🍂ٱمراة جهالة إذا قرأت عن الحرية خلعت ملابسها
አላዋቂ ሴት ስለ ነጻነት ካነበበች ልብሷን ለማውለቅ ይቃጣታል።
ይህን የተናገረው ጠቢብ እውነት ብሏል።አንዳንድ እህቶቻችን የነጻነት ሃሴት በራቆት ገላ ልክ የሚመዘን ይመስላቸዋል።
ዶ/ር ዛኪር ናይክም ተመሳሳይ ንግግር አላቸው <<ዘመናዊነት በራቆትነት የሚገለጽ ቢሆን ኖሮ እንደ እንስሳቶ ዘመናዊ ፍጥረት አልነበረም>>
🍂እህቴዋ! ! መሸፋፈን የእንቁነት መገለጫ ነው።አሏህ ባህር ውስጥ ያለችዋን በጠንካራ ሽፋን የተለበጠች እንቁ ሸፍኖ ሲያበቃ የበረሃውን አሸዋ እና የሜዳውን ጠጠር ራቆታቸውን ትቷቸዋል! ለምን? ማንም አይፈልጋቸውማ!
🍂ተሸፈኚ! የጥበብ መካነ ቀብር •ቀልብን• ተመልከቺአትማ! ከሌላው ገላ ነጠል አድርጎ በጎድን አጥንት አጥሮች ሸፈናት፡ሸፍኖኣትም አላበቃም የሰውነታችን ዋና ከተማ አደረጋት!
🍂ተገላልጣ የወጣችዋ እንስት አታሳስትሽ! እሷ ማለት ሸቀጥ ናት ! ሸቀጥ ናት አንድ ቀን ተሽጣ የምትረክስ! የአንቺ ገበያ ደግሞ ዱንያ አይደለም! ነፍስሽን አስቀድመሽ ለሃያሉ ጌታ ሽጠሻልና!
🍂ተሸፈኚ! ••ጥሩዎቹን ለጥሩ•• ነውና የፈጣሪ ፍርድ!
አልማዝን የሚያገኛት ጎበዝ ዋናተኛ ብቻ ነው! ሰነፉማ አፈር አፋሽ ብቻ ነው! ተሸፈኚ ከእጁ ሥር ላትወድቂ ዘንዳ!
🌹ሰውነትሽን ሸፍነሽ ስታበቂ ልብሽን አትገላልጪ ይህ የመናፍቃን ባህሪ ነውና!
@LIJ_MUAZ