ALERT Comprehensive Specialized Hospital @alertspecializedhospital Channel on Telegram

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

@alertspecializedhospital


This is an official ALERT Comprehensive Specialized Hospital telegram channel.

ALERT Comprehensive Specialized Hospital (English)

Welcome to the official ALERT Comprehensive Specialized Hospital Telegram channel! Here, you will find the latest updates, news, and information about our hospital's specialized services and healthcare offerings. ALERT Comprehensive Specialized Hospital is a leading healthcare facility dedicated to providing comprehensive and specialized medical care to patients. From state-of-the-art technology to a team of experienced and compassionate healthcare professionals, we are committed to delivering high-quality services to meet the diverse needs of our patients. Whether you are looking for specialized treatment in cardiology, oncology, neurology, or any other medical specialty, our hospital is equipped to provide you with the care you need. Stay tuned to our channel for updates on upcoming events, health tips, and patient success stories. Join us in our mission to promote health and wellness in our community. Follow @alertspecializedhospital for reliable and accurate information from a trusted source. We look forward to keeping you informed and engaged in your healthcare journey. Welcome to the ALERT Comprehensive Specialized Hospital family!

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

08 Feb, 16:09


በአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የእሳት አደጋ ደህንነት ስልጠና ተሰጠ።

ባለፉት ሶስት ቀናት የአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል
የህክምና ደህንነት ጉዳዮች ቡድን፣ ከአዲስ አበባ እሳት አደጋ እና አደጋ አያያዝ ቢሮ ጋር በመተባበር ለአለርት ሆስፒታል 60 ሠራተኞች የእሳት አደጋ ደህንነት ስልጠና ሰጡ።

ስልጠናው የእሳት አደጋ ዓይነቶች፣ እሳት ማጥፊያዎችን መጠቀም እንዲሁም በአደጋዎች ጊዜ በፍጥነት እና በተገቢው መንገድ መስራት የሚችሉ ለመሆን አስፈላጊ የሆኑ መሰረታዊ ነገሮችን አካቷል። ተሳታፊዎች በንድፈ-ሀሳብ እና በተግባራዊ ልምምዶች ተሳትፈዋል፣ በስልጠናው መጨረሻም አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የደህንነት እና አደጋ አያያዝ ኮሚቴ ተመሠርቷል።

ዋና ውጤቶች፡
- ዝግጁ ሠራተኞች
- የተሻለ ደህንነት
- የተሻለ አደጋ አያያዝ

“ደህንነቱ ያልተጠበቀ እንክብካቤ እንክብካቤ አይደለም”

Fire Safety Training at ALERT Comprehensive Specialized Hospital

Over the past three days, ALERT Comprehensive Specialized Hospital Patient Safety Case Team, in collaboration with the Addis Ababa Fire and Disaster Management Office, trained 60 staff members on fire safety.

The training covered fire types, extinguisher use, and emergency response, ensuring staff can act swiftly and effectively in fire emergencies. Participants engaged in theoretical lessons and hands-on exercises, culminating in the formation of the ALERT CSH Security Risk Reduction Committee.

Prepared staff
Enhanced safety
Stronger emergency response

“If it’s not safe, it’s not care.”

#FireSafety #PatientSafety #ALERTCSH #EmergencyPreparedness

***
Join our social media
👉🏼 Facebook 👉🏼 Telegram
👉🏼 Website 👉🏼 YouTube 👉🏼 TikTok 👉🏼 X

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

05 Feb, 15:25


ዶ/ር ሽመልስ ንጉሴ – በአለርት ሆስፒታል የቆዳና አባላዘር ህክምና ስፔሻሊስት 🏥

ዶ/ር ሽመልስ ንጉሴ በአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የቆዳና አባላዘር ህክምና ስፔሻሊስት እና ተመራማሪ ሆነው የሚያገለግሉ ሲሆን፣ በተጨማሪም የኢትዮጵያ የቆዳና አባላዘር ህክምና ማህበር ፕሬዘዳንት ናቸው፡፡

የፊት ቆዳ ጤና እና የቆዳ ጤና ጉዳዮችን በተመለከተ የሚያቀርቡትን ዕውቀት እና ምክሮች ለማግኘት “ጤናዎ በቤትዎ” ፕሮግራም ላይ ይከታተሉዋቸው፡፡
📺 ፕሮግራሙን ለማየት እንዲህ ይጫኑ 👉 እዚህ ይጎብኙ


Dr. Shimelis Negussie – Dermatology & Venereology Specialist at ALERT Hospital 🏥

Dr. Shimelis Negussie serves as a specialist and researcher in dermatology and venereology at ALERT Comprehensive Specialized Hospital. He is also the President of the Ethiopian Society of Dermatology and Venereology, contributing significantly to advancing skin health in Ethiopia.

For expert insights and advice on facial skin health and dermatological concerns, follow him on the “Your Health at Home” program.
📺 Watch the program here: 👉 Click Here

#ALERTHospital #SkinHealth #YourHealthAtHome #Ethiopia

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

04 Feb, 15:00


አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልና አርማወር ሃንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመሆን ዓለም አቀፉ የካንሰር ቀንን ‹እኔም ስለ ካንሰር ያገባኛል፤ ካንሰርን በጋራ እንከላከል›! በሚል መሪ-ሃሳብ በተለያዩ ትምህርታዊ ዝግጅቶች በጋራ አከበሩ።

በተካሄደው የካንሰር ግንዛቤ ማስጨበጫና መከላከያ ዝግጅት ላይ፣ የጤና ሚኒስቴር የበሽታ መከላከያና መቆጣጠር፣ የተለያዩ የመንግስትና የግል ሆስፒታሎች እና ክሊኒኮች ተወካዮች እንዲሁም አጋር ድርጅቶች ተሳትፈዋል።

“የካንሰር ህክምናን ቢቻል መከላከል፣ ካልተቻለ አክሞ ማዳን ይቻላል” በሚል መሪ-ሃሳብ፣ የተለያዩ የህክምና ባለሙያዎች የተዘጋጀውን የክህሎት ስልጠና ስፋት ያለው ዝማሬ ሰጥተዋል።

በተጨማሪም፣ የጤና ሚኒስቴር የህክምና ምርምራን በማስፋት ከሆስፒታሎችና ከምርምር ተቋማት ጋር በስፋት እየተሰራበት እንደሆነ ተገልጿል።

ALERT Comprehensive Specialized Hospital and Armauer Hansen Research Institute together with Ministry of health commemorated World Cancer Day under the global theme “I Am and I Will: Together, We Can Fight Cancer!” through various educational events and awareness activities.

The Cancer Awareness and Prevention Event brought together representatives from the Ministry of Health, public and private hospitals, clinics, and partner organizations.

Under the theme “If Possible, Prevent Cancer; If Not, Early Detection Saves Lives”, medical professionals delivered in-depth educational sessions on cancer prevention, early diagnosis, and treatment.

Additionally, the Ministry of Health emphasized its commitment to expanding medical research and collaborating with hospitals and research institutions to improve cancer care and treatment across the country.

#WorldCancerDay #MoH #ALERTHospital #AHRI

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

03 Feb, 13:35


የዳሽን ባንክ ጀሞ ቅርንጫፍ ሰራተኞች የደንበኞችን ሳምንት ምክንያት በማድረግ በሆስፒታሉ የሚገኙ ተገልጋዬችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
በተጨማሪም በአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ህክምናቸውን ተከታትለው በመልካም ጤንነት ላይ የሚገኙት አቶ ሲሳይ እና ጓደኛቸው ህክምናቸውን በመከታተል ላይ የሚገኙ ታካሚዎችን በመጎብኘት ያበረታቱ ሲሆን ወደ ቀድሞጤናቸው እንዲመለሱ ክትትልና ድጋፍ ያደረገላቸውን ሆስፒታልና የህክምና ባለሙያዎችን አመስግነዋል፡፡
***
Join our social media
👉🏼 Facebook 👉🏼 Telegram
👉🏼 Website 👉🏼 YouTube 👉🏼 TikTok 👉🏼 X

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

30 Jan, 12:07


የ‹‹ሔርኒያ›› ምንነትና መፍትሄው
በዶ/ር በለጠ ሽኩር
አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

30 Jan, 07:35


ዜና እረፍት
የአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የስራ ባልደረባ የሆኑት ወ/ሮ ሰርካለም አሽኔ ደሳለኝ በገጠማቸው ድንገተኛ ህመም ህይወታቸው በማለፉ የሆስፒታሉ አመራሮችና ሰራተኞች የተሰማንን ሃዘን እየገለፅን ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለስራ ባልደረቦቻቸው መፅናናትን እንመኛለን፡፡
አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

27 Jan, 11:20


አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የሚከተለውን የወረቀት አልባ/Digitalization/ አሰራር ለማዘመን፣ለመደገፍና ወደ ART የህክምና ክፍል ለማስፋፋት ያግዝ ዘንድ AHF-Ethiopia የተባለ ግብረሰናይ ድርጅት አንድ ሚሊዮን ሦስት መቶ ሰላሳ አምስት ሺ /1,335000/ ብር የሚያወጡ UPS እና የዲስክ ቶፕ ኮምፒውተሮችን ድጋፍ አድርገዋል፡፡
AHF-Ethiopia ከዚህ በፊት የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገ የሚገኝና በዛሬው እለት ያደረገው ድጋፍ የወረቀት አልባ አሰራርን በማጠናከር ART አገልግሎትን ከፍ በማድረግ የተገልጋይን እርካታ የበለጠ እንደሚጨምርም ተገልጿል፡፡

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

26 Jan, 13:05


ጤና ሚኒስቴር ከአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ጋር በመተባበር የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለጤናማ እናትነት! በሚል መሪቃል የጋራ አካል ብቃት እንቅስቃሴ አካሄደ!
————
ጥር 18/2017 ዓ.ም በአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የስፖርት ማዘውተሪያ ሜዳ ላይ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ፣የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ፣የፊደራል ሆስፒታል አመራሮችና ሃላፊዎች፣የግልና የመንግስት ጤና ተቋማት አመራሮች፣የተለያዩ የስፖርት ማህበራትና አሰልጣኞች፣የጤና ሚኒስትር ዴኤታዎች፤ እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች የተገኙበት መርሃ-ግብር ተካሄዷል።
አለርት ሆስፒታል የህክምና አገልግሎት ከመስጠት በተጨማሪ ባማረና በተዋበ የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታ ላይ ወርሃዊ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እንዲከናወን ከፍተኛ ድርሻ በመወጣት አለሁ የሚልና የአብሮነትና የወንድማማችነት ስሜትን እየፈጠረ መሆኑን ክብርት ሚኒስትሯ እና ሌሎች ተሳታፊዎች አመስግነዋል፡፡
በእለቱ የጤናማ እናትነት ወርን ምክንያት በማድረግ ነፃ የጤና ምርመራና ለእናቶች የተለያዩ ስጦታዎች ተበርክተዋል፡፡

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

23 Jan, 20:57


Invitation to Save Motherhood Month Celebration and Monthly Mass Sport Activity

Dear All,

We are delighted to invite you to the Save Motherhood Month Celebration and Monthly Mass Sport Activity, which will be led by H.E. Dr. Mekdes, along with esteemed State Ministers.

This event aims to highlight the importance of maternal health by promoting safe motherhood and encouraging a healthy lifestyle through sport activities.

Event Details:
Theme: Quality Labor and Delivery for All Women: For a Positive Childbirth Experience
Date: January 26, 2025
Starting Time: 7:00 a.m
Location: ALERT Comprehensive Specialized Hospital
Dress Code: Sport clothes and shoes

We encourage everyone to participate in this important event and help spread awareness about safe motherhood and maternal health. Your presence will contribute to making a positive impact on the lives of women and families.

We look forward to your participation!

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

23 Jan, 10:25


ደም ለግሰው ህይወትን ያድኑ!

በአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሐሙስ
ጥር 15/2017 ዓ.ም እና አርብ ጥር 16/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ጀምሮ ባንዲራው አካባቢ የደም ልገሳ ፕሮግራም ስለሚካሄድ በዚህ የመልካም ተግባር ላይ የሆስፒታሉ ሰራተኞችና ተገልጋዮች ተሳታፊ በመሆን የበኩለዎትን ድርሻ እንዲወጡ እናሳውቃለን፡፡

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

23 Jan, 06:07


በፎቶ የምትመለከቱት ግለሰብ ጥር 4/2017 ዓ.ም በአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በድንገተኛ ህክምና አገልግሎት ገብተው የፅኑ ህክምና ክፍል እርዳታ እየተደረገላቸው ስለሚገኙ ታካሚው በአሁኑ ሰዓት ቤተሰብ ያልተገኘላቸው በመሆኑ ቤተሰባቸውን እና ታካሚውን የምታውቁ ካላችሁ በሆስፒታሉ የጽኑ ህክምና ክፍል ማግኜት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡            
አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል!

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

20 Jan, 07:51


የDay Care ቀዶ ህክምና በአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል
የDay Care ቀዶ ህክምና የሚባለው አንድ ታካሚ ሆስፒታል ከገባበት ጊዜ አንስቶ የ ቀዶ ህክምናውን ጨርሶ የሚወጣው በተመሳሳይ ቀን ውስጥ ሲሆን እና ቀዶ ህክምናው አስቀድሞ ለDay Care surgery የታቀደ ሲሆን ነው፡፡
በአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከአንድ አመት ተኩል ጀምሮ ሲሰራ ቆይቷል፡፡ በዚህም ቀዶ ህክምና ተራቸውን ሲጠብቁ ከነበሩት /Waiting List/ 330 በላይ ታካሚዎች በአጭር ጊዜ ቀዶ ህክምናውን በመስጠት ተራ የሚጠብቁትን ታካሚዎች ቁጥር ለመቀነስ እገዛ አድርጓል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ሁለት እና ሶስት ቀን አልጋ ይዘው ያድሩ የነበሩት ታካሚዎች ቀዶ ህክምናውን በተሰሩበት ቀን ወደቤታቸው ስለሚመለሱ ከአላስፈላጊ ወጪና እንግልት እንዲሁም በሆስፒታል ቆይታ ከሚመጡ ህመሞች /Hospital acquired infectons/ይታደጋሉ፡፡
የሆስፒታሉም አልጋ ለሌሎች ይውላል፡፡

በሆስፒታሉ ሲካሄድ የቆየው ይህ የ Day Care ህክምናወደ ስራ ከመግባቱ በፊት የመመሪያ ማንዋል የተዘጋጀለት ሲሆን እንደሆስፒታሉ አቅም በቂ ዝግጅት ተደርጎበት የተጀመረ ነው፡፡ህክምናውም ለዚህ ህክምና ስርዓት አመቺ በሆኑ እና በ24 ሰዓት ውስጥ ወደቤታቸው መላክ የሚችሉ ወደ 7 ያክል እክሎች /Cases/ ተመርጠው ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡
ታካሚዎችንም ከቀዶ ህክምና በኋላ ሊያጋጥም ከሚችሉ ውስብስብ ችግሮች ለመታደግ በስልክ ጥሪ ያሉበት ሁኔታ ክትትል ይደረግላቸዋል፡፡
ይህ የ Day Care ቀዶ ህክምና የታካሚ ፍሰቱ ከፍተኛ በሆነበት አለርት ኮ/ስ ሆስፒታል ትልቅ ፋይዳም እንዳለው የጠቅላላ ቀዶ ህክምና ክፍል ሃላፊ ዶክተር በለጠ ሽኩር ገልፀዋል፡፡

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

20 Jan, 07:51


የDay Care ቀዶ ህክምና በአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል
Day Care Surgery at Alert Comprehensive Specialized Hospital

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

19 Jan, 20:02


Ethiopia Strengthens Leprosy Case-Finding Efforts

Ethiopia has made remarkable progress in the fight against leprosy, eliminating it as a public health problem in 1999. However, around 3,000 new cases are still reported annually, with 10% resulting in severe disabilities due to late diagnosis.

ALERT Comprehensive Specialized Hospital, recognized by WHO and the Ministry of Health, Ethiopia, is at the forefront of this fight. In 2023, the hospital successfully treated 30% of all new leprosy cases. With WHO’s support, ALERT provides free multidrug therapy and preventive chemotherapy, ensuring patients receive lifesaving treatment.

Dr. Shimeles Niguse, a consultant dermatologist with over 15 years of experience at ALERT, emphasized the hospital’s vital contributions, including its outreach programs to five referral centers across the country. Together with the Ministry of Health, WHO, and partners like ENAPAL, ALERT Hospital continues to combat stigma and raise community awareness, achieving a 7% reduction in new cases and a 25% decrease in severe disabilities between 2022 and 2023.

As a WHO- and Ministry of Health-recognized center of excellence, ALERT remains committed to early diagnosis, treatment, and the elimination of leprosy by 2030.

#LeprosyElimination #WHORecognition #MinistryOfHealthEthiopia #ALERTHospital #HealthcareLeadership

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

19 Jan, 20:01


https://www.afro.who.int/photo-story/ethiopia-strengthens-leprosy-case-finding-bolster-early-diagnosis

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

18 Jan, 09:41


ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለከተራና ለጥምቀት በዓል በሠላም አደረሳችሁ!

አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

17 Jan, 15:39


በአለርት ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በማገልገል ላይ ካሉ ስፔሻሊስት ሀኪሞች ለዛሬ የምናስተዋውቃችሁ ዶ/ር ገረመው ሰንበታ የ አንጎል እና ህብረሰረሰር ቀዶ ጥገና ስፔሻሊስት ናቸው።

***
Introducing the specialist doctors serving at ALERT Comprehensive Specialized Hospital.

Today, we feature Dr. Geremew Senbeta , a specialist in neurosurgery and spinal surgery.

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

17 Jan, 04:23


ማስታወሻ
የአለርት ሆስፒታል ሳምንታዊ የጽዳት ዘመቻ

ዛሬ ጠዋት 2፡00 ሰዓት - 3፡00 ሰዓት

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

16 Jan, 17:42


አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በትስስር ከሚደጋገፍባችው የግል ስፔሻሊቲ ክሊኒኮች እና ሆስፒታል ሀላፊዎች ጋር በአሰራር ላይ ያሉ ክፍተቶችን እና ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ ትኩረት ያደረገ ውይይት አካሄደ።

በውይይት መድረኩ አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከግል ስፔሻሊቲ ክሊኒኮችና ሆስፒታሎች ጋር ያለውን የትስስር አገልግሎት እንደሚያጠናክር የተገለፀ ሲሆን አስራርን ሊያሻሽሉ የሚችሉ የተለያዩ ሃሳቦች ተነስተው ፍሬያማ ውይይት ተደርጓል:: በቀጣይም ይህንን የመሳሰሉ መድረኮች በቋሚነት እንዲቀጥሉ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡ የመድረኩ ተሳታፊዎች ከውይይቱ በኋላ የተለያዩ አገልግሎት መስጫ ቦታዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

16 Jan, 12:02


አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል  ለአዲስ አበባ ፖሊስ አካዳሚ ዋና መምሪያ የተለያዩ ድጋፎችን በማድረጉ ላበረከተው ጉልህ አስተዋፅኦ የምስጋና ምስክር ወረቀት ከታላቅ አክብሮት ጋር ተበርክቶለታል፡፡

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

15 Jan, 08:23


ሰላም ውድ የማህበራዊ ሚዲያ ተከታዮቻችን
ዛሬ ታሕሳስ 07/2017 ዓ.ም ፋና ጤና ቀጥታ ፕሮግራም ስለሚተላለፍ
ከቀኑ 7፡30 እስከ 8፡30 ሰዓት  የሐሞት ጠጠር ህክምና በአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ስለተደረገላቸው አገልግሎት ተገልጋዮች ይመሰክራሉ፡፡
ፕሮግራሙን እንዲከታተሉት ጋብዘነዎታል
!

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

06 Jan, 15:37


ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

04 Jan, 04:43


የክልል ጤና ቢሮ ሃላፊዎች በአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እየተሰሩ ያሉ የጽዱ ጤና ተቋም ፕሮጀክቶችን ጎበኙ

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

31 Dec, 07:01


📞የአለርት ነፃ የጥሪ ማእከል 6880 ይደውሉ
- በነፃ ካሉበት ሆነው መረጃ ይጠይቁ ! እራሶን ካላስፈላጊ እንግልት ይታደጉ

👉🏼በጥሪ ማእከሉ የሚያገኙት አገልግሎቶች

- ሆስፒታላችን ስለሚሰጣቸው አገልግሎቶች ሙሉ መረጃ ማግኘት
- ሆስፒታላችን ሪፈራል የሚቀበላቸው የመንግስት ጤና ጣብያ እና የግል ሆስፒታሎች መረጃዎችን መስጠት
- የተለያዩ ከጤና ጋር የተገናኙ ትምህርቶችን መስጠት
- ካሉበት ሆነው ቀጠሮ ማስቀየር እና የተቀየረው ቀን በፅሁፍ መልእክት መላክ

“የእርሶ ጤና የኛ ተልዕኮ ነው”

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

27 Dec, 14:05


የአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በስሩ ከሚገኙ ኣስራ አንድ catchment ጤና ጣቢያዎች ጋር ውይይት አካሄደ!
***

አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልና ጤና ጣቢያዎች ያላቸውን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር አላማ ባደረገው የውይይድ መድረክ ላይ የተለያዩ የጤና ጣቢያ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች የተገኙ ሲሆን ለሚደረግላቸው የተለያዩ የድጋፍና የክትትል ስራዎች ሆስፒታሉን አመስግነዋል፡፡
Alert Comprehensive Specialized Hospital held discussions with eleven health centers in its catchment area!
Various health center officials and experts attended the forum, which aimed to further strengthen their collaboration with, and thanked the hospital for the various support and monitoring activities that would be done.

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

26 Dec, 08:51


ነገ አርብ ነው!! 🧹

የአለርት ሆስፒታል ሳምንታዊ የጽዳት ዘመቻ
“ጽዱ አካባቢ፤ ጽዱ የጤና ተቋማት ለተሟላ ጤንነት”

ቀን ፡ዘወትር አርብ
ሰዓት ፡ ጠዋት 2፡00 ሰዓት - 3፡00 ሰዓት
ቦታ፡ በሁሉም የስራ ክፍሎች

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

25 Dec, 15:01


ጥቆማ አንድ! በተለያዩ የስራ ክፍሎች ላይ የህክምና ባለሙያ ሳይሆኑ ጋወን ለብሰው የማጭበርበር ስራ የሚሰሩ ግለሰቦች ስላሉ ሰራተኞችም ሆነ ተገልጋዮች ጥንቃቄ
እንድታደርጉ፡፡
ጥቆማ ሁለት! በሆስፒታሉ በተተከሉ የኤቲኤም ማሽኖች አካባቢ ገንዘብ አበድሩኝ፣ ትራንስፈር አድርጉልኝ ለኦፕሬሽን 30 ሺ እና 40 ሺ ተጠይቄ ነው የሚሉ አጭበርባሪዎችም ስለሚስተዋሉ እንደዚህ አይነት ድርጊቶችን ሰራተኞችም ሆነ ተገልጋዮች ሲገጥማችሁ ለጥበቃ ክፍል ፈጥነው እንዲያመለክቱ እናሳውቃለን፡፡
አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

22 Dec, 10:03


የድባቴ ህመም መጨመር የፈጠረው ዓለም አቀፍ ስጋት!
ዶ/ር በረከትፀጋዬ
አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

21 Dec, 13:08


https://youtu.be/7Lf91n5T9wg?si=tEs_kFvFUCLbfGmG

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

20 Dec, 16:31


አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የካይዘን ትግበራውን አስጎበኘ
***
በጤና ሚንስቴር አስተባባሪነት ከ Japan international kaizen (JIK) እና ካይዘን ልዕቀት ማዕከል  technical support grou ፣
ከየካቲት 12 ሆስፒታል ፣ እንዲሁም ከቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ለተውጣጡ የ quality improvement technical (QIT) ባለሙያዎችና ለሌሎች የስራ ክፍል ሰራተኞች ሆስፒታሉ የተገበረውን የካይዘን ተሞክሮ አስጎብኝቷል።
ጉብኝቱ በዋናነት ትኩረት ያደረገው አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ካይዘንን ተግባራዊ በማድረግ ለተገልጋዩ ህብረተሠብ አካባቢውን ምቹ ካደረጉ ሆስፒታሎች አንዱ በመሆኑ ጥሩ ተሞክሮውን ወደሌሎች ሆስፒታሎች ማስፋት እንዲቻል ልምድ ልውውጥ ለማድረግ ታሳቢ ያደረገ ነው።
Alert Comprehensive Specialized Hospital toured its Kaizen center of excellence implementation
***
Under the coordination of the Ministry of Health, the hospital toured the implemented Kaizen experience for experts from Japan International Kaizen (JIK), the Quality Improvement Technical support Group (QIT) from Yekatit 12 and saint Peter Hospital.
Alert Comprehensive Specialized Hospital is one of the hospital that has implemented Kaizen and made its environment more convenient for the user community, and the visit is intended to exchange experiences so that the good experience can be expanded to other hospitals.

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

06 Dec, 12:46


በአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልና በአርማወር ሃንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት ህፃናት ማቆያ ማዕከል ለሚገኙ ህፃናት በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ35ኛ በሃገራችን ለ19ኛ ጊዜ ”ሕፃናት የሚሉት አላቸዉ፤እንስማቸዉ” በሚል መሪ ቃል ዓለም ዓቀፉ የህፃናት ቀን በትናንትናው እለት ተከብሮ ዉሏል፡፡
የሁለቱ ተቋማት የሴቶች፣ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ አካቶ ትግበራ ስራ አስፈፃሚዎች በእለቱ የተገኙ ሲሆን ለወላጅ እናቶችና ህፃናት ተንከባካቢዎች ህፃናት አያያዝ ላይ በተለያዩ ተላላፊ በሽታዎች እንዳይጠቁ የጤና ትምህርትና ለህፃናት ጤንነት ሲባል ተገቢውን ትኩረት መስጠት እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል።
World Children’s Day Celebrated at ALERT Comprehensive Specialized Hospital and Armauer Hansen Research Institute.
Under the theme "Listen to the future. Stand up for children’s rights" the 35th annual global and 19th national celebration of World Children’s Day was marked yesterday at the Children’s Shelter Center shared by ALERT Comprehensive Specialized Hospital and Armauer Hansen Research Institute.
Executives from the Women, Youth, and Social Affairs sectors of both institutions attended the event. Messages were delivered to mothers and child caregivers emphasizing the importance of health education and taking preventative measures to protect children from various infectious diseases. The importance of focusing on children’s health and well-being was also highlighted as a key priority.

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

06 Dec, 10:31


አስደሳች ዜና !

የአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከ Smile train ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር የከንፈርና ላንቃ ክፍተት ላለባቸው ሕጻናት እና አዋቂዎች ነፃ የቀዶ ሕክምና አገልግሎት በመደበኛነት ሳምንቱን ሙሉ እንደሚሰጥ ያውቃሉ?

እንግዲያውስ የከንፈርና ላንቃ ክፍተት ችግር Cleft lip እና Cleft palate ያለባችሁ በመሉ በ 0948898284 በመደወል ወይም ወደ አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በመሔድ መመዝገብ ይችላሉ::

ከአዲስ አበባ ውጭ ለሚመጡ ታካሚዎች የትራንስፖርት እና የምግብ አገልግሎት እንዲሁም ለሚያድሩት ;የአልጋ (መኝታ ) ወጪ ይሸፈናል፡፡

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

05 Dec, 12:16


በአለርት ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በማገልገል ላይ ካሉ ስፔሻሊስት ሀኪሞች ለዛሬ የምናስተዋውቃችሁ ዶ/ር ሳምሶን አሰፋ የ አንጎል እና ህብረሰረሰር ቀዶ ጥገና ስፔሻሊስት ናቸው።

***
Introducing the specialist doctors serving at ALERT Comprehensive Specialized Hospital.

Today, we feature Dr. Samson Asefa, a specialist in neurosurgery and spinal surgery.

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

05 Dec, 09:38


ነገ አርብ ነው!! 🧹

የአለርት ሆስፒታል ሳምንታዊ የጽዳት ዘመቻ
“ጽዱ አካባቢ፤ ጽዱ የጤና ተቋማት ለተሟላ ጤንነት”

ቀን ፡ዘወትር አርብ
ሰዓት ፡ ጠዋት 2፡00 ሰዓት - 3፡00 ሰዓት
ቦታ፡ በሁሉም የስራ ክፍሎች

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

04 Dec, 18:36


ዓለም-አቀፉ የፀረ-ፆታዊ ጥቃት ቀን "የሴቷ ጥቃት የእኔም ነው ፤ ዝም አልልም” በሚል መሪ ቃል በአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ተከበረ

ከጤና ሚኒስቴና አርማወር ሐንሰን ምርምር ተቋም ጋር አብሮ በመሆን
በአለም አቀፍ ለ33ኛ በሃገራቸ‍ን ለ19ኛ ጊዜ የሚከበረው ዓለም-አቀፉ የፀረ-ፆታዊ ጥቃት ቀን "የሴቷ ጥቃት የእኔም ነው ፤ ዝም አልልም” በሚል መሪ ቃል በአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በተለያዩ ዝግጅቶች ታስቦ ውሏል።

በእለቱ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበና የጤና ሚኒስቴር የሴቶች፤ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ አካቶ ትግበራ ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ፋጡማ ሰዒድ ፕሮግራሙ  ላይ በመገኘት መልእክት አስተላልፈዋል።

በመረሃግብሩ ላይ የተከናወኑት ተግባራት በወጣቶች እና ሴቶች ፎረም ኮሚቴነት ላገለገሉ እና ጥሮታ ለወጡ ሰራተኞች እውቅና መስጠት፣ዓለም-አቀፉን የፀረ-ፆታዊ ጥቃት ቀን በተመለከተ ሪፖርትና ፆታዊ ጥቃት አልፈጽምም ሲፈጸም ሳይ ዝም አልልም የሚሉ  ቃል መግባት ናቸው።

The International Day for the Elimination of Violence Against Women Observed at ALERT Comprehensive Specialized Hospital

Under the theme “Her Fight is My Fight: I Will Not Stay Silent,” the International Day for the Elimination of Violence Against Women was commemorated at ALERT Comprehensive Specialized Hospital. This year’s event was held in collaboration with the Ministry of Health and Armauer Hansen Research Institute as part of the 33rd global and the 19th national observance of the day.

The program featured participation from state Minister of Health, W/ro Frehiwot Abebe, and W/ro Fatuma Said, the Executive Director of Women, Youth, and Social Affairs at the Ministry of Health, who delivered messages emphasizing the importance of the day.

The activities included recognition for committee members of the Youth Forum, awarding certificates to retiring staff members, and a report highlighting the significance of the day. Key messages, such as “I will not stay silent; I will not commit violence or allow it to happen,” were shared to raise awareness and inspire action against gender-based violence.

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

28 Nov, 16:45


አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአለም አቀፍ የፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች የጀርሞች መለመድ የግንዛቤ ማስጨበጫ  ሳምንትን አከበረ።

አለም አቀፍ የጸረ ተህዋስያን መድሀኒቶች በጀርሞች መላመድ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሳምንት “ህዳር 15 - 19" እናስተምር፣ እናሳውቅ፣ አሁን እንተግብር" በሚል መሪ ቃል እየተከበረ ይገኛል።

ይሄን ምክንያት በማድረግ የተለያዩ የሆስፒታሉ የስራ ክፍል ሃላፊዎችና የህክምና ባለሙያዎች በተገኙበት በዛሬው እለት ውይይትና ግንዛቤ መስጫ መድረክ  ተካሄዷል፡፡

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

28 Nov, 12:26


ነገ አርብ ነው!! 🧹

የአለርት ሆስፒታል ሳምንታዊ የጽዳት ዘመቻ
“ጽዱ አካባቢ፤ ጽዱ የጤና ተቋማት ለተሟላ ጤንነት”

ቀን ፡ዘወትር አርብ
ሰዓት ፡ ጠዋት 2፡00 ሰዓት - 3፡00 ሰዓት
ቦታ፡ በሁሉም የስራ ክፍሎች

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

28 Nov, 06:14


ይህ ሳምንት ማለትም (ህዳር 09- 15 2017 ) ዓ.ም የአለም አቀፍየፀረተሀዋስያን መደኃኒቶች በጀርሞች መለመድ የግንዛቤማስጨበጫ ሳምንት ተከብሮ የምዉልብት ነዉ፡፡

በአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የፀረተሀዋስያን ስተዋርድሺፕ ኮሚቴ የተለያዩ ተግባራትንባለፉት አመታት ስፈፅም ቆይተዋል፡፡

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

27 Nov, 15:05


የአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በተመረጡ የህክምና ዘርፎች የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ ይገኛል።
የአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በቆዳ ህክምና፣ በፕላስቲና ሪኮንስትራክቲቭ ሰርጀሪ ህክምና፣ በአይን ህክምና፣ በድንገተኛና ፅኑ ህሙማን ህክምና፣ በአጥንት ህክምና፣ በኒውሮ ሰርጀሪ/ስፓይን ህክምና የልህቀት ማዕከል ለመሆን ከፍተኛ ባለሞያዎችን ያካተተ ኮሚቴ በማዋቀር እየሰራ ይገኛል።
ኮሚቴው እየተገነቡ ያሉትን ትልልቅ መሰረተልማቶች በመጎብኘት ጤና ሚኒስቴርን አመስግኖ ሞያዊ አስተያየት ሰጥቷል።
ኮሚቴው ቀጣይ ትኩረት የሚፈልጉ የአገልግሎት አይነቶች ልየታ፤ የሰው ሃይልና የሚያስፈልጉ ግብአቶች ላይ እቅድ በማውጣት እንዲሁም ከጤና ሚኒስቴርና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት የተቋሙን ማነጅመንት እንደሚያግዝ ገልጸዋል፡፡
Alert Comprehensive Specialized Hospital is working to become a center of excellence in selected medical fields.
Alert Comprehensive Specialized Hospital is working by setting up a committee that includes senior experts to become a center of excellence in dermatology, plastic & reconstructive surgery, ophthalmology, emergency and intensive care, orthopedics, neurosurgery/spine medicine.
The committee visited the big infrastructures under construction and thanked the Ministry of Health and gave a professional opinion.
The Committee planned to work with ministry of health and other stakeholders on identifying focus area, plans on manpower and equipments needed for centers.

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

26 Nov, 06:44


ይህ ሳምንት ማለትም (ህዳር 09- 15/2017ዓ.ም ) የአለም አቀፍየፀረ-ተህዋስያን መደኃኒቶች በጀርሞች መለመድ የግንዛቤማስጨበጫ ሳምንት ተከብሮ የሚውልበት ነዉ፡፡
በአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የፀረ-ተህዋስያን ስተዋርድሺፕ ኮሚቴ የተለያዩ ተግባራትን ባለፉት አመታት ሲፈፅሙ ቆይተዋል፡፡
ከእነዚህ ተግባራት ዉስጥ በተለያዩ የሆስፒታላችን ታካሚ መገልገያ ክፍሎች ስለፀረ-ተህዋስያን መደኃኒቶች በጀርሞች መለመድ የግንዛቤማስጨበጥ እና የሆስፒታል ዋርዶች ከጀርም ማንፃት የሚጠቀሱ ናቸዉ፡፡

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

25 Nov, 06:31


አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የመጀመሪያውን ሲኒየር ክሊኒካዊ መድረክ አካሄዷል።
የአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከ ሲኒየር ዶክተሮች፣ ወጣት ዶክተሮች እና ሌሎች የጤና ባለሙያዎች ጋር በጋራ በመሆን የመጀመርያውን ሲኒየር ክሊኒካል ፎረምን በተሳካ ሁኔታ አካሄዷል፡፡
የመድረኩ ቁልፍ አላማዎች፡-

1. ራዕይ እና ተልእኮ ማሳወቅ፡- የሆስፒታሉን ሰራተኞች ከሆስፒታሉ ተልዕኮው፣ ራእይ እና እቅድ ጋር በማጣጣም የጋራ ተግባርን ለማነሳሳት፡፡
2. ትብብርን ማጠናከር፡ ጠንካራ የእርስ በርስ ግንኙነቶችን መገንባት እና በሁሉም ደረጃዎች ክሊኒካዊ አመራርን ማሳደግ።
3. የላቀ ደረጃን ማወቅ፡- ከፍተኛ አፈጻጸም ያላቸውን ክፍሎች እና በሆስፒታሉ ስኬት ውስጥ ትልቅ ሚና የተጫወቱ ግለሰቦችን እውቅና መስጠት ናቸው።
የዝግጅቱ ዋና ዋና ክንውኖች፡-

• የልምድ መጋራት፡ ሲኒየር እና ወጣት ሐኪሞች ስለ ጉዞዎቻቸው፣ ተግዳሮቶቻቸው ፣ ስለ የስራ ልምምድ እና የ ፈጠራ ስራዎች ውይይት አድርገዋል።
• በክሊኒካል ሊደርሺፕ ላይ ስልጠና፡ ስልጠናው ከጤና ሚኒስቴር በክቡር ዶ/ር ሰለሞን የተሰጠ ሲሆን ጠንካራ አመራር በ ጤና አሰጣጥን ስርአት ላይ ያለውን አዎንታዊ ሚና አጽንኦት ሰጥቷል።
• እውቅና እና ስንብት፡- ሆስፒታሉ ለነባር እና ለቀድሞ የክፍል ሀላፊዎች እና ሌሎች ግለሰቦች በልዩነት ላሳዩት ልዩ ስራ እውቅና የሰጠ ሲሆን በልዩ ጥንካሬ አገልግለው ወደ ጡረታ ለወጡት የአጥንት ህክምና ስፔሻሊስት ሀኪም ዶ/ር ይኸይስን የሽኝት ፕሮግራም ተደርጓል።
ሲኒየር ክሊኒካል ፎረም ለሆስፒታሉ ወደ ልዕቀት ጉዞ፣ የትብብር ባህልን፣ ፈጠራን እና የጋራ ዓላማን በማጎልበት ላይ ትልቅ ምዕራፍ ነው።

ALERT Comprehensive Specialized Hospital Hosts Its First Senior Clinical Forum
ALERT Comprehensive Specialized Hospital successfully hosted its First Senior Clinical Forum, bringing together senior physicians, young doctors, and other healthcare professionals in an atmosphere of knowledge sharing and collaboration.
The forum focused on key objectives:
1. Communicating Vision and Mission: Aligning the hospital community with its mission, vision, and strategic goals to inspire collective action.
2. Strengthening Collaboration: Building stronger interpersonal relationships and fostering clinical leadership across all levels.
3. Recognizing Excellence: Celebrating the contributions of high-performing departments and individuals who have played pivotal roles in the hospital’s success.
Highlights of the event included:
• Experience Sharing: Senior and young physicians engaged in meaningful discussions about their journeys, challenges, and innovations in clinical practice.
• Training on Clinical Leadership: Delivered by His Excellency Dr. Solomon from the Ministry of Health, the training emphasized the role of strong leadership in advancing healthcare delivery.
• Recognitions and Farewells: The hospital recognized current and former departments, and individuals for their exceptional performance, including a heartfelt farewell to Dr. Yeheyes, a retired orthopedic surgeon who served with distinction.
The Senior Clinical Forum marks a significant milestone in ALERT’s journey toward excellence, fostering a culture of collaboration, innovation, and shared purpose.

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

22 Nov, 12:54


ጤና ሚኒስቴር የመፀዳጃ ቤት እና የአለም እጅ መታጠብ ቀንን ከአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ጋር በጋራ በመተባበር በሆስፒታሉ አከበረ።
***
በዓሉ በአለም አቀፍ ደረጃ ለ16ኛ ጊዜ በአገር አቀፍ ለ15ኛ "መፀዳጃ ቤትን በንፅህና መያዝና መጠበቅ ዘመናዊነት ነው " " እጃችን ጤናችን " በሚል መሪ ቃል በዓሉ በድምቀት የተከበረ ሲሆን በፕሮግራሙ ላይ ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ ባለድራሻ አካላት፣ ሲቪል ማህበራቶችና የተለያዩ የመንግስትና የግል ድርጅት ከፍተኛ ሃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
የአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዋና ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ሽመልስ ገዛኸኝ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት አስተላልፈው ሆስፒታሉ በጽዱ ኢኒሼቲቭ ተግባራት ላይ እያከናወናቸው ያሉትን ስራዎች አብራርተዋል፡፡
በእለቱ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ድጉማ የተገኙ ሲሆን ጤና ተቋማትን ጽዱ፣ምቹና ማራኪ በማድረግ ጤናማ ማህበረሰብን ለመፍጠር የተሻሻሉና በቂ ውሃ ያላቸው መጸዳጃ ቤቶች እየተሰሩ መሆናቸውን ጠቅሰው አጋርነትና ትብብርን በማጠናከር እየተሰራ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡
በተጨማሪም የውሃና ኢነርጅ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ በፕሮግራሙ ላይ የተገኙ ሲሆን የውሃወለድ በሽታዎችን ለመከላከልና ወጪን ለመቀነስ የሚያስፈልጉ መጸዳጃቤቶችን መገንባትና በንጽህና መያዝ ዘመናዊነት መሆኑን ገልፀዋል፡
በመጨረሻም የእጅ መታጠብና የመፀዳጃቤትን የሚገልፁ ኤግዚቭሽኖችን እና በሆስፒታሉ የተሰሩ ክንውኖችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

17 Nov, 06:01


አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እና አርማወር ሐንሰን ምርምር ኢንስቲትዩት የተመዘገበውን የስፖርት ስኬት በጋራ አከበሩ።
***
የጤና ቡድን ወክለው በስፓርታዊ ውድድር ላይ የተሳተፋት የ አለርት ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እና አርማወር ሐንሰን ምርምር ኢንስቲትዩት በ18ኛው የአዲስ አበባ ወጣቶች ውድድር በወንዶች በእግር ኳስ እና  በሴቶች የእጅ ኳስ የዋንጫ አሸናፊ በመሆን የሁለቱን ተቋማት ስም ከፍ ብሎ እንዲጠራ አድርገዋል።

ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋፅኦ የሁለቱም ተቋማት ከፍተኛ ኋላፊዎች አመስግነው ለአጠቃላይ ለስፖርቱ አባላት  የስፖርት ቱታና የምስጋና እውቅና ሰርተፍኬት አበርክቶላቸዋል።

በመጨረሻም የሁለቱ ተቋሟት የስፖርት የመተዳደሪያ መነሻ ሰነድ፣ የጋራ የእቅድ እና የስፖርቱ ታሪካዊ አመሰራረት ላይ የጋራ ውይይት ተደርጎበታል።

——————
ALERT Comprehensive Specialized Hospital and Armauer Hansen Research Institute Celebrate Sports Achievements

Representing the health sector, the institutions participated in the 18th Addis Ababa Youth Sports Competition, where the men’s football team and the women’s handball team both emerged as champions, elevating the names of both organizations.

The leadership of both institutions expressed gratitude for the outstanding contributions of their teams and awarded certificates of recognition and appreciation to all athletes. They emphasized the importance of these achievements and the significant role they play in raising the profile of their institutions.

The event concluded with discussions on a joint sports management framework, collaborative planning, and a historical review of their sports programs.

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

15 Nov, 16:44


በአለርት ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በማገልገል ላይ ካሉ ስፔሻሊስት ሀኪሞች ለዛሬ የምናስተዋውቃችሁ ዶ/ር አለም ገዛቸው፣ የ ህፃናት ህክምና ስፔሻሊስት ናቸው።

***
Get to know the specialist doctors serving at ALERT Comprehensive Specialized Hospital.

Dr. Alem Gezachew is a pediatrician.

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

14 Nov, 14:08


የአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልና አርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት የማኔጅመንት አባላትና ሰራተኞች በሁለቱ ተቋማት እየተሰሩ ያሉ የፅዱ ጤና ተቋም፣ እየተገነቡ ያሉ ግንባታዎች እና ከ70 በላይ የተለያዩ ዝርያ ያላቸውና ለመድኃኒትነት የሚያገለግሉ እፅዋቶች ማዕከል የሆነውን ALERT-AHRI botanical garden ጎበኙ።
The management members and staff of Alert Comprehensive Specialized Hospital and Armauer Hansen Research Institute visited the TSEDU health facility work, the Building under construction, and the ALERT-AHRI botanical garden which is the center of more than 70 different species of medicinal plants.

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

14 Nov, 08:25


ነገ አርብ የ አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሳምንታዊ የጽዳት ዘመቻ በሁሉም የስራ ክፍሎች ይካሄዳል!
“ጽዱ አካባቢ፤ ጽዱ የጤና ተቋማት ለተሟላ ጤንነት”

ሰዓት ፡ ጠዋት 2፡00 ሰዓት - 3፡00 ሰዓት

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

11 Nov, 17:01


በአለርት ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በማገልገል ላይ ካሉ ስፔሻሊስት ሀኪሞች ለዛሬ የምናስተዋውቃችሁ ዶ/ር ፌቨን ፈለቀ ፣ የአይን ህክምና ስፔሻሊስት ናቸው።

***
Get to know the specialist doctors serving at ALERT Comprehensive Specialized Hospital.

Dr. Feven Feleke is an Ophthalmologist.

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

09 Nov, 03:11


የአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከCBM ጋር በመተባበር ለብሔራዊ የአይነ-ስውራን ማህበር አባላት ስልጠና አድርጓል።

በስልጠናው የእይታ ችግሮች መጠንና ምክንያቶች፣ እንዴት እና መቼ መከላከል እንደሚቻል እና ከአይነ-ስውርነት በኋላ እራሳቸውን እንዴት ማሻሻል እንደሚችሉ ማስገንዘብ ተችሏል።

ለዚህም ሁሉም ተቋማት ለአካል ጉዳተኞች ምቹ እንዲሆኑ ተደርገው መሰራታቸውን ማረጋገጥ፣ የተሻለ እይታ እንዲያገኙ የተለያዩ ድጋፍ ሰጭ መሳሪያዎችን ማቅረብ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል፡፡
ALERT Comprehensive Specialized Hospital, in collaboration with CBM, provided training for members of the National Association of the Blind.

The training focused on understanding the extent and causes of vision problems, how and when to seek preventive measures, and ways to adapt and improve after experiencing blindness.

It was also emphasized that all institutions should ensure accessibility for individuals with disabilities and that providing various supportive tools is necessary to help them achieve better vision

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

08 Nov, 15:45


የአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሰራተኞች ለተገልጋዮችም ሆነ ለሰራተኞች ምቹ፣ውብና ማራኪ የስራ ቦታዎችን ለመፍጠር ሳምንታዊ የጽዳት ዘመቻዎችን አካሄደዋል!
                                                      
The staff at ALERT Comprehensive Specialized Hospital have conducted weekly cleaning campaigns to create comfortable, pleasant, and attractive workspaces for both clients and employees!

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

07 Nov, 03:43


በአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በቤተሰብ ህክምና እና የማህበረሰብ ጤና የስራ ክፍል የተመራ የህክምና ቡድን ጥቅምት 27/2017 ዓ.ም በረጲ የደረቅ ቆሻሻ ሀይል ማመንጫ ድርጅት ለሚሰሩ ሰራተኞች ቦታው ድረስ በመሄድ የሳንባ ካንሰር ቅድመ ምርመራና የምክር አገልግሎት አድርጓል፡፡
በዚህም የድርጅቱ ሰራተኞች ስለተደረገላቸው መልካም ስራ ሆስፒታሉን አመስግነዋል፡፡
                                                   On November 6/2024, a medical team led by the Department of Family Medicine and Community Health at Alert Comprehensive Specialized Hospital went to the site for lung cancer screening and counseling for the workers working at the Solid Waste Power Generation Company.
The employees of the organization thanked the hospital for the good work done to them.

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

06 Nov, 17:59


በአለርት ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በማገልገል ላይ ካሉ ስፔሻሊስት ሀኪሞች ለዛሬ የምናስተዋውቃችሁ ዶ/ር ጉተታ ገ/ሚካኤል ፣ የአይን ህክምና ስፔሻሊስት እና የግላኮማ ሰብ ስፔሻሊስት ናቸው።

***
Get to know the specialist doctors serving at ALERT Comprehensive Specialized Hospital.

Dr. Guteta Gebremichael is an Ophthalmologist and a glaucoma subspecialist.

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

05 Nov, 08:14


በአለርት ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በማገልገል ላይ ካሉ ስፔሻሊስት ሀኪሞች ለዛሬ የምናስተዋውቃችሁ ዶ/ር ቤዛዊት ገዛኀኝ ፣ የአይን ህክምና ስፔሻሊስት ናቸው።

***
Get to know the specialist doctors serving at ALERT Comprehensive Specialized Hospital.

Dr. Bezawit Gezahegn is an Ophthalmologist.

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

04 Nov, 07:49


"የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ክብካቤ እመርታ ለተፋጠነ የዘላቂ ልማት ግቦች ስኬት"  በሚል መሪ ቃል 26ኛው የጤና ዘርፍ ዓመታዊ ጉባዔ 
ላይ የአለርት ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የበጀት አመት ዋና ዋና አፈፃፀሙን በኤግዚቢሽን መርሀ-ግብር ለጉባዔው ተሳታፊዎች አቅርቧል እንዲሁም የሆስፒታላችን የሰራተኛ የማትጊያ /Incentive/ ስትራቴጂክ  ተሞክሮ ለጉባኤው ተሳታፊዎች በሰው ሀብት ልማት ዳይሪክቶሬት በኩል  ቀርቧል።

The 26th Annual Health Sector Conference with the theme "Primary Health Care Improvement for Accelerated Achievement of Sustainable Development Goals" 

Alert Comprehensive Specialized Hospital presented the main performance of the fiscal year to the participants of the conference through the exhibition program and the strategic experience of our hospital's employee incentive was presented to the participants of the conference through the Directorate of Human Resource Development.

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

01 Nov, 17:10


አስደሳች ዜና!

የአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከ Smile train ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር የከንፈርና ላንቃ ክፍተት ላለባቸው ሕጻናት እና አዋቂዎች ነፃ የቀዶ ሕክምና አገልግሎት በመደበኛነት ሳምንቱን ሙሉ እንደሚሰጥ ያውቃሉ?

እንግዲያውስ የከንፈርና ላንቃ ክፍተት ችግር Cleft lip እና Cleft palate ያለባችሁ በመሉ በ 0948898284 በመደወል ወይም ወደ አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በመሔድ መመዝገብ ይችላሉ::

ከአዲስ አበባ ውጭ ለሚመጡ ታካሚዎች የትራንስፖርት እና የምግብ አገልግሎት እንዲሁም ለሚያድሩት ;የአልጋ (መኝታ ) ወጪ ይሸፈናል፡፡
***
Oduu gammachiisaa!

Hospitaalli ALERT Comprehensive specialized, Smile train Ethiopia waliin ta’uun, daa’immanii fi ga’eessota baqaqa laagaa fi hidhii qabaniif tajaajila baqaqsanii yaaluutiin sirreessuu bilisaan kennaa Jira.

Kanaafuu, yoo namoota rakkoo baqaqa laagaa fi hidhii qabaniif yaala tolaa barbaaddan lakkoofsa bilbilla: 0948898284 irratti bilbiluun ykn Hospitaala ALERT Comprehensive specialized dhaquun tajaajila argachuu ni dandeessu.

Maamiltoota Finfinneen ala dhufaniif kaffaltiin geejjibaa fi nyaataa ni kaffalama, akkasumas warra siree qabatanii buluu isaan barbaachisuuf baasiin siree ni kaffalamaaf.

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

01 Nov, 09:55


የአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ጽዱ አካባቢና ጽዱ የጤና ተቋምን ለመፍጠር ሰራተኞችንና ተገልጋዮችን በማሳተፍ ሳምንታዊ የጽዳት ዘመቻ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡
Alert Comprehensive Specialized Hospital is conducting a weekly cleaning campaign involving employees and customers to create a clean environment and a clean health facility.

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

26 Oct, 08:18


ለሆስፒታሉ የሥራ ክፍል ኋላፊዎች፤ የዲሲፕሊንና የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎች የፌደራል መንግስት ሠራተኞች አዋጅ ቁ 1064/2010ና ደንብ ቁ 77/1994 ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ። ስልጠናው በሆስፒታሉ የህግ ዳይሬክቶሬት አቶ ፍቅረማርያም ስዩም የተሰጠ ሲሆን ከህግ አተገባበር አንፃር ሊከሰቱ የሚችሉ ችግሮችን ቅድመ መከላከል ላይ በመስራት የህግ የበላይነትን በማስከበር የተገልጋዮችን እርካታ በመጨመር ህጎችን ማስታወስ አስፈላጊ እንደሆነም በስልጠናው የተነሱ ነጥቦች ናቸው።
A capacity-building training was provided to the hospital’s department heads, disciplinary, and grievance committees on Federal Employees Proclamation No. 1064/2010 and Regulation No. 77/1994.
Led by Mr. Fikremariam Seyoum, Director of the Legal Directorate, the training focused on preventing potential legal issues, upholding the rule of law, and enhancing service user welfare. It emphasized the importance of legal awareness and compliance.

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

25 Oct, 18:32


በ አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የሚሰሩ ስፔሻሊስት ሀኪሞችን አንድ በ አንድ እናስተዋውቃችሁ።

ዶ/ር ህላዊ ተዋበ የአጥንት ቀዶ ጥገና ስፔሻሊስት፣
የውስብስብ ስብራትና የመገጣጠሚያ ቅየራ ሰብ-ስፔሻሊስት ናቸው።

***

Get to know the specialist doctors working at ALERT Comprehensive Specialized Hospital, one by one.

Dr. Helawi Tewabe is an Orthopedic surgeon, Complex Trauma Pelvic/ Acetabulum and Arthroplasty Sub-Specialist

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

25 Oct, 15:38


የአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሰራተኞች ለተገልጋዮችም ሆነ ለሰራተኞች ምቹ፣ውብና ማራኪ የስራ ቦታዎችን ለመፍጠር ሳምንታዊ የጽዳት ዘመቻዎችን አካሄደዋል!
Alert Comprehensive Specialized Hospital staffs have conducted weekly cleaning campaigns to create comfortable, beautiful and attractive workplaces for both clients and staffs!

ALERT Comprehensive Specialized Hospital

25 Oct, 06:48


ተጠሪነቱ ለጤና ሚኒስቴር የሆነው አለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በተለያዩ የስራ ክፍሎች ውስጥ ካይዘንን ከፅዱ ኢኒሼቴቭ ጋር በማቀናጀት እየተገበረ ነው።

የጤና ሚኒስቴር፣የጃፓን አለማቀፍ ትብብር ድርጅት፣የኢትዮጵያ የካይዘን የልዕቀት ማዕከል ከፍተኛ ባለሙያዎች በአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እየተተገበረ ያለውን የካይዘን አፈፃፅም ጉብኝት አድርገዋል፡፡ 

 ALERT Comprehensive Specialized Hospital, accountable to the Ministry of Health, is implementing Kaizen alongside the Clean Initiative across various departments.

High-level experts from the Ministry of Health, the Japan International Cooperation Agency (JICA), and the Ethiopian Kaizen Center of Excellence visited the hospital to observe the ongoing implementation of Kaizen.