Kafa Zone Government Communication Affairs

@ahkafazgcaffairs


Kafa Zone Government Communication Affairs

23 Oct, 17:42


ሀገሪቱ የያዘቹን ህልምና ራዕይ የጋራ በማድረግ የሀገራችንን የብልጽግና ጉዞ ማሳለጥ ከሁሉም አመራር ይጠበቃል፦ አቶ የሺዋስ ዓለሙ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ ።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የካፋ ዞን የ3ኛ ዙር የመካከለኛ አመራሮች "የህልም ጉልበት ለእመርታዊ ዕድገት" በሚል ርዕስ ሲሰጥ የነበረው ሥልጠና ቀጥሏል ።

በዛሬው የስልጠና ውሎ "የህልም ጉልበት ለእመርታዊ ዕድገት" በሚል ርዕስ ስለ ሀገራዊ ህልም ምንነትና አስፈላጊነት ዙሪያ ገለፃና ማብራሪያ ተደርጓል።

በመቀጠል ገለፃውን መሰረት አድርጎ የቡድን ውይይት በቡድን አወያዮች አማካይነት እንዲካሄድ ተደርጓል።

በመጨረሻም የዕለቱ የሥልጠና መድረክ በክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊው በአቶ የሺዋስ ዓለሙ ማጠቃለያ ተደርጎ መቋጫ ያገኘ ሲሆን ስልጠናው በነገው ዕለትም የሚቀጥል ይሆናል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የካፋ ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው ።
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፦
ፌስቡክ ገፃችንን
https://www.facebook.com/kfzgca
የቴሌግራም ቻናላችንን
https://t.me/ahkafaZGCAffairs
ዩቲዩብ ቻናላችንን
@KaffaZoneCommunicationAffairs
የቲክቶኮ ቻናላችንን
https://vm.tiktok.com/ZMrxuoNNL/
Like, comment ,share በማድረግ ድረገፃችንን ይወዳጁ ።

Kafa Zone Government Communication Affairs

22 Oct, 18:37


የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ከቻይናው ኮሙኒስት ፓርቲ ተወካይ እና ከሀገሪቱ ምክትል ትምህርት ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሃላፊ እና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ በቻይና ምክትል ትምህርት ሚኒስትር እና የቻይና ኮሙኒስት ፓርቲ ተወካይ ዉ ያን የተመራ ልዑክ ጋር ተወያይተዋል።

ሁለቱ የስራ ኃላፊዎች በፓርቲ ለፓርቲ ግንኙነት ብሎም በሁለቱም ሀገራት በተመዘገቡ የለውጥ ስራዎች ዙሪያ በዝርዝር መክረዋል።

አቶ አደም ፋራህ በዚህ ወቅት እንዳሉት እየጎለበተ የመጣው የሁለቱ ፓርቲዎች ወዳጅነት እና ስትራቴጂካዊ አጋርነት የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው።

ባለፉት የለውጥ ዓመታት ኢትዮጵያ እየተገበረች ላለው ሁሉን አቀፍ ሪፎርም ስኬታማነት የቻይና ኮሙኒስት ፓርቲ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጉን አስታውሰው፤ የትምህርት ዘርፉን ለአብነት ጠቅሰዋል።

በፓርቲው የሚመራው የቻይና መንግስት በተለይም በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና እንዲሁም የነጻ ትምህርት ዕድል በመስጠት በአቅም ግንባታ ስራዎች ላይ ለተጫወተው ቁልፍ ሚና ዕውቅና ችረዋል።

ይህም የሁለቱን ፓርቲዎች ስትራቴጂካዊ አጋርነት እና ትብብር ፍሬያማነት የሚያሳይ መሆኑን በመጥቀስ አድንቀዋል።

ባለፉት ስድስት የለውጥ ዓመታት ኢትዮጵያን በፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ተቋማዊ የሪፎርም ስራዎች የተመዘገቡ ተጨባጭ ለውጦችን በተመለከተም በዝርዝር አብራርተውላቸዋል።

የቻይና ምክትል ትምህርት ሚኒስትር እና የቻይና ኮሙኒስት ፓርቲ ተወካይ ዉ ያን በበኩላቸው፥ ኢትዮጵያን ሁነኛ እና ስትራቴጂካዊ አጋር ሀገር አድርገን እንቀጥላለን ብለዋል።

የሁለቱ ፓርቲዎች ጠንካራ ግንኙነት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ጠቅሰው፤ ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ለተመዘገበው የለውጥ ጉዞና ስኬት የለውጡ አመራር ያሳየውን ቁርጠኝነትም አድንቀዋል።

የቻይና መንግስት እና ፓርቲያቸው ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአፍሪካ ሀገራት ጋር የጋራ ዕድገትና ብልጽግና ላይ የተመሰረተ ሁሉን አቀፍ ግንኙነትን ለማጠናከር አበክረው እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።

ፓርቲያቸው የኢትዮ-ቻይና በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ሁሉን አቀፍ ስትራቴጂካዊ ግንኙነት ይበልጥ እንዲጎለብት ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ነው የተናገሩት።

የቻይና ኮሙኒስት ፓርቲ ያሳለፋቸውን የውሳኔ ሃሳቦች ይዘትና ውጤቶች በተመለከተም በዝርዝር ማብራራታቸውን ከፓርቲው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የካፋ ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው ።
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፦
ፌስቡክ ገፃችንን
https://www.facebook.com/kfzgca
የቴሌግራም ቻናላችንን
https://t.me/ahkafaZGCAffairs
ዩቲዩብ ቻናላችንን
@KaffaZoneCommunicationAffairs
የቲክቶኮ ቻናላችንን
https://vm.tiktok.com/ZMrxuoNNL/
Like, comment ,share በማድረግ ድረገፃችንን ይወዳጁ ።