የካቲት 08/2017 ዓ/ም
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት እያካሄደ ባለው 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤው የኮሌጃችን ማቋቋሚያ አዋጅን ጨምሮ የመስኖ ውሃ ተጠቃሚዎች ማህበርን ለማቋቋም ፣ የክልሉ ሰንደቅ አላማ አርማን ለመደንገግ ፣ የኢንቨስትመንት አስተዳደር ፣የበጎ ፈቃደኝነት ፖሊሲ እንዲሁም የሪጂዮ ፖሊስ ከተሞችን ለማደራጀት የወጣ ረቂቅ አዋጆችና የ2017 ዓ.ም ተጨማሪ በጀት መርምሮ አጽድቋል።
አዋጁ ኮሌጃችን ከኮሌጅ ወደ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ማደግ በሚችልበት ደረጃ በመጽደቁ መምህራን፣ አስተዳደር ሠራተኞች፣ተማሪዎችና ባለድርሻ አካላት እንኳን ደስ አላችሁ!