ሶስተኛው ምዕራፍ የዳሸን ከፍታ የስራ ፈጠራ ቅድመ-ውድድር ሥልጠና በአዲስ አበባ ከተማ ተሰጠ የዳሸን ባንክ የቺፍ ስትራቴጅ ኦፊሰር ተወካይ አቶ ወልደማርያም ደረሰ ባንኩ የሰራ እድልን ለመፍጠር የሚያግዝ ፕሮጀክት ቀርጾ እየሰራ መሆኑን ገልጸው፤ የስራ ፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን በፋይናንስ እያገዘ እንደሆነም አስረድተዋል።
ዳሸን ባንክ በስራ ፈጠራ ዘርፍ የበኩሉን አስተዋፅኦ ለማበርከት እየተገበረ ባለው ዳሸን ከፍታ የስራ ፈጠራ ውድድር ከመካሄዱ በፊት የሚሰጠው ስልጠና በተለያዩ ከተሞች እንደተሰጠም አስታውሰዋል።
የአዲስ አበባ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጅ ልማት ቢሮ በስማርት ሲቲ የአቅም ግንባታና ስልጠና ዳይሬክተር አቶ አመሐ ሲሳይ በበኩላቸው ዳሸን ባንክ በዘርፉ እያበረከተ ያለው ጉልህ አስተዋጽኦ የሚመሰገን እንደሆነ ተናግረዋል።
ቢሮው ሁልጊዜም ከባንኩ ጎን እንደሚቆም ያመላከቱት አቶ አመሐ አስፈላጊውን እገዛ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውንም ተናግረዋል ።
ዳሸን ባንክ ከውድድሩ በፊት ለሰልጣኞች ተግባራዊ ሥልጠና ለመስጠት በተለያዩ ከተሞች እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው ዳሸን ባንክ አማካሪ ድርጅት ቀጥሮ ውጤታማ ስራ እያከናወነ ይገኛል፡፡
ሥልጠናው የስራ-ፈጠራ ሃሳብ ያላቸው ተወዳዳሪዎች ሃሳባቸውን በምን መልኩ ማቅረብና ወደ ሥራ መቀየር እንዳለባቸው የሚያግዝ ነው፡፡
የዘንድሮው ቅድመ-ውድድር ስልጠና ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በደሴ፣ መቀሌ፣አዳማ፣ድሬዳዋ፣ወላይታ፣ ሃዋሳና ጅማ ተሰጥቷል፡፡
ስልጠና ከተሰጠ በኋላ ሰልጣኞቹ የፈጠራ መነሻ ሃሳባቸውን በፅሁፍ በ
[email protected] በኩል እንዲያቀርቡ ይደረጋል፡፡