.
ሃድ ባር
.
.
ከሚወደኝ ጆሮሽ
ከምትወጂው ቧልቴ
ከሳቆችሽ መኃል
"እብድ ነህ" ስትዪኝ
በስሱ በስሱ...ተጀመረ እብደቴ
.
.
ምንም አልገረመኝ!
ላ'ለም ልቡን ዘግቶ..ባንድ ሰው ታዛ ስር ለቆመች ህይወቱ
'እብደት' ማለት ምንም...ጨርቅ መጣል ከንቱ!
.
እኔን መች ደነቀኝ?
"ማበዱ ነው" ሲሉ
..ትናንቴን የሚያውቁ
እርቃን ልብ ላይሸፍን
ወግድ! ብዬ ነበር..
ምን ሊረባኝ ጨርቁ?
.
.
ይኸው!
"አንተ እብድ" ስትዩኝ
አሜን ብዬ እንደኖርኩ..ቅንጣት ሳልከፋ ራሴን ሳልሰስት
ጤናዬን ገብሬሽ..ለደስታሽ ስለፋ
.
ያሳደገኝ ሳቅሽ...
ያሳበደኝ ሳቅሽ...
ለታዛቢ ሰጥቶ...ሳያኖረኝ ጠፋ።
.
.
ያኔ ራሴን አየሁ..!
ከሳቅሽ ባሻገር..ሌላ ዓለም እንዳለ ለፈገግታ ብቻ ጥርስ እንዳልበቀለ
ለመንከስ ..ለመብላት..ለመስበር.. ለማድቀቅ..እንደተተከለ
.
.
ያኔ ራሴን አየሁ!
ሰውኛ ስሜትሽ...ወረት ከወለደ
ቁምነገሬን አጥቶ
ተራማጅ ልቡናሽ እንደተሰደደ
.....ጥሎኝ እንደሄደ
.
.
ይኸው...ከዛን ጊዜ
.
ስክነት እርቃን ወጣ
.....ጤንነት ተነነ
ነገን ማለም ቀረ...ትዝታሽ ገነነ
ናፍቆትሽ ገነነ....ሽንፈቴ ጀገነ!
.
ከብቻነቴ ጋር...ሳቅሽን እያሰብኩ
መሳቅ.... መሳቅ
...መሳቅ...መሳቅ ብቻ ሆነ
.
.
እንኳን ተሳካልሽ!
እንኳን ደስ አላችሁ!
ትንቢት ተፈጸመ
እብደት ምሉዕ ሆነ።
@betagitim
@betagitim