መሆኑ፤ የስልጠና ጥራቱን ለማሳደግ ከግዙፍ አገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር በትብብር መስራቱ  እና ባለው ተቋማዊ ዘርፈ ብዙ ፋሲሊቲዎች ለስልጠና ጥራቱ ትኩረት መስጠቱ ተመራጭነቱን ይበልጥ ስላሰፋው ከፍተኛ ተመዝጋቢ ካላቸው የመዲናችን ቴክኒክና ሙያ ተቋማት ውስጥ ከመጀመሪያዎቹ ተርታ ይሰለፋል።

ውድ አዳዲስ ተመዝጋቢዎች! በመሉ እምነት እኛን ተማምናችሁ መርጣችሁን ስለመጣችሁ እናመሰግናለን።

የምዝገባ ቀናትን በተመከለተ ምንም እንኳን እስከ ጥቅምት 25 ቀን 2017 ዓ.ም ለማጠናቀቅ ቢታቀድም በተለያየ ምክኒያት ምዝገባቸውን ላላጠናቀቁ አመልካቾች ተጨማሪ 4 ቀናት ዕድል ተመቻችቷል።                                                    
ስለሆነም እስከ ጥቅምት 29 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ባሉት ቀናት ባሉበት ሆነው በበየነ መረብ /online/ ወይም በኮሌጁ በአካል በመገኘት መመዝገብ የሚችሉ መሆኑን ስናበስርዎት በታላቅ ደስታ ነው።      

የሙያ ምርጫን በተመለከተ በማታና በቅዳሜና እሁድ ለምትሰለጥኑ በፍላጎታችሁ የምትስተናገዱ ሲሆን ለቀን አመልካቾች ደግሞ ከቢዝነስ፣ ከአይሲቲ፣ ከአውቶሞቲቭ እና ከፉሽን ዲዛይን ዲፓርትመንቶች ውጪ ባሉ ሙያዎች እንደ ምርጫችሁ ትስተናገዳላችሁ።  

ስለሆነም በተቀመጡበት ቀሪ ቀናት ፈጥነው እንዲመዘገቡ እየሞከርን ከዚያ በኋላ የመመዝገቢያ ሰንደቁ /ሊንኩ/ የሚዘጋ መሆኑን እንገልፃለን።

   "በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"

General Wingate Students Channel

04 Nov, 12:41


ልዩ የትምህርት  ድጋፍ እድል ከፋዌ ኢትዮጵያ !

ፋዌ ኢትዮጵያ ከማስተርካርድ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር እድሚያቸው ከ 15 እስክ 25 የሆኑ ወጣቶችን በተለይም በዝቅተኛ ኢኮኖሚያዊ ደረጃ የሚገኙ ሴት እና የአካል ጉዳተኛ ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የከፍተኛ የትምህርት እድል ተጠቃሚ እንድትሆኑ ሲጋብዝ ታላቅ ደስታ ይሰማዋል፡፡

ድጋፉ ሁሉን አቀፍ የገንዘብ፣የትምህርትና ስልጠና እንዲሁም የማህበራዊ ድጋፍን የሚያካትት ሲሆን የትምህርት ድጋፉ የሚሰጠው በቴክኒክና ሙያ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ በሚሰጡ የሳይንስ፣ቴክኖሎጂ፣ምህንድስናና ተዛማጅ የትምህርት ዘርፎች/STEM/ኮርሶች ነው፡፡

ምዝገባው የሚካሄደው በአዲስ አበባ  ከተማ  በጄኔራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ እና አዲስ አበባ ተግባረ እድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች፣ አዳማ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ፣  ሀዋሳ ፖሊ ቴክኒክና ሀዋሳ ተግባረ እድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች እንዲሁም በባህርዳር ፖሊ ቴከኒክ ኮሌጅ በሚሰጡት የመደበኛ የትምህርትና ስልጠና መርሃግብሮች ሲሆን አመልካቾች በ2014፣2015 ወይም 2016ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና የወሰዱ እና የ2017ዓ.ም የቴክኒክና ሙያ መግቢያ ውጤት የሚያሟሉ መሆን አለባቸው፡፡

የማመልከቻ ቀናት ከጥቅምት 22-29/2017 ዓ.ም ባሉት የስራ ቀናት ብቻ ይሆናል፡፡ 
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥሮች
አዲስ አበባ በ 0911330024 / 0902662688
አዳማ  በ 0911383055
ባህርዳር በ 0913042043
ሀዋሳ በ 0965679139 በመደወል ወይም በድረ፟ገጻችንwww.faweethiopia.org ይጎብኙ፡፡
ሴቶችን ማስተማር ህብረተሰብን ማስተማር ነው!

ምዝግባዉም ሆነ የመረጣው ሂደተ ከማንኛዉም ክፍያ ነጻ መሆኑን እናሳዉቃልን

General Wingate Students Channel

04 Nov, 04:52


https://youtu.be/ods9Sms7HkE

General Wingate Students Channel

03 Nov, 04:52


የ2017 ዓ.ም የመጀመሪያው ደይ የጋቢ ደይ አርብ በ29 / 02 /2017 ይካሄዳል🎉
ፕሮግራሙ ጠዋት እንዲሁም ከሰዓት ይከበራል። ከእናንተ የሚጠበቀው ጋቢ ይዞ መምጣት ብቻ ነው። ማንም ሰው እንዳይቀር 🔥🔥

General Wingate Students Channel

02 Nov, 06:36


General Wingate Students Channel pinned «ፕሮግራሙ ሙሉ በሙሉ የግቢው ማህበረሰብ የሚሳተፍበት ነው ። ስለዚህ የእናንተን እገዛ እንፈልጋለን በፕሮግራሙ ላይ ምን አይነት ዝግጅቶች እንዲኖሩ የምትፈልጉ ሀሳባችሁን በ @eliaz_hussien ላይ ገብታችሁ መናገር ትችላላችሁ ። መልካም ቀን🎉»

General Wingate Students Channel

02 Nov, 06:12


ፕሮግራሙ ሙሉ በሙሉ የግቢው ማህበረሰብ የሚሳተፍበት ነው ። ስለዚህ የእናንተን እገዛ እንፈልጋለን በፕሮግራሙ ላይ ምን አይነት ዝግጅቶች እንዲኖሩ የምትፈልጉ ሀሳባችሁን በ @eliaz_hussien ላይ ገብታችሁ መናገር ትችላላችሁ ። መልካም ቀን🎉

General Wingate Students Channel

02 Nov, 06:07


Something exciting is coming your way! 👀

Get ready for Gabi Day, a fun-filled event you won't want to miss.

Stay tuned🎉🎉

General Wingate Students Channel

01 Nov, 18:02


Get ready for an unforgettable start to 2017! 🎉

General Wingate Students Channel

01 Nov, 14:13


https://gwptc.aatvetb.edu.et/

General Wingate Students Channel

01 Nov, 05:45


ማሳሰቢያ

በ2016ዓ.ም ተመርቃችሁ የሶፍት ስኪል ስልጠና የወሰዳችሁ ዛሬ በ22/02/2017 4:00 የሰልጣኞች ኳውንስል በመገኘት ሰርተፊኬት እንድትወስዱ እናሳስባለን።

መታወቂያ መያዝ እንዳትረሱ

General Wingate Students Channel

31 Oct, 17:34


General Wingate Students Channel pinned «ማስታወቂያ ለ2016ዓ.ም ተመራቂ ሰልጣኞች የሶፍት ስኪል ስልጠና ወስዳችሁ የነበረ ተመራቂዎች ነገ ቀን 22/02/2017ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00 በሰልጣኝ ካውንስል ቢሮ ራሳችሁን የሚገልፅ መታወቂያ ይዛችሁ በመገኘት ሰርተፊኬት እና አበላችሁን እንድትወስዱ እናሳስባለን። ከነገ በኋላ ለሚመጣ ሰልጣኝ ሀላፊነቱን አንወስድም።»

General Wingate Students Channel

31 Oct, 17:03


ሐሙስ:- ጥቅምት 21 ቀን 2017 ዓ∙ም

   በኮሌጃችን ሌላም አዲስ የምስራች ይዘን መጥተናል!!

ፋዌ ኢትዮጵያ ቻፕተር እና ፋዌ አፍሪካ ከማስተር ካርድ ፋውንደሽን ጋር በመተባበር በ2017 ዓ.ም ሃርድ ስኪል ስልጠና ላይ ለመከታተል ለተመዘገባችሁ አዳዲስ ሰልጣኞች የትምህርትና ስልጠና ድጋፍ ፕሮግራም ተጠቃሚ እንዲትሆኑ ጥሪ ቀርቦላችኋል፡፡

እንደ አዲስ አበባ የዕድሉ ተጠቃሚ ከሆኑ 2 ፖሊ ኮሌጆች መካከል ጀነራል ዊንጌት አንዱ ሲሆን ከፍተኛውን ዕድል ለሴቶች አድርጎ የሚተገበር ነው፡፡

ስለሆነም ከ15 እስከ 25 ዕድሜ የሆናችሁ፣ የስልጠና መግቢያውን መስፈርት የምታሟሉ፣ ሃርድ ስኪል ስልጠና ላይ ያመለከታችሁ ተጠቃሚዎች መሆን የምትችሉ ሲሆን የተጠቃሚዎች ስብጥር ደግሞ 80 ከመቶ ለሴቶች 20 ፐርሰንት ለወንዶች ይሆናል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ ከ5 እስከ 10 ፐርሰንት ለአካል ጉዳተኛ ከ10 እስከ 15 ፐርሰንቱ ደግሞ ለተፈናቃይ መሆኑ ታውቋል፡፡

የማመልከቻ ጊዜ ከጥቅምት 22 እስከ ጥቅምት 29 ቀን 2017 ዓ.ም ሲሆን ለተጨማሪ መረጃ 0911330024 ወይም 0902662688 መደወል ትችላላችሁ ተብላችኋል፡፡  

የድጋፉ ተጠቃሚ አካል ለመሆን መስፈርቱን የምታሟሉ አዳዲስ ሰልጣኞች በኮሌጁ አስተዳደር ህንፃ ግሪውንድ ላይ የስልጠና እና አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ዲን ቢሮ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ማመልከት እንደምትችሉ ተነግሯል።

"በላቀ አግልግሎት የመረጃ ተደራሽነት"

General Wingate Students Channel

31 Oct, 14:52


ማስታወቂያ ለ2016ዓ.ም ተመራቂ ሰልጣኞች

የሶፍት ስኪል ስልጠና ወስዳችሁ የነበረ ተመራቂዎች ነገ ቀን 22/02/2017ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00 በሰልጣኝ ካውንስል ቢሮ ራሳችሁን የሚገልፅ መታወቂያ ይዛችሁ በመገኘት ሰርተፊኬት እና አበላችሁን እንድትወስዱ እናሳስባለን። ከነገ በኋላ ለሚመጣ ሰልጣኝ ሀላፊነቱን አንወስድም።

General Wingate Students Channel

30 Oct, 12:42


Further information contact us @eliaz_hussien

General Wingate Students Channel

28 Oct, 12:51


Happening Now


በኦንላይን ምዝገባው ያልተመዘገባችሁ ሰልጣኞች ኮሌጁ ግቢ በመምጣት መመዝገብ ትችላላችሁ

General Wingate Students Channel

26 Oct, 07:19


ያልተፈተናቹትን ትምህር ኦንላየን ስትሞሉ 0(ዜሮ) ብላቹ ሙሉ

General Wingate Students Channel

24 Oct, 15:49


የኦንላይን የምዝገባ ሊንክ

https://gwptc.aatvetb.edu.et/

General Wingate Students Channel

21 Oct, 16:41


ማንኛውም ከአዲስ ምዝገባ ጋር የተያያዙ ጥያቄዎች ካላችሁ በዚህ ሊንክ በመግባት መጠየቅ ትችላላችሁ።

General Wingate Students Channel

21 Oct, 16:39


https://vm.tiktok.com/ZMha4un9W/

General Wingate Students Channel

21 Oct, 10:52


የ2017 የቴክኒክና ሙያ የመደበኛ ስልጠና ዘመን መቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆኗል።

የተፈጥሮ ሳይንስ የመግቢያ ውጤት !

🟢 የስልጠና ደረጃ 1 እና 2

° ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን
#ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 141 እና ከዚያ በታች፤

° ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 137 እና ከዚያ በታች፤

° ሴቶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን
#ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 138 እና ከዚያ በታች፤

° ሴቶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 134 እና ከዚያ በታች፤

° ለሁሉም የአካል ጉዳተኞ የመቁረጫ ነጥቡ 124 እና ከዚያ በታች፤

🟡 የስልጠና ደረጀ 3 እና 4 ፦

° ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን
#ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 142 እና ከዚያ በላይ፤

° ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 138 እና ከዚያ በላይ፤

° ሴቶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን
#ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 139 እና እና ከዚያ በላይ፤

° ሴቶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 135 እና ከዚያ በላይ፤

° ለሁሉም የአካል ጉዳተኞ የመቁረጫ ነጥቡ 125 እና ከዚያ በላይ፤

🔴 የስልጠና ደረጀ 5 ፦

° ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን
#ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 179 እና ከዚያ በላይ፤

° ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 167 እና ከዚያ በላይ፤

° ሴቶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን
#ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 170 እና እና ከዚያ በላይ፤

° ሴቶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 162 እና ከዚያ በላይ፤

° ለሁሉም የአካል ጉዳተኞ የመቁረጫ ነጥቡ 154 እና ከዚያ በላይ፤

⬇️

የማህበራዊ ሳይንስ የመግቢያ ውጤት !

🟢 የስልጠና ደረጃ 1 እና 2

° ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን
#ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 139 ከዚያ በታች፤

° ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 135 እና ከዚያ በታች፤

° ሴቶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን
#ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 134 እና ከዚያ በታች፤

° ሴቶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 124 እና ከዚያ በታች፤

° ለሁሉም የአካል ጉዳተኞ የመቁረጫ ነጥቡ 124 እና ከዚያ በታች፤

🟡 የስልጠና ደረጀ 3 እና 4 ፦

° ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን
#ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 140 ከዚያ በላይ፤

° ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 136 እና ከዚያ በላይ፤

° ሴቶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን
#ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 135 እና እና ከዚያ በላይ፤

° ሴቶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 125 እና ከዚያ በላይ፤

° ለሁሉም የአካል ጉዳተኞ የመቁረጫ ነጥቡ 125 እና ከዚያ በላይ፤

🔴 የስልጠና ደረጀ 5 ፦

° ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን
#ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 172 ከዚያ በላይ፤

° ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 164 እና ከዚያ በላይ፤

° ሴቶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን
#ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 165 እና እና ከዚያ በላይ፤

° ሴቶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 160 እና ከዚያ በላይ፤

° ለሁሉም የአካል ጉዳተኞ የመቁረጫ ነጥቡ 154 እና ከዚያ በላይ፤

General Wingate Students Channel

21 Oct, 09:57


የ2017 የቴክኒክና ሙያ ስልጠና መርሃ ግብር የመግቢያ መቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ

General Wingate Students Channel

15 Oct, 06:45


Happening Now

General Wingate Students Channel

15 Oct, 05:07


ማስታወሻ ለተመራቂ ሰልጣኞች

ዛሬ የሚጀመረው የሶፍት ስኪል ስልጠና በአሮጌው አዳራሽ ነው የሚካሄደው ስልጠናው ከጠዋቱ 2:30 ስለሚጀመር በሰዓቱ እንድትገኙ አሰናሳስባለን።

General Wingate Students Channel

14 Oct, 14:04


Two days training content focused on the above titles

General Wingate Students Channel

14 Oct, 14:04


Are you planning to attend the biggest job fair of the year?

If you’re a 2023/2024 graduate, you’re in luck!

Why? Because with our ESJR training, you’ll be one step closer to being fully prepared for the National Career Expo!

Here’s what you’ll get with our ESJR Training:
🚀 Self-awareness
🎯 Employability skills
🕵️‍♂️ Understanding of the job market
🔍 The job searching process
📝 Job fair clinic

Don’t just show up—stand out!

Get prepped, get noticed, and get hired!

General Wingate Students Channel

10 Oct, 18:56


General Wingate Students Channel pinned «ማስታወቂያ የ2016 ዓ.ም ተመራቂ ሰልጣኞች በሙሉ ጥቅምት 05/02/2017 እና 06/02/2017 ዓ.ም ማለትም የፊታችን ማክሰኞና ረዕቡ የሶፍት ስኪል ስልጠና በጀኔራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አሮጌው አዳራሽ ከጥዋቱ 2:30 ስዓት ጀምሮ ለሁለት ተከታታይ ቀናት ኢንፎማይንድ ሶልሽን በተባለ ድርጅት ይሰጣል በተጠቀሰው ቀንና ስዓት በመገኘት መሳተፍ ትችላላችሁ። ማሳሰቢያ:_1. ስልጠናው የሙሉ ቀን…»

General Wingate Students Channel

10 Oct, 16:14


📌Notice

General Wingate Students Channel

09 Oct, 15:59


ማስታወቂያ
የ2016 ዓ.ም ተመራቂ ሰልጣኞች በሙሉ ጥቅምት 05/02/2017 እና 06/02/2017 ዓ.ም ማለትም የፊታችን ማክሰኞና ረዕቡ የሶፍት ስኪል ስልጠና በጀኔራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አሮጌው አዳራሽ ከጥዋቱ 2:30 ስዓት ጀምሮ ለሁለት ተከታታይ ቀናት ኢንፎማይንድ ሶልሽን በተባለ ድርጅት ይሰጣል በተጠቀሰው ቀንና ስዓት በመገኘት መሳተፍ ትችላላችሁ።
ማሳሰቢያ:_1. ስልጠናው የሙሉ ቀን ስልጠና ነው።
2. የሁለቱንም ቀን ስልጠና የተከታተለ ሰርተፊኬት ያገኛል።
3. የትራንስፖርት አበል አለው።

General Wingate Students Channel

08 Oct, 09:03


ማሳሰቢያ
መፅሄት ያልወሰዳችሁ ሰልጣኞች በዚህ ሳምንት መጥታችሁ እንድትወስዱ። ከዛ በኋላ ለሚመጣ ሀላፊነቱን አንወስድም።

General Wingate Students Channel

01 Oct, 08:28


መፅሄት ያልወሰዳችሁ ሰልጣኞች የአስተዳደር ህንፃ ላይ ቢሮ ቁጥር 2 ደረሰኝ ይዛችሁ በመምጣት እንድትወስዱ

General Wingate Students Channel

30 Sep, 17:19


ማስታወቂያ

ለ2016ዓ.ም የመፅሔት የከፈላችሁ ተመራቂ ሰልጣኞች መፅሄቱ ታትሞ ስላለቀ ነገ ከ4:00 ጀምሮ የከፈላችሁበትን ደረሰኝ ይዛችሁ በመምጣት መውሰድ ትችላላችሁ።