ራስን መለወጥ

@changeitwow


እንዴት ናችሁ? ቢዝነስ ፕላን(ቢዝነስ ዕቅድ) እንዲሰራለት የሚፈልግ በተመጣጣኝ ዋጋ  ቢዝነስ ፕላን እንሰራለን!
በውስጥ መስመር ያናግረን!

ለውጥ በትክክልም ይመጣል።
💪ዕድገታችንም ይሳካል!!!

Hello everyone, we make best Business plan. In good price contact us inside! just pick a what kind of business plan!
We can chang

ራስን መለወጥ

21 Oct, 03:21


#የአንተ_ስበብ ምንድነው?!

#1_ለምንህን_ፈልግ

መነቃቃትን ሳይሆን ለምንህን ፈልግ። ያን ጊዜ ባንተና በግብህ መካከል ሰበብ አይፈጠርም!

ለግቦችህና ለድርጊቶችህ ጠንካራ ምክንያት የሚሆንህ ለምን? ፈልግ እንጂ በየ ጊዜው የሚቀያየር የመነቃቃት ስሜትን በመጠበቅ ጊዜህን አታባክን። ሲደክምህም፣ ፈተና ሲበዛብህም ብርቱ የሚያደርግህ ለምንህ እንጂ ስሜትህ አይደለም።

#2_ካልፈራህ_በቀር_ሰበብ_አታበዛም!

አዎ ሰበብ የፈሪዎች መደበቂያ ነው። አንተ ግን ፈሪ አይደለህም። ስለማትፈራ ሰበብ በማብዛት አትደበቅም። ትወጣለህ፣ ትጋፈጣለህ፣ ታሸንፋለህ!

#3_የማታገኘውን_ዛሬህን_ሁሌም_በምታገኘው_ሰበብ_አትጣው!

ሰበብ ሁልጊዜ አለ። መልካም እድልና አጋጣሚ የሚመጣው ግን አልፎ አልፎ ነው። ሰበብን ከፈለግከው ዛሬ፣ ነገ ወይም ከዓመታት በኋላም አታጣውም። ዛሬህ ግን የዛሬ ብቻ ነውና ተጠቀምበት!

#4_ሰበብ_ማሸነፍን_አጥበቀው_ለማይፈልጉት_ሰዎች_ነው!

ግብህን ምን ያህል ትፈልገዋለህ? የአሸናፊነት ርሃብህ እስከ የት ድረስ ነው? ሰበብ ካበዛህ በቂ ፍላጎትና ርሃብ የለህም ማለት ነው።

#5_ወዴት_እየሄድክ_ነው?

የት ነበርክ ወይም የት ነህ የሚለው አያሳስብም። ዋናው ወደ የት እየሄድክ ነው የሚለው ነው። ሰበብ አታብዛ!

ዋናው ቁምነገር መድረሻህ ነው። መነሻህ የትም ሊሆን ይችላል። ሁሉም የተደላደለ መነሻ አይኖረውም፤ ሁሉም ግን መድረሻውን የተደላደለ ማድረግ ይችላል። ይህ የሚሆነው ደግሞ ሰበብን የቆሻሻ ቅርጫት ውስጥ በመጣል ነው!!

ሰበብህን የቆሻሻ ቅርጫት ውስጥ በመጣል ሕልምህን መኖር ያስፈልጋል!!!

ራስን መለወጥ

t.me/changeitwow

ራስን መለወጥ

17 Oct, 04:27


#የማይቀየሩ_እውነታዎች

#ምንም ነገር ለዘላለም አይቆይም፡፡ ችግሮችህ፣ የከበቡህ ሰዎች፣ ስራህ፣ ትዳርህ እና ግንኙነቶችህ ሁሉ ለጊዜዉ ነዉ፡፡ የሁሉም ነገር ፍፃሜ የሆነ ቀን ላይ ሲሆን ታየዋለህ፡፡ በህይወቴ ሁሉ አብረዉኝ ይኖራሉ ያልካቸዉ ነገሮች እንኳን ሳይቀሩ ሲፈረካከሱ ታያቸዋለህ።

#ለሁሉም ነገር ተራ አለዉ፡፡ ሰዉን ብትጠቅም ጊዜዉን ጠብቆ አምላክህ ይከፍልሃል፡፡ ብትጎዳም እንዲሁ። በሰፈርከዉ ማንነት ጊዜዉ ሲደርስ ትሰፈራለህ።

#ማንም ሰዉ ስላንተ አይጨነቅም፡፡ 20 ፐርሰንቱ ብቻ ስላንተ ሲጨነቁ (እነሱም የቅርብ ጓደኞችህና ቤተሰቦችህ መሆናቸዉን አትዘንጋ) 80 ፐርሰንቱ ግን ኑር አትኑር አንዳች ቅንጣት ስላንተ አያስቡም፡፡ ችግሮችህን ለነዚህ ለ 80 ፐርሰንት መናገር እራስህን ማባከን ነዉ ምክንያቱም ችግርህ ለነሱ ምናቸዉም አይደለምና! የራሳቸዉ ጉዳይ ብቻ ያሳስባቸዋልና ቆጠብ በል።

#ሰዎች በህይወትህ ይመጣሉ ደግሞም ይሄዳሉ፡፡ አንድ ቀን ለብቻህ ሰዉ በሌለበት ልትሞት ትችላለህና ሰዎችን አትደገፍ።

#ከ5-6 የልብ የምትላቸዉ ሰዎች በቀር ፌስቡክ ላይ ያሉት የጓደኛ ጋጋታ ምንም አይጠቅሙህም፡፡ ብትሞት እንኳ ቀብርህ ላይ የማይመጡ ብዙዎች መሆናቸዉን እወቅ።

#የስራ አለቃህ እንድታድግና የተሻለ ቦታ እንድትይዝ ሊመኝ ይችላል ግን መቼም እንድትበልጠዉ አይፈልግም፡፡ ምንም ሽልማትና ጭብጨባ ቢበዛልህ ከሱ እንደምትበልጥ ካሰበ አንተን ለመገፍተር ወደኋላ አይልም።

#98 ፐርሰንቱ ሰዉ መቼ እንደተወለድክ እንኳን አያዉቅም (2 ፐርሰንቱ መቼም እነማን እንደሆኑ መገመት አያቅትህም)፡፡ ካላመንከኝ ሞክረህ እየዉ!

#የዉሸት ጓደኞችህ የተሻለ ህይወት እንድትመራ በፍጹም አይፈልጉም፡፡ ነገሮች መልካም ሲሆኑ የሚሰበሰቡ ሰዎች ሊያስገርምህ አይገባም! አንድ ቀን ህልምህ 'ወለም' ብሎ ካዩ እጃቸዉን ቀስረዉ ይስቁብሃል፡፡ የዛኔ ያልሳቁብህን የልብ ጓደኞችህ አድርጋቸዉ።

#ገንዘብ ያለዉና ፀዳ ብሎ የሚመላስን ሰዉ ብዙዎች ሲያከብሩት ትመለከታለህ ፡፡ የማያዉቅህ እንኳን ቢሆን ፀዳ ካልክበት ሊያከብርህ ሲዳዳዉ ታየዋለህ።

#ለሰዎች ምክር መስጠት በጣም ቀላል ነዉ ነገር ግን ምክርን ወደተግባር መቀየር ከባዱና አስቸጋሪዉ ነገር ነዉ፡፡ አንዳንዴ ሰዉን ካለበት ማጥ ለማዉጣት ካሰብክ ከምክር በላይ የሆነ ስብዕና ሊኖርህ ይገባል፡፡

#አንድ ዉሸታም ጓደኛህ ከ 100 ጠላትህ ጋር እኩል ጥፋት ያደርሳል፡፡ ጠላቶችህን ተከታተላቸዉ ጓደኞችህን ደግሞ በጣም ተከታተላቸዉ።

#ነገሮች መልካም እንዲሆኑና እንዲሳኩ ያለ የሌለ ጥረትህን አድርገህ ሳይሳካልህ ቀርቶ ይሆናል፡፡ ይሄ ያንተ ደካማነት ሳይሆን ህይወት እንዲህ አይነት ገፅታም ስላላት ነገሩን ተቀበለዉ።

#ለመወደድ ልዩ ሰዉና ሁሉንም ሞካሪ መሆን አይጠበቅህም፡፡ እንዳንዴ ሰዉ ሁሉ ባይወድህ እንኳን ይሄ ምንም ማለት እንዳልሆነ ተረዳ፡፡

#በሰዎች መጠላትንም ቀለል አድርገህ ዉሰደዉ ምክንያቱም እንዴት እራስህን ማሳደግ እንዳለብህ ማጤን ወሳኙ ነገር ሲሆን የሰዎችን ስሜት እያዳመጥክ ከፍና ዝቅ እያልክ መኖር አይጠበቅብህም፡፡

#የራስህ አስተሳስብ ይኖርሃል፡፡ ሌሎችም እንዲሁ...ሰዎች በሀሳብህ አለመስማማታቸዉ አንተነትህ ላይ የሚያመጣዉ ነገር የለም፡፡ ሃሳብህን ለማሳመን የሰዎችን አስተሳሰብ ረጋግጠህ አትዉጣ፡፡ የሰዎችን ሃሳብ አክብር ሰዎችም ሃሳብህን እንዲያከብሩ አድርግ።

#ይቺ አለም የምትፈልግህ ጠቃሚ ነገር አንተ ጋር እንዳለ ስታምን ብቻ ነዉ፡፡ ባጠቃላይ አለም እራስ ወዳድ ናት።

#ሰዎች ስለ ደስታ አጋነዉ ሲያወሩ ትሰማ ይሆናል፡፡ በኣጭሩ ደስታ ማለት ስሜትህ ሳይሆን አእምሮህ ያለበት ሁኔታ ነዉ፡፡ ደስተኛ ሆነህ በሰዎች ልትጎዳ ትችላለህ፡፡

#ህይወት እኩል አይደለችም፡፡በሆነ ነገር ጎበዝ ብትሆን ካንተ የበለጠ በጣም ጎበዝ ሰዉ አለ...እኩልነት ዉሸት ነዉ፡ ስለዚህ በመኖርህ ብቻ ተደሰት፡፡

t.me/changeitwow

ራስን መለወጥ

ራስን መለወጥ

15 Oct, 13:07


ምንም ጠላት የሌለው የህንዱ ቢሊየነር...!
(A MAN WITH ZERO HATERS)
ራታን ታታ ፡ ጠላት አልባው ፡ ባለወርቅ ልብ ቢሊየነር ።

........

በወጣትነት እድሜው ወደ አሜሪካ ተጉዞ እዛው የተማረው  ወጣቱ ህንዳዊ ራታን ታታ ፡  ሎስ አንጀለስ በሚገኘው የአርክቴክቸር ካምፓኒ ውስጥ እያለ ነበር ከመጀመሪያ ፍቅረኛው ጋር የተገናኘው ።
....
ራታን ታታ ይህን ጊዜ ሲያስታውስ. .
በህይወቴ ምርጡ የምለው ጊዜ ይህ ከመጀመሪያ ገርልፍሬንዴ ጋር ያሳለፍኩት ጊዜ ነበር ይላል ።
.....
እና ከዚህች ልቡን ጥቅልል አድርጎ ከሰጣት ሴት ጋር ወደ ህንድ አብረው ተጉዘው በትዳር እንደሚኖሩ ወስነው እያለ ። ህንድና ቻይና ፡  በሂማልያ አካባቢ በሚገኙ ቦታዎች የነበራቸው የይገባኛል ጥያቄ እየከረረ ሄዶ ጦርነት ውስጥ ገቡ ።
......
ይህን የተረዱትና ፡ በልጃቸው ወደህንድ መጓዝ  ስጋት የገባቸው የፍቅረኛው ቤተሰቦች ልጃቸው ወደ ህንድ መላክ አልፈለጉም ።
....
ወጣቱ አርክቴክት ራታን ታታ ፡ የሚወዳትን ሴት ሳይወድ በግድ  ትቶ ወደ ህንድ ተጓዘ ።
.....
ያ የመጀመሪያ ፍቅሩን ያጣው ልቡ ሌላ ሴት አልለምድ አለው ። እና ሙሉ ትኩረቱን ስራው ላይ አድርጎ ፡ ያንን የወጣትነት ፍቅር እድሜ ልኩን እያስታወሰ ፡ ሳያገባ ፡ ሳይወልድ ኖረ ።
....
የፍቅር ህይወቱ ያልተሳካለት ራታን ታታ ፡ ሙሉ ትኩረቱን ስራው ላይ በማድረግ. . የቤተሰቡ ንብረት የሆነውን ፡ የ TATA  ፡ የጃጉዋር ፡ የሬንጅሮቨርና ላንድሮቨር መኪኖች አምራች  የሆነውን  ፡ ታታ ግሩፕን በመምራት ኩባንያውን ብቻ ሳይሆን ፡ ህንድንም ማሳደግ የቻለ ሰው ሆነ ።
.....
ሚስተር ራታን ታታ ከዚህም በላይ ፡  በዋናነት የሚታወቁበት " ባለወርቅ ልብ "  የሚል ቅፅል ስም እስከማግኘት ባደረሳቸው የሰብአዊ አድራጎታቸውና ፡ እጅግ በበዛ ትሁት ስብእናቸው  ነው  ።
.....
......
እና ይህ A Man With zero Haters በሚል ስም የሚታወቀው ፡ ከቢሊየን በላይ ህንዳውያን ያላንዳች ልዩነት የሚያከብሩት ፡ የሚወዱት ሰው ... ዘመኑን በሙሉ ለሰው ልጆች ሁሉ መልካም ሲያደርግ ኖሮ ዛሬ ምሽት  በ86 አመቱ ፡ መልካም ስሙን ትቶ ይህችን አለም መሰናበቱን በአለም አቀፍ ሚዲያዎች  በሰበር ዜና ሲዘግብ ሰማን ።

ታዋቂ የቦሊውድ የፊልም ተዋናዮች ፡ በኢንስታግራምና የፌስቡክ ፕሮፋይላቸውን በኚህ ደግ ፡ ትሁት ፡ እና ጎበዝ ሰው ምስል ቀየሩ ። ሚዲያዎች ጠቅላላ ፡ ህንድ አልማዟን አጣች ፡ የደግነት ፀሀይ ጠለቀ. ..  ሲሉ በሚያማምሩ ቃላት ስለ ህልፈታቸው ጻፉ ፡ ዘገቡ ።
.....
ከንግዲህ አደለም ህንዳውያን ፡ ሌላውም  ስለዚህ ሰው የሚያውቅ ሁሉ ራታን ታታ የሚለውን ስም ሲሰማ ጥሩ ምግባሩን ያስታውሳል ። ያ በህይወት እያሉ ያደረጉት መልካም ስራ ዘላለም ሲያስመሰግናቸው ይኖራል ።
.....
Legends are born, and they live forever !
ከዋሲሁን ተስፋዬ

ራስን መለወጥ
t.me/changeitwow

ራስን መለወጥ

14 Oct, 05:02


ከሊዮ ቶልስቶይ ተረቶች ውስጥ እንዲህ የሚል ይገኝበታል፡፡
አንድ ንሥር በዛፍ ላይ ጎጆ ትሠራለች፡፡ እዚያም ውስጥ ጫጩት ትፈለፍላለች፡፡ አንዲት አሳማ ደግሞ ግልገሎቿን ይዛ ዛፉ ሥር ትቀመጣለች፡፡ ንሥሩዋ ሩቅ በርራ አድና ልጆቿን ትቀልባለች፡፡ አሳማዋ ዛፉ ስር እየኖረች እጫካው ውስጥ እየገባች፣ እያደነች ውላ ማታ ለልጆቿ ምግብ ታመጣላቸዋለች፡፡ በዚህ ዓይነት ንስርና አሳማ እንደ ጎረቤት እየተማመኑ፣ እየተዋደዱ፣ አንዳቸው አንዳቸው ላይ ክፉ ላያስቡ ተስማምተው መኖራቸውን ይቀጥላሉ፡፡ በመሰረቱ ንሥርና አሳማ በተፈጥሯቸው አንዳቸው ያንዳቸውን ግልገል ካገኙ የማይምሩ፣ ተፃራሪ ፀባይ ያላቸውና ሊጠፋፉ የሚችሉ ናቸው፡፡ አንድ ቀን አንዲት አሮጊት ድመት ወደ ሁለቱ ሠፈር መጣች፡፡ የንሥሯንም ጫጩቶች፣ ጡት የሚጠቡትንም የአሳማዋ ግልገሎች ፣ ልትበላቸው አሰበች፡፡
ወደ ንስሯ ሄዳ፤
“ንሥር ሆይ፣ ለምግብና ለአደን ብለሽ ከእንግዲህ ሩቅ መንገድ እንዳትሄጂ፡፡ ይቺ አሳማ የምትተኛልሽ አይምሰልሽ፡፡ መጥፎ ተንኮል እያሰበችብሽ ነው፡፡ የዛፉን ሥር እየበጣጠሰችው ነው፡፡ እንደምታይው በየቀኑ የሥሩን አፈር እየማሰች ነው፡፡” አለቻት፡፡ ንሥሯም ስለ ምክሯ አመሰግናት ተለያዩ፡፡
ቀጥላ ደግሞ ወደ አሳማዋ ዘንድ ሄዳ፤
“አሣማ ሆይ፣ ዘንድሮ ጥሩ ጎረቤት አልተዋጣልሽም፡፡ ትላንት ማታ ንሥሯ ለጫጩቶቿ እንዲህ ስትል ሰማኋት፡፤ ወዳጄ ስለሆንሽ ሆዴ አልችል ብሎኝ ልነግርሽ መጣሁ አለች፡፡ አሳማም፤ “ምን አለችኝ እባክሽ?” ብላ በጉጉት ጠየቀች፡፡
ድመትም፣ “ምን ስትል ሰማኋት መሰለሽ፣ ልጆቼ፤ ከእንግዲህ አትራቡም፡፡ እንዲያውም ጥሩ ጥሩ ግልገል አሳሞች እያመጣሁ እቀልባችኋለሁ፡፡ አይዟችሁ፣ ይህቺ አሳማ የምንኖርበት ድረስ መጥታ ግልገሎቿን መሬት ላይ አፍስሳልናለች፡፡ እናታቸው ራቅ ብላ ስትሄድ ቆንጆ ቆንጆ ግልገሎቿን እያመጣሁ አበላችኋለሁ” አለች፡፡
ከዚህ ቀን ጀምሮ ንሥር ወደ ሩቅ ቦታ እየሄደች ማደኗን አቆመች፡፡
አሳማዋም ከዚህ ቀን ጀምሮ ወደ ጫካ መሄዷን አቆመች፡፡
የንሥርም ጫጩቶች፣ የአሳማም ግልገሎች ከቀን ወደ ቀን ለረሀቡ እየተጋለጡ ሄዱ፡፡ ውሎ አድሮ፣ የንሥር ልጆች አንድ በአንድ ከዛፍ ላይ እየተፈነቸሩ ይወድቁ ጀመር፡፡ የአሳማም ግልገሎች እናታቸው ለመኖሪያ በማሰችው ጉድጓድ ውስጥ ሞተው ይገኙ ጀመር፡፡ አሮጊቷ ድመት የሞቱትን ጫጬቶችና ግልገሎች እያፈራረቀች የተመጣጠነ ምግብ ማለት ይሁ ነው እያለች እየተመገበች ፌሽታ ስታደርግ ከረመች፡፡
ንስርና አሳማ ሲያለቅሱ ሰነበቱ፡፡

የስኬት ጉዟችን የሚሰናከለው በጥቂቶች ጥቅም ፈላጊነት የተነሳ እኛ መስዋዕት ስንሆን ነው

ራስን መለወጥ
t.me/changeitwow

ራስን መለወጥ

14 Oct, 05:00


የባህር ዳርቻ ወፍና የባህር አሣ ሲታገሉ፣ አሣ አጥማጅ ይጠቀማል

ራስን መለወጥ

11 Oct, 05:13


የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊየነር ማን ሊሆን ይችላል?
ዓለማችን በ2027 የመጀመሪያውን ትሪሊየነር እንደምታገኝ ፎርብስ አስታውቋል።

በቴክኖሎጂ ዘርፍ የተሰማሩ ኩባንያዎች በየዓመቱ ከፍተኛ የተባለውን ትርፍ በማግኘት ላይ ሲሆኑ ዓለማችን ካሏቸው ቀዳሚ ባለጸጋዎች መካከልም ዋነኞቹ ናቸው፡፡

236 ቢሊዮን ዩሮ ሀብት በመያዝ የዓለማችን ቁጥር አንድ ባለጸጋ የሆነው ኢለን መስክ በ2027 በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ትሪሊየነር ደረጃን እንደሚይዝ የብሉምበርግ ቢሊየነር ሪፖርት ትንበያ ያስረዳል፡፡

እንደ ትንበያው ከሆነ ከኢለን መስክ በመቀጠል የህንዱ ጓታም አዳኒ በ2028 ለይ ሁለተኛው ትሪሊየነር እንደሚባልም ተገልጿል፡፡

የ61 ዓመቱ እና የኒቪዳ ኩባንያ ባለቤቱ ጄሰን ሁዋንግ በ2028 የሀብት መጠኑ ትሪሊየን ይገባል የተባለ ሲሆን አሁን ላይ 112 ቢሊዮን ዶላር ሀብት ባለቤት ነው፡፡

የኢንዶኔዥያው ፕራጆጎ ፓንግስቱ በተመሳሳይ በ2024 አራተኛው የዓለማችን ትሪሊየነር እንደሚሆን የተገመተ ሲሆን ማርክ ዙከርበርግ፣ ፊል ናይት እና በርናርድ አርናውልት ከአምስት ዓመት በኋላ የሀብት መጠናቸው ወደ ትሪሊነር ያድጋል ተብሏል፡፡

በአጠቃላይ እስከ ፈረንጆቹ 2037 ዓመት ድረስ 15 ዓለማችን በላጸጋዎች የሀብት መጠናቸው ከቢሊዮን ወደ ትሪሊየነርነት እንደሚያድግ ተገልጿል፡፡

በቀጣዮቹ 10 ዓመታት ውስጥ ሀብት መጠናቸው ወደ ትሪሊየነርነት ከሚገባላቸው ባለጸጋዎች መካከል አስሩ አሜሪካዊያን ሲሆኑ ሁለት ህንዳዊያን እንዲሁም ኢንዶኔዢያ ፈረንሳይ እና ቻይና ደግሞ እያንዳንዳቸው አንድ ትሪሊየነር ይኖራቸዋል ተብሏል፡፡

ከአል ዐይን
t.me/changeitwow

ራስን መለወጥ

10 Oct, 02:55


#ከመፅሀፍ_ገፆች...

ጆርዳን የተባለው ደራሲና የሥነ ልቦና ባለሙያ የሰው ልጆች ከተዛባ አመለካከት ወደ ቅን አሳቢነት የሚያሸጋግሩና መልካምነትን የሚያጎናፅፉ #ዘጠኝ አስተሳሰቦች ብሎ ያስቀመጣቸው እንደሚከተለው ቀርበዋል።

1. ለሰዎች መልካም ሁን

መልካምነት ለተረጋጋ ህይወት መጀመሪያ ነው። መልካምነት ካንተ ጋር ከሆነ ሁሉም ነገር አብሮህ ይኖራል። ለሰዎች መልካም ነገር ባደረክ ቁጥር የተረጋጋ ህይወትን ለመምራት የሚያስችልህን መንገድ እየጠረክ ትሄዳለህ። የመልካምነትን መንገድ መከተል የጀመረ ሰው ለተሳሳቱና ላልጠሩ አመለካከቶች የሚሆን ቦታ ስለማይኖረው፤ የሚያጋጥሙትን ችግሮች በተለየ አቅጣጫ እየተመለከተ ለመፍታት ይሞክራል።

2.ማገዝ ከሚችሉ ሰዎች ጋር ተወዳጅ

አብዛኛውን ጊዜ ሰዎች በራሳቸው ጥረት ብቻ የሚፈልጉት የስኬት ጫፍ ላይ ለመድረስ ሲታገሉ እንመለከታለን። በተለይ የተሳሳተ አመለካከት ያላቸው ሰዎች የሌሎችን እገዛ መጠየቅ የውድቀት መጀመሪያ መስሎ ይታያቸዋል። በዙሪያ የሚያግዙ ሰዎች መኖር ጥንካሬና ብርታትን ይሰጣል። ስለዚህ የሚያግዝህና ሃሳብህን የምታጋራው አስተዋይ ወዳጅ ይኑሩህ።

3. ኃላፊነቶችን ለመወጣት ዝግጁ ሁን

ኃላፊነትን ለመቀበል ዝግጁ መሆን የተሳሳተ አመለካከትን አሽቀንጥሮ ለመጣልና ቀና አመለካከት ለማካበት ከሚረዱ ነገሮች አንዱ ነው። ኃላፊነትን በተሸከምክ ቁጥር ስለ ሌሎች ሰዎች ማሰብና ራስህን በሌሎች ቦታ አስቀምጦ ፍርድ የመስጠት ልምድ ማግኘት ይቻላል። ለሰዎች ማሰብ መቻል ደግሞ ለቀና አመለካከት እንደ ማሳያነት ይቀርባል። በተጨማሪም ከዚህ በፊት በነገሮች ላይ የነበረህን የተሳሳተ ግንዛቤ እያጠራልህ ይሄዳል። ቀስ በቀስ አመለካከትህ ተቀይሮ ሁኔታዎችን የመለወጥ አቅም እንዳለህ ማመን ትጀምራለህ።

4. ይቅር ባይ ሁን

በይቅርታ ማመን መቻል ሌላኛው ቀና አመለካከት ያለው ሰው መገለጫ ባህሪ ነው። አንድን ሰው በሆነ አጋጣሚ ቢያስቀይምህና ከቀናት በኋላ የሠራው ሥራ ትክክል እንዳልነበረ ተረድቶ ይቅርታ ቢጠይቅህ ይቅርታህን አትንፈገው። ቀና አመለካከት ያለው ሰው ይቅርታ ለጠየቁት ሰዎች ምህረት ከማድረግ ባለፈ በጥፋቱ ይቅርታ የመጠየቅ ልምድ አለው።

5. ሙሉነት ይሰማህ

የሙሉነት ስሜት በሥነ ልቦና ባለሙያዎች ዘንድ ትልቅ ትኩረት የሚሰጠው ጉዳይ ነው። በህይወትህ ብዙ ነገሮች ሊያጋጥሙህና እንዳልነበሩ ሆነው ልታገኛቸው ትችላለህ። ለራስህ ግን ሁሉም ነገር ሙሉ እንደሆነና ዘወትር መልካም ነገር ላይ እንዳለህ አስብ።

አብዛኛውን ጊዜ የተሳሳተ አመለካከት ያላቸው ሰዎች በራሳቸው ሙሉነት አይሰ ማቸውም። ቀና አመለካከት ያላቸው ሰዎች ግን የተዘበራረቁ የህይወት መስመሮች ውስጥ ቢሆኑም እንኳን እንዳልተዘበራረቁ አድርገው ማሰብ ይችላሉ። የጎደለ ነገር ሁሉ ባዶ አይሆንምና ሁል ጊዜ በራስህ ሙሉነት ይሰማህ። ሰዎች ዛሬ የምታሳልፈው ቀን ደስ የማይል እንደሆነ አስረግጠው ቢነግሩህ እንኳን ፍፁም ደስተኛ ሆነህ ማሳለፍ እንደምትችል ውስጥህን አሳምነው።

6. ከመጠን ያለፈ አታስብ

ሁሉም ነገር በተፈቀደለት ጊዜ መሆኑ አይቀሬ ነው። አእምሮህ ከሚችለው በላይ በሃሳቦች መወጠር ቀና አመለካከት እንዳይኖር ያደርጋል። ስለአንድ ነገር አብዝተህ የምትጨነቅ ከሆነ ትኩረትህን ሁሉ ጉዳዩ ላይ ይሆንና በዙሪያህ ስላሉ ሰዎች ማሰብ ታቆማለህ። ያኔ ከሰዎች ጋር አለመግባባት ውስጥ ትገባለህ።

7. ደስታ አይራቅህ

አብዛኛውን ጊዜ የተሳሳተ አመለካከት ያላቸው ሰዎች ፍፁም ደስታ የራቃቸው ናቸው። ነገሮች ላይ አብዝተው ስለሚጨነቁ፣ በይቅርታ ስለማያምኑና ሙሉነት ስለማይሰማቸው ለራሳቸው ደስታን መፍጠር ይሳናቸዋል። ቀና አመለካከት ያላቸው ሰዎች ግን ሁል ጊዜ ሙሉ እንደሆኑ ስለሚሰማቸውና አርቀው ስለሚያስቡ ደስታቸው በእጃቸው ነው።

8. ለዋዛ ፈዛዛ ነገሮች ቦታ አለመስጠት

ለሚረባውም ለማይረባውም ነገር ቦታ መስጠት የተዛባ አመለካከት እንዲኖር ከማድረጉም በላይ መንፈስን ላላስፈላጊ ጭንቀት ይዳርጋል። በመሆኑም ትኩረት መስጠት ለሚያስፈልገው ጉዳይ ብቻ ትኩረት በመስጠት የቀና አመለካከት ጎዳናን ማስፋት ይቻላል።

9. ግርማ ሞገስ መላበስ

በሌሎች ዘንድ ተቀባይነትንና ተወዳጅነትን ለማግኘት የሰዎችን ቀልብ መሳብ መቻል ተገቢ ነው ። ማድረግ የምትፈልጋቸው ድርጊቶች ሁሉ ግርማ ሞገስን የተላበሱ ቢሆኑ መልካም ነው ።


ራስን መለወጥ
t.me/changeitwow

ራስን መለወጥ

08 Oct, 12:31


#የአለም__እውነታወች
1. የሚከተልህ ሁሉ አድናቂህ አይደለም

2. ውሻ ጭራውን የሚቆላው ላንተ ሳይሆን በእጅህ ላለው ዳቦ ነው ፣ አስመሳይና ተለማማጭ ሰውም እንዲሁ ነው ።

3. ሕይወት ድልድይ ናት፣ አቋርጣት እንጂ በላይዋ ላይ ቤት አትስራ ።

4. ውሀ ቅርፁን ከመያዣው ጋር እንደሚስማማ ሁሉ ብልህም ራሱን ከሁኔታው ጋር ይስማማል ።

5. ምንም ያህል ርቀት በተሳሳተ መንገድ
ብትጓዝም ወደኋላ ተመለስ ።

6. ዝቅ ብለህ ብትመለከት ምን ያክል ከፍ እንዳልክ ታውቀዋለህ ።

6. አንድ ሰው ስትተዋወቀው በልብሱ ልትመዝነው ትችላለህ ፣ ስትለየው ግን በአስተሳሰቡ ትመዝነዋለህ ።

7. ሠርግና ቀብር አንድ ናቸው ። ልዩነቱ የሠርግ አበባን ባለቤቱ ማሽተት መቻሉ ብቻ ነው ።

8. አምላክህን ደስታህን በቅንነት ብትጠይቀው ይሰጠሀል ። ብቻ በቤትህ በሀቀኝነት ኑር ።

9. ማንክያ የሾርባን ጣዕም እንደማያውቅ ሁሉ ለስሙ የተማረም የጥበብን ጣዕም አያውቅም ።

10. ሀገር እንዳትጠፋ ትልቅ ነገርን አታጥፋ ። "ሰው ሆይ በትዕቢትና በንቀት መወጠርህን አቁም ። የውሸት መኖርህን ፣ ሰዎችን መበደልህን ፣ ፈጣሪህን ማሳዘንህን አቁምና መልካም ነገርን አድርግ ። ልብ በል ሺህ ጊዜ የውሸት ብትኖር አንድ ጊዜ የእውነት መሞትህ አይቀርም ።

ራስን መለወጥ
t.me/changeitwow

ራስን መለወጥ

05 Oct, 12:47


ፓትሪስ ኤቭራ ስለ ክርስትያኖ ሮናልዶ 🎙

🗣 "አንዴ 'ከትሬኒንግ ቡኃላ ና' አለኝ። ከዛ ሄድኩኝ። ታውቃላችሁ በጣም ደክሞኝ ነበር። ጠረቤዛው ላይ ሰላጣ እና plain white chicken ብቻ ነበር ያለው። እና እኔ በውስጤ 'እሺ እንግዲ ይሁን አልኩኝ' ከዛ ደግሞ ውሃ ብቻ ነበር ምንም ጁስ የለም። ከዛ መመገባችንን ጀመርን። አሪፍ ስጋ ይመጣል ብዬ እየጠበኩ ነበር። ግን ምንም የለም።"

🗣 "ልክ እንደጨረስን ተነሳ እና በኳሷ መጫወት እና የተወሰኑ ስኪሎችን መስራት ጀመረ። ከዛ 'ና በሁለት ንክኪ እንጫወት አለኝ'። እኔ እባክህ በልቼ ልጨርስ አልኩት። 'አይ ና በሁለት ንክኪ እንጫወት' አለኝ እና መጫወት ጀመርን።"

🗣 "ና እስኪ ወደ መዋኛው እንሂድ አለኝ። እሽ አልኩት። ከዛ ከጃኩዚ እና ሳውና ቡኃላ አልቻልኩም። እንዲህ አልኩት 'ክርስትያኖ እዚህ የመጣነው ነገ ጨዋታ ስላለብን ነው ወይስ ምሳ ለመብላት?'"

🗣 "ለዚህ ነው ክርስትያኖ ወደ ቤቱ ሲጋብዛችሁ እምቢ በሉ የምለው። ይሄ ሰውዬ ማሽን ነው። ልምምድ መስራቱን ማቆም አይችልም"
Marki sport

እኛስ ምን ያህል ራሳችንን ለመቀየር ዝግጁ ነን? ስኬት ማማ ላይ ለመቆየት?!!!!!!
ራስን መለወጥ

ራስን መለወጥ

02 Oct, 15:40


"ሞት ሰራቂው ሞተ" በጣም የሚደንቅ ታሪክ!

በአንድ ወቅት አንድ ሰው የፈጣሪን ተአምር ለመመስከር እሩቅ አገር ለመሔድ ከተሳፋሪዎች ጋር በአውቶብስ ጉዞ ይጀምራል። ጉዞ ከተጀመረ በኋላ ግን መንገድ ላይ አንድ ከተማ ውስጥ ተሳፋሪው በሙሉ ምሳ ለመብላት ይወርዳል።

......ከተሳፋሪዎቹ መሐከልም አንዱ ወደ አንድ ምግብ ቤት ይሔድና ምሳውን ከበላ በኋላ ለመክፈል ቦርሳውን ሲፈልግ ያጣዋል።

......መሰረቁንም ከተረዳ በኋላ ለምግብ ቤት ባለቤቱ የደረሰበትን ስርቆት አስረድቶ በነበረበት ከተማ የሚያውቀው ዘመድ ስለነበር ገንዘብ አምጥቶ እንደሚከፍል ተናግሮ ገንዘብ ይዞ መጥቶ ይከፍልና ወደ አውቶብሱ ሲሔድ አውቶብሱ ለካ ጠብቆ ጠብቆ የደረሰበትን ነገር ስላላወቀ ትቶት ሔዷል።

........ ሠውየውም ገንዘቡም ተዘርፎ አውቶብሱም ጥሎት መሔዱ እየገረመው
"ይሄ_ፈተና_ነው_ሰይጣን_እፈር እኔ እንደሆነ ከአገልግሎት አልቀርም ብሎ ብዙ ከተንከራተተ በኋላ በሌላ አውቶብስ ተሳፍሮ ጉዞ ይጀምራል።

. ...... በመንገድ ላይም አንድ ትልቅ ገደል ውስጥ የገባ አውቶብስ ያያል። ከተሳፋሪዎቹም የተረፈ ሰው አለመኖሩ ይመለከታል። ደነገጠ።

....በጣም አዝኖ እያለም ወርዶ አውቶብሱን በደንብ
ሲያየው እርሱ ተሳፍሮባት የነበረችውና ጥላው የሔደችው አውቶብስ መሆንዋን ይረዳል።

....በጣም ገርሞት ለካ አውቶብሱ ጥሎኝ የሔደው ለበጎ_ነው በሚል ፈጣሪውን እያመሠገነ ጉዞ ይጀምራል። የሚያገለግልበት ቦታ ደርሶም ስለተደረገለት ነገር ለአንድ ሣምንት እዛው ፈጣሪውን ሲያመሰግን ሰንብቶ ወደ ቤቱ ሲመለስ መኖሪያ ቤቱ ድንኳን ተተክሎ ያያል።

.....ምን ተፈጥሮ ይሆን? በሚል ጠጋ ብሎ ሲመለከት ለቅሶ ነው። ጎረቤቶቹ በሙሉ ደንግጠው እርሱን ሲያዩት ያያል። ሠውየውም "ማን ነው የሞተው?" ብሎ ይጠይቃል።
እነርሱም "አንተ" ይሉታል።

እርሱም እንዴት እኔማ ይሄው አለሁ አይደል። ይላል። የእርሱን በሕይወት መምጣት የሰሙ ቤተሰቦቹም ማመን አቅቷቸው እየመጡ ይጠመጠሙበታል።

ሐዘኑም ወደ ደስታ ይለወጣል። ሰውየውም ቤተሰቡም ጎረቤቱም ረጋ ብለው ስለተፈጠረው ሁኔታ ያወራሉ።
...ለካ አውቶብሱ ሲገለበጥ አደጋው የከፋ ስለነበር የሰዎቹ ማንነት በመልክ መለየት ስላልተቻለ የሟቾች ኪስ ፓሊስ እየበረበረ ማንነታቸውን መለየት ሲጀምር የሰውየውም የጠፋው ቦርሳ አንዱ የሰረቀውና አንዱ ሟች ኪስ ውስጥ ይገኛል።

...ፓሊስም በመታወቂያው መሠረት ለሰውየው ቤተሰቦች መርዶ ይነገራል። ለቤተሰቡም በቤ/ክን በተዘጋጀ አዲስ የመቃብር ቦታ ይቀብሩታል።
ለካ ሠውየው ነው ተብሎ የተቀበረው ሌባው ነው። ሁሉም ሠው ይህን ሲሰማ ይገረማል።

ከሰወችም መካከል አንዷ ልጁ "የአንተ አዲሱ መቃብር የተቀበረው ሌባው ነው። አንተ መቃብር ላይ ሌባ አይቀበርም። ይውጣ።" ስትል

....ሠውየው አንድ አስገራሚ ነገርተናገረ "
አይሆንም ሌባውን እወደዋለሁ ሞቴን የወሰደልኝ ሞቴን የሰረቀኝ ባለውለታየ ነው። እርሱ ቦርሳየን ሰርቆኝ ለምሳ መክፈያ ብር ፍለጋ ባልሔድ ኖሮ አውቶብሱ አያመልጠኝም ነበር። እኔም ሟች ነበርኩ። አትንኩት።" ነበር ያለው።

ፈጣሪ ሲፈቅድ ለካ ሞትም ይሰረቃል። አይገርምም?
የሰውየው ንግግር በጣም ይገርማል። "ነገር ሁሉ ለበጎ ነው።'' ሁሌም በመንገዱ ፈጣሪውን ያስቀደመ አያፍርም!

from Yosi Yos
ራስን መለወጥ
t.me/changeitwow

ራስን መለወጥ

01 Oct, 05:13


ከማልቀስ... የቱ ይሻላል?

ራስን መለወጥ

29 Sep, 16:32


3ቱ ትልቅ ትምህርቶች
.
.
.
ራስን መለወጥ
t.me/changeitwow

ራስን መለወጥ

26 Sep, 11:58


ከመስከረም 16 እስከ ጥቅምት 5 ያለው ጊዜ በቤተ ጉራጌ ወጣቶች እጅግ ተወዳጅ ጊዜ ነው። በዚህ ጊዜ በተለያዩ የገበያ ቦታዎች እና አብያተ ክርስቲያናት ወጣቶች ባህላዊ ጭፈራዎቻቸውን ያሳያሉ፤ እግረ መንገዳቸውንም ለትዳር የምትሆናቸውን ጉብል መልከት መልከት ያደርጋሉ። የወጣቶቹ ባህላዊ ጨዋታ “አዳብና” በሚል ስያሜ የሚታወቅ ሲሆን እዚህም የተነፋፈቁ ወጣቶች ተገናኝተው በንግድና በተለያዩ ምክንያቶች ቆይተው ስለመጡባቸው ቦታዎች ይጨዋወታሉ። በአዳብና ጨዋታውም ወጣት ሴቶች ያላቸውን አዲስ ልብስ ለብሰው የሚወጡበትና የወደፊት የትዳር አጋራቸውን ያማልላሉ። ፀጉራቸውን ሹሩባ ተሰርተው፣ ቅቤ ተቀብተው ከወትሮው በተለየ መልኩ አምረውና ተኩለው ወደ “አዳብና” የጭፈራው ቦታ ይመጣሉ። ወጣት ወንዶችም ቀልባቸው ያረፈባትን ሴት ለሚ በመስጠት ይመርጣሉ፤ ከዚያም ለሃገር ሽማግሌዎች በመንገር ወጉን እና ባህሉን ጠብቀው ለከርሞ የትዳር አጋራቸውን ያገኛሉ።

በአዳብና ጭፈራ ወቅት ሌላው ሳይጠቀስ የማይታለፈው ጉዳይ “የሙየቶች” የተለየ የጥበብ ትዕይንት ነው። በቤተ ጉራጌ የተመረጡ ሰዎች ካልሆኑ በስተቀር ማንኛውም ሰው ‘ሙየት’ መሆን አይችልም። ሙየቶች የተለየ ቋንቋ እና አጨፋፈር ያላቸው የተረጡ ሰዎች ናቸው። ሙየቶች ለአዳብና ጨዋታው የተለየ ድባብን ያላብሱታል። የሚናገሩት ቋንቋ ብቻ ሳይሆን የሚይዙት ልምጭም በአደይ አበባ የተሽቆጠቆጠ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ የተለየ ነው። ሙየቶች በዕለቱ ከመግደል በቀር በምድር ያለ ሁሉንም ስልጣን ይሰጣቸዋል። በጨዋታው ላይ ያልተገባ እንቅስቃሴ የሚያደርግ እድምተኛ ካጋጠማቸው በያዙት ልምጭ እንካ ቅመስ የማለት መብታቸው በአዳብናው ህግ የተረጋገጠ ነው። የተለየ ዜማቸውና ዳንሳቸው ሙየቶችን በአካባቢው ከሚታየው ቁጥር ስፍር ከሌለው ታዳሚ ለየት አድርጎ እንዲታዩ ያደርጋቸዋል። ይህንን የመሰሉ እሴቶችን ጠብቆ በማቆየት ለቀጣይ ትውልድ ከማስተላለፍ ባለፈ የቱሪዝም መስህብ በማድረግ ተጠቃሚ መሆን እንደሚቻል የቤተ ጉራጌ የመስቀል አከባበር በአል የሚነግረን ነገር የለም ትላላችሁ? አበቃሁ።

በዚሁ አጋጣሚ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኩዋን ለመስቀል በአል በሰላም አደረሳችሁ ማለት እፈልጋልሁ::

በዓሉ የሰላም የፍቅር እና የአንድነት እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።

መልካም የመስቀል በአል !!!😍😍😍🙏

ጸሐፊ: #ቢኒ_ይመር
ተገኘ ከFacebook

ራስን መለወጥ

26 Sep, 11:58


#መስቀል_በጉራጌ በጨረፍታ

የመስቀል በአል ሃይማኖታዊ በአል ቢሆንም ኢትዮጵያውያን የተለያዩ ባህሎቻቸውን እና እሴቶቻቸውን በማሳየት የሚያከብሩት በአል ነው። የመስቀል በአልን ከሌሎች በአላት ለየት የሚያደርገው ሰዎች በተለያዩ ንድፎች ያማሩ ባህላዊ ልብሶቻቸውን በመልበስ በጋራ ዳመራ በመደመር የሚያከብሩት በአል መሆኑ ነው። የበአሉ አከባበርም በርካታ የውጭ ሃገር ቱሪስቶችን ቀልብ የሳበና የዳመራው በአል በሚከበርበት ወቅት በርካቶቹ ወደ ሃገራችን በመምጣት ታዳሚ መሆን ከጀመሩ ሰነባብተዋል።

የመስቀል ደመራ በአል በ2006 ዓ.ም በዩኔስኮ በአለም ቅርስነት ተመዝግቧል። ስለሆነም በአሉ ከሀገራችን አልፎ በሌሎች ልዩ ስፍራ እንዲሰጠው ምክንያት ሆኗል። በገጠራማው የሃገራችን ክፍል በወንዝ ሙላት ምክንያት ተለያይተው የከረሙ የማህበረሰብ ክፍሎችን በማገናኘቱ ረገድ የመስቀል በአል የራሱ አዎንታዊ ሚና አለው። የመስቀል በአል በሁሉም አካባቢዎች የሚከበር ቢሆንም በደቡቡ የሀገራችን ክፍል (በተለይም በጉራጌ ማህበረሰብ) በተለየ ድምቀትና ባህላዊ ሁነት ይከበራል። በደቡብ ኢትዮጵያ የመስቀል በኣል ከሃይማኖታዊ ገፅታው በተጨማሪ በተለያዩ ባህላዊና ማህበራዊ እሴቶች ታጅቦ ይከበራል። የበኣሉ አከባበር እንደ የአካባቢው ይለያያል። በጉራጌ፣ በከንባታ እና በዶርዜ የመስቀል በአል ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ይከበራል።

የመስቀል በአል በቤተ ጉራጌ ከወትሮው የተለየ ቦታ አለው። በስራ ምክንያት ተለያይተው የቆዩ ቤተሰቦች የሚገናኙበት ብቻም ሳይሆን በጋራ እየበሉና እየጠጡ የሚያከብሩት በኣል ነው። በቤተ ጉራጌ የመስቀልን በአል ሰዎች ብቻ ሳይሆኑ እንስሳትም ጭምር ያከብሩታል። ለወትሮው ወደ ግጦሽ ሜዳ ወጥተው የዕለት ጉርሳቸውን ያገኙ የነበሩ የቀንድም ሆኑ የጋማ ከብቶች ታጭዶ በተዘጋጀላቸው መኖ ከቤት ሳይወጡ በአሉን እንዲያሳልፉ ይደረጋሉ። በቤተ ጉራጌ የመስቀል በኣል ለአንድ ቀን ብቻ ተከብሮ የሚያልፍ ቀን አይደለም። በብሄረሰቡ ተወዳጅ የሆነው የመስቀል በኣል በቀናት ተከፋፍሎ የሚከበር በኣል ነው። በቤተ ጉራጌ የመስቀል በአል ከመስከረም 12 እስከ ጥቅምት 5 ቀን ይከበራል። ከህፃናት ጀምሮ ወጣቶች እና አዛውንቱ የብሄረሰቡን ባህላዊ ምግብ ክትፎና ሌሎችን በመመገብ፣ በጭፈራና በፈንጠዝያ የመስቀልን በአል ያከብራሉ። የቀናቶቹን ስያሜና ባህላዊ ክዋኔዎቹን ቀጥለን እንመልከት።

መስከረም 13 ቀን የወልቀነ /ወሬት የኸና /

በሰባት ቤት ጉራጌ 'ወሬት የኸና’ ማለት እንቅልፍ ከልካዩ ቀን የሚል ትርጓሜን የያዘ ሲሆን ለዚህም በምክንያትነት የጉራጌ ሴቶች ለበአሉ ዝግጅት ለማድረግ የሚጓጉበት ቀን ከመሆኑ ጋር በተያያዘ እንደሆነ ይነገራል። በዚህ ቀን ለበአሉ ለመመገቢያነት የሚያገለግሉ ባህላዊ ቁሳቁሶች ለአመት ከተሰቀሉበት ቦታ ወርደው በጥንቃቄ ተጣጥበው ዝግጁ ይሆናሉ። የፅዳት ተግባሩ ከአጥንት የተሰሩ ባህላዊ የመመገቢያ ማንኪያዎች፣ ከሸክላ የተሰሩ ጣባዎች እና ሌሎችንም ይጨምራል። ይኸው ቀን በሶዶ ክስታኔ ጉራጌዎች ‘የወልቀነ’ ወይም የሴቶች ቀን በመባል ይታወቃል። ቤቶች ከአፈር በተዘጋጁ ቀለማት ያሸበርቃሉ፤ አዳዲስ የኬሻ ጅባዎች ተነጥፎባቸው ለበኣሉ ዝግጁ ይሆናሉ።

መስከረም 14 ቀን #ደንጌሳት

ይህ ቀን ልጆች እና ህፃናት ደመራ ደምረው ባህላዊ ጭፈራዎቻቸውን የሚያቀልጡበት ነው። ‘ደንጌሳት’ ወይም የልጆች ደመራ/እሳት የሚል ትርጓሜን የያዘ ሲሆን ልጆች ቀኑን በተለያዩ ባህላዊ ዘፈኖች ለቀኑ ስላበቃቸው ፈጣሪያቸውን ያመሰግኑታል። ከደመራው በኋላም ሴቶች የጎመን ክትፎ በማዘጋጀት በእያንዳንዱ የቤተሰብ አባል ውክልና በተዘጋጀ ጣባ በማድረግ ለምግብነት ያዘጋጃሉ። ባለትዳር የሆኑ የቤተ ጉራጌ አባላት በአንድ ጣባ የጎመን ክትፎው ተዘጋጅቶ ይሰጣቸዋል። ተምሳሌትነቱም የትዳር አጋሮች አንድ አካል አንድ አምሳል ናቸው ተብሎ ስለሚታመን የሚፈፀም ነው።

መስከረም 15 ጨርቆስ /ወኸመያ /

የጨርቆስ ቀን በቤተ ጉራጌ ዋናው የመስቀል በኣል የሚከበርበት ቀን ነው። ‘ወኸመያ’ ወይም አመት በአል የሚል ትርጉም አለው። በዚህ ቀን በሁሉም የብሄረሰቡ አካባቢዎች የእርድ ቀን ነው። በዕለቱም የሚታረደው በሬም ሆነ ወይፈን ሽማግሌዎች ፊት ቀርቦ ስለ ሃገር ሰላም እንዲሁም ስለ በአሉ መልካሙን የመመኘት ምርቃት የሚወርድበት ነው። የቤተሰቡ አባላትም በእያንዳንዱ ምርቃት መጨረሻ ላይ ሶስት ጊዜ “ኬር ይሁን” በማለት ምርቃቱን ይቀበላሉ። ‘ኬር ይሁን’ ትርጉሙ ሰላም ይሁን እንደማለት ነው። በዚህ ባህላዊ የምርቃት ስነ ስርአት አብዛኛውን ጊዜ እንዲመርቁ የሚጋበዙት በዕድሜያቸው ገፋ ያሉ አረጋውያን ሲሆኑ ወንዶችም ሆኑ ሴቶች እኩል ተሳትፎ ይኖራቸዋል። ከምርቃቱ በኋላም የቀረበውን ሰንጋ በማረድ ቁርጥ ስጋውን በተነጠረ ቅቤ በተዘጋጀ መበያ (ጨፉየ) እየነከሩ መመገብ የተለመደ ጉዳይ ነው።

መስከረም 16 የጉርዝ እሳት /ያባንዳ እሳት /

የጉርዝ እሳት /ያባንዳ እሳት/ ማለት የአባቶች ደመራ ማለት ሲሆን በዚህ ዕለት ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ተሳትፎ የሚያደርግበት የደመራ በአል ይከወናል። በዕለቱ አባቶች የተለየ ክብር ተሰጥቷቸው የደመራ በአሉን በምርቃት ያስጀምሩታል። ቀኑ ከባህላዊው ይልቅ መንፈሳዊ ይዘትን ተላብሶ ይከበራል። ጎረምሳና ልጃገረዶች ዳመራውን በመክበብ በተለያዩ ጭፈራዎች አካባቢውን ያደምቁታል። እገረ መንገዱንም ወጣቶቹ ለመተጫጨት የመጀመሪያ እይታ የሚያደርጉበትም ቀን ነው። ከጭፈራው በኋላም ሁሉም ወደ ቤቱ በመመለስ በራሱ ጣባ የተዘጋጀለትን ክትፎ ይበላል። በአንዳንድ የቤተ ጉራጌ አካባቢዎች ዕለቱ ‘የብርንዶ ቀን’ የክትፎ ቀን በመባል ይታወቃል።

መስከረም 17 የከሰል ማይ /ንቅባር /

በዚህ ቀን ከማለዳው 12 ሰአት ጀምሮ በአንድ አካባቢ የሚገኙ የቤተ ጉራጌ ነዋሪዎች ዳመራው ወደ ተቃጠለበት ቦታ በመሄድ የአካባቢያቸውን የዕድር ዳኛ በመቀየር አዲስ የሚመርጡበትና ቃለ መሃላ የማስፈፀም ተግባርን የሚያከናውኑበት ነው። ሁሉም የአካባቢው የቤተሰብ አባላት የተቃጠለውን የደመራ ከሰል እየዘለሉ በመጪው ዘመን መልካም ነገር እንዲገጥማቸው የሚመኙበት አልፎ ተርፎም የሚማፀኑበት ቀንም ነው።

መስከረም 18 የፊቃቆ ማይ

የአካባቢው ልጃገረዶች ለመጠቀሚያነት የሚውሉ ሰፌዶችን ለመስፋት የሚያገለግሉ ስንደዶዎችን የሚለቅሙበት ቀን ነው። የስንደዶ ለቀማው በባህላዊ ዜማዎች ታጅቦ ይከወናል።

በቤተ ጉራጌ ከመስከረም 17 እስከ መስከረም 23 የዘመድ መጠየቂያ ጊዜ ነው፤ የጀወጀ/የጀመቸ ተብሎም ይጠራል። ለአመት ተነፋፍቀው የቆዩ ቤተሰቦች ተገናኝተው ናፍቆታቸውን የሚገልፁበት ጊዜ ነው። የባል እንዲሁም የሚስት እናት እና አባት የሚጠየቁበት የተለያዩ ነገሮች በስጦታ የሚቀበሉበት ዕለት ነው። ሴት ልጆች ለእናቶቻቸው የፀጉር ቅቤ፣ ባርኔጣ፣ ጭራ እና ሌሎች ስጦታዎችን ሲያቀርቡ ባሎቻቸው ደግሞ የበግ ሙክት በመያዝ ይጠይቋቸዋል። ስጦታው የቀረበላቸው እናትና አባቶችም የልጆቻቸውን ባሎች እና ሚስቶች በየተራ ይመርቋቸዋል።

ራስን መለወጥ

24 Sep, 07:59


ታሪክን በፎቶ
ምን ተማራችሁ?
ራስን መለወጥ