Lemi kura Communication @lemikuracom Channel on Telegram

Lemi kura Communication

@lemikuracom


Lemi kura Communication (English)

Welcome to Lemi kura Communication, a Telegram channel dedicated to providing valuable insights and information on effective communication strategies. Whether you are a professional looking to improve your communication skills in the workplace or an individual seeking to enhance your personal relationships, this channel is the ideal destination for you. Lemi kura Communication offers tips, tricks, and resources to help you become a confident and articulate communicator in any setting. From public speaking to active listening, from nonverbal cues to written communication, this channel covers a wide range of topics to help you master the art of effective communication. Join us today and take the first step towards becoming a more effective and influential communicator! Channel username: @lemikuracom

Lemi kura Communication

11 Feb, 16:44


ለ38ኛው የአፍርካ መሪዎች ጉባኤ ለማስተናገድ በከፍተኛ ርብርብ ዝግጅቱ እየተጠናቀቀ ያለው አዲስ አለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል የከተማው ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ጉብኝት ተደረገ

አዲስ አለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በ7/24 ስራ ባህል ፣የከፍተኛ አመራሩ ልዩ ድጋፍና የቅርብ ክትልል በፍጥነትና ጥራት በመገንባት ለአዲስ አበባ ተጨማሪ ገፀ በረከትና አለም አቀፍ የቱሪዝምና ኮንፍረንስ ደረጃ ያሟላ እንዲሁም የአዲስ አበባን የቱሪዝም መስህብ በትልቅ ደረጃ በመጨመር ረገድ ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል የተባለው ማዕከል ነው።

ይህ ማዕከል ለ38ኛው የአፍርካ መሪዎች ጉባኤ የሚመጡ እንግዶችን ለማስተናገድ የሚያስችሉ ቅድመ ዝግጅቶች ዙሪያ የአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፍ አቶ ሞገስ ባልቻ ፣በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥራቱ በየነ ፣የከተማ ደጋፊ አመራሮች የክ/ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አድማሱ ደቻሳ እና ሌልች አመራሮች በተገኙበት የመስክ ምልከታ እና ጉብኝት አድርገዋል። ።

በግምገማው ለ38ኛው የአፍርካ ሕብረት መሪዎች ጉባኤ በተሳካ ሁኔታ ለማስተናገድ የተሻለ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን በማረጋገጥ የቀሩ ስራዎች ዙሪያ አቅጣጫ ተቀምጧል ።

ለሚ ኩራ ኮሙኒኬሽን
የካቲት 04/2017 ዓ.ም

Lemi kura Communication

11 Feb, 13:20


በቅሬታና አቤቱታ አቀራረብ፣ ምርመራና አወሳሰን ዙሪያ ለባለድርሻ አካላት ስልጠና ተሰጠ።

የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ፍትህ ጽ/ቤት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቅሬታና አቤቱታ፣ምርመራ፣አወሳሰን እና የተጠያቂነት ስርዓትን ለመወሰን በወጣው ደንብ ቁጥር 143/2015 ዙሪያ በቅሬታና አቤቱ ጽ/ቤት ለሚሰሩ ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል።

የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ፍትህ ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ተሾመ መገርሳ ስልጠናው የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመቅረፍ የህብረተሰቡን ቅሬታ በተገቢው መንገድ ለመፍታትና የተሳለጠ አገልግሎት ለመስጠት ትልቅ ሚና ይኖረዋል ብለዋል።

በሌላ በኩል በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ፍትህ ጽ/ቤት የህግ ስርጸትና ግንዛቤ መፍጠር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት ወ/ሮ መሰረት መብራህቶም ደንቡ የህግ የበላይነት የሰፈነበት እና ፍትሀዊ የሆነ አገልግሎት ለመስጠት ትልቅ አስታዋጽኦ እንዳለው የገለጹ ሲሆን አስተዳደራዊ በደሎችንም ለመከላከል የጎላ ፋይዳ እንደሚኖረው ገልጸዋል።

ለሚ ኩራ ኮሚዩኒኬሽን
የካቲት 4/2017

Lemi kura Communication

11 Feb, 10:01


130 ለሚሆኑ እናቶች የተስማሚ ቴክኖሎጂ ድጋፍ ተደረገ።

የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ሴቶች ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ጋር በመተባበር 130 ለሚሆኑ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው እናቶች የተስማሚ ቴክኖሎጂ ድጋፍ አድርጓል።

የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ሴቶች ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ሙሉ እመቤት ስራህ ብዙ ከ10ሩም ወረዳዎች ተመልምለው ለመጡ አነስተኛ ገቢ ላላቸው 130 እናቶች እንደ ምጣድ፣ የዳቦ መጋገሪያ፣የሽንኩርት መፍጫ እና የመሳሰሉትን ግብዓቶች ድጋፍ መደረጉን ተናግረዋል።

ኃላፊዋ የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው ሴቶች የተደረገላቸውን ድጋፍ ለተፈለገው ዓላማ በማዋል ራሳቸውን እንዲለውጡ የተጣለባቸውን አደራ መወጣት እንዳለባቸውም ተናግረዋል።

ለሚ ኩራ ኮሙዩኒኬሽን
የካቲት 04/2017

Lemi kura Communication

11 Jan, 15:58


የቅዳሜ ገበያ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ባሉት የግብይት ቦታዎች በበዓል ዋዜማ ደምቆ እየተካሄደ መሆኑን በቅኝታችን ይሄንን ይመሴላል።

Lemi kura Communication

11 Jan, 15:57


የለውጥ ስራዎችን ውጤታማ በመሆነ መንገድ በመምራት አገልግሎት አሰጣጡን ለማሳለጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት የ2017 በጀት አመት የ6 ወራት ስራ አፈጻጸም የክፍለ ከተማና የወረዳ የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች በተገኙበት ግምገማ አካሂዷል ።

በመድረኩ በ6 ወራት የተከናወኑ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት ፣በልማት ምክንያት ከይዞታቸው ለሚነሱ ተነሺዎች መልሶ ማቋቋም ፣በ6 ወራት ውስጥ የመሬት ወረራን መከላከልና መቆጣጠር ስራና የተቋሙን የመፈጸምና ማስፈፀም አቅም ከማሳደግ አኳያ ውጤታማ ስራ መስራቱን በሪፖቱ ቀርቧል።

በመድረኩ በክብር እንግድነት የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ አማካሪ የሆኑት አቶ ተስፋዬ ጥላሁን እንደተናገሩት ተቋሙ ከሪፎም ወዲህ ውጤታማ ስራዎችን የሰራ፣እየሰራ የሚገኝና ቴክለኖሎጂን በመጠቀም የተሻለና ፈጣን አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ገልፀው ከላይ እስከ ታች ያለው አመራርና ባለሙያ ህብረተሰቡን በትጋትና በታማኝነት በማገልገል ብልሹ አሰራሮችን ለመቅረፍ በጋራ መታገል ያስፈልጋል ብለዋል።

የቅርንጫፍ ፅ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ፈይሳ እንደተናገሩት በግምገማው ጥንካሬዎችን ማጉላትና ክፍተቶችን ፈጥኖ በማረም አገልግሎት አሰጣጡን የበለጠ ማቀላጠፍ ያስፈልጋል በማለት ቀጣይ የለውጥ ስራዎችን ውጤታማ በመሆነ መንገድ በመምራት አገልግሎት አሰጣጡን ለማሳለጥ በትኩረት ይሰራል ብለዋል ።

ባለፉት 6 ወራት የተገልጋዩን ጥያቄ ለመመለስ ቅዳሜና እሁድን ጨምሮ እስከ ምሽት ድረስ በመስራት በርካታ የአገልግሎት ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ መደረጉን ገልፀው በተቋሙ የሚሰጡ አገልግሎቶችን በማዘመን ህገ ወጥነትን ፣ሌብነትንና ብልሹ አሰራሮች መከላከል መቻሉንም የቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊው ተናግረዋል ።

በመጨረሻም የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ተቋማትና ባለሙያዎች የእውናና ሽልማት በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል ።

ለሚ ኩራ ኮሙኒኬሽን
ጥር 03/2017 ዓ.ም

Lemi kura Communication

11 Jan, 11:44


በTVET ፖሊሲ፣የትብብር ስልጠና አተገባበር እና የስራ ትስስርን አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሄደ።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስራ እና ክህሎት ቢሮ ከቦሌ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ ጋር በጋራ በመሆን ከከፍተኛ፣መካከለኛ እና አነስተኛ ኢንዱስትሪዎች በTVET ፖሊሲ፣የትብብር ስልጠና አተገባበር እና የስራ ትስስርን አስመልክቶ ከመንግስትና መንግስታዊ ካልሆኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሄደ።

ውይይቱን የመሩት የቦሌ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ ዋና ዲን ዶ/ር ታደሠ መኮንን የዚህ ውይይት አላማ በትብብር ስራዎችን ለመስራትና ያሉ ጥንካሬዎችን ለማስቀጠል እንዲረዳ ያለመ መድረክ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የስራ እና ክህሎት ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ቤዛ ደመቀ እንዳሉት እስከ አሁን ከቦሌ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ ጋር በጋራ በመሆን ከ12 ሺ በላይ የሆኑ ሠልጣኞችን በጋራ የትብብር ስልጠና መሠልጠናቸውን ጠቁመው በቀጣይም በትብብር በመስራት በሙያና በተግባር የበለፀገ ዜጋ ለመፍጠር የምንሠራ ይሆናል ብለዋል።

የለሚ ኩራ ኮሚኒኬሽን
ጥር 3/2017 ዓ.ም

Lemi kura Communication

07 Jan, 11:33


የገና በዓል ሀገራዊ አብሮ የመኖር እሳቤ አጉልቶ ያሳየ ተግባር ነው።

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ በወረዳ 8 በተገነባው ሎኮስት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚኖሩ የማህበረሰብ ክፍሎችን በዓሉን ምክንያት በማድረግ የምሳ ፕሮግራም ማካሄዱን ገለፀ።

በዚህ ዝግጅት ላይ የተገኙት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስራ እና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥራቱ በየነ አስቀድመው ነዋሪዎችን እንኳን ለጌታችን ለመድሐኒታችን የልደት ቀን በሠላም አደረሳቹ ሲሉ በዓሉን ካለን አካፍለን ኢትዮጵያዊ የመደጋገፍ እሴቶችን የምናዳብርበት እንዲሁም በዓሉ የሠላም፣የደስታ፣የጤና እንዲሆን እመኛለው ሲሉ መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አድማሱ ደቻሳም በነዋሪዎቹ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን አብረን በርብር የምንመልሳቸው ነገሮች እንዳሉ ሆነው የዘንድሮውን የገና በዓል ስናከብር በአብሮነት፣በወንድማማችነትና በእህትማማችነት በጋራ የምናከብረው በዓል እንዲሆን እመኛለው ብለዋል።

የለሚ ኩራ ኮሚኒኬሽን
ታህሳስ 29/2017 ዓ.ም

Lemi kura Communication

07 Jan, 04:35


"ሰው ተኮር ተግባሮቻችን ለአብሮነታችን"


በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ አስተባባሪነት በወረዳ 05 የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ የተሰራው የሰው ተኮር ተግባር የሆነው የአቅመ ደካማ ሙሉ የቤት እድሳት በማጠናቀቅ ርክክብ ተደረገ።

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ አስተባባሪ በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው እንደገልፁት በየጊዜው እየተሰሩ ያሉ ሰው ተኮር ስራዎች አበረታች እንደሆነ እና ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚያስፈልግ እና በቀጣይም መሰል ተግባራትን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልፀዋል።

አክለውም የበጎ ፈቃድ ተግባር የህሊና እፎይታ የሚሠጥ የተቀደሠ ተግባር ከመሆኑ ባሻገር እንደ ፓርቲ ማህበራዊ ፍትህን የምናረጋግጥበት ዋንኛው የፓርቲያችን መገለጫ ነው በማለት ምስጋና በማቅረብ የእንኳን አደረሳችሁና የመልካም በዓል ምኞታቸውን ገልፀዋል።

የለሚ ኩራ ኮሚኒኬሽን
ታህሳስ 29/2017 ዓ.ም

Lemi kura Communication

07 Jan, 04:25


በዓልን በጋራ በማሳለፍ አብሮነታችንን እናጠንክር

በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽንና ኤግዚብሽን መዓከል በ2ኛው ዙር የኮሪደር ልማት ስራ ላይ 24/7 እየተሳተፉ ሞያተኞችና የበን ስራ ላይ ለተሰማሩ ሰራተኞች የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ የእራት ግብዣ ተደረገላቸው።

የእራት ግብዣውን የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ያዘጋጀ ሲሆን በቦታው በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ስራ እና ክህሎት ቢሮ ሀላፊ አቶ ጥራቱ በየነ ፣ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አቶ አድማሱ ደቻሳ እና ሌሎች ኮር አመራሮች ተገኝተው የእራት ግብዣ ፕሮግራሙን አከናውነዋል።

ለሚ ኩራ ኮሚኒኬሽን
28/04/2017 ዓ.ም

Lemi kura Communication

26 Dec, 14:11


የሥራ ዕድል ፈጠራና የሌማት ቱሩፋት የንቅናቄ ሥራዎችን እና የምግብ ዋስትና ተጠቃሚ ልየታ አፈፃፀም ተመገምገም ።
የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የስራ ዕድል ፈጠራ፣ የልማት ትሩፋት የንቅናቄ ስራ እና የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ ቀጣይ በሚተገበረው የምግብ ዋስትና ፕሮግራም የተጠቃሚዎች ልየታ፣ የደረጃ ፍረጃ እና የ2ኛ ዙር ተጠቃሚዎች ምርቃት ተገምግሞ የስራ አቅጣጫ ማስቀመጡንም ገልጿል።

መድረኩን የመሩት የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፈንታሁን ሌማንቾ እንዳሉት ተግባራቱን አመራሩ ትኩረት በመስጠት በከፍተኛ እርብርብና ቅንጅት ሊሠራ ይገባል ሲሉ አክለው አመራሩ የተለያዩ የንቅናቄ እና ሰው ተኮር ስራዎችን አቀናጅቶ የመምራት አቅሙን ተጠቅሞ ወጣቶችን ሴቶችን እና ሌላውን የህብረተሰብ ክፍል በማሳተፍ የሌማት ትሩፋት ስራውን በከፍተኛ እርብርብ መስራት ይኖርበታልም ብለዋል።

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚና የሥራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ልመንህ ምህረቱ አክለው እንዳሉት ከሥራ ዕድል ፈጠራና ከሌማት ቱሩፋት የንቅናቄ ሥራዎች አንፃር የአፈፃፀም ሂደቱን አጠናክሮ መቀጠል ጥራቱን በሱፐርቪዥንና ድጋፍ በማድረግ ሥራዎችን ተሳስሮ እንዲቀጥል የአመራር ትኩረት ይፈልጋል ሲሉ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ ተግባራዊ በሚደረገው የከተማ ምግብ ዋስትና እና ልማታዊ ሴፍቲኔት ተጠቃሚዎችን ለመለየት የምዝገባ ሥራው መጠናቀቁ በመድረኩ በጠንካራ ጎን የተነሳ ሲሆን በቀጣዮቹ ቀናት ተመዝጋቢዎችን በደረጃ የመፈረጅ ሥራውን በማጠናቀቅ ለማህበረሰቡ ማስተቸት እንደሚገባ አቅጣጫ ሠጥተዋል።

Lemi kura Communication

26 Dec, 14:08


በእረፍት አልባ አመራሮቻችን እና በበረቱ እጆች እየተሰራ ያለው ሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት ስራው እያደር አዲስ ውበት እያጎናፀፈ መሆኑን የሚያሳይ የአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን እና ኤግዚብሽን ማዕከል አሁናዊ ገፅታ በፎቶ

Lemi kura Communication

26 Dec, 14:07


ለልማት ስኬታማነት የሚተጉ እጆች ሊመሰገኑ ይገባል"

አቶ ጥራቱ በየነ
በምክትል ከንቲባ መዓረግ የአዲስ አበባ ከተማ
አስተዳደር ስራ እና ክህሎት ቢሮ ሀላፊ

በሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት ስራ ከተባበሩት ሰሚት ጎሮ እንዲሁም አዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽንና ኤግዚብሽን ማዕከል ቀን ከሌሊት ለሚሰሩ የቀን ሰራተኞች ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አስተዳደር አስተባባሪነት የወረዳ 2 አስተዳደር እና የወረዳ 8 አስተዳደር የእራት ግብዣ አደረገ።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ስራእና ክህሎት ቢሮ ሀላፊ አቶ ጥራቱ በየነ በእራት ግብዣው ላይ በመገኘት ለሰራተኞቹን እየሰራችው ያላችሁት ሀገር ነው የምትገነቡት ከተማን ነው ለዚህም የከተማ አስተዳደሩ ለድካማችሁ ዋጋ ይሰጣል በትልቅም ያመሰግናችዋል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አድማሱ ደቻሳ በበኩላቸው በ24/7 አዱስ የስራ ባህል ብርድ እና ውርጩን ተቋቁማችሁ ለምትሰሩት ስራ በክፍለ ከተማው ስም እያመሰገንን በቀጣይም አብረን ምቹ አካባቢን እንገነባለን ብለዋል።

Lemi kura Communication

15 Dec, 09:41


በዶ/ር ፍጹም አሰፋ የተመራ የፌዴራል የሱፐርቪዥን ቡድን በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ  በመጀመሪያው  ዙሪ የተሰሩ የኮሪደር የልማት ስራዎችን ጎበኙ

በኢፌዴሪ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዶ/ር ፍጹም አሰፋ፣
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራልና ከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ያካተተው የሱፐርቪዥን ቡድን በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በመጀመሪያው  ዙሪ የተሰሩ በኮሪደር የልማት  የተገነቡ  የአረንጓዴ  ልማት፣የስፖርት ሜዳዎች፣ብስክሌት መንገዶችና ልሎች በኮሪደሩ ልማት የተሰሩ ስራዎችን ጎብኝቷል።

ለሚ ኩራ ኮሙኒኬሽን
ታህሳስ 05/2017ዓ.ም

Lemi kura Communication

30 Nov, 20:05


እንኳን በሰላም ወደ ቤታችሁ መጣችሁ!!!

የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር በዛሬው ዓለት ከተለያዩ ክ/ከተሞች በልማት ምክናያት ተነስተው ወደ ወረዳው የመጡ ዜጎችን በጥሩ የኢትዮጵያዊ አቀባበል እየተቀበለ ነው።

ከየካ፣ አራዳ፣ ካሳንችስ እና ቂርቆስ አከባቢ ይኖሩ የነበሩ ዜጎች በተለያዩ የከተማ ማልማት እና ማዘመን ጋር ተያይዞ እየተሰሩ ባሉ ዘርፈ ብዙ ስራዎች ም/ት አራብሳ ለመኖር የመጡ ዜጎችን የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ምክትል እና ፖለቲካ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ሲሳይ ኬኔ ጨምሮ፣ ሰላም እና ፀጥታ፣ ደንብ ማስከበር፣ የለሚ ኩራ ወረዳ 06 ኮር አመራሮች ፣የሰላም ሰራዊት፣ የደንብ ማስከበር ኦፊሰሮች እንደተለመደው በልዩ ዝግጅት አቀባበል እየተደረገ ይገኛል።

በአጠቃላይ በዛሬው እለት 239 የሚሆኑ ዜጎች ወደ ተዘጋጀላቸው ማረፊያ እንደሚገቡ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
ህዳር 17/2017

Lemi kura Communication

19 Nov, 14:44


በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ "የህልም ጉልበት፤ለእምርታዊ እድገት" በሚል መሪ ቃል በክፍለ ከተማ እና በወረዳ ደረጃ በተለያዩ ደማቅ ዝግጅቶች ሲካሄድ የቆየው የ5ኛ አመት የብልፅግና ፓርቲ የምስረታ ክብረ በዓል በክፍለ ከተማ ደረጃ በርካታ ህዝብ ባሳተፈ መልኩ የማጠቃለያ ፕሮግራም መካሄድ ጀመረ።
የለሚ ኩራ ኮሚኒኬሽን
ህዳር 7/2017 ዓ.ም

Lemi kura Communication

19 Nov, 14:37


የ19ኛው የኢትዮጵያ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀንን ምክንያት በማድረግ የፓናል ውይይት ተካሄደ ።
በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ሴቶች ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ፅ/ቤት አዘጋጅነት "ሀገራዊ መግባባት ለህብረ - ብሄራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል የ19ኛው የኢትዮጵያ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀንን ምክንያት በማድረግ የሴቶች ፓናል ውይይት ተካሂዷል ።
በመድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሪት ወይንሸት አስናቀ በመልዕክታቸው ዘንድሮ የኢትዮጵያ የብሔሮች፣ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ልዩ የሚያደረገው የብልፅግና ፓርቲ 5ኛ አመት ምሰረታ በዓል በሚከበርበት ወቅት መሆኑ በዓሉን ልዩ እንደሚያደርግ ገልፀው ቀኑን ስናከብር አብሮነትን ፣ወንድማማችነት በተለይም የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች የእርስ በእርስ ግንኙነት የሚያጠናከር መሆኑ ገልፀዋል ።
የክፍለ ከተማ ሴቶች ህፃናት ማህበራዊ ጉዳይ ፅ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሙሉእመቤት ስራህብዙ በበኩላቸው ሀገራችን የብዙ ባህል ፣ቋንቋዎች ያሉባት ሀገር ላይ እንዲህ አይነት በዓላትን አብሮ ማክበር አንድነትና መቻቻልን የሚያጠናክርና የወል ትሪክትን ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል ።
ለሚ ኩራ ኮሙኒኬሽን
ህዳር 06/2017 ዓ.ም

Lemi kura Communication

01 Nov, 16:46


የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎች አገልግሎት ጽ/ቤት የብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) ምዝገባ ሂደት ያለበትን ደረጃ ገመገመ

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎች አገልግሎት ጽ/ቤት የብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) ምዝገባ ሂደት ያለበትን ደረጃ የአስሩም ወረዳ የዘርፉ አመራሮች፣የክፍለ ከተማና የወረዳ ቡድን መሪዎች በተገኙበት ገምግሟል።

ይህንን የመድረክ የመሩት የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ወንድማገኝ ታደሠ እንዳሉት ይህ የብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) ምዝገባ መካሄድ በዋናነት የተደራጀ የዲጂታል መታወቂያ ስርዓትን ለመዘርጋት፣አገልግሎት አሠጣጥን የሚያዘምን፣ማጭበርበርን የሚቀንስና የመንግስትን ሀብት ከብክነት የሚከላከል እንዲሁም አጅግ በርካታ ሀገራዊ ፋይዳዎች ያሉት በመሆኑ ተግባሩን እጅግ ትኩረት ሠጥቶ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎች አገልግሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ባጫ ጅሬኛ በበኩላቸው ተግባሩ በዋናነት በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት ብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ፋይዳ ዲጂታል የሚመራና የኢትዮጵያን ሁለተናዊ ብልፅግና ከማስፈን አንፃር የሚኖረው ሚና እጅግ የላቀ ነው ያሉት አቶ ባጫ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባን በተመለከተ ከክፍለ ከተማ እስከ ወረዳ ብሎም እስከ ብሎክ ድረስ ያሉ ቁልፍ ባለድርሻ አካላት በቂ ግንዛቤ በማስጨበጥ እንደ ክፍለ ከተማ የተሠጠንን እቅድ ማሳካት ይኖርብናል ሲሉ ተናግረዋል።

የለሚ ኩራ ኮሚኒኬሽን
ጥቅምት 22/2017 ዓ.ም

Lemi kura Communication

01 Nov, 16:45


መስሪያ ቦታዎች ልማት አስተዳደር ጽ/ቤት መፍትሔ በሚሹ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ዙሪያ ከኢንተርፕራይዞች ጋር ውይይት አካሄደ።

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የመስሪያ ቦታዎች ልማት አስተዳደር ጽ/ቤት መፍትሔ በሚሹ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ዙሪያ ከኢንተርፕራይዞች ጋር ውይይት አካሄደ።

በመድረኩም በዋናነት ትኩረት ተደርጎ ተሳታፊዎች ውይይት ካደረጉባቸው ጉዳዮች መካከል አምስት አመት የሞላቸው ኢንተርፕራይዞች ውል በሚያድሱበት አግባብ ምን መሆን አለበት በሚሉ እና በኢተርፕራይዞች እየተነሡ ያሉ የመሠረተ ልማት የመልካም አስተዳደር ችግሮች እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

ተሳታፊዎች ላነሷቸው ጥያቄዎች ምላሽ የሠጡትና ውይይቱን በንግግር የከፈቱት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የመስሪያ ቦታዎች ልማት አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ት ቤተልሔም ግዛው እንዳሉት ተቋሙ ሪፎርም ከተደረገ በኋላ በውጤት ደረጃ የሚቆጠሩ ስራዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ሠርቷል ሲሉ አሁንም ያሉ በኢተርፕራይዞች ዘንድ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ከሌሎች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን በአጭር ጊዜ ውስጥ እልባት እንደሚሠጥም ተናግረዋል።

የለሚ ኩራ ኮሚኒኬሽን
ጥቅምት 22/2017 ዓ.ም

Lemi kura Communication

24 Jul, 12:19


በ2ኛ ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ጥናት ላይ ውይይት ተካሄደ

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በምዕራፍ ሁለት የኮሪደር ልማት ጥናት ላይ ከክፍለ ከተማ አጠቃላይ እና ከወረዳ የአስተባባሪ ኮሚቴ አባላት እንዲሁም ከሚመለከታቸው አመራሮች ጋርም ውይይት አካሄዷል።

ጥናቱ በተመረጡ አምስት ኮሪደሮች ላይ የተከናወኑ ሲሆን እነሱም
👉 ከጎሮ አደባባይ እስከ 72 አካባቢ
👉ከሲሚት ለስላሳ ፋብሪካ እስከ ፍየል ቤት
👉ከሲ ኤም ሲ አደባባይ እስከ ከፍየል ቤት
👉ከፊጋ እስከ ሳሊተምህረት እንዲሁም
👉 ከሲ ኤም ሲ አደባባይ እስከ ደራርቱ አደባባይ እንደሆነ በውይይቱ ተገልጿል።

ይህን የውይይት መድረክ የመሩት የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ታረቀኝ ገመቹ እንዳሉት በመጀመሪያው የኮሪደር ልማት ስራ የተሠሩ በርካታ ስኬታማ ስራዎችን እንደ ምርጥ ተሞክሮ በመውሰድ አመራሩ በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል ሲሉ ውይይትም ከህብረተሰብ እንዲሁም ከተቋማት ኃላፊዎች ጋር በተናጥልም ሆነ በጋራ ማድረግ እና መግባባት ያስፈልጋልም ሲሉ ተናግረዋል። የቀጣይ አቅጣጫዎች አስቀምጠዋል።

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ /ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ደንድር በበኩላቸው ከላይ የተሠጡ አቅጣጫዎችን ተቀብሎ ወደ ተግባር በመግባት የተሻለ የስራ አፈፃፀም ማስመዝገብ ያሻል ሲሉ አያይዘውም አመራሩ በቁርጠኝነት ወደ ስራ ገብቶ ተግባሩን እውን ማድረግ አለበት ብለዋል።

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስጨንቅ ብርሃኑ እንዳሉት በመጀመሪያው ምዕራፍ ያገኘናቸውን ልምዶችና ተግባራት በላቀ ትጋት በሁለተኛው ምዕራፍ በመድረገም ውጤታማ ስራ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

የለሚ ኩራ ኮሚኒኬሽን
ሐምሌ 17/2016 ዓ.ም

Lemi kura Communication

24 Jul, 09:36


አስደማሚ ውበት በለሚ ኩራ የኮሪደር ልማት