ህይወት ምንድን ናት? ዝም ተብላ የምትኖር ወይንስ በዓላማና እና ግብ የተቃኘች? በትኩረት እና በምልዓት የምትኖር ወይንስ ዕለት በቀደደው ቦይ የምትፈስ?
በስነልቦናው አለም ህይወት በአራት ማዕዘናት/ አዕማዳት የተዋቀረች እንደሆነ እና እነዚህ ማዕዘናት ሚዛናቸውን ሊጠብቁ እንደሚገባ ይነገራል። ሚዛኑ ወደ አንዱ ካደላ ቅርጽና ይዘቷ ጥሩ አይመጣም።
እነዚህ አራቱ ማዕዘናት የሚከተሉት ናቸው:-
1. መንፈሳዊ ህይወት (Spirituality):- ይህ አምድ በሃይማኖትም ይሁን ያለ ሃይማኖት የሚኖሩ መንፈሳዊ ክዋኔዎችን ይመለከታል። አምልኮ፣ ምስጋና፣ ዮጋ፣ ሜዲቴሽን፣ ውስጥን ማድመጥ.. የመሳሰሉትን።
2. አካል (body):- ህይወታችን ምልዓት እንዲኖራት አካላዊ ጤንነታችን መጠበቅ አለበት። በዚህ ስር ስፖርት መስራት፣ የተመጣጠነ ምግብ መመገብ፣ በቂ እረፍት ማድረግ ህመም ካለም መታከምን የመሳሰሉ ክዋኔዎችን መጥቀስ ይቻላል።
3. የስራ ህይወታችን (Job):- ስራ ለሰው ልጅ እጅግ አስፈላጊ ነገር ነው። ሲግመንድ ፍሮይድ ሁለት አበይት ጉዳዮች ያስፈልጉታል ይላል፤ ስራ እና ፍቅር።
በሌላ አንጻር.. ጤናማ ያልሆነ የስራ አከባቢ ጤናችንን እና ህይወታችንን ማናጋቱ አይቀርም። ስለዚህ በሁለት በኩል የተሳለ ሰይፍ ነው ስራችን.. አንዱ ሰይፍ መልካም..ሌላው ገጹ ደግሞ ህማም!
4. ማህበራዊ ህይወት:- የሰው ልጅ ማህበራዊ እንስሳ ነው ይባላል። ምንም እንኳን በራስ መተማመን ቢኖረን እና ጠንካሮች ብንሆን..ባንድም በሌላም መልኩ የሌሎችን እገዛ መሻታችን አይቀርም። መቆም ከሌሎች ጋር ነው! ይህም ማህበራዊ ህይወታችን ከቤተሰብ፣ ከጓደኛ፣ ከፍቅረኛ፣ ከጎረቤት እና ወዘተ..ጋር የሚኖረንን ግንኙነት ይመለክታል።
https://telegram.me/counselingA
ዶ/ር እስጢፋኖስ እንዳላማው (የአዕምሮ ህክምና ስፔሻሊስት)