Amhara NRS Public Health Institute (APHI) @anrsaphi Channel on Telegram

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

@anrsaphi


Amhara NRS Public Health Institute (APHI) (English)

Welcome to the Amhara NRS Public Health Institute (APHI) Telegram channel, where we aim to provide valuable information and resources related to public health in the Amhara region. Our channel, @anrsaphi, serves as a platform for healthcare professionals, policymakers, and the general public to stay updated on the latest developments in public health initiatives, research, and programs in the region. We strive to promote health education, disease prevention, and community wellness through our channel. Who is it? The Amhara NRS Public Health Institute (APHI) is a reputable organization dedicated to improving the health and well-being of the Amhara community through research, education, and advocacy. Our team of experts and professionals work tirelessly to address public health challenges and promote healthy living practices among residents of the region. What is it? The APHI Telegram channel is a valuable resource for anyone interested in public health issues in the Amhara region. From updates on disease outbreaks to tips on maintaining a healthy lifestyle, our channel covers a wide range of topics that are relevant to the community. Whether you are a healthcare professional looking for the latest research findings or a concerned citizen seeking information on health promotion activities, our channel has something for everyone. Join us on @anrsaphi to stay informed, engaged, and empowered when it comes to public health in the Amhara region. Together, we can work towards creating a healthier and happier community for all.

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

07 Feb, 10:42


ዘላቂ የአዕምሮ ጤና እና የማህበራዊ ስነ-ልቦና ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለፀ፤

የአብክመ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከጤና ቢሮ እና አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር በዘላቂ የአዕምሮ ጤና እና የማህበራዊ ስነ-ልቦና ችግሮችን መቅረፍ በሚቻልበት ሁኔታ የምክክር መድረክ ጥር 29/2017 ዓ.ም በባሕር ዳር ከተማ ተካሂዷል።

የአብክመ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ በላይ በዛብህ በግጭት በተጎዱ ማህበረሰቦች ውስጥ ዘላቂ የአዕምሮ ጤና እና የስነ-ልቦና ድጋፍን ለመገንባት የረዥም ጊዜ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የአዕምሮ ጤናን ከመጀመሪያ ደረጃ የጤና እንክብካቤ ጋር ማቀናጀት ይገባል ብለዋል።

በዘላቂነት የተመሰረተ ትብብርና አጋርነት ከችግሮቻችን ለመውጣት ቁልፍ መንገድ በመሆኑ ለአዕምሮ ጤና እና የስነ-ልቦና ድጋፍ በቁርጠኝነት ልዩ ትኩረት ሰጥተን እንሰራለን ብለዋል አቶ በላይ።

በምክክር መድረኩ ላይ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር መንገሻ አየነ ከሀገር አቀፍ ውዥንብር፣ ግጭቶች እና አሳሳቢ ቀውሶች የአዕምሮ ጤና እና የስነ-ልቦና ችግር እያስከተሉ እና ህብረተሰቡን በከፍተኛ ሁኔታ እየጎዱ መምጣታቸውን ተናግረዋል።

የግጭት ሥነ ልቦናዊ ጉዳቱ ከፍተኛ መሆኑን፣ አካላዊ ውድመት እና ከግጭት በኋላ የማይታዩ ጉዳቶችን የሚያስከትል መሆኑን የገለፁት ዶክተር መንገሻ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣው አሰቃቂ ድርጊት እና የስነልቦና-ማህበራዊ ጭንቀት በፍጥነት መፍትሄ ካልተሰጠው የግለሰብ ደህንነትን ብቻ ሳይሆን የማህበራዊ አለመረጋጋትን የሚፈጥር፣ የኢኮኖሚ እና የሀገር መሰረትን ጭምር የሚጎዳ ነው ብለዋል።

የአዕምሮ ጤና እና የስነ-ልቦና ተግዳሮቶች ላይ ግንዛቤ ማሳደግ፤ ክፍተቶችን በመለየት እና በማስረጃ ላይ የተመሰረቱ መፍትሄዎችን መፈለግ፤ እንዲሁም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና በሙያ ማህበራት መካከል ያለውን ትብብር ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ዶክተር መንገሻ  ተናግረዋል።

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሶሻል ወርክ መምህር ዶክተር ሙሉነሽ አበበ በክልላችን በተለያዩ ጊዜያት በተፈጠሩ ግጭቶች ምክንያት የሰው ሕይወት ጠፍቷል፤ የአብሮነት፣ የመተሳሰብ እና የሰብዓዊነት መሠረት የሆኑ እሴቶቻችን ተሸርሽረዋል፤ በማህበረሰቡ ዘንድ ከፍተኛ የአዕምሮ ጤና መቃወስ እና የስነ ልቦና ጫናዎች ደርሰዋል ብለዋል።

ያጋጠመንን ችግር በቅንጅት እና በመናበብ መፍታት ይጠበቃል ያሉት ዶክተር ሙሉነሽ ምርምር በማድረግ እና በማስረጃ የተደገፈ የመፍትሔ ሀሳብ በማቅረብ ከችግሩ መውጣት እንደሚገባ አሳስበዋል።

በአብክመ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች መከላከል እና መቆጣጠር መልሶ ማቋቋም ኬዝቲም አሥተባባሪ ቢረሳው ታዛየ ክልሉ ረጅም ጊዜ የቆዬ ግጭት፣ የወባ ወረርሽኝ፣ የሀገር ውስጥ እና የሱዳን ተፈናቃዮች እና ሌሎች በርካታ ውስብስብ ችግሮች ያሉበት በመሆኑ በማህበረሰቡ ላይ የአዕምሮ ጤና እና የሥነ ልቦና ችግሮች እንደፈጠሩ ገልፀዋል።

የአዕምሮ ጤና ችግር በማህበረሰቡ ላይ ለከፋ ጉዳት ስለሚዳርግ ለመከላከል በትብብር መሥራት እንደሚጠበቅ አቶ ቢረሳው ጠቁመዋል።

ለሕብረተሰብ ጤና ልማት እንትጋ!
ጥር 30/2017 ዓ.ም

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

04 Feb, 06:51


ትኩሳት ያለባቸውን ሰዎች የወባ ምርመራ ዘመቻ ዙሪያ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

02 Feb, 10:30


የሐዘን መግለጫ
============
በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጠቅላላ ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስት እና የጉበት፣ የቆሽት እና የሃሞት ከረጢት ሰብ ስፔሻሊት ሃኪም፣ ተመራማሪ እና መምህር እንዲሁም በጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የቀዶ ሕክምና አገልግሎት ክፍል ዳይሬክተር የነበሩት ዶ/ር አንዷለም ዳኘ በደረሰባቸው የግድያ ሞት የአብክመ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የተሰማውን መሪር ሃዘን ይገልፃል።

ዶ/ር አንዷለም በአገራችን ብሎም በክልላችን አሉን ከምንላቸው የዘርፉ ጥቂት ሰብ ስፔሻሊስት ሐኪሞቻችን መካከል አንዱ የነበሩ ሲሆን ይህን ዓይነት አረመኔያዊ የሆነ ግድያ በንፁህን ዜጎቻችን እና ከፍተኛ ባለሞያዎቻችን ላይ የሚደረግ ኢሰብዓዊ ድርጊት ኢንስቲትዩታችን ከማህበረሰብ ጤነኝነት ባለፈ በዓለም አቀፍ ህግ ጭምር በፅኑ እያወገዘ ለመላው የጤና ሞያተኞች፣ ተመራማሪዎች፣ ለህብረተሰባችንና ለሟች ቤተሰቦች፣ ለጓደኞች እና ለሥራ ባልደረቦች መፅናናትን እንመኛለን።

የአብክመ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

18 Jan, 09:27


የአብክመ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የ2017 በጀት ዓመት የጀመሪያውን ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ በባሕር ዳር ከተማ ጥር 9/2017 ዓ.ም ከባለድርሻ አካላት ጋር አካሄደ፤

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ በላይ በዛብህ ክልላችን በተለያዩ ችግሮች ውስጥ ሆኖም ጥሩ የሚባሉ ዋና ዋና  ተግባራትን እየፈፀመ፣ ውጤት የተገኘባቸውንና ሊተገበሩ የሚገቡ ያልተተሰሩ ወይም በውስንነት የተለዩትን ተግባራት ለመገምገም ውይይት መካሄዱ አስፈላጊ ነው ብለዋል።

የህብረተሰቡን የጤና ደህንነት ማሻሻልና መጠበቅ ኢንስቲትዩቱ የተቋቋመበት ቁልፍ ዓላማ ነው ያሉት አቶ በላይ የጤና እና ስርዓተ-ምግብ ላይ ምርምር በማድረግ መረጃ ማመንጨትና ጥቅም ላይ እንዲውሉ ማድረግ፤ በሰው ሰራሽና በተፈጥሮ የሚከሰቱ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎችን በመከላከልና በመቆጣጠር ዘርፍ በክልሉ በዋናነት በማስተባበርና ኃላፊነት በመወጣት የተሻለ ልምድ የሚወሰድበት ስራ ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል።

ከላቦራቶሪዎች አቅም ግንባታና አገልግሎት አሰጣጥ የተሻለና ጥራቱን የጠበቀ እንዲሆን ጥረት እየተደረገ መሆኑ፣ ጤና እና ጤና ነክ መረጃ ቅመራ፣ ትንተና እና አስተዳደር ማዕከልን በማጠናከርም ኢንስቲትዩቱ ክልላዊ የህብረተሰብ ጤና የመረጃ ማዕከል በመሆን የማህበረሰብ ጤነኝነት እንዲሰፍን በትኩረት እንደሚሰራ ገልፀዋል።

በበጀት ዓመቱ በመጀመሪያው ግማሽ ዓመት የተከናወኑ ተግባራት አፈፃፀም፣ ተግዳሮቶች እና ወደፊት መከናወን ያለባቸው ተግባራትን በተመለከተ በኢንስቲትዩቱ የእቅድ ዝግጅት፣ ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ፍቅርተ እስጢፋኖስ ሪፖርት ቀርቧል።

ዝቅተኛ አፈፃፀም ያላቸው ተግባራትን የአጭርና የረጅም ጊዜ እቅድ በማዘጋጀት መስራት ይጠበቃል ያሉት ወ/ሮ ፍቅርተ የግብዓት እጥረትና የዋጋ መጋነን፣ ወቅታዊ ሁኔታ እና የፖለቲካ አለመረጋጋት፣ ማህበረሰቡን ያሳተፉ ስራዎች ለመስራት መቸገር እና የአጋር አካላት ተሳትፎ መቀነስ ተግዳሮቶች እንደነበሩ ተናግረዋል።

በመድረኩ የተቀናጀ ድጋፋዊ ጉብኝት ሪፖርት በኢንስቲትዩቱ የእቅድ ዝግጅት፣ ክትትልና ግምገማ ባለሙያ በአቶ ለዓለም ገደፋው የቀረበ ሲሆን በቀረቡት ሪፖርቶች ላይ ከተሳታፊዎች አስተያየትና ጥያቄዎች ተነስተው ውይይት ተደርጓል።

የአብክመ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ስሜነህ አያሌው በችግር ውስጥ ሆነን ተግባሮቻችንን ለመፈፀም የተደረገውን ርብርብ ገልፀዋል። በዕቅዱ ላይ መግባባት ተፈጥሮ ወደ ስራ መገባቱን አስታውሰው አሁንም ክልሉ መፈናቀል፣ የወረርሽኝ ክስተት እና ሌሎች ጤና እና ጤና ነክ ችግሮች ውስጥ በመሆናችን በቁልፍ አመላካቾች ላይ ትኩረት አድርጎ ቀሪ ተግባራትን መፈፀም እንደሚገባ አሳስበዋል።

አቶ ስሜነህ አክለውም ችግሮቻችን በርካታና ውስብስብ በመሆናቸው በራስ አቅም የሚፈቱትን በመለየት ለመፍታት ጥረት ሊደረግ ይገባል ብለዋል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የአብክመ ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ ገስጥ ጥላሁን በግጭት ውስጥ ሆነን ትልቅ ውጤት መመዝገቡን ጠቁመው የህብረተሰብ ጤና አደጋዎችን ከመከላከልና መቆጣጠር አኳያ ችግሩን ለመቀልበስና ከተከሰተ በኋላም ምላሽ በመስጠት ረገድ በርካታ ተግባራት እየተፈፀሙ እንደሆነ እና ተግባራትን አቀናጅቶ መስራት ይገባል ብለዋል።

ዋና ዳይሬክተሩ አንገብጋቢ የህብረተሰብ ጤና ችግሮችን ቅድሚያ ሰጥቶ ችግር ፈቺ ምርምር፣ የማህበረሰብ ተኮር ጤና ቅኝት ስርዓት ላይ ትኩረት ማድረግ፣ የስጋት ተግባቦትና የማህበረሰብ ተሳትፎ ስራ ማጠናከር እና ለሚከሰቱ ችግሮች አካባቢያዊ መፍትሔ በመስጠት መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
ለሕብረተሰብ ጤና ልማት እንትጋ!
ጥር 10/2017 ዓ.ም

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

06 Jan, 19:06


ከአብክመ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር 
ለ2017 ዓ.ም ለጌታችን ለእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል የተላለፈ መልዕክት

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

የአብክመ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የጤናውን ሴክተር በማጠናከር የህብረተሰቡን የጤና ደህንነት መጠበቅና ማሻሻል ዋና ዓላማው ሲሆን፤ በክልሉ ዘርፈ ብዙ ችግሮች ላይ ትኩረት በመስጠት እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ አስተዎፅኦ የሚያደርግ ስትራቴጅክ የክልሉ ህዝብ ስትራቴጅክ ተቋም ጭምር ነው።

ኢንስቲትዩቱ በክልል አቀፍ የህብረተሰብ ጤና ምርምር አጀንዳዎች ላይ ተመስርቶ ቅድሚያ ትኩረት በተሰጣቸው የጤና ችግሮች ላይ የጥናትና ምርምር ስራዎችን በማካሄድ የሳይንሳዊ፣ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጅያዊ እውቀትን በማመንጨትና በማሰራጨት የህብረተሰቡን ጤና ማሻሻል፤ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች መከላከልና ቁጥጥር ስራዎችን ማስተባበርና መምራት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅትና በትብበር ተገቢውን ቅኝት በማካሄድ ሥጋቶችን መለየትና በቂ ዝግጅት በማድረግ ሊደርስ የሚችለውን አደጋ አስቀድሞ መከላከል፣ ሲከሰትም አፋጣኝ ምላሽ መስጠት እና መረጃዎችን በወቅቱ በማስተለለፍ የተጎዳው የህብረተሰብ ክፍል ከአደጋዉ ተጽዕኖ በፍጥነት ሊያገግም የሚችልበትን ምቹ ሁኔታ መፍጠር፤ የክልሉን የጤና እና የስነ-ምግብ ላቦራቶሪዎች አቅም መገንባትና ጥራት ያለዉና ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት እንዲሰጡ በማድረግ ተግባራትን እየፈፀመ ይገኛል፡፡ በቅርቡም የክልል ጤና እና ጤና ነክ መረጃዎች ቅመራ፣ ትንተና እና አስተዳደር ማዕከል በማደረጀት ከፍተኛ እንቅሰቃሴ ውስጥ ይገኛል።

ኢንስቲትዩቱ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ቢሆነውም ''የዓለም አቀፍ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቶች ማህበር'' /Public Health Institutes of the World/ አባል መሆን የቻለ ተቋም ነው።

በአሁኑ ወቅት ክልላችን ውስብስብ በሆነ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ውስጥ የደሚገኝ ሲሆን ከደረሱብን ችግሮች ለመውጣት ሰብዓዊነትን በማስቀደም በዓለም አቀፍ መርህ ሁሉም በመረዳዳት እና በአንድነት መንፈስ ርብርብ በማድረግ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ለጤና አገልግሎት ተደራሽ እንዲሆን ማስቻል ይገባል፡፡ 

ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል በዓሉን ሲያከብር የግልና የአካባቢ ንፅህናን በመጠበቅ ከተላላፊ በሽታዎች ራስን፣ ቤተሰብንና እና አካባቢን መጠበቅና ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ እየገለፅኩ  ማናቸውንም የጤና እና ጤና ነክ መረጃዎች በ6981 ነፃ የስልክ መስመር እንድታደርሱ እናሳውቃለን።

በመጨረሻም ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በድጋሚ እንኳን ለ2017 ዓ.ም ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ እላለሁ።

ለህብረተሰብ ጤና ልማት እንተጋለን!

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

03 Jan, 18:19


https://www.facebook.com/100069040512305/posts/897311685913507/

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

03 Jan, 18:13


የጥናትና ምርምር ሴሚናሮች [Fortnight Research Seminars/FoRSe] ስለምርምር ጥያቄዎች የሚነሱበት፣ ጠንካራ ሳይንሳዊ ውይይቶች የሚካሄዱበት እና አብሮ ለመስራት ትስስሮችን ለመፍጠር የሚያስችሉ መድረኮች ናቸው ።

29ኛው ዙር የጥናትና ምርምር ሴሚናር [Fortnight Research Seminar/FoRSe ] ሲካሄድ ለመሳተፍ የተገኙት የአብክመ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ በላይ በዛብህ ሴሚናሮች መካሄዳቸው ስለምርምር ጥያቄዎች የሚነሱበት፣ ጠንካራ ሳይንሳዊ ጉዳዮችን በስፋት በውይይት የሚነሱበትና ትስስርን በመፍጠር በትብብር ለመስራት የሚያስችሉ መድረኮች ናቸው ብለዋል፡፡

የኢንስቲትዩቱ ባለሞያዎች ምርምርን በመደበኛነት በመያዝ በቀጥታና በፍጥነት ሊሰጡ ከሚገቡ አገልግሎቶች ጋር በማጣጣም በትኩረት ሊሰሩት እና እንዲህ ያሉ መድረኮችን በላቀ ተሳትፎ የተቋሙ ባህል ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ ምርምር ለዕድገትና ልማት ቁልፍ መንገድ በመሆኑ ለምርምር ስራ መንግስት በመደበኛነት በጀት እንዲመድብ መረጃዎች ጭምር መቅረብ ያለባቸው መሆኑን ጠቁመው ጥያቄዎች እቀረቡ መሆኑን አንስተዋል።

በሴሚናሩ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ በሆኑት ፕሮፌሰር ሙሉጌታ ክብረት "Key messages on Changes in practices and behavior for better tackling Antimicrobial Resistance in the Akaki River catchment: One-health perspective and strategies for preventing and Reducing waterborne AMR in Ethiopia:" በሚል ርዕስ የተሰራ የምርምር ውጤት አቅርበው ከተሳታፊዎች አስተያየት እና ጥያቄዎችተነስተው ውይይት ተደርጓል። በቀጣይነትም በጉዳዩ ላይ በጋራ ለመስራት ሃሳብ ቀርቦ ስምምነት ተደርሷል።

በመጨረሻም የቀረበው ጥናት ጥሩ መሆኑን እና አስቻይ ሁኔታዎች ያሉን በመሆኑ በርካታ ስራ መስራት እንደሚጠበቅ የገለፁት አቶ በላይ በምርምር የተደገፈ መረጃ ማመንጨት እና ለውሳኔ ሰጪዎች የፕሮጀክት እና የትግበራ አማራጮችን ማሳየት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

ሴሚናሩ በየ2 ሳምንቱ ሃሙስ የሚካሄድ ሲሆን ታኅሳስ 24/2017 ዓ.ም 29ኛው ዙር በተያዘው መርሃግብር መሰረት ተካሂዷል።

ለሕብረተሰብ ጤና ልማት እንትጋ!
ታህሳስ 25/2017 ዓ.ም

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብክመ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የመረጃ መረቦች ከታች ያሉ ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡

ዌብሳይት፡ http://www.aphi.gov.et/
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/HealthofInstitute
ቴሌግራም፡ https://t.me/anrsaphi
ዩቱዩብ፡ https://www.youtube.com @amharapublichealthinstitut8998
ትዊተር፡ APHI_anrs
ነፃ የስልክ መስመር:- 6981

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

02 Jan, 18:25


https://www.facebook.com/100069040512305/posts/896699185974757/

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

02 Jan, 12:53


ማኅበረሰቡ የወባ ትንኝ መራቢያ ቦታዎችን የማፋሰስ፣ የማዳፈን እና የማጽዳት ሥራ እንዲሠራ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ.ር) አሳሰቡ። 

ባሕር ዳር: ታኅሣሥ 24/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ታኅሣሥ 25/2017 ዓ.ም በክልሉ ሁሉም ወባማ ቀበሌዎች የሚኖሩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የወባ ትንኝ መራቢያ ቦታዎችን የማፋሰስ፣ የማዳፈን እና የማጽዳት ሥራ እንዲሠራ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የማኅበራዊ ክላስተር አሥተባባሪ እና የክልላዊ የወባ መከላከል ግብረ ኀይል ሠብሣቢ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ.ር ) አሳስበዋል።

በአማራ ክልል ከሐምሌ 1/2016 ዓ.ም እስከ ታኅሣሥ አጋማሽ 2017 ዓ. ም ድረስ 3 ሚሊዮን 112 ሺህ 772 ሰዎች የወባ ምርመራ አድርገዋል። 

ከተመረመሩት ውስጥ 1 ሚሊዮን 315 ሺህ 970 የሚኾኑት የወባ በሽታ ሕሙማን እንደኾኑ አንስተዋል። 

በተለይም ደግሞ በክልሉ 40 ወረዳዎች የክልሉን 70 በመቶ የወባ ሥርጭት ይሸፍናሉ ተብሏል።

እስከ ታኅሣሥ አጋማሽ ያለው የወባ ሥርጭት ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር 64 በመቶ መጨመሩንም ነው ያነሱት።

የወባ ትንኝ መራቢያ ቦታዎችን ለይቶ ማኅበረሰቡን በማሳተፍ የአካባቢ ቁጥጥር ሥራ በትኩረት አለመሥራት፣ የአየር ንብረት ለውጥ፣ የመኝታ አጎበር በወቅቱ አለመተካቱ እና ማኅበረሰቡም የተሰጠውን የመኝታ አጎበር በአግባቡ አለመጠቀም ለወባ በሽታ ጭማሬው እንደ ዋና ምክንያት ተቀምጠዋል።

በኬሚካል እጥረት ምክንያት የፀረ ወባ ትንኝ ኬሚካል ርጭት የሚካሄድባቸው ቀበሌዎች ቁጥር መቀነስ፣ ወደ ወባማ አካባቢዎች የሚደረግ የሰዎች እንቅስቃሴ እና ከፍተኛ የኾነ የሀገር ውስጥ ተፈናቃይ በክልሉ መኖር ለሥርጭቱ ሌላው ምክንያት ኾኖ ተቀምጧል።

ሥርጭቱን ለመከላከል ባለፉት ወራት ከፍተኛ የወባ ጫና ባለባቸው 27 ወረዳዎች በሚገኙ 233 ቀበሌዎች የቤት ውስጥ የጸረ ወባ ትንኝ ኬሚካል ርጭትም ተካሂዷል።

ከጥቅምት 15/2017 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ ዘወትር አርብ "የአርብ ጠንካራ እጆች የወባ በሽታን ይገታሉ" በሚል መሪ መልዕክት ለተከታታይ 11 ሳምንታት ክልላዊ የአካባቢ ቁጥጥር ሥራ ዘመቻ  እየተሠራ ይገኛል። 

የወባ በሽታን ለመቆጣጠር በማኅበረሰቡ ተሳትፎ እና ከአጋር አካላት ጋር በመቀናጀት  እየተሠራ እንደሚገኝም አስገንዝበዋል።

ጤና ተቋማትም የወባ መከላከልን መደበኛ ሥራ አድርገው በትኩረት እንዲሠሩም አሳስበዋል።

ታኅሣሥ 25/2017 ዓ.ም በክልሉ ሁሉም ወባማ ቀበሌዎች የሚኖሩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ከጠዋቱ 1 ሰዓት እስከ 2 ሰዓት  የወባ ትንኝ መራቢያ ቦታዎችን የማፋሰስ፣ የማዳፈን እና የማጽዳት ሥራ እንዲሠሩም ጠይቀዋል።

                  ምንጭ:- ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

02 Jan, 11:20


https://www.youtube.com/watch?v=HD5lDiFT6pY

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

01 Jan, 16:11


በአንድ ሰዓት የሚሊዮኖች ጠንካራ የአካባቢ ቁጥጥር ስራ በክልሉ በሁሉም ወባማ ቀበሌዎች ትርጉም ያለው የወባ በሽታ ቅነሳ [Millions' 1 hour Engagment in Environmental Management for Signficant Malaria Reduction - SMaR]
"የዓርብ ጠንካራ እጆች የወባ ወረርሽኝን ይገታሉ!"

በክልላችን ባልተለመደ ሁኔታ እየጨመረ የመጣው የወባ በሽታ በህብረተሰባችን በተለይ አምራች በሆነው ዜጋ ላይ ከፍተኛ የጤና ስጋት በመሆን ጫና እያሳደረ ይገኛል።

የወባ በሽታ ስርጭትን ለመግታት "የዓርብ ጠንካራ እጆች የወባ ወረርሽኝን ይገታሉ!" በሚል መሪ ቃል ሁሉንም የክልላችን የህብረተሰብ ክፍል ባሳተፈ መልኩ የሚተገበር ክልላዊ ጤና ጣቢያ መር ማህበረሰብ አቀፍ የአካባቢ ቁጥጥር ስራ ሲሆን ህብረተሰቡ በሚኖርበት አካባቢ እና በስራ ቦታ በዘመቻ ለወባ ትንኝ መራቢያ ምቹ የሆኑ ውሃ ያቆሩ ቦታዎችን እና ውሃ በሚቋጥሩ ቁሳቁሶች የማፋሰስ፣የማዳረቅ  እና የማፅዳት ተግባራትን ከጥቅምት 15/2017 ዓ.ም ጀምሮ ዘወትር አርብ ጠዋት ከ1:00 - 3:00 ሰዓት ሲከናወን ቆይቷል።

ታኅሳስ 25/2017 ዓ.ም የወሩ የመጨረሻው ዓርብ ስለሆነ ይህን ሳምንት ከፍተኛ ንቅናቄ አድርገን በተጠቀሰው ቀን ማለትም አርብ ጠዎት 1:00 ሰዓት ላይ ሁላችንም ሚሊዮኖች ሆነን በመውጣት በየሰፈራችን ውሃ የቋጠሩ ወይም የያዙ ቦታዎችንና ቁሳቁሶችን የማፋሰስ፣ የማዳረቅ እና የማፅዳት ስራ በርብርብ መተግበር ይገባናል።

የወባ በሽታ ስርጭቱ አሁንም በክልሉ በከፍተኛ ሁኔታ ላይ ስላለ በየሳምንቱ ቀጣይነት ባለው ሁኔታ  ይህንን ተግባር በመደበኛነት የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ክብካቤ አሃዶች (ጤና ጣቢያዎችና ጤና ኬላዎች) ከቀበሌ አመራሮች፤ ከሴቶች ወጣቶችና አጠቃላይ ነዋሪዎች ጋር በቅንጅትና በትብብር እና ባለመሰልቸት በመስራት የወባ በሽታን የህብረተሰብ ጤና ችግር እንዳይሆን በማድረግ ወሳኝ የማህበራዊ ልማትን ማሳደግ ይገባል።

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

01 Jan, 06:47


ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

31 Dec, 05:40


የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጂሚ ካርተር በ100 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

በበጎ አድራጎት ስራው ዓለም አቀፍ ዝናን ያተረፈው 39ኛው የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጂሚ ካርተር እ.ኤ.አ. የ2022 የኖቤል የሰላም ሽልማትን በማሸነፍ በአሜሪካ ታሪክ ረጅም እድሜ ያስቆጠሩ የቀድሞ ፕሬዝዳንት በ100 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

በ1982 ጂሚ ካርተር ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ80 በሚበልጡ አገሮች በምግብ ዋስትና፣ በሰላምና በጤና ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጎ "ዘ ካርተር ሴንተር" የተሰኘ የእርዳታ ድርጅት አቋቁሟል። የካርተር ማዕከል ለኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ዘርፍ ከአብክመ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር ልዩ ትብብርን ጨምሮ ከፍተኛ አስተዋጾ አድርጓል።

የካርተር ማዕከል እንደ ጊኒ ዎርም በሽታ፣ ሪቨር ብላይንድነስ፣ ትራኮማ፣ ሊምፋቲክ ፋይላሪሲስ እና ወባን የመሳሰሉ በሽታዎችን በመዋጋት ረገድ ትልቅ አስተዋፅኦ አበርክቷል።

የካርተር ማዕከል ለኢንስቲትዩቱ ሰራተኞች የቴክኒክ ድጋፍ እና ስልጠና ሰጥቷል፣ APHI የመረጃ አያያዝ እና ትንተና ስርዓቱን በማሻሻል፣ በምርምር ፕሮጄክቶች ላይ ትብብር አድርጓል።

በአጠቃላይ የአማራ ክልል ሕብረተሰብ ጤና ተግዳሮቶችን ለመፍታት የተቋሙን አቅም ለማጠናከር የካርተር ማዕከል ከኢንስቲትዩቱ /APHI/ ጋር ያለው ትብብር ወሳኝ ነው።

የጂሚ ካርተር ለአማራ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ያበረከቱትን አስተዋጾ ሁሌም እናስታውሳለን!

Former US President Jimmy Carter died at the age of 100.

The 39th former President of the United States, Jimmy Carter, who gained worldwide fame for his philanthropic work, won the 2022 Nobel Peace Prize and was the longest-lived former president in American history passed away at the age of 100. In 1982, Jimmy Carter founded an aid organization, The Carter Center, focusing on food security, peace and health issues in more than 80 countries, including Ethiopia.

The Carter Center has made significant contributions to Ethiopia's public health sector, including specific collaborations with the Amhara Public Health Institute (APHI). The Carter Center has been instrumental in combating diseases like Guinea worm disease, river blindness, trachoma, lymphatic filariasis, and malaria. The Carter Center has provided technical assistance and training to APHI staff in various areas of public health, supported APHI in improving its data management and analysis systems, and collaborated on research projects. Overall, the Carter Center's partnership with APHI has been crucial in strengthening the institute's capacity to address public health challenges in the Amhara region.

We will always remember Jimmy Carter’s Contributions to Amhara Public Health Institute!

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

30 Dec, 17:46


https://www.facebook.com/100069040512305/posts/894600906184585/

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

30 Dec, 07:06


3ኛው ዓለም አቀፍ የጤና ምርምር ጉባዔ ድህረ ግምገማ ተካሄደ፤

የአብክመ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት እና በአማራ ክልል ከሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፎረም በጋራ ከታህሳስ 3-5/2017 ዓ.ም የተካደውን 3ኛው ዓለም አቀፍ የጤና ምርምር ጉባኤ የድህረ ግምገማ ተካሂዷል።

የአብክመ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ በላይ በዛብህ ባለፉት ዓመታት ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር ከነበረው የተናጠል ጉባዔዎች በተለየ መልኩ በዚህ ዓመት በክልሉ ካሉ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፎርም ጋር በጋራ መካሄዱን እና መድረኩ በጉባዔው የነበሩ ሂደቶችን ለመገምገምና በቀጣይ ለሚካሄዱ ጉባዔዎች ከዚህ በተሻለ መልኩ ለማስኬድ ዓላማ አድርጎ የተዘጋጀ ነው ብለዋል፡፡
በጉባዔው ውጤታማ ስራ መሰራቱን እና በቀጣይ ለሚካሄዱ ጉባዔዎች ከዚህ በተሻለ ሁኔታ ለማካሄድ የምክክር መድረኩ ወሳኝ መሆኑን የጠቆሙት አቶ በላይ ጉባኤው ለየት ያለ እና ከተለመደው ውጭ የተካሄደ መሆኑን እንዲሁም ከጉባኤው የሚወጡ ምርምሮች ተግባር ላይ እንዲውሉ የሚደረግበትን ስርዓት ለመፍጠር፤ ጀማሪ ተመራማሪዎች ልምድ ካላቸው የተማሩበት እና ለፖሊሲ አውጭዎች ጥቅም ላይ እንዲውል ምርምሮች የቀረቡበት እንደነበር ገልፀው ተመራማሪዎች ለዚህ ታሳቢ ያደረገ ምርምር መስራት እንደሚጠበቅባቸዋል አሳስበዋል።

የኢንስቲትዩቱ የጤና ምርምር ልማት ዳይሬክቶሬት ተ/ዳይሬክተር ዶ/ር አዳነ ንጉሴ የምርምር ጉባዔው የነበሩ ሂደቶችን እና በቀጣይ መከናወን ባለባቸው ተግባራት ዙሪያ ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን በጉባዔው ከወቀቱ ጋር የሚሄዱ የምርምር ስራዎች ተመርጠው መቅረባቸውን ገልፀዋል።
በጉባዔው 52 ምርምሮች 41 የቃል እና 11 የፖስተር ከአገር ውስጥና ውጭ የሚገኙ ተመራማሪዎች በአካል እና በበየነመረብ ያቀረቡ መሆኑን የገለፁት ዶክተር አዳነ የተለያዩ አካላት በትብብር አብረው እንዲሰሩ ግንዛቤ የተፈጠረበት እና ተቀናጅቶ ለመስራት ግብዓት የተገኘበት እንደነበር ተናግረዋል።

የአብክመ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ስሜነህ አያሌው በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲዎች በፎረሙ አማካኝነት ተሳታፊ መሆናቸው ከተናጠል ግንኙነት የተሻለና የሚያበረታታ መሆኑን ገልፀው በችግር ውስጥ ሆኖ ተግባርን መከወን የተማርንበት ነው ብለዋል።
ከባለፉት ዓመታት ጉባዔዎች የነበሩ ክፍተቶችን ለይተን መስራታችን ለዚህ ውጤት በቅተናል ያሉት አቶ ስሜነህ የቀጣይ ዓመት ጉባዔ ከወዲሁ ስራ መጀመር እንደሚገባ እና በቡድን አንድ ሆኖ ከተሰራ ከዚህ የበለጠ መስራት ይቻላል ብለዋል። በጀት ዋና ጉዳይ በመሆኑ ከወዲሁ የማፈላለግ ስራ መስራት፣ ለጉባዔው የሚመጥን በጀት መመደብ እና አጣጥሞ መጠቀም እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የነበሩ ጥንካሬዎችን ማስቀጠል፤ ክፍተቶችን ለይቶ በማስተካከል፤ ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ለጉባዔው በበጀት አስተዋፅኦ እንዲያደርጉና ጉባዔው ወደ ኋላ እንዳይቀለበስ በቅንጅት መስራት እንደሚጠበቅ አሳስበዋል።

በአማራ ክልል የሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፎረም ዋና ፀሃፊ ዶ/ር ታፈረ መላኩ ጉባዔው ካለው ነባራዊ ሁኔታ አንፃር በርካታ መልካም ተግባራት የቀረቡበት፤ የቀረቡ ምርምሮች ለፖሊሲ የሚጠቅሙና በክልሉ ላይ ሊተገበሩ የሚችሉ መሆናቸውን ገልፀው የጉባዔው ጭብጥ ጥሩና መልስ የሰጠ የማይበገር የጤና ስርዓት እንዲፈጠር የሚያግዝ ነበር ብለዋል።

የክልሉን የጤና ስርዓት ለማሻሻል ከፍተኛ ሀገራዊ ኃላፊነት ያላቸው ሰዎች በጉባዔው መሳተፋቸው ጥሩ አጋጣሚ የፈጠረ ነበር ያሉት ዶክተር ታፈረ የሚቀርቡ ምርምሮች ለጤናው ስርዓት መሻሻል አስተዋፅዖ ያላቸው እንዲሆኑ አመራረጥ ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በምርምር የጤና ስርዓቱ ተጠቃሚ እየሆነ እንደሆነ የገለፁት ዋና ዳይሬክተሩ የቀጣይ ጉባዔ አቅዶ በመስራት በተሻለ መንገድ መፈፀም እንደሚገባ፤ ከአርቴፊሻል ኢንቴሊጀንሲ ጋር የተያያዘ የምርምር ስራዎች ላይ ትኩረት ተደርጎ እንዲሰራ እንዲሁም የበጀት ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ መንግስት ጉባዔውን በበጀት መደገፍ እንዳለበት ጠቁመዋል።

በመጨረሻም በኮሚቴ ተመድበው በመስራት ለጉባዔው መሳካት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ የኮሚቴ አባላት የምስጋና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል።

ለሕብረተሰብ ጤና ልማት እንትጋ!
ታህሳስ 21/2017 ዓ.ም

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብክመ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የመረጃ መረቦች ከታች ያሉ ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡

ዌብሳይት፡ http://www.aphi.gov.et/
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/HealthofInstitute
ቴሌግራም፡ https://t.me/anrsaphi
ዩቱዩብ፡ https://www.youtube.com @amharapublichealthinstitut8998
ትዊተር፡ APHI_anrs
ነፃ የስልክ መስመር:- 6981

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

25 Dec, 19:14


ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

25 Dec, 17:54


"ኢንስቲትዩቱ የሚያናከናውናቸው የጤና ስራዎች ለህብረተሰቡ ተደራሽ ይሆኑ ዘንድ የህዝብ ተሳትፎ እና ተግባቦት ወሳኝ ናቸው" የአብክመ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ በላይ በዛብህ

በአብክመ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት እና አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን አብረው ለመሥራት የሚያስችላቸውን የጋራ መግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡

ስምምነቱን የተፈራረሙት በአብክመ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ በላይ በዛብህ እና የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሙሉቀን ሰጥዬ ናቸው፡፡

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ በላይ በዛብህ ኢንስቲትዩቱ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ቢሆነውም እያደገ የሚገኝ የክልሉ ሕዝብ ተቋም መሆኑን ገልፀው ለእድገቱ አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዋነኛ አጋር ሆኖ ሲያገለግል ቆይቷል ብለዋል።

ሁለቱም ተቋማት ለአማራ ክልል ቁልፍ ጠቀሜታ የሚሰጡ የሕዝብ ተቋማት ናቸው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ እነዚህ ተቋማት ተቀናጅተው መስራታቸው ለህብረተሰቡ የጤና ስጋቶች ፈጣን ምላሽ በመስጠት ጤናማ እና አምራች ማህበረሰብ ለመፍጠር ጉልህ ሚና እንደሚኖረውም አመላክተዋል።

ኢንስቲትዩቱ የሚያናከናውናቸው የጤና ሥራዎች ለህብረተሰቡ ተደራሽ ይሆኑ ዘንድ የተግባቦት ስራ ወሳኝ እንደሆኑ የተናገሩት ዋና ዳይሬክተሩ ለዚህ ደግሞ አሚኮ የላቀ የሙያ ባለቤት በመሆኑ በጋራና በመደጋገፍ እንሰራለን ብለዋል።

በክልሉ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎችን ከመቆጣጠርና ከመከላከል አኳያ እስካሁን የምሰራውን ስራዎች አሚኮ ከጎናችን በመሆን ለህብረተሰቡ ተደራሽ በማድረግ ግንዛቤ ሲፈጥር የቆየ መሆኑን እና ዛሬ የተስማማንባቸውን ብቻ ሳይሆን አዳዲስ ሃሳቦችን እየጨመርን መስራት እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል።

ለህዝባችን ጠንካራ ተቋማት ያስፈልጉታል ያንን ለማሳካት በጋራ ቆመን እንሰራለን ያሉት የአሚኮ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሙሉቀን ሰጥዬ ሁለቱ ተቋማት ሁሌም ቢሆን በጋራ የሚሰሩ የሕዝብ አገልጋዮች ናቸው ብለዋል።

ስምምነቱ አገልግሎታችንን የበለጠ ለማስፋት ያለመ የቤተሰብ ስምምነት እንጅ በማይተዋወቁ እንግዳ ተቋማት መካከል የተደረገ አይደለም ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው ሰነዱ በመቀራረብ እና በጋራ በማቀድ ሕዝብን መሰረት ያደረገ ውጤታማ ስራ ለማከናወን እንደሚያግዝ ገልፀዋል።

ሁለቱም ተቋማት የሚያገለግሉት ሕዝብን ነው ያሉት ሙሉቀን በተለይም የጤና ጉዳይ የሰውን ሕይወት በቀጥታ የሚነካ በመሆኑ አሚኮ ከኢንስቲትዩቱ የጤና ባለሙያዎች ጋር በመሆን የቅድመ መከላከል መልዕክቶችን ተደራሽ ያደርጋል ብለዋል።

አሚኮ ብዝሃ ቋንቋ የሥርጭት አቅሙን በመጠቀም እና የጤና ዘርፍ ባለሙያዎችን በመጋበዝ በዕውቀት ላይ የተመሠረተ መረጃ ለሕዝብ እንደሚያደርስ አቶ ሙሉቀን ገልጸዋል።

ሕዝባችን ቀድሞ መከላከል በሚችላቸው በሽታዎች መጠቃት የለበትም፤ ቅድመ የጤና ጥንቃቄዎችን ለማስገንዘብ እና ለሕዝብ ጤና ለመሥራት አሚኮ ዝግጁ በመሆኑና ኢንስቲትዩቱ ደግሞ የጤና ዕውቀትን በመሙላት ውጤታማ ሥራ እናከናውናለን ብለዋል።

አሚኮ በሁሉም የሥርጭት ቋንቋዎች መረጃ ሰጭ የጤና መልዕክቶችን እንደሚያስተላልፍ እና የኢንስቲትዩቱ አመራሮችና ባለሙያዎችም ከበፊቱም ሲያደርጉት የነበረውን ሙያዊ አስተዋጽኦ የበለጠ አጠናክረው በመቀጠል ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ አቶ ሙሉቀን አሳስበዋል።
በተናጠል ቆመን ጠንካራ ተቋማትን መገንባት አንችልም ዋና ሥራ አሥፈጻሚው በጋራ በመቆም ለሕዝብ የሚሠሩ ሁነኛ ተቋማትን መገንባት ያስፈልጋል ብለዋል።

የዛሬውን የአሚኮ እና የአብክመ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተፈርሞ የሚረሳ ሳይሆን ውጤት የሚያስገኝና ለህዝቡ አገልግሎት የሚሰጥበት እንደሚሆን አቶ ሙሉቀን ጠቁመዋል።

ለህብረተሰብ ጤና ልማት እንትጋ!
ታኅሳስ 16/2017 ዓ.ም

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብክመ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የመረጃ መረቦች ከታች ያሉ ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡

ዌብሳይት፡ http://www.aphi.gov.et/
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/HealthofInstitute
ቴሌግራም፡ https://t.me/anrsaphi
ዩቱዩብ፡ https://www.youtube.com @amharapublichealthinstitut8998
ትዊተር፡ APHI_anrs
ነፃ የስልክ መስመር፡ 6981

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

24 Dec, 12:43


በአብክመ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በየ2 ወሩ የሚዘጋጅ ዜና መፅሔት ቅፅ 1 ቁጥር 32

ለህብረተሰብ ጤና ልማት እንትጋ!
ታኅሳስ 15/2017 ዓ.ም

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብክመ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የመረጃ መረቦች ከታች ያሉ ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዌብሳይት፡ http://www.aphi.gov.et/
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/HealthofInstitute
ቴሌግራም፡ https://t.me/anrsaphi
ዩቱዩብ፡ https://www.youtube.com @amharapublichealthinstitut8998
ትዊተር፡ APHI_anrs
ነፃ የስልክ መስመር፡ 6981

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

20 Dec, 17:30


https://www.facebook.com/100069040512305/posts/887802726864403/

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

07 Dec, 12:48


የአብክመ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አመራርና ሰራተኞች የፀረ- ሙስና ቀንን በፓናል ውይይት አከበሩ፤

በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ21ኛ ጊዜ በሀገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ20ኛ ጊዜ "ወጣቶችን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል የነገን ስብዕናን ይገነባል!" በሚል መሪ ቃል የፀረ-ሙስና ቀንን ኅዳር 27/2017 ዓ.ም ኢንስቲትዩቱ አመራርና ሰራተኞች በተገኙበት በፓናል ውይይት ተከብሯል።

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ በላይ በዛብህ ነገን የተሻለ ለማድረግ የፀረ-ሙስና ትግል እንደሚያስፈልግ ገልፀው ጥሩ ዜጋ ለመፍጠር፤ የተሻለ የስራ ባህል እንዲኖር ከብልሹ አሰራር መውጣት እና በታታሪነት ለሕብረተሰቡ ጥቅም ወገንተኛ ሆነን መስራት ይገባል ብለዋል።

የተቋማችን የስራ ባህሪ ዓላማው የህብረተሰቡን ጤና ደህንነት ማስጠበቅ በመሆኑ ከሌሎች ተቋማት ጋር በመተባበር የበለፀገ አምራች ዜጋ፣ በዓለም ላይ ተወዳዳሪ እና ተፅዕኖ ፈጣሪ ትውልድ እንዲፈጠር የበኩላችንን አስተዋፅኦ መወጣትና ሙስናን መታገል እንደሚገባ ተናግረዋል።

የመወያያ ፅሁፍ ያቀረቡት የኢንስቲትዩቱ የህግ ባለሙያ አቶ ይታየው ተሾመ የውይይቱ ዓላማ በክልሉ ደረጃ የተጀመረውን የሙስና ትግል በመደገፍ ሙስና የልማትና የሰላም ጉዟችንን እንዳያደናቅፍ የሚያደርግ ተግባር መፈፀም ለኢንስቲትዩታችን ሰራተኞች በስነ-ምግባርና በሙስና ምንነት ላይ ግንዛቤ ለመፍጠር ነው ብለዋል።

የኢንስቲትዩቱ ሰራተኛች በስነ-ምግባር ምስጉን ሁነው ሙስናን የሚፀየፋ እንዲሆኑ ግንዛቤ መፍጠር እና ሙስና መከላከል ስራችን ውጤታማ ማድረግ ይጠበቃል ያሉት አቶ ይታየው የሙስና መከላከል ተግባራችንን በመተላለፍ የሚፈፀሙ የሙስና ወንጀሎች ሲኖሩ ለሚመለከተው አካል ጥቆማ ማድረግና ሙሰኞችን በተባበረ ክንድ መታገል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በመድረኩ ከተሳታፊዎች አስተያየቶች ተነስተው ውይይት የተደረገ ሲሆን ሙስና ለአገርም ሆነ ለክልላችን ትልቅ ችግር እየሆነ መምጣቱን የገለፁት የኢንስቲትዩቱ የውስጥ ኦዲት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እያደር መለሰ ሰራተኛው ግንዛቤ ኑሮት ማህበረሰቡን ማስተማርና አመለካከቱን መቀየር እንዳለበት እንዲሁም ሙሰኞች ተገቢ ቅጣት እንዲያገኙ በትብብርና በቅንጅት በመስራት በዘላቂነት መከላከል እንደሚገባ ገልፀዋል።

ለሕብረተሰብ ጤና ልማት እንትጋ!
ኅዳር 28/2017 ዓ.ም

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብክመ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የመረጃ መረቦች ከታች ያሉ ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡

ዌብሳይት፡ http://www.aphi.gov.et/
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/HealthofInstitute
ቴሌግራም፡ https://t.me/anrsaphi
ዩቱዩብ፡ https://www.youtube.com @amharapublichealthinstitut8998
ትዊተር፡ APHI_anrs
ነፃ የስልክ መስመር :- 6981

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

07 Dec, 10:51


https://www.facebook.com/100069040512305/posts/879071131070896/?mibextid=rS40aB7S9Ucbxw6v

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

07 Dec, 07:40


https://www.facebook.com/100069040512305/posts/878988721079137/?mibextid=rS40aB7S9Ucbxw6v

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

07 Dec, 01:21


https://www.facebook.com/100069040512305/posts/878826837761992/?mibextid=rS40aB7S9Ucbxw6v

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

29 Nov, 11:41


በአብክመ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የጤና ምርምር ልማት ዳይሬክቶሬት አስተባባሪነት በየ2 ሳምንቱ ሀሙስ የሚካሄደው የጥናትና ምርምር ሴሚናር (Fortnight Research Seminar/FoRSe/ ኅዳር  19/2017 ዓ.ም 27ኛው ዙር ተካሂዷል።

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ መምህር በሆኑት ተባባሪ ፕርፌሰር መሃመድ ሁሴን "Financial viability of a community based health insurance scheme in two districts of northwest Ethiopia"በሚል ርዕስ የተሰራ የጥናት ውጤት አቅርበው ውይይት ተደርጓል።

ለሕብረተሰብ ጤና ልማት እንትጋ!
ኅዳር 20/2017 ዓ.ም

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብክመ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የመረጃ መረቦች ከታች ያሉ ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡

ዌብሳይት፡ http://www.aphi.gov.et/
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/HealthofInstitute
ቴሌግራም፡ https://t.me/anrsaphi
ዩቱዩብ፡ https://www.youtube.com @amharapublichealthinstitut8998
ትዊተር፡ APHI_anrs
ነፃ የስልክ መስመር :- 6981

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

28 Nov, 07:22


"የዓርብ ጠንካራ እጆች የወባ ወረርሽኝን ይገታሉ!"

ለሕብረተሰብ ጤና ልማት እንትጋ!
ኅዳር 19/2017 ዓ.ም

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብክመ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የመረጃ መረቦች ከታች ያሉ ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡

ዌብሳይት፡ http://www.aphi.gov.et/
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/HealthofInstitute
ቴሌግራም፡ https://t.me/anrsaphi
ዩቱዩብ፡ https://www.youtube.com @amharapublichealthinstitut8998
ትዊተር፡ APHI_anrs
ነፃ የስልክ መስመር :- 6981

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

21 Nov, 10:36


"የዓርብ ጠንካራ እጆች የወባ ወረርሽኝን ይገታሉ!"


ለሕብረተሰብ ጤና ልማት እንትጋ!
ኅዳር 12/2017 ዓ.ም

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብክመ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የመረጃ መረቦች ከታች ያሉ ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡

ዌብሳይት፡ http://www.aphi.gov.et/
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/HealthofInstitute
ቴሌግራም፡ https://t.me/anrsaphi
ዩቱዩብ፡ https://www.youtube.com @amharapublichealthinstitut8998
ትዊተር፡ APHI_anrs
ነፃ የስልክ መስመር :- 6981

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

21 Nov, 07:17


ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

21 Nov, 05:43


https://www.facebook.com/AmharaMediaCorporation/videos/1092709552234540/?mibextid=rS40aB7S9Ucbxw6v

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

20 Nov, 06:37


https://www.facebook.com/100069040512305/posts/867807095530633/?mibextid=rS40aB7S9Ucbxw6v

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

19 Nov, 11:33


https://ameco.et/bekur/%e1%8b%a8%e1%8b%93%e1%88%ad%e1%89%a5-%e1%8c%a0%e1%8a%95%e1%8a%ab%e1%88%ab-%e1%8a%a5%e1%8c%86%e1%89%bd-%e1%8b%a8%e1%8b%88%e1%89%a3-%e1%8b%88%e1%88%a8%e1%88%ad%e1%88%bd%e1%8a%9d%e1%8a%95/

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

15 Nov, 19:43


የአብክመ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት እና ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ አገልግሎት ስራ አመራር ኮሚቴ በጋራ መስራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ኅዳር 06/2017 ዓ.ም ምክክር አካሂዱ፤

የአብክመ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ በላይ በዛብህ ውይይቱ መካሄዱ በሁለቱ ተቋማት የሚፈፀሙ ተግባሮችን ለማወቅና በጋራ ለመፈፀም ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል።

ኢንስቲትዩቱ ከጤና አንፃር የምርምር የተረጋገጡ መረጃዎችን በማመንጨት የውሳኔ ሰጭ አካላት እንዲጠቀሙባቸው ከሚሰራቸው ተግባራት መካከል አንዱ መሆኑን ገልፀው ተቀናጅተን በመስራት ተግባሮቻችንን ውጤታማ እናደርጋለን ብለዋል።

የአብክመ ወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ አገልግሎት ኃላፊ ወ/ሪት መዓዛ በዛብህ ሁለቱም ተቋማት መዳረሻቸው ህዝብ እና ለህዝብ ቀጥተኛ አገልግሎት መሆናቸውን ገልፀው ቀጣይ አንድነታችንን አጠናክረን እንሰራለን ብለዋል።

ሁለቱ ተቋማት የሚፈፅሟቸው ተግባራት ተመሳሳይነት ያላቸው እና በጋራ ሁነው ቢሰሩ ይበልጥ የክልሉን ህብረተሰብ የሚጠቅሙና ውጤታማ እንደሚሆኑ የገለፁት የአብክመ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ስሜነህ አያሌው ይህንንም ለማጠናከር በጋራ መስራት የሚያስችል የስምምነት በማድረግ ተግባራትን ለይተው ወደ ስራ መግባት እንደሚገባ ጠቁመዋል።

ክልሉ በውስብስብ ችግር ውስጥ ያለ መሆኑን የተናገሩት ኃላፊዋ ሁለቱ ተቋማት መረጃ በመለዋወጥ፣ አጋርነትና ትብብር በማጠናከር ክልሉ ለሚቀርፃቸው ፖሊሲዎችና እስትራቴጂዎች ትክክለኛና ታማኝ መረጃ በመስጠት የበኩላቸውን ድርሻ ለመውጣት በጋራ እንደሚሰሩ ተናግረው መረጃ ከመሰብሰብ ባለፈ አሻጋሪ ስራ እየተሰራ በመሆኑ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ በላይ በዛብህ በበኩላቸው 
የጋራ ስምምነት ማድረግ፤ አፈፃፀማቸውን መከታተል እና ተግባራትን መገምገም እንዲሁም ሁለቱ ተቋማት በሚያካሂዷቸው የዕቅድ ዝግጅት እና የግምገማዊ መድረኮች ላይ በመሳተፍ ተባብረንና ተቀናጅተን በመስራት ቀጣይነት ያለው ስርዓት መገንባት እንችላለን ብለዋል።

ለሕብረተሰብ ጤና ልማት እንትጋ!
ኅዳር 6/2017 ዓ.ም

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብክመ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የመረጃ መረቦች ከታች ያሉ ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡

ዌብሳይት፡ http://www.aphi.gov.et/
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/HealthofInstitute
ቴሌግራም፡ https://t.me/anrsaphi
ዩቱዩብ፡ https://www.youtube.com @amharapublichealthinstitut8998
ትዊተር፡ APHI_anrs
ነፃ የስልክ መስመር :- 6981

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

15 Nov, 13:58


26ኛው ዙር የጥናትና ምርምር ሴሚናር (Fortnight Research Seminar/FoRSe/ ተካሄደ፤

በአብክመ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የጥናትና ምርምር ልማት ዳይሬክቶሬት አስተባባሪነት በየ2 ሳምንቱ ሀሙስ የሚካሄደው የጥናትና ምርምር ሴሚናር ኅዳር  05/2017 ዓ.ም 26ኛው ዙር ተካሂዷል።

በሴሚናሩ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የ3ኛ ዲግሪ ተማሪ በሆኑት ተባባሪ ፕርፌሰር ዮሀንስ መርሻ "Exploring Women's  Experiences During Pregnancy, Delivery, and PostPartum Periods in Bahir Dar City, North West Ethiopia" በሚል ርዕስ የተሰራ የጥናት ውጤት አቅርበዋል፡፡

በቀረበው የጥናት ውጤት ላይ ከተሳታፊዎች በተነሱ አስተያየት እና ጥያቄዎች በጥናት አቅራቢው ተባባሪ ፕርፌሰር ዮሀንስ ማብራሪያ ተሰጥቶ ውይይት ተደርጓል።

በሴሚናሩ ከኢንስቲትዩቱ እና ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተመራማሪዎች ተሳትፈዋል።

ለሕብረተሰብ ጤና ልማት እንትጋ!
ኅዳር 5/2017 ዓ.ም

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብክመ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የመረጃ መረቦች ከታች ያሉ ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡

ዌብሳይት፡ http://www.aphi.gov.et/
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/HealthofInstitute
ቴሌግራም፡ https://t.me/anrsaphi
ዩቱዩብ፡ https://www.youtube.com @amharapublichealthinstitut8998
ትዊተር፡ APHI_anrs
ነፃ የስልክ መስመር :- 6981

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

15 Nov, 11:40


ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

14 Nov, 06:51


"የዓርብ ጠንካራ እጆች የወባ ወረርሽኝን ይገታሉ!"

አራተኛው ዓርብ ኅዳር 06/2017 ዓ.ም የሚካሄድ ክልላዊ ጤና ጣቢያ መር ማህበረሰብ አቀፍ የአካባቢ ቁጥጥር የዘመቻ ስራ ዘወትር አርብ በአካባቢያችን እና በስራ ቦታችን ለወባ ትንኝ መራቢያ ምቹ የሆኑ፦
• ውሃ ያቆሩ ቦታዎችን /በወንዝ፣ በሃይቅ፣ በኩሬ ወዘተ./
• ውሃ በሚቋጥር የዛፍ ቅጠል፣ የእንስሳት ዱካ፣ በተጣሉ ጎማዎች፣ በሰባራ ሸክላዎች፣ ሰው ሰራሽ የሆኑ የውሃ  ማጠራቀሚያዎችን የማፅዳት፣ የማፋሰስ እና የማዳረቅ ስራን ዘወትር አርብ ጠዋት በመስራት የወባ ስርጭትን እንግታ።

ለሕብረተሰብ ጤና ልማት እንትጋ!
ኅዳር 5/2017 ዓ.ም

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብክመ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የመረጃ መረቦች ከታች ያሉ ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡

ዌብሳይት፡ http://www.aphi.gov.et/
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/HealthofInstitute
ቴሌግራም፡ https://t.me/anrsaphi
ዩቱዩብ፡ https://www.youtube.com @amharapublichealthinstitut8998
ትዊተር፡ APHI_anrs

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

11 Nov, 18:44


የተጀመረውን ማህበረሰብ አቀፍ ጤና ጣቢያ መር የአካባቢ ቁጥጥር ስራ አተገባበር በተመለከተ የውይይት መድረክ ኅዳር 2/2017 ዓ.ም በባሕር ዳር ከተማ ተካሂዷል፤

የአብክመ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ በላይ በዛብህ ዋናው እና በእጃችን ያለው ሳይንሳዊ የሆነው የወባ መከላከል ተግባር የአካባቢ ቁጥጥር ስራ መሆኑን ጠቅሰው ተግባሩን አጠናክሮ በመስራት የወባ ትንኟ እንዳትራባ ማድረግ ይቻላል ብለዋል፡፡

ማህበረሰብ አቀፍ ጤና ጣቢያ መር የአካባቢ ቁጥጥር ስራ የተጀመረው የወባ መከላከልና መቆጣጠር ስራን ጤና ጣቢያዎች ማህበረሰቡን ባለቤት አድርገው በማስተባበርና በማነቃቃት እንዲሰሩ መሆኑን የተናገሩት ዋና ዳይሬክተሩ በቀጣይ ሁለት ወራት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

ሁሉም ዞኖች በርካታ ተግባራትን እየፈፀሙ ቢሆንም በወቅቱ ሪፖርት የማድረግ ክፍተት መኖሩን ጠቁመው ማህበረሰብ አቀፍ የቅኝት ስራን ማጠናከር ይጠበቃል ብለዋል፡፡

በመድረኩ ክልላዊ የወባ በሽታ ሁኔታ፣ ጤና ጣቢያ መር የአካባቢ ቁጥጥር ስራ እና ያጋጠሙ ችግሮችን የተመለከተ የኢንስቲትዩቱ የወባ ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ዳምጤ ላንክር ሪፖርት አቅርበዋል፡፡

የጤና ስርዓቱ ችግርን መቋቋም የሚችል፤ የማይበገር ሆኖ እየቀጠለ መሆኑን የገለፁት የመድረኩ ተሳታፊዎች የግብዓት እጥረት መኖሩን እንዲሁም የወባ በሽታን ለመከላከል አመራሩ ቁልፍ ተግባራትን ይዞ መስራት እንደሚገባና በደንብ መደገፍ ይገባል ሲሉም ጠቁመዋል፡፡

የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ስሜነህ አያሌው በርካታ ተግባራት ወባን በመከላከል ዙሪያ እየተሰሩ መሆኑን ጠቁመው ወባ እንደ ክልል ጫና እያሳደረብንና እየፈተነን በመሆኑ ያለንን አቅም አሟጠን በመጠቀም በሽታውን የመከላከልና የመቆጣጠር ስራን አጠናክሮ መስራት ይገባል ብለዋል፡፡

ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም አመራሩና ባለሙያው ማህበረሰቡን ይዘው ተቀናጅተው በትብብር በመስራት ከችግሩ መውጣት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

በሽታውን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በአቅማችን ልክ የምንፈፅማቸውን ተግባራት ለይተን ማከናወን እንደሚገባ የጠቆሙት የኢንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች መከላከልና መቆጣጠር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አብርሃም አምሳሉ በክስተት አስተዳደር ስርዓት የሚከናወኑ ተግባራት የሚከሰቱ ወረርሽኞችን በአጭር ጊዜ መቆጣጠር የሚያስችል በመሆኑ በልዩ ትኩረት ማስቀጠል ይገባል ብለዋል፡፡

በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የወባ በሽታ ገዳይ መሆኑን አስረድቶ፤ ማህበረሰቡን አስተባብሮ "የአርብ ጠንካራ እጆች የወባ ወረርሽኝን ይገታሉ" በሚል እየተፈፀመ ያለውን ማህበረሰብ አቀፍ ጤና ጣቢያ መር የአካባቢ ቁጥጥር ስራን በተጠናከረ መንገድ በመስራት ወረርሽኙን መግታት እንደሚገባ ዋና ዳይሬክተሩ በአፅንኦት ተናግረዋል፡፡

በመድረኩ ከሁሉም ዞን ጤና መምሪያ የመጡ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች መከላከልና መቆጣጠር አስተባባሪዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም ከኢንስቲትዩቱ ቅርንጫፍ ተቋማት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡

ለሕብረተሰብ ጤና ልማት እንትጋ!
ኅዳር 2/2017 ዓ.ም

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብክመ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የመረጃ መረቦች ከታች ያሉ ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡

ዌብሳይት፡ http://www.aphi.gov.et/
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/HealthofInstitute
ቴሌግራም፡ https://t.me/anrsaphi
ዩቱዩብ፡ https://www.youtube.com @amharapublichealthinstitut8998
ትዊተር፡ APHI_anrs

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

30 Oct, 18:33


በአማራ ክልል በተካሄደው የመጀመሪያ ዙር የልጅነት ልምሻ(ፖሊዮ) መከላከያ ክትባት ዘመቻ 95 በመቶ ማሳካት መቻሉ ተገለፀ፤

የአብክመ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የልጅነት ልምሻ(ፖሊዮ) ክትባት ዘመቻ አፈፃፀም በምዕራብ አማራ ከሚገኙ ዞኖች ከመጡ የዞን ጤና መምሪያ ባለሙያዎች ጋር ጥቅምት 20/2017 ዓ.ም በባሕር ዳር ከተማ የውይይት መድረክ አካሂዷል፡፡

በመድረኩ የተገኙት በኢንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች መከላከልና መቆጣጠር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አብርሃም አምሳሉ በክልሉ በተለያየ ጊዜ በሚያጋጥሙ ችግሮች መደበኛ ክትባትን በአግባቡ ከመስጠት አንፃር ክፍተቶች በመኖራቸው በተለያዩ ጊዜያት ወረርሽኞች በተደጋጋሚ እንደሚከሰቱ ገልፀዋል፡፡

የፖሊዮ በሽታ በዋግኸምራ ብሔረሰብ ዞን በመከሰቱና ለዚህ ምላሽ የሚሆን ክትባት ለመስጠት ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን አውስተዋል፡፡

ክልሉ ባለበት አስቸጋሪ ሁኔታ የዕቅዱን 95 በመቶ በመፈፀም ውጤታማ የሆነ ዘመቻ መካሄዱን የገለፁት አቶ አብርሃም ከክልል እስከ ቀበሌ ሁሉንም ተደራሽ ለማድረግ ጥረት ሲደረግ መቆየቱንና አንዳንድ ወረዳዎች ዘመቻውን ዘግይተው ቢጀምሩም ውጤታማ ስራ መስራታቸውን ተናግረው ለ2ኛው ዙር ክትባት ዘመቻ የቅድመ ዝግጅት ስራን ዘመጀመር ከዚህ የተሻለ ለመፈፀም መዘጋጀት ይገባል ብለዋል፡፡

በክትባት ዘመቻው የተከናወኑ ተግባራት፣ ያጋጠሙ ችግሮች እና የተሻሉ ተሞክሮዎችን በኢንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ምላሽ ሰጭ ባለሙያ በአቶ ሀይሉ አያሌው ሪፖርት ቀርቧል፡፡

በዘመቻው 4 ሚሊዮን 28 ሺህ 5 መቶ ሃምሳ ህፃናት ለመከተብ በዕቅድ ተይዞ 3ሚሊዮን 813 ሺህ 33 ህፃናትን የእቅዱን 95 በመቶ ማከናወን መቻሉን በሪፖርቱ ተመላክቷል፡፡

ለክትባቱ ውጤታማነት ስልጠና መሰጠቱ፤ ሚዲያዎችን መጠቀም፤ ቅንጅታዊ አሰራር መፈጠሩ፣ የጤና ባለሙያዎች ቁርጠኝነት፤ ለሚያጋጥሙ ችግሮች አካባቢያዊ መፍትሔ መፈለግና መጠቀም እና የአመራሩ ድጋፍ ከፍተኛ መሆናቸውን የገለፁት አቶ ሀይሉ የፀጥታ ችግሩ ግብዓት በተፈለገው ጊዜ ማድረስ፣ ድጋፍና ክትትል ማድረግ አለመቻል፤ የአጋር አካላት ድጋፍ አናሳ መሆን እና የመሳሰሉት በዘመቻው ተግዳሮት እንደነበሩ ተናግረዋል።

የኢንስቲትዩቱ የበሽታዎችና ጤና ሁኔታዎች ቅኝትና ምላሽ ቡድን መሪ ፅጌረዳ አምሳሉ ለዘመቻው ውጤታማነት የጤና ባለሙያዎች ያሳዩት ቁርጠኝነት የሚበረታታ መሆኑን ገልፀው በዚህ ዙር ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን መሰረት ያደረገ የድርጊት መርሃ-ግብር  አውጥቶ ለቀጣይ በቅንጅትና በትብብር መፈፀም እንደሚገባ አሳስበዋል።

በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ በቀጣይ በሚካሄደው 2ኛ ዙር ክትባት አዳዲስ የተፈጠሩ ጎጦችን እና በመጀመሪያው ዙር ተደራሽ ያልሆኑ ህፃናትን ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ የገለፁት አቶ አብርሃም ለዚህ አፈፃፀም ውጤታማነት አስተዋፅዖ ላበረከቱ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ለሕብረተሰብ ጤና ልማት እንትጋ!
ጥቅምት 20/2017 ዓ.ም

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብክመ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የመረጃ መረቦች ከታች ያሉ ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡

ዌብሳይት፡ http://www.aphi.gov.et/
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/HealthofInstitute
ቴሌግራም፡ https://t.me/anrsaphi
ዩቱዩብ፡ https://www.youtube.com @amharapublichealthinstitut8998
ትዊተር፡ APHI_anrs

Amhara NRS Public Health Institute (APHI)

27 Oct, 11:35


የአብክመ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ''Regional Information Platform for Nutrition (RIPN)'' ፕሮጀክት ያከናወናቸውን እና በቀጣይ በሚከናወኑ ተግባራት ዙሪያ ጥቅምት 16/2017 ዓ.ም ውይይት አካሄደ፤

በመድረኩ የአብክመ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ በላይ በዛብህ እንደተናገሩት ኢንስቲትዩቱ ከተቋቋመበት ዓላማዎች መካከል አንዱ በምርምር ላይ የተመሰረተ የጤና መረጃ በማመንጨት ውሳኔ ሰጪ አካላት እንዲጠቀሙበት ማድረግ እና የምግብና ስርዓተ - ምግብ ስራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ እና በእነዚህ ጉዳዮች ላይ ማስተባበር መሆኑን ገልፀው በሚጠበቀው ልክ እየተሰራ ባለመሆኑ በክልሉ ከርዕሰ ጉዳዩ ጋር የተያያዙ ዘርፈ ብዙ ችግርን በሚገባ የጋራ ግንዛቤ በመያዝ በአንድነትና በትብብር ተግባራትን ለይቶ መስራት ይገባል ብለዋል።

የፕሮጀክቱ መኖር ለክልሉ ማህበረሰብ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን የተናገሩት ዋና ዳይሬክተሩ የምግብና ስርዓተ -  ምግብ ፖሊሲን ወደ ተግባር መለወጥና መረጃ ላይ ተመስርቶ ምን ያህል ህፃናት የስርዓተ-ምግብ ተጠቃሚ መሆናቸውንና ተደራሽ ያልሆኑትን ለይቶ በአጭር፣ በመካከለኛና በረጅም ጊዜ ምላሽ እንዲያገኙ ይሰራል ብለዋል።

በክልሉ የስነ - ምግብ ላቦራቶሪ ምርመራ እንደሚያስፈልግ በመረዳት በኢንስቲትዩቱ የባዮ ሜዲካል ሪፈረንስ ላቦራቶሪ ምርመራ እየተደራጀ ያለ መሆኑን ገልፀዋል።

በመድረኩ የኢንስቲትዩት የዕቅድ ዝግጅት፣ ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር እና የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ወ/ሮ ፍቅርተ እስጢፋኖስ ፕሮጀክቱ ያለበትን ሁኔታ እንዲሁም በኢንስቲትዩቱ የስርዓተ-ምግብ ተመራማሪና በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የ3ኛ ዲግሪ ተማሪ ግሩም መሰረት ስርዓተ-ምግብ የሚሹ ጉዳዮችን በተመለከተ ሰነድ አቅርበዋል።

በክልላችን ያሉትን የምግብና ስርዓተ ምግብ ችግሮችን ለመፍታት ትክክለኛ መረጃ መስጠት እንደሚጠበቅ የጠቆሙት ወ/ሮ ፍቅርተ የፕሮጀክቱ ቀጣይነት ላይ መስራት እንደሚገባ ገልፀዋል።

የበጀትና የፀጥታ ችግር ቢኖርም ብዙ የሚጠበቁብን ስራዎች አሉ ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ በዕለቱ የተገኙ ተሳታፊዎች በርዕሰ ጉዳዩ ብዙ ልምድ እና እውቀት ያለቸው በመሆኑ በቋሚነት መገናኘና መምከር እንዲሁም ተግባራትን መገምገም፤  ሃብት በጋራ ማፈላለግና መጠቀም፤ የግንዛቤ ፈጠራ ስራዎችን በሴክተር ተቋማት በቅንጅት መስራት እንደሚጠበቅ አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ፕሮጀክቱን ወደ አማራ ክልል አውርዶ ለመስራት ጥቅምት 2016 ዓ.ም በጋራ መስራት የማያስችል ስምምነት መፈራረሙ የሚታወስ ነው።

በመድረኩ የሚመለከታቸው የሴክተር መስሪያ ቤት እና የአጋር አካላት ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።

ለሕብረተሰብ ጤና ልማት እንትጋ!
ጥቅምት 17/2017 ዓ.ም

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብክመ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የመረጃ መረቦች ከታች ያሉ ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡

ዌብሳይት፡ http://www.aphi.gov.et/
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/HealthofInstitute
ቴሌግራም፡ https://t.me/anrsaphi
ዩቱዩብ፡ https://www.youtube.com @amharapublichealthinstitut8998
ትዊተር፡ APHI_anrs