Min Addis?

@min_ddis


ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ሚዛናዊ ፣ አዝናኝ እና አስተማሪ የሆኑ ወሬዎች የሚለቀቁበት የኢንፎቴይንመንት ቻናል ነው

Min Addis?

22 Oct, 09:25


በዚህ ፈተና ውስጥ እያለፋችሁ ያላችሁ ሁሉ ፈጣሪ ያበርታችሁ🙏

ለፍቶ አዳሪው ለዘመናት የለፋበት ንብረት ሲወድም ማየት በጣም ልብ ይሰብራል። በመርካቶ ሸማ ተራ አከባቢ የተከሰተው የእሳት አደጋ እና ያስከተለው ውድመት እጅግ ልብ የሚሰብር ነው::
መርካቶ የሁላችንም ናት!
@min_ddis

Min Addis?

22 Oct, 05:43


መርካቶ የእሳት አደጋው የደረሰበት አካባቢ
@min_ddis

Min Addis?

21 Oct, 20:08


በመርካቶ ሸማ ተራ አከባቢ የተከሰተውን የእሳት አደጋ እስከ አሁን መቆጣጠር ባለመቻሉ አሁንም ድረስ የአደጋ መከላከል ሰራተኞች በሄሊኮፕተር በመታገዝ ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ይገኛል ።
@min_ddis

Min Addis?

21 Oct, 19:47


"በመርካቶ ሸማ ተራ አከባቢ የተከሰተውን የእሳት አደጋ ለማጥፋት ሄሊኮፕተር ለመጠቀም እየጣርን ነው":- ከንቲባ አዳነች አበቤ

Min Addis?

20 Oct, 18:46


ከንቲባ አዳነች አቤቤ "የ97 የኮንዶሚኒየም ተመዝጋቢዎች የሚባል አናውቅም " አሉ‼️

ይህ የተባለው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችና ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ ነው።

በብሔራዊው ቴሌቪዥን ጣቢያ በተሰራጨውና ትኩረቱን የኮሪደር ልማት ላይ ባደረገው በዚህ ውይይት የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ ( ኢሕአፓ ) የአዲስ አበበ ኮሚቴ ሰብሳቢ አበበ አካሉ የ97 ተመዝጋቢዎችን የተመለከተ ጥያቄ ይሰነዝራሉ።

ፖለቲከኛው ጥያቄያቸውን ሲጀምሩ የኮሪደር ልማቱን ተከትሎ ቤታቸው ለፈረሰባቸው ሰዎች የሚሰጠው የኮንዶሚኒየም ቤቶች እና ከተማ አስተዳደሩ ላይ የ97 ተመዝጋቢዎች ያነሱታል ያሉትን ሀሜት በማስቀደም ነው።

<< እኛ በቆጠብነው ገንዘብ ነው ተፈናቃዮች ወይም የልማት ተነሺዎች እያሰፈሩ ነው የሚል እሮሮ አለ >> ያሉት አበበ << ለዚህ ምን ምላሽ ነው ያላችሁ፤ ከ97 ጀምሮ የቆጠቡ ሰዎች ...መቼ ነው የሚኖሩበት? ሳይኖሩበት ሊሞቱ ነው እኮ >> ሲሉ በስሜት ተሞልተው ጠይቀዋል።

ለዚህ ጥያቄ ምላሽ የሰጡት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ << የ97 የሚባል የለም >> በማለት ማብራሪያቸውን ይጀምራሉ።

ከንቲባዋ ሲቀጥሉ << [ እኛ እስከምናውቀው ድረስ ] የ97 የሚባል ዘግተናል >> ሲሉ ተናግረዋል።

<< ባለፈው ያስጨረስናቸውን ኮንዶሚኒየም ቤቶች ቅድማያ ለ97 active [ ንቁ ] ቆጣቢዎች ሁሉ ዕጣ እንዲወጣላቸው ተደርጓል >> ሲሉ አስታውሰዋል።

አክለውም << እነርሱ እንዲወጣላቸው ከተደረገ በኋላ deactivate ያደረገውን [ የዘጋውን] አካውንት activate [መቆጠብ የጀመረ ] ያደረገ ካለ
እሱ ለሚቀጥለው ጊዜ ..ያው ቆጥቧል፤ ቤት ስለሚፈልግ ነው activate  የሚያደርገው ሊታይ ይገባል እንጂ በዚህ መንገድ መቅረብ ያለበት አይመስለኝም >> ሲሉ ደምድመዋል።
Via:አሻም
@min_ddis

Min Addis?

19 Oct, 16:46


መቆዶኒያ  እያስገነባ ባለዉ ህንጻ ስር በሚገኝ መጋዘን ላይ የእሳት አደጋ ደረሰ

በለሚኩራ ክፍለ-ከተማ ወረዳ 3 መቆዶኒያ የአእምሮ ህሙማንና የአረጋዊያን መርጃ ማህበር  እያስገነባ ባለዉ ህንጻ ስር ባለ መጋዘን ላይ ዛሬ ጥቅምት 9 ቀን 2017 ዓ.ም የእሳት አደጋ ተከስቶ እንደነበር የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።

ለኮሚሽን መ/ቤቱ በደረሰዉ ጥሪ መሰረት የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች በቦታዉ ፈጥነዉ በመድረስ እሳቱ ሳይስፋፋ በፍጥነት መቆጣጠር መቻሉን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

በእሳት አደጋዉ በመጋዘን ዉስጥ የነበሩ ልዩ ቁሳቁሶች ላይ መጠነኛ ጉዳት የደረሰ ሲሆን በሰዉ ላይ ምንም ጉዳት አልደረሰም።

በሌላ በኩል በለሚኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ፍልዉሀ ሳይት እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ ክፍቱን በተተወና ዉሀ ባቆረ ጉድጓድ ዉስጥ ዋና ለመዋኘት ከገቡ ታዳጊዎች መካከል ዕድሜዉ 17 ዓመት የሆነ ታዳጊ ህይወቱ ማለፉን አቶ ንጋቱ ጨምረው ለብስራት ተናግረዋል።

የታዳጊዉን አስከሬን የኮሚሽን መ/ቤቱ ጠላቂ ዋናተኞች አዉጥተዉ ለፖሊስ አስረክበዋል።

ለእሳትና ለሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች  እንዲሁም ለአንቡላንስ አገልግሎቶች ነዋሪዎች በ939 ነፃ የስልክ መስመር እንዲያሳውቁ ኮሚሽኑ አሳስቧል።

በትግስት ላቀው/ዳጉ_ጆርናል
@min_ddis

Min Addis?

18 Oct, 18:28


ሙሉ መረጃውን ከላይ ያንብቡ
@min_ddis

Min Addis?

18 Oct, 17:11


ሰሞኑን በሀገራችን የተፈፀመ አሳፋሪ ድርጊት እንገራችሁ።

"ባለቤትሽ ጋር ለምን አልመለስም አልሽ በማለት ልጆቿና ህዝብ ፊት በባለቤቷ እንድትገረፍ የተወሰነባት የልጆች እናት"

ጉዳዩ እንዲህ ነው። ወ/ሮ ኩሹ ቦናያ ምስራቅ ቦረና ዞን ዋጪሌ ወረዳ ቃቀሎ ቀበሌ ነዋሪ ናት። ወ/ሮ ኩሹ ከአቶ ገልገሎ ዋሪዮ ጋር ትዳር ከመሰረቱ 12 አመታት አስቆጥሯል ሶስት ልጆም ወልዷል።

ፋስት መረጃ ከቤተሰብ የደረሰው መረጃ ወ/ሮ ኩሹ ሶስተኛ ልጃቸውን ነፍስጡር ሆነው ባለቤታቸው የሀገር መከላከያ ተቀላቅለው ለግዳጅ 4 አመት ሌላ ቦታ ቆይቷል።

አራት አመታትን ሶስት ልጆችን ብቻቸውን ያሳደጉት ወ/ሮ ኩሹ ከአራት አመታት በኋላ ባለቤታቸው ከመከላከያ ተሸኝቶ ወደ ቤቱ ይመለሳል። ጉዳዩን ለፋስት መረጃ ያስረዱት የቤተሰብ አባል አቶ ገለግሎ ሲመለሱ የተለያዩ ሱሶችን ስለለመዱ ትዳሩ እንደቀድሞ ሰላማዊ ሊሆን አልቻለም ጭቅጭቅ እና ግጭት ተከሰተ ይላሉ።

ወ/ሮ ኩሹ ትዳራቸው እንዳይፈርስ በተደጋጋሚ በሽማግሌ ብታስመክርም ባለቤቷ ሊስተካከል ስላልቻለ ከአቅሟ በላይ ሲሆን ወደ ቤተሰቦቿ ትሄዳለች።

ይህን ጊዜ ባል ሀገር ሽማግሌዎችን በመላክ ወደ ቤቷ እንድትመለስ ያስጠይቃል፣ ወ/ሮ ኩሹ የእኔ ጉዳት አልታየም በፍፁም አልመስም በማለት የሽማግሌዎቹን ጥያቄ ውድቅ ታደርጋለች።

ሽማግሌዎቹም የምንልሽን ስሜ ቶሎ ወደ ቤትሽ ተመለሺ ካልሆነ ቅጣት እንጥልብሻለን በማለት ሲያጠነቅቋት እንደቆዩ ተበዳይ ትናገራለች።

በእምቢታ የፀናችው ወ/ሮ ኩሹ በሽማግሌዎቹ የቅጣት ውሳኔ ተላልፎባት በገመድ ከግንድ ጋር ታስራ በልጆቿ እና በህዝብ ፊት በባለቤቷ እንድትገረፍ ተደረገ።

ስትገረፍ የሚያሳየው ቪዲዮ በማህበራዊ ሚዲያ ከተለቀቀ በኋላ ህዝቡ ቁጣውን መግለፅ ጀመረ። (ቪዲዮ ከተች ይገኛል👇)።

ይህን ውሳኔ አስተላልፏል የተባሉት ሽማግሌዎች ጃርሶ ቦሩ፣ ገልገሎ ጃተኒ፣ ዲዳ ዋሌ፣ ዲዳ ጃተኒ፣ አለካ ጃርሶ፣ ባርጪ ኢያ፣ ዲባ ጎሊቻ የተባሉ ሲሆኑ ፋስት መረጃ በደረሰው መረጃ እነዚህ ሽማግሌ የተባሉ ግለሰቦች 5 ቀን ታስረው በዋስትና መለቀቃቸውን ሰምተናል።

Via fast mereja
@min_ddis

Min Addis?

18 Oct, 13:57


ባል ውጭ ጉዳይ ሚንስትር:: ሚስት ፍትሕ ሚንስትር ሆነው ተሹመዋል:: ዶ/ር ጌዲዮን ከሹመቱ በፊት ፍትሕ ሚንስትር ነበሩ::

ሹመቱን እንዴት አያችሁት?
Via:ZeHabesha
@min_ddis

Min Addis?

17 Oct, 11:05


ፈጣሪ ወጥቶ ከመቅረት ይጠብቃችሁ🙏🙏
ዛሬ ጥዋት አሳዛኝ ክስተት!💔😭

ክስተቱ የተከሰተዉ ከቢሮዬ ጀርባ፣ CMC ሚካኤል ነዉ፡፡
ወዳጆቼ ከእንደዚህ ዓይነት ጎዶሎ ቀን መድኃኔዓለም ይጠብቃችሁ!

አንዲት እናት ልጇን ትምህርት ቤት አድርሳዉ፣ ለጉሊት ስራዋ ዕቃ ገዝታ ዜብራ ስትሻገር ምግባረ*-ቢስ አሽከርካሪ ገ*ጭቷት ገደላ*ት፡፡

አስቧት፣ ኑሯን ለመግፋት፣ ልጆቿን ለማሳደግ፣ ያልፍልኛል ብላ ጉሊት እየሰራች፣
አስቡት፣ ባልሞላት ኑሮ የምታሳድገኝ እናት አለችኝ እያለ ትምህርት ቤት የተሸኘዉ ልጇ ሲመጣ እናትህ እንዲ ሆናለች ሲባል፣😭😭😭

የሀገረቷን ምግባረ-ቢስ አሽከርካሪዎችን የሚያስተካክል ጠንከራ ሥራ ያስፈልጋል፡፡

ሥራዬን መስራት አቅቶኝ እየቃዠኝ ነዉ፡፡
(ፍቅሩ መንገሻ)
@min_ddis