ይህ ትብብር ተማሪዎቻችን ዓለምአቀፍ ልምድና እውቀት እንዲቀስሙ፣ አመለካከታቸውን እንዲያሰፋ እና ጠቃሚ ክህሎት እንዲያገኙ በማለም የተደረገ ስምምነት ነው። ስምምነቱ የሚከተሉትን ጨምሮ የተለያዩ የጋራ ጥቅሞችን ያጠቃልላል::
ተማሪዎች በአጋር ተቋማት እንዲማሩ መፍቀድና ማመቻቸት ፣የተማሪ ልውውጥ ፕሮግራሞች፣ በሁለቱ ተቋማት መካከል የባህል እና የአካዳሚክ ልውውጥን ማመቻቸት ፣በውጭ አገር ሰመርካምፕ የመሳተፍ እድሎች መፍጠር ፣፣ የስኮላርሺፕ ዕድሎች መስጠት ፣ የትብብር የምርምርና ጥናት ፕሮጀክቶች በጋራ መሳተፍና ተሳትፎን ማበረታታትን ያጠቃልላል::
ጄኔቫ ቢዝነስ ስኩል በሲውዘርላንድ በተጨማሪ በስፔን ሃገር ፣ ባርሴሎና ማድሪድ ከተሞች ካምፓሶች ያሉት ሲሆን በሲውዘርላንድ ውስጥ ከሚገኙ ቢዝነስ ስኩል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ በትምህርት ጥራት በ2ኛ ደረጃ ላይ እንዲሁም በዓለም አቀፍ 50ኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ነው።
🚀Kibur College Signs MoU with Geneva Business School to Enhance Student Mobility and International Opportunities.
#KiburCollege #GenevaBusinessSchool