የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College) @wolaitasodoagricollege Channel on Telegram

የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College)

@wolaitasodoagricollege


የግብርና ሙያዎች ቤት

የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College) (Amharic)

ለወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ ቤት የትምህርት ምርጫ ወደአንድ ድምፅ ተገኝቶ እንዲሆኑ ያስፈልጋል። ወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ ቤት ውስጥ የእቃ ሲያሰቡበት ወይም የበጋም ሲታደጉበት ከተወለደ የግብርና ሙያዎች እና የመከላከያ መንገዶች ከሚሆንበት ምኒልክ ተዘጋጅተው የተጠቀሱ ናቸው። የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ ቤት የአካባቢ የትምህርት ቤት ለማግኘት በአጭር ድምፅ የምንኖረውን የአንድነት ወሳኝ ከሆነ፣ በተቋቋመ ጉዳዩ ይጠይቃል። ወደ ታገደ ክፍት የትምህርት እና ሌሎች የአካባቢ መረጃዎች ይሂኳል።

የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College)

15 Feb, 13:57


የክልሉ ምክር ቤት የኮሌጃችን ማቋቋሚያ አዋጅን ጨምሮ 7ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ አጸደቀ።

የካቲት 08/2017 ዓ/ም

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት እያካሄደ ባለው 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤው የኮሌጃችን ማቋቋሚያ አዋጅን ጨምሮ የመስኖ ውሃ ተጠቃሚዎች ማህበርን ለማቋቋም ፣ የክልሉ ሰንደቅ አላማ አርማን ለመደንገግ ፣ የኢንቨስትመንት አስተዳደር ፣የበጎ ፈቃደኝነት ፖሊሲ እንዲሁም የሪጂዮ ፖሊስ ከተሞችን ለማደራጀት የወጣ ረቂቅ አዋጆችና የ2017 ዓ.ም ተጨማሪ በጀት መርምሮ አጽድቋል።

አዋጁ ኮሌጃችን ከኮሌጅ ወደ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ማደግ በሚችልበት ደረጃ በመጽደቁ መምህራን፣ አስተዳደር ሠራተኞች፣ተማሪዎችና ባለድርሻ አካላት እንኳን ደስ አላችሁ!

የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College)

07 Feb, 17:48


የኮሌጃችን መስኖና ዲይኔጅ ት/ት ክፍል አንደኛ ዓመት መደበኛ መርሐ-ግብር ተማሪዎች የአየር ንብረት መረጃ መመልከትና መቆጣጠር ላይ የተግባር ልምምድ ማድረጋቸውን ት/ት ክፍሉ አስታወቀ።

ወ/ሶ/ግ/ኮ ጥር 30/2017 ዓ/ም

የኮሌጃችን መስኖና ዲሬይኔጅ ት/ት ክፍል አንደኛ ዓመት መደበኛ መርሐ-ግብር ተማሪዎች ወደ የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሜትሮሎጂ ኢኒስቲትዩት ወላይታ ሶዶ ቅርንጫፍ በመሄድ የአየር ንብረት መረጃ መመልከትና መቆጣጠር ላይ የተግባር ልምምድ ማድረጋቸውን የትምህርት ክፍሉ ኃላፊ መ/ር ዳህላክ ጨመሰ አስታውቀዋል።

መ/ር ዳህላክ አያይዘውም ፣ ተማሪዎቹ የአየር ፀባይ መሣሪዎች ልየታና መረጃ አመዘጋገብ፣የተመዘገበውን መረጃ ወደ ተግባር መቀየርና ሪፖርት አጻጻፍ ላይ ተግባር ልምምድ ማድረጋቸውን አስረድተዋል ።

የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College)

07 Feb, 08:30


የኮሌጃችን አዲሱ ድህረገጽ ይፋ ሆነ።

የኮሌጃችን የተሟላ፣ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ የምናሰራጭበት አዲሱ ድሀረግጽ(Website) ይፋ አድርግናል።

የድህረገጹ አድረሻም፦https://wsavet.edu.et/

የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College)

28 Jan, 12:09


ከወላይታ ሶዶና ጉኑኖ ሐሙስ ከተማ አስተዳደር ለተውጣጡ ነዋሪዎች በሽቅብ ግብርና ላይ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል።

ወ/ሶ/ግ/ኮ ጥር 20/2017 ዓ/ም

ኮሌጃችን ከወላይታ ሶዶና ጉኑኖ ሐሙስ ከተማ አስተዳደር ለተውጣጡ ነዋሪዎች በሽቅብ ግብርና ላይ የተግባር ተኮር ሥልጠና እየሰጠ ይገኛል።

በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሌጃችን ዲን ዶ/ር አሉላ ታፈሰ፣ ኮሌጃችን የወላይታ እርሻ ልማት ዩኒት(WADU) ሆኖ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ለአገራችን ኢኮኖሚ ዋልታ ለሆነው ግብርና ብቁ ባለሙያ አሠልጥኖ በማበርከት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ኮሌጃችን አሁኑ ሰዓት ከመማር ማስተማር ሥራ ጎን ለጎን የግብርና ቴክኖሎጂ ለማሸጋገር ለአከባቢው ማህበረሰብ የተለያዩ ሥልጠናዎችን እየሰጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ሰልጣኞች ሥልጠናውን ለራሳቸው ወስደው መተው ብቻ ሳይሆን ከሥልጠናው ያገኙትን ዕውቀትና ክህሎት በመጠቀም በራሳቸው ግቢ በመስራት ሌሎችን ማስተማር እንዳለባቸው መክረዋል።

የኮሌጃችን ትምህርት ሥልጠና ዘርፍ ኃላፊና ም/ዲን አቶ ታሪኩ ጨመረ በበኩላቸው፣ ኮሌጃችን በዋናነት በመማር ማስተማር፣ በምርምርና የአከባቢ ማህበረሰብ ችግር በመለየትና በመፍታት ለማህበረሰቡ ለውጥ እንደሚሰራና ሥልጠናውም የዚህ አካል መሆኑን አስገንዝበዋል።

ሥልጠናው የተዘጋጀው ሠልጠኞች ከመሬት በላይ የጓሮ አትክልቶችን በራሳቸው ግቢ ማምረትና መመገብ እንዲችሉ ለማድረግ መሆኑን ጠቁመዋል።

የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College)

24 Jan, 15:45


በኮሌጃችን ምርምርና የማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፍ እየተሠሩ ያሉ ሥራዎች ላይ የመስክ-ምልከታና ውይይት ተደረገ::

ወ/ሶ/ግ/ኮ ጥር 16/2017 ዓ/ም

የኮሌጃችን ምርምርና ስርፀት አስተባባሪና የኮሚቴ አባላት እንዲሁም የተለያዩ ፕሮጀክት ሥራዎችን እየሠሩ ያሉ መምህራን አሳማና ንብ እርባታ፣ ሆም ጋርዴን፣ ሽቅብ ግብርናና ቨርሚ ኮምፖስት ላይ የመስክ-ምልከታና ውይይት በዛሬው ዕለት አካሂደዋል።

ውይይቱና መስክ-ምልከታው በተደረገበት ወቅት ላይ አስተያይታቸውን የሰጡ መምህራን እንደተናገሩት ፣ እየተሰሩ ያሉ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ሥራዎች ይበል የሚያሰኙ በመሆናቸው ወደ አከባቢው ማህበረሰብ በስፋት የማድረስና የማስረጽ ሥራ ልሰራ እንዳለበት ተናግረዋል።

የኮሌጃችን የምርምርና ስርፀት ማስተባበሪያ ኃላፊ መ/ር መስፍን ጌታቸው፣ የተሰሩ የምርምና የማህበረሰብ አገልግሎት ሥራዎችን ወደ አከባቢው ማህበረሰብ የማድረስና የማስረጽ ሥራ እንደተሰራና በቀጣይም በስፋት ለማድረስ መታቀዱን ገልጸዋል።

የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College)

18 Jan, 10:06


የኮሌጃችን ዲን ዶ/ር አሉላ ታፈሰ የጥምቀት በዓል አስመልክተው ለክርስትና እምነት ተከታይ መምህራን፣ አስተዳደር ሠራተኞች፣ ተማሪዎችና ባለድርሻ አካላት ያስተላለፉት የመልካም ምኞት መግለጫ፡-

እንኳን ለጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን!

የጥምቀት በዓል የሚያስታውሰንና የሚያስተምረን መታደስን፣ትህትና፣አንድነትና አብሮነት ነውና የኮሌጃችን ራዕይና ተልዕኮ በጋራ ለማሳካት የተሰጠን ኃላፊነት በትህትና፣ በአንድነትና በአብሮነት መወጣት ይጠበቅብናል፡፡

በዓሉ በክልላችን እንዲሁም አገራችን ደረጃ በእምነቱ ተከታዮች ዘንድ በድምቀት ከሚከበሩ በዓላት መካከል አንዱ ሲሆን የሃይማኖታዊ ይዘቱን፣ትዉፊቱንና ባህላዊ እሴቱን ሳይለቅ ለዘመናት ሲከበር የቆዬ በመሆኑ በዓለም አቀፍ ደረጃ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትምህርት፣የሳይንስና የባህል ተቋም (UNESCO) በማይዳሰስ ቅርስነት ልመዘገብ ችሏል፡፡ ስለሆነም ይህንን ሃይማኖታዊ፤ ባህላዊ እና ኅብረ ብሔራዊ በዓላችን ለመጪው ትውልድ የሃይማኖታዊ ይዘቱ፣ትዉፊቱንና ባህላዊ እሴቱ ሳይሸራረፍ ለማስተላለፍ ሁላችን ገንቢ ሚና መጫወት እንዳለብን አሳስባለሁ!

በዓሉን ስናከብር የተመለደውን የመረዳዳት፣ የመጠያየቅ፣የመተባበርና የመቻቻል ባህላችን ሳንዘነጋ ይሁን እያልኩ፤በዓሉ የሰላም፣ የጤና፣ የደስታ፣ የብልጽግና የአብሮነት እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ!

በድጋሚ እንኳን በሰላም አደረሳችሁ፣አደረሰን!

መልካም በዓል!

ወ/ሶ/ግ/ኮ ጥር 10/2017 ዓ/ም

የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College)

16 Jan, 15:13


በቨርሚ ኮምፖስት አዘገጃጀትና ሽያጭ ላይ ያተኮረ ሥልጠና ከወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ለተውጣጡ አርሶአደሮች ተሰጠ፡፡

ወ/ሶ/ግ/ኮ ጥር 08/2017 ዓ/ም

ኮሌጃችን ከወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ለተውጣጡ አርሶ አደሮች በቨርሚ ኮምፖስት አመራረትና ሽያጭ ዙሪያ የተግባር ተኮር ሥልጠና ሰጥቷል፡፡

በሥልጠናው ማስጀመሪያ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሌጃችን ዲን ዶ/ር አሉላ ታፈሰ፣ ኮሌጁ በተሻለ መልክ አዳድስ ቴክኖሎጂ ወደ ማህበረሰቡ ለማድረስ ከመማር ማስተማር ሥራ ጎን ለጎን ይሰራል ሲሉ በመግለጽ፣ ሥልጠናው የዚህ አንዱ አካል መሆኑን አስታውቀዋል።

የትምህርት ሥልጠና ዘርፍ ኃላፊና ም/ዲን ተወካይ መ/ር አገኘሁ አላሮ በበኩላቸው፣ ኮሌጃችን መማር ማስተማር ሥራ ጎን ለጎን ማህበረሰቡን የሚጠቅም የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ሥራዎች ወደ ማህበረሰቡ ማድረስ ተልዕኮው አካል እንደመሆኑ መጠን በሽቅብ ግብርና፣ በክይሆል ጋርዴንና በቨርሚ ኮምፖስትን ጨምሮ በእንስሳት እርባታ ዘርፍ የተለያዩ ሥራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

መ/ር አገኘሁ አክለውም፣ የሥልጠና ዓላማ ሠልጣኞች በተፈጥሮ የሚገኝ ማዳበሪያ ማምረትና መጠቀም እንዲችሉ ማድረግ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ሥልጠናውን ከወሰዱት መካከል ያነጋገርናቸው የድል በገሬራ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አቶ አዳሙ ዲማ፣ በሥልጠናው አዲስ ነገር ማግኘታቸውና በራሳቸው ለመሥራት በቂ ዕውቀት ማግኘታቸውን በመናገር፣ ከራሳቸው አልፈው በአከባቢያቸው ያሉ ሌሎች አርሶአደሮችን በማስተማርና በማስረጽ ቴክኖሎጂውን እንደሚያስፋፉ ጠቁመዋል፡፡

የፋና ወምባ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ አበራሽ ገብሬ በበኩላቸው፣ ሥልጠናው ደስ የሚያሰኝ መሆኑን በመናገር፣ያልተበከለና ተፈጥራዊ የሆነ ምግብ በራሳቸው መሬት አምርተው ለመመገብ ዕውቀት መቅሰማቸውን አመላክተዋል፡፡

የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College)

14 Jan, 17:37


የኤስ ኤን ቪ ፕሮጀክት ክልላዊና አገር አቀፍ ደረጃ አስተባባሪዎችን ጨምሮ ከኒዘርላንድ ኢምባሲ የተውጣጣ ልዑካን ቡድን ወደ ኮሌጃችን በመምጣት ውይይትና መስክ ምልከታ አካሄደ።

ወ/ሶ/ግ/ኮ ጥር 06/2017 ዓ/ም

የኤስ ኤን ቪ (SNV) ፕሮጀክት ክልላዊና አገር አቀፍ ደረጃ አስተባባሪዎችን ጨምሮ ከኒዘርላንድ ኢምባሲ የተውጣጣ ልዑካን ቡድን ወደ ኮሌጃችን በሆርቲ ላይፍ ፕሮጀክት ታቅደው የተሰሩ ሥራዎችን በሚመለከት ውይይትና መስክ ምልከታ አደርጓል።

ልዑካን ቡድኑ ውይይትና መስክ ምልከታ ባደረገበት ወቅትም ፣ኮሌጃችን ከፕሮጀክቱ ጋር በመቀናጀት በተማሪዎች ማሳ፣ በሥርዓተ ጾታ፣በአቅም ግንባታና በሌሎች ዘርፎች ባከናወናቸው ተግባራት ላይ ገለጻ ተደርጓል።

ልዑካን ቡድኑ በተማሪዎች ማሳ ላይ በሰብል ልማት ትምህርት ክፍል ተማሪዎች እየተሰሩ ያሉ የእርሻ ልማት ሥራዎችንና ሽቅብ ግብርና በመጎብኘት መስክ ምልከታ አድርጓል።

በማጠቃለያው ላይ አስተያየት የሰጡ የልዑካን ቡድኑ አባላት፣ ከውይይቱና መስክ ምልከታው ብዙ ልምድ እንዳገኙና ኮሌጃችን እንዴት ከፕሮጀክቱ በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝ መመልከት መቻላቸውንና ያዩት ነገር እጅግ ጥሩ መሆኑን ተናግረዋል ።

የኮሌጃችን ዲን ዶ/ር አሉላ ታፈሰ በማጠቃለያው ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ፕሮጀክቱ የሰራው ሥራ እጅግ ጠቃሚና አስፈላጊ መሆኑን በመጥቀስ፤ ፕሮጀክቱ ላበረከተው አስተዋፅኦ ምስጋና አቅርበዋል።

ዲኑ አክለውም፣ በፕሮጀክቱ የተሰሩ ሥራዎች የማዝለቅና በሌሎች ዘርፎችም የማስፋት ሥራ በኮሌጃችን እንደሚሰራ ጠቁመዋል።

የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College)

13 Jan, 18:13


የሐዘን መግለጫ

የኮሌጃችን አንደኛ ዓመት ሰብል ልማት ትምህርት ክፍል መደበኛ መርሐ-ግብር ተማረ በነበረው ተማሪ ታምራት አቤል መና ድንገተኛ ህልፈተ ህይወት የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን እየገለጽን፤ ለወላጆቹ፣ዘመዶቹ፣ ወዳጆቹና ክፍሉ ተማሪዎች መጽናናትን እንመኛለን!

የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College)

06 Jan, 11:25


የኮሌጃችን ዲን ዶ/ር አሉላ ታፈሰ የኢየሱሰ ክርስቶሰ ልደት በዓል አስመልክተው ያስተላለፉት የመልካም ምኞት መግለጫ፡-

የክርስትና እምነት ተከታይ የሆናችሁ የኮሌጃችን መምህራን፣ አስተዳደር ሠራተኞች፣ተማሪዎችና ባለድርሻ አካላት በቅድሚያ በራሴና በኮሌጁ ስም እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣አደረሰን ለማለት እወዳለሁ!

በዓሉ የእምነቱ ተከታዮች ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ልጅ ለማዳን ከላይ ከሰማያት ሰማይ ወርዶ፣ከድንግል ማርያም በከብቶች በረት ውስጥ የተወለደበትን በማሰብ የሚውሉበት፣ የተለያዩ መንፈሳዊና ማህበራዊ ኩኔቶችን የሚያከናውኑበት ነው፡፡

የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት የሚያስተምረን ፍቅር፣ ርሕራሔና ደግነት ነውና በዓሉን በምናክበርበት ጊዜ በመተሳሰብ፣እርስበርስ በመዋደድና በመተጋገዝ፣ ማዕድ በማጋራትና መሰል በጎ ተግባራበትን በፍቅር፣ርሕራሔና ደግነት ማከናወን እንዳለብን አሳስባለሁ፡፡

በዓሉ የሰላም፣ የአብሮነት፣ የብልጽግና፣ የጤናና የደስታ እንዲሁናችሁ እመኛለሁ!

በድጋሚ እንኳን በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን!

መልካም በዓል!

ዶ/ር አሉላ ታፈሰ
የኮሌጁ ዲን

የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College)

25 Dec, 19:42


የዩንቨርሲቲው ሦስተኛ ዓመት ዕፅዋት ሳይንስ መደበኛ መርሐ-ግብር ተማሪዎች ወደ ኮሌጃችን በመምጣት የተግባር ልምምድና ልምድ ልውውጥ አደረጉ፡፡

ወ/ሶ/ግ/ኮ 16/04/2017 ዓ/ም

የወላይታ ሶዶ ዩንቨርሲቲ ሦስተኛ ዓመት ዕፅዋት ሳይንስ መደበኛ መርሐ-ግብር ተማሪዎች ወደ ኮሌጃችን በመምጣት በቨርሚ ኮምፖስት ላይ ተግባር ልምምድ አድርገዋል፡፡

ከተግባር ልምምዱም በኋላ ቦቴኒካል ጋርዴንና ሽቅብ ግብርን ጨምሮ ሌሎችን በመጎብኘት ልምድ ልውውጥ አድርገዋል፡፡

የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College)

20 Dec, 04:05


የኮሌጃችን መሰረታዊ የመምህራን ማህበር ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ የሥራ ሪፖርት በማዳመጥ የዓመቱ ዕቅድ በማጽደቅ ፣የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ምርጫ አደረገ፡፡

ወ/ሶ/ግ/ኮ ታሕሳስ 11፣ 2017 ዓ/ም
የኮሌጃችን መሠረታዊ መምህራን ማህበር ጠቅላላ ጉባኤ ያካሄደ ሲሆን በጉባኤውም የሥራ ሪፓርትና 2017 ዓ/ም ዕቅድ ላይ ገለጻና ውይይት እንዲሁም የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ምርጫ አካሂዷል፡፡

በመድረኩ ላይ በመገኘት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሌጃችን ዲን ዶ/ር አሉላ ታፈሰ፣ የጉባኤው ታዳሚዎች እንኳን ለጠቅላላ ጉባኤ አደረሳችሁ በማለት፣ምቹ የሆነ የመማር ማስተማር ሁኔታ ለመፍጠር ጠንካራ ማህበር አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በመድረኩ ቀድሞ የማህበሩ ሊቀ-መንበር መ/ር ዳህላክ ጨመሰ የማህበሩ ሥራ ሪፖርትና 2017 ዓ/ም ዕቅድ ላይ ለጉቤኤው ገለጻ አድርገዋል፡፡

በቀረበው የሥራ ሪፖርትና ዕቅድ መነሻ በመድረኩ ዕድል የወሰዱ የማህበሩ አባላት ለኮሌጃችን ሁለንተናዊ ለውጥ መሰረታዊ ማህበሩ ስላበረከተው አስተዋጽኦ በማመስገን፤የመምህራን ጥቅምን ለማስከበር፣የመማር ማስተማርና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ማህበሩ ስለሰራቸው ተግባራት በተመለከተ ጥያቄና አስተያየት ሰጥተዋል፡፡
ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ከመድረኩ ሰፋ ያለ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል ፡፡

ከውይይቱ በኋላ የማህበሩ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ምርጫ የተካሄደ ሲሆን ከጉባኤው ከተጠቆሙ መካከል አብላጫ ድምጽ ያመጡ መ/ራን ተመርጠዋል፡፡ በዚህም መሰረት፡-መ/ርት ብርቱካን ኢሳያስ የማህበሩ ሊቀ-መንበር፣ መ/ር ክሩቤል ተስፋዬ ዋና ፀሐፊ፣ መ/ርት ሊድያ ቦጋለ ሥርዓተ-ጾታ፣ መ/ር ንጋቱ ማርቆስ ገንዘብ ያዥና መ/ር እሸቱ ጳውሎስ ሂሳብ ሹም በመሆን ተመርጠዋል፡፡

የማህበሩ ሰብሳቢ በመሆን አዲስ የተመረጡት መ/ርት ብርቱካን ኢሳያስ ባስተላለፉት መልዕክት፣ጉባኤው እኔን አምኖ እስከመረጠኝ ድረስ ዘር፣ቀለምና ሀይማኖት ለይቼ አድሎ ሳላደርግ ሁሉንም አባላት በእኩልነት አገለግላለሁ ሲሉ ጠቁመዋል፡፡

የኮሌጃችን ዲን ዶ/ር አሉላ ታፈሰ በመድረኩ ማጠቃላያ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፣የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበር ኮሌጃችን የተሻለ መስመር እንዲያዝ ስላበረከተው አስተዋጽኦ አመስግነዋል፡፡

የክልሉ መምህራን ማህበር ዋና ፀሐፊ አቶ ጌታቸው ካሳ ለጉባኤው ባስተላለፉት መልዕክት፣የመሰረታዊ ማህበሩ አባላት ለእውነት የሚሰሩ አመራሮችን በማግኘታቸው ዕድለኞች እንደሆኑ በማመላከት፤ከጎናቸው ሆነው መደገፍ እንዳለባቸው መክረዋል፡፡

የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College)

19 Dec, 17:10


ኮሌጃችን በትምህርት ዘመኑ በሣምንቱ መጨረሻ ቀናት የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎችን መልምሎ ለመቀበል የመግቢያ ፈተና ተሰጠ።

ወ/ሶ/ግ/ኮ 10/04/2017 ዓ/ም

ኮሌጃችን በ2017 ዓ/ም የትምህርት ዘመን በተከታታይ ትምህርት መርሐ-ግብር ሣምንቱ መጨረሻ ቀናት የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎችን መልምሎ ለመቀበል፣ ለመማር ላመለከቱ ዕጩ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና በዛሬው ዕለት ተሰጥቷል።

በስድስቱ የሙያ ዘርፎች ማለትም በሰብል ልማት፣ እንስሳት እርባታ፣ ተፈጥሮ ሀብት አያያዝ፣ እንስሳት ጤና፣ መስኖና ዲሬይኔጅ እንዲሁም በሕብረት ሥራ ሂሳብ አያያዝና ኦዲት ለመማር ያመለከቱ ዕጩ ተማሪዎች ከ900 በላይ ናቸው።

የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College)

07 Dec, 09:38


በክልሉ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ኤጄንሲ መሪነት በተለያዩ የሙያ መስመሮችና ደረጃዎች በኮሌጃችን ሲካሄድ የቆየው የሙያ ብቃት ምዘና ሂደት በሰላምና በስኬት መጠናቀቁ ተገለጸ፡፡

የኮሌጃችን ት/ት ሥልጠና ዘርፍ ኃላፊና ም/ዲን አቶ ታሪኩ ጨመረ፣በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሙያ ብቃት ማረጋገጫ ኤጄንሲ መሪነት በተለያዩ የሙያ ደረጃዎችና መስመሮች ከቀን 26/03/17 ዓ/ም እስከ 27/03/17 ዓ/ም ድረስ ሲካሄድ የቆየው የሙያ ብቃት ምዘና ሂደት በሰላምና በስኬት መጠናቀቁን አስታውቀዋል፡፡

የዘርፉ ኃላፊዉና ም/ዲኑ አያይዘውም፣ ለሥራው ስኬት የበኩላቸውን የተወጡ የኤጄንሲው ማኔጅሜንትና መዛኞችን፣የኮሌጃችን ት/ት ክፍል ኃላፊዎችን፣ የሙያ ብቃት ምዘና ሠራተኞችን፣ኮሚቴ አባላትን ና የኮምፒውተር ባለሙያዎችን ጨምሮ ሌሎችን አመስግነዋል፡፡

የኮሌጃችን ሙያ ብቃት ምዘና ማስተባበሪያ ኃላፊ መ/ር በለጠ ቦቴ በበኩላቸው፣ምዘና የተሰጠው በአሮጌውሥርዓተ-ትምህርት በሰብል ልማት በሙያ ደረጃ ሁለት እስከ ዓራት፣በእንስሳት እርባታ በሙያ ደረጃ ዓራት፣በተፈጥሮ ሀብት አያያዝ በሙያ ደረጃ በሦስትና ዓራት መሆኑን በመግለጽ፤ በአዲሱ ሥርዓተ-ትምህርት በሰብል ልማት፣በእንስሳት እርባታ፣በተፈጥሮ ሀብት፣በመስኖና ዲሬይኔጅ እንዲሁም ሕብረት ሥራ ሂሳብ አያያዝና ኦዲትንግ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

መ/ር በለጠ አክለውም፣ በአሮጌው ሥርዓተ-ትምህርት የተመዘኑትን 253 ና በአዲሱ ሥርዓተ-ትምህርት የተመዘኑትን 254 ተመዛኞችን ጨምሮ በአጠቃላይ 507 ተመዛኞች መመዘናቸውን ተናግረዋል፡፡

የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College)

05 Dec, 19:06


ኮሌጃችን ከልማት ማህበሩ ጋር በመተባበር ከሁምቦ ወረዳ ለተወጣጡ አርሶ አደሮች በቨርሚ ኮምፖስት አዘገጃጀትና ሽያጭ ዙሪያ ሥልጠና ሰጠ።

ኮሌጃችን ከጤረጴዛ ልማት ማህበር ጋር በመተባበር ከሁምቦ ወረዳ ለተወጣጡ አርሶ አደሮች በቨርሚ ኮምፖስት አመራረት፣አያያዝ፣ምርት አሰባሰብና ሽያጭ ላይ ያተኮረ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡

ሥልጠናውም ተግባር-ተኮር ሲሆን አርሶ አደሮቹ በራሳቸው ለማምረት እንዲችሉ ከማድረግ ባለፈ  ምርቱን አምርተው እንዲሸጡ ለማስቻል  ያለመ ነው፡፡

የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College)

03 Dec, 20:21


ኢቢሲ ኮሌጃችን ላደረገው አስተዋጽኦ የምስጋና ሰርተፊኬት አበረከተ።

ኢትዮጽያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን(ኢቢሲ) ተጨማሪ የይዘት ምንጭ በደቡብ ኢትዮጽያ ክልል ወላይታ ሶዶ ከተማ በዛሬው ዕለት ላስመረቀው ስቱድዮ ኮሌጃችን ግቢውን በአረንጓዴ ውበት በማሳመር ላደረገው አስተዋጽኦ የምስጋና ሰርተፊኬት አበርክቷል።

የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College)

30 Nov, 15:57


ኮሌጃችን በትምህርት ዘመኑ የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎችን መልምሎ ለመቀበል ያካሄደው የመግቢያ ፈተና በሁሉም ማዕከላት በሰላም ተጠናቅቆ፣ ውጤቱን በቅርብ ቀናት ውስጥ ለመግለጽ እርማቱ እየተፈጣነ ይገኛል።

ኮሌጃችን በ2017 ዓ.ም  የትምህርት ዘመን የመጀመሪያ ዓመት መደበኛ መርሐ-ግብር ተማሪዎችን መልምሎ ለመቀበል  በደቡብ ኢትዮጽያ ክልል በወላይታ፣ ጋሞ፣ ጎፋ፣ ጌዴኦ፣ ደቡብ ኦሞ፣ አሪ፣ አማሮ፣ ባስኬቶ፣ ቡርጂ፣ኮንሶ፣ ኧሌ እና ጋርዱላ የዞን ማዕከላት ያካሄደው የመግቢያ ፈተና(Entrance Exam) በሰላም ተጠናቅቆ፣እርማቱ እየተፋጠነ ይገኛል።

ውጤቱን በቅርብ ቀናት ውስጥ የምንገልጽ ሲሆን ያለፉ ተማሪዎች ምዝገባ በቅርብ ቀናት ውስጥ እንደሚካሄድ ከወዲሁ ለመግለጽ እንወዳለን።

ለሥራው ስኬት አስተዋጽኦ ያበረከቱ የክልሉ ግብርና ቢሮንና ሕብረት ሥራ ኤጄንሲን፣አሥራ ሁለቱ ዞኖች የግብርናና ሕብረት ሥራ መምሪያዎችን ፣የፀጥታ ዘርፎችን፣ የኮሌጃችን መምህራንና ሌሎችን እናመሰግናለን!

የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College)

23 Nov, 07:05


ኮሌጃችን ለሰንበት ገበያ የግብርና ምርቶችን ማቅረቡን አጠናክሮ ቀጠሏል።

ኮሌጃችን ለሰንበት ገበያ የግብርና ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ማቅረቡን አጠናክሮ በመቀጠል የአከባቢውን ገበያ ለማረጋጋት በሚደረገው ጥረት የበኩሉን እየተወጣ ይገኛል።

የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College)

19 Nov, 11:04


የኮሌጃችን  መስኖ አውታር /Irrigation canal/ የማጽዳት  ዘመቻ በመከናወን ላይ ይገኛል።

  ኮሌጃችን ካልቴ ወንዝ የገደበው የመለስተኛ መስኖ አውታር በዘንድሮው በጋ ወቅት የበጋ መስኖ ስንዴን ጨምሮ የተለያዩ ሰብሎችን ለማምረት እንዲቻል  የማጽዳት ዘመቻ በመከናወን ላይ ይገኛል።

በዘመቻውም የኮሌጃችን ከፍተኛ አመራሮች፣የሥራ ክፍል ኃላፊዎችና ተማሪዎችን ጨምሮ ሌሎች እየተሳተፉ ይገኛል።

በዘመቻው በመሳተፍ የድርሻቸውን እየተወጡ ያሉትን ሁሉ እናመሰግናለን!

የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College)

16 Nov, 10:16


ኮሌጃችን ያመረታቸውን የግብርና ምርቶች በተከታታይ ለሰንበት ገበያ እያቀረበ ነው።

ኮሌጃችን ያመረታቸውን የግብርና ምርቶችን ለሰንበት ገበያ በተከታታይ በማቅረብ የአከባቢውን ገበያ ለማረጋጋት የድርሻውን እየተወጣ ይገኛል።

የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College)

09 Nov, 15:54


ተመራቂዎቹ መንግስት የቀረጻቸውን የብዝኃን ዘርፍ ኢኮኖሚ ፖሊሲንና ሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሥራዓትን እንዲሁም የአረንጓዴ አሻራ፣ የሌማት ትሩፋት፣የበጋ መስኖ ስንዴና ሌሎች ኢንሼቲቮች ላይ የጠራ ግንዛቤ በመያዝ የሀገራችን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ በሚደረገው ርብርብ የድርሻቸውን ለማበርከት ቆርጠው መነሳት እንዳለባቸው መከሩ፡-ኮምሽነር ጋንታ ጋምአ

ኮሌጃችን በዛሬው ዕለት በተለያዩ የሙያ መስኮች 534 ተማሪዎችን በመካከለኛ ደረጃ ማስመረቁን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

በምረቃው ሥነ-ሥርዓት የሥራ ሪፖርት ያቀረቡት የኮሌጃችን ዲን ዶ/ር አሉላ ታፈሰ፤ኮሌጁ በተጠናቀቀው 2016 የሥልጠና ዘመን በመደበኛና ተከታታይ ትምህርት መርሐ-ግብር በአጠቃላይ 5229 ተማሪዎችን በአካዳሚክ ካሌንደር መሰረት ማሰልጠኑን በመግገለጽ፤ ከነዚህ ውስጥም 1135 ተማሪዎችን በአዲሱ ሥርዓተ-ትምህርት በመደበኛ መርሐ-ግብር በንድፈ-ሃሳብና በተግባር በመካከለኛ ደረጃ በማሰልጠን ሐምሌ 6 2016 ዓ/ም ማስመረቁን አስታውሰዋል፡፡

በሥልጠና ዘመኑ የ70/30(70% በተግባርና 30% በንድፈ-ሃሳብ) ሥልጠና ሞዳሊቲ በተጠናከረ መልኩ ተግባራዊ መደረጉን ያወሱት ዲኑ፤ተማሪዎች በኮሌጃችን ባሉ ሠርቶ ማሳያዎች እና ቤተ-ሙከራዎች ከሚሰሩት የተግባር ልምምዶች በተጨማሪ አከባቢያችን ባሉት ተቋማት ላይ የትብብር ሥልጠናዎችን ከወትሮ በተሻለ ሁኔታ መከታተላቸውን አስረድተዋል፡፡

የኮሌጃችን የውስጥ አቅሙን ለማሳዳግ፣የውስጥ ገቢ የማሰባሰብ አቅም ለማጎልበት እና ምቹ የሥራ ሁኔታን ለመፍጠር እየተሰሩ ከሚገኙ ሥራዎች መካከል የመምህራን ማደሪያ ሕንጻዎች ግንባታ ወደ 45% መጠጋቱን፣ዘመናዊ የዶሮ ቤቶች ግንባታ፣ የዋና እና ተማሪዎች መግቢያ በሮች ሙሉ በሙሉ መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል፡፡

ለተመራቂዎች የሥራ መመሪያ የሰጡት በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አደጋና ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር እና የኮሌጃችን አስ/ር ቦርድ ሰብሳቢ እንዲሁም የዕለቱ ክቡር እንግዳ ኮምሽነር ጋንታ ጋምአ ፤መንግስት ግብርናችን አሁን ለኢኮኖሚው የሚያበረክትው አስተዋዕጾ ከፍ እንዲል እያጋጠሙ ያሉ ማነቆዎችን ለመፍታት የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን፣ የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትን፣ መሰረተ-ልማቶች እና ዘላቂ አሠራሮችን መዘርጋት ላይ በተቀናቀጀ መልኩ እየሰራ እንደሚገኝ አመላክተዋል፡፡

አገራችን ኢትዮጵያ አገር በቀል ኢኮኖሚ ተግባራዊ በማድረግ በ2018 ዓ/ም ከተስፋ ወደ ሚጨበጥ ብርሀን ለመሸጋገር፣በ2023 ዓ/ም የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌትና 2040 ዓ/ም አለም አቀፍ የብልጽግና አርአያ ለመሆን ራዕይ ሰንቃ እየሰራች ትገኛለች ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የዘሬው ተመራቂዎች በቀጣይ የግብርናውን ዘርፍን ለማዘመንና በኢኮኖሚ ዘርፍ ያለውን የጎላ ሚና ለመጫወት ያላቸው ሚና ላቅ ያለ መሆኑን በማመላከት፣ተመራቂዎቹ በኮሌጃችን በነበራቸው ቆይታ የገበዩትን ዕውቀት፣ ያዳበሩትን ክህሎት እና ያገኙትን ልምዶችን እንደ መነሻ በመጠቀም በሚሠሩበት አከባቢ ያሉ አርሶ እና አርብቶ አደሮች ህይወትን ለመለወጥ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ለማላመድ እና ለማባዛት ተነሳሽነት መውሰድ፣በሥነ-ምግባር ራሳቸውን ለመምራት እና ለዓላማ ጽኑ መሆን እንደሚጠበቅባቸው መክረዋል፡፡

ተመራቂዎቹ መንግስት የቀረጻቸውን የብዝኃን ዘርፍ ኢኮኖሚ ፖሊሲንና ሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሥራዓትን እንዲሁም የአረንጓዴ አሻራ፣ የሌማት ትሩፋት፣የበጋ መስኖ ስንዴና ሌሎች ኢንሼቲቮች ላይ የጠራ ግንዛቤ በመያዝ የሀገራችን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ በሚደረገው ርብርብ የድርሻቸውን ለማበርከት ቆርጠው እንዲነሱ አሳስበዋል፡፡

በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ በትምህርታቸው የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ የምስክር ወረቀትና ዋንጫ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡ በዚህ መሰረት ከአጠቃላይ ከተመረቁት መካከል የላቀ ውጤት በማስመዘገብ አንደኛ ለወጣው ና የሰብል ልማት የሙያ ዘርፍ ተመራቂ ለሆነው ለተማሪ አስፋው አያኖና ከአጠቃላይ ሴት ተማሪዎች መካከል የላቀ ውጤት በማስመዝገብ አንደኛ ለወጣችውና የሰብል ልማት ሙያ ዘርፍ ተመራቂ ለሆነችው ተማሪ መብራት ጋናሞ ዋንጫ ተሸልመዋል፡፡

በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አደጋና ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር እና የኮሌጃችን አስ/ር ቦርድ ሰብሳቢ እንዲሁም የዕለቱ ክቡር እንግዳ ኮምሽነር ጋንታ ጋምአ፣ የወላይታ ዞን ረዳት መንግስት ተጠሪና አስተዳዳሪው ተወካይ አቶ መስፍን ቶማስ፣ የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባና የኮሌጃችን አስተዳደር ቦርድ አባል ዶ/ር ፍሬው ሞገስን ጨምሮ ሌሎች የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

ውድ ተመራቂዎች በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ!

የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College)

24 Oct, 16:29


ኮሌጃችን የ70/30 ሥልጠና ሞዳሊቲን ለማሳለጥ፣የውስጥ ገቢ ለማመንጨትና ማህበረሰብ አገልግሎት ለማቅረብ በማሳው ላይ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን የማምረትና የማሰባሰብ ሥራዎችን እየሰራ ይገኛል፡፡

ኮሌጃችን በተለያዩ የግብርና ሙያ መስኮች በመካከለኛ ደረጃ ለማሰልጠን የሚከተለውን የ70/30 የሥልጠና ሞዳሊቲን ለማሳለጥ፣ የውስጥ ገቢ የማመንጨት አቅሙን ለማሳደግና ማህበረሰብ አገልግሎት ለማቅረብ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን የማምረትና የማሰባሰብ ሥራዎችን በስፋት እየሰራ ይገኛል፡፡

ከነዚህ መካከል የመኸር ስንዴ፣ጤፍና ባቀላን ጨምሮ ሌሎች ሰብሎችን በማሳው ላይ እያመረተ የሚገኝ ሲሆን በችግኝ ጣቢያ ላይ የቡናና የአቮካዶ ችግኞችን በሰፋት እያፈላና ለአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኞችን እንክብካቤ እያደረገ ይገኛል።

በተጨማሪም የደረሰውን በቆሎ የማሰባሰብ ሥራ እየተሰራ ነው።

የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College)

21 Oct, 18:38


ሚንስቴሩ የ2017 ዓ/ም የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት መግቢያ የመቁረጫ ነጥብ ይፋ አደረገ።

የኢፌዴሪ ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የ2017 ዓ.ም የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት የመግቢያ መቁረጫ ነጥብ በዛሬው እለት ይፋ አድርጓል፡፡

ለተፈጠሮና ማህበራዊ ሳይንስ የተቀመጡ መቁረጫ ነጥቦች ከታች በምስሎች ተቀምጠዋል።

የወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ(Wolaita Sodo Agricultural College)

05 Oct, 18:12


በክልሉ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ኤጄንሲ መሪነት በተለያዩ የሙያ ደረጃዎችና መስመሮች በኮሌጃችን ሲካሄድ የቆየው የምዘና ሂደት በሰላምና በስኬት መጠናቀቁ ተገለጸ፡፡

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ኤጄንሲ መሪነት በተለያዩ የሙያ ደረጃዎችና መስመሮች ከቀን 23/01/17 ዓ/ም እስከ 25/01/17 ዓ/ም ድረስ ሲካሄድ የቆየው የሙያ ብቃት ምዘና ሂደት በሰላምና በስኬት መጠናቀቁን የኮሌጃችን ትምህርት ሥልጠና ዘርፍ ኃላፊና ም/ዲን አቶ ታሪኩ ጨመረ ገልጸዋል፡፡

አቶ ታሪኩ አክለውም፣ የምዘናው ሂደት በሰላምና በሰኬት እንዲጠናቀቅ የድርሻቸውን ለተወጡ የኤጄንሲው ማኔጅመንትና መዛኞች፣ የኮሌጃችን ት/ት ክፍል ኃላፊዎች፣የሙያ ብቃት ምዘና ኮሚቴዎች፣የኮምፒውተር ባለሙያዎችና ሌሎችን አመስግነዋል፡፡

የኮሌጃችን ሙያ ብቃት ምዘና ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ መ/ር በለጠ ቦቴ በበኩላቸው፣ ምዘናው የተሰጠው በሙያ ደረጃ አንድ እስከ ዓራት በሰብል ልማት፣ በተፈጥሮ ሀብትና እንስሳት እርባታ እንዲሁም በአዲሱ ሥርዓተ-ትምህርት መሰረት በሆሊስቲክ ሲኦሲ በሰብል ልማት፣እንስሳት እርባታ፣ በተፈጥሮ ሀብት፣እንስሳት ጤና፣ በመሰኖና ዲሬይኔጅና በሕብረት ሥራ ሂሳብ አያያዝና ኦዲት የሙያ መስመሮች መሆኑን አብራርተዋል፡፡

መ/ር በለጠ አያይዘውም ፣ በሦስቱ የሙያ ዘርፎች ከደረጃ አንድ እስከ ዓራት የተመዘኑትን 305(ሦስት መቶ አምስት) እና በስድስቱ የሙያ ዘርፎች በሆሊስቲክ ሲኦሲ የተመዘኑትን 376(ሦስት ሰባ ስድስት) ተመዛኞችን ጨምሮ በአጠቃላይ 681(ስድስት መቶ ሰማኒያ አንድ) ተመዛኞች መመዘናቸውን አስረድተዋል፡፡

በምዘናውም በኮሌጃችን ተከታታይ ትምህርት መርሐ-ግብር ሥልጠናቸውን ያጠናቀቁ የሣምንቱ መጨረሻ ቀናትና የክረምት ተመራቂ ተማሪዎችን ጨምሮ የግል ተመዛኞች መመዘናቸውን በመጥቀስ፤ የክረምት ተማሪዎቹ የተመዘኑት በሰብል ልማትና በተፈጥሮ ሀብት በሙያ ደረጃ ሦስት እንደሆነ አመላክተዋል፡፡