በሺዎች የሚቆጠሩ ተቃዋሚዎች በአንድ ሌሊት በፈጸሙት ጥቃት የሼክ ሀሲና ደጋፊዎች ቤት እና ንብረት ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ፈጽመዋል፡፡
የጥቃቱ መንስዔ የሼክ ሀሲና ደጋፊዎች የሽግግር መንግስቱን ለመቃወም አደባባይ ለመውጣት በማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ማድረጋቸው ነው፡፡
የቀድሞዋ ጠቅላይ ሚኒስትር ሼክ ሀሲና በስደት ከሚገኙባት ህንድ ሆነው ስለተቃውሞው ንግግር ያደርፋሉ ተብሎ ተጠብቆ ነበር፡፡
ተቃዋሚዎቹ ቤቱን ለማፍረስ ዶማና ሌሎች ቁሳቁሶችን ይዘው የገቡ ሲሆን፤ ኤክስከቫተር መኪና ይዘው የገቡ መኖራቸውም ተዘግቧል፡፡ #Algezira
@ThiqahEth