Benishangul Gumuz Health Bureau

@bghealthbureauofficial


This channel is an official channel for Benishangul Gumuz Health Bureau. For more, 0577750204

Benishangul Gumuz Health Bureau

20 Jan, 20:44


በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ዞን ኡንዱሉ ወረዳ የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ማስጀመሪያ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሄደ።

የቤ/ጉ/ክ/መ/ጤ/ቢሮ ኃላፊ አቶ አለም ደበሎ በኡንዱሉ ወረዳ ወረዳ በተካሄደዉ የጤና መድህን ማስጀመሪያ ፕሮግራም ላይ እንዳሉት ወረዳዉ ከ50 በመቶ በላይ የጤና መድህን ተጠቃሚ ማህበረሰብ መዝግቦ ለጉባኤ መድረስ መቻሉ የወረዳውን ጥንካሬ የሚያሳይ መሆኑን ገልጸው ማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት እስከታች በማውረድ ለማህበረሰቡ አገልግሎቱን ተደራሽ ለማድረግ የሁሉንም ርብርብ የሚጠይቅ ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ቢሮ ኃላፊው አክለው እንዳሉት ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተየይዞ የተነሱ ችግሮችን አስመልክቶ የወረዳው ጤና ጽ/ቤት በጤና ተቋሙ ያለውን ክፍተት ለይቶ እንዲያቀርብና ቢሮው በተቻለው መጠን ችግሮቹን ለመቅረፍ የበኩሉን ድርሻ ለመወጣት ዝግጁነታቸውን ገልጸው በወረዳው የጤና ጣቢያ ጤና ኬላ ትስስርን በማጠናከር ችግሮችን በጋራ መቅረፍ መቻል እንዳለባቸውም አሳውቀዋል፡፡

የፌደራል ጤና መድህን አገልግሎት ባለሙያ አቶ ጋሻው አሰፋ በበኩላቸው የኡንዱሉ ወረዳ በአገር አቀፍ ደረጃ የጤና መድህን ከጀመሩ ወረዳዎች 1057ኛ እንዲሁም በክልል ደረጃ 9ኛ ወረዳ በመሆናቹ እንኳን የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ከጀመሩት ወረዳዎች መሆናቸውን ገልፀዉ የወረዳው አመራሮች ለሥራዉ ቅድሚያ ሰጥተዉ መሥራት እንዳለባቸዉ ገልፀዉ ለፕሮግራሙ መሳካት በተቋማቸዉ በኩል አስፈላጊውን ሁሉ እገዛ እንደሚያደርግላቸው ቃል ገብተዋል፡፡

የኡንዱሉ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታጁዲን አልጀሊ በበኩላቸው የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ተግባራዊ እንዲሆን በነበረው ሂደት ውስጥ የወረዳው አመራሮች፤ የወረዳው ነጋዴ ማህበረሰብ እና አጠቃላይ ማህበረሰቡ ላደረገው ጥረት ምስጋናቸውን በማቅረብ ለብዙ አመታት ማህበረሰቡ ሲያቀርብ የነበረው ጥያቄ ዛሬ መልስ በማግኘቱ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

አስተዳዳሪው አክለውም ምንም እንኳን ወረዳው የጤና መድህን ተጠቃሚ መሆኑ ትልቅ ድል ቢሆንም ስራውን አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚመለከታቸው አካላት የበኩላቸውን ድርሻ እንዲያበረክቱ ጠይቀዋል ።

በጉበኤው ላይ የተሳተፉ የወረዳ ነዋሪዎች በማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን በወረዳቸው መጀመሩ እንዳስደሰታቸውና አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልፀዋል።


በጉባኤው ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ላይ የቤ/ጉ/ክ/መ/ክልል መስተዳድር ምክር ቤት የማህበራዊ ዘርፍ አማካሪ አቶ ጌታቸው ፊሊጶስ ፤ የአሶሳ ዞን/ም/አስተዳዳሪ አቶ አህመድ ሙሳ የቤ/ጉ/ክ/መ/ጤ/ቢሮ ኃላፊ አቶ አለም ደበሎ ፤የቤ/ጉ/ክ/መ/ ጤና የፕሮግራም /ም/ቢሮ ኃላፊ
አቶ አብዱልሙኒየም አልበሽር እንዲሁም የአሶሳ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ አንዋር ያሲን ተገኝተዋል፡፡

Benishangul Gumuz Health Bureau

20 Jan, 20:40


ማስታወቂያ

ለቤ/ጉ/ክልል ነዋሪዎች በሙሉ
የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ሂውማን ፓፒሎማ ቫይረስ በተባለ ረቂቅ  ህዋስ አማካኝነት የሚከሰት በግብረስጋ ግንኙነት የሚተላለፍ በሽታ ነው፡፡

ይህ  በሽታ በሴቶች ላይ ከሚከሰቱ ካንሰሮች መካከል  በገዳይነቱ በሁለተኝነት ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡

በአገራችን በማህጸን በር ጫፍ ካንሰር  አዲስ ከሚያዙት  6000 ሴቶች ውስጥ 5000  እንደሚሞቱ በጥናት ተረጋግጧል፡፡

ይህን ሞት እና ህመም ለመቀነስ   የቅድመ ምርመራ በማድረግ  በሽታውን 90 በመቶ መከላከል ይቻላል፡፡

በመሆኑም አንዲት ሴት ለሂውማን ፓፒሎማ  ቫይረስ   ከተጋለጠች ጀምሮ  የማህጸን በር ጫፍ   ካንሰር እስኪከሰት ድረስ  ምንም አይነት ስሜትና ምልክት ሳይታይባት ከ15-20 አመት  በመቆየት  ለመስፋፋት በጣም አዝጋሚ በመሆኑ ቅድመ ካንሰር ምርመራ በማድረግ   በሽታው ተባብሶ  ለህይወት አስጊ ከመሆኑ በፊት  ታክሞ  መዳን  ስለሚቻል  እድሜያቸው  30-49 ዓመት የሆናቸው ሴቶች ወቅታዊና ተከታታይ ምርመራ  ማድረግ ይጋባቸዋል፡

የቤ/ጉ/ክ/መ/ጤና ቢሮም  ይህንን  አገልግሎት   በክልሉ  በሚገኙ  በተመረጡ  ጤና ተቋማት  እየተሰጠ በመሆኑ  እድሜየቸው ከ30 አስከ 49 ዓመት የሆናቹ ሴቶች በሙሉ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንድትሆኑ እያሳወቅን አገልግሎቱ የሚሰጠው በነጻ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

የቤ/ጉ/ክ/መ/ጤና ቢሮ  እና አጋሮቹ

Benishangul Gumuz Health Bureau

20 Jan, 20:38


የጤና መረጃዎችን ለዉሳኔ ለመጠቀም በሚያመች መልኩ እንዲጠናከሩ ለማድረግ
የቢሮ የማኔጅመንት አባላትና ባለሙያዎች በትኩረት መስራት አለባቸው ተባለ። በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ3ኛ ጊዜ የሚከበረዉን የጤና መረጃ ሳምንት ጨምክንያት በማድረግ በመረጃ አጠቃቀም ላይ ያተኮረ ዉይይት ተካህዷል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ የፕሮግራም ዘርፍ ምክትል የቢሮ ሀላፊ አቶ አብዱልሙኒየም አልበሽር የዉይይት መድረኩን ሲከፊቱ እንዳሉት
የጤና መረጃዎችን ለዉሳኔ ለመጠቀም በሚያመች መልኩ እንዲጠናከሩ ለማድረግ የቢሮ የማኔጅመንት አባላትና ባለሙያዎች በትኩረት መስራት እንዳለባቸው ነው ።

በጤና መረጃዎች ላይ የሚስተዋሉ የጥራት፣ የወቅታዊነት፣ሙሉዓዊነት እንዲሁም መረጃን ለዉሳኔ ከመጠቀም ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የቢሮ ማኔጅመንት እና ባለሙያዎች በትኩረት መስራት እንዳለባቸው ምክትል ሀላፊው ገልጸዋል ።

ምክትል ሀላፊ አክለውም የጤና መረጃ ከህይወት ጋር የተያያዘ በመሆኑ ልዩ ትኩረት የሚሻ መሆኑን አስረድተዋል ።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ የጤና መረጃ አስተባባሪ አቶ አህመድ ወዳጀ በበኩላቸው የዉይይት መድረኩ የቢሮ የማኔጅመንት አባላትና የቢሮ ባለሙያዎች በጤና መረጃዎች ትንተና እና አጠቃቀም ላይ የጠራ ግንዛቤ ኑሮአቸው ከጤና ተቋማት አልፎ አልፎ የሚመጡ የመረጃ ልዩነቶችን ለመቅረፍ ያግዛል ብለዋል።

የጤና መረጃዎች በሀገር አቀፍ ደረጃ በተቀመጠው እስታንዳርድ መሠረት ወጥ በሆነ መልኩ ከላይ እስከታች በተናበበ መልኩ በቢሮ በኩል በተሰጡ ፎርማቶች መሆን እንዳለበት የጠቀሱት አቶ አህመድ ከቢሮ እዉቅና ዉጪ በተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተዘጋጅተው ወደ ጤና ተቋማት የሚሰራጩ ቅፃቅፆች ከቢሮ ጋር መናበብ እንዳለባቸው አሳስበዋል ።

Benishangul Gumuz Health Bureau

20 Jan, 20:36


3ተኛው አገር አቀፍ የጤና መረጃ ሳምንት የማስጀመሪያ መርሀ ግብር በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተካሄደ።

‹‹የተጠናከረ አመራር እና ተጠያቂነት በመረጃ ላይ ለተመሰረተ የጤና ዘርፍ ትራንስፎርሜሽን!›› በሚል መሪ ቃል የሚከበረው የዘንድሮ አገር አቀፍ የጤና መረጃ ሳምንት፣ በክልሉ በልዩ ልዩ የጤና ተቋማት በተለያዩ ዝግጅቶች ከግንቦት 5 እስከ 9 /2016 ዓ.ም ድረስ እየተከበረ እንደሚቆይ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ሀላፊ አቶ አለም ደበሎ በመክፈቻ ስነስርአቱ ላይ ገልፀዋል ።

አቶ አለም አክለውም የጤና መረጃ ሳምንት ለማክበር ብቻ ሳይሆን ለመረጃ ትኩረት በመስጠት በተለያዩ ደረጃዎች የተለያዩ ስራዎች የሚሰራበት፤ ትልቅ ንቅናቄ የሚፈጠርበት፤ ከአመራር ጀምሮ እስከ ባለድርሻ አካላት የጤና መረጃን በደንብ የሚረዱበት፣ የራሳቸውን አስተዋጽኦ የሚያደርጉበት መድረክ እንዲሆነም በመክፈቻቸዉ አሳስበዋል።

አመራሩ የመረጃ ስርዓት ለማጠናከር ትልቁን ድርሻ ይወስዳል ያሉት አቶ አለም የጤና መረጃ ከህይወት ጋር የተያያዘ ስለሆነ ተጠያቂነትን ፣ጥራትን እና ወቅታዊነትን ያሻዋልም ብለዋል፡፡

መድረኩ በጤና መረጃ ሥርዓት ላይ የሚታዩ የጥራት ፣ የወቅታዊነት እና ሙሉዓዊነት እንዲሁም መረጃን ለዉሳኔ ከመጠቀም አንፃር ያሉ ችግሮችን ለመፍታት ያስችላል ተብሎ መዘጋጀቱን ሀላፊው ተናግረዋል ።

የመረጃ ሥርዓት ማጠናከር ሌሎች
የትራንስፎርሜሽን አጀንዳዎችን ለማሳካት የጎላ አስተዋጽኦ ስለአለው በጤና ፖሊሲዎች፣
ፕሮግራሞች፣ እስትራቲጂዎች፣ እቅዶች ስታንዳርዶች እና መመሪያዎች ውስጥ የጤና መረጃ ስርአት ትኩረት መደረጉን አቶ አለም አስረድተዋል ፡፡

በንቅናቄ መድረኩ ላይ የተገኙት የቤ/ጉ/ክ/ምክር ቤት ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ስብሳቢ ወ/ሮ መሬም አብዱራሃማን በበኩላቸው የጤና መረጃ ሥርዓት ማጠናከር ጤና ማህበረሰብ ለመፍጠር ወሳኝ በመሆኑ በንቅናቄው መድረክ ላይ የተገኙ የአመራር አካላት ለተግባራዊነቱ የበኩላቸውን ድርሻ መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል ።

በንቅናቄ መድረኩ ላይ ከክልል ሴክተር መ/ቤት የሚመለከታቸው ሀላፊዎች እኔ ከአሶሳ ዞን ሁሉም ወረዳ የጤና ጽ/ቤት ሀላፊዎና ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን በክልል ደረጃ ያለዉ የጤና መረጃ አጠቃቀም ዙሪያ በአሶሳ ዞን ሥር በሚገኙ ጤና ተቋማት ላይ የተደረገ የዳሰሳ ጥናት ግኝቶች ቀርበዉ ዉይይት ተደርጎባቸዋል ።