Ministry of Health, Ethiopia @mohethiopia Channel on Telegram

Ministry of Health, Ethiopia

@mohethiopia


The official Telegram Channel of the Ministry of Health of the FDRE.

Our vision is to see healthy, productive & prosperous Citizens of Ethiopia.

HEALTHIER CITIZENS FOR PROSPEROUS NATION!

📞 +251-11-551-8031
🔗 www.moh.gov.et
📧 [email protected]

Ministry of Health, Ethiopia (English)

Welcome to the official Telegram Channel of the Ministry of Health of the Federal Democratic Republic of Ethiopia, also known as MOH Ethiopia. Our vision is to see healthy, productive, and prosperous citizens of Ethiopia. At MOH Ethiopia, we are dedicated to promoting the health and well-being of all Ethiopians, ensuring they have access to quality healthcare services and information.

Join us in our mission to create healthier citizens for a prosperous nation! Stay updated on the latest health news, initiatives, and campaigns by following our channel.

For any inquiries or assistance, feel free to contact us:

📞 +251-11-551-8031
🔗 www.moh.gov.et
📧 [email protected]

Ministry of Health, Ethiopia

09 Jun, 18:15


የሃዋሳ ዩኒቨርስቲ ኮምፕርሄሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የካንሠር ማእከል የጨረር ህክምናን ጨምሮ አምስት አዳዲስ የህክምና አገልግሎቶችን አስመርቆ ለአገልግሎት አቀረበ።

ዩኒቨርሲቲው የካንሠር የጨረር ህክምና፣ የስነ አእምሮ ተኝቶ ህክምና፣ የፎሮንሲክ እና የስነ መመረዝ ህክምና እንዲሁም የማህበረሰብ ሞዴል መድሀኒት ቤት አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት አድርጓል። ከዚህ በተጨማሪ የጨቅላ ህጻናት የጽኑ ህክምና የልህቀት ማእከል፣ የአጥንትና መገጣጠሚያ ህክምና በአዲስ መልክ አደራጅቶ ወደ ስራ ያስገባ ሲሆን የሴንትራል ኦፕሬሽን ክፍል የማስፋፋያ ስራዎች እየሰራም ይገኛል።

በማስመሪቂያ መርሀ ግብሩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ድጉማ ለብዙ ጊዜ ሲጠበቅ የቆየው የካንሰር ማእከል የጨረር ህክምና ለአገልግሎት በመብቃቱ እንኳን ደስ አላችሁ ካሉ በኋላ በሲዳማ ክልል የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በጤና ሳይንስ ኮሌጅ እየተሰሩ ያሉ የጤና ፕሮጀክቶች በቅርቡ ይፋ የሆነውን አራተኛው የጤና ፓሊሲ ላይ የተቀመጡ ጉዳዮች ጋር በእጅጉ የተሳሰሩ መሆናቸው ገልጸዋል። እነዚህ አገልግሎቶችን ወደ ስራ ማስገባቱ የጤና ፖሊሲውን ለመተግበር ብሎም ዜጎች በጤናው ዘርፍ ላይ ያላቸውን ፍላጎት ማርካት እንደሚያስችል ተናግረዋል።

የአዋሳ ዩኒቨርስቲ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ የተገነባው የጨረር ህክምና በአገራችን አራተኛው የጨረር ህክምና መሆኑን የገለጹት ዶክተር ደረጀ የህክምና ዘርፉን አንድ እርምጃ ወደፊት የሚወስድ በመሆኑ ስራው ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት እንደሆነም ነው የተናገሩት።

በከፍተኛ ወጪ ተገዝተው በጤና ሚኒስቴር በኩል የቀረቡት ማሽኖችን በአግባቡ ወደ ስራ በማስገባት፣ ተገቢው ጥገና እየተደረገላቸው ረጅም ጊዜ አገልግሎት እንዲሠጡ ጥንቃቄ እና እንክብካቤ እንዲደረግላቸው ዶክተር ደረጀ ያሳሰቡ ሲሆን ማሽኖችን ወደ አገር ውስጥ በማስገባት ለተባበሩት፣ ለማሽኖቹ አቅራቢ ኩባንያ፣ ማእከሉን ላስገነባው እና ስራው ስኬታማ እንዲሆን ጥረት ያደረጉ አካላትን ሁሉ አመስግነዋል።

መንግስት አቅዶ እየሰራቸው ካሉ ስራዎች መካከል አንዱ የጤናው ዘርፍ መሆኑን አንስተው የህዝቡን ጤና ሊያሻሽሉ የሚችሉ ፕሮግራሞችን ቀርጾ በመተግበር ላይ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የሲዳማ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር አቶ በየነ በራሶ ሲሆኑ እንደ ክልል የጤና አገልግሎቱን በማሻሻል ህዝቡ ከዘርፉ ተጠቃሚ ለማድረግ የተለያዩ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ መሆኑን ገልጸዋል። ይኼውም በእለቱ ተመርቀው ወደ ስራ የገቡት አገልግሎቶች ለዚህ ማሳያ መሆናቸው ጠቅሰው ከዚህ በፊት ብርቅ የነበሩ የህክምና አገልገሎቶች መንግስት ባሳየው ቁርጠኝነት በክልሉ ማቅረብ መቻሉን ገልጸዋል። እነዚህ አገልግሎቶች በህመሙ ለተጋለጡ ሠዎችን ችግር መቅረፍ የሚችል መሆኑን አክለዋል። አሁንም ሌሎች መሠል አገልግሎቶች በሆስፒታሉ እንዲሠፋፉ የጤና ሚኒስቴር የበኩሉን እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።

የአዋሳ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት አቶ አያና በራሶ በበኩላቸው
በደቡብ የአገሪቱ ክፍል የካንሠር ህክምና ማእከል በአዋሳ ለመገንባት ተመርጦ ማእከሉ መሠራቱን የተናገሩ ሲሆን ከሁለት አመት በፊት ግንባታው ተጠናቆ የኬሞቴራፒ አገልግሎት በማስጀመር ከ6 ሺህ በላይ ታካሚዎችን ሲያክም መቆየቱንና ዛሬ ላይ የጨረር ህክምናው የጤና ሚኒስቴር ባደረገው የራድዮ ቴራፒ እና ሲቲ እስካን ማሽን ድጋፋ የጨረር ህክምና መጀመር መቻሉን ገልጸው ለጤና ሚኒስቴር እና ደጋፍ ላደረጉ አካላት ምስጋና ቅርበዋል።

በተጨማሪም የፎረንሲክ እና ሦስት ሌሎች አዳዲስ አገልግሎቶች ተመርቀው ስራ መጀመራቸውን ያስረዱ ሲሆን ጥገና የሚያስፈልጉ የሆስፒታሉ ህንጻዎች እንዳዲስ የመገንባት፣ የኦክስጅን ጋዝ ማምረቻ ፕላንት የተጀመሩ ግንባታዎችን በመገንባት ላይ መሆናቸውን አቶ አያና አስተውቀዋል።

በ800 ተማሪዎች እና 104 መምህራን፣ በሁለት ፋካሊቲ ስር አምስት የስራ ክፍሎች በማቀፍ በ1989 የተቋቋመው የጤና ሳይንስ ኮሌጁ በአሁኑ ጊዜ 12 የመጀመሪያ ዲግሪ፣ 17 ሁለተኛ ዲግሪ፣ 10 ስፔሻላቲ ፣ አንድ ሰብ ስፔሻሊቲ እና አንድ ሶስተኛ ዲግሪ ፕሮግራሞች በመያዝ መማር ማስተማሩን በማሣለጥ ላይ እንደሚገኝ እንዲሁም ሪፈራል ሆስፒታሉ በአራት የአገልግሎት ዘርፎች መጀመሩን የአዋሳ ዩኒቨርስቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኩቲቭ ዳይሬክተር አቶ አለሙ ጫሜሶ ገልጸዋል። በዚህም ላለፉት 27 አመታት በርካታ የጤና ባለሞያዎች ማበርከቱን የገለጹ ሲሆን
ሆስፒታሉ በአሁኑ ጊዜ በአመት በአማካይ 150 ሺህ ታካሚዎችን በማስተናገድ ላይ እንደሚገኝና የተወሰኑ የትኩረት መስኮችን የልህቀት ማእከል ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ አቶ አለሙ አክለው ገልጸዋል።

ከዚህ በፊት ያልነበሩ አዳዲስ አምስት አገልግሎቶችን ማስጀመር መቻሉንም የተናገሩት ዳይሬክተሩ እነዚህ አገልግሎቶች መቅረባቸው የህብረሰተቡን ችግር የሚፈቱና ከአላስፈላጊ ወጪ እና እንግልት የሚያድኑ መሆናቸውን ገልጸው በቀጣይ የልብ እና ኩላሊት ህክምና አገልግሎትም ለማቅረብ የባለድርሻ አካላት ድጋፍ ጠይቀዋል።

በመጨረሻም የተጠናቀቁ አምስት ፕሮጀክቶች በእለቱ ክብር እግዶች የተመረቁ ሲሆን የህክምና ክፍሎቹ እና የተጀመሩ ፕሮጀክቶች ተጎብኝተዋል።


📱 www.moh.gov.et

📱 @MoHEthiopia

📱 Ministry of Health,Ethiopia

📱 twitter.com/FMoHealth

📱 YouTube.com/FMoHealthEthiopia

Ministry of Health, Ethiopia

09 Jun, 18:15


የሃዋሳ ዩኒቨርስቲ ኮምፕርሄሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የካንሠር ማእከል የጨረር ህክምናን ጨምሮ አምስት አዳዲስ የህክምና አገልግሎቶችን አስመርቆ ለአገልግሎት አቀረበ።

📱 www.moh.gov.et

📱 @MoHEthiopia

📱 Ministry of Health,Ethiopia

📱 twitter.com/FMoHealth

📱 YouTube.com/FMoHealthEthiopia

Ministry of Health, Ethiopia

06 Jun, 08:19


ጤናችን በምርታችን!
የሃገር ውስጥ የህክምና ግብዓት ምርትና ኢኖቬሽን ኤግዚቢሽን
ከሰኔ 15-20፣ 2016 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ
ይምጡ፣ ይጎብኙ፣ ይካፈሉ!

📱 www.moh.gov.et

📱 @MoHEthiopia

📱 Ministry of Health,Ethiopia

📱 twitter.com/FMoHealth

📱 YouTube.com/FMoHealthEthiopia

Ministry of Health, Ethiopia

03 Jun, 16:31


ቆልማማ እግር በፈጣሪ ቁጣ ወይም በዘር የሚከሰት አይደለም!

#clubfootawareness


📱 www.moh.gov.et

📱 @MoHEthiopia

📱 Ministry of Health,Ethiopia

📱 twitter.com/FMoHealth

📱 YouTube.com/FMoHealthEthiopia

Ministry of Health, Ethiopia

03 Jun, 16:28


በጄኔቫ ስዊዘርላንድ ሲካሄድ የነበረው 77 ኛው የዓለም ጤና ጉባኤ በ2005 ዓለም አቀፍ የጤና ደንብ (International Health Regulations 2005 ) ላይ የተደረገዉን ማሻሻያ በማጽደቅ ተጠናቋል።

በጄኔቫ ስውዘርላንድ የአባል አገራትን ተሳትፎ ባረጋገጠ መልኩ ሲካሄድ የነበረው 77 ኛው የዓለም ጤና ጉባኤ በ2005 ዓለም አቀፍ የጤና ደንብ (International Health Regulations 2005 ) ላይ የተደረገዉን ማሻሻያ እና ሌሎች የመፍትሄ ሀሳቦችን ( Resolutions) በማጽደቅ ተጠናቋል።

ሃገራችን የአፍሪካ ቡድንን በማስተባበር የጋራ አቋም እንዲያዝና በቀረቡት ማሻሻያዎች ውስጥ ፍትሃዊ ተደራሽነትን ለማሳደግ ለታዳጊ ሃገራት ትርጉም ያለው ለውጥ የሚያመጡ ማሻሻያዎች እንዲጸድቁ ከፍተኛ አስተዋጾዖ ያበረከተች ሲሆን የሃገራትን ሉዓላዊነት የሚጋፉና በተለይም በአፍሪካ ሃገራት ላይ የንግድና ትራንስፓርትና ኢኮኖሚ ረገድ አስገዳጅ ግዴታዎች የሚጥሉ ሃሳቦች እንዳይካተቱ ማድረግ ተችሏል፡፡

ከ300 በላይ ፕሮፓዛል በአባል አገራት ቀርቦ ማሻሻያ ተደርጎ የፀደቀዉ ዓለምአቀፍ የጤና ደንብ (International Health Regulations 2005 ) በዋናነት በህብረተሰብ ድንገተኛ የጤና አደጋዎች ወቅት የሀገራት ዝግጁነትና ምላሽ አሰጣጥ አቅምን ለማሻሻል እንዲሁም አለም አቀፍ ወረርሽኞችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ታሳቢ ያደረገ ነዉ። በዚህ መሰረት ተሻሽሎ የጸደቀው የዓለም አቀፍ የጤና ደንብ ድንገተኛ የህብረተሰብ ጤና አደጋና ወረርሽኝ ሲከሰት ፍትኃዊ የሆነ የህክምና ግብዓት ተደራሽነት እንዲኖርና መሰረታዊ የሆኑ የህብረተሰብ ጤና አቅም ለማዳበር የሚያስችል የፋይናንስ ድጋፍ በተለይም ለታዳጊ ሃገራት ለማሰባሰብ እንዲቻል አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያስኬድ መሆኑም ተገልጿል።

በጉባኤዉ ማጠቃለያ ላይ የአፍሪካ አባል ሀገራትን በመወከል ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ማሻሸያ ተደርጎበት የፀደቀዉ ይህ ዓለም አቀፍ የጤና ደንብ አገራት ከተባበሩና በጋራ ከሰሩ ለጋራ ዓላማ በጋራ መቆም እንደሚቻል አይነተኛ ማሳያና ምስክርነት መሆኑን በማበከር ደንቡ ለድንገተኛ የህብረተሰብ ጤና አደጋ ወረርሽኝ ቅኝትና ቁጥጥር ፣ዝግጁነት እንዲሁም ፈጣን ምላሽ ለመስጠት እጅጉን እንደሚያግዝ ገልጸዋል። ይህ እዉን እንዲሆን ላለፉት 2 ዓመታት ከሚመለከታቸዉ አካላት ጋር በመሆን ጥረት ሲያደርጉ የነበሩ አካላትን በሙሉ አመስግነዋል።

በሌላ በኩል አገራት ለህብረተሰብ ድንገተኛ ጤና አደጋዎች ፈጣን ምላሽ መስጠት እንዲችሉ ፣ እንዲሁም ቀጣይነት ያለዉ ጠንካራ የጤና ስርዓት እንዲኖራቸዉ የሚያግዙ ሌሎች የመፍትሄ ሀሳቦችና ውሳኔዎች (Resolutions) በጉባኤዉ ቀርበዉ ፀድቀዋል።

በስዊዘርላድ ጄኔቫ ሲካሄድ በነበረዉ 77ኛው የዓለም ጤና ጉባኤ ላይ የተሳተፈዉ የኢትዮጵያ ልዑክም ወደ አገር ውስጥ የተመለሰ ሲሆን የ 155ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ስብሰባ በክብርት የጤና ሚኒስትሯና የሚመለከታቸው የስራ ሃላፊዎች ተሳትፎ እየተደረገበት ይገኛል፡፡

📱 www.moh.gov.et

📱 @MoHEthiopia

📱 Ministry of Health,Ethiopia

📱 twitter.com/FMoHealth

📱 YouTube.com/FMoHealthEthiopia

Ministry of Health, Ethiopia

02 Jun, 10:08


በህፃናት ላይ በተፈጥሮ የሚከሰተው ቆልማማ እግር በወቅቱ ከታከመ መዳን እንደሚችል ያውቃሉ?
#clubfootawareness

📱 www.moh.gov.et

📱 @MoHEthiopia

📱 Ministry of Health,Ethiopia

📱 twitter.com/FMoHealth

📱 YouTube.com/FMoHealthEthiopia