ማክሰኞ ጥቅምት 12 ቀን 2017 (አዲስ ማለዳ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በጠቅላላ ጉባዔ፣ በኦዲት እና በሴት አባላት አማካኝነት ከሚገኝ የገንዘብ ድጋፍ ጋር በተያያዘ የዕግድ ደብዳቤ ይፋ አድርጓል፡፡
የወላይታ ብሄራዊ ንቅናቄና፣የአገው ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲን ጨምሮ 11 ፓርቲዎች ናቸው በቦርዱ እግድ የተጣለባቸው፡፡
ቦርዱ ፓርቲዎቹን ለምን እንዳገደ እስኪያሳውቅ ድረስም ፓርቲዎች ምንም አይነት ህጋዊ እንቅስቃሴ ማድረግ እንደማይችሉም ነው ያስታወቀው፡፡
ቦርዱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት እግድ የተጣለባቸው ፓርቲዎች ምንም አይነት የፖለቲካ እንቅስቃሴ እንዳያደርጉ ክትትል እንዲያደርግም አሳስቧል፡፡