#1_ለምንህን_ፈልግ
መነቃቃትን ሳይሆን ለምንህን ፈልግ። ያን ጊዜ ባንተና በግብህ መካከል ሰበብ አይፈጠርም!
ለግቦችህና ለድርጊቶችህ ጠንካራ ምክንያት የሚሆንህ ለምን? ፈልግ እንጂ በየ ጊዜው የሚቀያየር የመነቃቃት ስሜትን በመጠበቅ ጊዜህን አታባክን። ሲደክምህም፣ ፈተና ሲበዛብህም ብርቱ የሚያደርግህ ለምንህ እንጂ ስሜትህ አይደለም።
#2_ካልፈራህ_በቀር_ሰበብ_አታበዛም!
አዎ ሰበብ የፈሪዎች መደበቂያ ነው። አንተ ግን ፈሪ አይደለህም። ስለማትፈራ ሰበብ በማብዛት አትደበቅም። ትወጣለህ፣ ትጋፈጣለህ፣ ታሸንፋለህ!
#3_የማታገኘውን_ዛሬህን_ሁሌም_በምታገኘው_ሰበብ_አትጣው!
ሰበብ ሁልጊዜ አለ። መልካም እድልና አጋጣሚ የሚመጣው ግን አልፎ አልፎ ነው። ሰበብን ከፈለግከው ዛሬ፣ ነገ ወይም ከዓመታት በኋላም አታጣውም። ዛሬህ ግን የዛሬ ብቻ ነውና ተጠቀምበት!
#4_ሰበብ_ማሸነፍን_አጥበቀው_ለማይፈልጉት_ሰዎች_ነው!
ግብህን ምን ያህል ትፈልገዋለህ? የአሸናፊነት ርሃብህ እስከ የት ድረስ ነው? ሰበብ ካበዛህ በቂ ፍላጎትና ርሃብ የለህም ማለት ነው።
#5_ወዴት_እየሄድክ_ነው?
የት ነበርክ ወይም የት ነህ የሚለው አያሳስብም። ዋናው ወደ የት እየሄድክ ነው የሚለው ነው። ሰበብ አታብዛ!
ዋናው ቁምነገር መድረሻህ ነው። መነሻህ የትም ሊሆን ይችላል። ሁሉም የተደላደለ መነሻ አይኖረውም፤ ሁሉም ግን መድረሻውን የተደላደለ ማድረግ ይችላል። ይህ የሚሆነው ደግሞ ሰበብን የቆሻሻ ቅርጫት ውስጥ በመጣል ነው!!
ሰበብህን የቆሻሻ ቅርጫት ውስጥ በመጣል ሕልምህን መኖር ያስፈልጋል!!!
ራስን መለወጥ
t.me/changeitwow