ተዋሕዶን እንወቅ።

@letsknowtheeotc


አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ ሥረይ ለነ ኲሎ አበሳነ ኢታብአነ ውስተ መንሱት እግዚኦ አድኅነነ እምዕለት እኪት ወባልሐነ ውስተ መንሡት።

በከመ ምሕረትከ አምላክነ ወአኮ በከመ አበሳነ

የየእለቱን ስንክሳር፥ ውዳሴ ማርያም፥ ጸሎተ አርጋኖን፥ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን፥ የጻድቃንና የሰማዕታትን ገድል፥ የተለያዩ መንፈሳዊ ጥያቄዎችን፥ የድሮ እና አዳዲስ መዝሙራትን የሚያገኙበት ቻናል ነው። ይቀላቀሉን።

ተዋሕዶን እንወቅ።

23 Oct, 07:25


ነቢያት ስለራሳቸው ምን አሉ? (በጣም በጥቂቱ)

ሊቀ ነቢያት ቅዱስ ሙሴ እንዲኽ አለ። “ጌታ ሆይ፥ እኔ አፌ #ኰልታፋ ምላሴም ጸያፍ የሆነ ሰው ነኝ፤ ትናንት ከትናንት ወዲያ ባሪያህንም ከተናገርኸኝ ጀምሮ አፈ ትብ ሰው አይደለሁም።” (ዘጸ. 4፥10)

ትኁቱ መዝሙረኛው ቅዱስ ዳዊትም እንዲኽ ብሏል። “እኔ ግን #ትል ነኝ ሰውም አይደለሁም፤ የሰው ማላገጫ በሕዝብም ዘንድ የተናቅሁ ነኝ።” (መዝ. 22፥6)

ብዙ መከራን የተቀበለው ጻድቁ ኢዮብም “እነሆ፥ እኔ #ወራዳ ሰው ነኝ፤ የምመልስልህ ምንድር ነው? እጄን በአፌ ላይ እጭናለሁ” አለ። (ኢዮ. 40፥4)

ልዑለ ቃል ነቢዩ ኢሳይያስም እንዲኽ ይላል። “ከንፈሮቼ #የረከሱብኝ ሰው በመሆኔ፥ ከንፈሮቻቸውም በረከሱባቸው ሕዝብ መካከል በመቀመጤ ዓይኖቼ የሠራዊትን ጌታ ንጉሡን እግዚአብሔርን ስለ አዩ ጠፍቻለሁና ወዮልኝ!” (ኢሳ. 6፥5)

እስራኤልን ከአምልኮተ ጣዖት ወደአምልኮተ እግዚአብሔር ለመመለስ ለ23 ዓመታት የተጋው፥ መከራንም የተቀበለው ነቢዩ ኤርሚያስም “ወዮ ጌታ እግዚአብሔር፥ እነሆ፥ #ብላቴና ነኝና እናገር ዘንድ አላውቅም” አለ። (ኤር. 1፥6)

ንጉሥ ዳዊት ‛ልጄ ኾይ ሰው ኹን’ ብሎ የመከረው ጠቢቡ ሰሎሞንም እንዲኽ አለ። “እኔ በእውነት ከሰው ሁሉ ይልቅ #ደንቆሮ ነኝ፥ የሰውም ማስተዋል የለብኝም።” (ምሳ. 30፥2)

ከአስራ ኹለቱ ደቂቀ ነቢያት እነዱ የኾነው አሞጽም ይናገራል። “እኔ ላም #ጠባቂና ወርካ ለቃሚ ነኝ እንጂ ነቢይ ወይም የነቢይ ልጅ አይደለሁም፤ እግዚአብሔርም በጎቹን ከመከተል ወሰደኝ፥ እግዚአብሔርም፦ ሂድ፥ ለሕዝቤም ለእስራኤል ትንቢት ተናገር አለኝ። አሁንም የእግዚአብሔርን ቃል ስማ፤ አንተ በእስራኤል ላይ ትንቢት አትናገር፥ በይስሐቅም ቤት ላይ አትስበክ ብለሃል።” (አሞ. 7፥14-16)

እናንተስ ስለራሳችኹ ምን ትላላችኹ?

እግዚአብሔር ቢፈቅድ ቀጣይ ክፍል ይኖረዋል፤ ተከታተሉን!

ተዋሕዶን እንወቅ።

22 Oct, 05:09


አዳማ ያላችኹ ኦርቶዶክሳውያን የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችኹ ተኩላዎች ('ፍኖተ ጽድቅ' ተብዬ መናፍቃን) ተጠንቀቁ!

ተዋሕዶን እንወቅ።

19 Oct, 15:59


አዳር ለምታድሩ መልካም ቁመት ይኹንላችኹ

በተለያዩ ምክንያቶች ማደር ላልቻላችኹ ይኽችን የማኅሌተ ጽጌ ክፍል ጋበዝኳችኹ🥰 ደኅና እደሩልኝ!😘

“እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕጻንኪ ጽጌ ፀዓዳ ወቀይሕ፥🌹
አመ ቤተ መቅደስ ቦእኪ በዕለተ ተአምር ወንጽሕ፥
ንዒ ርግብየ ትናዝዝኒ እምላሕ፥
ወንዒ ሠናይትየ ምስለ ገብርኤል ፍሡሕ፥
ወሚካኤል ከማኪ ርኅሩኅ።”

ትርጉም፦

“በመንጻት ወራት በተዓምርም ቀን ወደቤተ መቅደስ ስትገቢ፥
ነጭና ቀይ አበባ የሚመስል ልጅሽን ታቅፈሽ፥
ከኀዘኔ ታረጋጊኝ/ታጽናኚኝ ዘንድ ርግቤ ኾይ ነይ፥
መልካም እናቴ ኾይ ደስ የሚል ዜና ከያዘ ከገብርኤልና፥
እንደ አንቺ ርኅሩኅ ከኾነ ከሚካኤል ጋር ነይ።”

ተዋሕዶን እንወቅ።

18 Oct, 17:13


"ከ ዐኹኑ ሕይወት ይልቅ በ እግዚአብሔር ዘንድ ያለው ደሥታ ብርቱ ነው። ዕና ይኽን ደሥታ ያገኘ ሠው ለፍላጎቶች ትኩረት ዐይሠጥም፤ ለራሡ ሕይወት ዕንኳ ዐያሥብም፤ ሥለ ሌላ ነገር ግንዛቤ ዐይኖረውም፤ የዚኽ ደሥታ ልምድ ዕውነት ከኾነ ፍቅር ከ ሕይወት የበለጠ ጣፋጭ ነው። ፍቅር የተወለደበት የ እግዚአብሔር ሥምምነት ከማር ይልቅ ይጣፍጣል። ለሚወደው ሢል መራራ ሞትን መሞት ለ ፍቅር የሚያሣዝን ዐይመሥልም... ይኽን ደሥታ ለተቀበለ ልብ ደግሞ የዚኽ ዓለም ጣፋጮች ኹሉ ከመጠን ያለፈ ይመሥላል። በ እግዚአብሔር ዕውቀት ጣፋጭነት የሚመሠል ምንም የለምና!"

[ቅዱስ ይሥሐቅ ሦርያዊ]

ተዋሕዶን እንወቅ።

18 Oct, 03:29


“ክብደታችንን ለመቀነስ የምንጨነቀውን ያኽል ኃጢአታችንንም ለመቀነስ ተጨንቀን ቢኾን ኖሮ እግዚአብሔር ወደኛ ልብ እጅጉን በቀረበ ነበር።”

ተዋሕዶን እንወቅ።

17 Oct, 09:12


“በዚኽ ዓለም ስንኖር በምንም ነገር እርግጠኞች መኾን አንችልም። ሐብታም ልንኾንም ላንኾንም እንችላለን። ባለሥልጣኖች ልንኾንም ላንኾንም እንችላለን። ግን በአንድ ነገር ብቻ እርግጠኛ ነን።

ሟ ቾ ች ነን!

መምህር ኢዮብ ይመኑ ካስተማሩት

ተዋሕዶን እንወቅ።

12 Oct, 18:12


አዳር ለምታድሩ መልካም አገልግሎት

ለማታድሩትም እግዚአብሔር ረድቷችኹ አብረን የምንቆምበትን ዘመን ያቅርብልን🙏

ተዋሕዶን እንወቅ።

12 Oct, 16:36


ትመጫለሽ አይደል?

ቤተመቅደስሽን ከበን አለን - መቅደስ ገላችን ቢረክስም
በሕንጻ መቅደስሽ ከትመናል - ሕንጻ ሥላሴን ብናፈርስም

በልማድና በእምነት መሐል – በተወጠረ መንፈሳችን
በጎጥ በጎሳ በታጠረ - በተፍረከረከ አንድነታችን

ስቀለው ስቀለው እንጂ – ምን በድሎ? በማይል ልሳናችን
ለክፋት ባደገደገ - በጎ ግብር በራቀው

ኃጢአት ባጠራቀመ – የጽድቅ መንገድ በናፈቀው
ነውርን መግለጥ እንጂ - ከባቴ አበሳነት በማያውቀው

በረከሰ ማንነት ነው – ንዒ ማርያም የምንልሽ
ከልዑሉ ሚካኤል ጋ ከደስተኛው ገብርኤል ጋ

            ጽጌ ጸዐዳ ልጅሽን ይዘሽ
            ነይ ርግባችን የምንልሽ

በሚገባ ንጽህና – ሆነን አይደለም ድንግል
ግን ነይ ስንልሽ አትቀሪም.... ትመጫለሽ አይደል?

ልባችን ቂምን ቋጥሮ በአፍ ዜማ ብቻ - ብንጠራሽም ንዒ ብንልም ድንግል

ርሕርሕተ ሕሊና እመ ትሕትና.....

ትመጫለሽ አይደል?

ስለተጠራው ስምሽ
ድንግል ትመጫለሽ አይደል?

ስለኪዳንሽ
ድንግል  ትመጫለሽ አይደል?
አልቦ ምግባር ብንሆንም - እንደ ቃና ማድጋ
ማርያም አትቅሪ እኛ ጋ

ንዒ ስንል
አዛኝቱ ድንግል
ትመጫለሽ አይደል?

[ገጣሚ - ሀገሬ ኑሪ]

ተዋሕዶን እንወቅ።

11 Oct, 03:38


ለኛ ሲል በዕለተ ዓርብ የከፈለልንን ዋጋ እያሰብን ከኃጢአት ርቀን የምንውልበት ቀን ይኹንልን፤ ደኅና ዋሉልኝ!😘

ተዋሕዶን እንወቅ።

10 Oct, 14:34


🔴ወርኀ ጽጌ | የእመቤታችን ስደት | እመቤታችን በጽጌ የተመሰለችው ለምንድነው? | እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕጻንኪ | ማይ ቲዩብ May Tube |


#ሙሉ_ቪዲዮውን_ይመልከቱ

YouTube - Subscribe
https://youtu.be/zc9gDwupN2o?si=8Oh40klepdY9v0aV

ተዋሕዶን እንወቅ።

10 Oct, 10:15


“እግዚአብሔር የዘላለም ብርሐንሽ ይኾናልና፥ የልቅሦሽም ወራት ታልቃለችና ፀሐይሽ ከዚያ በኋላ ዐትጠልቅም ጨረቃሽም ዐይቋረጥም።”
  [ዒሣይያሥ 60፥20]

ፅጌ❤️‍🩹

ተዋሕዶን እንወቅ።

10 Oct, 04:24


በዐይነ ሥጋ የማይታይና የማይመረመር፣ ሁሉን ማድረግ የሚችል፣ የሰው ህሊና አስሶ የማይደርስበት፣ ሁሉን የፈጠረ፣ መጀመሪያና መጨረሻ የሌለው፣ ለዘላለም የሚኖር አምላክ መኖሩን እናምናለን፡፡ እርሱም በአካል፣ በስም፣ በግብር ሦስት፤ በባሕርይ፣ በመለኮት፣ በሕልውና፣ በፈቃድ አንድ ነው፡፡ ከዚህም ባሻገር በመስጠት በመንሳት፣ በመፍጠር በማሳለፍ፣ በመግዛትና በአኗኗር አንድ ነው፡፡

“ሥላሴ” የሚለው ቃል “ሠለሰ” ሦስት አደረገ ካለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም ሦስትነት ማለት ነው፡፡ ቅድስት ሥላሴ ስንል ለሥላሴ ቅድስት ብለን እንቀጽላለን፡፡ ቅድስት ሥላሴ ማለት ልዩ ሦስትነት ማለት ነው፡፡ ይህም ሦስት ሲሆኑ አንድ፣ አንድ ሲሆን ሦስት ስለሚሆኑ ልዩ ሦስትነት ተብሏል፡፡ ሥላሴ የሚለውን ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ ያለና የሚኖረውን አምላክ ለመግለጽ የተጠቀመው የአንጾኪያው ቴዎፍሎስ በ169ዓ.ም ነው፡፡ኋላም በኒቅያ ጉባዔ 318ቱ ሊቃውንት አጽንተውታል፡፡ እነዚህ ሊቃውንት በቅዱሳት መጻሕፍት የተመሰከረውን የእግዚአብሔርን ፍጹም አንድነትና ልዩ ሦስትነት ለእኛ በሚረዳ ቋንቋ ገለጡት እንጂ አዲስ ትምህርት አላመጡም፡፡ ይልቁንም ነገረ ሥላሴን ሳይረዱ በሥላሴ መካከል የክብርና የተቀድሞ ልዩነት ያለ አስመስለው በክህደት ትምህርት የተነሱ መናፍቃንን ክህደት ለማስረዳት፣ የሐዋርያዊት ቤተክርስቲያንን የቀናች ሃይማኖት ለመግለጥ ምሥጢረ ሥላሴን አብራርተው አስተምረዋል፡፡

ምስጢረ ሥላሴ (Mystery of the Trinity) ማለት የአንድነት የሦስትነት ምስጢር ማለት ነው፡፡ ምሥጢር መባሉም በእምነት የተገለጠ፣ ያለ እምነትም የማይመረመር ስለሆነ ነው፡፡ ይኸውም አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በስም፣ በአካል፣ በግብር ሦስት ሲሆኑ በባሕርይ በሕልውና፣ በመለኮት ደግሞ አንድ ናቸው፡፡ እንደዚህ ባለ ድንቅ ነገር አንድ ሲሆኑ ሦስት፣ ሦስት ሲሆኑ አንድ ይባላሉና፣ ይህም ልዩ ሦስትነት ረቂቅ እና በሰው አእምሮ የማይመረመር ስለሆነ ምስጢር ይባላል፡፡ ስለዚህም በአንድ አምላክ፣ በሦስቱ አካላት እናምናለን፡፡

የክርስትና ዶግማ (መሠረተ እምነት) በምስጢረ ሥላሴ ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ ምስጢረ ሥላሴ የእምነታችን ዋነኛው ምሰሶ ነው፡፡ በመዳን ትምህርት ውስጥ የመጀመሪያውን ደረጃ የሚይዘው ምስጢረ ሥላሴ ነው፡፡ ለመዳናችንም መሠረት ነው፡፡ ክርስቲያኖች ሁላችን የተጠመቅነው በሥላሴ (በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ) ስም ነው (ማቴ 28፡19)፡፡ የሥራችን ሁሉ መጀመሪያም አድርገን በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ስንልም በሥላሴ ማመናችንን እየመሰከርን ነው፡፡ በሥራችን መጨረሻም “ምስጋና ይሁን አንድ አምላክ ለሚሆን ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ አሜን” ብለን ሥራችንን በሥላሴ ስም ጀምረን በሥላሴ ስም እንፈጽማለን፡፡ሆኖም ግን ምስጢረ ሥላሴ ለሰው አእምሮ እጅግ የረቀቀ ስለሆነ የሰው አእምሮ ሊያውቅ የሚችለው እግዚአብሔር በገለጠለት መጠን ብቻ ነው፡፡


አበው ሥለ ሥላሴ እንዲህ አሉ

“እግዚአብሔር አንድ ነው፤ የማትከፈል የማትፋለስ መንግስትም አንዲት ናት፤ ከሥላሴ ምንም ምን ፍጡር ደኃራዊ የለም፤ በእነርሱ ዘንድ አንዱ ለአንዱ መገዛት የለም፡፡ አብ ከወልድ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም፣ ወልድም ከመንፈስ ቅዱስ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም፤ መንፈስ ቅዱስም ከአብ ከወልድ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም፤ ሥሉስ ቅዱስ በዘመኑ በቀኑ ሁሉ በግብርም በስምም ሳይለወጥ ሳይፋለስ ጸንቶ ያለ ነው እንጂ፡፡” (ሃይማኖተ አበው ዘሠለስቱ ምዕት ምዕራፍ 19፡5-6)

“ወንድሞቻችን እኛስ እንዲህ እናምናለን፤ ያልተወለደ እግዚአብሔር አብ በተለየ አካሉ አንድ ነው፤ የተወለደ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ ኢየሱስ ክርስቶስም በተለየ አካሉ አንድ ነው፤ በወደደው የሚያድር የአብ የወልድ እስትንፋስ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስም በተለየ አካሉ አንድ ነው እንላለን፡፡…አብ አምላክ ነው፤ ወልድም አምላክ ነው፤ መንፈስ ቅዱስም አምላክ ነው፡፡ ግን ሦስት አማልክት አይባሉም አንድ አምላክ እንጂ፡፡” (ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ምዕራፍ 25፡2-4)

“ከሦስቱ ፍጡር የለም ፍጡራን አይደሉምና፡፡ ከዕውቀት ከሃይማኖት የተለዩ መናፍቃን ከቅድስት ሥላሴ መለኮት መከፈልን በአካላት መጠቅለልን ሊያመጡ አይድፈሩ ሦስት አማልክት ብለን አንሰግድም አንድ አምላክ ብለን እንሰግዳለን እንጂ፡፡ በስም ሦስት ናቸው እንላለን፤ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አንድ ባህርይ አንድ ሥልጣን ናቸው፤ በአንድ መለኮት በባህርይ አንድነት የጸኑ ሦስት አካላት ሲሆኑ ከሦስቱ አንዱ የሚበልጥ አንዱ የሚያንስ አይደለም፤ በማይመረመር በአንድ ክብር የተካከሉ ናቸው እንጂ፡፡” (ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ ምዕራፍ 60፡6-7)

“ወልድ ሳይኖር አብ ከአዝማን በዘመን ፈጽሞ አልነበረም፤ ወልድም ከመንፈስ ቅዱስ ተለይቶ በዘመን አልነበረም፤ ሳይለወጡ ሳይለዋወጡ በገጽ በመልክ ፍጹማን በሚሆኑ በሦስት አካላት ጥንት ሳይኖራቸው በዘመን ሁሉ የነበሩ፤ ፍጻሜ ሳይኖራቸው የሚኖሩ ናቸው እንጂ፡፡” (ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ቴዎፍሎስ ምዕራፍ 68፡5)

“አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በአካል ሦስት በባህርይ አንድ ነው ብሎ ማመን ይህ ነው፤ የማይመረመር በቅድምና የነበረ አብ በገጹ በአካሉ ፍጹም ነው፤…የማይመረመር በቅድምና ነበረ ወልድም በገጹ በአካሉ ፍጹም ነው፤….የማይመረመር በቅድምና የነበረ መንፈስ ቅዱስም በገጹ በአካሉ ፍጹም ነው፤ ሐዋርያት ያስተማሩዋት ቅድስት ቤተክርስቲያን የተቀበለቻቸው ቅዱሳት መጻሕፍት እንደተናገሩ፡፡” (ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ቄርሎስ ምዕራፍ 70፡14-17)

“እኛ ግን በሥላሴ ዘንድ በማዕረግ ማነሥና መብለጥ የለም በመለኮት አንድ ወገን ናቸው እንላለን” (አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ተግሳጽ ዘሰባልዮስ)

ተዋሕዶን እንወቅ።

09 Oct, 09:13


የቅዱሳንን መታሰቢያ ማድረግ ከመፅሐፍ ቅዱስ አንፃር እንዴት ይታያል?

በመጀመሪያ እንኳን ለእናታችን ለሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ🙏

ቅድስት ቤተክርስቲያናችን እያንዳንዱ የምታደርጋቸው ስርዓቶች መፅሐፍ ቅዱስን የተከተሉ ናቸው። ከዚህም ውስጥ አንዱ ማሳያው ራሳቸውን የክርስቶስ ጃንደረባ አድርገው የእዚህን አለም ጣዕም ንቀው ስለስሙ መከራ አልፎም ሰማዕትነትን የተቀዳጁትን ቅዱሳን ፣ ፃድቃን ፣ ሰማዕታት ቅድስት ቤተክርስቲያናችን በደንብ አድርጋ ታከብራቸዋለች ለዚህም ይህንን የቤተክርስቲያን ስርዓት የሚደግፉ የመፅሐፍ ቅዱስ ክፍሎችን እንመልከት!

ከብሉይ ኪዳን

ኢሳይያስ 56
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁴ እግዚአብሔር ሰንበቴን ስለሚጠብቁ ደስ የሚያሰኘኝንም ነገር ስለሚመርጡ ቃል ኪዳኔንም ስለሚይዙ ጃንደረቦች እንዲህ ይላልና፦
⁵ በቤቴና በቅጥሬ ውስጥ ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች ይልቅ የሚበልጥ መታሰቢያና ስም እሰጣቸዋለሁ፤ የማይጠፋም የዘላለም ስም እሰጣቸዋለሁ።


ከሐዲስ ኪዳን

“እንግዲህ ምን እላለሁ? ስለ ጌዴዎንና ስለ ባርቅ ስለ ሶምሶንም ስለ ዮፍታሔም ስለ ዳዊትና ስለ ሳሙኤልም ስለ ነቢያትም እንዳልተርክ ጊዜ ያጥርብኛልና።”
ዕብራውያን 11፥32


እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና።”
ዕብራውያን 12፥1-2


1ኛ ቆሮንቶስ 16
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁵ ወንድሞች ሆይ፥ የእስጢፋኖስ ቤተ ሰዎች የአካይያ በኩራት እንደ ሆኑ ቅዱሳንንም ለማገልገል ራሳቸውን እንደ ሰጡ ታውቃላችሁ፤
¹⁶ እንደ እነርሱ ላሉትና አብሮህ ለሚሠራ ለሚደክምም ሁሉ እናንተም እንድትገዙ እለምናችኋለሁ።
¹⁷ በእስጢፋኖስና በፈርዶናጥስ በአካይቆስም መምጣት ደስ ይለኛል፥ እናንተ ስለሌላችሁ የጎደለኝን ፈጽመዋልና፤ መንፈሴንና መንፈሳችሁን አሳርፈዋልና።
¹⁸ እንግዲህ እንደነዚህ ያሉትን እወቁአቸው።


“እንግዲህ በሙሉ ደስታ በጌታ ተቀበሉት፥ እርሱን የሚመስሉትንም አክብሩአቸው፤”
ፊልጵስዩስ 2፥29


እነዚህ ክፍሎች ቅዱሳንን ማወቅ ማክበር መፅሐፍ ቅዱሳዊ መሆኑን በግልፅ የሚያስተምሩ ክፍሎች ናቸው!
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በዘመኑ ስለነበሩ ቅዱሳን ገድል ለመናገር ጊዜ እንደሚያጥርበት ተጋድሎአቸውም ብዙ ስለመሆኑ በግልፅ ይናገራል!

ተዋሕዶን እንወቅ።

09 Oct, 06:06


📜 አንዳንድ ጊዜ ሃይማኖትን (ሃይማኖት ውስጥ ያሉ ነገሮችን] ከlogic ወይም ከአእምሯችን በላይ ስለሚኾኑ ዝም ብለን መቀበል እንጂ እንዴት ሊኾን ይችላል እያልን አጉል መፈላሰፍ አይገባንም!

ተዋሕዶን እንወቅ።

09 Oct, 03:19


በብሉይ ኪዳን ሕዝቡን ከግብፅ ምድር ያወጣው፣ የእስራኤል አምላክ ጌታ እግዚአብሔር መሆኑን ቅዱሳት መጻሕፍት ደጋግመው የሚነግሩን እውነት ነው፤ የተወሰኑትን ለመመልከት ያህል፦
“የከነዓንን ምድር ልሰጥህና አምላክህ (ኤሎሂም) ልሆን፣ ከግብፅ ያወጣሁህ እኔ ያህዌ ኤሎሂም ነኝ።”
  — ዘሌዋውያን 25፥38
“ከግብፅ ምድር ያወጣኋችሁ፣ አምላካችሁ እግዚአብሔር እኔ ነኝ፤ በዓመት በዓላችሁ ቀን ታደርጉ እንደ ነበረው ሁሉ፣ እንደ ገና በድንኳኖች እንድትቀመጡ አደርጋችኋለሁ።”
  — ሆሴዕ 12፥9
““እኔ ግን ከግብፅ ምድር ያወጣሁህ፣ አምላክህ እግዚአብሔር ነኝ፤ ከእኔ በቀር ሌላ አምላክ አታውቅም፤ ከእኔም በቀር ሌላ አዳኝ የለም።”
  — ሆሴዕ 13፥4
ክርስቶስ ጌታችን ሕዝቡን ከግብፅ ያወጣው ያህዌ ነው!
ሥላሴ በይሁዳ መልዕክት
ሐዋርያው ይሁዳ ስለ ኢየሱስ ያህዌ መኾን ሲናገር ልክ ዘመነኞቹ “የሐዋርያት ቤተክርስቲያን” እንደሚያምኑት ኢየሱስ አብ ነው እያለ አለመሆኑን በዚሁ ምዕራፍ አብ፣ ወልድ እና መንፈስ ቅዱስን ለይቶ በመግለጽ የሐሰተኞቹ የእምነት አቋም ትክክል አለመሆኑን ግልጽ አድርጓል።
ይሁዳ 1፥20-21 “እናንተ ግን ወዳጆች ሆይ፤ እጅግ ቅዱስ በሆነው እምነታችሁ ራሳችሁን ለማነጽ ትጉ፤ በመንፈስ ቅዱስም ጸልዩ (ἐν πνεύματι ἁγίῳ προσευχόμενοι) ። ወደ ዘላለም ሕይወት የሚያደርሳችሁን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ምሕረት (τὸ ἔλεος τοῦ κυρίου ἡμῶν Ἰησοῦ Χριστοῦ)  ስትጠባበቁ ሳለ፣ በእግዚአብሔር ፍቅር (ἐν ἀγάπη θεοῦ) ራሳችሁን ጠብቁ።”
ይሁዳ አብ፣ ወልድንና መንፈስ ቅዱስን ለይቶ መግለጽ ብቻ ሳይሆን፣ ዘለዓለማዊው  ቅዱሱ እምነታችን በእነዚህ መለኮታዊ አካላት ላይ የተመሠረተ መሆኑንም እየነገረን ነው። ስለዚህ የይሁዳ መልዕክት የክርስቶስ የጌታችን መለኮትነት የሚክዱትን ወገኖች ብቻ ሳይሆን ሦስቱን የሥላሴ አካላት (ማንነቶች) በመካድ አንድ ማንነት ብቻ የሚሉትንም ወገኖች ትክክል አለመሆናቸውን የሚያሳይ ታሪካዊውንና መጽሐፍ ቅዱሳዊውን የሥላሴ አስተምህሮ የሚያጸና የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ነው።
ማጣቀሻዎች
[1] Richard Bauckham, Jude and the early relative of Jesus in the Early Church ገጽ 303-304
[2] Ann Shelton, As the Romans Did: ገጽ 17
[3]J.K.Elliot, New Testament Textual Criticism: The Application of Thoroughgoing Principles, ገጽ 65

ተዋሕዶን እንወቅ።

09 Oct, 03:19


የኢየሱስ አምላክነት በይሁዳ መልዕክት

የይሁዳ መጽሐፍ በአዲስ ኪዳን ውስጥ ካሉት እጅግ አጫጭር መጻሕፍት መካከል አንዱ ሲሆን አንድ አጭር ምዕራፍ ብቻ የያዘ አነስተኛ መጽሐፍ ነው፤ ሆኖም  በእነዚህ ጥቂት መስመሮች ውስጥ ይሁዳ ስለ ክርስቶስ መለኮትነት በአጽንዖት ሲገልጽ እናነባለን።
ቍጥር ዐራት፦
“ረጅም ጊዜ በፊት ለዚህ ፍርድ የተጻፉ አንዳንድ ሰዎች ሾልከው ወደ እናንተ ገብተዋልና፤ እነርሱ ፈሪሀ እግዚአብሔር የሌላቸው፣ የአምላካችንን ጸጋ በርኵሰት የሚለውጡና እርሱ ብቻ ልዑል ገዣችንና ጌታችን የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን የሚክዱ ናቸው።” (አ.መ.ት)
παρεισεδύησαν γάρ τινες ἄνθρωποι, οἱ πάλαι προγεγραμμένοι εἰς τοῦτο τὸ κρίμα, ἀσεβεῖς τὴν τοῦ θεοῦ ἡμῶν χάριτα μετατιθέντες εἰς ἀσέλγειαν καὶ τὸν μόνον δεσπότην καὶ κύριον ἡμῶν Ἰησοῦν Χριστὸν ἀρνούμενοι.
ግራንቪል ሻርፕ የተሰኘ የግሪክ ቋንቋ ሊቅ ለይቶ ካስቀመጣቸው የግሪክ ሰዋስው ሕግጋት መካከል አንዱ በሆነው ሕግ  1 መሠረት ይሁዳ ከላይ ባነበብነው ጥቅስ፣ “ገዣችንና ጌታችን” ብሎ የሚገልጸው አንዱን አካል ይኸውም ኢየሱስን መሆኑን እንረዳለን። ሕጉ እንደሚለው “በዋናው የግሪክ አወቃቀር (ትርጉም ባልሆነ ግሪክ) “ካይ” በሚል መስተጻምር የተያያዙ ሁለት ስሞች አንድ መስተኣምር ከፊታቸው ከገባ እና ሁለቱም ባሕርይ ገላጮች (1) በሰዋሰውም ሆነ በቃል ደረጃ ነጠላ ከሆኑ (2) ማንነታዊ ከሆኑ (ህልውና ያላቸውን አካላት አመልካች ከሆኑ) እና (3) የወል ስሞች ከሆኑ (የተጸውዖ ስሞች ወይንም ቅደም ተከተላዊ ካልሆኑ) አንድን አካል ያመለክታሉ፡፡” በዚህ መሠረት τὸν μόνον δεσπότην καὶ κύριον ἡμῶν Ἰησοῦν Χριστὸν (ቶን ሞኖን ዴስፖቴን ካይ ኩሪዮን ሄሞን ኢዬሱን ክሪስቶን)  በሚለው ውስጥ “ዴስፖቴን” (ገዣችን) እና “ኩሪዮን” (ጌታችን) የሚሉት ባሕርይ ገላጮች “ቶን” በሚል አንድ መስተአምር የተቀደሙና “ካይ” በሚል መስተጻምር የተያያዙ በመሆናቸው ሕጉን ያሟላሉ፤ እናም በዚህ ቦታ “ገዣችን እና ጌታችን” የተባለው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። በተጨማሪም፣ በዐውደ-ምንባቡ ውስጥ  ብቸኛ አምላክ የተባለው አብ፣ በብቸኛው ጌታ  በክርስቶስ በኩል አኮቴት እንደሚቀርብለት ይናገራል (ቍጥር 25)፤ ይኽውም ይሁዳ ብቸኛ አምላክ የሚለውን ቅጽል ለአብ፣ “ብቸኛ ጌታ” የሚለውን ደግሞ ለወልድ ይጠቀማል ማለት ነው። ታዲያ በዚህ ጥቅስ ውስጥ “ገዣችንና ጌታችን የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን የሚክዱ ናቸው” የሚለውን የመጨረሻ ሐረግ አሁንም በጥንቃቄ ማስተዋል አስፈላጊ ነው። “ገዣችን” ተብሎ የተተረጎመው የጽርእ ቃል δεσπότην “ዴስፖቴን” የሚል ሲሆን፣ δεσπότης “ዴስፖቴስ” ከሚል የጽርእ ቅጽል የመጣ ነው። በዚኽ ቅጽል የሚጠራ ግለሰብ፣ በአንድ ማሕበረሰብ ወይም ቤተሰብ የበላይ መሪ ወይም ከሁሉም የላቀ ሥልጣን ያለው አካልን ለማመልከት የሚገባ ቃል ነው[1]። በይበልጥ ደግሞ ይኼ ቅጽል በሮማውያን ባሕል ውስጥ ያለው ሥልጣን እጅግ የላቀ ነው፤ ይኸውም የአንድ ቤተሰብ ራስና ባለ ሙሉ ሥልጣን ከመሆኑ የተነሳ፣ የአብራክ ልጆቹ ምን ትልቅ እና ራሳቸውን የቻሉ ቢሆኑ እንኳ ሥነ ምግባራቸው ደስ ካላሰኘው እስከ መግደል የደረሰ ሕጋዊ መብት አለው[2]። ይሁዳ ይኽንን ቃል የተጠቀመው በብሉይ ኪዳን ስመ-ያህዌን ወክሎ ለእልፍ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለውን “ጌታ” በጽርእ  κύριος “ኩሪዮስ” ከሚል ቃል ጋር በማጣመር ነው። እነኚህ ኹለት ቅጽሎች ማለትም፣ δεσπότην “ዴስፖቴን” እና  κύριον “ኩሪዮን” በአንድ ላይ ተያይዘው የቀረቡት እውነተኛውን አምላክ ያህዌን ለመግለጽ መሆኑን የብሉይ ኪዳን የሰብዓ ሊቃናት ትርጉምን (LXX)  ስንመለከት እንገነዘባለን። ለምሳሌ፦
“አብራምም፣ “ገዢ ጌታ ሆይ (Δέσποτα Κύριε)፤ ይህችን ምድር እንደምወርሳት በምን ዐውቃለሁ?” አለ።”
  — ዘፍጥረት 15፥8 LXX
“እኔም፣ “ጌታ ገዢ ሆይ (δέσποτα Κύριε)   ፤ ሰይፍ አንገታቸው ላይ ተቃጥቶ ሳለ፣ ‘ሰላም ይሆንላችኋል’ ብለህ ይህን ሕዝብና ኢየሩሳሌምን ለምን እጅግ አታለልህ?” አልሁ።”
  — ኤርምያስ 4፥10 LXX
“ስለዚህ የሠራዊት ገዢ (δεσπότης)  ጌታ (Κύριος) እንዲህ ይላል፦ ለእስራኤል ኃያላን ወዮላቸው። ቍጣዬ በጠላቶቼ ላይ አይወገድምና፥ በጠላቶቼም ላይ ፍርድን አደርጋለሁ” ኢሳይያስ 1፥24 LXX
ኢየሱስ የኛ ብቸኛ ገዢ እና ጌታ ሊሆን የሚችልበት ብቸኛው መንገድ እርሱ ያህዌ አምላክ ከሆነ ብቻ ነው።
ቍጥር አምስት፦
“ምንም እንኳ አስቀድማችሁ ይህን ሁሉ የምታውቁ ቢሆንም፣ ኢየሱስ  ሕዝቡን ከግብፅ ምድር እንዴት እንዳወጣ፣ በኋላ ግን ያላመኑትን እንዳጠፋ ላስታውሳችሁ እወዳለሁ።”
  — ይሁዳ 1፥5 (ESV)
Ὑπομνῆσαι δὲ ὑμᾶς βούλομαι, εἰδότας ἅπαξ πάντα ὅτι Ἰησοῦς  λαὸν ἐκ γῆς Αἰγύπτου σώσας τὸ δεύτερον τοὺς μὴ πιστεύσαντας ἀπώλεσεν,
አንዳንድ የግሪክ የእጅ ጽሑፎች “ኢየሱስ” የሚለውን “ጌታ ሕዝቡን ከግብፅ ምድር እንዴት እንዳወጣ” ይላሉ፤ ነገር ግን በቍጥር 5 ላይ ጌታ ብለው  የጠቀሱት ክርስቶስ መሆኑን በመካድ አይደለም፤ ምክንያቱም፣ በቍጥር 4 ላይ፣ ብቸኛ ጌትነቱ የተነገረለት ኢየሱስ ነው፤ ሆኖም ግን በቊጥር 5 “ጌታ” የሚለው ቀዳማይ የግሪክ ዕደክታብ ኮዴክስ ሳይናቲከስ ሲሆን፣ ከእርሱ በዕድሜም ሆነ በጥራት ቀዳማይና ተመራጭ የሆነው ኮዴክስ ቫቲካነስ “ኢየሱስ” ይላል። ከዚህ በፊት በሌላ ጽሑፍ ላይ እንደገለጥነው በአዲስ ኪዳን የምንባባዌ ሕያሴ ሊቃውንት (New testament textual critics ) ዘንድ ከሳይናቲከስ ይልቅ ቫቲካነስ ይበልጥ ተቀባይነት አለው[3]፤ እንዲሁም፣ እንደ አርጌንስ፣ ቆጵርያኖስ፣ ጀሮሜ፣ ወዘተ. ያሉ ቀደምት የቤተክርስቲያን አበው ይሁዳ 1፥5ን በሚጠቅሱበት ጊዜ “ጌታ” ከሚለው ቃል ይልቅ “ኢየሱስ” የሚለውን በጽሑፋቸው ውስጥ ተጠቅመዋል። ይበልጡኑ ደግሞ ፓፒረስ 72 በመባል የሚታው የይሁዳ መልዕክት የመጀመሪያው የእጅ ጽሑፍ፣  “አምላክ ክርስቶስ” (θς χρς) በማለት “ኢየሱስ” ለሚሉት ዕደክታባት  ጥሩ ግብአት ሆኗቸዋል።

ፓፒረስ 72
ክርስቶስ ሕዝቡን ከግብፅ ማውጣቱን በተመለከተ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ተመሳሳይ ሐሳብ አንጸባርቋል፦
“ወንድሞች ሆይ፥ ይህን ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ። አባቶቻችን ሁሉ ከደመና በታች ነበሩ ሁሉም በባሕር መካከል ተሻገሩ፤ ሁሉም ሙሴን ይተባበሩ ዘንድ በደመናና በባሕር ተጠመቁ፤ ሁሉም ያን መንፈሳዊ መብል በሉ፥ ሁሉም ያን መንፈሳዊ መጠጥ ጠጡ፤ ይከተላቸው ከነበረው ከመንፈሳዊ ዓለት ጠጥተዋልና፥ ያም ዓለት ክርስቶስ ነበረ።” (1ቆሮ. 10፥1-4)

ተዋሕዶን እንወቅ።

08 Oct, 10:24


ክርስቲያን የምንባለው ዕኛ ዖርቶዶክሣዊያን ብቻ ነን?🙄

ተዋሕዶን እንወቅ።

08 Oct, 06:53


ጌታችን ኢየሱስ ሥልጣንን ከአብ መቀበሉ አምላክ አለመሆኑን ያሳያልን?
ጥያቄ፡-
“ኢየሱስም ቀረበና እንዲህ ብሎ ተናገራቸው፦ ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ። እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።” (ማቴዎስ 28፡18-20)፡፡
ሥልጣን የራሱ ቢሆን ኖሮ ግን “ሥልጣን ተሰጠኝ” ሳይኾን “ሥልጣን አለኝ ” ነበር የሚለው ስለዚህ ለኢየሱስ ሥልጣን የሰጠው አምላክ መኾኑን እንረዳለን፡፡

መልስ፡-
ይህንን ጥያቄ የሚጠይቁ ሰዎች እግዚአብሔር አንድ አካል ብቻ እንዳለው ቅድመ ግንዛቤ የያዙ ናቸው፡፡ የሥሉስ ቅዱስ አካላት አንዳቸው ከሌላቸው የመቀበላቸውና አንዳቸው ለሌላቸው የመታዘዛቸው እውነታ መታየት ያለበት አብ፣ ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ የአንዱ ግፃዌ መለኮት አካላት መሆናቸውን በሚናገረው መጽሐፍ ቅዱሳዊ አስተምሕሮ መሠረት እንጂ በነጠላ አሓዳዊነት መሠረት  መኾን የለበትም፡፡ ኡስታዝ አሕመዲን ጀበል ግን ከሞላ ጎደል በእያንዳንዱ ጥያቄያቸው ውስጥ ይህንን መሠረታዊ ሃቅ በመዘንጋት የራሳቸውን ቁርአናዊ እምነት በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ለመጫን ሲሞክሩ ይስተዋላሉ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ኢየሱስ ከአብ እንደሚቀበል ብቻ ሳይኾን ለአብ እንደሚሰጥም ጭምር ይናገራል፡- “በኋላም፥ መንግሥቱን ለእግዚአብሔር ለአባቱ አሳልፎ በሰጠ ጊዜ አለቅነትንም ኹሉና ሥልጣንን ኹሉ ኃይልንም በሻረ ጊዜ፥ ፍጻሜ ይሆናል” (1ቆሮ. 15፡24)፡፡ ስለዚህ እግዚአብሔር በመለኮት አንድ ቢሆንም በአካል ግን ሦስት በመኾኑ አንዱ የሥላሴ አካል ከሌላው መቀበሉ ከአንዱ ግፃዌ መለኮት ውጪ ከሚገኝ ሌላ አካል እስካልተቀበለ ድረስ አምላክነቱን ሊያጠራጥር አይችልም፡፡ ሌላው መረሳት የሌለበት ነጥብ በባሕርዩ ፍጹም አምላክ የሆነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ክብሩን ጥሎ የባርያን መልክ በመያዝ ወደ ምድር መምጣቱ ነው (ዮሐ. 6፡38፣ ማቴዎስ 20፡24-28፣ ፊልጵሲዩስ 2፡5-8)፡፡ ስለዚህ ተልዕኮውን ከፈፀመ በኋላ አብ አክብሮታል፡-
“በዚህ ምክንያት ደግሞ እግዚአብሔር ያለ ልክ ከፍ ከፍ አደረገው፥ ከስምም ኹሉ በላይ ያለውን ስም ሰጠው፤ ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ኹሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ፥ መላስም ኹሉ ለእግዚአብሔር አብ ክብር ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ እንደ ሆነ ይመሰክር ዘንድ ነው” (ፊልጵሲዩስ 2፡9-11)፡፡
በማቴዎስ 28፡18 ላይ የሚገኘውን ቃል በዚህ ማዕቀፍ ውስጥ ከተመለከትን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰው ልጆችን ለማዳን ለአባቱ ታዝዞ በገዛ ፈቃዱ ትቶት የመጣውንና መለኮታዊ መብቱ የሆነውን ሥልጣን መልሶ ተቀበለ እንጂ የእርሱ ያልሆነውን ስላልተቀበለ ይህ አባባል አምላክነቱን አጠራጣሪ ለማድረግ ምክንያት አይኾንም፡፡
ሌላው መታወቅ ያለበት ነገር ቢኖር ከተሠግዎ በፊት ጌታችን ፍጹም አምላክ እንደነበረና ከተሠግዎ በኋላ ግን አምላካዊ ባሕርዩ ሳይለወጥ ፍጹም ሰው መኾኑ ነው፡፡ ስለዚህ ወደ ክብሩ የተመለሰው ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው ኾኖ ነው፡፡ የአባቱን ፈቃድ ያለ ምንም እንከን ከዳር በማድረሱ ምክንያት መለኮታዊ ባሕርዩ ብቻ ሳይኾን ሰብዓዊ ባሕርዩም ጭምር ክብርን ተቀዳጅቷል፡፡ ይህ ደግሞ በስሙ የሚያምኑት ቅዱሳን የርስቱ ወራሽና የግዛቱ ተካፋይ ስለመሆናቸው ማረጋገጫ ነው (ሉቃ 22፡29-30፣ ዮሐ 17፡24፣ ሮሜ 8፡17፣ ራዕ 2፡26-27፣ ራዕ 3፡21)፡፡
ጠያቂው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሥልጣንን ከአብ መቀበሉን የሚናገረውን ቃል ብቻ ነጥለው ጠቀሱ እንጂ ሙሉ አውዱን ቢያነቡት ኖሮ የኢየሱስን አምላክነት አሻሚ ባልሆነ ኹኔታ በተመለከቱ ነበር፡፡ እስኪ በክፍሉ አውድ ውስጥ የሚገኙትን ደምቀው የተጸፉትን ቃላት ልብ ብለን እንመልከት፡-
“አሥራ አንዱ ደቀ መዛሙርት ግን ኢየሱስ ወዳዘዛቸው ተራራ ወደ ገሊላ ሄዱ፥ ባዩትም ጊዜ ሰገዱለት፤ የተጠራጠሩ ግን ነበሩ፡፡ ኢየሱስም ቀረበና እንዲህ ብሎ ተናገራቸው፦ ሥልጣን ኹሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ፡፡ እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ኹሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ኹሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ” (ማቴ 28፡16-20)፡፡
በዚህ ቦታ ላይ ሐዋርያት ለኢየሱስ ሰግደዋል፡፡ የጠያቂው ሃይማኖት አጥብቆ እንደሚያስተምረው ኢየሱስ ሰው ብቻ ቢሆን ኖሮ ሌሎች ቅዱሳን ሰዎችና መላዕክት እንዳደረጉት ሐዋርያቱ እንዳይሰግዱለት በነገራቸው ነበር (ሐዋ. 10፡25-26፣ ራዕ 22፡8-9)፡፡ ነገር ግን ኢየሱስ አንድም ጊዜ ያንን አድርጎ አያውቅም፡፡ ኢየሱስ በሰማይና በምድር ሥልጣን ኹሉ እንደተሰጠው ተናግሯል፡፡ የእግዚአብሔር አንድያ ልጅና ወራሽ ባይኾን ኖሮ አብ እንዴት በሰማይና በምድር ሥልጣንን ኹሉ ይሰጠው ነበር? የጥምቀቱ ደግሞ ከኹሉም በላቀ ኹኔታ አምላክነቱን ይገልጣል፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት የእግዚአብሔር ስም ባሕርዩን ይወክላል (ዘጸ 33፡17-23፣ 34፡5-7)፡፡ የእግዚአብሔርን ስም ማመስገን ማለት እግዚአብሔርን ማመስገን ማለት ነው (መዝ 7፡17)፡፡ የእግዚአብሔር ስም ረዳታችን እንደሆነ መናገር እግዚአብሔር ረዳታችን እንደሆነ መናገር ነው (መዝ. 124፡8፣ 121፡2)፡፡ በእግዚአብሔር ስም መምጣት ማለት በእግዚአብሔር ኃይል መምጣት ማለት ነው (1ሳሙኤል 17፡45፣ ዮሐንስ 5፡43)፡፡ ስለዚህ እግዚአብሔርና ስሙ አይነጣጠሉም፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በጥምቀት የገዛ ስሙ ከአብ እና ከመንፈስ ቅዱስ እኩል እንዲጠቀስ በማዘዝ አንድ ስም እንዳላቸው ግልፅ አድርጓል፡፡ ይህም ከአብ እና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በባሕርይም ሆነ በአገዛዝ አንድ መኾኑን ያሳያል፡፡ ማንም ፍጡር እንዲህ ዓይነት ነገር ቢናገር በእውነተኛው አምላክ ላይ ክህደትን መፈፀም በመኾኑ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ አሁንም በዚሁ ስፍራ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እስከ ዓለም ፍፃሜ ድረስ ሁል ጊዜ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር እንደሚሆን በመናገር በኹሉም ቦታ መገኘቱን አስታውቋል፡፡ በእርግጥ በኹሉ ቦታ መገኘት መቻሉን ሲናገር ይህ ለመጀመርያ ጊዜ አይደለም (ማቴ 18፡20 ይመልከቱ)፡፡ ማንም ሰው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ሥልጣን ከአብ መቀበል በዚህ አውድ ውስጥ በማንበብ መረዳት ያስፈልገዋል እንጂ ከአውዱ ገንጥሎ በማውጣት የተለየ ትርጉም መስጠት የለበትም፡፡

ተዋሕዶን እንወቅ።

07 Oct, 09:17


ለኔ😭

1,734

subscribers

2,368

photos

89

videos