ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر @islamawigetem Channel on Telegram

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

@islamawigetem


አድናቆትን ዝናን ስምን ፈልጌ ሳይሆን
አሏህ በሰጠኝ እዉቅና ወንድምና
እህቶቼን ለማገልገል አንድ ጊዜ
ተፈጥሪያለዉ እናም ዱኒያ አኼራዬን
እንዲያሳምርልኝ በዱዓ አግዙኝ

ለማንኛዉም ጥያቄ
👇 👇
@seidabuzerbot

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر (Amharic)

እነዚህ እንዴት እናደረጋለን፦ ከብዙ የእስላምነት ግጥሞች በመሆኑ፣ 'ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر' ማለት እናያትን ወይስ 'islamawigetem' የተለያየ ችግር ላይ። በዚህ ቦታ የሚገኙትን አገልግሎቶች ለማስተካከል ወንዶችንና እናቶችን ከሚገኙ ወገኖች ያስወግዱ ይገልጻሉ። በአንድ ጊዜ በኢስላማዊ ሰዶች እና ዱኒያ አኼራዬን ለማንኛዉም ጥያቄ፣ 'islamawigetem' እና @seidabuzerbot የሚገኙ ችግሮች እንዲሁም ስንት አገልግሎች አለመረጋገጥ እንዲቆይ ማግኘት ይችላሉ።

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

16 Feb, 03:48


šéîď àbužëŕ سيد أبو ذر:
አላሁ ሱሃሁ ወተዓላ አደምን ዐ ሰ ለመፍጠር በፈለገ ግዜ
ጂብሪልን ወደ መሬት ወርዶ አፈር ዘግኖ እንዲያመጣ ላከው።
ጅብሪልም ወደ መሬት ከወረደ በኋላ ከመሬት አፈር ሊዘግን ሲል
መሬት፦"እንዳትቀንሰኝ በአላህ እጠበቃለሁ" አለችው።
ጅብሪልም በአላህ እጠበቃለሁ ስትለው ምንም ሳይነካት ትቶ
ተመለሰ።
አላህም ዘንድ መጣ'ና ፦"ጌታዬ ምድር ባንተ እጠበቃለሁ ስትለኝ
ተመለስኩ" አለው።
ከዚያም አላህ ሚካኢልን ላከው።ሚካኢልም ትእዛዙን ሊፈፅም ወደ
ምድር ሲወርድ መሬት፦" እንዳትቀንሰኝ በአላህ እጠበቃለሁ"
አለችው።
ሚካኢልም በአላህ እጠበቃለሁ ስትለው ምንም ሳይነካት ትቶ
ተመለሰ። አላህም ዘንድ መጣ'ና ፦"ጌታዬ ምድር ባንተ
እጠበቃለሁ ስትለኝ ተመለስኩ" አለው።
በመጨረሻም አላህ አዝራኢልን ላከው አዝራኢልም ተልዕኮውን
ሊፈፅም ምድር ላይ ወረደ'ና አፈር ሊዘግን ሲል ምድር፦"
እንዳትቀንሰኝ በአላህ እጠበቃለሁ" አለችው።
አዝራኢልም፦"እኔ እራሴ የአላህን ትዕዛዝ ሳልፈፅም ከመመለስ
በአላህ እጠበቃለሁ" ብሏት አፈር ከተለያየ ቦታ መዘጋገን ጀመረ።
ከጥቁሩም፣ከነጩም፣ከቀዩም ዘገነ።ለዝያም ነው የሰው ልጆች
መልክም የተለያየው። ከዚያም አዝራኤል አፈሩን ይዞ አላህ ዘንድ
ሲቀርብ አላህም፦"አፈሩን አንተ እንዳመጣህ ሁላ ነፍሳቸውንም
እንድታወጣ አንተን ወክዬሃለሁ" አለው።
ከዚያም ከምድር የመጣው አፈር ረጥቦ ጭቃ በሆነ ግዜ አላህ
ለመላዕክቶቹ፦"እኔ ከጭቃ ሰውን ልፈጥር ነው። ፍጥረቱንም
ባስተካከልኩና ከመንፈሴ በነፋሁበት ጊዜ ለእርሱ ሰጋጆች ኾናችሁ
ውደቁ።" ብሎ መልዕክት አስተላለፈላቸው።
ከዚያም አላህም ኢብሊስ እንዳይኩራራ አደምን በእጁ
ፈጠረው።ከዚያም ለ40 አመት ያህል ጭቃው ቅርፅ ብቻ ሁኖ
ከረመ። መላዕክትም በዝያ በኩል ሲያልፉ አደምን ሲያዩት በጣም
ይፈሩ ነበረ፤ ነፍስም አልገባለትም ነበር።
ከሁሉም በላይ እሚፈራው ኢብሊስ ሁሌ ከአደም ጭቃ አጠገብ
ሲያልፍ በእግሩ መታ አድርጎት ነበር ሚያልፈው። ያን ግዜ ሸክላ
ሲመታ እሚወጣው ድምፅ ይሰማ ነበር።
ከዚያም ኢብሊስ ከአደም ጭቃ ጎን ላይ ቁሞ፦"አንተማ ለሆነ ነገር
ነው የተፈጠርከው" እያለ በአፉ እየገባ በመቀመጫው ይወጣ
ጀመር።
ለመላዕክትም፦"እኔ በዚህ ላይ ከተሾምኩ አጠፋዋለሁ። እሱም እኔ
ላይ ከተሸመ አምጸዋለሁ" በማለት ይዝት ጀመር።
አላህም በአደም ገላ ላይ ነፍስ መንፋት በፈለገ ግዜ
መላዕክትን፦"ልክ ሩሁን/ነፍሱን እንደነፋሁለት ሰጋጆች ሆናችሁ
አጎብድዱ" ብሎ አዘዛቸው።
መላዕክትም ዝግጁ ሁነው መጠባበቅ በጀመሩ ግዜ አላህ በአደም
ሩሁን/ነፍሱን መንፋት ሲጀምር ገና ነፍሱ በአደም ጭንቅላት በኩል
ስትገባ አደም አስነጠሰው።
መላዕክትም፦"አልሀምዱሊላህ በል" አሉት።
አደምም፦"አልሀምዱሊላህ" ሲል...
አላህ ደግሞ፦"ጌታህ ይማርህ" ብሎ መለሰለት።
ከዚያም ነፍሱ አይኑ ጋ ስትደርስ የጀነት ውስጥ ፍራፍሬዎችን
ተመለከተ አንገቱ ላይ ስትደርስ ደግሞ ፍራፍሬዎችን መብላት
አሰኘው'ና ገና ነፍሱ እግሩ ላይ ሳትደርስ ሄዶ ለመብላት ተጣደፈ።
ነፍሱ መላ ሰውነቱ ላይ ስትሰራጭ ከመላዕክት ሁሉ ቀድሞ
ሱጁድ ያደረገለት ኢስራፊል ነበር። ከዚያም አላህ ለአደም፦"ሂድ
እነዛን ሰላም በላቸው'ና ምን ብለው እንደሚመልሱልህ አድምጥ"
ብሎ ላከው።
ሄዶ ሰላም ሲላቸውም መላዕክትም፦"ወዐለይኩሙሰላም
ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ" ብለው መለሱለት። አላህም
ለአደም፦"አደም ሆይ! ካሁን በኋላ ይህ ያንተ እና የዝርዮችህ
ሰላምታ ሆኖ ይዘልቃል" አለው።
አደምም፦"ጌታዬ ዝርዮቼ እነ ማን ናቸው?" ብሎ ጠየቀው።
አላህም፦"ከሁለቱ እጆቼ ምርጥ" አለው።
አደምም፦"ቀኝህን መርጫለሁ ሁለቱም እጆችህ ቀኝ ናቸው" ብሎ
ሲል...
አላህም እጁን ሲከፍትለት አደም እስከቂያማ ድረስ ያሉ ልጆቹን
ሁሉ ተመለከተ።በዚያም መሀል አንድ ብርሀናማ ሰው
ተመለከተ'ና፦"ያ አላህ ይህ ማን ነው?" ሲል ጠየቀ።
አላህም፦"እሱ ልጅህ ዳዉድ ነው"ብሎ መለሰለት።
አደምም፦"ጌታዬ ለዚህ ልጄ እድሜውን ስንት ነው ያደረግክለት?"
ብሎ ሲጠይቅ...
አላህም፦"60 ነው" አለው።
አደምም፦"ጌታዬ ከኔ እድሜ 40 ቀንስ'ና ለሱ ጨምረህ መቶ
ሙላለት" አለው።(ለአደም የተመደበለት እድሜ 1000 ነበር)
አላህም እሺ ብሎ ሞላለት'ና ምስካሪ መላዕክቶችንም አደረገ።
ከዝያም አላህ ዳግም ለአደም ልጆቹን ሁሉ ሲያሳየው አንዱ ጤነኛ
ነው፣አንዱ እግር የለውም፣አንዱ መስማት የተሳነው ነው፣አንዱ
ማየት የተሳነው ነው።
ይህን ሁሉ ሲመለከት፦"ምንው ጌታዬ ሁሉን እኩል ብትፈጥር ምን
አለበት" ሲለው
አላህም፦"አንተ አደም ሆይ! እኔ እንድመሰገን እፈልጋለሁ" ብሎ
መለሰለት፡፡
ከዚያም አላህ የአደምን ጀርባውን አንድ ግዜ አብሶ የሰው ልጆችን
ሁሉ አወጣ።
ከዚያም ሰበሰባቸው'ና፦"ጌታችሁ አይደለሁምን?" ብሎ
ሲጠይቃቸው፦"አዎ ጌታችን ነህ እንመሰክራለን" አሉ።
ከዚያም አላህም፦"እኔ ሰባት ሰማያትን እና ሰባት
ምድርን፣መላዕክቶችንም፣አባታችሁ አደምንም እናንተ ላይ ምስክር
አድርጊያለሁ።
የቂያማ ቀን ስጠይቃችሁ አላወቅንም ነበር ብላችሁ እንዳትክዱ
አሁንም እወቁ!!!
ከኔ ሌላ አምላክ የለም ከኔ ሌላም ጌታ የለም።በኔም ምንንም
አካል እንዳታጋሩ።
እኔ ወደ እናንተ መልዕክተኞቼን/ነቢያቶችን ቃል ኪዳኔን እና ዛቻዬን
የሚነግሯችሁ ሲሆኑ እልክላችኋላሁ። መፅሀፎቼንም
አወርድላችኋለሁ" አላቸው።
የአደም ዝርያዎችም፦"ካንተ ሌላ ጌታ እንደሌለ እንመሰክራለን ፤
ካንተ ሌላ አምላክ እንደሌለም እንመሰክራለን" ብለው ቃል ኪዳን
ገቡ።
አሁን ወደ ኢብሊስ ልመልሳችሁ፡፡
ቅድም ከመላዕክት ሁሉ ቀድሞ ለአደም ሱጁድ ያደረገው
ኢስራፊል ነው ብለናል ። እስራፊልን ተከትለው ሁሉም መላዕክት
ሱጁድ አድርገው ነበር ግና ኢብሊስ ሁሉም ሱጁድ ሲወርድ እሱ
በኩራት ቆመ።
አላህም፦" ኢብሊስ ሆይ! በሁለት እጆቼ (በኃይሌ) ለፈጠርኩት
ከመስገድ ምን ከለከለህ? (አሁን) ኮራህን? ወይስ (ፊቱኑ)
ከትዕቢተኞቹ ነበርክ?" ብሎ ኮነነው፡፡
ኢብሊስም፦" እኔ ከእርሱ በላጭ ነኝ፡፡ ከእሳት ፈጠርከኝ፤ አደምን
ደሞ ከጭቃ ፈጠርከው" አለ።
አላህም፦" ከጀነት ውጣ፤ አንተ የተባረርክ ነህና ፤ እርግማኔም
እስከ ፍርዱ ቀን ድረስ ባንተ ላይ ይኹን" አለው።
ኢብሊስም፦" ጌታዬ ሆይ! እስከሚቀሰቀሱበት (የቂያማ) ቀን
ድረስ አቆየኝ" አለው።
አላህም ጥያቄውን ተቀብሎት እስከቂያማ ድረስ ኢብሊስን
ሊያቆየው ቃል ገባለት።
ከዚያም ኢብሊስ፦"ጌታየ በአሸናፊነትህ ይኹንብኝ፤ የአደምን ልጆች
ከእነርሱ ምርጥ የኾኑት ባሮችህ ብቻ ሲቀሩ በመላ
አሳስታቸዋለሁ፡፡" ሲል ዛተ።
አላህም፦"አንተን እና ከአደም ልጆች የተከተሉህን ሁሉ ጀሀነም
እንደምሞላችሁ ቃል እገባለሁ" አለ።
ከዚያም አላህ ኢብሊስን ከጀነት አውጥቶ አደምን ጀነት
አስቀመጠው።
አደምም እማያውቀው ቦታ ላይ አንድ አጫዋች በሌለበት ቁጭ
ብሎ የድብርት ስሜት ተሰማው።
ከዝያም እዝያው ጋደም አለ፡፡ ድንገት እንቅልፍ ሸለብ አደረገውም።
ልክ ከእንቅልፉ ሲነቃ እራስጌው ላይ አንዲት ሴት ተመለከት
ከአይኖቿ ፍቅር እና እዝነት ይነበብባታል።
አደም፦"ከመተኛቴ በፊት እዚህ አልነበርሽም"

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

16 Feb, 03:48


ሀዋ፦"አዎ"
አደም፦"በተኘሁበት ነው የመጣሽው ማለት ነዋ!!!"
ሀዋ፦"አዎ"
አደም፦"ከየት ት ነው የመጣሽው"
ሀዋ፦"ካንተ ውስጥ ነው የመጣሁት።አንተ በተኛህበት ነው አላህ
ካንተ የፈጠረኝ።
አደም፦"ለምንድነው አላህ የፈጠረሽ?"
ሀዋ፦"አንተ እኔ ላይ ልትረጋ"
አደም አላህን አመሰገነ'ና፦'ብቸኝነት እየተሰማኝ ነበር" አለ።
ከዚያም መላዕክት መጡ'ና፦"ስሟ ማን ነው?" አሉት።
አደምም፦"ሀዋ" አለ።
መላዕክትም፦"ለምንድነው ሀዋ ተብላ የተሰየመችው" ብለው
ሲጠይቁት
አደምም፦'እሷ ከኔ ነው የተፈጠረችው እኔ ደግም ህያው ነኝ ለዛ
ነው ሀዋ ያልኳት"ብሎ መለሰላቸው።
ከዚያም አድም እና ሀዋ በጀነት ውስጥ ሳሉ አላህ አደምን
እንዲህም አለው፦"አንተ አደም ጀነት ውስጥ ላንተ ሁሉ ነገር ሀላል
ሲሆን ይህችን ቅጠል ላንተም ለሚስትህም ሀራም አድርጌያለሁ'ና
እንዳትቀርቧት"
አደም በጀነት የተደገሰለትን ድግስ ከሚስቱ ሀዋእ ጋር ሁኖ
እየተዟዞረ በመመገብ ላይ ነው፡፡ ንፋሱ መዓዛው፣ ጅረቱ፣
ልምላሜው፣ ፍራፍሬው...ሁሉም ለአደም እና ለሚስቱ ያለ ገደብ
የተቸራቸው የጌታቸው ስጦታ ነው፡፡ አንዲት ቅጠል ስትቀር፡፡
ከቀድሞ ርስቱ የተባረረው ኢብሊስ በመላዕክት የታጠረችውን
ጀነት በቅርብ ርቀት አሻግሮ ይመለከታል፡፡ መላ ዘየደ ፤
የመላዕክቱን ጥበቃ በብቃት ተሸግሮ ከጀነቱ አለም ከአደም ግዛት
ተከሰተ፡፡
አደም ከባለቤቱ ጋር ሁነው አለማቸውን እየቀጩ ነው፡፡ ከምግቡ
ይመገባሉ፣ ከጅረቱ ይጎነጫሉ፣ ፍራፍሬውን እየለቀሙ ከማሳው
ይዘዋወራሉ፡፡
ድንገት ከቅርብ ርቀት ለቅሶ ተሰማ፡፡ የለቅሶን ምንነት እማያውቁት
ሁለቱ ጥንዶች በሚሰሙት ድምጽ አንጀታቸው ተላውሶ በድንጋጤ
የድምጹን ምንጭ እያነፈነፉ ፍለጋ ጀመሩ፡፡
ድምጹን ካደመጡበት ስፍራ ሲደርሱ ኢብሊስን ቁጭ ብሎ
ሲያለቅስ አገኙት፡፡ሲመለከታቸው ለቅሶውን ያባብሰው ጀመር፡፡
‹‹ምንድነው የሚያስለቅስህ›› ብለው ጠየቁት፡፡
‹‹እንዲ ስትዝናኑ አይቼ በጣም ተደሰትኩ ፤ ግና መሞታቹን
ሳስበው አልቻልኩም አስለቀሰኝ፡፡›› ብሎ መለሰላቸው፡፡
‹‹ለምንድነው ምንሞተው›› ብለው ጠየቁት፡፡
‹‹እንዳትሞቱ የመዘውተርያን ሚስጥር ላመላክታቹህን?›› ብሎ
ጠየቃቸው፡፡
‹‹አዎን›› አሉት፡፡
‹‹ጌታቹህ ይህችን ቅጠል እንዳትበሉ ያስጠነቀቃቹህ በዚህ ደስታ
እንዳትዘወትሩ ነው ፤ ወላሂ ይችን ቅጠል ከበላቹህ ሞት
አያገኛችሁምም ፤ አዚሁ ዘውታሪ ትሆናላቹም›› አላቸው፡፡
በአላህ ስም የማለ ይዋሻል ብለው ስላልገመቱ መኃላውን
አምነው ቅጠሏን ጎረሱ፡፡ ልብሶቻቸው ከላያቸው መብረር ጀመረ ፤
ከጌታቸው የተቸራቸውም የክብር ዘውድ ከራሳቸው ላይ በረረ፡፡
አላህም ተቆጣ ከራህመት ግዛቱም አባረራቸው፡፡ በማያውቁት
ፍጠረተ አለም ውሰጥ መግቢያ መውጫ ቢጠፋቸው በእርቃኑ
ሰውነታቸው ቅጠላትን እየለጣጠፉ በጀነት ሀገር ይባክኑ ጀመር፡፡
አላህ በቁጣ ባህሪው በተገለጸበት በዝያ አሰፈሪ ትዕይንት መሀል
አደም ድንገት ከዐርሽ ላይ ከአላህ ስም ጋር የተቆራኘ አንድ ስም
ተጽፎ ተመለከተ፡፡
‹‹ሙሀመድ›› ሰዐወ
አደምም እንዲህ ሲል ጠየቀ-‹‹ጌታዬ! ይህ ሙሀመድ ማን ነው››
አላህም አለ-‹‹ይህ ልጅህ ነው››
አደምም እንዲህ ሲል ተዋደቀ-‹‹ጌታዬ በዚህ ልጅ ክብር ይሁንብህ
ወላጁን ይቅር በለው››
አህም አለ-‹‹አደም ሆይ ሙሀመድ እኔ ዘንድ ክቡር ፍጡር ነው ፤
ሙሀመድን ይዘህ ስለ ሰማያት እና ስለ ምድር ፍጠረታት
ብታማልደኝ አማልድሀለሁ››
አደም እና ሃዋም በፈፀሙትም ሀፅያትም ተፀፅተው እንዲህ
በማለት አላህን ይማፀኑ ጀመር፦" ጌታችን ሆይ! ነፍሶቻችንን
በደልን፡፡ አንተ ለእኛ ባትምር ባታዝንልንም በእርግጥ ከከሳሪዎቹ
እንኾናለን"
አላህም ወደ ምድር እንዲወርዱትዕዛዙን አስተላለፈ እንዲህም
አላቸው፦" ከፊላችሁ ለከፊሉ ጠላት ሲኾን ውረዱ፡፡ ለእናንተም
በምድር ላይ እስከ ተወሰነ ጊዜ ድረስ መርጊያና መጠቀሚያ
አላችሁ።
በእርሷ/በምድር ላይ ትኖራላችሁ፡፡ በእርሷም ላይ ትሞታላችሁ፡፡
ከእርሷም ውስጥ ትወጣላችሁ"
ይቀጥላል...

ምንጭ፦
ﺍﻟﺒﺪﺍﻳﻪ ﻭﺍﻟﻨﻬﺎﻳﻪ
ﺍﻟﻜﺎﻣﻞ ﻓﻲ ﺍﻟﺘﺎﺭﻳﺦ

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

15 Feb, 17:36


....በተስፋ እራመዳለሁ🌸

እኔ ግን ያልገባኝ - ህይወት ለምን ከበደች
በዚህ ቢሏት በዚያ - በርግጋ የሮጠች
የድሃን ተስፋን - በእጇ የነጠቀች
እውነት እላችኋለሁ - አረመኔ ነች
ስኬትና ስህተት - እንዲሁም ውድቀት
ተደበላልቀው - አንድላይ ነው የሆኑት
ግራ ቢገባኝ ነው - እንዲህ መጠየቄ
ለዛም ነው የፃፍኩት - የሰው ብዕር ነጥቄ
እንዴት ልለያቸው - አንዱን ከአንዱ መንጥቄ
ስኬትን እዤ ልሮጥ - ከውድቀት ሰርቄ
ህይወት አልገፋ ብላ - ልክ እንደ ተራራ
ስንቱን አንገት አስደፋች - አስባለችው ተራ
ስንቱ ተንገላታ - ደርሶበት መከራ
በሐሳብ ሰመመን - ስንቱ ተሰበረ
ስንቱ ተሰቃየ - ስንቱ ሄዶ ቀረ
ክንፍ ሳይኖረው - በሰማይ በረረ
ምንም ሳይስቅ ከርሞ - ስንቱ ተቀበረ

በአስቸጋሪ ፈተና - በውጣውረድ መሃል
እድል ተቀምጣ - ሊሆንም ይችላል
በዚህች ምድር - ሁሉም ነገር ያልፋል
ከትላትናው እለትም - ዛሬ ይሻላል
በዛሬው ጨለማ ቀን - ብርኃን ይተካበታል
እንደዚህ እያልኩኝ - እራሴን አፅናናለሁ
እተክዝና ለአፍታ - ህልም አልማለሁ
መሄጃዬን ሳላቅ - ዝምብዬ ሮጣለሁ
ግራ ይግባት ህይወት - ድንብርብሯ ይውጣ
እያዘለለ ያፍርጣት - ልክ እንደ ፌንጣ
እኔ ተስፋ አልቆርጥም - የመጣ ቢመጣ
ተስፋ ባለመቁረጤ - በማንም አልቀጣ
አረ በጊዜ ትጃጅ - ፀጉሯ ይመለጥ
በሙርኩዝ ትግባ - ሰውነቷ ይላላጥ
ሐቅን አርግዛ - እውነትን ታምጥ
ያኔ እንደሰት - እንቦርቅ ያለቅጥ

በቃ እንዲህ ሆነ - እንዲህ ነው ነገሩ
አቅጣጫው ብዙ ነው - የህይወት መስመሩ
ኮድ ሁኖ አረፈ - የኑሮ ቀመሩ
ተደብቆ ቀረ - የህይወት ሚስጥሩ
ሽርፍራፊ ሆነ - ወጣ ስብርብሩ
በሻማ ልፈልግ - ቤት ይሆን በሩ
ሰምቼ ነበር ግን - ሰዎች ሲያወሩ
እና ብሰማስ ወዴት - እሄዳለሁ
እኮ ንገሩኝ - ወዴትስ አመራለሁ
እና ምን ላመጣ - ወዴትስ ገባለሁ
ተናጋሪ በበዛበት ዘመን - እኔ ዝም እላለሁ
ብሶቴን ደምሬው - ለኑሮ አካፍለዋለሁ
ብሽቀቴን ቀንሼው - በሐሳብ እጓዛለሁ
በብጣሽ ወረቀት - ፅፌ ሰርዛለሁ

እንደ ጠዋት ፀኃይ - እንደ ጠዋት ጤዛ
መለየት ቢያቅተኝ - ህይወትም ተላዛ
የኖሮን ጣዕም - ቅመሙን አፍዝዛ
የኔንም አይምሮ - በመርፊ አደንዝዛ
ግራዬን ትላለች - በቀኜ ተይዛ
ማሽተት አቅቷት ነው - የኑሮን መዓዛ?
ለካስ እንደዚያ ነው - እኔንም ቀልሳ ደልዛ
ግራ ሲገባት በዚህ - ቀኝ ስትሆን በዚያ
ጠዋት ተኮማትራ - ከሰዓት ፍንጥዚያ
በማለዳ ቦርቃ - ከሰዓት ተኮማትራ
ደስታን ፍለጋ - ታክሲ ተኮናትራ
በቃ ህይወት እቺ ናት - የገባት ግራ
ጨልማ ውላ - አመሻሽ ላይ የምትበራ
ሺያሻት ምታመልጥ - በቤቱ ወጋግራ
ህይወትን በዚህ መልክ - በጥሞና እያነበብኩት
መፃፉ ሳያልቅ - በድነገት ዘጋሁት

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

15 Feb, 02:01


.
.
በእድሜ የገፉ አዛውንት ባልና ሚስት በወጣትነት ዘመናቸው ያሳለፉትን የፍቅር ጊዜያት ለማስታወስ ይፈልጉና "ባልየው
ነስሩ ሱቅ አጠገብ ያለው ጎረምሶቹ የሚቀመጡበት  ድንጋይ ላይ ቁጭ ብዬ እጠብቅሻለሁ ... አንቺም ተሽሞንሙነሽ በአጠገቤ ስታልፊ ለክፌ አስቆምሽና  እጅሽን ይዤ  እያሽኮረመምኩ አዋራሻለሁ " ይላታል  ሚስትም  በደስታ ተውጣ ትስማማለች ።
.
ባል ድድ ማስጫው ላይ ለሁለት ሰዓታት  ተቀምጦ ቢጠብቅም ሚስት የውሃ ሽታ  ትሆናለች ።  ይሄኔ " ምን አጋጥሟት ይሆን ?" በማለት ወደ ቤቱ ይመለሳል....
ቤቱ ሲደርስም ያልጠበቀውን ነገር ተመለከተ ሚስት አቀርቅራ ትንሰቀሰቃለች፣
ጠጋ ብሎ ምን እንደሆነች ሲጠይቃት
" እናቴ ከቤት መውጣት ከለከለችኝ "
🤣🤣🤣

Wave-@ASMYN1
.

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

14 Feb, 18:21


ከኛ የሚፈለገው
~

ከኛ የሚፈለገው የቀልባችን መሰበር እንጂ የሰዉነት መሰበር አይደለም፤ የልብ ማጎንበስ እንጂ የአካል ማጎንበስ አይደለም፣ የነፍስ መታዘዝ እንጂ የጡንቻ መታዘዝ አይደለም፣ የዉስጥ መተናነስ እንጂ የገላ ማስመሰል አይደለም፡፡ 

አላህ (ሱ.ወ.) ቀልባቸዉን ለርሱ ብለው ከሰበሩ ሰዎች ጋር ነው፡፡ በትዕቢትና ጉራ አትለምኑት፡፡ በመመፃደቅና ፉከራ አትጠይቁት፣ በታይታና ጥብረራ አታምልኩት፡፡

ሲደክማችሁ፣ ሲያማችሁ፣ ግራ ሲገባችሁ … ወደማንም ዘንድ ከመሄዳችሁ በፊት ወደሱ ሂዱ፡፡ ለአንድም ሰው ችግራችሁን ከመንገራችሁ በፊት ለሱ ንገሩ፡፡ ለማንም በሽታችሁን ከመግለጣችሁ በፊት እሱ ዘንድ ታከሙ፡፡ ችክ ብላችሁ ለምኑት፤ ከልብ ሆናችሁ ጠይቁት፡፡ ድህነታችሁን፣ ፈላጊነታችሁን፣ አቅመቢስነታችሁን በራሣችሁ ላይ መስክሩ፡፡

እንዲህ እንዲህ በደልከኝ፣ ጣልከኝ ብላችሁ መክሰሱን ተዉና ቀርባችሁ አዋዩት፡፡ ይኸው ሁሉን ትቼ አንተ ጋ መጣሁ በሉት፡፡ እሱን ዉደዱ፣ ለሱ ዉረዱ፣ ለሱ ተዋረዱ

ደካሞች ናቸዉና ወደ ሰዎች የሚያደርሰዉን በር ሁሉ ዝጉ ወደሱ የሚያስገባዉን በሰፊው ክፈቱ፣ ሳታፍሩና ሳትፈሩ ወደርሱ ግቡ፣ ይኸው ወንጀሌ፣ ይኸው እንከኔ ይኸው ዉርደቴ፣ ይኸው ክፋቴ፣ ይኸው ጥፋቴ በሉት

አላህ ዘንድ ተናዞ መውጣት ከሁሉ በሽታ መዳን ነው
አላህ ይጠብቃችሁ ወዳጆቼ!  

ጠቃሚ መስላ ከታየቻችሁ ይህችን ምክር አካፍሉ። ከሚደርሰኝ ምንዳም አንድም ሳይጎድል ተካፈሉ

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

14 Feb, 02:38


.
ዱንያ እና አኼራ ልክ ሁለት ሚስቶች
እንዳሉት ወንድ ናቸው
አንዷን ሲያስደስት ሌላኛዋ ትቆጣለች!
.
.      በዚህ ሀሳብ ትስማማላቹ?

         Wave- @ASMYN1
.

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

13 Feb, 18:15


السلام عليكم ورحمة الله وبركاته ዉዶቼ የጥያቄ እና መልስ ዉድድሩ ተጀምሯል በርቱልኝ አሏህ ይርዳችሁ

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

12 Feb, 18:30


አዝናኝ የፍቅር ጥቅሶችን ለምን አላቃብላችሁም? የባላችሁ/ ሚስታችሁ ናፍቆት ላንገላታችሁ ላኩላቸው። አትስነፉ ፍቅራችሁን አድሱ ....


1- ምርጡ ልብ ያንተ ልብ ነው፡፡ ምርጡ ንግግርም ያንተ ሹክሸታ ነው፡፡ ምርጡ ሕይወቴም አንተን መውደዴ ነው፡፡፡


2- ለሰዎች አንድ ሰው ነሽ፡፡ ለኔ ግን ዓለሜ ነሽ ዉዴ፡፡


3- ነፍሴን እንደማልረሳው ሁሉ፣ በነፍሴ ዉስጥ ያለችዉን ነፍስም አልረሳም፡፡ ነፍሴ ሆይ እንዴት ነሽ?፡፡
💚💚💚💚💚💚

4- ከብዙ ተወዳዳሪዎች መካከል መርጠን በፍቅር ስለተቀበልንህ እንኳን ደስ አለህ፡፡  ቀልቤ አንተ የተመደብክበት ዩኒቨርስቲ ነው፡፡ የትምህርት ክፍሉ "ፍቅር" ይሠኛል፡፡ ተመርቄ እወጣለሁ ብለህ ፈጽሞ እንዳታስብ፡፡

💜💜💜💜💜💜💜💜💜

5- ዝናብ የክረም ስጦታ ነው፣ ፀሐይ የበጋ ስጦታ ናት፣ አበባ የፀደይ ስጦታ ናት፡፡ አንቺ ደግሞ የኔ ስጦታ ነሽ ፍቅሬ፡፡
💘💘💘💘💘💘💘💘💘


6- ሚሊዮን ሰው ቢወድህ እኔ አለሁበት፤ አንድ ሰው ቢወድህ እሷ እኔ ነኝ፣ አንድም ሰው ካልወደደህ ስወድህ የኖርኩት እኔ ሞቼ እንደሆነ እወቅ፡፡
💔💔💔💔💔💔💔💔

7- ብቸኝነት ሲናፍቀኝ ወዳንቺ እመጣለሁ፣ ዝም ማለት ስፈልግ ካንቺ ጋር አወራለሁ፤ ብዙ ነገር ባልችል እንኳን አንቺን መውደድ እችላለሁ፡፡
💟💟💟💟💟💟💟💟

8- እናትሽ ንብ ሳትሆን አትቀርም ዉዴ!፡፡ አንችን የመሰለች ማር አበረከተችልኝ፡፡

💕💕💕💕💕💕💕💕💕
9- እባክሽን ትንሽ ላስቸግርሽ፡፡ ሳቂልኝና ዓለም ሁላ ትሳቅልኝ፡፡

አንድ ማስታወሻ ልመርቅ የኔ ዉድ 💞


10- ወንድ ልጅ “መከበር እፈልጋለሁ” ተብሎ የተፃፈበት ቆዳ ነው፡፡ ሴት “እንክብካቤን እሻለሁ” ተብላ የተፃፈባት ብርሃን ናት፡፡ ባልሽን አክብሪ ይንከባከብሻል፡፡ ሚስትህን ተንከባከባት ታከብርሃለች፡

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

12 Feb, 15:00


አንድ ሰው ከሚስቱ ጋር መቀለድ ፈልጎ ነው አሉ፤ እንዲህም አላት፦"ፈጣሪ አንቺን ቆንጆ አድርጎ ፈጥሮሻል ነገር ግን ጭንቅላት የለሽም የማሰብ አቅም ጎድሎሻል!"

እሷም፦“ፈጣሪ እኔን እንድትወደኝ ውብ አድርጎ ፈጠረኝ፤ አንተን ለመውደድ ደሞ የጭንቅላት ጉድለት ጨመረልኝ..!”🙊
                    ተጨማሪ ለማንበብ ይቀላቀሉ!
             
                          Wave @ASMYN1

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

10 Feb, 17:27


አላመልካቸውም

ከፍጡራን ሁሉ ቢልቅ ውዴታቸው
ከሰው አስበልጨ ምንም ብወዳቸው
ልቤ ቢሽመደመድ ለውዱ ፍቅራቸው
አይኔ እንባ ቢያረግፍ ሲወራ ሲራቸው
ሰለዋት ባወርድ ሲጠራ ስማቸው
ጌታዬ ቢያዘኝም እንድታዘዛቸው
ያሉትን በሙሉ እንድቀበላቸው
ፍላጎቱ አይደለም ቢጤ እንዳደርጋቸው
ውዱ ነቢይ(صلى الله عليه وسلم)
ምንም ብወዳቸው አላመልካቸውም
በአሏህ መብት ላይ አላጋራቸውም
ብለውን የለም ወይ ከፍ ከፍ አታድርጉኝ
መልዕክተኛውና የአሏህ ባሪያ ነኝ
ምክርን ሲመክሩ ለውድ ልጃቸው
ከዱንያ ጠይቂኝ ከምትከጅያቸው
ግን ከአሏህ ዘንዳ ምንም አልጠቅምሽም
ነፍስሽን አድኒ እኔ ላንች አልሆንም
ታዲያ ይህን ካሉ ካወሩ በኃላ
ለምን ይሆን ከቶ የምንለው ችላ???
ያ በኒ አደም ሆይ ተነስ ተኝተሀል
ከሸሪዓው ትዕዛዝ ብዙን ርቀሀል
ከቁርዓን ሀዲስ ስሜትህ ገዝቶሀል
ተመለስ ተመለስ ሀቁ ይሻለሀል
ሽርክን አታጣጥም ሀጃህም ላይሞላ
ለሸይጧን ማጎብደድ ይጎዳሀል ኃላ
በጀሀነም እሳት አካልህ ሲበላ
በቁጭት ተሞልተህ ጣትህን ብትበላ
እንባህ ጎርፍ ቢሆን ባህሩን ቢሞላ
ምንም አይጠቅምህም ዛሬ ካልተመለስክ
ዒባዳን በሙሉ ለአሏህ ካላረክ
ከአሳማሚው ቅጣት ማንም አያድንህ
ስቃዩ ብርቱ ነው ሞት እንኳን አይገድልህ
አይንህ እያየ ነው ፍርዱ የሚሰጥህ
ይልቁን
አሏህን እንገዛ ምንም ሳናጋራ
ከፊቱ ስንቆም ከሚገባን ግራ፡፡

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

09 Feb, 21:52


መንታ መንገድ የተሰኘው እጅግ በጣም ተወዳጅ ልቦለድ ታሪክ እነሆ ተጀምሯን!

ይህን መሳጭ ታሪክ ለማንበብ ይቀላቀሉን!
Wave-@ASMYN1

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

09 Feb, 18:12


አንዳንዴ “ደከመን” የምንለው በአላህ ሳናምን ቀርተን እንዳይመስላችሁ፡፡ቀዷና ቀደሩንም የማንቀበል ሆነን አይደለም፡፡ ግና ተከታታይ ፈተና ያንበረክካል፣ የሕይወት ዱላ ይጥላል፣ የዱንያ መከራ ይሰብራል

የአላህ መልዕክተኛ ሶልለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም ደዕዋ ለማድረግ ወደ ጣኢፍ በሄዱ ጊዜ ፈጽሞ ያልጠበቁት ከባድ መከራ ነበር ያገኛቸው፡፡ ከእግራቸው ደም እየፈሰሰ፣ አዝነው፣ ተክዘዉና ተሰብረው ጧኢፍን ለቀው ወጡ፡፡ ከባድ ሐዘንና ትካዜ ዉስጥ ገብተው ሠዓሊብ የሚባል ኮረብታ አጠገብ ሲደርሱ ነበር የነቁት፡፡ እዚያም  ሆነው ወደ አምላካቸው እንዲህ በማለት ተመፃኑ

“አላህ ሆይ ኃይል የሌለኛ ደካማ መሆኔን፣ መላም ብልሃትም እንደሌለኝ አንተ ታውቃለህ፡፡ በሰዎች ላይ መብት የለኝም፡፡ የአዛኞች ሁሉ አዛኝ እና የደካሞች ሁሉ ጌታ ሆይ ለማን ትተወኛለህ!? ለሚያጠቃኝ ባዳ ሰው ወይስ የበላይ ለሚሆንብኝ ለጠላት?  ብቻ ያንተ ቁጣ አይሁን እንጂ የቱን ያህል መከራ ቢደርስብኝ ምንም ግድ የለኝም፡፡ ግን ደህንነትህ ይሻለኛል፤ … ” አሉ፡፡

ማዘንና መተከዝ የሰው ልጅ ባህሪ ነው፡፡ ሰው ደካማ ፍጡር ነውና ይደክመዋል፣ ነገሮችን መሸከም ያቅተዋል፣ ሆድ ይብሰዋል፣ አገር ይናፍቀዋል፣ ሀሳብ ከአቅም በላይ ይሆንበታል፡፡

አንዳንዴ ከሀሳብ መብዛት የተነሳ አንዳንድ ጊዜ ቃል እንኳ መተንፈስ ያቅተናል፡፡ የሌሎች ምክር ሁሉ ያስጠላናል፡፡ ይህ የአንድ ሳይሆን የብዙ ሰው ችግር ነው፡፡

ሩሕ ትታመማለች፣ ነፍስ ትደክማለች፣ ሰውነት እጅ ይሠጣል፡፡

አንድ ሰው ራሱን ካስጠላው፣ ከጨነቀው፣ ከደከመው፣ ከሠለቸው … ቀርባችሁ ተረዱት አይዞህ በሉት እንጂ አትቆጡት፣ አታነውሩት አትሳለቁበት፣ በሀሳብ ላይ ሀሳብ አትጨምሩበት፡፡ መደገፊያ ግድግዳ ሁኑት፣ ትካዜውን ተረዱለት፣ ብሶቱን አዳምጡት፣ ችግሩን ጉዳዬ ብላችሁ ስሙት፡፡

አንድ ሰው መጥቶ የጨነቀውን ጉዳዩን ሲነግረን ምናልባት የመጨረሻ አማራጩ ሆነን ሊሆን ይችላል። ስለዚህ ሸክሙን ማራገፍ፣ እንባውን ማበስ፣ ወሬውን ማስጨረስ፣ ቀልቡን  ማከም፣ ሞራሉን መጠገን የኛ ድርሻ መሆን አለበት፡


t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

09 Feb, 02:30


አንድ ሰው ከሚስቱ ጋር መቀለድ ፈልጎ ነው አሉ፤ እንዲህም አላት፦"ፈጣሪ አንቺን ቆንጆ አድርጎ ፈጥሮሻል ነገር ግን ጭንቅላት የለሽም የማሰብ አቅም ጎድሎሻል!"

እሷም፦“ፈጣሪ እኔን እንድትወደኝ ውብ አድርጎ ፈጠረኝ፤ አንተን ለመውደድ ደሞ የጭንቅላት ጉድለት ጨመረልኝ..!”🙊
                    ተጨማሪ ለማንበብ ይቀላቀሉ!
             
                          Wave @ASMYN1

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

08 Feb, 18:41


#እኔ_እና_እኔ


በአንድ እኔነት መሐል ሁለት እኔነት ኑሮኝ
አንዱ እኔን ስማኝ አንዱ እኔን እያለኝ
በሁለት እኔ መሐል እኔ ሁኘ አለሁኝ

እኔ አንድ፡-
ወንጀልህ ቢበዛም ከባህር አረፋ
ርዝመቱ ቢርቅ ከአድማስ ቢሰፋ
ፍፁም አትጨነቅ ከቶ አትቁረጥ ተስፋ
ጌታህ መሃሪ ነው እዝነቱ የሰፋ
ጀነቱም ሰፊ ናት ፈረስ አያስርባት
በምን ሊሞላት ነው አንተ ያልገባህባት
ስለዚህ ዘና በል ከቶም እንዳይጨንቅህ
እድሜህን አጣጥም ዛሬን ዘና ብለህ
ብሎ ይሰብከኛል
ይሸነግለኛል

ሌላኛው እኔ ደግሞ፡-
ወንጀልህ ብዙ ነው ከአድማስ የሰፋ
መልካም ስራህ ትንሽ ከቁጥር ማይገባ
የጌታህም ቅጣት እጅጉን ከባድ ነው
የመማርህ ነገር የማይታሰብ ነው
ስለዚህ ዘና በል ላይቀርልህ ነገር
ዱንያን ተጠቀማት ጀነቱ እንኳን ብትቀር
እያለ በዛቻ ደርሶ ያስጨንቀኛል
ከልቦናዬ ውስጥ ተስፋን ይነጥቀኛል

ይሄው እኔና እኔ እኔ ላይ አድመው
በተስፋና ዛቻ ግራና ቀኝ ቁመው
ያወዛግቡኛል እኔን ሞኝ አግኝተው

በእኔና እኔ መሃል ግራ እንደገባኝ
ምይዘው አጥቼ ቁጭ ብዬ እንዳለሁኝ
በሁለት እኔነቶች ተከብሮ የሚኖር
ያምላኬን ቃል ሰማሁ እንደዚህ ሲናገር
"እኔ መሃሪና ይቅር ባይ ጌታ ነኝ
ቅጣቴም ብርቱ ነው ተዳፍሮ ላመፀኝ"
እያለ እኔነቱን ሲያብራራ ሰምቼ
ባ'ንዱ እኔነቱ(በእዝነቱ) ተስፋዬን ሰንቄ
ባ'ንዱ እኔነቱ (በቀጭነቱ) ፍራቻን አንግቤ
ሁለት እኔዎቼን በአንድ አስታርቄ
አንድ እኔን ፈጠርኩኝ ሁለት እኔን ትቼ

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

08 Feb, 01:39


"ሁለታችንም የጀነት ነን!"

"ዒምራን ቢን ሃሰን ሚስቱ በጣም ቆንጆ ናት።እሱ ግን መልከ ጥፉ ነበር።አንድ ቀን ዒምራን ለሚስቱ "ሁለታችንም የጀነት ነን አላት"። ሚስቱም እንዴት ባክህ? አለችው።ምን መሰለሽ ባለቤቴ እኔ አሏህ አንቺን የመሰለች ውብ ሚስት ስለሰጠኝ አመሰገንኩት፤አንቺ ደሞ እኔን ያህል መልከ ጥፉ ባል ጋር እየኖርሽ ትዕግስት አደረግሽ።ታዲያ አመስጋኝ እና ታጋሽ ሁለቱም የጀነት አይደሉምን! ሲል መለሰላት።"

🔹እነኚህን የመሰሉ አጠር ያሉ እና  መልክታቸው ጠለቅ ያሉ  ታሪኮችን ለማግኘት ይቀላቀሉን

Wave ላይ ቻናላችሁን ለመቀላቀል➡️@ASMYN1

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

07 Feb, 18:22


የሁለቱ ፍቅር ልዩነት  💞
፨፨፨፨፨፨፨፨

ከፍቅርም መካከል እንዲሁ ከመሬት ተነስቶ የሚያበር የሚያከንፍ አለ የሚያንዘፈዝፍ የሚያንሰፈስፍ፣ የሚያቀባዥር ፍቅር አለ ከማይሆን ሰው ጋር የሚያጣብቅ፣ የሚያፋቅር፡፡

ያ ፍቅር መነሻው በሥራ፣ በትምህርትም ሆነ በሌላ አጋጣሚ በተፈጠረ የዕለት ተዕለት ቀረቤታ የተነሳ ሊሆን ይችላል ቅርርቡም ከፍ እያለ ሲሄድ መሳሳብ ይመጣል፡፡ ስህበትም መውጫ ከሌለው አጓጉል ፍቅር ላይ ይጥላል፡፡  ለምሳሌ በሃይማኖት ከማይገናኙት ሰው ጋር፤ አደገኛ ሱሰኛ ከሆነ ሰው ጋር፣ አላህን ከማይፈራ ወንጀለኛ ሰው ጋር፣ በምግባረ ብልሹነቱ ከሚታወቅ ሰው ጋር፡፡

የዚህ ዓይነቱ ፍቅር አዋጭ አይደለም አክሳሪ ነው፡፡ እስልምናም፥ ህሊናም አይቀበለዉም፡፡ እውነት ላይ አልተመሠረተምና፡፡ አዎንታዊም አይደለምና፡፡ ፍፃሜውም ያማረ አይሆንምና፡፡ ወደመጥፎ ሰው የሚመራዉና የሚያመላክተው ፍቅር እንደ አደገኛ አውሬ ሊጠነቀቁት የሚገባው ነው መድኃኒት አይደለም መርዝ ነው፡፡ ፈዉስ አይደለም መከራ ነው፡፡ ሕይወት አይሆንም ሞት ነው፡፡

ስለሆነም ወንድም እህቴ .... ሳይገቡበት ቶሎ መውጣት፣ ሳይቀጥሉት ቶሎ መቁረጥ፣ ሳይሄዱበት ቶሎ መንቃት ግድ ይላል፡፡ የዉሸት ፍቅር ነውና፡፡

እውነተኛ ፍቅር እዉር አይደለም፡፡ ማየት የተሣናቸዉና የሚታወሩት አፍቃሪዎች ናቸው፡፡ በእዉር ድንብር ተጉዘው፣ ሆነብለዉና ፈልገው ታዉረው የፍቅርን ሥም አጠለሹ፡፡ ነጭ እና መልካም የሆነዉን ታሪኩን አበላሹ

እውነተኛ ፍቅር ያያል፣የሚጠቅም የሚጎዳዉን ያውቃል፣ ጥሩና መጥፎን ይለያል፣ የሚያተርፍ የሚያከስረዉን ያሰላል፡፡
 
እውነተኛ ፍቅር ምክንያታዊ ነው ዓላማና መርህ ያለው ነው፡፡ በደመንፈስ አያጓጉዝም፡፡ በአጉል ስሜት አይነዳም
አርቆ አስተዋይ ነው፡፡ ዐይኑ እያየ ከማይሆን ነገር ላይ አይወድቅም

ፍቅር ፍቅር ስለተባለ ብቻ ፍቅር አይሆንም፡፡ በፍቅር ሥም የሚጠሩ ግና ፍቅር ያልሆኑ በርካታ “ፍቅሮች” አሉ
በስመ ፍቅር የተነሣ ብዙዎች ከያዙት ትክክለኛ መንገድ ወጥተዋል፡፡ ዓላማቸውን ስተዋል፡፡ ከመስመራቸው ተንሸራተዋል እምነታቸዉን ለውጠዋል፡፡ ሲጀመር ለአላህ ብለን እንጂ ለሰው ብለን የምንለዉጠው ሃይማኖት መኖር የለበትም

እውነተኛ ፍቅር እውነት ነው፡፡ አዛኝ ነው
በጎ ነው፡፡ መልካም ነው፡፡ ቅን ነው፡፡ ግልጽ ነው፡፡ ፊትለፊት ነው፡፡ ሚስኪን ነው፡፡ ፍፁም በደግነት የተሞላ ነው፡፡

እውነተኛ ፍቅር የጀርባ አጀንዳ የለዉም
ድብቅ ሀሳብ፣ ዓላማና ፍላጎት የለዉም ቀልቡን አስቀምጦ በምላስ አያወራም ዉስጡና ዉጪው ተመሳሳይ ነው አይመስልም ያስመስልም

እውነተኛ ፍቅር ቁምነገረኛ ነው ሐላልን አጥብቆ ፈላጊ ነው፡፡ ጊዜያዊ ጥቅምን አስቦ አይንቀሳቀስም፡፡ ወረት አያጠቃዉም፡፡ ማግኘት አያርቀዉም ማጣት አያቀርበዉም፡፡ ጥቅም አይለውጠዉም፡፡ ያሰበዉን ባገኘ ጊዜ የሚሸሽ የሚፈረጥጥ አይደለም

እውነተኛ ፍቅር ለሐላል ኗሪ ነው፡፡ ለሐላል ተገዢ ነው፡፡ በሐላል ተብቃቂ ነው፡፡ ለሐላል ሟች ነው
እውነተኛ ፍቅር በሐራም አይደሠትም ለሐራም አይስገበገብም፡፡ ሐራም አያሳድድም፡፡ በሐራም አይዝናናም በሐራም አይረካም
እውነተኛ አፍቃሪ ለራሱም ይጠነቀቃል ላንቺም ያስብልሻል፡፡ 💔ለራሱ ስሜት ሲል ሕይወትሽን አያበላሽም፡፡ ከመንገድሽ አያሰናክልሽም፡፡ ከዓላማሽ አያስቀርሽም፡፡ በሐላል ካልሆነ አይቀርብሽም፣ ለሐላል ካልሆነ አያስቸግርሽም፡፡ ሲያወራ የምሩን ነው፡፡ ሆዱና ምላሱ ተመሳሳይ ነው፡፡ ሺህ ጊዜ አንድን ነገር ብትጠይቂው ሺህ ጊዜ መልሱ ተመሳሳይ ነው፡፡ 

እናም እህቴ … ከዉሸት አፍቃሪዎች ተጠንቀቂ፡፡ … መሰሪ በዝቷልና ንቁ እና ብቁ ሆነሽ ተገኚ፡፡ ዉሸታሞች ምላሣቸው ቅቤ ነው፡፡ ዉስጣቸው ግን ጩቤ  ነው፡፡ ስለ ስሜታቸው እንጂ ስላንች ግድ የላቸውም እስኪያሳምኑሽና እስኪጥሉሽ እንቅልፍ የላቸዉም፡፡ ሰው ለሐራም እንዴት እንቅልፍ ያጣል በረቢ፡፡

ዉሸታሞች በሰው የተመሰሉ ሸይጣኖች ናቸው፡፡ እልም ያሉ የሰው ሸይጣኖች ሲበዛ ራስ ወዳድም ናቸው ስለራሣቸው ሥጋ መርካት እንጂ ስለሌላው መርከስ አይገዳቸዉም፡፡ ቀድሞዉኑ ተነጅሰዋልና ሌላዉንም መነጀስ ነው ልማዳቸው ማን ወድቆ ማን ይቀራል፤ ማን ፀድቆ ማን ይከስማል … ነው መፈክራቸው
ዉሸታሞች የሚያስቡት ስለራሣቸው ብቻ ነው፡፡ ስለማንም እና ስለምንም ዕድልና ዕጣፈንታ ግድ የላቸዉም፡፡ የሚፈልጉትን እስኪያገኙ ድረስ የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም፡፡ ያላንዳች ሀፍረት በዉሸት ይምላሉ፣ የሌላቸዉን አለን፣ ያልሆኑትን ነን ይላሉ፡፡ 
ዉሸታሞች ማቆላመጥና መለማመጥ ያበዛሉ፡፡ እስክትደክሚና እጅ እስክትሠጭ ድረስ በጥረታቸው ይቀጥላሉ
ንግግራቸው በእጅጉ የተጠና ነው አንደበታቸው ልብ የሚሰነጥቅ ስል ነው የሰዉን ሥነልቦና ያውቃሉ፡፡ የሚጠቀሙትን ቃል ይመርጣሉ፡፡ እውነት የሚመስል፣ የሚሸረሽርና አቅም የሚያሳጣን አባባል ይጠቀማሉ፡፡  እንኳንስ ሰው ድንጋይ ያቀልጣሉ፡፡ ዉሸትን እውነት ያስመስላሉ ዘዴ እየፈጠሩ ያታልላሉ በዉሸት ቃል ይገባሉ፡፡ የማይፈጽትን ያወራሉ፡፡ ለሰው ያዘኑ መስለው ይቀርባሉ፡፡ የዋህ መስለዉም ያዘናጋሉ፡፡ ምንም እንደማያውቁ ሆነው ይተዉናሉ
ሐራምን ስለተላመዱ ሐራም ጉዳያቸው አይደለም፡፡ ቀልባቸው ደርቋልና አላህን አይፈሩም፡፡ ኃጢኣት መሆኑን እያወቁ ትልቁን ነገር ትንሽ ፣ ከባዱን ነገር ቀላል ያስመስላሉ፡፡ ቀለል አድርገሽ እንድታዪው እንዳትጨነቂም ይሰብካሉ
ዉሸታሞች ሐላል ነገር ሞታቸው ነው በአጀንዳቸዉና ፕሮግራማቸው ዉስጥ “ሐላል” የሚል ቃል የለም፡፡ ኑሯቸው ግስብስብ ነው፡፡ ሐያታቸው የጨቀየ ነው መቼ እንደሚያገቡ እነርሱ ራሣቸው አያውቁም፡፡  ትዳር ሲነሳ ሞት የታወጀባቸው ያህል ይደነግጣሉ የሆነ ያልሆነ ምክንያት ያቀርባሉ የትዳር ነገር ያቅለሸልሻቸዋል፣ ሀሳቡ ራሱ ይጣላቸዋል ወደላይ ወደላይ ይላቸዋል
ወደደኝ፣ ለመነኝ፣ አባባለኝ፣ አደነቀኝ … ብለሽ አትዘናጊ፡፡ ላንች ብሎ ሳይሆን ለራሱ አስቦ ነው፡፡ በወጥመዱ ጠልፎ ሊጥልሽ ነው፡፡ የፈለገዉን እስኪያገኝ ብቻ ነው ማባበሉና ማሳዘኑ፡፡ ቢያሳዝንሽም አትመኚው፣ ቢጨቀጭቅሽም ጆሮም ልብም አትስጪው፡፡ አላህን ከምታስቆጪ እሱ ቢቆጣብብሽ ይሻላል፡፡  አንች እኮ ማለት ለኔ “ሀ ነሽ፣ የመጀመሪያዬ ነሽ” ልልሽ ይችላል፡፡ በእጁ ካስገባሽና ያሰበዉን ካደረገ በኋላ “ሆ” ነሽ” ማለቱ አይቀርም የዚህ ሁሉ ሩጫው ፍፃሜ እስከ አልጋ መሆኑን እወቂ፡፡ ከዚያ በኋላ ልጁ የለም በሰፈርሽ ዝር አይልም፡፡ ዘመኑ እንዲህ ሆኗል፡፡ እንደ ሃይማኖትሽ አስተምህሮ እንጂ እንደዘመኑ አትሁኚ፡፡

ዉሸታም አፍቃሪ ትክክለኛ ልቡ አይገኝም እውነተኛ ሕይወቱም፣ እውነተኛ ማንነቱም አይታወቅም፡፡ ሲያደባና ሲያሴርልሽ ከኖረ በኋላ አድክሞ አድክሞ የጣለሽ ቀን በራሱ ብልሃትና ዘዴ ይደነቃል፣ ራሱንም እንደ ጀግና ያደንቃል፣ በዉስጡ ይስቅብሻል ከሌሎች ጋር ይሳለቅብሻል፤ በቁጭት ያነድሻል፡፡ ከፀፀትሽ እንዳትወጪ ያረግሻል፡፡ 

ያኔ ታዲያ ከብዙ ጅንጀና በኋላ የወደቅሽ ቀን … ከወደቅሽበት ቀን አንስቶ እንደ ርካሽና ተራ ሰው ያይሻል፡፡ ቀኑና ሰዓቱን ይፅፍልሻል፡፡ ራሱን እንደ ፃዲቅ አንችን እንደ ኃጢአተኛ ለማድረግም ይሞካክረዋል፡፡ ከዚያ በኋላ አንችን ለማየት እንኳን ይጠላል፡፡ ምክንያት እየፈጠረ ሊያገኝሽ እንዳልደከመ ሁሉ አሁን ደግሞ ምክንያት እየፈጠረ ይሸሻል

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

07 Feb, 18:22


በኃጢኣት አብረው የወደቁ ሰዎች ፈጽሞ አይዋደዱም፣ ጥፋታቸዉን ያውቃሉ ወንጀላቸዉን ይረዳሉ፡፡ ስለዚህ አብረሽው ከወደቅሽ ቀን ጀምሮ ከዐይኑ ወድቀሻል ተጠልተሻል፡፡ ቢቀርብሽም ለጥቂት ቀናት ለማስመሰል ያህል ነው፡፡ ከዚያ በኋላ ጉድ ተሠራሁ ብሎ ብትጮሂ ዋጋ የለዉም ወንዶችን ሁሉ መራገምና መቆጣትም ቁኑት ማድረግም ዉጤት አይኖረዉም ወደሽና ፈቅደሽ  ከተደፋሽ በኋላ ቢረግጡሽ ቢያዋርዱሽ አይክፋሽ መሰተርያሽን በራስሽ እጅ ገልጠሻልና በራስሽ እዘኚ፡፡ ስህተትሽንም እመኚ ቀድሞዉኑ ነበር በትልቁ መጠንቀቅ፡፡ አሁን ለቅሶ አይጠቅምም፡፡ ባይሆን ከዚያ ስህተት የምትወጪበትን መንገድ ፈልጊ ዳግም ላለመሳሳት ሞክሪ፡፡ በድርብ ስህተትም ፈጣሪሽንም አታስቆጪ ተመለሺ፡፡ አላህ ተመላሾችን ይወዳልና፡፡

እባክዎ ሼር ያድርጉ

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

06 Feb, 17:28


ምንኛ ያማሩ ሰዎች ናቸው
ድንቁ ነብይ ከነ ሶሀቦቻቸው
ያንሳቸዋል አይኔ ቢያነባላቸው
ሲመሽ ሲነጋ ሁሌ ባወድሳቸው
ያንን ገድል ያንን ፊትና
ሲወጡት በተውሂዱ ጎዳና
ለኛ ሲሉ ስንቱን ሆኑ
በየሀገር ሲበተኑ
ሀብት ንብረታቸውን ጥለው
ሳይሰስቱ ህይወታቸውን ሰውተው
በዛ በበረሀ ተጋድለው
የተውሂድን ባንዲራ አንግበው
ሲያስረክቡን ያንን ትልቅ አማና
አደራ ሲሉን እንድንጓዝ በሱና
እንዳይጠፋን አመላክተው
ሽርክ ካለበት አጥፍተው
ለጨለማው ብርሀንን አብርተው
ሄዱ ዑመቴ ዑመቴ ብለው
ሳያዩን ለእኛ አልቅሰው
ባዛኝ አንጀታቸው እኛን ናፍቀው
ግና
እኛም አደራን በላነው
ከሱና ቢድዓን አስቀደምነው
ንቁ ያዑመተ ነብይና
እንሰብሰብ በተውሂድ በሱና
ያጠፋነው ትልቅ አማናን ነውና.....

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

05 Feb, 18:34


ሂሻም ኢብን ዐብዱል መሊክ...ይህን ሰው ታውቃላችሁ!!!? ኑ ዐጀብ እንመልከት...።

ሂሻም ማለት በታቢዒዮች ዘመን የሙስሊሞች መሪ የነበረ ንጉስ ነው። አንድ ቀን ይህ ንጉስ ለሀጅ ወደ መካ መጣ'ና፦"አንድ ሰሀባ አምጡልኝ" ሲል አዘዘ።

ነዋሪያኑም፦"ሰሀባዎች ሁሉ ሙተው አልቀዋል" በማለት መለሱለት።
ሂሻምም፦"እሽ አንድ ታቢዒይ(የሰሀባዎች ደረሳ) አምጡልኝ" ሲልም አዘዘ።

ይህን ግዜ ጣዉስ አልየማኒ የተባለውን ሊቅ ታቢዒይ ይዘውለት መጡ። ከዝያም ይህ ጣዉስ የተባለው ታቢዒይ ንጉሱ ወደሚገኝበት ክፍል በመዝለቅ ጫማውን አውልቆ፦"አሰላሙ ዐለይኩም ሂሻም" ብሎ ገባ።ምንም አይነት የማዕረግም ሆነ የክብር ስም አላካተተም ነበር።

ሁኔታው ንጉሱን አናድዶታል። አንደኛ በክብር ስሙ አሚረል ሙእሚኒን/የምእመናን መሪ ብሎ አልጠራውም። ሲቀጥል ሳይፈቅድለት ነው ቁጭ ያለው፤ ሌላው ደግሞ ፍራሹ መዳረሻ ላይ ነው ጫማውን ሁላ ያወለቀው።

ንጉሱ እንዴት እናቃለሁ በሚል ፍፁም ተናድዶ ይህን ታቢዒይ ለመግደል ቢወስንም በዙርያው ያሉ ሰዎች በተከበረው ሀገር እና በተከበረው ወር መግደል ተገቢ እንዳልሆነ ነግረው አረጋጉት።

ንጉሱም ንዴቱን እንደመቆጣጠር እየሆነ፦" አንተ ጣዉስ!!! ይህን ለመፈፀም ምንድነው ያነሳሳህ?" አለው።

ጣዉስም፦"ምን ፈፀምኩ?" ሲል ጠየቀው።
ንጉሱም ይልቅ ንዴቱ እየተፋፋመ፦"አንደኛ ፍራሼ መዳረሻ ላይ ጫማህን አወለቅክ፣ ሁለተኛ የምእመናን መሪ አላልከኝም፣ ሶስተኛ ወይ በልጆቼ ስም/የእገሌ አባት ብለህ አልጠራኸኝም፣ አራተኛ ደግሞ ሳልፈቅድልህ ዝም ብለህ ቁጭ አልክ...ከዝያም እንዴት ነህ ሂሻም ብለህ አቀለልከኝ" ብሎ ጮኸበት።

ጣዉስም እጅግ ዐሊም ነበሩ'ና እንዲህ ሲሉ መለሱለት፦"ፍራሼ መዳረሻ ላይ ጫማ አወለቅክ ላልከው፤ እኔ እጌታዬ ፊት ለፊት እንኳን 5 ግዜ አወልቀለሁ። አይቀጣኝም ለምን አወለቅክብኝ ብሎ ተቆጥቶኝም አያውቅም።

የምእመናን መሪ ያላልኩህ ባንተ መሪነት ሁሉም ምእመናን ስላልተስማሙበት ነው። ሁሉም ሳይስማማ እኔ ብልህ ውሸታም እንዳልሆን ሰግቼ ነው።

የእገሌ አባት ብለህ አልጠራኸኝም ላልከው አላህ ወዳጆቹን እና ነቢያቶቹን እንኳን <<አንተ ያህያ፣ አንተ ዒሳ...>> እያለ ነው በስማቸው የጠራው። ግን እንደ አቡ ለሀብ ያሉ ጠላቶቹን ሲጠራ <<የለሀብ አባት ሁለት እጆች ከሰሩ>> ስለሚል ነው።

ያለ ፍቃዴ ቁጭ ብለሀል ላልከው ደግሞ ዐሊይ ረዐ እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ<<የጀሀነም ሰውን መመልከት ከፈለግክ እሱ ቁጭ ብሎ ከዙርያው ሰዎችን የሚያቆም ሰው ዱንያ ላይ ተመልከት>> ለዝያ ነው።" አለው።

ይህን ግዜ ሂሻም የተባለው ንጉስም በለዘበ ድምፁ፦"ጣዉስ ሆይ ምከረኝ" አለው።
ጣዉስም፦"የምእመናን መሪ ዐሊይ ረዐ እንዲህ ሲል ሰምቻለሁ <<ጀሀነም ውስጥ ትላልቅ አውሬ ሚያክሉ ጊንጦች እና እባቦች አሉ። እነዚህ እባቦች ለህዝቡ ፍትህን በማያሰፍን ሰው ላይ መርዛቸውን እየረጩ ይነድፉታል>>" ብሎ ትቶት ሄደ።

____
ምንጭ፦
ﻛﺘﺎﺏ ﺍﻷﺣﻴﺎﺀ - ﺍﻟﻤﺠﻠﺪ ﺍﻟﺜﺎﻧﻲ - ﺻﻔﺤﺔ 160

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

05 Feb, 04:54


ለብቻ ማደርን እስልምና ለምን ጠላው? ወይም ከለከለው … የሚለዉን ነገር በማስተንተን ላይ ነኝ፡፡ በተለይ ለላጤና ለላጢት ፡፡
ምናልባት ሰውዬው/ልጅቷ ቢታመም/ብትታመም ዉሃ እንኳን የሚያቀብለው/ላት ሰው ስለሌለ ሊሆን ይችላል፤ ድንገት ትን ብሎት በዚያው ድፍት ቢልስ?፣ ሞቶ ቢያድርስ ማን ሰዉነቱን ያፍታታለታል? እና ለብቻ ማደር መልካም አይደለም ...

ለብቻ በሚያድር ሰው ላይ ፈተናው ብዙ ነው፡፡ የሸይጧንም የነፍሲያም ነፃ የመጫወቻ ሜዳ ነው፡፡ ሲቃዥ የሚያድርም ብዙ ነው።
የሸይጧን ዉትወታው የሚበረታው ብቸኛዉን በሚያድር ሰው ላይ ነው፡፡ ሰው ብቻዉን ሲሆን ነው ለአላህ ያለው ፍራቻ ምን ያህል እንደሆነ የሚለካው። አላህን ካልፈራ የፈለገዉን ነገር ዘና ብሎ መሥራት ይችላል፤ በተለይ በዚህ በቴክኖሎጂ ዘመን ፡፡ ስልክ አጠገቡ ነው፣ ኢንተርኔት ቅርቡ ነው፡፡ ዋትሳፑ፣ ቪዲዮ ኮሉ፣ ኢሞው፣ ቻቱ … ሁሉም ሲጀመሩ ጥሩ ነገር ይመስላሉ፣ ደስ የሚል ስሜት ይሠጣሉ፣ እንጂ መጨረሻቸው አያምርም፡፡ ለባለቤቱም መልካም ነገር ይዘው አይመጡም፡፡

ብቸኝነት ሲደመር ነፃ መሆን ለሸይጣን ዱላ ያጋልጣል፤ መከላከሉም ይከብዳል፡፡ በተቻላችሁ መጠን ብቻችሁን አትደሩ፡፡

ሰው ብቻዉን ሲሆን ደካማ ነው፤ ሶላት መስገድ እንኳን ሊከብደው ይችላል፡፡ ከወንድም/እህቱ ጋር ሲሆን ግን ብርቱ ነው፡፡ በዚህ ዘመን ላይ ና መስጊድ እንሂድ፣ ተነስ ሱንና እንስገድ፣ ና የሆነ ኸይር ሥራ አለ፣ አረ እሱ ነገር ይብቃህ ! የሚለን ሰው ሁላችንም ያስፈልገናል፡፡
እንዴት አደራችሁ ለማለት ነው።

ሼር አድርጉ

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

04 Feb, 16:41


እናትነት የማያረጅ ፍቅር ❤️

ውዷ እማምየ አቤት ፍቅርስ ያንቺ
አይነጥፍ አያረጅ ፈፅሞ አትሠለቺ
በምድር ያየሁት ዘላለም ከራሚ
ከሁሉም የላቀ እጅግ አስገራሚ
እማ እንዳንቺ የለም የሞላው ሙሃባ
በምድር ላይ ለፍቅር ገነት የገነባ
እውነት እናት ባትኖር
ዛሬ በሠዎች ግፍ አንገቴ ሲሠበር
ፍቅር ለናሙናስ የት ይገኝ ነበር?
ሠውን በወደድኩት በፍቅሩ ስቀጣ
ሲጨልም ሲገባ ሲነጋ እየወጣ
ሲዝጎረጎርብኝ እንደ ነብር ቆዳ
በሠው የፍቅር ጥም ብቻየን ስጎዳ
ሁሉንም ጨርሼ ባዶየን እያለሁ
ያንቺን ፍቅር ብቻ አብሮኝ አገኛለሁ
ልክ እንዳንቺ ሆኖ ማን አንጀት ያርሳል
እናት ስትነካ
እንኳንስ የሠው ልጅ ወንዝ ይደፈርሳል
ሳትኖርም የምትኖር በሠጠችው ፍቅር
የሷን ላልጨርሠው አልጀምረው ይቅር
የእናትን ፍቅር
ፈፅሞ አልገልፀውም ከቶም የለኝ አቅም
አባይ ቀለም ሆኖ
በምድር ወረቀት ቢከተብ አያልቅም::

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

04 Feb, 04:59


#መች_ይሆን

ተርቦ ተጠምቶ ለስደት ተገዶ
በድህነት መረብ ህይወቱን ገምዶ
አብሮነትን ጠልቶ ተለያይቶ ኑሮ
ያለመጠለያ ጎዳና ላይ አድሮ
በውጣ ውረድ ጧት ማታ ተጉዞ
የወደፊት ህልሙ ከአይኑ ላይ ደብዝዞ
ጉልበቱን አሟጦ ተስፋውን ጨርሶ
አልሳካለት ሲል አንገት ደፍቶ ለቅሶ
መሆኑን ተረዳሁ የመኖር ትርጉሙ
መች ይሆን የሰው ልጅ የሚሳካው ህልሙ

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

03 Feb, 16:44


🧕 ሚስት
ዉዴ በናፍቆትህ ነው የከሳሁኝ
እኔ የምበላዉ መች አጣሁኝ
አንተን ሲያስብ ነዉ የሚኖረዉ
ልቤ ለማረፍ ያልታደለው


👳‍♂  ባል
መጠራጠሬም አይደል ማዪልኝ ስምኝ ፍቅሬ
እንዳላጣሽ ብዬ ነው ስኖር ቃሌን አክብሬ
እስቲ እኔም እፎይ ልበል ሰምቼ መሃላሺን
ላውጀው ባደባባይ የግሌ መሆንሽን

🧕 ሚስት
የተጫወትነዉን ምንግዜም አልረሳም
እንዲህ ተለያይተን በናፍቆት ብከሳም
አይከዳህም ልቤ ሰው መክዳት አያውቅም
እስኪለያይ ድረስ ከለቅሶ ከሳቅም
ያሳለፍነው ዘመን ደስታን ያየንበት
ተመልሶ ቢገኝ አሁን ምናለበት
 
 👳‍♂  ባል
ፍቅር ሰው ሲገዛ፣ ባይመስል የሚጎዳ
ግን ውስጥ ውስጡን ባታውቂ፣ ያስከፍላል እዳ
በእጄ ስለሆነ፣ የሀሳቤ ቁልፍ
ያላንቺ አይገኝም፣ ሰላም እና እንቅልፍ

🧕 ሚስት
ጭር አለ ፣ አንተን ያጣው ደጄ
እምባ ነው ፣ ከእንግዲህ ወዳጄ
እኔማ ሳላይ ከርሜ
እህህህ እላለሁ ፣ በናፍቆት ታምሜ

👳‍♂  ባል 😁
ቁጣና ኩርፊያዬ፣ ሳቄ ጫዋታዬ
አላስቀምጥ ብሎሽ፣ ፍቅሬ ትዝታዬ
ይቅር ማረኝ ብለሽ፣ ደጄ ካላዋለሽ 
እኔ አይደለሁማ፣ እጄ ላይ ካልጣለሽ

🧕 ሚስት
ፍቅሬ፣ የማይሰለቸኝን ፍቅርህን ፍለጋ
እኔም  ቸኩያለሁ፣ እስክደርስ አንተ ጋ
እንዲህ፣ እየተጨናነክ፣ አታስጨንቀኝ
እስቲ ተረጋጋ ትንሽ ጠብቀኝ
         😁
👳‍♂  ባል
የትዝታዬ እናት የስሜቴ እመቤት
የፍላጎቴ ምንጭ የእድሌ ባለቤት
የምታስታውሺኝ ያለፍኩትን ደስታ
አንቺ ብቻኮ ነሽ የኔ ልብ አለኝታ

🧕 ሚስት 🙈 ሰይድ አቡዘር
ካንዴም ሁለት ሶስቴ፣ ፍቅር ደርሶብኛል
የአንተ ግን ከሁሉም፣ አዲስ ሆኖብኛል
ትንፋሽህን ስርቅ ያመኛል
ታዲያ ምን ይሻለኛል


👳‍♂  ባል ❤️
ከወደድሽኝ  በላይ፣ ልውደድሽ ጨምሬ
አልበቃ ብሎኛል፣ የእስካሁኑ ፍቅሬ
ሺ ግዜ ብወድሽ፣ ባለኝ በሌለ አቅም
ላንቺ ያለኝ ፍቅር፣ ምንም ጊዜ አያልቅም

            እወድሻለዉ
    🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰
     ❤️ጀሊሉ ሀላሉን ይወፍቀን❤️

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

02 Feb, 17:27


#ፈገግታ ሱና ነዉ ፈገግ በሉልኝማ 😂

ልጅቱን ሌቦች አስክደዋት ዋይ ዋይ ትላለች ቦሌ አከባቢ በስፍራዉ የነበሩ ፌድራሎች  ደረሱ ,,,,,

አንደኛዉ   ፌድራል ምን ቢላት ጥሩ ነዉ
ስልክ ቁጥሩን ንገሪኝ እስቲ ልደዉል ይላታል ቁጥሯን  ትነግረዉና ይደዉላል ሲደዉል
ተይዟል   ይላል  ስልኩ
ከዛን  ሲስተር አታልቅሺ በቃ የቴሌዋ ሴትዮ የደወሉላቸዉ ደንበኛ  ተይዟል ብላለች
መናፈረቁን  ትተሽ #እልል_በይ  ይላታል

    ይቺ ስታለቅስ የነበረችዉ ልጅ ለቅሷን ትታ በሳቅ 😂😂 ፈነዳች
ፌድራሉ  ምን ቢል  ጥሩ  ነዉ

  እንኳን   ደስ  አለሽ  እኛ አገር እኮ ሌባ ማምለጥ  አይችልም በሄደበት ቦታ ይያዛል አላት ይባላል 😜😜😜😅😅😅


መልካም ምሽት ይሁንላችሁ ወዳጆቼ

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

01 Feb, 17:47


ከትላንቱ የቀጠለ

በምናብህ ስለህ በልብህ ተመኝተህ እንኳ እማታውቀውን እጅግ ውብ አለም በባለቤትነት ተረክበህ እና በአስደማሚ ዐጀብ ታጅበህ ወደ ዙፋንህ ስትጓዝ ነገረ ዐለሙ በደስታ እንዳይገልህ ሞት ወደዝያ አለም ዝር አይልም።

የምትራመድበት መሬትህ ወርቅ ተጠርቦ ተነጥፎልሀል። ከወርቁ ላይ የተበተነው ሚስክ አከባቢብህን በግሩም መአዛ አውዶታል። ከግራ ቀኝህ የምትመለከታቸው ዛፎች ቅርንጫፎቻቸው በተሸከሙት የበሳሰሉ ፍራፍሬዎች ፍፁም ከመሬት ቀርበው አዘቅዝቀዋል። የወፎቹ ዝማሬ እና የስፍራው ፀጥታ ፍፁም ሰላም ሰጥቶኻል።

የአንዷ ዛፍ ጥላ ስፋቷ ጎበዝ ፈረሰኛን ለብዙ ሺህ አመታት ታስጋልባለች። እንዲህ አይነቱ ዛፍ በግዛትህ እልፍ አእላፍ ይገኛል። የግዛትህ ስፋት ለስሌት ምቹም ስላልሆነ በመደመም ጉዞህን ትቀጥላለህ።

ድንገት ከፊትህ ፕሮቶኮሉን ያሟላ፤ ገፅታው ንጉስ የመሰለ ሰው ከነ አስፈሪ ግርማ ሞገሱ ይከሰትልህ'ና የክብር ሰላምታውን ዝቅ ብሎ ያቀርብልሀል። እንዲህም ይላል፦‹‹ሰላም ባንተ ላይ ይሁን! እንኳን ደህና መጣህ፤ እንኳን ለዚህ ቀን አበቃህ››ግራ ትጋባለህ፤ ንጉስም ይመስልኃል።

የሰው ግዛት የገባህ በሚመስል ስሜት፦‹‹አንተ ማን ትሆን!›› ብለህ ትጠይቀዋለህ።
‹‹ከእልፍ አእላፍ ህንፃዎችህ ውስጥ የአንዱ ህንፃ የአገልጋዮች አስተዳዳሪ ነኝ። በእያንዳንዱ ህንፃ  እንደኔ ያሉ የህንፃ አገልጋዮችን የሚያስተዳድሩ እልፍ አእላፍ አስተዳዳሪዎች ይገኛሉ።

ከእያንዳንዳችን ስር 1,000 አገልጋዮችም አሉ። በእያንዳንዱ ህንፃ እልፍ ሁረልዒኖች እና እልፍ አእላፍ አገልጋዮች አሉልህ። በዚህ አለም ንጉሱ አንተ ስትሆን የዱንያዋ ሚስትህ የግዛቱ ንግስት ናት›› ሲልህ አግራሞቱ ከህሊናህ በላይ እየሆነ ይመጣል።

ንጉስ መሳይ ሰውየውን ትተህ ከተነተነልህ ህንፃዎች ውስጥ ወደ አንደኛው ቅጥር ግቢ ያለውን ለመመልከት በዝግታ ትዘልቃለህ። ህንፃው እጅግ ግዙፍ ሲሆን ከመሀሉ አንድ ትልቅ አድማሱን የነካ እሚመስል ከአረንጓዴ ወርቅ የተሰራ ጉልላት ትመለከታለህ። በሱ መድመምህ ሳያንስ ከዝያ ጉልላት ውስጥ ዘልቀህ ስትገባ 70 ግዙፍ ቤቶችን ታገኛለህ።

ይህ ሁሉ ግዛት ያንተ መሆኑን እንዳትጠራጠር የሸለመህ አላህ መሆኑን ታስባለህ። ድሎትን ከየት መጀመር እንዳለብህ ማለም ትጀምራለህ። ከህንፃው ውስጥ በውብ ግንባታ ከተሰሩ ቤቶች ደጃፍ መ ዟዟሩን ተያይዘኸዋል። ህንፃው ውስጥ ያሉ እንያ እሚያማምሩ ቤቶች በእያንዳንዳቸው ውስጥ 70 ክፍሎች ይገኙበታል።

ከሰባዎቹ ክፍሎች አንዱን ለመመልከት ወደ አንደኛው ጠጋ ስትል ወደ ክፍሉ መግቢያው በር አናቱ ላይ ከወርቅ የሆኑ የጉልላት ጌጥ ትመለከታለህ፤ የክፍሉን በር ካንተ ሌላ ማንም ከፍቶትም ሆነ ገብቶበት እንደማያውቅ ሲነገርህ ለመግባት ያለህ ጉጉት በእጥፍ እየጨመረ በሩን ትከፍተዋለህ።

ወደ ቤቱ ዘልቀህ ስትገባ ቤቱን እጅግ ግዙፍ ሁኖ ታገኘዋለህ። ከቤቱ ውስጥ በተርታ የተደረደሩ እልፍ ክፍሎች በቀይ አልማዝ አሸብርቀው ስትመለከት ጉጉቱ፣ ደስታው እና ሀሴቱ ያፈኩኻል። ወደ ክፍሎቹ ለመግባት ያለው ጉጉት ልብህን ያናውዘዋል።

ከክፍሉ ስትገባ ጠርዙ በወርቅ አጊጦ ከተንጣለለው አልጋ ላይ ለስላሳ ከሀር የተሰራ አልጋ ልብስ ላይ ንግስትህን ታገኛታለህ። ይሄኔ ግራ በመጋባት ስሜት እየዋለልክ ፈዘህ ትቆማለህ፦‹‹አትዘይረኝም እንዴ? እኔ'ኮ ሚስትህ ነኝ›› ስትልህ ያን ሁሉ የተመለከትከውን የጀነት ፀጋዎች ረስተህ በሷ ደስታ ትፈነጥዛለህ።

ጠጋ ብለህ ልትመለከታት ስትሞክር እንደ መስታወት ኩልል ካለው ከፊቷ ውበት የተነሳ ያንተን ምስል በሷ ፊት ትመለከተዋለህ። ልብሷ ያማልላል፤ መቅረምያዋ በበርካታ ቀለማት ያጌጠ በመሆነ ከሰውነቷ ቀለም ጋር ልዩ ውበት ፈጥሮላታል።

አይንህን ከድነህ በምትከፍት ግዜ ንግስትህ ውበቷ በሰባ እጥፍ  ጨምሮ ስታገኘው ህይወትን ከሷ ጋር ማጣጣም ምን ያህል ዕድል እንደሆነ ትረዳለህ።

ከግዛትህ ነህ'ና ምግብ ባሰኘህ ግዜ ማዘዝ አይጠበቅብህም። ያሻህን መመኘት ብቻ በቂህ ነው። ስትመኝ የምግብ ማዕድህን ለማነጣጠፍ 80 ሺህ አገልጋዮችህ ይረባረባሉ።

መሀሉን ቀይ ያቁት ከተሰኘ ማጌጫ የተሰራ ምንጣፍ ዘርግተውልህ ዳርዳሩን በአረንጓዴ ያስውቡታል። ዙርያው ላይ ለመረጋገጫህ ሉል ይበተንልኻል። የማዕድህ ርዝመት ኪሎ ሜትሮችን ይዘልቃል።

ብዙ ድካም እና እንግልት ያስተናገድክ እንደመሆንህ መጠን ዛሬ የጉድ ምግብ ተዘጋጅቶልኻል። እፊትህ ከተነጠፈው ውብ ሱፍራ ላይ 70 ሺህ አይነት ምግቦች ተደርድረዋል።

ከዚህ በተጨማሪ ከፊትህ የተሰለፉት ውበታቸው የተበተኑ ሉል የሚመስሉት አገልጋዮችህ ብዛታቸው 80 ሲሆን እያንዳንዳቸው በአንደኛው እጃቸው የሳህን ምግብ በሌላኛው እጃቸው ደግሞ መጠጥ ይዘው በክብር ትዕዛዝህን ይጠባበቃሉ። ሁሉም የያዙት ምግብም ሆነ መጠጥ ይለያያል።

በበላህ እና በጠጣህ ቁጥር ጥፍጥናው እየባሰ የሚሄደው ይህ ማዕድ የመጠጡ ለዛ ጥፍርህ ድረስ ይሰማኻል። በበላህ ቁጥር ፍላጎትህ እየጨመረ ይመጣል።

ዛሬ ከጀነት አለም ገብተህ ውሎህን ልትጀምር ሀ ብለሀል።



ይቀጥላል

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

31 Jan, 18:30


በቂያማ ነውጥ ሒሳብህ ሊመዘን ተራ ይዘህ ሳለ፤ መልካም ብለህ ምታስባቸው ሰዎች አይንህ እያየ  ወደ ጀሀነም ሲወረወሩ በራስህ ተስፋ ትቆርጣለህ። መጥፎ ስራዎችህ ሁሉ ያኔ ከፊትህ ድቅን ይሉብኃል።

የሚዛኑ ስለት እና የመዛኙ ቁጣ መፈጠርህን እስክትጠላ ድረስ እያሸበሩህ የመመዘኛ ተራህን ትጠብቃለህ። ለወጉ ልትተሳሰብ እንጂ ስራህ እንኳ የት እንደሚዶልህ ያኔውኑ ትረዳለህ።

ተራህ ደረሰ። ከጌታህ ልትተሳሰብ መዛግብቶችህ ተከፋፍተው እግሮችህ ተብረከረኩ። ጌታህም በህይወት ዘመን የረሳኃቸውን ውስልትናህን ከነቦታው እና ሰአቱ አስቃኘህ። አንተም አምነህ ነፍስህን ወደ ጀሀነም ልትዶላት ዝግጅት ጀመርክ።

ጌታህ አዘነ። ባርያውንም ከውርደት እና ቅጣት ሊያድነው ሽቶ የእዝነትን ግርጆ በባርያው ላይ አከናነበ። እንዲህም አለ፦‹‹ባርያዬ! ትናንት ስታምፅ ሸሸግኹህ፤ ዛሬም አላዋርድህም››

ሒሳብህ ተሳክቶ ወደተመደበልህ የጀነት አለም የሚወስደው ጎዳና ላይ ተለቀቅክ። የዘለ አለም ንግስና።

እየፈነጠዝክ እና እየቦረቅክ ያለ ከልካይ ወደ በሩ ተመምክ። አንደኛው በር ጋ ስትደርስ የበሩን ስፋት ከጉበን እስከ ጉበን 1300 km ሁኖ ታገኘዋለህ። ማመን እያቃተህ  በሩን ስታንኳኳ የክብር ዘበኛው ፦‹‹ማን ነህ›› ይልኃል።
‹‹እገሌ ነኝ›› ትለዋለህ ስምህን ጠርተህ።
‹‹ላንተ እንጂ ለሌላ እንዳልከፍት ቀድሞውኑ ታዝዣለሁ›› ይልኃል በሩን እየከፈተ።

ልክ ከበሩ ዘልቀህ ስትገባ ከበሩ አንስቶ የአይንህ አድማስ እስካየልህ ርቀት ድረስ አቀባበል የሚያደርጉ አገልጋዮችህ ልክ የተደረደረ ሉል ይመስል ተሰልፈው ጠብቀውሕ ትመለከታለህ።

መላዕክቱም ላንተው ክብር ከአንድ ረድፍ ቆመው ሲጠብቁህ በተመለከትክ ግዜ ይህ ሁላ ፍፁም የጌታህ ችሮታ እንጂ ስራህ እንዳልሆነ ተገንዝበህ የመጀመርያውን ምስጋና ለጌታህ ታደርሳለህ።

ለአቀባበል ከተሰለፉት ሰልፎች መሀል ጉዞህን ቀጥለህ ወደ ግዛትህ ትዘልቃለህ ተቀባዮችህ በአጠገባቸው ባለፍክ ቁጥር በክብር እና በትህትና እያገበደዱ ያሳልፉኃል። የመዘውተርንም ብስራት ያበስሩኃል። ያኔ ደስታው ያፍነከንክኃል።

ከርቀት የምታያቸው ከወርቅ፣ ከአልማዝ፣ ከሉል እና ከተለያዩ የከበሩ ድንጋዮች የተገነቡት ህንፃዎች ውበታቸው ቀልብህን ያናውዙታል። ‹‹ዕውን ይህ የኔ ግዛት ነው? ባለ ቤቱ እኔው ነኝ?›› የደስታ ጥያቄዎች ከውስጥህ ይመላለሳሉ።

የምትራመድበት የግቢህ ወለል በሽቶ የታሸ ነው። እልፍ ኣእላፍ አገልጋዮችህ ትዕዛዝህን ለመቀበል አይን አይንህን በጉጉት እየተመለከቱ በተጠንቀቅ ይከተሉሃል። አንተ በግዛትህ ውበት እና በንግስናህ ስፋት በመደመም ላይ ነህ።

በምናብህ ስለህ በልብህ ተመኝተህ እንኳ እማታውቀውን እጅግ ውብ አለም በባለቤትነት ተረክበህ እና በአስደማሚ ዐጀብ ታጅበህ ወደ ዙፋንህ ስትጓዝ ነገረ ዐለሙ በደስታ እንዳይገልህ ሞት ወደዝያ አለም ዝር አይልም።

ነገ ይቀጥላል...


ክስተቱን ምናባዊ ለማድረግ የራሴን መንገድ ተከትያለሁ። የተጠቀምኳቸውን ኪታቦች ከፅሁፌ መቋጫ ላይ እዘረዝራቸዋለሁ።

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

31 Jan, 15:34


ሞትን ለምን ልፍራ የሚያስፈራ ሞልቶ
ቅናት ተንኮል ክፋት ሀሜት ተበራክቶ
ሰው የተሰጠውን መልካሙን ባህሪ
እውነቱን ተቀባይ በአምላክ ቃል ነዋሪ

በስሙ የሚኖር ከወንጀል የጠራ
በጌታው ያመነ ግንባሩ ሚያበራ
በህይወት እስካለ አንጀቱ ሚራራ
ያለውን አካፍሎ ሚበላ በጋራ
ክፉን ያልተመኘ ለወንድም ለእህቱ
ቀና የሆነ ታዛዥ ለእናትና አባቱ

ያጣውን የሚያገኝ በዱሀ በፀሎት
በደስታ በፍቅር ይኖራል በድሎት
እስትንፋሱ እስካለ ደግ ደጉን ሰርቶ
ያሟሟቱን ጉዳይ ለአምላክ ሰቶ

የ,ፈጣሪ ቃሉን ሰምቶ ሀቁን የተረዳ
ካሜት ካሉባልታ ከወንጀል የፀዳ
እንዴት ሞትን ይፍራ የላይኛው ቤቱን
ገድቦት የኖረ ፍላጎት ስሜቱን
አካሄዱ ያማረ አምላኩን አዋቂ
በሞት አይገታም ጀነትን ናፋቂ
መልካም የተመኘ ጥሩ የሆነ ሀሳቡ
ከቶ ሞት ላይፈራ ደንድናለች ልቡ

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

30 Jan, 18:40


ቀና በይ
~~~~

ባለፈው የነገርሽኝን አልረሳሁም
የከዚያ በፊቱንም  አልዘነጋሁም
መልሼ ስጠይቅሽ ያው ነው ምንም አዲስ ነገር የለም ብለሽኛል
ዱንያ እንዳደከመችሽ
ነገሮች እንደከበዱሽ
ያሰብሽው እንዳልተሳካ
የጠበቅሽው እንዳልሆነ
መላ መፍትሄ እንደጠፋሽ …. ነግረሽኛል
ታዲያ ከሐዘን ምን ይገኛል እህቴ!
አሁንም ቀና በይ ነው መልሴ
እስቲ አሁንም ቀና በይ
አዎ ከአንገትሽ ቀና በይ
እስቲ ቀና በይ አትደፊ 
ቀና ማለት እኮ ምስጋና ነው
ጌታዬ አምኜሃለሁ፣ የወደድክልኝን ወድጃለሁ ማለት ነው
የቱን ያህል  መከራ ቢያገኝሽም
መንከራተትሽ ቢበዛም
በዳመና መካከል እንደምትወጣ ፀሐይ ፈገግ በይ …
ቀና፣ ጠንከር፣ በርታ፣ ቀጥ፣ ገጭ … ቀና በይ
አዎን እንደዚያ ቀና በይ
ጥርስሽ ለምን ይደበቅ
ጠላትሽ ደንግጦ ይውደቅ
ፎቶ እንደሚነሳ ሰው ፈገግ 
ሞልቶ እንደተረፈው ሰው ወገግ
የታባቱ … አዎን እንደዚያ ቀና
ዱንያ ለማን ሞልታ ለማንስ ሆና!!
ቢሞላም ቢጎድልም ቀና
ቢከፋም ቢለማም ቀና
ቀና ማለት ምስጋና ነው፤
ብሶት ማማረር  ክህደት ነው
ቀና 
አዎን እንደዚያ ቀና
ሸይጣን ጉዳትሽን እንዳይሰማ 
ምቀኛ አይቶሽ እንዳያማ 
አላህ ፊት ብቻ ዉድቅ 
ለአምላክሽ ብቻ ብርክክ
ለፈጣሪሽ ብቻ ድፍት
ለልብሽ ጌታ ብቻ ንግር
ሰው ፊት ግን ቀና
ምቀኛ ፊት እንዲህ ዘና 
እና እንዳልኩሽ እንደነገርኩሽ 
አንቺ እኮ ቆንጆ ልጅ ነሽ
ታዲያ ቁንጅናሽ ለምን ይበላሽ
ቁርኣንሽን ዚክርሽን ያዢ
መንፈስሽን በራስሽ አድሽ
ህእ …
የምን ዘግቶ ማደር መዋል
ሐዘን ዉበትን ያበላሻል
ጭንቀት ዉስጥን ያምሳል
ሀሳብ ያለ ዕድሜ ያስረጃል
መነጫነጭ ዉሎን ይረብሻል
መበሳጨት አጅር የለውም
መብሰልሰል መፍትሄ አያመጣም፡፡ 
እኔ የምልሽ
ጊዜ ሰጥተው ቢያዳምጡት 
ቢቆሰቁሱት እህ .. ቢሉት
ሁሉም ሰው የሚናገረው 
ያልተፃፈ ብዙ ታሪክ አለው
ይለፋል ዉጤት የለውም
ያገኛል እርካታ ያጣል
ያልማል ስኬት ከብዶታል
ተነሳሁኝ ሲል ይወድቃል 
ያስባል ትዳር ርቆታል
ይወልዳል ልጅ ይሞትበታል
በሀገሩ መካከል ስደተኛ አለ
በወንዙ ዳር ባይተዋር  ሞልቷል
ሁሌም በዱንያ ተነክቷልና 
ስለዚህ እታለሜ ቀና 
የደስታ ምንጩ አላህ ነውና 
የሚያረጋጋው እሱ ነውና
ሐዘን ደስታም ከሱነውና
ኔትወርክሽን ወደ ሰማይ 
እጆችሽን ከፍ ወደ ላይ
መረብሽ ይሁን ጠንካራ 
ግንኙነትሽ አይላላ
እዚያው አካባቢ ተመላለሽ
መልስ አጣሁ ብለሽ አትመለሽ
ሰው ምስኪኑ ምን ሊጠቅምሽ
የፈጠረሽ  እያለልሽ፡፡
ባለፈው ቀና በይ ብዬሽ አልነበር?
አሁንም አንገትሽ አይሰበር፣
ጠላት ለምን ደስ ይበለው፣
ወዳጅስ ስለምን ይክፋው፣
እኔስ ብሆን ለምን ልዘን
ኑሮ ቀዳዳዋ ብዙ ነውና
ሀብታም ጌታ እንዳለው ባርያ ቀና
አልሐምዱ ሊላህ በይ ቀና  
ይኸው ይታየኛል ለኔ 
ቀና ስትይ ቀኑ በራ
ፈገግ ስትይ ፎቶሽ ፈካ
እና እህቴዋ
ቆንጆ ፎቶ እንዲወጣልሽ ቀና
ቆንጆ ሕይወት ለመኖርም ቀና
ቀና በማለት ዉስጥ ቀን አለና

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

29 Jan, 18:35


ማን አለ ❤️

~

ያኔ በዛ ዘመን ፍትህ ባልኖረበት
እውቅና ተችሮ ጭካኔ እና ክፋት
የበላይ የታቹ ሲገዛ ሲፈለጥ
በእኩይ ስነምግባር አለም ሁሉ ሲናጥ
ሀብት ሆኖ ጉልበት
ዘርሆኖ መመኪያ ነብስያና ኩራት
ያኔ በዛን ዘመን …
ጥፋት ሆኖ ሲታይ የሴት ሴትነቷ
በቁም ስትቀበር እስከነህይወቷ
ክብር ሳይቸረው ውድ እናትነቷ
ያኔ በዛን ዘመን
በቀነ ጨለማው
ኑ!!ወደበጎ ሊል ተላከ ለኡማው
ለአለም ብርሀን ከስህተት ማውጫ
ነፍስን ማስጠንቀቂያ ከቅጣት ማምለጫ
ዝናው የማያልቅ ሁሌ ዘውታሪ
መመሪያ ቁርአን ዘመን ተሻጋሪ
አርት ስነፅሁፍ ሶሻል ሳይኮሎጂ
ታሪክ ጅኦግራፊ ሳይንስ ባዮሎጂ
መተዳደሪያ ደንብ ከሰው እስከእንስሳ
ከግኡዝ እስከ ህያው ሁሉን እያነሳ
መመሪያ ተሰቶት የመጣ ወደእኛ
ረሱል አሚን ነው የዝነት መልክተኛ
ሆኖ የተላከ ለአለም አስጠንቃቂ
ዘመን ዘመን ሲሽር ቃሉ ግን ዘላቂ
መመሪያው ቁርአን ሁሌ የሚነበብ
ሁሉ ተደናቂ
መሀመዱል አለሚን የዝነት መልክተኛ
ለአለም አስጠንቃቂ
ያኔ እንኳ…ያኔ በዛን ዘመን
ተመስክሮለታ እንደሆነ አሚን
አወ…… አሚን(ታማኝ)ብለው ጠሩት
መካድ ተስኗቸው ምን እንኳ ቢጠሉት
ዛሬም በኛ ጊዜ
ጥላሸት ሊቀቡት ስሙን ሊያጎዱፉ
ታሪክ ሊያቆሽሹ በስሙ ቢያሾፉ
ግና አልተቻላቸው እውነትን ሊያስክዱ
ድንቅ ስብእናን ማንነትን ሊንዱ
ምሳሌ ነውና ፍቅር የአንድነት
የመቻቻል ሚስጥር ከሰው ከሌላ እምነት
እና ታድያ……
ማን አለ እንደረሱል ንገሩኝ ማንአለ
በድንቅ አመራሩ አንቱ የተባለ
ጥላቻን ደምስሶ አለም ያካለለ
አልኩ እኔም አልሀምዱሊላሂ ይገባው ምስጋና
የዚህ ድንቅ ነብይ ተከታይ ነኝ እና

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

28 Jan, 18:07


السلام عليكم ورحمة الله وبركاته ዉዶቼ እስቲ ሀሳብ አስተያየታችሁን ስጡኝ 🙏

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

28 Jan, 17:20


ይህ ታታሪ እንደለመደዉ ፅኑ ገበሬ
  ለመሸጥ ሄዶ የቤቱን በሬ
አልሸጥ ብሎት አነባ ዛሬ
አንጁቱን አስሮ ገንዘብ ፍለጋ
   ወደ ቤት ሳይሄድ መሽቶበት ነጋ
😭~~

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

21 Jan, 17:38


የኸልቁ አይነታ❤️

ሰላም ላንቱ ይሁን እዝነት ላንቱ ይሁን
አላሕ ፈቀደልን ያንቱን ዑመት መሆን
ምስጋና ይድረሰው በእድያው ላላቀን
ከበስተኋላ አምጥቶ ያንቱ ላደረገን
ዘመናት በመቅደም ቢናፍቁ እኛን
እኛም ናፈቅንኹ የኋሊት ተጉዘን
ሲፋሁ ብንሰማ ሳናይዎ ብናምን
አያደር እየባስ ናፍቆትዎ ጠናብን
ናፍቆትዎ ቢጠና መላ ቢጠፋብን
በቀለም በመንከር ስላንቱ ከተብን
አንቱ የኔ ነብይ የበጎነት ጥጉ
ውልደቶ አበራው የአለም ጭጋጉ
አንቱ የኔ ሐቢብ የነፍሴ አለኝታ
አድርጎ ቢልክዎ የኸልቁ አይነታ
ጀሊሉ ቢሰጠን ትልቁን ስጦታ
ተሞላን በሀሴት አነባን በደስታ
አሳየን ልቅናው ዋለልን ዉለታ
ባልደረቦቻቸው አብሯቸው የኖሩ
ስለ ቁመናዎ እንዲህ ሲዘክሩ
ድንቅ ነበር አሉ የመልክዎ ማማሩ
ረዥምም አጭርም አይደሉ ሙክታሩ
ቁመቶ የሚያምር ልከኛም ነበሩ
በክብ ፊታቸው አይናቸዉ ማማሩ
ደማቅ መልከመልካም ከሉል የሚያበሩ
አፍንጫው መቆሙ ቀጥታው መስመሩ
ጠረኑ የሚያውድ ከሚስክ ከአንበሩ
የእጅሁ ብርታት ክንድዎ መጠንከሩ
ተክለ ሰዉነቱ አጃኢብ ነው ሲርሩ
አንደበተ ርቱእ መልካም ንግግሩ
የተቆጠበ ነው በስነ ምግባሩ
ስርአት የተሞሉ ሰዉን የሚያከብሩ
አድማጭ ብዙ ሰሚ ተግባቢም ነበሩ
ሲራመዱ እግሮቹ የሚንደረደሩ
መተናነሱ ነዉ ሲሄድ ማቀርቀሩ
ባንቱ ቢደነቁ የሁዲ ካፊሩ
በዲኑ አመኑ እውነት መሰከሩ
የተገለጠ እለት ከአጽናፍ ኸበሩ
አበራ ደመቀ አለሙ ድንበሩ
እያሰብኩዎ ብኖር ናፍቆቴን ታቅፌ
አላስተኛ ቢለኝ ብባንን ከእንቅልፌ
ቃላት ቢጠፋበት ባያወራው አፌ
ቢዘግን ብዕሬ ባልጨርሰው ፅፌ
ላላቆም ጀምሬ ላልጠልቀው ወስፌ
እንደው ለአመሌ ቀመስኩኝ ቀጥፌ
~
አልሏሑመ ሰሊ ወሰሊም አላ ሰይዪዲና መዉላና ሞሐመድ ወአላ አሊ ሰይዪዲና
ሞሐመድ;

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

20 Jan, 17:54


ሹክረን መከራ
~

መከራ ሰውን ከሰው ማበጠርያ ነው
መከራ ስብእናን ከስብእና መለያ ነው
መከራ ፍሬን ከገለባው ጊንጊልቻ ነው

የመከራ ቀን ሰዎችን የመፈተኛ ቀን ነው
መከራ በሰላሙ ጊዜ በዙርያህ ካሉ በሺዎች ከሚቆጠሩ ሰዎች መካከል መከራ ሲደርስብህ ማን ከጎንህ እንደሚቆም የምታበጥርበት ሁነኛ መሣርያ ነው
መከራ የአንድን ሰው አቋም ማወቂያ ነው

መከራ ፡ ማን እንደሚደነግጥልህና ማን እንደማይደነግጥልህ፣ ማን ሮጦ እንደሚደርስልህና ማን እጁን ኪሱ ከቶ ቆሞ እንደሚያይህ፣ ማን የዱንያ ጣጣውን ትቶ እንደሚያስታውስህና ማን ጭራሹኑ ልብ እንደማይልህ፣ ማን በልቡ ውስጥ እንደያዘህና ማን በምላሱ እንደሚሸነግልህ፣ ማን አስመሳይ እንደነበረና ማን እውነተኛ እንደሆነ ….  የምትለይበት ጉደኛ የክፉ ቀን ወንፊት ነው

በሰላሙ ጊዜ በፀጉር ልክ ጓደኛ የነበረህ ሰውዬ መላጣ መሆንህን የምታረጋግጠው መከራ ሲደርስብህ ነው፡፡

እናም በሌላ ጎኑ መከራ ጥሩ ነገር ነው  ለማለት ነው፡
ሹክረን መከራ
መከራ ሆይ አንተ እኮ የማትዋሽ ሚዛን ነህ
ሁሉን ስላሳየኸንና ሁሉን ስለሳወቅከን እናመሰግንሃለን
ሰዎችን በልባችን ውስጥ በቅደምተከተላቸው እንድናስቀምጥ አድርገሃልና እናከብርሃለን

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

19 Jan, 05:17


ላይነጋ መስሎ ቢጨልምም
ተስፋሽ የተሟጠጠ ቢመስልም
የጠለቀች ፀሀይ ስጠብቂያት ጠፍታ
ለቅሶሽ ማታ ሆኖ ጧት  ላይ ጠፍቶ ደስታ
በችግር ላይ ችግር ቢደራረብብሽ
አለኝ ያልሽዉ  ሁሉ ፊቱን ቢያዞርብሽ
አንድ ነገር አድርጊ ቀና በይ ወደ ላይ
ተስፋን የሚቀጥል አለና በሰማይ
ፍፁም አታቀርቅሪ አትይ ወደ ምድር
ደስታም ሆነ ሀዘን ያልፋል ሁሉም ነገር
እጅሽን አንሺና አላህን ተማፀኚዉ
ቀን ከሌት በዱዓ ሁል ጊዜ ተጣሪዉ
ያረቢ ያህረህማን እያልሽዉ ጥሪዉ
እሱ አይሰስትም ለጋሽ ነዉ ጌታችን
ካለሱ ማን አለን ለኛ መመኪያችን

    
t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

18 Jan, 08:38


  
                   
እሩቅ አይባልም አውሮፓ ያለው           
እሩቅ አይባልም ኤዥያ ውስጥ ያለው    
ሩቅ የሚባለው ከአጠገብ የራቀዉ       
ከፈኑን ደራርቦ ቀብር የገባው ነው       
በዱንያ ላይ ስኖር ስበላ ስጠጣ
አስክሮኝ ስቸገር የዚች አለም ጣጣ 
ነገ እቶብታለው እያልኩ ሳወራ        
የሀራምን አይነት ሳዳርስ በተራ         
ለአላህ ሳልሰግድ ሳልደፋ ግንባሬን      
ወንጀል ሳግበሰብስ ጨረስኩት እድሜዬን       
አጅሬም ከች አለ ሊቆርጥ እስትንፋሴን
በድን  አድርጎት ሊሄድ መላ አካላቴን   
ያኔ ተረዳሁኝ እጅግ መታለሌን          
አኺራን በዱንያ ሽጬ መለወጤን

ያኔ ገና አወቅኩኝ ነገሩን ተረዳሁ        
በማይጠቅም ነገር በከንቱ እንደለፋሁ 
ነፍሴን መዞ አወጣ ያ መለከል መውት
ከዱንያ ነጠለኝ ምንም ሳልዘጋጅ ሳልጠቀምባት
ቀብር አስገብተው ዘጉብኝ በጣውላ  
ምንም ሳይተውልኝ ከሰራሁት ሌላ::         
ዘመዶቼም ሄዱ እኔን ቀብር ጥለው        
የሰራሐው ስራ ነጃ ያውጣህ ብለው::      
ገንዘቤም አልበጀኝ ያ ያከማቸሁት             
እድሜልክ ለፍቼ ግሬ ያመጣሁት
ልጆቼም አልሆኑኝ እነዚያ የወለድኳቸው    
ለክፉ ቀንደራሽ ይሆናሉ ያልኳቸው::        
ቀባሪ ሲመለስ አፈር እኔ ላይ ጭነው       
ሲንጓጓ ተሰማኝ የጫማ ኮቴያቸው      
ብንን ከማለቴ አይኔን ከመክፈቴ              
ከተጋደምኩበት ቀና ከማለቴ                   
ከፊቴ ቆመው አየው ሁለት መላኢኮች
እጅግ አስጨናቂ በጣም አስፈሪዎች
ጥያቄ ጀምሩ ብለው ማነው ጌታህ?        
እምነትህ ምንድነው እንዲሁም ነብይህ
ያአላህ አትንፈገኝ ከሰፊው እዝነትህ
የምመልስ አርገኝ በሰፊው ችሮታህ
አንተ ባለፀጋ እድሜውን የሰጠህ
በደስታህ በድሎት እንድትኖር ያረገህ
ለአኼራ አዘጋጅ ለመጪው አለምህ          
ይህችን አለም በሞት ሳይደርስ መለየትህ
መቼም ግዴታ ነው የትም አይቀርልህ      
ይህችን አለም ትተህ በሞት ውስጥ ማለፍህ

ነገ እቶብታለው ማለቱ ይቅርብህ
አሁኑኑ ቶብት ተመለስ ወደ አላህ ::
ገንዘቡን የሰጠህ አንተ ባለሐብት
አሁኑኑ ለግስ ለሚስኪን መፅውት::          
ችግርተኛን መርዳት የተራበን ማብላት
ነገ ያደርግሐል የጀነት ባለቤት


    t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

17 Jan, 18:38


ወዳጄ ደስተኛ ሆነህ ለመኖር ራስህን ዉደድ
ራስህን ዉደድ ስልህ ምን መሰለህ ....
* በሰው ለመወደድ አትልፋ፣
* እንዲህ ለማለት ፈልጌ ነው ብለህ ለማሳመን አትድከም፣
* ከግትር ሰው አትከራከር
* ስለ መጪው ጊዜ አትጨነቅ
* ጥለዉህ ስለሄዱት አታስብ፣
* ሥምህን ያጠፉትን እርሳ፣
* ለመታወቅ አትፍጨርጨር፣
* መጥፎ ጥርጣሬን ራቅ፣
* ሰው ስለኔ ምን አለ አትበል፣
* የሰዉን ነዉር አትከተል፣
* መጥፎ ስብስብ አትቀላቀል፣
* ብቸኝነትን አዘውትር፣
* ጊዜህ በአግባቡ ተጠቀም፣

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

16 Jan, 18:20


ልጅህ ተበደልኩኝ አልቻልኩም ብላ ቤቷን ትታ ቤትህ ከመጣች ሶብር አድርጊ፣ ሂጂ እዚያው ቤትሽ ተመለሽ፣ እኛም በዚሁ ዓይነት ሁኔታ ዉስጥ አልፈን ነው እዚህ የደረስነው አትበላት። ይህን ከማለትህ በፊት ምን እንደሆነችና ምን እንደገጠማት ጠይቃት፣ በትዕግሥትም አድምጣት። ሀሳቧን ከምታጣጣልና አፍ አፏን ከምትላት ችግሯ ምን እንደሆነ ፈትሽና ከመሠረቱ ለመፍታት ሞክር። ባልሽ ሀብትና ገንዘብሽ ነው እሱ ነው የሚያዋጣሽ እዚህ ምንም የለሽም አትበላት። ባይሆን ያንተ የአባቷ ቤት ሁሌም ቤቷ እንደሆነ ንገራት። ዛሬም ነገም ከጎኗ እንደምትሆን አበረታታት።

እርግጥ ነው ሴት ልጅ በባለቤቷ፣ ድህነት፣ በሽታና ችግር ላይ ልትታገስ ትችላለች። ነገር ግን በመጥፎ ባህሪው ላይ መታገስ ይከብዳታል። ሲንቋትም በእጅጉ ነው የምትጠላው።

ትዳር ሁለት ሰዎች አብረው የሚመሩት የጋራ መርከብ ነው። የዚህ መርከብ ትልቁ ነዳጅ መከባበር ነው። መከባበር ከሌለ  ትዳር የለም። የሰው ልጅ ያለ ክብር መኖር ይከብደዋል።

ትዳርን ጤና እና ሰላም አጥተው በሂደትና ቀስ በቀስ የሚሞቱበት እስር ቤት አታድርጉት

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

16 Jan, 08:11


💧ግጥም 🌧
📖ስለኡም

እህቴን ወንድሜን እኔንም ጨምራ
ወላጅን እንኻድም ሳይሄዱ አኼራ
ብላለች ብእሬ _•_አላህን እንፍራ

>>>>>>>>>>>>>>>>
በዚህች ምድር ላይ  ከእናት የተሻለ☜
እስኪ በሉ አሳዩኝ ድንቅ ፍጡሩ ካለ☜
>>>>>>>>>>>>>>>>

``ታዲያስ ለምን? ወንድሜ እባክህ
``እንዲህ ተሰቃይታ   ላሳደገችህ
``ለመሳደብ ዳዳው ያንተ ምላስህ
``እንዴት ችሎ አወጣ ስድብ ለኡሚህ
~~~~
እናት እኮ ማለት* ላንተ መገኘት \
እንደሆነች እወቅ  ትልቅ መሰረት\


~~~~~
🔮👇👇👇👇👇👇👇🔮

``ያለንበት ዘመን ነገሩ ይገርማል
``ልጅ ለወላጆቹ አልታዘዝ ብሏል

||እናትና አባቱን  እንደፋራ ቆጥሮ []
||ፀጉሩን ፈርዞ በጂንስ  ተወጥሮ []
||እናቱን ይሰድባል`` እየገባ  ዞሮ []
||ሆኖበት እኮ ነው ጭንቅላቱ ዜሮ[]

____
ኡሚ አትከፊ ማሰቡን ተይንጂ       []
ለኔ ካለኝ ነገር ያሻሽን ውሰጂ        []
_
ዛሬም እንደገና ስላንቺ እፅፋለው •
እርግጠኛ ሁኚ ኡሚ ወድሻለው  •
•••••••••••••••••••••••••••••••••••

አራዳ ነኝ ባዩ   አንተ   ባለ  ቃራው☜
ነገር ግን ሀቂቃ አራዳ  ያልሆንከው☜
እናት መገልመጡ አያዋጣም ተወው☜

እኛ ቁጭ  ብለን  ኡሚ  ስትሰራ•
ተነስተን እንርዳት አላህን እንፍራ•__

እንዳትቆሽሽብን ልብሷንም እንጠብ🌹
ነገ እንድናገኘው    የረህማንን  ሁብ🌹

~እህት አደራሽን  ኸድሚያት  እንግዲ~
~አይጠይቅም ነዳማ ካመለጠች ወዲ~


እናቱን ከሚሰድብ ሲወጣ ሲገባ*
ለሱ  ይሻለዋል  መቃብር  ቢገባ*


ያለንበት ግዜ  _ ነገር  ተቀያይሮ
ልጆች እንደ ወላጅ ሆነዋል ዘንድሮ

°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
እናቱን የሚያዝ ቁጭ   ብሎ በሶፋ
ህሊና ቢስ ወጣት መጥቷል እየሰፋ


ስለ አሳደገችን በረህማ በእዝነት
አንተ የኔ ወንድም አንቺ የኔ እህት
ማስከፍቱ ቀርቶ  #እንንከባከባት
ክብር ይገባታል  ለወለደች  እናት
ስንወጣ ስንገባ  ዱዓ  እናርግላት
ጌታዬ ያ አላህ 💧አንተ   እዘንላት
ስትኖር በአዱንያ   ከሽርክ አፅዳት
የቂያማም እለት ከጭንቅ ጠብቃት
ከእሳት አርቀህ  ወደ  ጀነት  አግባት

👌
ዝም ከማለቴ  እንድ  ሁለት መናገር
ይሻላል ብዬ ነው ስፅፍ ይህን ነገር
ስለዚህ ከእንግዲ እናትን እናክብር
እንኸድማት በደንብ እንበላት አብሽር
ጀነት እኮ ነች  በሁለት እግሯ ስር

°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
አሁንም ደግሜ ^ ^ አደራ ምላችሁ
ኡሚን አታስከፏት ወላሂ እባካችሁ

💧

~የገጣሚ መሐት • ሊፅፍ ሊያቀልም
~ብእር ቢያነሳ  ስለ  እናት ቢገጥም
~የኡሚን ውለታ መግለፅ አይችልም
~የጀመረው እንጂ __ይህን ከዚ ቀደም
~ የእናትን ነገር __  የጨረሰው የለም
~እንደ ሌሎች ሁላ _ብሞክረው እኔም
~ብእሬን መዝዤ _ ብጭር  ስለ  ኡም
~እሷን ምገልፅበት _  የለኝም አቅም
~ስለማልጨርሰው _እዚህ ላይ ላቁም
~ፁሁፌን አንብቡት ከልባችሁ በጣም
~እንደሚታወቀው አይደለውም ፍፁም
~ስህተት ካገኛችሁ   አድርጉኝ ጠቆም
~ወዲያው አርማለው እኔ አላቅማማም

🗒
~እስኪ አሁን በቃኝ ብእሬን ልሰብስብ
~የእናቴን ሁኔታ ላጢነው በደንብ
~እሷን ማስደሰቻ _ _ መንገዱን ላስብ


ልቋጨው ስለ እሷ እዚህ ላይ ለዛሬ
ተጠቃሚ ያርገኝ _ _ በዚህ ንግግሬ

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

15 Jan, 17:36


ከሰዎች ጋር ለመኖር ..
በርህን ገርበብ አድርገህ ተወው
የገባ ይግባ፣ የወጣም ይውጣ
በገቡት ብዙ አትደሰት
በወጡትም ብዙ አትዘን
ሰው ይሄዳል ይመጣል
የመጣዉን አላህ ነው ያመጣው
የሄደዉንም አላህ ነው የሸኘው
እወቅ
ሁሌም ካንተ ጋር ቀሪ አላህ ብቻ ነው
ከሰው አንፃር ጉዳይህ አቡበከር ረ.ዐ. በነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ.) ሞት ጊዜ  እንዳሉት ይሁን
ሙሐመድን የሚያመልክ ካለ ሙሐመድ ሞቷል አላህን ለሚያመልክ ግን አላህ አይሞትም ምንጊዜም ሕያው ነው
በሰው ተስፋ የሚያደርግና የሚደገፍ ካለ ሰው ተሰባሪ ነው፣ በአላህ ለሚመካ ግን እሱ ምን ያምር መጠጊያ ነዉ !!

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

13 Jan, 17:18


ይህም ቀን ያልፍና!

ያቡጧሊብ ሸለቆ ምንኛ ታደለ
ነብይ ከሶሃባው 3 አመት አዘለ
ረሱልን ላይሰጥ በአላህ የማለ
አብሯቸው ሆነና ስቃይ ተካፈለ

ታሪኩን ሚያውቀው እስኪ አሁን ይናገር
ያኔ እዛ እያሉ በኑ ሃሺም ጎሶች ምን ይበሉ ነበር?

በራሳቸው ገንዘብ እንዳይሸምቱ ሄደው
የግፍ ሰነድ አለ ግፈኛ የወለደው
ማን ከነሱ ይግዛ? ማን ይሽጥላቸው?
ተቀዶ ሳይነሳ ካዕባ የተሰቀለው

ድሮ ድሮ ህፃን የእናት ጡት ሲጎርስ
ወተት ያገኝ ነበር አንጀት ሚያርስ
ታዲያ ይሄ ነጭ ህይወት በደንብ የሚገኘው
ተመጣጣኝ ምግብ እናት ስትበላ ነው
እዚህ ሸለቆ ውስጥ ይሄን መች አገኙት
ቅጠልና ቆዳ ነበር ሚመገቡት
ታዲያ የሰቆቃው ድምፅ መነሻ ምክንያት
እነሱ እኮ ናቸው የተራቡ ህፃናት

ይህን ከባድ ችግር ያኔ የቀመሰው
ረሱል ያሉበት ስብስብ እኮ ነው
ግን ያ ቀን አልፎ በኃላ የሆነው
ያንን ታላቅ ገድል ታሪክ ነው ያሰፈረው

ያኔ ወተት አጥቶ ያለቀሰው ህፃን
ለእስልምና ኑሮ ተሞልቶ በኢማን
በጦሩ ድል አርጓል ፋርስና እሮምን
በሸሪዓ ገዝቷል ሩብ የአለምን

ታሪክ ራሱን ሲደግም እንዲሉ ነውና
በሻም ከተማ ላይ ችግሩ ቢጠና
ያኔ እንደነበረው ይሄም ነው ፈተና

ምንም ቢቸገሩ ቢራቡም አሁን ላይ
ፈታኙ ጌታቸው ሁሉንም ነው ሚያይ
አያድርገውና ወንዶቹ ቢያልቁ
ጀግና ሴቶች አሉን ለዲኑ የነቁ
ወንዶች የሚወልዱ ለጂሃድ የበቁ
በአላህ ሃቅ ላይ ድርድር ማያቁ

ታዲያ እንደዛኛው ይህም ቀን ያልፍና
ይህ የዛሬው ህፃን በኢስላም ያድግና
ሮም ላይ አዛን ይላል የባጉዙ ጀግና
አለምን ይመራል ዳግም እንደገና!!!
ቢኢዝኒላህ


t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

12 Jan, 12:56


ማላ የዕኒ

አንዳንድ ንግግሮች አሉ ከአላህ ዘንድ አጅር የማናገኝባቸው፤ ለስኬትም የማንበቃባቸው፡፡ አንዳንድ ወሬዎች አሉ ለዱንያችን የማይጠቅሙን ፣ ለአኺራችንም የማይፈይዱን፡፡ አንዳንድ ወጎችም አሉ ወደ ጀነት የማይመሩን ከእሣትም የማያድኑን፡፡ ወይ ዚክር ሆነው አላህን አላወሳንባቸው ወይ ደግሞ ሹክር አይደሉ አምላካችንን አላመሰገንባቸው፡፡

የዚህ ዓይነቶቹ ወሬዎችና ንግግሮች ‹ማላ የዕኒ› ይላቸዋል እስልምና፡፡ የማይመለከቱን ጉዳዮች፣ ዝባዝንኬዎች፣ አሉባልታዎች፣ እንቶፈንቶዎች፣ እርባና ቢስ ጉዳዮች ልትሏቸው ትችላላችሁ፡፡ ወዳጆቼ … በዚህ ዓይነቱ ማዕድ ላይ ድንገት ከገባችሁ እንኳን ብዙ አትቆዩ፤ ቁምነገር ካጣችሁና ጥቅሙ ካልታያችሁ ቶሎ ዉጡ፡፡ ጊዜያችሁ ይቃጠላልና፡፡ ትልቁን ሀብታችንን ጊዜን አቃጠልን ማለት ትልቅ ኪሣራ ላይ ወደቅን ማለት ነው፡፡

ወደዚህ ዓለም የመጣነው ለቁምነገር ነውና እኛን የሚመለከቱን ጉዳዮች ‹ቁምነገሮች› ናቸው፡፡ ነፍሣችንን የምንጠቅምባቸው፣ ሌሎችን የምንፈይድባቸው፣ ዓላማችንን የምናሳካባቸው፣ ኻቲማችንን የምናሳምርባቸው፡፡

የሆነ ጊዜ ላይ ከሆነ ሰው ጋር ረጅም ጊዜ ወሬ ልታወሩ ትችላላችሁ፡፡ ቀኑን ሙሉ ጊዜ ወስዳችሁ ወይም ሙሉ ሌሊቱን እንቅልፍ አጥታችሁ ፌስ ቡክ ላይ ልትቸተችቱ ትችላላችሁ (ቻት መሆኑ ነው)፡፡ ከአንድ ግሩፕም ገብታችሁ ሀሳብ ልትለዋወጡ ወይም እዚያው አካባቢ ፈንጠር ብላችሁ በመቆም ሀሳብ የሚለዋወጡትን ትታዘቡ ይሆናል፡፡ 

አንዳንድ ጊዜ ግን ቆም ብላችሁ የዕለት ቻታችሁንና የግሩፕ ዉሏችሁን ስትገመግሙና ፍሬውን መልቀም ስትሞክሩ ዉጤቱ ባዶ ይሆንባችኋል፡፡ ባዶ፡፡ ምሽት እቤቴ በር ላይ ስደርስ ‹ወይኔ ዛሬም ወድቄ ገባሁ!› ብዬ ከራሴ ጋር የማወራባቸው አጋጣሚዎች እጅግ ብዙ ናቸው፡፡ በጣም ብዙ!! መውደቅ በኃጢአት ብቻ አይደለም፤ በተጨመረ ዕድሜ ላይ ምንም መልካም ነገር ሳይጨምሩ መዋልም መዉደቅ ነው፡፡ ዕድሜ የተሠጠው ለዓላማ ነውና፡፡

ሳያጣሩ መረጃን ማሠራጨት፣ የሰሙትን ነገር ሁሉ ለማውራት መቸኮል፣ በማያገባ ነገር ገብቶ መፈትፈት፣ እዚህም እዚያም ሄዶ መከራከር፣ አዋቂ መስሎ ለማስረዳት መሞከርና … ሌላው የጊዜው ማላ የዕኒ ነው፡፡ ዛሬ ላይ ማንን መስማት እስኪያቅተን ድረስ ሁሉም ተንታኝ፣ ሁሉም መካሪ፣ ሆኗል፡፡ የሚችለውም የማይችለውም፣ የሚያገባውም፣ የማያገባውም ይናገራል፡፡ የዚህ ዓይነቱ ባህሪ የጥሩ ሙስሊም መገለጫ አይደለም፡፡ የአንድ ሰው እስልምና ማማርን ከሚያመለክቱ ነገሮች መካከል አንዱ የማይመለከተውን ነገር መተዉ ነው፡፡ አንዳንድ ዝምታና ከሰው መገለል ጥሩ ነው፡፡ ትኩረትህን ይሰበስብላህል፡፡ ጊዜህን ሙጥጥ አድርገህ ለዉጤታማ ሥራ እንድትጠቀምበት ያግዝሃል፡፡

እናም ወዳጆቼ … ለጊዜያችን በትልቁ እንጨነቅ፡፡ እያንዳንዷን ሰከንድ በምን ላይ እንዳዋልናት መለስ ብለን እንቃኝ፡፡ ምድር ላይ የምናሳልፋትን ይህችን አጭር የሀምሳ እና ስልሳ ዓመት ዕድሜ ከተራ ብዙ ነገሮች ይልቅ ጥቂት ቋሚና ጠቃሚ ቅርሦችን እንለፍ፡፡ መዝናናት መቀለዳችንም በልክ ይሁን፡፡ መልካም ሥራችን ይብዛ ይክበድም፡፡ የነገ ሥራችን ይመዘናል እንጂ አይቆጠርም፡፡ ከመልካም ሥራ በላይም ምንም ዋስትና የለንም፡፡

አምላኬ ሆይ ! አንተን በማውሳት በማመስገንና አምልኮህን በማሳመሩ ላይ እርዳኝ፡፡

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

09 Jan, 10:53


‍ ‍ ሳየው ሳየው ያስደምመኛል
ልበ ሙሉነታቸው ይሰማኛል
ውጥንቅጡ በወጣበት
እላይ ታቹ በጠፋበት
ሂጃብ ክብሯ ሲፈተንባት
ትታያለች ደምቃ በርታ
ከፍንዳታው በላይ ታይታ
አቤት ወኔ ጥንካሬ
አፈር ለብሶ ሂጃብ ክብሬ
አላወልቀው ጠላት ይውለቅ
እስከ ሂጃቤ ልበል ድቅቅ
ልጄ እይ ስቃይ ክብሬን
ሲያደባልቁት ማንነቴን
ፅናት ብርታት ሞልቶት ውስጤን
ምፈልገው እንዲ እንድቶን
ካደክልኝ አስታውስ እኔን
ከሞትክብኝ ካልደረስን
ከቆመብን እድሜያችን
አላማርም አላህ ባለው
ይሁን ባለው በወሰነው
ልጄ ውዴ ሲረጋጋ ነግርሃለው
ሳለቅስ ስጮህ አትሰማኝ
ከተለያየንም ደህና ሁንልኝ
የሱ ምርጫ የተሻለው
የወሰነው የፈረደው
ከፈለግነው ካሰብነው ።

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

08 Jan, 18:04


የአየር ሁኔታዎች መቀያየር ጭምር ነገሮች ባሉበት እንደማይቀጥሉ ያሳዩናል። አላህ ሁሌም ሥራ ላይ ነው። ባላሰባችሁበት ጊዜና ሁኔታ ከመቅጽበት ከባድ ሁኔታችሁን ሊቀይር ይችላል። ብቻ ጊዜው ይርዘምም ይጠር ተረጋግታችሁ፣ ተስፋ አድርጋችሁ፣ ታግሳችሁ የአላህን የለውጥ ቀን ጠብቁ። እሱ ለውጡን ሲያመጣው አይሰስትም።

የተጎዳችሁ፣ የተበደላችሁ፣ ሥራ ያጣችሁ፣ ልጅ ያላገኛችሁ፣ ትዳር የዘገባችሁ አሁንም ጠብቁት እሱን ብቻ ተስፋ አድርጉ

ከአላህ ዉጭ ማን አለን!!

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

07 Jan, 17:44


ነቢ ሰዐወ አሉ፦
የአደም ልጅ ሞት በቀረበው ግዜ አላህ 5 መላዕክትን ይልክበታል።

ነፍሱ በመውጣት ላይ ሳለች የመጀመርያው መልዓክ ይቀርበው'ና‹‹የአደም ልጅ ሆይ! ያ ፈርጣማ ጡንቻህ የት ገባ? ዛሬ ምን አደከመው? ያ ርቱዕ አንደበትህ የት ግባ፤ ዛሬ ስለምን ተለጎመ? ዘመድ አዝማዶች አልነበሩህ! ስለምን ጭርታ ሰፈነብህ?›› ሲል ይጣራል።

የአደም ልጅ ነፍሱ ወጥታ በተከፈነ ግዜም ሁለተኛው መልዓክ ይመጣ'ና፦‹‹የአደም ልጅ ሆይ! ከሀብትህ ለድህነቴ እለት ብለህ ያጠራቀምከው የት ገባ? ለመጠለያ ብለህ የገነባኸው ህንፃህ የት ሄደ? ከወዳጅ አዝማድ የያዝካቸው ጓደኞችህ የት ጠፉ?›› ሲል ይጣራው'ና ትቶት ይሄዳል።

የአደምን ልጅ ጀናዛ ሰዎች ተሸክመው ወደ ቀብሩ ሲሄዱ ሶስተኛው መልዐክ ይመጣ'ና ይጣራል፦‹‹የአደም ልጅ ሆይ! ዛሬ... ተጉዘህ የማታውቀውን አይነት ሩቅ ጉዙ ትጓዛለህ ዛሬ...ጎብኝተህ እማታውቃቸውን አይነት ሰዎች ትጎበኛቸዋለህ፤ ዛሬ... ገብተህ በማታውቀው ጠባብ መግቢያ ውስጥ ትገባለህ። የአላህ ውዴታ ከተሳካልህ ምንኛ ታደልክ፤ በአላህ ጥላቻ ከተመለስክ ዋ! መጥፋትህ!›

ሟች ከቀብሩ ገብቶ በተጋደመ ግዜ አራተኛው መልዓክ ይመጣ'ና፦‹‹የአደም ልጅ ሆይ! ትናንት ከምድር በላይ ሆነህ ስትራመድ ነበር፤ ዛሬ ከስሯ ገብተህ ተኝተኻል። ትናንት ከላይዋ ሆነህ ስትስቅ ነበር፤ ዛሬ ከስሯ ሁነህ ታለቅሳለህ ትናንት ከላይዋ ሆነህ ስታምፅ ነበር ዛሬ ከስሯ ሆነህ ትፀፀታለህ›› ሲል ይጣራል

ቀባሪ ቀብሮ ሲመለስ የመጨረሻው መልዓክ ይመጣ'ና፦‹‹የአደም ልጅ ሆይ! ቀበሩህ እኮ ትተውህም ሄዱ። አብረውህ ቢቀመጡም አይጠቅሙህም። ንብረት ሰበሰብክ ግና ለሌላ ሰው ትተኸው ሄድክ። ዛሬማ! ወይ ከላዕላይቷ ጀነት ትከትማለህ፤ አልያም ከነዲዷ ጀሀነም ትነጉዳለህ›› ሲል ተጣርቶ ይሰናበተዋል።

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

06 Jan, 16:28


ቢስሚላሂ ብዬ ልጀምር በስምህ
አራህማኒ ረሂም በላቀው ንግስናህ
በዚች አንደበቴ በትንሽ ምላሴ
ተገልፆ ባያልቅም አንተን ማወደሴ

የሁሉም ነገር ምንጭ ሰሪና ፈጣሪ
አንተ በመሆንህ ጨራሹም ጀማሪ
ይሁንልኝ ለኔ ለአኼራ ምስክር
ፃፍልኝ በበጎ ቢጠቅመኝ ለቀብር

ከፍ ባለው ባህሪህ በመልካሙ ስምህ
እስኪ ላሞግስህ እኔም ለ ልቅናህ
አድርገኝ ከሀቁ ከእውነተኛ አማኝ
አፅናኝ በመንገድህ ከኢብሊስ ጠብቀኝ

የለውም አጥማሚ አንተ የመራሀው
አይኖረውም አቅኚ አንተ ያጠመምከው
አልሀምዱሊላሂ ረቢል ዐለሚን
ኢስላምን የምትሰጥ ነህና አልሙእሚን

ይህን አፅናፍ አለም ብቻውን ፈጣሪ
ቀንና ጨለማን ጊዜ ላይ ቀያሪ
ሰማይን አስጊጦ በኮኮብ ጨረቃ
ብርሀኗን እንደትሰጥ ፀሀይ ሙቃ ደምቃ

ሁሉን ምቹ አድርጎ ምድርን ፈጠራት
የሰው ልጅ ለኑሮ እንዲጠቀምባት
በዚህ ድንቅ ስራ ጥበብ በተሞላ
ኩን ፈየኩን ብለህ ኸልቁን ስትሞላ
ሁሉም ባንተ አደረ ፍጥረታለም ሁሉ
ክብርና ምስጋና ይገባህ ጀሊሉ

እስኪ እናስተንትነው ሰማይና ምድሩን
የሰጠንን ኒዕማ ለኛ የዋለውን
የዘራነውን ዘር በደረቅ መሬት ላይ
ዝናብን አዝንቦ ከዛ ከሩቅ ሰማይ

ሰብሉን በየ አይነቱ አብዝቶ ይሰጣል
የሰው ልጅ ከሱ ሀቅ ወስዶ ይጠቀማል
የአዝነቱ በር ሰፊ ገደብ እማያውቀው
ሰጪና ነሺ ነው እሱ ለፈለገው

ሰውን የሚፈጥር አርጎ በየ አይነቱ
ከሚፈሰው ውሀ ከዛ ከስሜቱ
ሁኖ የረጋ ደም አጥንትና ስጋ
ልጅን ትሰጣለህ ሳታስከፍል ዋጋ

እኔም ሰው ነኝና ከፈጠርከኝ አንዱ
ጠብቀህ አቆየኝ ከቀናው መንገዱ
መጨረሻዬ አርገው  በሸሀደተይኒ
ምህረትን ለግሰኝ ነህና አልሙቅኒ

ምድርን ዘርግቶ ቸክሎ ተራራን
እንዳታረገርግ ጠብቆ ሚዛኗን
በውሀ የተሞላ ውቅያኖስ ባህሩ
ፍጥሩን ሞላህበት ነህና አል ኑሩ

ሁለት ሁለት አርጎ ሁሉንም ፈጠረ
በአፈጣጠሩ እጅግ ያሳመረ
ከትንሿ ረቂቅ ስውር አፈጣጠር
እስከ አፅናፍ አለሙ ሁሉን ብንመረምር
ተአምረ ብዙ በገደብ ያልፀና
የድንቆች ድንቅ ነው ጌታችን መውላና
በአራት አይነት መንገድ ሰውንም ፈጥረሀል
ላንተ ሁሉም ቀላል ሆኖ አሳይተሀል
መጥቀስ ካስፈለገ  አራቱን በተራ
ከአደም እንጀምረው ያንተን ጥበብ ስራ

ከዚያ ከአፈሩ ከነበረው ጭቃ
አደምን ቀርፀህ ሰርተህ ስታበቃ
እሩህ  ዘራህበት እውቀትም ሰጠሀው
ከፍጡራን በላይ አክብረህ ፈጠርከው

ፈጥረህ አልተውከውም አደምን ብቻውን
ልትሰጠው ፈልገህ የህይወት አጋሩን
እንቅልፍም ጣልክበት እራሱንም ሳተ
ከወንድ ሴትን መፍጠር መቼም ገር ነው ላንተ

ከዚያም ከስተ ግራው ከሰጠራ አጥንቱ
ሀዋን ፈጠረክለት አርገህ ባለቤቱ
ከአደምና ሀዋ የዘር ሀረግ ኡደት
ይችን ሰፊ ምድር  በሰው ልጅ ሞላሀት

አራት ሆኖ ይሙላ ልጥቀስ  መርየምን
ያለአባት ወላጇን አልመሲህ ዒሳን
እናት ሳትሆን በፊት ኢሳንም ሳትወልድ
ክብሯን የጠበቀች ያልተነካች በወንድ
ፈጣሪን ተገዢ ሆና ስትኖር ነበር
በመላኩ ጅብሪል ብስራት ስትበሰር
ሀዋን  ከአደም አጥንት ፈልቅቆ የፈጠረ
ለመርየም ልጅ መስጠተ  ለአላህ ገር ነበረ
የአላባት ያደገው ኢሳ ኢብኑል መርየም
የአላህ ነብይ እንጂ ሌላም አልነበረ

አልኻሊቅነትህ ይከበር ዘላለም
ምህረትን ለግሰኝ በሁለቱም አለም
በየቂን በሀቁ አንተን ማወደሴ
አልሽኩር ነህና  ጥቀማት ለነፍሴ

መመርያ አደረከው ቁርአንን ለሂወት
ከሰይጣን እርቆ ሰው እንዲመራበት
ፍቅርና ፍራቻ ፀንቶ በልባችን
የረሱሉን ሱና አርገን መንገዳችን

ከፈጠርከው ፍጡር መጥፎ ክፋት ሁሉ
ብቅ እልም በሚሉት በቀንም በለይሉ
ጠብቀን ጌታችን ከዚህ ሁላ ተንኮል
አንተ የጠበከው መቼም አይበደል
           

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

05 Jan, 16:28


😭...ስንብት"

የሰዉ መዉደድ አለኝ
አዉቃለሁ ቀን በቀን
ልቤ ግን ደከመኝ በዚህ
በታህሳስ ቀን
አድናቂዎች አሉኝ እኔም ምወዳቸዉ
እንዴትስ አድርጌ ልሰናበታቸዉ
በምን አንደበቴ ሞትኩኝ ልበላቸዉ
ጥልቅ ፍቅሬን ትቼ እንዴት ልለያቸዉ
የሚፍለቀለቅ ጥርሴም በቃ ተከደነ
አላይም ብሎኛል አይኔም ተሸፈነ
መተወን አልችልም ይልቁ ደክሞኛል
የሚራመድ እግሬም በቃ ዝሎብኛል
መነሳት አልቻልኩም ተኝቼ ከአልጋ
ፀጥ ረጭ አለብኝ ልሳኔም ተዘጋ
ቀጠሮ የያዝኩት ለአዲስ አመት ብዬ
ምርጥ ሞዴላችን አንተነህ ተብዬ
በነዛ አርቲስቶቹ በትወናዉ አለም
ለካ ሞት ግድ ነዉ የሚኖርም የለም
ኮንትራት ናት አለም
ከንቱ ናት ይች አለም
ጥምብ ናት ይች አለም
ለኪራይ ነዉ እንጂ አታኖር ዘላአለም
እና እኔ እንዲህ ሁኛለሁ
ይልቅ ልምከራችሁ
ለየትኛዉ አለም ለምኑ ብላችሁ
የምትናቆሩት ዘር እየለያችሁ
እስኪ ተዋደዱ ሰላምን ዉደዷት
የጥላቻ ደብተር ዛሬዉን ቅደዷት
አደራ ፍቅር አብሩ ዘረኝነት ይጥፋ
እንደወደዳችሁኝ እኔም ሳልከፋ
ምስጋናየን ትቼ በቃ አኔም እጃለሁ
ነብስ ይማር በሉኝ እወዳችሃለሁ
~~~~~
😭

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

04 Jan, 18:14


የቀጠለ

ወንድሜ

እና

ወንድ ሁን

የወንድ አልጫ ከመሆን ተጠንቀቅ
ሰው ቤት በልቶ መጥቶ 'አቤት የሷ ወጥ!' ይላል፣
የሰዉን ኑሮ በቤቱ ላይ ያዳንቃል
የሌላዉን ቤት ከራሱ ጋር ያነፃፅራል፣
የቤቱ አይጣፍጠዉም፣
ለማጣፈጥም ወጭ አያወጣም
 
በቤትህ እርካ፣
በቤትህ ተብቃቃ፣
ለሆድህ አትኑር፣
 በሆድህ አትመዝን፣
ዉጭ ካልከፈልኩ ብለህ እየተገለገልክ ለቤት የምትሰስተው ነገርስ ...
 
ሰነፍ ባል
እሱ ጥሩ ሳይሆን ከሰው ጥሩነት ይጠብቃል፣
እሱ ምርጥ ሳይሆን ከሌላው ፍፁምነትን ያስባል፣
ሲገባ ኃይለኛ ነብር ሲወጣ ለስላሳ ድመት ይሆናል፣
ሲወጣ ቁጥብ ነው ፣ ሲገባ ምላሱ ረጅም ይሆናል፣

እና
ኸይሩኩም ኸይሩኩም ሊአህሊሂ ነው ነገሩ፣
ምርጡ ሰው ለቤቱ ምርጥ የሆነ ነው
ወንድ ሁን
በገባህ በወጣህ አትጨቃጨቅ
አታነዉራት
አትስደባት
አትበድላት
አታስለቅሳት
አታስፈራራት
አትናቃት 
ፊቷ ላይ አትምታት

አትበላት …
አስቀያሚ ነሽ አትበላት
የማትረቢ ነሽ አትበላት
ትልቁ ስህተት የሠራሁት አንቺን ያገባሁ ቀን ነው አትበላት
አንቺን ካገባሁ ጀምሮ ደስታ አግኝቼ አላውቅም አትበል
“አትበል! … ያሉት ነቢያችን ናቸው  አትበል

አላህ እንደሚያይህ አውቀህ አብረሃት ኑር
ወገን የላትም ብለህ አትጉዳት
ወላጆቿ እሩቅ ናቸው ያለችበትን ሁኔታ አያዩም፣ አይሰሙም ብለህ አትጨቁናት
ወንድ ሁን
ሰፋ በል፣
ዋጠው
ቻል አድርገው
ሰው ሁን …
ስትታመም ችላ አትበላት
ስትተክዝ አይተህ አትለፋት
ብትሰበር አካልህ ናት
ሆድ ቢብሳት ክፋይህ ናት
ሁለት ነፍስ ስትሆን ይበልጥ ተንከባከባት
ብታረግዝ ጉዳዩ ጉዳዩዋ ብቻ አይደለም ጉዳይህም ነው፣

 አክብራት፣ ነቢዩ ናቸው ያከበሯት
ይፈራታል ይሉኛል ብለህ አትፍራ
የምታናገረዉን አዳምጣት
የምትለዉን ስማት
አግብተህ አትጣላት
አብረህ እየኖርክ አትርሳት
አንጠልጥለህ አትተዋት
 
አንተ ደግሞ ሴት ልጅ ታቀብጥብናለህ” ነው ያልከኝ፤
“ አንተ ደግሞ ለሴት ታደላለህ ነው” ያልከኝ፤
አዎን
ባስብላት ነቢዩ ናቸው ያሰቡላት
ባዝንላት ነቢዩ ናቸው እዘኑላት ያሉት
ብንከባከባት እርሣቸው ናቸው ተንከባከቧቸው ብለው የመከሩት
አደራ ብል ነቢዩ ናቸው ሞት አፋፍ ላይ ሆነው አደራ ያሉላት፤ 
“ሪፍቀን ቢልቀዋሪር”
“ኡሐሪጅመኩም ሐቅቀ ዶዒፈይን”
“ኢስተውሱ ቢንኒሳኢ ኸይረን”
“ላ የክሪሙሁንነ ኢልላ ከሪም”
ጥቂት በቃሌ የማስታዉሳቸው ሐዲሦች ናቸው፡፡
“እዘኑላቸው አስቡላቸው ጥሩ ሁኑላቸው አክብሯቸው … ነው አጠቃላይ መልዕክቱ

 ሄይ አንቺ ደግሞ

እቀጥላለሁ

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

03 Jan, 18:18


አለች ወላሂ ላላወልቀው
የጌታዬ ትእዛዝ ክብሬ እኮ ነው

መዋቢያየ ነገም ጀነት መግቢያዬ
አለች ስጦታ እኮ ነው ለኔ ከጌታዬ

ሲበዛባት ድብደባው ስቃዪ ሲፈራረቅባት
ምን ትያለሽ ስለ ሂጃብ ብለው ጠየቋት

እሷም መለሰች   እናንተ  አሪያቶች 
ሂጃብ ውድ እኮ ነው ልብሴ የጀነት

  መስሏቸው ነበር የምታወልቀው በስቃይ መብዛት
እሷ እኮ ቆራጥ ለጌታዋ ትእዛዝ  ሙሉ ልቧን የሰጠች ናት !! ።።

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

01 Jan, 20:03


ሌሊቱ የሰማይ ግዛት ላይ ዘምቶ በፀሀይቱ ብርሀን ላይ የፅልመትን ካባ ባከናነበ ቁጥር አላህ ዘውትር እንዲህ ይላል፦

‹‹ፍጥረታት ሁሉ አማፅያን ሁነው ሳለ እንደኔ ሚንከባከባቸው ማን ነው?
በስስት እጠብቃቸዋለሁ፣ ምንም የማያምፁ ፃድቃን ይመስሉ በተኙበት አንዳች መጥፎ እንዳያገኛቸው እሸሽጋቸዋለሁ።

በወንጀል አምፀውኝ እንደማያውቁ ነገር የጥበቃ ሀላፊነታቸውን እኔው እወስዳለሁ። ወንጀለኛ ባርያዬ ላይ ፀጋዬን አልሰስትም፤ ለአጥፊውም እለግሰዋለሁ።

ማን ነው ጠርቶኝ አቤት ያላልኩት!?
ማንስ ነው ጠይቆኝ የነፈግኩት!?
ወይስ ማን ነው ደጄን ጠንቶ ያባረርኩት?

እኔ ቸር ነኝ፤ ቸርነትም ከኔ ይመነጫል። እኔ ለጋስ ነኝ ልግስናም ከኔ ነው ምንጩ።

ከዘመናት የአመፅ ቆይታ በኋላ አመፅን እምራለሁ። ባርያ ጠይቆኝ ብቻ ሳይሆን ሳይጠይቀኝም የምለግሰው ሁላ የቸርነት መገለጫዬ ነው።

ባርያ አምፆ ሲፀፀት፤ ምንም እንዳላመፀ አድርጌ ይቅር የምለውም የቸርነቴ ባህሪ ነው።

ፍጥረታት ከኔ ወዴት ነው እሚሸሹት?
አማፅያኑ ከኔ ደጃፍ ወደየት ነው የሚያፈገፍጉት?  ››


ምንጭ፦
حلية الأولياء  وطبقات الأصفياء

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

01 Jan, 15:19


السلام عليكم ورحمة الله وبركاته  ዉዶቼ ዛሬ ምሽት 3.10 ላይ የጥያቄ እና መልስ ዉድድር አለ  ዉድድሩን ያሸነፈ የ1GB ሜጋ እና የ100 ብር ካርድ ባልተቤት  ይሆናል እናም እንድትሳተፉ ስል በአክብሮት እጠይቃችኋለዉ 🙏

               👇

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

31 Dec, 18:39


...ከንቱ ሆኜ እንዳልቀር የዱኒያ ላይ ጌጥ
በምድራዊ ደስታ ጠልቄ እንዳልሰምጥ
አደራ ረሂሙ በራህመትህ እየኝ
ከውዶችህ መንገድ እባክህ ወፍቀኝ
ሐያቴን በኢማን ሀብቴን በበረካ
ቀልቤን በዲን አጥራው ኑሮዬ እንዲፈካ
ደግሜ ደግሜ ስምህን ጠርቼ
አልሃምዱሊላሂ ልበል አፍ አውጥቼ
አላህ ያ ረሂሙ አላህ ያ ረበና
ላረክልን ሁሉ ይድረስ ምስጋና...!

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

30 Dec, 18:50


ቂያማ ለት አላህ ድኃ ባርያውን ጠርቶ እንዲህ ይለዋል፦‹‹በክብሬ እና በልቅናዬ እምልልኃለሁ፤ አንተን ሳላከብርህ ቀርቼ አይደለም ዱንያ ላይ ድኃ እድርጌ ያኖርኩህ። እዚህ ያዘጋጀሁልህ ክብር እና ምንዳ ይበልጥልኃል ብዬ ነው

ባርያዬ ሆይ! ሂድ ወደ ህዝቡ ተገለጥ። ስለኔ ብሎ ያጎረሰህን እና ስለኔ ብሎ ያለበሰህን ለይተህ ወደ ጀነት ንዳቸው ››

ድኃው ባርያ ይህንን ካደመጠ በኋላ ወደ ህዝቡ ሲሄድ ፀሀይ ከአናታቸው የሚያፈላቸውን ህዝቦች በላቦቻቸው ተጥለቅልቀው ሲተራመሱ ያገኛቸዋል።

ዱንያ ላይ ያበሉትን እና ያለበሱትን እየለየ ከዝያ መከራ ይዟቸው ይወጣ'ና ወደ ቀዝቃዛይቱ ጀነት ያቀናል።

ይህን ሀዲስ ከተናገሩ በኋላ ረሱል ሰዐወ እንዲህ አሉ፦‹‹የድኃ ጓደኞችን አብዙ፤ የቂያማ ለት ግዛቱ የነሱ ነው'ና››

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

29 Dec, 17:13


አየህ አይደል 💕

አየኸው ወንድሜ ሀዲሱን ሰማኸው
ከዱኒያ በላጯ መልካሚቱ ሚስትህ
መሆኑን አወከው
እናስ ምን ላድርገው ብለህ እትዳትከሰኝ
በደንብ ላስረዳህ ጆሮህን አውሰኝ
እናማ የምልህ ላንተ የምመክረህ
ከውዷ ሚስትህ ጋር መቻቻል ይኑርህ
እሷ ስትከፋ ሀዘኗን ተካፍለህ
እሷ ስትደሰት  አንተም ተደስተህ
የዛሬውን ሳይሆን አኼራን አስታውሰህ
ጥሩ ባል ሁንላት አላህንም ፈርተህ
ሀዲስ ቁርአንን ዲኗን አስተምራት
መልካም ሴት እንድትሆን ኢማን እንዲኖራት
ሀራምና ሀላል ለይታ ካወቀች
ዲኗን የተረዳች መልካም ሴት ከሆነች
እሷም በበኩሏ አንተን አስደስታ
ሁሌም ትኖራለች ፈጣሪዋን ፈርታ
ሷሊሆች ሁናችሁ መኖርን አስቡ
ከሙእሚኖች ጋራ ጀነት እንድትገቡ
ይህ ሁሉ ምክር ይህ ሁሉ ሀተታ
ለእኔ እና ላንተ ነው በትዳርህ በርታ
አየህ አይደል ሁሉን የአላህን ፀጋ
ትዳር መስርት ሲልህ እንድትረጋጋ
ነገ በአኼራ አለውና ዋጋ
ሁሉም ሰው ይሯሯጥ አጅሩን ፍለጋ

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

28 Dec, 19:49


ምድር ከመስፏቷም ጋር ባንተ ከጠበበችብህ፣ ባልደርባህ ደልቶት አንተ
ከተቸገርክ ተጣሪህን፦‹‹ያ ሀዩ ያ ቀዩም በእዝነትህ እታገዛለሁ ›› እያልክ
ጥራው።
ህይወት ፊቷን አዙራብህ እድለ ቢስነትህ ሲበረታ እጅህን ከከፍታው አኑረህ፦‹‹ያ
ሀዩ ያ ቀዩም በእዝነትህ እታገዛለሁ ›› እያልክ ተጣራ።
በሮች ሁላ ከፊትህ ተዘጋግተው መግቢያ መውጫ ብታጣ ፤ ወደ ባለ ብዙ በሩ
ጌታ ተጠግተህ፦‹‹ያ ሀዩ ያ ቀዩም በእዝነትህ እታገዛለሁ ›› እያልክ
አንሾካሽክለት።
ጓደኛ ከድቶህ ፣ ወዳጅህ አሲሮ መንገዶችን ሁላ ሲዘጉብህ ፤ ከመንገድህ
ቁመህ፦‹‹ያ ሀዩ ያ ቀዩም በእዝነትህ እታገዛለሁ ›› ብለህ ተማፀነው።
ሪዝቅህ ተቋርጦ፣ ገንዘብም አጥሮህ፣ እዳዎች ባካበቡህ ግዜ እጅህን ከፍ
አድርገህ፦‹‹ያ ሀዩ ያ ቀዩም በእዝነትህ እታገዛለሁ ›› ስትል ተጣራ።
በሰው መሀል ሁነህ ብቸኝነት በተሰማህ ግዜ፣ ሁሉ ኖሮህ ሰላም ባጣህ ግዜ፣
ሰላም ኖሮህም ገንዘብ ባጣህ ግዜ፤ ወገብህን ሰበር እጅህን ከፍ አድርግና፦‹‹ያ
ሀዩ ያ ቀዩም በእዝነትህ እታገዛለሁ ›› ስትል የይድረሱልኝ ጥሪህን አሰማ።
ህሊናህ አላርፍ ብሎ፣ ኢማንህ ጎሎ ወደጌታህ መመለስን ሽተህ ግና መመለስ
ተነፍጎህ ልብህ ጥብብ ጭንቅ ባለው ግዜ ወደ ጌታህ መመለሻ መንገድ
ሲጠፋህ፦‹‹ያ ሀዩ ያ ቀዩም በእዝነትህ እታገዛለሁ ›› እያልክ ደጋግም።
ሚድያው አድክሞህ፣ ቁርአን ናፍቆህ የቀደመ ኢማንህን ባሰብክ ግዜ ሀፍረት
ከተሰማህ ወደ ቀድሞ የኢማን ከፍታህ ለመመለስ፦‹‹ያ ሀዩ ያ ቀዩም በእዝነትህ
እታገዛለሁ ›› እያልክ ታገዝ።

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

27 Dec, 18:28


ይሁን እንጂ ረሱል (ሰዐወ) ጥሪያቸውን እና ጣኦት ማውገዛቸውን አላቆሙም
ነበር።ይህ ያሳሰባቸው የቁረይሽ ባላባቶች የረሱል (ሰዐወ) አጎት ወደሆነው አቡ
ጣሊብ ዘንድ በመሄድ፦"አባ ጣሊብ ሆይ! ይህ የወንድምህ ልጅ አማልክቶቻችንን
እየሰደበ ነው...።ሀይማኖታችንን እያንቋሸሸ ነው...።ህልማችንን እያመከነ
ነው...።ቀደምት አባቶቻችንን ጥመት ላይ ነበሩ እያለ ነው...። ስለዚህ አስቁምልን
አይ የምትል ከሆነ ለኛ ተውልን" አሉ። አቡ ጣሊብም አረጋግቷቸው መለሳቸው።
ረሱል (ሰዐወ) ግን ዳዕዋቸውን አጧጡፈው ተያይዘውታል...።ቁረይሾቹ ይሄ
ጉዳይ ምንም አላማራቸውም ነበር'ና ዳግም አቡ ጣሊብ ዘንድ በመሄድ፦"አባ
ጣሊብ ሆይ! የወንድምህን ልጅ አስቁምልን ብንልህ ዝም አልከን...።እኛ
አባቶቻችን ጥሜት ላይ ነበሩ ሲባል እና አማልክቶቻችን ሲሰደቡ ማየት
አልቻልንም። አባ ጣሊብ ሆይ! አንተ እኛ ዘንድ የተከበርክ እና በእድሜም የገፋህ
ነህ አክብረንሀል። አሁን ግን ወይ ሙሀመድን አስቁምልን ወይም ደም
እንፋሰስ'ና ወይ እናንተ ወይ እኛ እናልቃታለል" አሉ።
ይህን ግዜ አቡ ጣሊብ ረሱልን (ሰዐወ) አስጠራቸው'ና፦"የወንድሜ ልጅ ሆይ!
ቁረይሾች መጥተው (እንዲህ እንዲህ...) ብለው ዝተው ሄደዋል...።ልጄ
ተዋቸው እንጂ...፣ በደከመ እድሜዬ የማልቋቋመውን አታሸክመኝ...፣አማልክቶ
ቻቸውንም አትንካባቸው....፣የሚጠሉትንም (ላኢላሀ ኢለላህ) ንግግር
አትናገር..." በማለት መከራቸው።
ረሱልም (ሰዐወ) ፦" ወላሂ ነው ምልህ አጎቴ ፀሀይን በአንድ እጄ ጨረቃን በአንድ
እጄ ቢያስጨብጡኝ ይህን ጉዳይ አልተወውም። ወይ አላህ ጉዳዩን ያስፋፋልኛል፤
ወይም እነሱ እኔን ይገድሉኛል" አሉት።
አቡ ጣሊብም፦"እንደፈለግክ ሁን የፈለግከውንም ስራ...፤ ወላሂ እኔ አንተን
ለማንም አሳልፌ አልሰጥህም" አላቸው።
(እእእ...ደከማችሁ አይደል !!! እኔም ደክሞኛል ወላሂ ግን መቆሚያዋን እስክደርስ
ነው. ..። ደሞ እኮ ደከመን እንጂ አልሰለቸንም...አይደል!!!? በቃ ትንሽ ብቻ
ኑ...ደርሰናል።)
ቁረይሾች ምንም እንኳን ሙሀመድን ለማታለል ብዙ ብልጭልጮችን
ቢጠቀሙም እሳቸው ግን ከቆብ አልቆጠሩትም።ረሱል (ሰዐወ) አጋጣሚዎችን
እየተጠቀሙ ተከታዮቻቸውን ማበራከትን ተያያዙት።
አሁን የሀጅ ስነስርአት ተቃርቧል...። የሀጅ ወር ሲገባ አረብ የተባለ ሁሉ
ከነመሪዎቻቸው መካ በመምጣት ያሳልፋሉ...። ቁረይሾች ግን እጅጉን
ሰግተዋል...ምናልባት ለሀጅ ስነስርአት የሚመጣው የዐረብ ነገድ የሙሀመድን
ጥሪ ሰምተው እንዳይቀበሉትም እጅጉን ስጋት አድሮባቸዋል።
ከዚያም ለሀጅ የሚመጡ ዐረብ ነገዶች የሙሀመድን ጥሪ እንዳይሰሙ ምን
ማድረግ አለብን በማለት በእድሜ ከሚበልጣቸው ከወሊድ ኢብን ሙጊራ ዘንድ
ተሰባሰቡ።
ግማሹ፦" ሙሀመድ ጠንቋይ ስለሆነ ወሬውን እንዳትሰሙ ብለን ስሙን እናጥፋ"
ሲሉ ግዜ...
ወሊድ፦"አረ እሱ እንደጠንቋይ እኮ አይደለም። ጠንቋይ ሲያዜምም
ሲያጉረመርምም ተመልክተን የለ እንዴ!!!" በማለት ሌለ ሀሳብ እንዲመጡ
ጠየቀ።
እነሱም፦"በቃ ሙሀመድ እብድ ነው እንዳትሰሙት እንበል" ተባባሉ።
ወሊድም፦"አረ ይሄም አያስኬድም እብድ ምን አይነት እንደሆነ አይተን የለ እንዴ"
አላቸው።
እነሱም፦"በቃ ሙሀመድ ገጣሚ ነው እንዳትሰሙት እንበል" ተባባሉ።
ወሊድም፦"ስለ ግጥም እና ስለገጣሚ ማያውቅ አለ እንዴ!!! ሙሀመድ
ሚናገረው እኮ ግጥም አይደለም" አላቸው።
እነሱም፦"እሺ ድግምተኛ ነው እንበል" አሉት
ወሊድም፦"ስለድግምትስ ማን የማያውቅ አለ'ና ነው ድግምተኛ ምትሉት"
አላቸው።
እነሱም፦"እሺ ምን ብለን ነው በዐረብ ነገዶች ዘንድ ስሙን የምናጠፋው?"
ብለው ሲጠይቁት...
ወሊድም፦"ይህን የጠቀሳችሁትን ሁሉ ብታወሩ ማንም ሊያምንላችሁ አይችልም
ትንሽ ያምንላችኋል ብዬ የምገምተው፤ እኛን እንደከፋፈለን ሁላ (ባልን
ከሚስት...፣ ወላጅን ከልጅ... የሚከፋፍል ደጋሚ ነው) እንላለን" ብሎ
ሲነግራቸው በሱ ተስማሙ።
_
ለዛሬ እዚ
ህች ጋ እናቁም'ና ነገ አላህ ካለ የዐረብ ነገዶች ለሀጅ መካ ሲመጡ
የሚከሰተውን እንመለከታለን።ደሞ በዛውም እኛም ሀጅ እናደርጋለን እንዳትቀሩ
ሀ..!!! ክክክ..
ነገ በተመሳሳይ ሰዓት እስክንገናኝ ሰላማችሁ እና ደስታችሁ ይብዛ

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

27 Dec, 18:28


እያንዳንዱን የቁረይሽ ጎሳ መሪ ጠርተው የፎጣውን ጫፍ እንዲይዙ ካደረጉ በኋላ
ሁሉም የያዙትን የፎጣውን ጫፍ ተቸክመው ወደ ካዕባ እንዲጠጉ አደረጉ።
ከዚያም በሁሉም ጎሳዎች ተይዞ በፎጣው የተጠጋውን ሀጀረል አስወድ ረሱል
(ሰዐወ) በተከበረችው እጃቸው አንስተው ካዕባ ላይ አሳረፏት።
ከዚህ በኋላ ረሱል ሁኔታቸው እየተቀያየረ መጣ...።ብቸኝነትን የቅርብ ጓደኛም
አድርገው በመያዝ ስለዚህ ፍጥረተ አለሙ አፈጣጠር እና ስለፈጣሪው በጥልቀት
ማሰላሰል ጀመሩ።
አብዝሀኛውን ግዜ ከሰዎች ተነጥለው ስለፍጥረተ አለሙ እና ስለ አስተናባሪው
ለማስተንተን ትልቁን ተራራ ስንቃቸውን ይዘው በመውጣት ሌት ተቀን ሂራእ
በሚባል ዋሻ ውስጥ ያሳልፉ ጀመር።
ሁሌም ወደዚያ ዋሻ ሲሄዱ መንገድ ላይ አንድ ሰላምታ የሚያቀርብላቸው ድንጋይ
አለ።ሁሌም ያስታውሱታል።
አሁን አሁን ነገሩ ሊገላለጥ እየተቃረበ ነው...።ረሱልም (ሰዐወ) በህልማቸው
ያዩትን ሁሉ በጋሀዱ አለም መመልከት ጀምረዋል።
በወረሀ ረመዳን (በአርባኛው አመታቸው) ከእለታት አንድ ቀን ረሱላችን (ሰዐወ)
እንደወትሮዋቸው እዚያ ዋሻ ውስጥ ሆነው በማስተንተን ላይ ሳሉ ድንገት
ጂብሪል በሰው ተመስሎ ወደ ዋሻው ዘልቆ ገባ።
ከዚያም ልክ እንደገባ ምንም ሳይናገር፦"አንብብ" አላቸው።
እሳቸውም፦"ማንበብ አልችልም" አሉት..።
እሱም አንድ ግዜ ወደሳቸው ጠጋ አለ'ና እቅፍ በማድረግ በጣም ጨመቃቸው።
ከዚያም ለቀቅ አደረጋቸው'ና አሁንም፦"አንብብ" አላቸው።
ረሱልም፦"እኔ ማንበብ አልችልም" አሉት...።
ይህን ግዜ ጂብሪልም እንደቅድሙ በተደጋጋሚ ግዜ እየጨመቀ ካለማመዳቸው
በኋላ ለቀቅ አደረጋቸው'ና፦" አንብብ በዚያ (ሁሉን) በፈጠረው ጌታህ ስም፡፡
ሰውን ከረጋ ደም በፈጠረው (ጌታህ ስም)፡፡
አንብብ፤ ጌታህ በጣም ቸር ሲኾን..." የሚል የቁርአን አንቀፅ አወረደላቸው።
ይህን ግዜ ረሱል (ሰዐወ) በፍጥነት እየተንቀጠቀጡ ወደ ቤት መጡ።እቤት
ከዲጃ ነበረች ወዲያ ፍራሻቸው ላይ በመተኛት፦"አከናንቡኝ....አከናንቡኝ...."ማለ
ት ጀመሩ ..። ከዲጃም አከናነበቻቸው'ና ሲረጋጉ የሆኑትን ሁሉ ነገሯት።
እሷም ብልህ እና አስተዋይ ናት'ና የቀድሞው መልካም ስነ ምግባራቸውን
በማስታወስ አላህ ለመጥፎ አሳልፎ እንደማይሰጣቸው አፅናናቻቸው።
ይህን ጣፋጭ ንግግር ከከዲጃ አንደበት ሲሰሙ ረሱል (ሰዐወ) መረጋጋት
ሰፈነባቸው።ከዚያም በማስተዋል ያጋጠማቸውን ክስተት ማስተንተን ጀመሩ።
ከዲጃ ምንም እንኳን ውድ ባለቤቷን ለማፅናናት እንዲህ ብትናገርም ነገሩ
እረፍት ስላልሰጣት ረሱልን (ሰዐወ) ይዛ የክርስትና እምነት ላይ ወዳለው እና
በድንቁርናው ዘመን ስለ ራዕይ (ዋህይ) እውቀት ወዳለው አጎቷ (ወረቃ እብን
ነውፈል) ይዛቸው ሄደች።
ከዚያም፦" አጎቴ...እስቲ ሙሀመድ ሚልህን ስማው" አለችው።
አጎቷም፦"ልጄ ምን ገጠመህ" ብሎ ጠየቀው።
ረሱልም (ሰዐወ) በጣፋጭ አንደበታችው ክስተቱን ዘርዝረው ነገሩት።
ወረቃም፦"ይህማ በሙሳ ላይ ይወርድ የነበረው መንፈስ ነው። እኔ በህይወት
ቆይቼ ባንተ ነብይነት ባምን እና ህዝቦችህ ከሀገር ሲያባርሩህ ከጎንህ ሆኜ
ብረዳህ ምንኛ በታደልኩ" አለው
ይሄን ግዜ ረሱል (ሰዐወ) ድንግጥ አሉ...።(እኔ ልደንግጥሎት) ከዚያም ወደ
ወረቃ ዞር በማለት፦"ወገኖቼ እኔን ከሀገሬ ያስወጡኛል???" ብለው ጠየቁት።
ወረቃም፦"አዎን...እንዳንተ ያለ ተልዕኮ ይዞ የመጣን ሰው ሁሉ ይዋጋዋል"
አላቸው። ከዚያ በኋላ ረሱል (ሰዐወ) ያ ራዕይ ናፈቃቸው...ያ አንብብ የሚለው
መልዐክ እጅጉን ናፈቃቸው።
ከእለታት አንድ ቀን ረሱላችን (ሰዐወ) መንገድ ላይ ሳሉ የሆነ ድምፅ ከወደ
ሰማይ በኩል ሰሙ። የሰሙትንም ድምፅ ለማጣራት ወደ ላይ ቀና ሲሉ ያን
መልዐክ በምድር እና በሰማይ መሀክል በዙፋን ተቀምጦ ተመለከቱት....ትዕይንቱ
በጣም ያስፈራ ነበር።
ከዚያም ወደ ቤት በመገስገስ ከዲጃን ጠርተዋት፦"ልብስ ደርቢልኝ...ልብስ
ደርቢልኝ..." አሏት እና ደራረበችላቸው።
ልክ እንደተኙትም ጂብሪል መጣ'ና፦" አንተ (ልብስህን) ደራቢው ሆይ!
ተነሳ አስጠንቅቅም፡፡
ጌታህንም አክብር፡፡
ልብስህንም አጥራ፡፡
ጣዖትንም ራቅ" አለው።
ከዚያ በኋላ ረሱል ዳዕዋ የማድረግ ግዳጅ እንደተጣለባቸው ተገነዘቡ።ያኔ
ዳዕዋውን ከጎናቸው ባለው ሰው መጀመር ፈለጉ'ና ከዲጃን ወደ አላህ
ጠሯት....እሷም ለአላህ ጥሪ እጅ ነሳች።
የቅርብ ጓደኛቸውን እና በምልካም ስነምግባሩ እውቅ የሆነውንም አቡ በክርንም
ወደ አላህ ጠሩ እሱም ለአላህ ጥሪ አጎበደደ።ዐሊይ ኢብን አቡ ጣሊብም
የአስራ ሁለት አመት ልጅ ሲሆን ወደ አላህ ጠሩት እሱም ለጥሪው እጅ ነሳ።
ከዚያም አቡ በክርም ከዙሪያ ያሉትን ሰዎች በሚስጥር ወደ አላህ መጣራት
ጀመረ....
ዐብዱረማን ኢብን ዐውፍ
ዑስማን ኢብን ዐፋን
ዙበር ኢብኑል ዐዋም
ጠልሀ ኢብን ዑበይዲላህ....እና በርካታ ሰዎች በአቡ በክር አማካኝነት ዲኑን
ይቀላቀሉ ጀመር።
ያን ግዜ ሰላት እኛ በምናውቀው አይነት አልተወሰነም ነበር። ብቻ ጎህ ከመቅደዱ
በፊት እና ጀንበር ከመጥለቋ በፊት ሁለት ሁለት ረከዐ በረሱል (ሰዐወ) መሪነት
በድብቅ ይሰግዱ ነበር።
ከእለታት አንድ ቀን ረሱል (ሰዐወ) ከሰሀቦች ጋር በድብቅ ሲሰግዱ የሳቸው አጎት
የሆነው አቡ ጣሊብ ብቅ አለባቸው።ሰላታቸውን እስኪያጠናቅቁ ከጠበቀ
በኋላ፦"ምን አይነት አዲስ ሀይማኖት ነው?" በማለት ረሱልን (ሰዐወ)
ጠየቃቸው።
ረሱልም (ሰዐወ) በመለሳለስ ካስረዱት በኋለ ወደ ኢስላም ጥሪ አደረጉለት።
ይሁን እንጂ የአባቶቼን ሀይማኖት አልለቅም በሚል ደባሪ ምክንያት ጥሪውን
መቀበል እንቢ ብሎ ልጁን ዐሊይን ግን ከረሱል (ሰዐወ) እንዳይለይ መከረው።
የሰሀቦችም ቀጥር ቀን በቀን እየጨመረ በየግዜው እና በየአጋጣሚው
የሚወርደው የቁርአን አንቀፅ በሶስት ወር ውስጥ ልባቸውን በኢማን
አጠነከረው።
ከዚያም አላህ ረሱልን (ሰዐወ) የቅርብ ዘመዶቻቸውን ዳዕዋ እንዲያደርጉላቸው
አዘዛቸው።ረሱል (ሰዐወ) ዋዛ አይደሉም'ና ገራሚ ስልት ነበር የተጠቀሙት።
አንድ ተራራ ላይ በመውጣት የመካን ህዝብ ተጣሩ....።ከዚያም ሁሉም
ተሰበሰበ...ረሱል (ሰዐወ)፦" ወገኖቼ እኔ እናንተ ዘንድ ታማኝ አይደለሁምን?"
አሉ። ሁሉም፦"ነህ" ብሎ መሰከረላቸው...።
ከዚያም ረሱልም፦"ወራሪዎች ሊወሯችሁ እየመጡ ነው ብላችሁ አተምኑኝምን?"
አሏቸው። ሁሉም፦"እናምናለን" በማለት መለሱላቸው,,,።
ያን ግዜ ረሱል (ሰዐወ)፦"የበኒ ካዕብ ጎሳዎች ሆይ! እራሳችሁን ከእሳት አድኑ...።
የዐብድ ሸምስ ጎሳዎች ሆይ! እራሳችሁን ከእሳት አድኑ...።
የበኒ ዐብድ መናፍ ጎሳዎች ሆይ! እራሳችሁን ከእሳት አድኑ...።
የሀሺም እና የዐብዱል ሙጠሊብ ጎሳዎች ሆይ! እራሳችሁን ከእሳት አድኑ...።
አንች ልጄ ፋጢማ ሆይ! ነፍስሽን ከእሳት አድኚ። እኔ ለማናችሁም አላህ ዘንድ
ልጠቅማችሁ አልችልም። ዝምድናውን እንኳን እዚህ ብቻ ነው የምቀጥለው"
በማለት ተጣሩ።
ይህ ንግግር በቁረይሽ ወራዳዎች ላይ እንደ መብረቅ ነበር
ያስበረገጋቸው።የረሱልንም ጥሪ ምላቹን ፌዝ እና ማላገጥ አደረጉባቸው።

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

27 Dec, 18:28


እሽ አሁን ከረሱላችን (ሰዐወ) ጋር በምናባችን ጉዞ ወደ ሻም ልንጀምር
ነው።እእእ...ሁላችሁም ተዘጋጅታችኋላ...charger ምናምን ይዛችኋል??? እሺ
ሀያ ፊ አማኒላህ...!!!
ረሱል (ሰዐወ) ከከዲጃ በተስማሙት መሰረት የሷን ንግድ ተገባይተውላት
ሊመለሱ ከቁረይሽ ነገዶች ጋር የሻምን ረጅሙን ጉዞ በጠዋት መጓዝ ጀመርዋል።
ከረሱል (ሰዐወ) ጎን ለጎን አንድ መይሰራ ሚባል የከዲጃ አገልጋይ
ይራመዳል።ሁሉም በንቃት እና በሞራል የመኪናን ጎማ የሚፈትነውን የዐረቢያን
አሸዋ በእግር እያቆራረጡ በፍጥነት በመጓዝ መንገዱን ተያይዘውታል።
ከላይ ፀሀይዋ የምትለቀው ንዳድ ከአሸዋው ግለት ጋር ተዳምሮ እጅጉን አስቸጋሪ
ጎዞ ነበር።ይሁን እንጂ የአየሩን ሁኔታ ችላ በማለት ጎዞዋቸውን በመቀጠል እጅግ
ብዙ መንገድ ካቋረጡ በኋላ አንድ ዛፎች ያሉበት ቦታ ደረሱ'ና ሁሉም እዚያ ቦታ
ላይ እረፍት ለማድረግ ተሰበሰበ።
ረሱላችንም (ሰዐወ) ከቀዬያቸው ሰዎች ነጠል በማለት አንዲት ጥላ ስር ሄደው
ቁጭ አሉ።(ሳሉት እስቲ በምናባችሁ...ሌላው ለእረፍት ተሰብስቦ ሲሳሳቅ እና
ሲጫወት እሳቸው ዝም ብለው ብቻቸውን ቁጭ ብለዋል።ኡፍፍፍፍ ሄጄ
በሳምኳቸው...!!!)
ከዚያም ረሱል (ሰዐወ) ቁጭ ካሉበት የዛፍ ጥላ አቅራቢያ ላይ አንድ መናኩሴ
ትንሽ ጎጆ ነገር ውስጥ ቁጭ ብሏል። እሳቸውን ሲመለከት በድንጋጤ ስሜት
እራሱን መቆጣጠር እየተሳነው ብዙ ከተመለከታቸው በኋላ መይሰራ ወደተባለው
የከዲጃ አገልጋይ ዘንድ ጠጋ በማለት፦"ይህ እዚያች ጥላ ስር ቁጭ ያለው ማን
ነው?" ብሎ ጠየቀው።
መይሰራ'ም፦ይህ ቁረይሻዊ ሰው ሲሆን የሀረም ቤተሰብም ነው" በማለት
መለሰለት።
መናኩሴውም፦"በዚህች ጥላ ስር ነቢያት እንጂ ማንም አልተቀመጠባትም"
ብሎ ሄደ።
አሁን ሁሉም ሚበቃውን ያህል አርፏል ግመሎቻቸውን በመፍታት ዳግም ጉዞ
ጀመሩ።አሁንም በዚሁ ሁኔታ እያረፉ ብዙ ከተጓዙ በኋላ የንግድ ከተማ
የሆነችውን የሻምን ምድር ደረሱ።
ልክ ከተማዋን እንደረገጡ ሁሉም ገበያ ሲገባ ሊገበያይ ይበታተናል።ረሱልም
(ሰዐወ) ግብይታቸውን ሊጀምሩ መይሰራን ይዘውት ወደ መሀል ገበያ ዘልቀው
ገቡ።እሳቸው ሲገበያዩ የስነምግባራቸው ምጥቀት የመይሰራን ትኩረት ሙሉ
በሙሉ ተቆጣጥሮታል።
ታማኝነታቸው..፣ቅንነታቸው...፣የአነጋገር ብስለታቸው...በቃ ሁለንተናዊ
ባህሪያቸው መይሰራን ስራ ትቶ እሳቸውን እንዲመለከት አስገድዶታል።
በዚህ ሁኔታ ለተወሰኑ ቀናት ከተገበያዩ በኋላ የነጋዴዎቹ የመመለሻ ቀጠሮ
ደረሰ'ና ሁሉም የሸመተውን ሸምቶ የሸጠውን ሽጦ በትርፍ ሲመለሱ የረሱል
የንግድ ስኬት ግን ከሁሉም በተሻለ መልኩ በእጥፍ ትርፋማ ነበር።
ረሱልን (ሰዐወ) በስሩ ያቀፈው የነጋዴዎች ጉዞ የዐረቢያን ጋራ ተራራውን ለቀናት
በማቆራረጠ ጎዞ ጀመረ። (ነግሪያችኋለሁ የዐረብያ ምድር አሸዋው በጣም ከባድ
ነው።ፀሀዩም አይቻልም...እዚያ ያላችሁ ታውቃላችሁ።) በዚህ አስቸጋሪ የአየር
ፀባይ ሁሉም የፀሀይዋን ሀሩር በፀጋ ተቀብሎ ግመሎችን መንዳት ተያይዟል።
በዚህ መሀል ረሱል (ሰዐወ) በዝምታ እና በእርጋታ ሲጓዙ አንዲት ዳመና በስቸው
እስትሬት በመሆን ከፀሀዩ ንዳድ እሳቸውን ብቻ በማስጠለል እስከ መካ ድረስ
ትሸኛቸው ጀመር።ሁሉም በአግራሞትት ይመለከታቸዋል።
የተጓዥ ነጋዴው ቡድን እልህ አስጨራሹን ጎዞ ካጠናቀቁ በኋላም ወደ መካ
ከተማ በሰላም ደረሱ።የመካ ነዋሪያን የሸቀጦቻቸውን ነጋዴዎች ለመቀበል
በሰልፍ ቆመው ነበር።
ነገዴዎቹ ከሻም ምድር ሸቀጦችን ይዘው መካ በመግባታቸው ነዋሪያኑን እጅጉን
አስፈንጥዞታል።በዚህ መሀል ባለፀጋዋ እና ከበርቴዋ ከዲጃ የንግዱን ሁኔታ
ልትመለከት ሸቀጧ ጋ ስትመጣ ከጠበቀችው በላይ ትርፋማ ሆኖ አገኘችው።
ከረሱላችን (ሰዐወ) ጋርም አብሯቸው የሄደው የከዲጃ አገልጋይ መይሰራም
ስለአስደናቂው ባህርያቸው...፣መናኩሴው ያለውን እና ስለዳመናዋም በዝርዝር
ነገራት።
ከዲጃ መይሰራ ስለረሱል (ሰዐወ) የሚነግራትን በተመስጦ ትሰማው ነበር።ይህን
ታማኝ እና መልከ መልካም ሰው የራሷ፤ የግሏ ልታደርገውም ወሰነች።
ከዚያም ከዲጃ፤ ነፊሳ ቢንት ሙነቢህ ወደተባለችው ጓደኛዋ ዘንድ በመሄፍ
ሁኔታውን አጫወተቻት።ከዚያም ረሱል (ሰዐወ) ዘንድም ጥያቄው
ቀረበላቸው።እሳቸውም ከዲጃን ጠንቅቀው ስለሚያውቋት መርሀባ አሏት'ና
ለአጎቶቻቸው አቡ ጣሊብ ከዲጃን ማግባት እንደሚፈልጉ አሳወቁ።
የረሱል (ሰዐወ) አጎቶችም በሁኔታው ተደስተው የከዲጃን ቤተሰብ ለማስፈቀድ
አቡ ጣሊብን ያካተተ የሽማግሌ ቡድን እነ ከዲጃ ቤት ላኩ።
ልክ እቤት ሲገቡም ምንም ሳያወሩ አቡ ጣሊብ፦"የኢብራሂም ዘሮች እና
የኢስማዒል ልጆች ላደረገን ጌታ ምስጋና ይገባው።ለኛም በአመት የሚግ'ጎበኝን
ቤት ለሰጠን እና ላከበረን ጌታ ምስጋና ይገባው።
እኛንም የዚያን ቤት(ካዕባ) አገልጋዮች እና የሰዎች ሁሉ ፈራጅ ላደረገን ጌታ
ምስጋና ይገባው።
በመቀጠልም እነሆ የወንድማችን ልጅ የሆነው በመልካም ስነ ምግባሩ እና
በታማኝነቱ ድፍን መካ የምትመሰክርለት የሆነው ሙሀመድ ኢብን ዐብዱላህ፤
ምንም እንኳን ያ ጠፊ አላቂ የሆነው ገንዘብ ባይኖረውም ለሷ ጌጥ ግን አሁንም
ሆነ ወደ ፊት በማሟላት ሊያገባት አስቧል። ይህ ልጅም ወደፊት ትልቅ
ሚስጥርም ይኖረዋል" በማለት ሽምግልናውን ጀመረ።
የከዲጃ ቤተሰብም ሙሀመድን (ሰዐወ) በፊትም ጠንቅቀው ስለሚያውቁት
ልጃቸውን ሳያቅማሙ በደስታ ዳሯት።(ወጣቶች ሆይ!!! ሙዳችሁን አስተካክሉ
ብያችኋለሁ ..!!! ሙዳችሁ ፒስ ከሆነ ዘዋጅ ላይ እንኳን ሽማግሌዎቻችሁ
አያፍሩም።)
ከዚያም ረሱል (ሰዐወ) ከዲጃን አግብተው የመካ ህዝብ ኖሮ የማያውቀውን
የተረጋጋ እና በፍቅር የተሞላ ኑሮ መኖር ጀመሩ።በዚህ መሀልም አላህ 6 ልጆችን
ሰጣቸው፦"
1፦ዘይነብ
2፦ሩቀያ
3፦ኡሙ ኩልሱም
4፦ፋጢማ
5፦ዐብዱላህ
6፦ቃሲም....በመባል ይታወቃሉ።
(ቆይ አረ ተረጋጉ...!!! አሁን የረሱልን ልጆች ስም ጥሩ ብትባሉ ትጠራላችሁ?
የምትጠሩ ብትኖሩም የማንጠራም አለን። ስለዚህ ዳግም ስሞቹን አንብቡና
ኑ....)
ከእለታት አንድ ቀን የመካ ነዋሪያን ካዕባን በማደስ ላይ ሳሉ ሀጀረል አስወድን
(ከካዕባ ታች በኩል ያለው ጥቁሩ ድንጋይ) ማን ያስቀምጥ በሚል በጣም
ተጨቃጨቁ።ለጦርነት ሁላ እስገመገባበዝ ጎሳዎቹ ተጋጋሉ።
በመጨረሻም ሁሉም ጎሳውን በማረጋጋት፦"በቃ በዚህ በር ቀድሞ የመጣ ሰው
ሀጀረል አስወድን ያስቀምጣል" በማለት ተስማሙ።
ሁሉም ቁጭ አለ...።ማን ይሆን በዚህ በር በመግባት ይህን የላቀ ክብር
ሚቀዳጀው በማለት በጉጉት በር በሩን ማየት ጀምረዋል።
ብዙም ሳይዘገይ ሁሉም ተመልካች አንድን ሰው በበሩ ሲገባ አይተው ፊታቸው
በደስታ ፈካ....።ሁሉም የሀጀረል አስወድን ክብር ለዚያ ሰው ለማስረከብ ደስተኛ
ሆኑ....።እንዴት አይሁኑ...!!! ሙሀመዱል አሚን እኮ ናቸው።
ከዚያም ረሱል (ሰዐወ) ሀጀረል አስወድን በካዕባ ታች እንዲያኖሩ ሲጠየቁ
በቁረይሽ ጎሳዎች መሀክል አለመስማማት መፈጠሩን በመረዳት የለበሱትን
ሪዳእ (ፎጣ) ከትከሻቸው አውልቀው መሬት ላይ አነጠፉት።
ከዚያም ሀጀረል አስወድን (ድንጋዩን)ብድግ አድርገው በፎጣው በማሳረፍ

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

26 Dec, 16:08


አልሆኑም።
ሁሉም አሳዳጊ ህፃናቱን ይዞ ወደ ሀገሩ ሊንቀሳቀስ ሲል ሀሊማ የተባለች እድለኛ
የህፃናቱን ገበያ ገብታ ረሱልን (ሰዐወ) ብቻ ስታገኝ ባዶ እጄን ከምመለስ ብላ
ይዛቸው ከአከባቢዋ ሰዎች ጋር ጉዞ ጀመረች።
ረሱል (ሰዐወ) ልክ የአሳዳጊያቸውን ሀገር ሲደርሱ ለዘመናት በድህነት
የሚታወቀው የአሳዳጊያቸው የሀሊማ ቤት በጥጋብ ደስታ ተሞላ።የሀሊማ ቤት
ታይቶ በማያውቅ የበረካ መዐት አሸበረቀ።በዚህ ሁኔታ ረሱል (ሰዐወ) እዚያው
ገጠር ውስጥ አድገው ከህፃናት ለመጫወት በቁ።
ከእለታት አንድ ቀን ረሱል (ሰዐወ) ከጥቢ ወንድማቸው(ከሀሊማ ልጅ) ጋር
ለመጫወት ከቤት ራቅ ብለው ሳለ ሁለት መላዕክት በሰው ተመስለው
መጡ።ረሱላችንንም (ሰዐወ) ወደ ዳር አወጧቸው'ና ደረታቸውን መሰንጠቅ
ጀመሩ።
ይህ ሁሉ ሲሆን የረሱል የጥቢ ወንድም በቅርበት እየተከታተለ ነበር።በፍጥነት
ወደ እናቱ በመሄድ፦"ሙሀመድን ሁለት ሰዎች አስተኝተው እየገፈፉት ነው"
አላት።
እሷም በድንጋጤ ስትሮጥ ረሱል (ሰዐወ) ወዳሉበት ቦታ ገሰገሰች።ቦታው ላይ
ስትደርስ ረሱልም (ሰዐወ) በድንጋጤ ተሞልተው ቆመው አገኘቻቸው።
ከዚያም በፍቅር እና በስስት አቅፋቸው፦"ምን ሆብክብኝ ልጄ!!!" ብላ
ስትጠይቃቸው ..ረሱልም በጣፋጭ አንደበታቸው፦"ከወንድሜ እየተጫወትን ሳለ
ሁለት ሰዎች(ጂብሪል ሚካኢል) ድንገት መጡ።ከዚያም አስተኝተዉኝ ደረቴን
ለሁለት ከከፈሉት በኋላ የሆነ ጥቁር ነገር ከደረቴ ፈልገው አወጡ።ከዚያም
በጣም ነጭ እና የሚያምርም ነገር በቦታው ተክተው ደረቴን እንደነበር መልሰው
ሄዱ" ብለው ነገሯት።
ከዚያም ሀሊማ ረሱልን (ሰዐወ) በእቅፏ አስገብታ እቤት አመጠቻቸው።ይህን
ግዜ ባለቤቷ፦"ሀሊማ ይህን ልጅ ለወላጆቹ መመለስ ያለብን
ይመስለኛል።ምክንያቱም ያሁኑ ቦታ ላይ ተለክፎ ሊሆን ይችላል'ና፤ ነገሩ
ሳይፀናበት መካ ወስደን እናስረክበው" አላት።
እሷም በዚህ ተስማምታ ለአመታት በአከባቢያቸው ኑር ያበራላቸውን ህፃን በ 4
አመቱ ወደ መጣበት መካ ይዘውት ሄዱ።
ከዚያም ብዙ ተጉዘው መካ ሲደርሱ የረሱልን (ሰዐወ) እናት አገኟት'ና ልጇን
አስረከቧት እሷም ለምን እንዳመጡት ስትጠይቃቸው ልክፍት እንዳይነካው
ፈርተው እንደሆነ ነገሯት።
ያን ግዜ እሷም፦"ወላሂ የኔን ልጅ ልክፍት አይነካውም። ሙሀመድን ነፍሰ ጡር
ሆኜ ምን እንዳየሁ ልንገራችሁ...!!? ከኔ ውስጥ የሆነ ብርሀን ወጥቶ የሻም ሀገር
ህንፃዎች ላይ ሲያንፀባርቅ ተመልክቻለሁ።ደግሞም እሱን አርግዤ ምንም አይነት
የእርግዝና ስሜት አልተሰማኝም።ይህ ልጅ ትልቅ ሚስጥር አለው" አለቻቸው።
ከዚያም ረሱላችን (ሰዐወ) ከእናታቸው አሚና መኖር ጀመሩ። ከእለታት አንድ
ቀንም የረሱል (ሰዐወ) እናት አሚና ልጇን ሙሀመድን እና አገልጋይዋን ኡሙ
አይመንን ይዛ የባለቤቷን ቀብር ልትዘይር እና ለረሱልም (ሰዐወ) አጎቶቻቸውን
ልታስተዋውቅ ወደ የስሪብ (መዲና) ጉዞ ጀመረች።
ጉዞው በጣም ከባድ ነበር...።አየሩም እጅጉን ይከብዳል...።ይሁን እንጂ ከመካ
ተነስተው ጋራ ተራራውን አቆራርጠው መዲና ደረሱ።አሚና ልጇን እና
አገልጋይዋን ይዛ በመዲና ምድር ለ1 ወር ያህል ተቀመጠች።
ከዚያም ወደ መካ መመለስ ስላለባት ልጇን እና አገልጋይዋን ይዛ ወደ መካ
በመመለስ ላይ ስለች አሚና እጅጉን ታመመች።ብዙም በሽታዋን መቋቋም
አልቻለችም ነበር'ና አብዋእ በተባለ ቦታ አሚና ህይወቷ አለፈ።(አብዋእ የሳውዲ
ነዋሪዎች ልታውቁት ትችላላችሁ)
አባታቸውን ሳያዩ ያደጉት ረሱላችንም (ሰዐወ) በስድስት አመታቸው እናታቸውንም
አጡ።ኡሙ አይመን የተባለችዋም አገልጋይ አሚናን እዛው አብዋእ ላይ ቀብራት
የቲሙን ልጅ ይዛ ወደ መካ ተመለሰች።
ከዚያም በኋላ ዐብዱል ሙጠሊብ የተባለው የረሱላችን (ሰዐወ) አያት ረሱልን
የማሳደግ ሀላፊነቱን ወሰደ። ከልጆቹ በላይም ይንከባከባቸው ነበር...።በካዕባ
ዙሪያ ላይ ሆኖ በትላልቅ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ሲወያይም ረሱልን (ሰዐወ)
በእቅፉ ያኖራቸው ነበር።
ይሁን እንጂ ዐብዱል ሙጠሊብም ብዙ ሳይቆይ ረሱል (ሰዐወ) በተወለዱ
በስምንተኛ አመታቸው ዐብዱል ሙጠሊብ ህይወቱ አለፈች።
ዐብዱል ሙጠሊብ ሲሞት የረሱል (ሰዐወ) አጎት የሆነው አቡ ጣሊብም በተራው
እሳቸውን ተንከባክቦ የማሳደጉን ሀላፊነት ተረከበ። አቡ ጣሊብ ለረሱል (ሰዐወ)
ያለው ቦታ እጅጉን ድንቅ ነው...። ልጆቹን ከሳቸው በፍፁም አያወዳድርም ነበር።
አቡ ጣሊብ ምንም እንኳን እንደ ሌሎቹ የረሱል (ሰዐወ) አጎቶች ባለሀብት
ባይሆንም ነገር ግን በጣም ክቡር ሰው ነበር።አቡ ጣሊብ የትም ይሂድ የት ብቻ
ከጎኑ ረሱል አይጠፉም ነበር።
ከእለታት አንድ ቀን የመካ ነጋዴዎች ለንግድ እና ሸቀጣ ሸቀጦችን ለመነገድ
ከመካ ሲነሱ አቡ ጣሊብም ረሱልን (ሰዐወ) በ 12 አመታቸው ይዟቸው ተነሳ።
የንግድ ተጓዦቹ እጅግ ብዙ ከተጓዙ በኋላም በስራ የምትባል ሀገር ሲደርሱ አንድ
መናኩሴ ብቻውን አላህን በሚያመልክበት ቦታ ብቅ አሉ።ይህን የነጋዴ ተጓዦችን
ሲመለከትም ይህ መናኩሴ በሩጫ ወደ ነጋዴዎቹ ገሰገሰ።
ከዚያም ይህ መናኩሴ ረስላችን (ሰዐወ) ላይ በጣሙን አፈጠጠባቸው'ና፦" ይህ
ልጅ የማን ነው???" ብሎ ጠየቀ።
አቡ ጣሊብም፦" የኔ ልጅ ነው" አለ።
መናኩሴውም፦"ይህ ልጅማ አባቱ በህይወት መኖር የለበትም (ሞቷል)" አለ።
አቡ ጣሊብም፦"በርግጥ ልክ ነህ አባቱ ሞቷል። እኔ አጎቱ ነኝ" አለ።
መናኩሴውም፦"በል ምክሬን ስማኝ እና ይህን ልጅ ይዘህ ወደ መካ ተመለስ።
ይህ ልጅ ትልቅ ሚስጥር ይታይበታል'ና አሁን አይሁዳውያን ካዩት ሳይገድሉት
አይለቁትም" ብሎ መከረው።አቡ ጣሊብም ቅፍለቱን ትቶ ውዱን ነብይ (ሰዐወ)
ይዟቸው ወደ መካ ተመለሰ።
አሁን ነብያችን የልጅነት ዘመናቸውን አጠናቅቀው ወጣት ሁነዋል።መካ ላይ
የሚገኙ ወጣቶች በወጣትነት ዘመናቸው ይጠጣሉ...፣ ዚና ያደርጋሉ
ይጨፍራሉ...ይደሰታሉ።ይሁን እንጂ የመካ ወጣቶ የሚሆኑት ረሱል
አይመስጣቸውም ነበር። ሁሌም ስራ ላይ ነበር የሚያሳልፉት...
ከእለታት አንድ ቀን ረሱል እንደማንም ወጣት ከተማ ላይ መጫወት አማራቸው'ና
ከብቶቹን ለባለቤቶቹ አስረክበው መሀል ከተማ ገቡ ሰዐቱ ጨላልሟል። ልክ
ከተማ ሲገቡ ድልልልል... ያለ ሰርግ ላይ እየተጨፈረ ተመለከቱ'ና ጠጋ ሲሉ
አላህ ያልታሰበ እንቅልፍ እዚያው ለቀቀባቸው'ና ሌሊቱን እዚያው ተኝተው
አሳለፉ።
አላህ እንዲህ እንዲህ እያደረገ የወጣትነትን ፈተናዎች ያሸጋግራቸውም ጀመር።
(አቦ እኛንም ከወጣትነት ፈተና ያሸጋግረና)
ቀናት በቀናት ሳምንታት በሳምንታት እየተተካኩ ክረምቱ ተጠናቅቆ የበጋው ክፍለ
ግዜ መጣ።በዚያ ዘመን አረቦች ይልቅ የንግድ እንቅስቃሴያቸው የሚጦፈው
በበጋው ክፍለ ግዜ ስለነበር እያንዳንዱ የመካ ተጓዥ ነጋዴ ወደ ሻም ለመሄድ
ዝግጅት ጀመረ።
ከነዚያ ነጋዴዎች ውስጥም ከዲጃ የምትባል በስነ ምግብሯ የምትታወቅ እና
በጣም ሀብታም ከበርቴ ሴት አለችበት።
ጉዞው ከመጀመሩ በፊት ግን ይህች ከዲጃ ደሞዝ ከፍላው የንግድ ስራዋን
የሚያከናውንላትን ታማኝ ሰው በማፈላለግ ላይ ነበረች። ብዙም ሳትቆይ ከዲጃ
ስለ ረሱላችን (ሰዐወ) ታማኝነት ሰማች'ና እሳቸውን ሄዳ በማናገር የንግድ
ስራዋን ሊያከናውኑላት ተስማሙ።
_
ለዛሬ እዚ
ህች ጋር እናብቃ እና ነገ ማታ አላህ ካለ ልክ ኢሻ ሰላት እንደተሰገደ
እንገናኝ። ደሞ በግዜ ኑ ጁምአ ማታ እኛም በምናባችን ከነቢያችን (ሰዐወ) ጋር ለንግድ
ሻም ሀገር እንሄዳለን...።ከዚያም የልባችን ማረፊያ በሻም ሀገር ምን
እንደገጠማቸው እንመለከታለን....።

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

26 Dec, 16:08


ዛሬ ምን ብዬ ከምን እንደምጀምር አላውቅም...።ለዚህ ቀን ሳምንት ሲቀረው
ነበር ሆድ ይብሰኝ የጀመረው....። ያ ረሱለላህ...!!!
ያ ሀቢበላህ (ሰዐወ) ዛሬ የርሶ ተራ ነው...።ምን ብዬ ስለርሶ እንደምፅፍ ሳስብ
አይኔ በእንባዬ ይሸፈናል...።
አንቱ ያይኔ ማረፊያ..!!!ምንም እንኳን ወንጀለኛ ኡመትዎ ብሆንም ለዘመናት
ዑለማኦች የፃፉትን ኪታቦች በእንባ ተውጬ ሳነብ ከርሚያለሁ...።ይሁን...ይሁን
እሱ ምንም አይደለም... የፍቅር ነገር ሆኖብኝ ስለርሶ ባነብ ችግር
አይኖረውም...።
ነገር ግን ዛሬ የማይመጥነኝን ነገር ልጀምር ነው...። ያ ረሱሉላህ (ሰዐወ)!!!! ዛሬ
እኮ ስለርሶ ላወራ ነው...። አዎ...ስላንቱ ላወራ ነው..።
አንቱ ያይኔ ማረፊያ...!!! ለዘመናት በወንጀል በተዘፈቁ ጣቶቼ ዛሬ ግን ስለርሶ
ልፅፍ ነው..።
አንቱ የኔ ማር...!!! ለዘመናት መጥፎ ባየሁባቸው አይኖቼ ተጠቅሜ ዛሬ ስለርሶ
ልፅፍ ነው...።
አንቱ የኔ ነብይ...!!! ዛሬ በፍቅርዎ ተውጬ ስለርሶ የማይመጥነኝን ታሪክ ልፅፍ
ነው...።
አንቱ የኔ ተናፋቂ...!!! ምንም እንኳን የወንጀሌ ብዛት ገዝፎ ስለርሶ መፃፍን
ቢያሳፍረኝም በፍቅርዎ ተውጬ በናፍቆት እንባ ተሞልቼ ዛሬ እርሶን ላወሳዎ
ቀጠሮ ይዣለሁ...።
አንቱ ያይኔ ማረፊ...!!! አውቃለሁ እኮ እርሶ ለኔ አልቅሰው እኔ ችላ እንዳልኮት...!
እርሶ ለኔ ሂዳያ ጥርስዎ ተሰብሮ እኔ ሱናዎትን እንደዘነጋሁ...!!!
አዎ የኔ አማላጅ...!!! ወላሂል አዚም እኔ የርሶን ታሪክ ለመፃፍ ይቅርና ስምዎን
ለማንሳት ብቁ ያልሆንኩ ወራዳ ሰው እንደሆንኩ አውቃለሁ...።
አንቱ አዛኝ ነብይ...!!! አንቱ የሁሉ በላጭ...፣የድሆች አባት....፣አንቱ የነቢያት
መደምደሚያ...፣አንቱ የአላህ ወዳጅ...፣አንቱ የወንጀለኞች አማላጅ...እኔ እኮ
አልቻልኩም ወላሂ ስለርሶ መፃፍ አልቻልኩም...። ጣቶቼ ተንቀጠቀጡ...፣እንባዬ
ፊቴን አራሰው...ያረሱለላህህህህህህህህ....!!!
ያ ረሱለላህ!!! ነፍሴ ለነፍስዎ ፊዳ ትሁን...። አንቱ የተሰቃዩት ለኔ ይሁን...አንቱ
የተራቡት ለኔ ይሁን...ያንቱ ጥማት ለኔ ይሁን...ያንቱ ደም ከሚፈስ የኔ አጥንቴ
ይሰባበር...። አዎን...ይሰባበር...!!! ስጋዬም ይበጣጠስ...።
አንቱ ተናፋቂ ነብይ...! እነሆ እርሶን ለዘመናት ሲናፍቁ የከረሙ ኡመትዎ ስላንቱ
ሊሰሙ በጉጉት እየተጠባበቁ ነው'ና ፍቀዱልኝ ስለርሶ ላውጋቸው...!!!!
እስቲ ፍቀዱልኝ ስለጣፋጭ ህይወትዎ ላጫውታቸው...።
እስቲ ፍቀዱልኝ ስላንቱ ነግሪያቸው ስላንቱን ላጓጓቸው...።ሁላችንም ከነፍሶቻችን
በላይ እንወድዎታለን ያ ረሱለላህ...!!!
__
ውድ አን
ባብያን አሁን ነቢያችሁን ዐሰ በማስታወስ የተረበሻችሁ እንባችሁን
ጠርጋችሁ ወደ ናፈቃችሁት ዘመን በምናባችሁ ልውሰዳችሁ...።
ግዜው ዒሳ ዐሰ ካረገ 600 አመታትን አስቆጥሯል...።አለም በጨለማ
ተውጣለች፣የሰው ዘር ድንቁር'ናው ከምንምን ግዜ በላይ አይሏል። በዚያ ዘመን
ዚና አለም ላይ እጅጉን ተስፋፍቶ ነበር።
የዐረብ ነገዶች በተለያዩ የጎሳ መሪዎች የሚመሩ ቢሆኑም ጉልበተኛው
ከደካማው...፣ሀብታሙ ከድሀው...፣ባለ ብዙ ዘመዱ ከባይተዋሩ እየቀሙ
የሚኖሩበት ዘመን ነበር...።
በዚያ ዘመን ስልጡን የሚባሉት ፐርሺያዎች እንኳን እሳት በማምለክ የዘቀጠ
የአስተሳሰብ ድንቁር'ና ውስጥ ነበሩ...።
በዚያ ዘመን ሴት ልጅ የተዋረደች ፍጥረት ነበረች....። ሴት ልጅ ያለው አባት
ከአቻዎቹ በነፃነት የማይቀላቀልበት ዘመን ነበር።
አዎ...!!! በዚያ ዘመን ሴት ልጅ የውርደት መገለጫ ናት በማለት ከነ ነፍሷ
የሚቀብሩበት ዘመን ነበር...።
በዚያ ዘመን...በተከበረው የአላህ ቤት (ካዕባ) ውስጥ 360 አማልክቶች
ይመለኩ ነበር..ይህም አላንስ ብሎ የካዕባ ጎብኚዎች እርቃናቸውን በካዕባ ዙርያ
ይዞሩ ነበር.።
የሰው ዘር በዚህ የድንቁር'ና ባህር ውስጥ በመዋለል ላይ ሳለ አንድ ነዋሪነቷ
መካ የሆነ እና እሷም አሚና የምትባል ዐረባዊት እንስት ዐብዱላህ ከተባለ
ህጋዊ ባለቤቷ በመካ ከተማ ፀነሰች።
ይሁን እንጂ የabdullah ባለቤት ሚሱት ነፍሰ ጡር ሆና ሳለ ከቁረይሽ ነጋዴዎች
ጋር ሸቀጥ ለማምጣት ከሀገር ወጣ።ከነጋዴዎቹ ጋር ያሰበበትን ደርሶ ለንግድ
አስፈላጊ የሆነውን እቃዎችን ሸምቶ ሲመለስ የስሪብ (መዲና) የተባለች ከተማ
ሲደርሱ ዐብዱላህ ትንሽ ተጫጫነው።
ነጋዴ ጓደኞቹም የንግድ ሸቆጦቻቸውን ይዘው የትም መቆየት ስለሌለባቸው
መዲናን ትተው ሊያልፉ ሲሉ ዐብዱላህ፦"እኔ እያመመኝ ስለሆነ እዚህ ሀገር
አጎቶቼ ጋር ትንሽ መቆየት እፈልጋለሁ" ብሏቸው እነሱን ሸኝቶ እሱ እዚያው መዲና
ቀረ።እነሱም ሸቀጣቸውን ይዘው መካ ጉዟቸውን ቀጠሉ...በመጨረሻም
ዐብዱላህ ያብራኩን ክፋይ ለማየት ሳይታደል ዱንያን በመዲና ከተማ ተሰናበተ።
ወራት በወራት እየተተካኩ የአሚናም የመውለጃ ግዜዋ ደረሰ።ምንም እንኳን
አሚና ባለቤቷ በመውለጃ ግዜዋ ከጎኗ ባይራኖርም የሷን መውለጃ ቀን
የሚጠባበቁ የዐብዱላህ ወንድሞች እና አባቱ በእንክብካቤ አቆይተዋታል።
በወረሀ ረቢዐል አወል በእለተ ሰኞ ምድር አለማችን ለብዙህ ሺህ አመታት
ትጠብቀው የነበር ሰው ብቅ አለ።
ያ የነቢያት መደምደሚያ የሆነው...
ያ የእዝነት መገለጫ የሆነው....
ያ ምድርን ከፅልመት የገላገለው.... ሰው ከአሚና ማህፀን ወደ ምድራችን
ተሸጋገረ።
ያ ሰው ስሙ፦
ሙሀመድ (ሰዐወ)ኢብን
ዐብዱላህ ኢብን
ዐብዱል ሙጠሊብ ኢብን
ሀሺም ኢብን
ዐብድ መናፍ ኢብን
ቁሰይ ኢብን
ኪላብ ኢብን
ሙራ ኢብን
ካዕብ ኢብን
ሉአይ ኢብን
ጋሊብ ኢብን
ፊህር ኢብን
ማሊክ ኢብን
ነድር ኢብን
ኪናና ኢብን
ኩዘይማ ኢብን
ሙድሪካ ኢብን
ኢልያስ ኢብን
ሙደር ኢብን
ኒዛር ኢብን
ማዕድ ኢብን
ዐድናን.....ምናምን እያለ የዘር ሀረጉ ከኢስማዒል ዐሰ ጋር ይገናኛል።
አሚና ረሱልን (ሰዐወ) ልክ እንደተገላገለች ሱወይበቱል አስለሚያ የምትባል
የአቡ ለሀብ ባሪያ ወደ አሳዳሪዋ አቡ ለሀብ ዘንድ ስትሮጥ
በመሄድ፦"የወንድምህ ሚስት አሚና ወንድ ልጅ ተገላገለች" ብላ ስታበስረው
እሱም በደስታ ሰክሮ፦"አንች ካሁን ጀምሮ ባሪያ አይደለሽም ነፃ ነሽ" አላት።
የረሱላችንም (ሰዐወ) አያት የሆነው ዐብዱል ሙጠሊብ ይህን የምስራች ሲሰማ
በሽማግሌ አቅሞ በሩጫ አሚና ዘንድ በመሄድ ህፃኑን በደረቱ አቅፎት በስስት
እየሳመው ወደ ካዕባ ገሰገሰ።
አላህም መሀመድ የሚለውን ስም በዐብዱል ሙጠሊብ ልብ ቀረፀለት'ና
የረሱላችንን (ሰዐወ) ስም ሙሀመድ ብሎ ሰየማቸው።(ሙሀመድ ማለት
ትርጉሙ የተመሰገነ ማለት ነው።)
ከዚያም በኋላ ዐረቦች በተለምዶ ህፃናት ልክ እንደተወለዱ በጥንካሬ እንዲያድጉ
ገጠር ይሸኟቸው ነበር'ና ረሱልም (ሰዐወ) ወደ ገጠር ሊሸኙ ገበያ ላይ የገጠር
ሴቶችን ፍለጋ ተወጣ።
መካ ውስጥ አንድ አከባቢ አለ። ህፃናቱን ተረካቢዎች'ና ህፃናቱን አስረካቢዎች
የሚገናኙበት።
እዚያ ቦታ የተሰለፉ ህፀናት በሙሉ አሳዳጊ አግኝተው ሲሄዱ ረሱል (ሰዐወ) ግን
አባት የሌላቸው የቲም ስለሆኑ ሁሉም አሳዳጊዎች ሊወስዷቸው ፍቃደኛ

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

25 Dec, 19:03


ከትላንት የባሰ ነገር ቢወሳሰብ
ዛሬ ላይ ቢከብድህ ነገህን ለማሰብ
ጫናው እጥፍ ሆኖ የኑሮ ግብግብ
ሌላኛው ቢለኮስ አንደኛው ሲረግብ
ወጣው ሲሉ መውደቅ ቀን እያዳለጠ
ያዝኩ ሲሉ ማጣት ከእጅ እያመለጠ
ነፍስን የሚፈትን የሌለው መባቻ
እሽቅድድም ቢሆን ሰርክ ድካም ብቻ
ቢበዛውም ህይወት ፈተና ቢከበው
እጅ መስጠት የለም ነገር ለበጎ ነው


t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

25 Dec, 06:40


አታስቡ አትጨነቁ ወዳጆቼ

- እንድንሠራ፣ እንድንበረታ፣ እንድንፀና ነው የሚያዘን ፈጣሪያችን
- እንዳንጨነቅ በጭንቀትም እንዳናልቅ  ነው የሚመክረን ጌታችን
- ከምንም በላይ የምናምነው የሱን ቃል ነው
በጥሩ ነገር አስቡኝ ብሏል፣
ተስፋ እንዳንቆርጥ መክሮናል

“እዝነቴ ከቁጣዬ ትበልጣለች” ብሏል
አዛኝ እና መሀሪ ነኝ ብሏል
ቸር እና የተከበርኩ ነኝ ብሏል
ዱዓችሁን እሰማለሁ ብሏል
ችግራችሁን አስወግዳለሁ ብሏል
ባሰባችሁኝ ቦታ ላይ እገኛለሁ ብሏል

ነፍስ ከምትችለው በላይ እንደማትገደድ ተናግሯል፣
  ከወለደችን እናታችን በላይ እንደሚያዝልን ነግሮናል፣
እናም ወዳጆቼ
“ላ ተይአሱ፣
ላ ተቅነጡ፣
ላ ተሂኑ፣
ላ ተሕዘኑ፣ ….

ኢንሻአላሀ አናስብም አንጨነቅም
እንሠራለን እንተጋለን
እንጥራለን፣ እንሞክራለን
የሱን ምክር እንሰማለን፣
ለትዕዛዙ እናድራለን፣
በሱ ቃልኪዳን እናምናለን፣
በሱ ላይም ተስፋ እናሳድራለን

አላህ እኮ ፈጣሪያችን ነው
ያስብልናል፣
ያዝንልናል፣
ያልፈናል፣
ይምረናል፣
ይቅር ይለናል …
ስለዚህ የምን ሐዘን የምን ጭንቀት! ወዳጆቼ … አብሽሩ አትጨነቁ


t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

24 Dec, 16:18


السلام عليكم ورحمة الله وبركاته ዉዶቼ ወደዚህ ቻናልገባ ገባ በሉልኝ እስቲ
👇

https://t.me/SOBRhttp

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

24 Dec, 05:15


ይገርማል የአሏህ ሰው ምኞቱ የላቀ
ከስልጣን ከድሎት ከኩራት የራቀ
አላማው አንድ ነው ለዚህ ነው ልፋቱ
ግልፅ ነው መንገዱ ከስር መሰረቱ
መከራ ስቃዪ ስደት እንግልቱ
ስድብና ዱላው ረሀብ ጥማቱ
ሌላ አይደለም የሱ ይኸው ነው አላማው
ይሀው ነው ልፋቱ ይሀው ነው ጭንቀቱ
            ይሀው ነው ጥበቱ ከላይ ታች ማለቱ ስደት እንግልቱ
ንፁህ የአሏህ ባርያ ክቡር የጀነት ሰው
አሏህ በራህመቱ ሁሉን ያወረሰው
ለራሱ እኮ አደለም...
ለኔና ላንቺ ነው ለአለም ነው ጭንቀቱ
ከእሳት እንዲርቅ ነው እንዲድን ኡመቱ
ኡመቴ ኡመቴ ህዝቦቼ ማለቱ

❤️فداك ابي وامي يا رسول الله❤️

❤️اللهم صلى وسلم علي سيدي الأولين و الأخرين  نبينا محمد❤️

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

23 Dec, 16:10


እልህ 😘
.
የፈለገቻቸዉን ዕቃዎች ከገዛዛች በኋላ ሄዳ ካሸሯ ፊት ቆመችና የክፍያ ካርዱን አቀበለቻት፡፡ አላስተዋለችም፡፡
 “የቲቪ ሪሞት እኮ ነው የሠጠሸኝ” አለቻት ካሸሯ ፈገግ እያለች፡፡
“አይ የኔ ነገር ባለቤቴ ና ዕቃ አጋዛኝ አብረን እንሂድ” ስለው እንቢ ስላለኝ እኮ ነው ሪሞቱን ወስጄበት የመጣሁት አለች እሷም እየፈገገች

ባል ሆዬ ምናለ ግን አንተም አንዳንዴ አብረሃት ወጣ ብትል
ታሪኩ አላለቀም፤

ካርዱን ከቦርሳዋ አውጥታ አቀበለቻት፡፡ ካሸሯ ካርዷን ካየች በኋላ እየሳቀች መለሰችላት
“ምነው ምንድነው?” አለቻት ደንግጣ፡፡
“ባለቤትሽ ካርዱን አዘግቶታል

ባሌ ምንም አያውቅም ብለሽ ቸኩለሽ “ሠራሁለት!” ብለሽ አትፈንጥዢ አንቺ ደግሞ

“አሃ ነው!” አለችና ሌላ ካርድ አውጥታ ሰጠቻት
ይህኛው ግን አልተዘጋም
ነገርግን ካሸሯ ካርዱን እንዳስገባች “ወደ ስልክዎ  የላክንልዎትን ባለ ስድስት ቁጥር ዲጂት የይለፍ ቃል ያስገቡ ይላል
ባል ድል የሚያዉጅበት ሰዓት የደረሰ መሰላት ካሸሯ
ታሪኩ አላለቀም

ለካ ስልኩንም ይዛ ወጥታ ኖሯል አወጣችና ቁጥሩን አንብባ ነገረቻት
ከፈተ
ደስ እያላት የምኞቷን ሁሉ ገዛዝታ ወደቤቷ ተመለሰች

ታሪኩ መቼ አልቆ …
እቤት ስትደርስ የባለቤቷ መኪና በሩ ላይ የለም፡፡ ግቢው በር ላይ አጭር ማስታወሻ ትቶላታል እንዲህ ይላል
“ ሪሞቱን ስለወሰድሽብኝ ኳስ ለማየት ጓደኛዬ ቤት ሄጃለሁ
ልቆይ ስለምችል ከፈለግሽኝ ደዉይ፡፡”
ስታስታዉስ  ሞባይሉ እሷ ጋ ነው
ተስፋ ቆርጣ ወደ ቤተሰቦቿ ቤት ሄደች፤ ቆንጆ ምግብም አገኘች ለመሥራቱ ሳትለፋ ርሃቧን አስታገሠች፣ ተደሰተች፣ ጠገበችና ተኛች፡፡

ባል እቤት ሲመለስ እጅግ ርቦት ነበር፤ የግቢዉን በር ከፍቶ ቤቱ ገብቶ እዉስጥ ቢዟዟር ምንም የሚበላ ነገር አጣ

ከቤት ስልክ ወደ ስልኳ ደወለ አታነሳም፡፡ ሮጦ ወላጆቿ ቤት ሄደ ተኝታለች፡፡ እናት ደክሟት ነው የተኛችው  እንዳትቀሰቅሳት ብላ አሳሰበችው፡፡
ከዚያም የሚወደዉን ምግብ አቀረበችለትና ቁጭ ብሎ መንቃቷን ይጠብቅ ጀመር፡

ባልና ሚስት - ምናለ እልሁ ቢቀር፡፡
 
ዝምብላችሁ ለምን አትኖሩም ግን

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

23 Dec, 04:46


🌸🥀ተምሳሌቴ ነሽ!!!

ተምሳሌት ያረጋት ለአለማት ሴት
በመታገሷ ነው ከፊርዐውን ቤት
ያሳለፈች ያኔ ግፍና ቅጣት
ዐቂዳን ጠብቃ በተውሒድ ፅናት
ማነው የሚታገስ እስኪ ለአላህ ብሎ
ባል ሲሆን በተራው ሁሉን ነገር ችሎ
መልካም ለቤተሰብ ጀነትን ከጅሎ
ሚስቱን የሚያስደስት ከአላህ ቀጥሎ
አሉ ብዙ ወንዶች በየመሳጅዱ
አምስት ወቅት ሶላት ሁሌ የሚሰግዱ
በሰለፎቹ ፈህም ዲኑን የተረዱ
ለዑማው አሳቢ ለሴትና ወንዱ
ተውሒድን ሰባኪ ሱናን የሚያስረዱ
እስከመኖራቸው መቼም አይካዱ

በዘመናችን ላይ አላህንም ፈርተው
ተጠንቅቃ ኗሪ ባሏንም አክብራው
አይናችን ስላየ መኖሯን አንክደው
እሱም ቢበድላት ትዕዛዙ ከላይ ነው
በኢኽላስ ትታገስ ጀነት ነው ክፍያው

ጊዜም አላጠፋ እነሱን በማውሳት
እኔን ያሳሰበኝ ደግሞ እንደግር እሳት
ሁሌ የሚፈጀኝ ቀንም ሆነ ሌሊት
የፊርዐውን ግፍ ነው በኛዋ ተምሳሌት
በሚስቱ ዐስያ ላይ ያፈራረቀባት
ድል አድርጋ ዐስያ አሳየች ትዕግስቷን
ከፊርዐውን ተንኮል ነፃ የመሆኗን
አሳወጀች በአላህ ያውም በቁርአን
በዱዓዋም ሰበብ አስገነባች ቤቷን
ፊርዐውን ስር ሆና ወረሰች ጀነቷን

እህት እስኪ ታገሽ በትዳርሽ ውስጥ
ሱናን በመዘንጋት የባል መለወጥ
የሁልጊዜ ጉዞው ከድጥ ወደ ማጥ
ቢሆን የሱ ምርጫ አንቺ መሆን ብልጥ
ኒካህ አውርድልኝ ፍታኝ ከምትይው
ትዕግስት እንደ ዐስያ በአላህ አሳይው
በተውሒድ ላይ ፀንተሽ በተግባርሽ ጥሪው
ወደ ሰላሟ እና ማራኪ ከተማ
የሱ ሚስት ሆነሽ በቀን በጨለማ
በዱዓሽም በርቺ ብሶትሽን ይስማ
አላህ ፈረጃውን ያቅርብልሽ እማ
ቤትሽም ትገንባ ጀነት ተሸልማ

እስኪ ልጠይቅሽ ባስቸኳይ ነው መልሱ
ምንድን ከለከለሽ ጀነት ከመውረሱ?
ከተውሒድ ለመሸሽ ሰበብ አይሆንም
መታገቱም ሆነ በጣም መዞለም
ከዐስያ ታሪክ ይማሩ ሁሉም
በርቺ ጠንክሪ እህት አይዞ አይክፋሽ
አትቸኩይ ለመውጣት ትዳርም ካለሽ
የኢማንን ጣዕም እዚያው ታግሰሽ
አላህን ፍራ እያልሽ በሐቅ ላይ ፀንተሽ
ሳትበሳጪና አላህንም ፈርተሽ
ከኖርሽ እንደ ዐስያ ተምሳሌቴ አንቺ ነሽ

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

22 Dec, 13:26


~ የቀንህን ማማር ከሌሎች ሰዎች ጋር አታሰሳስር
~ለዉድቀትህ ሰበብ አትደርድር
~ መንገድህን በእጆችህ አስምር
የኑሮ መሃንዲስህ አንተው ራስህ ሁን
~ለራስህ እንዳንተ ማን አለ!
~ተደሰት ለሌሎችም ደስታን ፍጠር

~ በጎ አስብ፣ ዘና በል
~ ነፍስህን በዱር ዉስጥ  አታግታት
~ በጨዋታም በፈገግታም ተንፍስ
~ ምድርን ጭንቅላትህ ላይ ተሸክመህ አትዙር
~ ሐላል እስከሆነ ድረስ በነፍስህ አትጨክን፣
~ካንተ በላይ ሚስኪን የለምና ለራስህ አስብ፣
~ለራስህ በራስህ ላይ ሶደቃ አድርግ፣

~ደስ ወዳለህ ቦታ ሂድ
~ ከሚጠቅምህ ተወዳጅ
~ በሁሉ ነገር ዉስጥ አስተንትን
~ በጀሊሉ ሥራ 'ሱብሐነላህ !' በል

~ ለኢማንህ ሳሳለት፣
~ ከአላህ ዉጭ ምንም እንዳልሆንክ እወቅ፣
~ ከሱ ዉጭ ምንም ጉልበት እንደሌለህ ተረዳ

አዎ
~ ጥሩ ዉሎ ከዋልክ አላህ ነው ያዋለህ፣
~ ስለ ዉሎህ አላህን አመስግን፣
~ ኃጢአት አፋፍ ደርሰህ ካመለጥክ ረሕማኑ ነው ያስመለጠህ፣
~ ለችሮታው ምስጋና አድርስ፣
~ የአላህ ዉለታ ክፍያው ምስጋና ነው፣
~ሐምድ እና ሹክር ነው

አዎ
ለራስህም ለሰዎችም ቅን ሁን፣
~ ሰዎችን በቻልከው ሁሉ ጥቀም
~ በገራልህ ነገር ሁሉ አግዝ
~ ያ ባይሳካልህ እንኳን እነርሱን ከመጉዳት ተቆጠብ
ይህ በራሱ ምፅዋት ነዉና

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

21 Dec, 05:21


ተመልከት! ከጡሩንባው ጩኸት በኋላ የሰው ልጆች ከቀብሮቻቸው ተነስተው ወደ መሰብሰብያይቱ ምድር ይተራመሳሉ።

እርቃናም፣ ባዶ እግር እና ያልተገረዙ ሁነው ወደሚነዱበት ሜዳ ይተማሉ። ከየት ወደ የት እንደሚሄዱ የሚያውቁት ነገር በሌለበት ሁኔታ ነጭ፣ ለጥ ያለች እና ምንም አይነት ኮረብታም ሆነ አቀበት ከሌለባት አርዱል ማሕሸር ከምትሰኘው ምድር ይጎርፋሉ።

ከዝንተ-አለም እስከ ዘለ-አለም የነበሩ ፍጥረታትን በቅፅበታዊ ክስተት የሰበሰበ አላህ ጥራት ይገባው።

አዎን! ለጥ ያለች ምድር፣ በአይነትም በይዘትም ንፅህት የሆነች ምድር፣ አላህ ያልታመፀባት እና ደሞች ያልፈሰሱባት ምድር ዛሬ ፍጥረትን ለሸንጎው ልታዘጋጅ ሰብስባለች።

ሰማይ የብርሀን ምንጩ የሆኑት ፀሀይን እና ከዋክብት ለክስተቱ ክብደት ተሰውረዋል፣ ብርሀኖቿ የተሰወሩባት ምድርም በፅልመት ታቃስታለች።

በፅልመቱ ጉዞ እርቃናም የሰው ልጆች እየተተራመሱ ወደ መሰብሰብያቸው ሲድሁ ድንገት አለሙ በከፍተኛ ድምፅ ይናወጣል።

ሰማይ ተቀደደ።

ለዘመናት የመላዕክት መኖርያ የሆነው ሰማይ፣ ከነግዝፈታቸው ችሎ የከረመው ሰማይ፣ ዛሬ ላይ የጀባር ቁጣ ቢያስፈራው ድንገት ተሰነጠቀ።

ያ ግዝፈቱ እና ስፋቱን እንዳንደርስ በአይናችን የአድማስን ግርጆ ሲከስትልን የነበረው ግዙፉ ሰማይ ዛሬ ላይ ሁኔታውን መቋቋም አቅቶት ሲሰባበር እና ሲፈረካከስ ቆይቶ በመጨረሻም እንደ ፅጌረዳ ቅጠሎች ተበታትኖ የታረበ ቄዳ መስሏል።

ያን ቀን ዐጀብ ታያለህ!
በዝያ ትርምስ ውስጥ ጋላቢዎች ግርግሩን እያቆራረጡ ሲያልፉ፣ ከፊሉ በሩጫ ሲተም፣ ሌሎች በአፍ ጢሞቻቸው እየተንፏቀቁ ሲሄዱ ትመለከታለህ።

ዋ! ኢላሂ!

ጉዞው ተቋጨ። ፍጥረታት በሙሉ...መላዕክት፣ ሰዎች፣ ሰይጣናት እና መላ እንስሳቶች ከአንድ ስፍራ ተሰበሰቡ። ለምድሪቱ የተሰወረችው ፀሀይ ሆዷን ገልብጣ ፍጥረቱ ላይ ልታፈጥ ብልጭ አለች።

ፀሀይቱ የደጋን ጫፎችን ያህል ከፍጥረቱ ትቀርብ'ና ፍጥረት የጥላን ምንነት እስኪራሳ ድረስ አናታቸውን ትማግደዋለች።

በዚህ የሀሩር ንዳድ ፍጥረቱ የላብ ውቅያኖስ መስርቶ ያለ ጀልባ ሲሰጥምበት፤ እዝያ ማዶ እጌታቸው ዘንድ ከዙፋኑ ስር የተጠለሉ ቅሩባን ባሮች የፀሀይቱ ሀሩር ለልቅናቸው ያጎበደደ ይሆናል።

በግርግሩ እና በትርምሱ መካከል የሚመነጩት የወበቅ ወላፈኖች ከፍራቻ ስሜቶች ጋር ተዳብለው የላቡን መጠን ጨምሮታል።

ከፊሉ እንደ ጎርፍ ጉልበቱ ድረስ በላብ ይጠመቃል፣ ሌላኛው እስከ ጭኑ ላብ ይይዘዋል፣ ገሚሱ እስከ ጆሮው ድረስ የገዛ ላቡ ያጠምቀዋል፣ ያላደለው ደሞ በገዛ ላቡ መላ እሱነቱ ሰጥሞ ሞትን ይመኛል።

በአላህ መንገድ ላይ (ፊ ሰቢሊላህ) ስትለፋ ያላወጣኻት እያንዳንዷ ላብ ተቆጥራ ያን ቀን እንደ ዶፍ ከሰውነትህ ትዘንባለች።

ዛሬ ላይ ጥቂት ደቂቃዎችን ለጀባር መቆም የተሰናቸው እግሮች ያን ቀን በላብ ውቅያኖስ ውስጥ እየተንሳፈፉ 50 ሺህ አመታትን ይቆማሉ።

ምግብ የለ፣ መጠጥ የለ፣ ንፋስ የለ...እንዲሁ በቅርጮ እንደተወተፉ ዶሮዎች ሁነው ያን ሁሉ ዘመናት በደረቀ ጉሮሮ ሲጮኹ ያሳልፋሉ።

«ወይ ጀነት ወይ ጀሀነም አስገብቶ ይገላግለን» የሚሉ ሀሳቦች እዚህ ከላቡ ውቅያኖስ ውስጥ ይስተጋባሉ።

በአማላጅ አማካይነት ጌታችን መላ ይበለን የሚሉ መፍትሄ ፈላጊ ሰዎች ከከበርት የአላህ ወዳጆች ዘንድ ሂደው ቢያግባቡም ነቢይ ሙርሰሎች በሙሉ «ጀባር ተቆጥቷል ዛሬ አልቀርበውም፣ እንዲያው ለነፍሴም ፈርቻለሁ» በማለት ተስፋ ያስቆርጣሉ።

ነብያት የአላህ ወዳጆች ቀኑን ፈርተው ሲርበተበቱ እና ከአላህ ፊት መቅረብ አስፈርቷቸው ነፍሲ ነፍሲ ሲሉ ያን ቀን ፍጥረት ምንኛ ፍርሀት ይውጠው ይሁን!

ነብያት ሙርሰሎች በሚያዩት ነገር ተርበትብተው «እገሌ ጋ ሂዱ...እግሌ ከኔ በላይ ለጀባር ቅርብ ነው» እያሉ የነፍሳቸው ጉዳይ ባሳሳበችው ቅፅበት እዝያ ማዶ« ኡመቲ ኡመቲ » እያለ ሚጣራ ነብይ ይደመጣል።

ሙሐመድ! ሰዐወ

ዱንያ ላይ ሲላት የነበራትን ቃል ሙሀመድ ዛሬም ከትርምሱ ሜዳ፦«ኡመቲ...ኡመቲ» እያለ ይጣራ ይዟል።

ዱንያ ላይ ሲያምፁ እና ሲዘናጉ የከረሙ ብኩን ኡመታቸውን የጀሀነም ነበልባል እንዳያገኛቸው ነቢ «ህዝቤ ህዝቤ...» ይላሉ።

መላዕክት፣ ነብያት ፈርተው ያልተጠጉትን ደጀ-ዙፋን ነቢ ሰዐወ በተከበረች እግራቸው ረግጠው ምታሳሳ ግንባራቸውን ለሱጁድ ይደፏታል።

«ሙሐመድ ሆይ! ምን ፈልገህ ነው? ጠይቅ ይሰጥኻል፣ አማልድ ትማለዳለህ» ረበል ዒዛ ነቢን ሰዐወ ጠየቀ።
«ኡመቲ...ኡመቲ» ነቢ ሰዐወ....

እናት ከልጆቿ ለአስቸጋሪው እንደምታዝነው ሁላ ነቢም ሰዐወ የአስቸጋሪ ኡመቶቻቸው ጉዳይ አሳስቧቸው የብኩኖችን እና የአመፀኞቹን ጉዳይ ሀላፊነት ወስደው ነፃ የማውጣት ስራ ይሰራሉ።

ይሄን ዝርክርክ ኡማ ከጀሀነም አፍ ሳያስጥሉ ያን ቀን ነቢ አያርፉም። ሲራጥ ላይ ስትሄድ ከድልድዩ ጫፍ ቁመው ዘግ ዘግ ሲሉ ትመለከታቸዋለህ።

ሚዛን ጋ ብትሄድ ሊማፀኑልህ ቁመው ትመለከታቸዋለህ፣ ከትርምሱ ብትገባ ሲጣሩ ወዲህ ወድያ ሲሉ ታስተውላለህ፣ ከመጠግያ ቢስ ድሆች ዘንብ ብትሄድ ነቢን ከመሀከላቸው ሲያፅናኑ ታያለህ።

ያን ቀን አንተን ነጃ ሊያወጡህ ነቢ የማይደርሱበት ቦታ አይኖርም። የደረቀ ጉሮሮህን በሀውድ መጠጣቸው ሳያርሱልህ አይለቁህም።

ያ ቀን ነቢ «ኡመቲ» ሲሉ ረቢ «ራሕመቲ» የሚልባት እለት ናት።

ለረቢ ጥራት እና ቅዳሴ ይገባው
ለነቢ ደሞ ሰላት እና ሰላም ይውረድላቸው።

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

20 Nov, 04:49


-        አስመሳይ ሰው አይታመንም
-        ሚስጢር የሚያባክን ሰው አይታመንም
-        ቁሳዊ ሰው አይታመንም
-        የጥቅም ሰው አይታመንም
-        ራስ ወዳድ ሰው አይታመንም
-        ዉለታ ካጅ ሰው አይታመንም
-        በትርፍ ጊዜው የሚፈልግህ ሰው አይታመንም፣
-        ከላይ ከተጠቀሱት ካልተጠነቀቅክ አንተ እራስህ አትታመንም ሀቢቢ

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

19 Nov, 12:10


ኢላሂ! የአመፅ እድፍ ባጠቆረው የማንነት ገፅታዬ እፊትህ አቀርቅሬ ቁምያለሁ።የቆምኩለትን አላማ ከመናዘዜ በፊት አንተ የምታውቀው ስትሆን፤ የልቅናህ መገለጫ እንዲጎላ ወራዳነቴን በልመና ልገልፅልህ ሻትኩ።

ሰዪዲ! የውሳኔ ቀለምህ ከማንነቴ እስከ ምንነቴ ከትቦ ሲያበቃ ቀለሙን የዘመን ንፋሶች አድርቀውታል። ውሳኔው ሊፈፀም ነፍስ ተሳስታ በሸይጣን ግዛት በተማረከች ግዜ የተፈፀመውን በሙሉ ይቅር በለኝ።

ከልዕልና ማማህ ሁሉን እያየህ ላጠፋኋቸው ጥፋቶቼ ሁሉ የወራዳነትን ካባ ለብሼ፣ የመዋረድ ክንፌን ዘርግቼ፣ የክብር ግንባሬን ደፍቼ ከምህረትህ ትለግሰኝ ዘንድ ኢላሂ! አላለሁ።

ጌታዬ! ብትምረኝ ለማርታ የተጋባህ ነህ። በውሳኔው መዝገብህ ቀጠሮዬ ቀርቦ ሳለ እኔ ወዳንተ ያልቀረብኩ ሆኜ ከተመለከትከኝ ፤ ፀፀቴን ለመቃረብያህ ድልድይ አድርግልኝ።

ረቢ! በንፋስ አለም ህያው ሳለሁ ትለግሰኝ የነበረውን እዝነትህን ከአፈር እቅፍ ገብቼ በምጋደምበት እለት አትንፈገኝ። እዘንልኝ።

መውላይ! ዱንያ ላይ ነፍሴ ስታምፅህ ትሸሽጋት ከነበረው በላይ ለሂሳብ እፊትህ ስትቆም እንድትሸሽጋት ከክብርህ እታች ተደፍቼ እለምንሀለሁ።

ኢላሂ! ከፅድቅ ንፅፅር ኩኔኔዎቼ በዝተው ከተገኙ፤ ከአምልኮ ንፅፅር የአንተን ተስፋ አብዝቼ ተመልክቻለሁ ና ተስፋዬ ባንተ ነው።

ሰዪዲ! ባንተ ያለኝ ተስፋ የሰማያትን አዕማድ የሚልቅ ሁኖ ሳለ እንዴታ ከልግስና ደጃፍህ ባዶ እጄን የተዋረድኩ ሆኜ እመለሳለሁ?!

ያ መውኢሊ! የወጣትነት ዘመኔን ካንተ የመዘናጋትን ጭንብል አጥልቄ ስባክን ወደምኩ። የአመፅ ውቅያኖስ ማዕበሉ ረግቶ ከመሀሉ ዘመናትን እንድተኛ ሸይጣን የውስልትናን ፍራሽ አነጠፈልኝ።

ከተነጠፈልኝ ፍራሽ ላይ ሆኜ የእዝነት ዝናብህ ገላዬን ቢነካኝ፤ ከዝንጋታ ባንኜ የልቅና ምሶሶ ከሆኑት እዝነት ማርታህ ስር ተደፍቼ የልግስና መገለጫ የሆነውን ራህመትህን ተማፀንኩህ።

ያ ከሪም! ለፍቅርህ ጠርተኸው በአምልኮ መሰላሎች ከዙፋንህ የሚቃረብ ባርያህ አድርገኝ። ፍቅርህ ወዳንተ ናፍቆት የሚያዋልለውን ልቦናም ለግሰኝ።

ያ ለጢፍ! ከዊላያ(አውሊያኦች) ቤተሰብ መድበኸኝ ከመኻከላቸው ጭማሪ ፍቅር ከተለገሱት ምሉአን ህዝቦችህ ላይ ሹመኝ። ትችላለህ!

ያ መሊክ! የትዝታህ ማዕበል ላይ ጭነኸኝ ከዚክርክ ወደ ዚክርህ እያሸጋገርክ ፤ ነፍሴንም ከቅድስና ስመ-ባህሪያት ስር አኑርልኝ።

ያ ቀዩም! ወዳንተ ምሉዕ መቋረጥን አቋርጠኝ፣ በብርሀናማው ማንነትህ የልቦናዬን እይታ አብራልኝ፣ የልቦናዬን እይታዎችም የግርዶሽ ብርሀኖሽችን የሚሻገሩ አድርግልኝ፣ የተሻገሩ አይኖቼንም ከልቅና ማዕድናት ምንጭ አኑርልኝ፣ ነፍሴንም ከልዕልናው ናፍቆት ስር አንጠልጥልልኝ።


t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

18 Nov, 15:43


((ይቅርብኝ አስመሳይ))

አስመሳይ አግብቼ ግራ ከምጋባ
ተደብቄ ልኑር ልቅር ሳላገባ
ተመሳሳይ ኮፒ በመቅረቷ አልባባም
እምነት አሰዳቢ ፍፁም አላገባም

የአላህን ትዕዛዝ ሂጃቧን አድርጋ
ከተጨማለቀች ከአጂነብይ ሰው ጋ
እሷን አላገባም ከቶ ቁሜ ልቅር
በብቻየ አለም ውስጥ ተደብቄ ልኑር
አቂዳየ እያለ ምን አለው ካለችኝ
እስልምናየን ይዤ ድሃ ካረገችኝ
መስፈርቷ ከሆነ ቤት ና መኪና
ኒቃቢስትም ብትሆን ብትሄድ ተሸፍና
ትቅርብኝ ይች ልጂ እኔ አላገባትም
ኪታቤን አዝየ ሄዳለሁ የትም
እውቀት ፍለጋየን  አቀጣጥላለሁ
እምነት አሰዳቢ ለምን አገባለሁ
ጀግና የጀግና ልጅ በመንሀጂ ያደገች
በሰለፎች አሰር አምራ የደመቀች
አላህ ከገጠመኝ ውብ ትዳር ፈላጊ
አስተዋይ መካሪ ንዴት አረጋጊ
የሙብተዲ ጠላት ጦረኛ ተዋጊ
ሽርክን አፈራራሽ የተውሂድ ምርኮኛ
የቢድአ ካንሰር የሱና ሱሰኛ
እምነቷ ሲደፈር የሚያንዘረዝራት
ከእግር እስከ ራሷ ንዴት የሚወራት
በአቂዳዋ ታጋይ ጀግና አርቆ አሳቢ
የእህቶቿ ሞዴል በሂጃብ ተዋቢ
ከመጥፎ ከልክላ በመልካም ላይ አዛዥ
ውዷ ባልተቤቷን በፍቅር አደንዛዥ
ለረጂሙ ጉዞ ስንቋን የሰነቀች
በተውሂድ በሱና በሀቅ የደመቀች
ከመንሀጀ ሰለፍ ሁሌ የማትለወጥ
ያወራ ቢያወራ ልቧን የማትሰጥ
ይህችን መሳይ ሞዴል ታስፈልገኛለች
እህትም ፣ባልተቤት እናት ትሆናለች
ችግሩ እሷ ግን የት አለች የት አለች
ልፈልግ በዱኣ ከአላህ ተስፋ አልቆርጥም
እምነት አሰዳቢ             አልለማመጥም
ተውሂድ ያልገባት ልጅ አርፋ አትቀመጥም
                ያ አላህ
እኔንም አድርገኝ ከነጓደኞቼ
ቀጥ ብዬ የምሄድ አንተኑ ፈርቼ
ሀቅ የምገልፅበት ስጠኝ እምቅ ወኔ
ተውሂድ ላስተምረው ይጠቀም ወገኔ
ጀግናይቱ የት አለች ለባሽ ጥቁር ካባ
ብቸኝነት ይብቃኝ አትፈትነኝ ላግባ

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

17 Nov, 12:15


እናት አባቶች አያት ቅድማያት
ቅኝ አልባገሬን ባይኖቸ እንዳያት
ቀኝ ክንድ ሆነው ሲያደርሱ እኔ ጋ
ከፍለውበታል ግዙፍ ውድ ዋጋ
-------
እንኳን ዛሬና  ሲጀመር ከጥንት
መስዋዕት ከፍለው በደምና አጥንት
ግንብ አጥር ሆነው ዋልታና ማገር
የቢላል ዘሮች ሰርተዋል  ሀገር
-----
ታላቆች ነን ሙስሊሞች
ኢትዮጵያዊ ነባር ህዝቦች
ከእልፎች ጋር ሀገር ሰሪ
እድገት ሰላም ፍቅር አብሳሪ
----
የቀዲሞቹን ገድል በወጉ ሸምኖ
ከጊዜጋ አዋዶ መልኩን አዘምኖ
በታሪክ መስተዋት እራሱን ያየ ሰው
እሱ ነው ሸማውን በልኩ ሚለብሰው
---
የጀግና ሰው ፍሬ እንዳይጠፋ ባክኖ
እርሻው እንዲያፈራ እንዳይነጥፍ መክኖ
ጠብቀው ከዘሩት ምርቱ ራብ ያበርዳል
ለመጪው ሲሻገር ትውልድ ይወለዳል
-----

የእውነትን ቅኝት ካለበት አንስ ...ቶ
ለራስ እንዲሰማ የሩቅ ድምፁ ጎልቶ
ይቀኙታልንጅ በውብ አንቂ ዜማ
ሙሾ አይወረድም ባዲስ ቀን ዋዜማ
-----

የእናት ሀገሩ ፍቅር ያነደደው
እልፍ አእላፍ ጀግና ባንድ የነጎደው
ፈረሰኛ ጦር  ጋልቦ የሄደው
ባእድ ወራሪን ያርበደበደው
ቢስሚላህ ብሎ ጠላት ያረደው
አድዋ ዘምቶ ድል ያደረገው
ላገሩ ክብር ሸሂድ የሆነው
ለኔ ነፃነት ነፍስ የገበረው
በደም ባጥንቱ ሀገር ያቆየው
የማይተመን ዋጋ ከፍሎ ነው
ሰሜን ደቡቡ
ምስራቅ ምእራቡ
በዱር በጢሻው ሜዳና ዳገት
እየሰየፉ የሰላቶ አንገት
ወሎ ኦሮሞ አፋር ሱማሌ
ቁመዋል ላገር ወድቀዋል ለኔ
ያሰን ኢንጃሞ የሸህ ሆጀሌ
ድላቸው ድሌ ገድላቸው ገድሌ

ጀግናው ደጅ አዝማች ዑመር ሰመተር
መሳት አያውቅም ሰይፉ ሲመተር
ያ ጀግና አባቴ የበርሃው መብረቅ
አይጣል ነው ክንዱ ጠላትን ሲያደቅ
ወገቡ ደቆ የተመለሰው
የዛን ያንበሳ ክንድ የቀመሰው
የዑመርን ጦር የጀግናን በትር
አፈር የገባው ጣሊያን ይመስክር
-----
ጦልሀ ጀእፈር ሀገሩን ክዶ
ለባእድ ጠላት ክብሩን አዋርዶ
ተገፋሁ ብሎ ባንዳነት መርጦ
መቼ ረከሰ ኢትዮጵያን ሽጦ
----
በረመጡ ሜዳ ፊት ግንባር አድዋ
ለኔ ነፃነት ሲል በክብር ሊሰዋ
አባት አያቴ ነው ሲከንፍ የደረሰ
አላሁአክበር ብሎ ጠላት የመለሰ
-----
የቢላሉል ሀበሽ የነጃሺ ልጆች
ነበልባል ረመጥ ፍም እሳት ንዳዶች
የወገን መከታ ውድ ሀገር ወዳዶች
እልፍ ዋጋ ከፍለዋል እልፍ ሙሀመዶች
----
ሙስሊም ውድ ዋጋ እየከፈለ
ድል ማድረግ ያውቃል ሱለላ እያለ

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

16 Nov, 17:23


በጣም የምትወዱትና የምትቀርቡት (እናት አባትም ሊሆን ይችላል) ሰው መልካም ነገር ሊመኝላችሁ ይችላል፡፡ ጥሩ ህልምም ሊያይላችሁም ይችላል፡፡

ግና ጥሩ ህልም አይቼልሃለሁ፣ ያንተ፣ ያንቺ ጉዳይ ገና ነው በሚል ሰበብ ከመጣላችሁ ጥሩ ሥራ፣ ጥሩ ትዳር፣ ጥሩ ሕይወት ሊከለክላችሁ አይገባም፡፡
እርግጥ ነው ጥሩ ህልም የሙእሚን ብሥራት ነው፡፡ በህልሙ ዙርያ መልካም ተመኙ። ግና ታድያ ህልም ስትጠብቁ አትኑሩ። ህልም ስትጠብቁም እውኑን እንዳታበላሹ።

ጎበዝ ሙእሚን በሚያየውም ሆነ በሚታይለት ህልም ራሱን ላይ አይጥልም፡፡ ይሠራል፣ በአላህ ይመካል፣ ይወስናል
ምሽቱን ጥሩ ህልም እንደምታዩ አስባለሁ ኸይር ይሁን፣ ይሳካ

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

16 Nov, 07:37


መካ ላይ እስልምና በይፋ መስፋፋት ባልጀመረበት ሁኔታ አንዲት እንስት ልቧ ወደ እስልምና ሸፈተ። ጀነት ብቻዋን መግባት አልፈለገችም ነበር ና የመካ እንስቶችን እየዞረች በግል ጥሪ ታቀርብላቸው ጀመረች።

ይፋ አይወጣ የለም ና ፤ ታወቀባት።እንስቲቱ ከሌላ አካባቢ መጥታ የመካን ከተማ ሰው አግብታ የምትኖት የቅርብ ወገን የሌላት ባይተዋር በመሆኗ መሳፍንቶቹ ይዘው እንዲህ አሏት።

‹‹ወገኖችሽ መጥተው ያጠቁናል ብለን ባንሰጋ የምናደርግሽን ታውቂው ነበር፤ ነገር ግን ትዳርሽን አፋተን ወደ ሀገርሽ እንሸኝሻለን››

የትዳሯ መፍረስ ከአላህ መንገድ ያላዛነፋት እንስት የዝያን ግዜ የነበረውን የጉዞ ታሪኳን እንዲህ ስትል እራሷ ትተርክልናለች።

"ከትዳሬ አፋተውኝ ወደ ሀገሬ ሊወስዱኝ ሰዎቹ ቤቴ መጡ። ከወገቡ ላይ ምንም አይነት ጨርቅ እንኳ ጣል ያልተደረገበትን አህያ አምጥተው ጫኑኝ። የተቀመጥኩበት ኮርቻ የሌለው ደረቅ የአህያ ወገብ ህመሙ ሳያንሰኝ እግሬን እማሳርፍበት መርገጫ እንኳ ከልክለውኝ ረዥሙን የበረኃ ጉዞ ይዘውኝ ተጓዙ።

በአረብያ ንዳድ በረሃ ላይ ምግብም ሆነ መጠጥ ሳያቀምሱኝ ለሶስት ተከታታይ ቀናት አስጓዙኝ። በጉዞአችን መኃል የፀኃዩ ንዳዳ ሲበረታባቸው ጥቂት ለመጠለል ከጥላ ስር ሲቀመጡ እኔን በሀሩሩ ፀሀይ ያስሩኝም ነበር።

ሶስተኛው ቀን ላይ እኔን በፀኃይ አስረውኝ ከጥላው ስር ተኝተው ሳለ በዝያ ሀሩር አንዳች ነገር ደረቴ ላይ ሲቀዘቅዘኝ ተሰማኝ።

ወደ ደረቴ ስመለከት ከላይ በገመድ የተንጠለጠለ ፈሳሽ ነገር ከፊቴ ተመለከትኩ። ይዤው አንድ ግዜ ስጎነጭ ቅዝቃዜው ፍፁም በራድ የሆነ እና ጠዐሙም የማር ብርዝ የመሰለ መጠጥ ሁኖ አገኘሁት።

አጣጥሜው ሳልጨርስም ወደላይ ተሳበብኝ። ብዙም ሳይቆይ መጠጡን ያንጠለጠለው ገመድ  ዳግም ወደ አፌ ዝቅ ብሎ አስጎነጨኝ ና ለሁለተኛ ግዜ ወደላይ ከፍ አለ።

ጉሮሮዬ የመጠጡን ቅዝቃዜ ከተላመደው በኋላ መጠጡ ዳግም ከአፌ ተገጠመልኝ ና እስክረካ ድረስ ጠጥቼ ደረቴ ላይ ፈሰሰ።

ሰዎቼ ሲነቁ ልብሴ በስብሶ እና የአካሌን ንቃት ተመልክተው፦‹‹ገመድሽን በጥሰሽ ውኃችን ላይ ተጫወትሽበትን? ›› ብለው ጮሁብኝ።

ምዬላቸው የተከሰተውን እውነታ ስነግራቸው፦‹‹ምትይው እውነት ከሆነማ ሀይማኖትሽ ከኛው ይሻላል ማለት ነው ›› እያሉ ውሀቸው መኖር አለመኖሩን ሊያረጋግጡ ሲከፍቱ ውሃቸው ምንም አልተነካም።

በአንድ አፍ ሁሉም እስልምናን ተቀበሉ። እኔም ቤተሰቤ ዘንድ ለአመታት ተቀመጥኩ ። ከአመታት በኋላ የነቢን ሰዐወ መሰደድ ሰምቼ ወደ መዲና በመሄድ ነፍሴን ለነቢ ሰዐወ ጀባ አልኩም።

አላህ መልካም ስራዋን ይውደድላት!

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

14 Nov, 14:36


📜

📑 ውዷ ሙስሊሟ እህቴ አላህ ባለሽበት ታላቅ የሆነው ፀጋው ያውርድብሽ እና የእኔ ውድ ዛሬም በርካቶቻችን የዘነጋነው አንድ ትልቅ ጉዳይ ለማስታወስ እሞክራለሁኝ።

💍 አቡ ሁረይራ የአላህን መልክተኛ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምን ዋቢ በማድረግ እንደዘገቡት የአላህ ነብይ እንዲህ አሉ፦

《አንድ ሰው ለሌላ ሰው እንዲሰግድ የማዝ ብሆን ኖሮ፤ ሚስት ለባሏ እንድትሰግድ አዝ ነበር።》
[📙 ቲርሚዚ ዘግበውቷል ሀዲሱ ሰሂህ ነው]

#ትኩረት

🔹 የእኔ ውድ ሰሏት አምልኮ ወይም ኢባዳ ነው፤ ፈፅሞ ከአላህ ውጪ ለሆነ አካል የማይሰጥ የአላህ ብቻ ሃቅ ነው። ታድያ የአላህ ነብይ ይህን የአላህ ሃቅ ለፍጡር ቢገባ ኖሮ ለባል ብቻ እንደሚገባ የገለፁት የባልሽን ታላቅነትና ትዕዛዙን እንድታከብሪ ሊያስገነዝቡሽ ነው።

🔹 ባልሽ በመልካም ሲያዝሽ ልትታዘዢውና ከፀያፍና መጥፎ ተግባር ሲከለክልሽ ልትርቂ ይገባል።

🔹 ለባልሽ ልዩ ቦታ በመስጠት ለእሱ ቅድሚያ በመስጠት ሃቁን በተገቢው ሁኔታ ልትወጪ ይገባል። እሱን ማስደሰትና እሱን መንከባመከብሽ አላህ ዘንድ የሚወደድ ተግባር  ነዉ


🔹 ባልሽ አላህ ጀነት የምትገቢበት ሰበብ አድርጎታል። ውዱ ባልሽን በመንከባከብ የአላህ ውዴታ ማግኘት ትችያለሽ የእኔ ውድ።

🔹 ባልሽ በጠራሽ ጊዜ እንቢ የሚል ቃል ከአንደበትሽ እንዳይወጣ ፣ አላህን የሚያስቆጣ ተግባር ነውና ባልሽን ለትዕዛዙና ለጥሪው እሺ ልትይው ይገባል። አንቺኮ የአይኑ ማረፊያው ነሽ። ከአንቺ ከሚስቱ ውጪ ሌላ ቢመለከት አላህ ዘንድ እንደሚያስቀጣው በማወቅ በአንቺ እንዲብቃቃና ወደ አንቺ ብቻ እንዲመለስ በመልካም ፍቅር ልታግዢው ይገባል።

ውዷ ሙስሊሟ እህቴ ፍቅር ማለት እኮ ሀላል በሆነ መንገድ ከውዱ ባለቤትሽ ጋር የምትኖሪው ጣፍጭ ህይወት ነው። አንቺ ምርጥ ስትሆኚ እሱም ምርጥ ይሆናል።

ጌታችንም እኮ «ምርጥ ሴቶች ለምርጥ ወንዶች » አይደል ያደረገው ስለዚህ ሰበቡን በማድረስ ላይ የበለጠ ልትታገይ ይገባል።

🔹 በገዛ እጅሽ ትዳርሽን አታውድሚው ቻይና ታዟዥ ጥበበኛ ልትሆኚ ይገባል።

አደራ አደራ እኔ በጣም እንደምወድሽ ልታውቂ ይገባል የእኔ እንቁ!!

📬 ሀቢብቲ ሼር በማድረግ መልዕክቴን ለእህቶቼ አድርሺ!! በጌታችን አላህ ፍቃድ የብዙ ቤት ትዳር ልንታደግ እንችላለን እና ሼር አድርጊው የእኔ ውድ ።

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

13 Nov, 16:39


★ማን እንደርስዎ★

ማን እንደርስዎ አለ እንደርሶዎ በሻሻ
ከዓለም መጀመሪያ እስከ መዳረሻ
የፈጢመት አባት ሙሀመድ አብደላ
ያላንቱ ከንቱ ነው ዓለሙ በሞላ
የአቡበከር ወዳጅ ደግሞ የዑመር
አላህን አገልጋይ ለይለን ወነሀር
አላህ ያወረስዎ ኑረል ሙነወር
ጅህልና በሚባል ተዛማች በሽታ
ዱንያን አፍቅረን ለሷ እንዳንረታ
በባዕድ አምልኮ በኩፍር ላንመታ
በአንቱ ላይ ወረደ የቁርአን ገበታ
እንድንቋደሰው ጠዋት ሆነ ማታ
የያእቁብ የዩኒስ የኢብራሂም ዝርያ
የኢልያስ የእስማኢል የነብዩ ያህያ
የሙሳ የኢሳ የሁሉም አንቢያ
አንቱ ነሁ ነብዩ የማጠቃለያ
አላህን አገልጋይ ያሸፊኡል ኡማ
ሞንግሎ ያወጣን ከድቅድቅ ጨለማ
ሙሀመድ እኮ ነው የዲናችን ማማ
በዚያች በትንሰኤ በዕለተ ቂያማ
ሁሉም ሲቀሰቀስ ከሙታን አውድማ
ከጭንቀቱ ብዛት አንዱ አንዱን አይሰማ
እህት ወንድም ሆነ አባባና እማማ
ለእኛ የሚያነባ ከአላህ ሊያስማማ
ወንጀላችን በዝቶ ምንም ቢገለማ
ለኡመቱ ሚቆም ሸፊኡ ለኡማ
ማን እንደ አንቱ አለ ሸፊኢ ሙሀመድ
የአላህ እዝነት ሰላም በርስዎ ላይ ይውረድ
የሩቅያ አባት ያ አበል ቃሲም
የዘይነብ የአብደላ የኡሙኩልሱም
የፋጢመት አባት ሸፊኡል ዓለም
ሙሀመድ ሙሀመድ ሙሀመድ ገራገር
አንደበትዎ አየውቅ አንዳች ክፉ ነገር
በዲኑ የማያሻሁ አንዳች ማንገራገር
ታማኝ ለመሆንዎ ያልተገኘ ወደር
ሙሀመድ ሙሀመድ ሙሀመድ ደጉ ሰው
እንኳን ለኡመቱ ለአውሬ እሚዋሰው
ሱናውን አምኖበት ለተገበረው
ሙሀባው ልዩ ነው ወደርም የለው
ሁሉም አፍ አውጥቶ ሲመሰክር
በሙሀባው ባህር ዋኝቶ ሲዳክር
ያ ሙሀመድ አሚን የኛ ሙደሲር
በጀነት ያኑረን አላህ ከርስዎ ጋር
የአይሻ ባለቤት ደግሞም የኸዲጃ
ለህይወታችን መንገድ ምሰሶ ማበጃ
ማን እንዳንቱ አለ ሙሀመድ ጀማል
አነቱ የአላህ ባሪያ የአላህ ባለሟል
ሙሀመድ ሙሀመድ ሙሀመድ ያሲን
ማን እንዳንቱ አለ ረሱሉን አሚን
ኡምሬን ባወድስዎ በኮልታፋ አፌ
በውስጤ ያለውን ሙሀባ ቀርፌ
ያለኝን በሙሉ ከውስጤ አንጠፍጥፌ
እኔስ መሞቴ ነው ስምሁን ለፍልፌ
መሞቱንስ ልሙት በጣም ደስ ይለኛል
በጀነት ከእርስዎ ጋር መኖር የት ይገኛል?
እባክህ ጌታዬ እባክህ ስማኝ
አሁኑኑ ወስደህ ከነቢ አኑረኝ
መልካምን ባልሰራ ምንም ባይኖረኝም
ረህመትህ ሰፊ ነው አትከለክለኝም
ሱናዎን አንገቤ ጀነት እንድገባ
አላህ ጨምርልኝ የነቢን ሙሀባ
ከአንተ አፈንገጨ እንዳልነድም ኋላ
እርዳኝ ያ ኢላሂ ያ ረቢ ያመውላ
ሞት በሌለበት በዚያ በሩቅ ሀገር
አኑረኝ በጀነት ከሙሀመድ ጋር።


አላሁመሰሊ ወሰለም አላ ሸፊኡል አለሚን!!!


t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

12 Nov, 17:56


ኢላሂ! በዚህች ዱንያ ላይ ባይተዋርነቴን እዘንልኝ በሞትኩ ግዜ ጭንቀቴን እንዲሁም በቀብር ውስጥ ጭርታዬን ስለ ደካማነቴ ስትል እዘንልኝ

ስለ ከፋው ስራዬ ለመተሳሰብ ከፊትህ በመተናነስ በቆምኩ ግዜ የመዋረድን ካባ ከመከናነብ ታደገኝ።

ከባሮችህ እይታ የተሰውሩ ፀያፍ ስራዎቼን ሸሽገህ፤ በእኔ ላይ ያካበበውን የነውር ደባቂ ግርጆህንም አትግፈፍብኝ።

ኢላሂ! አስክሬኔ ለትጥበት ከማጠብያው ላይ ተጋድሞ የወዳጆቼ እጆች ባገላበጡኝ ግዜ የእዝነት እጆችህን ዘርጋልኝ።

ያ ጀሊል! እግሮቼ በአዝራኢል አርጩሜ ተመትተው እና በበድንነት ገመድ ታስረው በሰዎች ጫንቃ ላይ ተንጋልዬ ወደ ቀብር በሄድኩ ግዜም እዝነትህን አትንፈገኝ።

ያ ካሊቂ! የምድር ላይ ውሌ ተጠናቅቆ ከምድር በታች በተዘጋጀልኝ አዲሱ ጎጆዬ ሙስሊሞች ሊያጋድሙኝ ከላህዱ ሲተረማመሱ ከምመለከተው የድንጋጤ ትዕይንት በቅርበትህ ታደገኝ።

አሚን ጌታዬ!

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

12 Nov, 04:43


ወዳጄ!
አንዳንዴ ስላንተ መጥፎ በመጠርጠር ብቻ የተጠመዱ ሰዎችን ለማረምና እውነትህን ለማሳየት ብለህ ብዙ አትድከም
ተዋቸው ራሣቸዉን በልተው በልተው ይለቁ
ምክንያቱም ንጽሕናህን ለማሳየት በደከምክ ቁጥር ጥርጣሬያቸው እየጨመረ ይሄዳል
ለምን ካልክ በልባቸው ዉስጥ ትልቅ በሽታ አለና

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

11 Nov, 06:46


ልባም ሴት የራሷ የሆነን ወንድ ታፈቅራለች
መልካም ወንድ ደግሞ ደስተኛ ቤተሰብን ይመስርታል ፍቅር የአላህ ስጦታ ነው
አንዳንዴ የቀረበልንን ትተን የተሻለ ስንፈልግ ለሁሉም ይረፍድብናል ከተንከባከብነው ግን ለዘለዓለም ይሆንልናል።

ጀሊሉ እውነተኛ ፍቅር ይስጠን  አሚን ❤️

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

11 Nov, 03:53


ሰው ከንቱ;…………

ሲታይ ከማያምር  ፈሳሽ ይፈጠራል
  በሆዱ ሰገራ  ተሸክሞ ይዞራል
ነገም ይሞትና  ጀናዛው ይገማል


እንዴት በዚህ መሃል………
ውበት አለኝ ብሎ  በመልኩ ይኮራል

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

10 Nov, 11:22


  የፅናት አስፈላጊነት

ወዳጄ ሆይ … ዘመኑ ወደፊት እየገፋ በሄደ ቁጥር ሕይወት ጫካነቷ እየከፋ መጥቷል፣  ዱሯ በዚህም በዚያም በዝቷል፣ ገደላገደሏ ተበራክቷል፡፡ ሁኔታዋ ብዙዎችን ግራ አጋብቷል በዚህም በዚያም ትወስዳለች፡፡ ወዲህም ወዲያም ትመልሳለች፡፡

ግና ታድያ ሰው ጠፍቷል ብለህ አትጥፋ፡፡ ሁሉም ተበላሽቷል ብለህ አትበላሽ፡፡ ብዙዎች እንደጠፉት በጫካው ዉስጥ ጠፍተህ አትቅር፡፡ በዱሩ ዉስጥ እልም አትበል፡፡ ዋናዉንና ትክክለኛዉን መንገድ በርትተህ ፈልግ፡፡ በፍለጋዉም ላይ በአላህ ታገዝ፡፡

የሚመራ አላህ ነው፡፡ የሚያድነን አምላካችን ነው፡፡ መንገዱን ባገኘህም ጊዜ  ቀጥ ብለህ ተጓዝ፡፡ በጎዳናው ላይ ፅና፡፡ ፍም እንደጨበጠ ሰው ታግሰህ ፅና፡፡ ነገሮች ቀላል ባይሆኑም፣ ፈተናዎች ቢበዙም፣ መሰናክሎች ቢበራከቱም … ወደፊት ቀጥ ብለህ ተጓዝ፣ ወደኋላ ሳታይ ተራመድ፣ ግራ ቀኝ አትመልከት፡፡ ከመጓዝ ዉጭ አማራጭ የለህም፣ ከመታገል ዉጭ መስመር የለህም፣ ነገሮች ሊጎዱህ ቢችሉም ተጓዝ፣ መንገዱ ቢመችም ባይመችም ተጓዝ፣ ሕይወት ትቀጥላለችና አትቁም፣ ከሕይወት ጋር ተጠንቅቀህ ተራመድ፣  ከቆምክ እና ለነገሮች ጆሮ ሠጥተህ ካዳመጥክ ትሞታለህ ።

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

09 Nov, 17:20


↔️መልካም ባል እና ታማኝ(የመከራ ጊዜ አጋር ) ሚስት

አዩብ ዐ.ሰ መልካም የአላህ ባሪያ፣ልጆችና ገንዘብ እንዲሁም ብዙ የአላህ ፀጋዎች የተቸሯቸው ነብይ ነበሩ። አላህም ሊፈትናቸው ፈለገና ሀብታቸውን ከሳቸው ላይ አነሳ አዩብም ታጋሽ ባሪያ ነበሩና አላህን ለምን ብለው አላማረሩም፡፡ ቀስ እያለ 14 ልጆቻቸውንም በሞት ተነጠቁ ፡ አሁንም እንደታገሱ ናቸው፤ቀጥሎም ጤናቸውን አጡ ሰውነታቸው በሙሉ ቆሰለ ሰዎች ለመጠጋት እከሚፀየፏቸው ድረስ ህመማቸው በረታ፡፡ እንዲህ እንዳሉ ለበርካታ ዓመታት ያህል ቆዩ፡፡ ታዲያ በዚህ የመከራ ጊዜያቸው ሁሉም ሲርቃቸው ከጎናቸው የነበረችው ያች መልካም ባለቤታቸው ብቻ ነበረች፡፡ሸይጧን በተደጋጋሚ በሰው ተመስሎ እየመጣ አዩብን ከእምነታቸውና ከትዕግስታቸው ሊያዘናጋቸው ቢጥርም አልቻለም፡፡ቀጥሎም ባለቤታቸውን ስለነበራቸው  ሀብትና ገንዘብ ፤የድሎት ጊዜ እያስታወሰ ሊወሰውሳት ሞከረ፡ አዩብ ዐ.ሰ ያ ሁሉ የመከራ መዓት ሲወርድባቸው አላህ ትዕግስቱንና ጥንካሬውን እንዲሰጣቸው እንጂ አድነኝ ብለው ለምነውት አያቁም ነበር፡፡ ባለቤታቸውም አዩብን" አላህን ለምን ከዚህ በሽታ እንዲያድንህ አትጠይቀውም አንት ነብይና ምርጡ ባሪያው ነህና " አለቻቸው፡፡ አዩብም የባለቤታቸውን ንግግር በሰሙ ጊዜ ተናደዱ በአላህ ላይ ያለሽ እምነትና ተወኩል ተዳክሟል ማለት ነው በማለት አላህ ጤናቸውን ሲመልስላቸው 100 ጊዜ ሊገርፏት ማሉ፡፡[እዚህ ጋር አዩብ ባለቤታቸውን ሊመቱ የማሉበት ምክንያት ተብለው የሚጠቀሱ ብዙ ሪዋያዎች አሉ ወሏሁ አዕለም)
ሆኖም ህዝቦቻቸው አዩብ ትክክለኛ የአላህ ባሪያ ቢሆኑና መንገዳቸው ልክ ቢሆን ኖሮ ይህ ሁሉ አይደርስባቸውም ነበር እያሉ ማውራት ጀመሩ፡ በዚህ ጊዜ አዩብ
እጃቸውን አነሱ እንዲህም አሉ፡-

أَنِّي مَسَّنِيَ الضُّرُّ وَأَنتَ أَرْحَمُ الرَّاحِمِينَ

«እኔ መከራ አገኘኝ አንተም ከአዛኞች ሁሉ ይበልጥ አዛኝ ነህ»
[ሱረቱል አንቢያዕ 83]

አላህም አላቸው

ارْكُضْ بِرِجْلِكَ ۖ هَـٰذَا مُغْتَسَلٌ بَارِدٌ وَشَرَابٌ
«በእግርህ (ምድርን) ምታ፡፡ ይህ ቀዝቃዛ መታጠቢያ መጠጥም ነው» (ተባለ)፡፡
[ሱረቱል ሷድ 42]

አዩብም ከፈለቀው ውሀ ጠጡ ታጠቡም ከበሽታቸውም ዳኑ።
በዚያ ሁሉ የመከራ ጊዜያቸው ያልተለየቻቸውን ሚስታቸውን ሊመቷት ቃል የገቡትን አስታወሱ ይወዷታልና ሊመቷት ከበዳቸው እንዳይተዋትም ማሀላቸው አሳሰባቸው አላህም እንዲህ ሲል ከጭንቀታቸው ገላገላቸው

وَخُذْ بِيَدِكَ ضِغْثًا فَاضْرِب بِّهِ وَلَا تَحْنَثْ ۗ إِنَّا وَجَدْنَاهُ صَابِرًا ۚ نِّعْمَ الْعَبْدُ ۖ إِنَّهُ أَوَّابٌ

«በእጅህም ጭብጥ አርጩሜን ያዝ፡፡ በእርሱም (ሚስትህን) ምታ፡፡ ማህላህንም አታፍርስ» (አልነው)፡፡ እኛ ታጋሸ ኾኖ አገኘነው፡፡ ምን ያምር ባሪያ እርሱ በጣም መላሳ ነው፡፡
[ሱረቱል ሷድ 44]

አዩብም በታጋሽነቱ ባለቤታቸውም በታማኝ አጋርነቷ አላህ አጥተውት የነበረውን ፀጋ በሙሉ እጥፍ አድርጎ መልሶላቸዋል።

☞እንባ ደርቆባቸው በውስጣቸው ለሚቃጠሉት፣ በጥርሶቻቸው ለሚያታልሉን ህመምተኞች፣ በብዙ ሰው ተከበው ብቸኝነት ለሚሰማቸው፣ የሚያፈቅራቸው የሚሳሳላቸው አግኝተው እውነት ነው ብለው አምነው ለመቀበል ለቸገራቸው፣ በየዋህነታቸው እንደ መስወዓት በግ ለሚታረዱት፣ ቃላት ሰብሯቸው ዝም ላሉ፣የቤተሰብ ፍቅር አጥተው ሕይዎት ለሰለቻቸው፣ ልጅ ናፍቀው ልጁ ለሌላቸው ትዳር አምሯቸው ትዳር ለዘገየባቸው…
በመሀከላችን እየተሰቃዩ ላላወቅንላቸው ሁሉ አላህ ይዘንላቸው አላህ ሶብሩን ይስጣቸው።

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

09 Nov, 09:10


ፅና!
---------
ልክ ባልከው ሂደት በሰው ሆዬ እይታ ሀሳብህ ቢንሻፈፍ
የገሳጮች ትችት ከመጠኑ ቢዘል ልኩን ቢተላለፍ
በእምነትህ ታግዘህ፣ከጅምሩ ንድፍህ፣ መስመርህን ሳትለቅ፣
እውነት ላልከው እውነት በአግባቡ ተናነስ አለያም ተዋደቅ ።

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

08 Nov, 18:05


السلام عليكم ورحمة الله وبركاته ያጀማ የጥያቄ እና መልስ ዉድድሩ ሊጀምር ስለሆነ ገባ ገባ በሉ ወደ ግሩፔ

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

07 Nov, 19:21


አስቂኝ ክስተት ፈገግ 😂በሉበት‼️
▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬
የመን ውስጥ ዘማር የተባለ ቦታ ላይ አንድ መስጂድ ውስጥ የተከሰተ በጣም አስቂኝ ክስተት ነው አንብበው ሳይጨርሱ በሳቅ ሟቋረጥ ግን አይቻልም¡
||
ይህ ክስተት እዚያው መስጂዱ ውስጥ ሶ'ፈል አወል (የመጀመሪያው ሰፍ) ላይ ቆሞ ሲሰግድ የነበረ አንድ ሰጋጅ ነው የሚያስተላልፍልን...
*
እናም ይህ ሰው እንዲህ ይለናል:-
«አንድ ሰው ይሞትና ተሰግዶበት ተቀበረ ከዚያም ከኢሻ ሶላት በኋላ ነእሹ (ጀናዛ መሸከሚያው) ሊመልሱት ይዘውት ወደ መስጂድ ሲመጡ ሰአት ሄዶ ስለነበር መስጂዱ ተዘግቷል።

ስለዚህ ኻዲሞች ለፈጅር ሶላት ሲመጡ እንዲያነሱት በሚል ጀናዛ መሸከሚያው ከመስጂዱ በር ከደረጃ ላይ ያስቀምጡታል።
:
ነገር ግን ሌሊት 9:30 ሰአት አካባቢ አንድ ሰውዬ ወደ መስጂድ ሲመጣ መስጂዱ ዝግ ሆኖ እና በረንዳው ተከፍቶ አገኘው የተወሰነ ቢጠብቅም መስጂዱን የሚከፍተው አጣ  ብርዱ በጣም ሲበረታበት ዞር ብሎ ሲያይ ጀናዛ መሸከሚያው ከአጠገቡ አገኘ በውስጡም ብርድልብስ ነገር አለ።
:
እና ይህ ሰው አገኘሁ ብሎ ጀናዛ መሸከሚያው ውስጥ ብርድ-ልብሱን ለብሶ ለጥ ብሎ እንቅልፉን ተኛ አባቴ! በብርድ ደንዝዞ የነበረው ሰውነቱ ትንሽ ምቾት ሲያገኝ ነፍሱንም አያውቅ ለጥ ብሎ ተኝቶልሀል...
ሃሃሃ!

ትንሽ እንደቆየ የመስጂዱ ኻዲም መጥቶ መሲጂዱ ሊከፍት ሲል በረንዳ ላይ ከነእሹ (ጀናዛ መሸከሚያው) ላይ የተኛ ሰውዬ ይመለከታል ከፈጅር በኋላ ሊሰገድበት ያመጡት ጀናዛ መሰለው...
:
ከኋላውም ሌሎች ሰዎች መጥቶ ግማሹ ሽንት ቤት ሌላው ውዱእ ሊያደርግ ይሄዳሉ ይህ በረንዳ ላይ ተኝቶ የሚያዩት ሰውዬ (ጀናዛ) ደግሞ ሁሉም ቀድመውኝ የመጡ ሰዎች ሊሰገድበት ያመጡት ጀናዛ ነው ብሎ ያስባል በውስጡ...
(ያዝ እንግዲህ¡)

በዚያ ላይ ፈጅር ነው ሰው ከእንቅልፉ ተነስቶ እየመጣ ነው ያለው ገና በደንብ ያልነቃ ህዝብ ነው።

ሊሰገድበት የመጣ ጀናዛ ይሆናል በማለት ተጋግዘው ወደ መስጂድ ኢማሙ ጋር ወደ ሚህራብ አስገቡት።
ሃሃ!
:
ብ ር ድ የቀጠቀጠው ሰውዬ ሲሸከሙት አያውቅ ተኝቷል¡ ህእ! ሰዎቹም የማን ይሁን ብለው አይጠይቁ ገና ከእንቅልፋቸው በደንብ አልነቁም እና ተሸክመው መስጂድ ውስጥ አስገቡት።

ፈጅር አዛን ብሎ ለመስገድ ወደ 50 የሚሆኑ ሰዎች ተሰበሰቡ።

ይህንን ታሪክ የሚያስተላልፍልን ሰው እኔም ከሰጋጆቹ አንዱ ነኝ የመጀመሪያው ሶፍ ላይ ነበርኩ ይላል።

ከፈርድ በኋላ ልንሰግድበት ጀናዛው ከፊት ተደርጎ የፈጅር ሶላት እየሰገድን ነው።
እህእ!
:
ልክ ለሁለተኛው ረከአ ስንነሳ ጂናዛው ሲንቀሳቀስ አየሁ እንዴዴዴ አይኔ ነው ወይስ ምንድ ነው¿ ብዬ አይኔን አበስኩ ጨፍኜም ገለጥኩ መንቀሳቀሱን ግን አልተወም በቃ እንቅልፍ አለቀቀኝም ይሆናል ብዬ አሰብኩ።

ነገር ግን ነእሹ በደንብ መንቀሳቀስ ጀመረ ያኔ መረባበሽና መፍራት ጀመርኩ።

ይህ የተኛው ሰውዬ ከብርድ ልብሱ ውስጥ ድንገት አንገቱ  አውጥቶ ሰገዳችሁ? ብሎ ጠየቀ።
:
ያኔ! ሁሉም ሰጋጆች ደንግጦ መተረማመስና መሮጥ ጀመሩ  እኔም አጠገቤ ከነበረው በር ወጥቼ በባዶ እግሬ ሮጥኩኝ ወደ 1 ኪ.ሜ ያክል የሚርቀውን ቤቴን በትንሽ ደቂቃዎች ደረስኩ ደግሞ ባዶ እግሬ መሆኔም የማውቀው ነገር የለም።
ኢማሙ (አሰጋጁም) ሲያየው ደንግጦ መሬት ላይ ይወድቋል ሌሎች ሰዎች ግማሹ ከግድግዳ ጋር ይጋጫል ሌላው ደግሞ ልክ እንደኔው በባዶ እግሩ ይሮጣል መስጂድ ውስጥ አንድ ሰው አልቀረም።
:
አሁንም ሌላኛው በጣጣጣም የሚያስቀው ክስተት ተከሰተ

ያ ከሬሳ መሸከሚያ(ከነእሹ) ላይ ተኝቶ የነበረው ሰውዬ ሲነሳ ሰዎች ሲሸሹ ሲሮጡ ሲያይ ከኋላቸው ተከትሎ መሮጥ ጀመረ።
እናንተ ምን ሆናችሁ ነው ? ቂያማ ቆሞ ነው እንዴ? እያለ ከኋላ ኋላቸው መሮጥ ጀመረ።
ሃሃሃ!
:
ሰዎቹ ደግሞ ወደ ኋላቸው ሲዞሩ ይህ ሰውዬ እየተከተላቸው  መሆኑ ያያሉ ያኔ ይብስባቸዋል ባለ በሌለ ሀይላቸው ይሮጣሉ።
በዚህ መልኩ ሁሉም  ሰላታቸውን አቋርጠው ሮጡ...»
ይለናል ቦታው ላይ የነበረ አንዱ ሰጋጅ።

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

06 Nov, 17:41


❤️እናቴ

አንቺ የኔ ዓለም የዘጠኝ ወር ቤቴ
በሆድሽ እያለሁ ቀላቢ ለህይወቴ
ችግር መቶሽ ከማይ የኔ ይቅደም ሞቴ
ዘጠኝ ወር በሸክም በሽንት በቅርሻት
ሁለት ዓመት ደግሞ ጡትሽን በማጥባት
ስወድቅ ስታመም እምባሽን በማንባት
ለዚህ ያደረሺኝ ወላጇ እናቴ
ያላንቺ በፍፁም አያምርም  ህይወቴ
ኑሪልኝ ዘላለም አንቺ ነሽ ኩራቴ
ስቸገር ደጋፊ ሳጠፋ መካሪ
በወርቅ ዕንቁ አልማዝ የማትቀየሪ
አንቺ ነሽ የኔ ሀብት ለዘላለም ኑሪ
የወላጅን ፀሎት አንተ እንደምሰማ
የኔንም ልመና ፈጣሪዬ ስማ
ዕድሜ ጤና ስጣት አደራ ለማማ


t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

06 Nov, 04:42


አላውቅም!
~~
ከሰውጋር ለመኖር ፣ ከሰው ለመካረም
ሚስጥር ሳትፈለፍል ፣ ነገር ሳትለቃቅም
ክብርህ እንዲጨምር በእውቀት እንድትመጥቅ
ከነገሩ ሁላ……
እያወክም ቢሆን አላውቅምን አጥብቅ
አላውቅም!

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

05 Nov, 04:34


ያረብ ያንተ ተስፋ ሲቀር ተስፋዎች ሁላ ተቋርጠዋል። ያንተ በር ሲቀር የንጉሳኑ በር ሁላ ተዘግቷል። ያንተ እዝነት ሲቀር የሁሉም ልቦና በወገኖቻችን ላይ ጨክኗል።

ጉልበተኞች ተሰባስበው ጉልበታቸውን በህፃናት እና በደካማዎች ላይ ባሳረፉ ግዜ የሚመዘዘውን የቅጣት በትርህን ምዘዛት። የዓድ ህዝቦች በግዝፈት እና በጉልበታቸው በተመኩ ግዜ በአየር ላይ አንሳፈህ የቀጣኻቸውን ተዓምርህን ዛሬ እንሻዋለን'ና በዳዮችን የውርደት መንሳፈፍን አንሳፍፍልን።

ኑምሩድ በንግስና ግዛቱ ተመክቶ ባመፀ እና በበደለ ግዜ በትንኝ ያዋረድከው ጌታ ሆይ! በዳዮቻችንን አዋርደህ ተበቀልልን።

አማፅያን ህዝቦች ላይ ምድርን መገልበጥህ ከመፅሐፍህ ደርሶናል፤ ጌታችን ሆይ ኢስራኢል በህፃናት ደም ላይ አመፀች፤ ምድርን በላይዋ ገልብጥባት።

ያ ጀባር! ነብያቶችህን በመግደል ታውቃቸው የነበሩ እኚህ አማፅያን ህዝቦች ዛሬ የነቢይህ ኡመት የሆኑ ህፃናት ባሮችህን ጨፍጭፈዋል'ና ባሻህ ቅጣት ተበቀልልን።

ቻይ ነህ እሚሳንህ የለም፤ ቀጪ ነህ እሚቋቋምህ የለም፤ ከባቢ ነህ ማንም ከከበባህ አያመልጥም። በዳዮችን ከበህ ያስለመድካቸውን ቅጣት እያየን ቅጣልን።

አሏሁመ ሰሊ ዓላ ሙሐመድ

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

04 Nov, 17:16


የአማኝ ነገር
...
‹ሐስቢየላህ!› በሚለው ቃል ተማምነን ከስንቱ ፍራቻ ድነናል፡፡
‹ማሻአላህ!› የሚለውን ቃል ተጠቅመን ሰንቱን ቅናት አባረናል፡፡
‹ለበጎ ነው› በሚል ቃል ተስፋ አድርገን ስንቱን ጉዞ ጨርሰናል፡፡
‹ሱብሓነላህ!› በሚለው ቃል ተገርመን ከስንቱ ጥላቻ ተርፈናል፡፡
‹አልሐምዱ ሊላህ› በሚለው ቃል ተንፍሰን ከስንቱ ህመም ተፈውሰናል፡፡
‹ላ ሐውላ ወላ ቁወተ ኢልላ ቢልላህ›ን ይዘን ከስንቱ ሐዘን ወጥተናል፡፡
‹ኢንና ሊላሂ ወኢንና ኢለይሂ ራጂዑን› ብለን ከስንቱ ጉዳት አገግመናል፡፡

እኛ በአላህ ሱ.ወ. የምናምንና የምንተማመን ሙስሊሞች ነን፡፡ ግራም ነፈሰ ቀኝ የትክክለኛ አማኝ ነገር ይገርማል፡፡ ሲያገኝ አብዝቶ ያመሰግናል፡፡ ሲያጣ  ደግሞ ከልብ ከሆነ ዉዴታ ጋር ይታገሳል፡፡ በዚህም የተነሳ ሁለቱም መልካም ይሆኑለታል ።

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

03 Nov, 18:52


ውዷ እህቴ ሆይ!! ምናልባት ሰምተሽ ይሆናል ፡-

" እከሊት እኮ ከ እከሌ ጋር ፍቅቅሮሽ ላይ ናቸው " ሲባል ይህን ስትሰሚ ግን ትልቅ ነገር እንዳይመስልሽ ።

እህቴ ሆይ! ምናልባት ወንዶች ቀረበው "እወድሻለው ! የኔ ውድ! የኔ ፍቅር !" እያለ በሚያወጣቸው ቃላቶች እንዳትሸነገይ።

ገና ተማሪ ተሁኖ እያለ የወጣትነት እና የጉርምስና ጊዜ ላይ ሲደረስ ብዙ ነገሮች በወጣቱ ላይ ይታያል፡

ምናልባት ጓደኞችሽ " ፍቅር ይዞኛል!!" እየተባባሉ ተራ ወሬ ሲያወሩ ትልቅ ቁም ነገር ሊመስልሽ ይችላል ። ግን ወላሂ አትሸወጅ እህቴ ገና ተቀራርባችሁ በደምብ ሳትተዋወቂው ወደ አልጋ ይጋብዝሻል።

እህቴ ሆይ! ክብርሺን ሊያጎድፍ ይሸነግልሻል ።" እወድሻለው ሁሌም እኮ ያንችው ነኝ! በጊዜ የተጀመረ ፍቅር ስሩ ያብባል ፍቅራችን ይጨምራል" ይልሻል ።

እህቴ ሆይ! እያሾፈብሽ ነው !!!!!

እህቴ ሆይ! ምናልባት ሰምተሽ ይሆናል " እከሊት ከእከሌ ጋር አንሶላ ተጋፈፉ! ክብሯ አሳልፋ ሰጥታ ተንጓላ ቀረች" ሲባል ዛሬም አንቺን እንደዛ እሚሸነግልሽ ክብርሺን ሊቀማሽ ነው  የሰው መጠቋቆሚያ ሊያደርግሽ ነው  የወደፊት ህይወትሺን ሊያጨልመው ነው።

እህቴ ሆይ ! ለአንቺ እኮ ክብርሽ ማለት የህይወትሽ ዋናውን መሰረት በሱ ይያዛል።
ሰምተሻል እኮ "ክብሯን ከወሰደ በኋላ ላሽ በይ አላት " እየተባለ ሰው ሲጠቋቆምባት።

ግን ያን ሁሉ እያየሽ "እሱ ከንደዚህ አይነት ወንዶች ይለያል እሱ እኮ ጥሩ ልጅ ነው ይወደኛል እሱ የሚወደውን ማድረግ ለኔ ደስታን ይሰጠኛል!!" እየተባለ አሁንም ክብሯን አሳልፋ ትሰጠዋለች ፡፡

ከዛ ከነመፈጠሯ እንደማያውቃት ይሆንባታል ። ያ በፊት  " ካላንቺ መኖር አልችልም መቼም አልለይሺም" እያለ ቃል ሲገባላት እንዳልነበረ ዛሬ "በናትሽ ተይኝ! ምንድን ነው እንደዚህ መንዘላዘል አልፈልግሺም አልኩሽ አይደል" ብሎ ከሰው ፊት ያዋርዳታል።

ለጓደኞቹ ይሄድ እና "እከሊትን እኮ ጠብ አደርግኳት" ይላል ።

እህቴ ሆይ! ይሄ ሁሉ ችግር ከመምጣቱ በፊት ወደ አንቺ ሲቀርብ በፈገግታ ባትቀበይው ሀገር ሰላም ይሆን ነበር ።

እወድሻለው ካለሽ፡ አንቺም ከወደድሺው፡
ወደ ኸይሩ መንገድ ፡ በቶሎ ጠቁሚው፡

አልፈልግም ካለ ፡ምክኒያቱን ካበዛ፡
እያጀጃለሽ ነው ፡ አድርጎ ፈዛዛ፡

እናማ እህቴ ጥሩውን ፈልጎ በሀላል ከመጣ፡
አንቺን ወዷል እና አታብዥበት ጣጣ፡

ያ አልሆን ብሎ በጓሮ ከመጣ ፡
በዛው አሰናብችው ችግር ሳያመጣ፡

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

03 Nov, 10:13


ልቤን ሀዘን ሰብሮት አንገቴን ደፍቼ
እየጠበኩህ ነው ሁሉን ላንተ ትቼ
ሁሉን ላንተ ሰጠው አቅም ቢያንሰኝ
ሰሚ ተመልካች ነህ አንተው ፍረደኝ
.
.
ችዬ ምገፉበት አቅም ባይኖረኝም
ባንተ ከተመካሁ ማንም አይጥለኝም
ጃሉትን ግዙፉን ዳውድ የጣለው
በጉልበቱ አይደለም ይህን አውቃለው

.
.
ባንተ ተመክቶ የለም የተረታ
ሁንልኝ ያወኪል ጋሻና መከታ
ሁኔታው ከፍቶብኝ እጅግ ብቸገርም
ሀስቢየላሁ ብዬእንዲሁ አተወኝም

.
ሀስቢየላሁ አልኩኝ አንተን ተማምኜ
ባንተ ከመመካት አላውቅም ቦዝኜ
ውሳኔህን እንጂ የምጠብቀው
ጥለህ እንደማጥለኝ እርግጥ አውቃለው

.
.
ስንቱን አሳፍኩ አረ ስንቱን ስንቱን
ስደት እንግልቱ ርሀብ ጥማቱን
ሁሉን እችላለው ይሁን ግድ የለኝም
ሀስቢየላሁ ካልኩኝ ማንም አይነካኝም
ሀስቢየላሁ ወኒመል ወኪል
.
.
ዛሬ ለሰው ብታይ የማልችል መስዬ
በሶብር እቆያለው ይደርሳል ተራዬ
ለኔም ቀን ወቶልኝ ስታይ ከፍ ብዬ
ያኔ ይታበሳል ይደርቃል እባዬ

.
ልጄን ቤተሰቤን ወዳጄን በትኜ
እንደተከራተትኩ አልቀርም ባክኜ
ስደት እንግልቱን ሁሉን እችላለው
ዛሬን ልችል እንጂ ነገ አገኘዋለው

ጋደም አልኩኝ እንጂ ጨርሶ አልተኛሁም ጀምበር ብቅ እስክትል እጠብቃለሁኝ
ሀስቢየላሁ ብዬ ባንተ ተመክቼ
በተስፋ እቆያለው በዱዓ በርትቼ

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

02 Nov, 17:16


ሁለት ተጓዥ መላእክት በጉዞ ላይ ሳሉ ይመሽና በአንድ ሀብታም ቤተሰብ ቤት ውስጥ ለማደር አሰቡ ፡፡ ቤተሰቡ ጨዋነት የጎደለው በመሆኑ መላእክቱ በግቢው የእንግዳ ማረፊያ ክፍል ውስጥ ለማደር  ደስተኛ አልሆኑም ፡፡
:
ይልቁንም መላእክቱ በቀዝቃዛው ምድር ቤት ውስጥ አንድ ቦታ ተሰጣቸው ፡፡ መተኛቸውን ሲያበጃጁ ትልቁ መልአክ ግድግዳው ላይ አንድ ቀዳዳ አይቶ ተቀደድውን ግድግዳ  ጠገነው
:
ታናሹ መልአክ ለምን ብሎ ሲጠይቅ ታላቁ መልአክ “ነገሮች ሁል ጊዜ አንድ አይነት አይደሉም ፡፡ሲል መለሰለት
:
በቀጣዩ ቀን ምሽት መልአኮቹ ድሃ ፣ ግን በጣም እንግዳ ተቀባይ ገበሬ የሆኑ ባል እና ሚስት ቤት አረፉ ፡፡ ባልና ሚስቱ ያገኙትን ትንሽ ምግብ ከተካፈሉ በኋላ መላእክቱ ጥሩ ሌሊት እንዲያሳልፉ  በሚችሉበት አልጋቸው ላይ እንዲተኙ አደረጉ ፡፡
:
በማግስቱ ጠዋት ፀሐይ ስትወጣ  መላእክቱ ገበሬው እና ባለቤቱ በከባድ ለቅሶ ላይ ሁነው  አገኛቸው  ፡፡ ወተታቸው ብቸኛ ገቢያቸው የነበረው ላሟ በሜዳ ላይ መሞቷን ተከትሎ  ፡፡
:
ታናሹ መልአክ ተቆጥቶ ትልቁን መልአክ “ይህ እንዳይሆን ማድረግ  ትችል ነበር? የመጀመሪያው ሰው ሁሉንም ነገር ነበረው ፣ ግን እርሱን ረድተኸዋል” ሁለተኛው ቤተሰብ እምብዛም ያልነበረው ነበር ነገር ግን ሁሉንም ነገር ለማካፈል ፈቃደኛ ነበሩ ፣ እናም ላሟ እንድትሞት ፈቅደሀል ፡፡
:
ትልቁ  መልአክ “ነገሮች ሁልጊዜ አንድ አይነት አይደሉም” ሲል መለሰ ፡፡ "እኛ በግቢው ምድር ቤት ውስጥ ስንቆይ እዛዚያ ግድግዳ ላይ በዚያው ቀዳዳ ውስጥ የተከማቸ ወርቅ እንዳለ አስተዋልኩ ፡፡
:
ባለቤቱ በስግብግብነት የተያዘ እና መልካም ዕድሉን ለማካፈል ፈቃደኛ ባለመሆኑ እኔ የደበቀውን ወርቅ እንዳያገኝ ግድግዳውን ደፈንኩት ፡፡ እሱ
:
"ትናንት ማታ በአርሶ አደሮች አልጋ ላይ እንደተኛን የሞት መልአክ የገበሬውን ሚስት ለመውሰድ መጣ ፡፡ ይልቁንም የሞት መልአኩ የገበሬን ሚስት እንዳይወስድ ላሚቷን ሰጠሁት ፡፡
:
ሲል መሉሰለት አንዳንድ ጊዜ ነገሮች እኛ እንዳሰብነው ​​ሳይሆኑ ሲቀሩ ይህ የሆኑው ለከይር ነው ( ለበጎ ) እንደሆነ ማሰብ መልካም ነው።
:
መልካም ነገር ማድረግ አስከፊ ነገሮችን የመከላከል አቅም አለው ።

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

01 Nov, 18:02


ብዙ ምሽቶች አባትን ያስታዉሱኛል
ስለ የትኛው አባት ካላችሁኝ

“ሱብሒ ወጥቶ ሲደክም ዉሎ አምሽቶ ስለሚገባው አባት፤ ልጆቼን እንዴት ላሳድግ ብሎ በሀሳብ እየተብሰለሰለ ያለ እንቅልፍ ስለሚያድረው አባት በባስ እየሄደ በታክሲ ልጁን ስለሚልከው አባት ጫማ ሳይቀይር ልጁን ስለሚያስዘንጠው አባት ባገኘ ጊዜ በሰባት እጆቹ አስቤዛ ሰብስቦ ስለሚገባው አባት ባጣ ጊዜ ሐዘን ፊቱን ስለሚያጠቁረው አባት በዱንያ ፈተናዎች ላለመዋጥ ስለሚታገለው አባት፣ ሀሳብ ጭንቀቱ ሁሉ ስለ ልጆቹ የወደፊት ዕጣፈንታ ስለሆነው አባት በዕዉን በህልሙ ልጆቼን! የሚል ቃል ከአፉ ስለማይጠፋው አባት

ልጅ ሆኜ የአባትነትን ግርማ ሞገስ ብላበስ ብዬ የአባቴን ትልቅ ኮቱን ለብሻለሁ ሰፊ ጫማው ዉስጥ ቆሜያለሁ፣ እጄን በእጁ ለክቻለሁ ከዘራዉን ይዣለሁ፣ ኮፍያዉን አጥልቄያለሁ አማማዉን ጠምጥሜያለሁ ሽርጡን ሸርጫለሁ
ልጅ ሆኜ በርግጥም እንደ አባቴ ትልቅ ለመሆን ጓጉቻለሁ፡፡ አባትነትን ናፍቄያለሁ

ድሮ ያኔ አባትነት ሲባል ቀላል ነገር ይመስለኝ ነበር፤ እሱ ልጆቼን! ሲል አፉ ስለለመደበት ብቻ ይመስለኝ ነበር፡፡ ልጁ ሲወድቅ እኔን ድፍት ያድርገኝ ሲል ልቡ የሚሰነጠቅ አንጀቱ የሚተረተር አይመስለኝም ነበር፡፡

አባት .... ሾፌር ሲሆን ልጁ ይደቀንበታል፣ ስልክ ሲደወል ልጄ ምን ሆና ይሆን? የሚል ሀሳብ ቀድሞ ጭንቅላቱ ላይ ይመጣበታል መንገደኛ ሲሆን መንገዱ በረዘመ ቁጥር የልጆቹ ናፍቆት ይጠናበታል፡፡

አባትህ እንዴት እንዳሳደገህ ብታውቅ ኖሮ ባንተ ላይ ያለው ሐቅ እንጂ በሱ ላይ ያለህ ሐቅ ትዝ አይልህም ነበር
ለዚህም መሰለኝ የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ.) “አንተም ሆንክ ሀብት ንብረትህ የአባትህ ናቸው የሚሉት

ጌታዬ ሆይ ባለፈው ዕድሜያችን ከወላጆቻችን አንፃር ያጎደልነዉን ሁሉ ይቅር በለን፤ በተቀረው ዕድሜያችን የምንኻድማቸው አድርገን፡፡ 

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

01 Nov, 06:59


ኢቅራዕ …!

በጥበብ ስም!
ሁሉን ባሳወቀ
ጥሬ ድንቁርናን ፈጭቶ ባደቀቀ
ኢቅራዕ …!
በእውቀት ስም!
ሁሉን በታቀፈ
የዓለምን ምስጢር በወግ በሸከፈ …
ለዚያ ግግር ሕይወት፣ ቅፍድድ ስብዕና
ከመርግ ለከበደ፣ ለድድር ልቦና
ለጎጠኝነት ጥግ፣ ለትብትብ ህሊና
ለዝተት ማንነት፣ ለቁልቁል ጎዳና…
ኢቅራዕ!
የቀራ ነው የተጠቀመ
ምድርን የከረከመ
ወደ ሰማይ የተመመ
ህዋው ላይ የከረመ!
ለዚያ ለሙት መንፈስ፣ በቁሙ ለቃዠ
በውሎው ባዳሩ፣ ለተንቀዠቀዠ
ለዚያ ዝርክርክ ቤት፣ ላልተሰነዳዳ
ለወልጋዳው ማጀት፣ ለጨለማው ጓዳ
ኢቅራዕ!
የቀራ ነው ህልሙ የፀና
አክራሞቱ ቀኑ የቀና
ብርሃን ፀዳል የለበሰ
በኑሮው ላይ የነገሰ!
በስማ በለው አፍ ለታመሰው ደጅህ
ለመንጋው ጋር አብሮ ለሚያቦካው እጅህ
ለእርሾው ለሊጡ ለዳቦው ለንጀራው
ለሙያው ለንግዱ ለትጋት ለስራው …
ኢቅራዕ!
የቀራ ነው የከበረ
ምድርን የበረበረ
ወደ ሰማይ የበረረ
አየር ላይ ውሎ ያደረ!
ለኑሮህ ለሞትህ፣ ለተፈጥሮህ ግዳጅ
ለሰውነትህ ልክ፣ ላንተነትህ አዋጅ
ጨለማህን አብራ፣ ነፍስያህን አግራ
ከከንቱ እንቶ ፈንቶ ህይወትህን አጥራ …
ኢቅራዕ!
የቀራ ነው የተጠቀመ
ምድርን የከረከመ
ድንቁርናን ያከመ
ሕይወትህን ያስደመመ
ኢቅራዕ!!!


t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

29 Oct, 15:55


መጅኑን ለይላ

( ክፍል 12

………መጅኑን የለይላን እምቢታ በሰማበት ቅፅበት በፍላፃ እንደተወጋ ሰው በቁሙ ተዝለፍልፎ በንብርክኩ ፈገመ፡፡ እሬት እንደቀመሰ ብላቴና ፊቱ በቅፅበት ተገለባብጦ ከንፈሩ እየተንቀጠቀጠ ተናገረ።

" ማ....ማ...ማለት? መንገዴ መንገድሽ አይደለም? እውነትም እንደሚሉት እሱ በልጦብሻል? ለይላዬ! እውነት የሌላን ሰው ቃል ኪዳን ልታጠልቂ በልብሽ የነበረን የኔን ኪዳን ፋቅሽው?" አላት፡፡

ለይላም የሚንቀጠቀጥ እጇን አፏ ላይ ጭና ከማልቀስ ውጭ መልስ አጣችለት፡፡ አንደበቷ ሲዋሽ አይኖቿ ያንደበቷን ውሸት አስተባብለው ያንጀቷን እውነት ሊናገሩ ያነባሉ፡፡እንባ ካይኖቿ እንደ ፏፏቴ እየተግተግለ ነው።

" ምነው ለይላዬ አነስኩብሽ? እብድ ነው አሉሽ አይደል? ግን እኮ ሁሉም ስላንቺ ነበር፡፡ ግን እኮ ቃል ተገባብተን ነበር? ውላችን እኮ እስከ ወዲያኛው ጀነት ድረስ ነበር! በቃ? ታዳ ይህ ነው መጨረሻው? መልሺልኛ!!!!! ላንቺ ጀነቱ ይህ ነው? ላንቺ ይሄን ያክል ቀላል ነው ወይይይይይ?"

እያለ መጅኑን ከመሬት እራሱን እያላተመ ጮኸ ፣ ሰከረ፡፡ ለይላም እንዲያ ሲሆን ማየት ተስኗት በፍርሃት የተወረረውን አካሏን፣ድንጋጤ ያብረከረከውን እግሯን አንስታ ከግቢ ሸሽታ አፈተለከች።ለይላ ስትንሰቀሰቅ እሮጠች፡፡ሰው እንደገደለ ሰው እያንዘፈዘፋት በመከራ ቤቷ ደረሰች፡፡

ከዛን ጊዜ በኀላ መጅኑንም ላይመለስ ቆርጦ የ ነጅድን  ከተማ ለቆ ወደ ሂጃዝ ጫካዎች፣ብቸኝነቱንና ፍቅሩን በልቡ ቋጥሮ፣ትዝታዋን ምናቡ ላይ አኑሮ አቀና፡፡ ከለይላ ያለውን ተስፋ በለይላ ቃል አሟጦ ገደፈ፡፡ ዘላለሙን ላያገኛት ግና ዘላለሙን እንዲያፈቅራት የተፈረደበትን እጣፋንታውን ተቀብሎ ከነጅድ ኮበለለ፡፡

እንደዋዛ ሳምንታቶችም ነጎዱ የለይላ ቤተሰቦች እና የወርድ ቤተሰቦች የልጆቻቸውን የሰርግ ቀን ቆርጠው የሰርጉ ሽርንጉድ በሁለቱም በኩል ተጧጡፏል፡፡ ለይላ የሰርጓን ቀን ምድር እንደምትጠፋበት የመጨረሻው ቀን በፍርሀት እየራደች ስትጠብቀው ቀኑ ደርሶ ከወርድ ጋር ተሞሸረች፡፡ ህይወቷን ሙሉ  ያለመችው ከመጅኑን ጋር የመኖር ህልሟ ተጨናገፈ፡፡ ህለሟ መና ሆኖ ቀረ።ልቧን ሌላ ሰው ጋር ገላዋን ሌላኛው ጋር እንድታሳድር ህይወት ፈረደችባት፡፡ ቀን በቀን መጅኑንን እያሰበች ብታነባም አንዴ የወሰነችውን ውሳኔ መልሳ ሽራ ነገሮችን መመለስ አትችልም፡፡ በዚህም ምክነያት ህይወቷን አምርራ ጠላችው፡፡ መጅኑን የሌለበት አለሟ ውስጥ መተንፈስ ቀፈፋት፡፡ ከምግብም ከውሀም ተከልክላ እራሷን ቀጣች፡፡ በየ ቀኑ ስለ መጅኑን እያብሰለሰለች ከስታ ሰለለች፡፡ ከነጅድ የሚመጣን የነጅድ ነዋሪ ባገኘች ጊዜ ስለሱ ከመጠየቅ ቦዝና አታውቅም፡፡

አንድ ጊዜ ዲመሽቅ የሚመላለሰው ነጋዴው አሊን አግኝታ ……
ለመጅኑን ደብዳቤ ያደርስላት ዘንድ ከአደራ ጋር ሰጠችው፡፡  አሊም ወደ ነጅድ ከተማ እንደተመለሰ በሂጃዝ ጫካዎች መጅኑንን አፈላልጎ በአደራ የተሰጠውን ደብዳቤ ሰጠው፡፡

መጅኑን የደብዳቤውን ተቀብሎ በጉጉት እየተጣደፈ ከፈተው።ከቆዳ ተልጎ በተሰራው ወረቀት ላይ የሰፈሩት የለይላ ቃላቶች ለይ አይኑን ቀሰረ፡፡ ለመጅኑን ከቃላትነት ባሻገር ጥልቅ ስሜት አላቸው፡፡
ደብዳቤው እንዲህ ይላል

ይቀጥላል

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

29 Oct, 06:02


እናት ልጇን ትከሳለች።
‹‹ልጄ ሚስቱን ከእኔ በላይ ይወዳታል››
ሸይኩም ይመልሳሉ፦‹‹ከብርትኳን እና ከቲማቲም የቱ ይጥማል?›› እናት ተጠየቀች።

የመገረም እይታ እየተመለከተች፦‹‹ለንፅፅር እማይመች እና ሁለት የማይተካኩ ነገሮችን ነው ያማረጥከኝ። ብርትኳን ፍራፍሬ ነው፤ ቲማቲም ደግሞ አትክልት። ሁለቱም የየራሳቸው ጣዕም ነው ያላቸው...››

ሸይኩ  ንግግሯን አቋርጧት፦‹‹አየሽ እማ! ፍቅርም እንዲሁ ነው። እንደ ፍራፍሬው እና አትክልቱ ሁላ ፍቅርም የማይተካካ አይነት ነው። ››

እናት ተገረመች፦‹‹እንዴት እንዴት?›› ማብራርያ ፈልጋ።
ሸይኩ፦‹‹አንቺ እናት ነሽ፣ ጀነቱም ነሽ። እሱ ደግሞ የአብራክሽ ክፋይ ነው። አንችን መውደዱ ዒባዳ(አምልኮ) ነው። ሌላኛይቱ ሴት ደግሞ አላህ ከጎድኑ የፈጠራት ሚስቱ ናት። እሷን መውደዱ ደስታው ነው።

እማ! ልጅሽን በአምልኮው እርጂው። ደስታውንም ውደጂለት። ቢወድሽ ጀነቱ ነሽ፤ ቢወዳት ደስታው ናት፤ ላንቺ ያለውን ፍቅር ለሚስቱ ካለው ፍቅር ጋር እያነፃፀርሽ ፍቅርሽን አታሳንሺው

ልጅሽን ተይው፤ በጀነቱ እና በደስታው መካከል በነፃነት ይመላለስ››

እናት አንገቷን እየነቀነቀች፦‹‹ትክክል! እኔን መውደዱ አምልኮ፤ እሷን መውደዱ ደስታ ነው'ና አምልኮው ሳይጓደልበት ደስታውንም እንዲያጣጥም እረዳዋለሁ››

t.me/muselimnegn

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

28 Oct, 04:55


ልሂድ ወደ ሀገሬ፣ ሻንጣዬን ጠቅልዬ
ሰላትን ለመስገድ፣ እኔ ለአላህ ብዬ
ትምህርት ብሎ ነገር፣ አልፈልግም በቃኝ
ኢስላም ሃይማኖቴን፣ ከሆነ ሚያሳጣኝ
ደግሞ ተራ ነገር፣ እርክስክስ ላለው
ለእውቀት ከሆነ፣ ዲኔ በቂዬ ነው
እስልምና እምነቴ፣ ከምንም በላይ ነው
ኒቃቤን አውልቄ፣ ሰላቴንም ትቼ፣ ዲግሪ ከማመጣ
ፈርዴንም ሱናውን፣ ሁሉንም ከማጣ
ትምህርቱ ይቅርብኝ፣ በአፍንጫዬ ይውጣ
ልሂድ ወደ ሀገሬ፣ ወደ ምኖርበት
ኒቃብ አትልበሱ ሰላት አትስገዱ፣ ወዳልተባለበት
አይደለም መማሩ፣ መኖሩም ይቅርብኝ
አላህን ረስቼ፣ እኔ ህይወት የለኝ
ሂጃቤን ለብሼ፣ ሰላቴን ሰግጄ፣ በዱዓ በርትቼ
መኖር ነው ምፈልገው፣ ከአላህ ተወዳጅቼ፡፡

@islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

27 Oct, 16:55


መጅኑን ለይላ

  ~~ ክፍል 11

አላህ እኮ ለይላን የሌላ ሰው ስጦታ አደረጋት፡፡ ለኔ አላደረጋትም፡፡ ነገር ግን የፍቅርሯ ፈተና የተሰጠው ለኔ ነው፡፡ ጌታዬ ሆይ????? ምናለ በሷ ፍቅር ባትፈትነኝ፡፡ ምናለ ከለይላ ፍቅር ውጭ በሆነ ነገር ብትፈትነኝ"፡፡

እያለ ሳግ በሚተናነቀው ሰላላ ድምፁ ሲያነበንብ ለይላ ደረሰች፡፡ አሊ እና ጓደኞቹም ለይላ እንደመጣች ሲመለከቱ እንደሚታረድ በሬ ከመሬት አጋድመው የያዙት ጓደኛቸውን ለቀቁት፡፡ "ለይላዬ መጣሽ? ተመልከች... ሁሉም ለኔና አንቺ አጥር እያበጀ ሊለያየን ይታትራል፡፡ ይሄው አሁን ደግሞ ጭራሽ አንቺን ለሌላ ሰው ሊድሩሽ እንደሆነ ሰማሁ፡፡ እውነት ነው የምሰማው? እባክሽ ውሸት ነው በይኝ"፡ አለ መጅኑን፡፡

ለይላም እንባ እያነቃተሸ ጭንቅላቷን ወደላይ ወደታች ነቅንቃ አዎንታዊ መልስ ባንገቷ መለሰችለት፡፡ "እና ምን እንጠብቃለን እንጥፋ ፣ እንሽሽ!  በጀበሉ ሰውባን ያለምነውን ህይወት ከምንኖርበት የኔና አንቺ አለም እንሂዳ! ሁሉንም እዚህ ትተን አንጥፋ! ተከተይኝ" ብሏት ከትቢያው ላይ ተነሳ፡፡

ለይላ በሚያነቡ አይኖቿ ቡዝዝ ብላ አስተዋለችው፡፡ ጥያቄውን ተቀብላ አብራው ብትኮበልል የሁለቱም እጣ ፋንታ ምን ሊሆን እንደሚችል አሰበችው፡፡ አባቷ ሰእድ  በሄዱበት ሁሉ ዳናቸውን ተከትሎ ሰላም እንደማይሰጣቸውና በህይወት እንዲኖሩ በፍፁም እንደማይፈቅድላቸው ታውቃለች፡፡ ስለዚህ "አይ አይሆንም! አሁን እኔ ላገባ ነው፡፡ ይህን እውነት ተቀበል፡፡ በቃ እርሳኝ!" ብላ ለመጨረሻ ልትሰናበተው ቆርጣለች።

በርግጥ ውሳኔዋ ምስቅልቅል ህይወታቸው ባይባጀውም ግና ከነፍሷ በላይ የምትወደው እሱን በህይወት ያቆይልኛል ብላ አስባ እየከበዳትም ቢሆን ልትነግረው ወስናለች፡፡
ግን ደግሞ ቃሉ ከጉሮሮዋ ተሰንቅሮ አውጥታ ልትናገረው አቃታት፡፡ ምን ያክል መጅኑንን ሊጎዳው እንደሚችል ታውቃለችና ፈተና ሆኖ ታከታት፡፡
ባንድ በኩል ያለው ውሳኔዋ ደግሞ እስከ መጨረሻ የሚገድለው ነውና ልትሰናበተው ቆረጠች፡፡

መጅኑንም "በያ ተከተይኝ?"እያለ እጁን ዘርግቶ ወደ ለ መንገዱ ጋበዛት፡፡
በመጨረሻ የሞት ሞቷን ተናገረች።

"አይ ፣ አይ አይሆንም"! እያለች ጭንቅላቷን ወዘወዘች፡፡

ይቀጥላል

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

26 Oct, 07:10


እህቴ ውበትሽን ተመክተሽ የሰዎችን አድናቆት ሰምተሽ ፍቅርን አትግፊ፤የቃላት ጋጋታ ልብሽን እንዳያሳስተው፤በዚህ ምድር አንቺን ከልቡ እንዲያፈቅር የተፈጠረው አንድ ሰው ነው እናም የነሱ አድናቆት በዝቶ ያንን ሰው እንዳያሳጣሽ
አንድ አሪፍ የእንግሊዞች አባባል አለ

👉ዕድለ ቢስ ቁንጅና ከሁነኛ ባል ይልቅ ብዙ አፍቃሪዎችን ይስባል !!

ዛሬ ላይ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ውበትሽን አይተው ወዳንቺ ሊመጡ ይችላሉ ግን እመኚኝ ማናቸውም ቢሆን አንቺን አያፈቅሩሽም፤እነሱ ፍቅር የያዛቸው ካንቺ ማንነት ሳይሆን ከውጫዊ ውበትሽ ጋር ነው ዛሬ ላይ ብዙ ነገር ሊያደርግልሽ ይችላል፤ምክንያቱም ቆንጆ ስለሆንሽ እሱ ቢተውሽ ሌላ ብዙ ፈላጊ እንዳለሽ ስለሚያውቅ።

ግን ደግሞ ነገ ከነገ ወዲያስ??? መቼስ እድሜ ልክ እንደዛ ቆንጆ ሆነሽ አትኖሪ ውበትሽ መርገፉ አይቀርም እና ያኔስ???
እውነት ያ ሰው በዛ ደረጃ ላንቺ ቦታ ይሰጥሻል???
በፍፁም……………መቼም ቢሆን አያደርገውም ምክንያቱም
እሱ ያፈቀረው ውበትሽን ነበር ዛሬ ላይ ደግሞ ያንን ውበት ካንቺ ሲያጣ ዞር ብሎ አያይሽም

ስለዚህ ምርጫሽ ላይ በደንብ አስቢበት የቃላት ዶፍ ልብሽን አይበግረው ምናልባት እውነተኛ አፍቃሪሽ ምን እንደሚልሽ ግራ ገብቶት በዙሪያሽ እየተንከራተተ ይሆናል፤አርቆ ማሰብን አትርሺ
ምን ለማለት ፈልጌ መሰለሽ   
ለትዳር እጁን የዘረጋልሽ ካገኘሽ አታንገራግሪበት እሺ ብለሽ አምነሽ ግቢበት  ትዳር ከብዙ ነገር መጠበቂያሽ ነዉና ።

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

24 Oct, 17:09


መጅኑን  ለይላ  (ክፍል 10)
………

በትንሳኤ ቀን የስቃይ ፍርድ ተበይኖባቸው ለስቃይ ወደ ጀሂም እንደተላኩ ቅጣተኞች ያለ ማቋረጥ ስቃየ ስቃያታቸውን አዩ፡፡ መንገዳቸው ባሜኬላ ተሞልቶት ተሰቃዩ፡፡ ለይላም ወደ መጅኑን ዘንድ ስትሄድ እስከዛሬ የመጡበትን መንገድ ወደ ኋላ ተጉዛ እያስተነተነች አሰበቻቸው፡፡ ከራሷ ጋር እየተማገተች የነጅድን ግርግር እያተረማመሰች ወደ መጅኑን መንገዷን ቀጥላለች፡፡

በውስጧም "ይህን ሁሉ ስቃይ በቃ ብዬ ላስቆመው ይገባል"፡፡ ስትል አሰበች፡፡ መልሳ ደግሞ "ግን ምን አልባት እጣፋንታችን ይህን ከሆነ የፃፈልን የኔ የበቃ ቃል ላጲፅ ሆኖ የእጣፋንታችንን መዝገብ ማጥፋት ይቻለዋልን? ግን ይሄው አሁንስ የልቤ ሰው እየጠፋ አይደል፡፡ እኔስ  በህይወት አለሁ?  እሱ በኔ ምክነያት ከፊቴ ከሞት ጋር ስንት ጊዜ ግብ ግብ ውስጥ ገብቷል? እኔስ ስንት ጊዜ እየተነሳሁ እሞታለሁ? አንድ ቀን በኔ ምክኒያት የምር የሆነችን ያቺን የመጨረሻ ትንፋሹን ቢስባትስ? ያኔስ ምን አይነት ሞትን ልሞት ነው"? እያለች ከራሷ ጋር ስትማገት ከነመጅኑን ቤት ደረሰች፡፡


ልቀቀኝ አሊ፡፡ እጅህን አንሳልኝ ካሁን በኋላ ምን እስከሚያደርጉ ነው የምጠብቀው፡፡ አታይም እንዴ እስከወዲያኛው ለይላዬን ቀምተው ሊቀብሩኝ ነው፡፡ እናንተም ለነሱ አብራችሁ ጉድጓዴን እየቆፈራችሁ ነው፡፡ ልቀቁኝ!!... እያለ መጅኑንን ተረባርበው ከያዙት ክንዶች ለማምለጥ ይጋጋጣል፡፡ እናቱ ዝም በሉት እንዳትለቁት፡፡

ወደ ሞቱ ለመሄድ ነው የሚለምናችሁ አሊ እንዳትለቀው ይገድሉብኛል፡፡ እያለች ታለቅሳለች፡፡ ከለይላ ተስፋ እንዲቆርጥ የለይላን መታጨት ባረዳችው ጊዜ እየሰከረ ወደ ለይላ ቤት ሲሄድ ለጓደኞቹ ነግራ አሊ እና ሌሎች ጓደኞቹ ተረባርበው አስቀርተውታል፡፡ አሊም እጁን የፊጥኝ አስሮ በቅፉ ጭምቅ አድርጎ ይዞታል፡፡ ሌሎቹ ጭኑን እና ባቱን ተጭነው የሚወራጭ እግሩን ጥፍንግ አድርው ቢይዙትም ስለ ለይላ ሲሆን እንደ ጣውላ የተፋቀ ሰውነቱ ለብዙ ጎበዞች አስቸግሮ አቃቅቷቸዋል፡፡ ወዲህም ያለ መታከት ልቀቁኝ እያለ ይጮሀል፡፡ እኮ ምን ልትሆን? ሂድ ሙት ብዬ ነው የምለቅህ? ይልቁንስ ላለቅህ ነገር እራስህን አታድክም፡፡ እያለ አሊ አብሮት ይጮሀል፡፡

በመጨረሻ መጅኑንም ሲታክተው ሲቃ እያነቀው የግጥም ሙሾውን ማውረድ ጀመረ ....

"ኸሊለየ ማአርጁ ሚነል አይሺ
በእደ ማ አራ ሀጀቲ ቱሽራ
ወላ ቱሽተራ ሊያ ፈቀዷሀ ሊገይሪ
ወብተላኒ ቢሁቢሀ ፈሀላ
ቢሸይኢን ገይሪ ለይላ ኢብተላኒያ"።

« አንተ ጓደኛዬ ሆይ የኔ ህይወት ካሁን በኀላ ምን ዋጋ አለው? ህይወቴን አልፈልገውም፡፡ ምክኒያቱም የኔ ፍላጎት እየተሸጠ ነው፡፡ እኔ ደግሞ ፍላጎቴን ማሟላት አልችልም፡፡ ለይላን ለሌላ ሰው ሊድሯት ነው?


ይቀጥላል…

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

23 Oct, 17:02


እማ ዋሽተሽኛል 😭

የኑሮ ሁኔታ ከአቅምሽ በላይ ሆኖ
ህመሙ ጭንቀቱ ሲፀናብሽ ገኖ
በተሰበረ ልብ ካይንሽ ዕንባ ሲፈስ
ማይጠገብ ፊትሽ በሀዘን ሲደፈርስ
     
   ምን ሆነሽ ነው ብዬ ያኔ ስጠይቅሽ
   ጽጉሬን እየዳበሽ እንዲ ነበር መልስሽ

   ፊቴን ታጥቤ ነው ለምን አለቅሳለው
   አንተ ካለህልኝ ሁል ጊዜ ስቃለው
 
   ብለሽ ዋሽተሺኛል እኔ እንዳልከፋ
   እንደዛ በለቅሶ አይንሽ እየጠፋ

ውስጥሽ የተጎዳ ክፉኛ እያመመሽ
ደናነኝ አታስብ እርሳው ትዪኛለሽ

ግን ልጅነት ሆኖ አምንሻለው ቶሎ
ከእቅፍሽ ስገባ እጅሽ እንኳን ዝሎ

ደግሞም አይቻለው ከሆድሽ አጉድለሽ   
ጥራጊ ስትበዪ  እኔን ጥግብ አርገሽ
ለምንስ ዋሸሺኝ ለምንስ ደበቅሺኝ
እንደዛ እየክፋሽ ደስተኛ ነኝ አልሺኝ

እርቦሽ ሳትበይ አንጀትሽም ታጥፎ
እኔን አብልተሻል ከጥጋብም አልፎ

ከህመምሽ በላይ ሚ'ያሳስብሽ ነገር
ስለኔ ደስታ ነው ሳልከፋ እንድኖር

ባይኖርሽ እንኩዋን ከሰው ተበድረሽ
አንሼ እንዳልታይ ሁሉን ታደርጊያለሽ

በመኖር አዙሪት አንችን እስካላጣሁ
እምዬ ሁል ጊዜ ደምቄ እታያለሁ
  
               አንቺ እኮ ነሽ ወዜ

በአንቺ ፈገግታ ውስጥ እኔ እንድበራ
ስንት ጊዜ ስቀሻል ሆነሽ በመከራ
ቢከፋሽ ለብቻሽ ደብቀሽ ሸሽገሽ
እማ ዋሽተሺኛል እያነባሽ ስቀሽ

      
t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

23 Oct, 03:27


አጭር፣ መልከ ጥፉ፣ የአከባቢ ሴቶች እንደ እብድ ሚመለከቱት፣ ፍፁም የነፃ ድኃ እና ከረሱል ስር ስር ሁሌም የማይጠፋ ሰው ነው።

‹‹ጁለይቢብ ለምን አትዘወጅም›› አሉት ነቢ ምስኪኑን እና መልከ ጥፉውን ባልደረባ እየተመለከቱ።

‹‹አንቱ ያላህ መልዕክተኛ! ለኔ ማን ይድረኛል...? ብር የለኝ፣ ክብር የለኝ...›› ተስፋ በቆረጠ መንፈስ ጥያቄ አዘል መልስ መለሰላቸው።

‹‹እኔ እድርኃለሁ›› አሉት ሙሽራ ያዘጋጁ በሚመስል መልኩ።

‹‹ምንም የለኝም ኮ መናጢ›› አላቸው በተስፋ እና በአግረሞት እየተመለከታቸው።

‹‹አንተ መናጢ አይደለህም›› እያሉ ይወተውቱት ጀመር። ከእለታት በአንዱ ቀንም አንድ የተከበረ የመዲና ሰው ልጁን ለረሱል ሰዐወ ለመዳር ከጅሎ ከመገኛቸው ብቅ አለ።

‹‹ልጅህን ትድርልኛለህ?›› አሉት ነቢ ሰዐወ።
‹‹ምን ያለ ደስታ ነው ለርሶ መዳር›› አላቸው ሰውዬው እፊቱ ላይ መቋቋም የማይችለውን ደስታ እያንፀባረቀ።

‹‹ግን የማገባት እኔ አይደለሁም›› አሉት።
‹‹ታድያ ማን ነው?››አለ ግራ በመጋባት እና ተስፋ በመቁረጥ መንፈስ ዋልሎ።

‹‹ለጁለይቢብ ልድራት ፈልጌ ነው›› አሉት።

ፊቱ ተቀያየረ፤ እንደ ንግስት የሚሳሳላትን ሴት ልጁን ለአንድ መልከ ጥፉ እና መናጢ ሊድር መጠየቁን ሲረዳ በረሱል ሰዐወ ፊት ምንም አይነት እንቢታን ላለማውጣት፦‹‹ ያ ረሱለላህ! ለጁለይቢብ ሊድሯት? ቆይ እስኪ ከሚስቴ ጋር ልመካከር?›› ብሎ ወደ ቤቱ ተመለሰ።

አባት ልክ ቤቱ እንደገባ ሚስቱን ጠርቶ፦‹‹ረሱል ሰዐወ ልጃችንን እንድንድርላቸው ጠይቀውናል›› አላት በቀዘቀዘ ድምፅ።

‹‹ምን ያማረ ዜና ይዘህልኝ መጣህ! ታድያ እሳቸው ጠይቀው ማን ነው ሚከለክላቸው? ›› አለች በደስታ መንፈስ እየፈነጠዘች።

‹‹ለእራሳቸው እኮ አይደለም የጠየቁት›› አላት የደስታ ስሜቷን አጣጥማ ሳትጨርስ ቅስሟን ሊሰብር።

ጉዷን ያላወቀች እናትም ‹‹ታድያ ለማን ነው?›› አለች እሷም በቅፅበት ቀዝቅዛ።

ሰውዬውም፦‹‹ለጁለይቢብ ነው›› አላት በሀዘን እና በትካዜ ተውጦ።

‹‹ጁለይቢብ!?›› አለች እናት በስሜት ተውጣ።
‹‹ስማ እኛ ኮ ልጃችንን እገሌ...፣ እገሌ እድሜ ልካቸውን ሲለምኑን የከለከልነው ለጁለይቢብ አይነቱ ልንድር አይደለም›› አለች ስሜቷን መቆጣጠር እየተሳናት።

አባት ተጨነቀ። ለዝያ መልከ ጥፉ እና የሴቶች መሳቅያ ለሆነ ሰው ይህችን ውብ ልጁን ይዳር ወይስ የረሱልን ሰዐወ ጥያቄ ውድቅ ያድርግ!!

ልጅቱ ወሬአቸውን በሙሉ ካዳመጠች በኋላ፦‹‹ማን ነው ዳሩኝ ያላችሁ?›› ብላ መጣች ወደ ሳሎን።
‹‹ረሱል ናቸው የጠየቁት›› አለ አባት።
‹‹ታድያ ረሱል ጠይቀው ልትከለክሉ ነው'ን? እሳቸው ጠይቀው አይመልለሱም...እኔንም አልባሌ ቦታ ላይ አይጥሉኝም›› ብላ እየመረራት ለነቢ ክብር ስትል ዋጠችው።

አባት ቅስሙ ተሰብሮ ወደ መልዕክተኛው ሰዐወ ሂዶ፦‹‹ ጥያቄዎትን ተቀብለናል›› አላቸው።
ረሱልም ኒካ ካሰሩላቸው በኋላ እጃቸውን ከፍ አድርገው እንዲህ ሲሉ &#0;ዱኣ አደረጉ።

‹‹ያ አላህ! ሲሳይህን በገፍ አዝንብባቸው፤ ኑሮአቸውንም ከችግር ነፃ አድርግላቸው››

ጁለይቢብ ሙሽሪቱን ይዞ የሙሽርነትን ጣዕም ብዙም ሳያጣጥም የመልዕክተኛውን የዘመቻ ጥሪ ተቀብሎ ወደ ጦር ሜዳ ሙሽራውን ትቶ ሄደ።

ጦርነቱ ተፋፍሞ ከተጠናቀቀ በኋላማ ሰሀባዎች አስክሬን ሲሰበስቡ ረሱል ብቅ አሉ።
‹‹ማን ማን ሞተብን ?›› ሲሉም ጠየቁ።
‹‹እገሌ ሞተብን፣ እገሌን አጣነው...›› እያሉ ሰሀባዎችም ሀብታሞችን እና ዘረ-ክቡሮችን ይዘረዝሩ ጀመር።

‹‹ሌላስ ማንን አጣን...?›› ሲሉ ረሱል ሰዐወ ጠየቁ።
‹‹ያው እነዚህኑ ነው ያጣናቸው...›› ሲሉ መለሱላቸው።
ረሱልም እንባ ባቀረረ አይናቸው እያማተሩ፦‹‹እኔ ግን አንድ ወዳጅ አጣሁ፤ ጁለይቢብን አጣሁ...ኑ እስኪ አፋልጉኝ›› ብለው በሜዳው ላይ ከተበታተኑት አስክሬኖች ፍለጋ ጀመሩ።

በመጨረሻም ጁለይቢብ በደም ተላውሶ ከአሸዋው ላይ ተዘርሮ አገኙት፤ ከዙርያው 7 የጠላት ወታደሮች በሱ ተገድለው ወድቀውም ነበር።

ረሱል ሀዘን ባደከመው ስሜት አስክሬኑን እየተመለከቱ፦‹‹እኚህን ሁላ ገደልካቸው፤ በመጨረሻም ገደሉክ። እንተ ከኔ ነህ፣ እኔም ካንተ ነኝ›› እያሉ ከአስክሬኑ አጠገብ ተንበርክከው በክንዳቸው ደግፈው አነሱት።

ሰሀባዎች ቀብሩን ቁፋሮ ጀመሩ። የቀብሩ ቁፋሮ እስኪጠናቀቅ ድረስ የጁለይቢ አንገት በረሱል ሰዐወ እቅፍ ውስጥ ሁኖ ከቆየ በኋላ በመጨረሻም በስራው ሊመናዳ ከቀብሩ ተጋደመ።

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

22 Oct, 18:03


(መጅኑን ለይላ)

ክፍል ( 9)

መጅኑን ነጅድ ከተማ እንደደረሰ ዋናውን ጓዳና ተከትሎ ግራ ቀኝ ሳይል ወደ ለይላ ቤት አቀና፡፡ ቤቷ አቅራቢያ ከደጃፋቸው ፈንጠር ብሎ ካንድ የቴምር ዛፍ ስር ተቀምጦ ለይላን ፍለጋ አይኑን እያንገዋለለ ቀኑን እና ምሽቱን ጭምር ጠበቃት፡፡ ካሁን ካሁን ብትወጣ እያለ በር በር ሲመለከት ቀን ላይ አብሮት ወደ ነጅድ የመጣው ወርድ እና አብረውት የነበሩት ሰዎች ወደነለይላ ቤት ሲገቡ ተመለከተ፡፡ ነጋዴው ወርድ ቀን ስለ ለይላ እንደጠየቀው አስታውሶ አሁን ደግሞ ከለይላ ቤት መገኘቱ ምቾት ነስቶታል፡፡ መጨረሻውን አያለሁ ብሎ እዛው ካለበት ሳይነቃነቅ እንደተቀመጠ ወርድና ሽማግሌዎቹ አመሻሽተው ወጥተው ሄዱ፡፡ መጅኑንም እዛው ቁጭ ብሎ ሌሊቱ ሲጋመስ የቴምሩን ዛፍ እንደተደገፈ በዛው እንቅልፍ ይዞት ሄደ፡፡ ጠዋት ላይ ነጅድ የደረበችውን የፅልመት ጋቢ ገልጣ በፀሀይ ንጋቷን ስታበስር ለሁለት ቀን ምግብ እና ውሀ ባፉ ያልዞረው መጅኑንንም ከተኛበት መሬት እየተጠራሞተ ተነስቶ ወደ ቤተሰቦቹ ቤት አመራ፡፡

አንተ? ተመልከት ተመልከት ማን እንደሆነ አውቀኸዋል? አለው ከጎኑ የተቀመጠውን ጓደኛውን "አጂብብብ! አይ ቀይስ ያን የመሰለ ልጅ በቃ መጨረሻው እንዲህ ይሁን? ብሎ አንገቱን ወዘወዘ፡፡ እኔም የማየውን ማመን አቅቶኛል፡፡ እኔ እምልህ? አስበኸዋል ግን ጭራሽ ለይላ ልትዳር እንደሆነ ሲሰማ ምን ሊሆን እንደሚችል"? ሌላኛው ጎረምሳ ጥያቄያዊ መልሱን አስከተለ፡፡ የነጅድ ጎረምሳዎች ድሮ የሚያውቁት ሸጋ ፣ ሽቅርቅሩ ቀይስ ዛሬ ዲባዲቦ ልብስ ለብሶ ፣ ከጀርባው ኮሮጆ አንግቦ ሲንቧተት ሲያዩት ጭራሹኑም "ኧረ በፍፁም ይሄ እሱ አይደለም"! ብለው የሞገቱም አሉ፡፡ መጅኑንንም ስለሱ የሚያንሾካሹኩትን ሰዎች አልፎ ቤት ደረሰ፡፡ ወደ ውስጥ ዘልቆ ሲገባ እናቱን ከቀኤው ላይ ስትቧድድ ተመለከታት፡፡ እሷም ላፍታ ቆም ብላ ኮሮጆ ይዞ ከፊቷ የቆመውን ምስኪን ልጇን አስተዋለችው፡፡ ቀይስ አንተ ነህ? መጣህ የኔ ልጅ? አለች እንደ መከራ ድንግት መከረኛው ልጇ ዱብ ሲልባት፡፡ መጅኑን በርሀብ ብዛት መናገር ተስኖታል፡፡ እንደምንም ተሟሙቶ "እራበኝ ምግብ አለሽ? አለ በተቆራረጠ ድምፅ፡፡ እናቱ ከጀርባው የተዛመደ ሆዱን አይታ ዘጠኝ ወር የተኛበት የናት ሆዷ እየተላወሰ በእርይታ እሩጣ ከነ ምናምኑ ተጠመጠመችበት፡፡ እንደ አራስ ልጅ በጉያዋ ሽጉጥ አድርጋ ውሀ ያልጎበኘው ሰውነቱን ሞጨሞጨችው፡፡ እናቱ ነችና ሳትጠየፍ በሚቀረና ሽታው ውስጥ የልጅነት ጣፋች ጠረኑንን እየማገች በመንታ አይኖቿ እምባዋን አፈሰሰች፡፡ መጅኑን ጠኔው ጠንቶበት እየተንገዳገ በሰለለ ድምፁ ደገመና "ምግብ" አላት፡፡ ቃሉ ካንጀቷ ደርሶ ጠብ! አለ፡፡ "ኧረ አፈር በበላሁት!! የኔ አንጀት ቅጥል ይበል"!! ሀዘኗ ከውስጧ ፈንቅሎ አንፈቀፈቃት፡፡

ወድያው በቆመበት ትታው ወደ ቤት እሮጣ ገብታ ከወደ ጓዳ ተንጎዳጉዳ በሰፊ ሸክላ የግመል ወተት እና ድርብርብ የስንዴ ዳቦ ይዛ ወጣች፡፡ ውጭ ካለ የእንጨት አልጋ ላይ ሆኖ የቻለውን ከበላ በኀላ የተረፈውን በያዘው ጆንያ ውስጥ ሸክፎ ወድያው ለመሄድ ተነሳ፡፡ እናቱ ገና አይታው እንኳን ሳትጠግብ ሲነሳ ስታይ "እህ...ገና ከመምጣትህ የት ነው ምትሄደው? ቁጭ በል እንጂ?" አለች ከሱ ጋር አብራ ብድግ እያለች፡፡ አሁን ጠግቤአለሁ እናቴ፡፡ አላት የወየበ ጥርሱን ግልጥጥ አድርጎ፡፡ እሺ ከጠገብክ እዚሁ ቆይ ከዚህ ከሄድክ ደግሞ ይርብሀል፡፡ አለች እንባ እየተናነቃት፡፡ ለይላም እርባኛለችና አሁን ደግሞ ወደርሷ ዘንድ መሄድ አለብኝ ብሏት መንገዱን ቀጠለ፡፡ በሩጫ ከፊቱ ቀደም ብላ " አይ! ወደ ለይላ አትሄድም ወደ እርሷ ዘንድ ከሄድክ ይገድሉሀል" ብላ መንገድ ከለከለችው፡፡ ነግሬአችሁ የለ!...እኔ አንድ ነፍስ ነው ያለኝ፡፡ እሱን ደግሞ ለይላ ወስዳለች ማንም የሚወስደው የቀረኝ ሁለተኛ ነፍስ የለም፡፡ አለ መጅኑን፡፡ "አዎ ሙተሀል ለይላም ያንን ታውቃለች፡፡ ታዳ ማነው ሙት የሚፈልገው? ለይላ አንተን አትፈልግህም፡፡ ቤተሰቦቿም አይፈልጉህም፡፡ እኛ ግን ሁል ጊዜ እንፈልግሀለን፡፡ ተመልከት ትላንትም ዛሬም ካንተ ጋር ነን እባክህ የኔ ልጅ እዚሁ ቁጭ በል አለች" በተማፅኖ እያስተዛዘነች፡፡ አይ አይ ለይላ ትጠብቀኛለች እሷ እኔን እንጂ ማንንም አትፈልግም፡፡ አለ መጅኑንን ከጀርባው ያዘለውን ኮሮጆ አደላድሎ፡፡ አይ ልጄ! በጭራሽ እሷ አንተን አትጠብቅህም ሌላ በጉጉት የምትጠብቀው ሰው አለ፡፡ አሁን እሷ ታጭታለች፡፡ ደግሞ በቅርቡም ታገባለች አለችው ከለይላ ተስፋ ቆርጦ ከሷ ዘንድ እንዲቀርላት ሽታ፡፡

ለይላ ከአባቷ እግር ስር ተደፍታ የለቅሶ ሳግ እያነቃት ለመነችው፡፡ እባክህ አባዬ በማልችለው ነገር አታስገድደኝ፡፡ እሱ ለኔ የሚገባ ሰው አይደለም እኔም ለሱ አልገባውም፡፡ ደግሞስ ልቤ ሳይፈቅድ ቢአገባኝ ሚስት ነው ሸቀጥ የምሆንለት? እባክህ አባዬ፡፡ አባቷ ሰዕድ የለይላን የክፍል በር ተደግፎ ከግሩ ስር የተደፋችውን ልጁን በትዝብት ተመለከታት፡፡  ስሚ እርሱ እጅግ የተከበረ ሰው ነው፡፡ ከሻም እስከ መስር ፣ ከመስር እስከ ነጅድ ስሙ የናኘ ነጋዴ ነው፡፡ ወዲህም ሸበላ ነው፡፡ ቆይ እስኪ መህርሽን አስር ግመል ያደረገን ሰው አላገባም ብለሽ ታዳ ማንን ልታገቢ ነው? አንቺስ የምትገቢው ላንቺ የሚገባው ያ...መልዐክ ማነው? ህህህ ዳሩ መች አጣሁሽ!!....እድል አንጥፋ ስትለምንሽ "ረግጫት ካልሄድኩ" የምትይው ያ እብድ ጋር ኮሮጆ ተሸክመሽ ጫካ ለጫካ ለመዞር ነዉ? እእእእ? ከሱ ጋር ሴትነትሽን በእሳት እያነደድሽ ልትሞቂ ነው? ስሚ! ወደድሽም ጠላሽም ታገቢያለሽ ታገቢያለሽ! አይ "እምቢኝ ፣ አሻፈረኝ" ካልሽ ግን ደሜን እንዳፈሰስሽ ቁጠሪው፡፡ የለይላ አባት ወርድ ቢን መህዲ የወርድን የትዳር ጥያቄ ለይላ ትቀበል ዘንድ ማስፈራርቾ ያዘለ ትዕዛዙን ተናግሮ ከተነጠፈችበት የክፍሏ ወለል ላይ ጥሏት ሄደ፡፡ ምንም ማለት አቅቷት እያለቀሰች በጥፍሯ መሬቱን ስትቧጥጥ ወድያ የአባቷን እግር ተከትላ ትንሽ እህቷ እያለከለከች ወደ ክፍሏ ዘላ ገባች፡፡ "እህቴ....እህቴ ጉድሽ! መጅኑን ወዳንቺ ካልመጣሁኝ ብሎ አገር ይያዝ ብሏል፡፡ ልትታጪ እንደሆነም ሰምቷል፡፡ አሁን ጓደኛው አሊ ነው እኔን ወዳንቺ የላከኝ "አንቺን ካላገኘሽ ማንም አያቆመውም እባክሽ ቶሎ ነይ ብሎሻል"፡፡ እዚህ ቢመጣ ምን ሊፈጠር እንደሚችል ታውቂያለሽ፡፡ እና እንዴት ልታደርጊ ነው እህቴ? አለች ፊቷን በጭንቀት ጭፍግግ አድርጋ፡፡ ምን? ደግሞ ምን ጊዜ ወሬው ደረሰው? ለይላ በጭንቀቷ ላይ ሌላ ጭንቀት ሲታከልላት ደነገጠች፡፡ እኔንጃ አሁን ማንስ ቢነገረው ምን ለውጥ አለው? ይልቁንስ የሆነ መላ ዘይጂ አለች እህቷ፡፡ እኔማ እዚህ ሞቱን ደግሼ አልጠብቀውም፡፡ አዎ አውቀዋለሁ እኔ ካልሄድኩኝ እሱ ይመጣል፡፡ ምን አማራጭ አለኝ? ካለበት እሄዳለሁ ብላ ፊቷን በጥቁር ሂጃብ ሸብባ በጓሮ በር ተሾልካ ወጣች፡፡ ከዚያ……

ይቀጥላል

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

21 Oct, 04:43


ይብቃ መኮራረፍ ይወገድ ጥላቻ ከመካከላችን
ችግር እንኳን ቢገኝ በመሀከላችን ባስተሳሰባችን
ቁርአን ሐዲስ አለ አስታራቂያችን
     ሰዎች ይፋጀሉ በሆነው ባልሆነ
    ብዙ ሰው ይጠቃል ማንም ካልባነነ

መንስኤው ምንድነው የመጣላታችን???
የሚያበጣብጠን በየመሀላችን፤
ምክኒያት ሚሆነው ለመለያየታችን
      እርስ በርስ በጥላቻ እንዲህ በመናቆሩ
    ባጢል ዟሒር ሆኖ ሀቅን መሰወሩ
      እኛ ተለያይተን ወህዳ አለመኖሩ
     እስቲ ሹራ አድርጉ ምንድነው ሚስጥሩ?
     በቁርአን በሐዲስ ይፈታ ችግሩ
አምላካችሁ አሏህ አንድ ሁኑ እያለን
ከመለያየትም እያስጠነቀቀን
ኃይላችሁ ይናዳል እያለ ሲነግረን
ሰምተን እንዳልሰማን ጆሮ ዳባ አልን
         የቁርአን አያቶች ተነበውልናል
        እኛ ችላ ብለን ዘንግተናቸዋል
አማኞች ሙስሊሞች በሉ ተጠንቀቁ
ቢሀብሊሏሂ(3) ላይ ወላ ተፈረቁ(4)
አትጨቃጨቁ አትፈራረቁ
ባይሆን ዲናችሁን በሱና አድምቁ
       ምን አልባት ቢፈጠር የሀሳብ ልዩነት ያለመስማማት
     ሹራ አድርጉበት በሱና በሐዲስ በቁርአን አያት
     ምታምኑ ከሆነ በአሏህ በረሱል በቂያማ ለት!!!!
       
 

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

20 Oct, 17:47


መጅኑን ለይላ

~~ ክፍል 8

ከዛን ቀን ጀምሮም ከእግረ ሙቅ እስሩ ፈተው ለቀቁት፡፡ እሱም ነጅድን ለቆ ጫካ ገባ፡፡ ከዛን ጊዜ በኀላ በአካል አልሞ ካጣት ለይላ ጋር በመንፈስ አብሯት ኮበለለ፡፡ ከጎኑ አብራው እንዳለች ያክል ብቻውን ያወራል ፣ ፀጥጥጥ ብሎ በአርምሞ ስታወራ ያደምጣታል ፣ በቀልዷ ይስቃታል፡፡ ከነጅድ እስከ ሂጃዝ ፣ ከሂጃዝ እስቀ አቂቅ ባካለለው የጫካ ጉዞው ከሱ ጋር ሳትሰለች አብራው ትጓዛለች፡፡ በርግጥም ለሱ በእውነተኛው አለም ያጣትን ለይላ እብደቱ በፈጠረለት አለም አግኝቷታልና አሁን ለሱ አለም አስር ሞልታለታለች፡፡

……ባንዱ ጠዋት በሂጃዝ ጫካ ውስጥ የወፎቹ ዝማሬ እየተንቆረቆረ የንጋት ብስራት ያበስራል፡፡ ማታ እያነደደ ያመሸው እሳት ተዳፍኖ ጭሱ ወደ ሰማይ እየተግተለተለ ይጨሳል፡፡ መጅኑንም ዲንጋይ ተንተርሶ ከተኛበት መሬት ላይ ተነስቶ በሚጨሰው ጭስ ስር ተቀምጦ ለይላውን ፈለገ፡፡ ነገር ግን እንደሁልጊዜው ዛሬ ለይላ ከጎኑ አልነቃችም ቢጠራትም መልስ አልሰጠችውም፡፡ "ለይላ ጥላኝ ሄደች ፣ ሄደች! ለይላ ሂዳለች" እያለ ከጁ አምልጦ እንደጠፋው መርፌ ዲንጋይ ሳይቀር እየፈነቀለ ፈለጋት፡፡ ለይላ የለችም፡፡ ወዲያው ተነስቶ ለይላን ፍለጋ ወደ ትውልድ ሀገሩ ነጅድ አቀና፡፡ በመንገዱ ላይ ሌሎች ወደ ነጅድ የሚጓዙ ሰዎችን አግኝቶ ተቀላቀላቸው፡፡ ነጋዴው ወርድ እና ቤተሰቦቹ ነበሩ፡፡ ወርድ ከሀር የተጠለፈ ቄንጠኛ ቶብ#3 ለብሶ ፣ እንዲሁ ከወርቃማ ቀለም ጋር የተቀየደ ነጭ ጥምጣም ጠምጥሞ በነጭ ፈረሱ ላይ ተጀብኗል፡፡ ሌሎችም በእድሜያቸው ገፋ ያሉ ሽማግሌዎች በሻም አለባበስ ሽክ ብለው አብረውት አሉ፡፡ ወርድ ባንድ ለሊት ልቡን ወደሰረቀችው ለይላ ቤተሰቦች ዘንድ የትዳር ጥያቄ ሊጠይቅ ፣ መጅኑንም ደግሞ በመንፈስ ከጎኑ ያጣትን ለይላን ለማግኘት...ሁለቱም ላንድ አላማ ወደ አንድ ሰው ባንድ ላይ መንገዳቸውን ቀጥለዋል፡፡ ወርድ እና አብረውት ያሉት ሰዎች ዲባዲቦ ለብሶ ባንገቱ ላይ አጥንትና ምናምን ያጠለቀውን መጅኑንን ቢያናግሩትም መልስ ነፍጓቸው ወደፊት በግሩ መንገዱ ተያይዞታል፡፡ በመሀል በመሀል ብቻ ካፉ ላይ የማይጠፉ የናፍቆት ግጥሞቹን ያነበንባል፡፡ ቆይ ግን የነጅድ ነዋሪዎች "ግጥማችሁ ይጣፍጥላችሁ" ብሎ ማነው የመረቃቸው?


አለ ወርድ የመጅኑን ግጥም ሲሰማ ውቧ ገጣሚት ለይላ ታውሳው፡፡ ምን...ይህ እኮ የታወቀ ነው፡፡ ሁሉም የነጅድ ነዋሪዎች ብዕራቸው የሰላ ነው፡፡ አለ ከወርድ ጋር ያለ አንድ ሽማግሌ፡፡ እእእ ያኔ...ነብያችን (ሰ.ዐ.ወ) በበረካ ምፅዋታቸው ጊዜ ነጅድ እንኳን የርሳቸውን ምርቃት አላገኘችም ነበር ግና ቡራኬ ያለበት የቀለም ቅምጫና ይሄው ወደነሱ ነው የፈሰሰው፡፡ አለ ከወርድ ጋር ያለው ሌላኛው ሽማግሌ፡፡ ቀጥሎም.. ያኔ ደጋግመው ሶስት ጊዜ አላህ ሆይ ሻምን ባርካት ፣ ሀበሻን ባርካት እያሉ ሀገራትን ሲመርቁ የነጅድ ነዋሪዎች "ምነው አንቱ የአላህ መልክተኛ ነጅድን እረሳችኀት"? ብለው ከፍቷቸውም ነበር፡፡ መልዕክተኛውም አይ ነጅድን የዘለልኳት ከነጅድ የመሬት ብቃይ የሸይጧን ቀንድ ይወጣባታል ብለው መለሱላቸው፡፡ እንደምታዩት እስካሁን ግን እብዱም ሳይቀር  ባለ ስል ብዕረኛ ነው፡፡ ምን አልባት ካሁን በኀላ ይሆናል የተተነበየለት ያ የሸይጧን ቀንድ የሚበቅለው ሲል በነጅዶች አንጓጠጠ፡፡ "ሀሀሀሀሀ" ሁሉም ባንድነት ሳቁ፡፡

እንዲህ እንዲህ እያሉ ከነጅድ ከተማ ደርሰው ሊለያዩ ሲሉ...ማነህ የማትናገረው እብዱ ገጣሚ? እስኪ አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ፡፡ ጥያቄውን ከመለስክልኝ 10 ዲርሀም እሰጥሀለሁ አለ ወርድ ከፈረሱ ላይ ቁልቁል መጅኑንን እየተመለከተ፡፡ መጅኑን አሁንም ዝም እንዳለ ነው፡፡ ወርድም ከሱ መልስ ሳይጠብቅ እእእ መቼም የነጅድ ነዋሪ ከሆንክ የነጅድ ኮከብ የሆነችው ለይላን ታውቃታለህ አይደደል? ሲል ጥያቄውን አስከተለ፡፡ የለይላን ስም ሲሰማ መጅኑን የተለጎመው አፉን ፈታ፡፡ መላ እሱነቱን የሚዘውረውን የለይላን ስም በሰማበት ቅፅበት ከሰጠመበት የአርምሞ ባህር ተርገፍግፎ ወጥቶ ለማውራት ተስገበገበ፡፡ አዎ ለይላ... ለይላን አውቃታለሁ ለይላን ከማንም በላይ አውቃታለሁ አለ መጅኑን እየደጋገመ፡፡ እሺ ጥሩ! እሷን ካወቅካት ታድያ መኖሪያዋንስ አታውቅምን? አለ ወርድ ፊቱ ፈገግ እያለ፡፡ እሱማ እንዴት ይጠፋኛል! የለይላ መኖሪያማ ከኔ ልብ ላይ ነው!! ለይላ ልቤ ላይ ነው ጎጆዋን የቀለሰችው አለ ቀኝ እጁን ከግራ ደረቱ ላይ አስቀምጦ፡፡ ከወርድ ጋር የመጡት ሽማግሌዎች በመጅኑን መልስ እየሳቁ ድሮስ አንተ ከእብድን ጋር ቁም ነገር ማውራትህ! እያሉ በወርድ እያሾፉ ሌላ የሚጠቁማቸውን ሰው ፍለጋ መጅኑንን ጥለውት ሄዱ፡፡

አዎ በርግጥም ባፍቃሪዎች ዘንድ ለተፈቃሪያኖች ቦታ ከልብ የተሻለ የለም፡፡ አፍቃሪዎችም ላፈቀሩት ጥሩውን ሁሉ ይመኛሉ፡፡ ለዛም ነው በልባቸው ሰፊ እርስት ፣ ምቹ ቦታ የሚሰጡት፡፡

ይቀጥላል…

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

20 Oct, 04:21


የኢንተርኔት ዘመን ፈተናው ብዙ ነው። ሳትፈልግ የማትፈልገውን ሆነህ ራስህን ታገኛለህ። በዚህ አማላይ የሶሻል ሚዲያ ዘመን ሊተዋወቅህ የሚፈልግህ ሰው ሁሉ ንፁህ ልብ ይዞ የሚቀርብ እንዳይመስልህ፡፡
እርግጥ ነው ካንተ ሊያተርፍ የሚቀርብህ እንዳለ ሁሉ፤ እንደ እባብ ባንተ ላይ ተጠምጥሞ ሊጥልህ የሚቀርብህም አለ፡፡

አንዳንዱ ሰው የሚቀርብህ ዋናው ሸይጧን፤ አሊያም ደግሞ የሰው ሸይጧንም ልኮት ይሆናል፡፡ ያንን ሰው መጣል አልቻልኩም ጣልልኝ ብሎት፡፡

እና አንዳንዴ ሳታውቅ የዚህ ዓይነት ተልዕኮ ባለው ሰው እጅ ላይ ልትወድቅ ትችላለህ፡፡  ሳይፈልግህ የፈለገህ፤ ሳይወድህ የወደደህ የሚመስል ሰላይ ይመጣብሃል፡፡ በጊዜ ሂደት ሆነብሎ እታች እንድትሆን ያደርግሃል፡፡ ከዚያ ዉስጥህ መሸርሸሩን ሲያውቅ ድንገት ከአጠገብህ ዘወር ይላል፡፡  ወደማትፈልገው መንገድ በስንት ውትወታ ከመራህ በኋላ መሀል መንገድ ላይ ትቶህ ይሄዳል፡፡ ከዚያ እህእ ስትለው መልሶ እንደማያውቅህ ሰው እህእ ምን ላርግልህ ይላል፡፡

እንዲህ የወደቁ ብዙ ናቸው።
ነቃ በል ነግሬሃለሁ፡፡ ሱንና የለበሰ ሁሉ ዲነኛ መስሎህ እንዳትበላ፡፡ ከሚያምሩ ኒቃቦችና ፂሞች ጀርባ ስንት ጉድ አለ መሰለህ፡፡ ከሱናና ዋጂቡ መገለጫ ባሻገር አሻግረህ ተመልከት፡፡ አቀራረብህን ቆጥብ፣ አታችመንትህን ቀንስ፡፡
ብዙ የዋህነት ይጎዳሃል፡፡ ጥቂት የዋህነትን ያዝና ብዙ ጥንቃቄን ምረጥ፡፡ ሰው ሁሉ የከተማ ሰው በሆነበት ዘመን የገጠር ልጅ አትሁን፡፡ በፍየል ዘመን በግ ከመሆን ተጠንቀቅ፡፡  ከወደቅክ በኋላ ሰው ስላንተ ምንም ጉዳይ የለውም ስልህ፡፡
አንተ ትልቁ ሰውዬ ብትወድቅ የዛሬ ሰው ምንም ዑዝር አይሰጥህም፡፡ በመጨረሻም ሊል የሚችለው ግዙፉ ዋርካ ወደቀ! ትልቁ ዳቦ ሊጥ ሆነ! ነው፡፡

ወዳጄ … የአንዳንድ ሰው ሴራው ከሸይጧንም በላይ ሆኗል፡፡ በገዛ እጁ ገዝግዞ ጥሎህ አያዝንልህም፡፡ ትንሽ ፈቅ ብሎ ቆሞ ይስቅብሃል፡፡ ጉድ ሠራሁት ይላል፡፡ ደግሞ የሴት ተንኮል መብዛቱ የወንዱም እንደዚያው ።

t.me/islamawigetem

ኢስላማዊ ግጥሞች الشعر الإسلامي لسيد أبو ذر

18 Oct, 16:18


መጅኑን ለይላ

~ ~ ክፍል   7

……ለይላ "ዋዋዋዋይይይይይ" ብላ እንደ መብረቅ ጩሀ ከእንቅልፏ ነቃች፡፡ ስትነቃ መላ አካላቷን የጭንቀት ላብ አጥምቋት እንደ ዶሮ እየተርገፈገፈች ነበር፡፡ በድንጋጤ የሚደልቀው ልቧም ደረቷን ቀዶ ሊወጣ ደርሷል፡፡ ተረባብሻ ከአልጋዋ ላይ ቁጭ እንዳለች እየተዟዟረች ክፍሏን ቃኘች፡፡ ማንንም ሰው አጣች፡፡ መጅኑንንም ሆነ አባቷ የሉም፡፡ ሁሉም ምስል ቅዠት እንደሆነ ሲገባት የደስታ እና የምሬት እንባዋ በጉንጮቿ ላይ ዱብ ዱብ እያሉ ባንገቷ ቁልቁል ፈሰሱ፡፡ በእውኗ ብቻ ሳይሆን በህልሟም የሚያመሳቅላትን የፍቅር እጣፋንታዋን አምርራ እረገመችው፡፡ ብዙም ሳይቆዩ የሷን ጩኸት የሰሙት ቤተሰቦቿም ተግተልትለው መጥተው በጥያቄ አዋከቧት፡፡ አባቷ ሰዕድ በህልሟ መጅኑንን ሲወጋበት ያየችውን ሰይፍ ይዞ ነበር የመጣው፡፡ በዕውኗም ሰይፉን ከእጁ ላይ ስታይ ስትቃዥ እንደጮኸችው እየጮኸች አንተ ጨካኝ አረመኔ ነህ! ፣ አንተ ገዳይ ነህ! እያለች አባቷ ላይ እንደ እብድ ዘላ ተከመረችበት፡፡ በድንገት እብደቷ ሁሉም ግራ ተጋብተው ተረባርበው ያዟት፡፡ "ዲመሽቅ የሆነ አንዳች ነገር ነክቷታል ፣ አብዳለች" ብለው የዘምዘም ውሀ እየጋቱ ቁርዐን ሲቀሩባት አደሩ ተከታታይ ሳምንታትንም እንደ እብድ እየተጠነቀቋት በዘምዘም ውሀ እና በቀሪና#1 ቂርዐት ሲያጣድፏት ከረሙ፡፡
___

የሙለወህ ዘመደ አዝማዶች በመጅኑን ዙ
ሪያ ተቀምጠዋ እናቱ ብቻ ከቤት ፣ ከደጅ እያለች ለመጅኑን ቁስል ማጠቢያ የሚውል ውሀ ለማሞቅ ደፋ ቀና ትላለች፡፡ ወዲህም ታለቅሳለች፡፡ ፡ አባቱ ሙለዋህ እኽኽኽ ብሎ ጉሮሮውን ጠራርጎ መጅኑንን መምከር ጀመረ... የኔ ልጅ እባክህን ከቀልብህ ሁነህ አዳምጠን፡፡ ካሁን በኀላ የለይላ ነገር የማይሆን ነገር ሆኗል፡፡ አንተም የማይሆን ነገር እንዲሆን ስትጠብቅ እንዳይሆኑ ሆነህ ይሄው ከሰውነት ተራ ወጣህ፡፡ እኛም ካሁን ፣ ካሁን ምን ሆነ? እያልን በስጋት አለቅን፡፡ ቆይ እንደው ለኛስ አታዝንልንም? እባክህ የኔ ልጅ ተውበት አድርግና ወደ አላህ ተመለስ ብሎ እያስተዛዘነ ያባታዊ ምክሩን ለገሰ፡፡ መጅኑን ባፉ እና ባፍንጫው ደሙን እያዘራ በግረ ሙቅ ታስሮ ቁጭ ብሏል፡፡ አሊ ዲመሽቅ ሄዶ ፈልጎ እንዳመጣው ማግስቱን በጠራራ ፀሀይ ከለይላ ቤት ሂዶ በሰዕድ ጠባቂዎች ተደብድቦ እዚህም እዚያም ሰውነቱ ቆሳስሏል፡፡ እንደውም ጠባቂዎቹ ደብድበው በሰይፍ ሊጨርሱት ሲሉ በመጨረሻ አጎቱ ሰዕድ አይኑ እያየ የወንድሙ ልጅ ሲሞት አላስችል ብሎት ነው ለቆ ወደ ቤት የላከው፡፡ መጅኑን ከበር ላይ በጠባቂዎቹ ሲወገር ለይላ በህልሟ ያየችው አሟሟቱ በገሀድ ሊፈፀም መስሏት ነፍሷ ባፏ ሹልክ ልትል ደርሳ ነበር፡፡

መጅኑን በዙሪያው ተቀምጠው ከሚመክሩት ዘመዶቹ ፊት ዝም ብሎ አይኑን እያቁለጨለጨ ምንም መልስ አይመልስም፡፡ አባቱ ዝም ሲል ሌላኛው አጎቱ መጅኑንን በለይላ የሞተ ልቡን በነጅድ ቆነጃጅቶች ሊያታልለው አስቦ ማግባባቱን ቀጠለ...ቀይስ ልጄ ሆይ? አለም እኮ ሰፊ ነች! ለይላ ላይ የቀሰርከውን አይንህን እስኪ ለአፍታ አንሳና እነ ኢልሀም እና ሠውደትን ተመልከት፡፡ አይ ካልክም ደግሞ የነጅድ ቆነጃጅቶች እንደ በረሀ አሸዋ የበዙ ናቸው ከነሱ መሀል ውብ የሆነች ፣ ላንተ የምትገባውን እንስት እንዳርህ፡፡ ባገሩ ሴት እንደሌለ ነገር ለይላ ለይላ እያልክ ትሞታለህ እንዴ? ቆይ ልክ አይደለሁ እንዴ  ሰዎች? አለ ወደ ሰዎቹ ዙሮ  አዎንታቸውን እየጠየቀ፡፡ ሰዎቹም "በርግጥም እንጂ! እንደ አሸዋ ተዘግነው ማያልቁ ኹረል አይን#2 የመሳሰሉ ቆነጃጅቶች ሞልተዋሉ፡፡ በርግጥም አሉ እንጂ"! እያሉ መጅኑንን ለማግባባት አጃኮሙ፡፡ ቀጥለውም እንትና ብትሆንስ? ወይስ እገሊት ትሻላለች? እያሉ ማማረጥ ሲጀምሩ መጅኑንም በድብደባ የበለዘ አይኑን ጨፍኖ ውስጣዊው የግጥም ሰንዱቁን ከፍቶ እንዲህ ሲል አነበነበ.....
:
ወለም ዩንሲኒ ኢፍቲቃሩን ወላ ጊና
ወላ ተውበቱን ሀታ ኢህተዶንቱ ሲዋሪያ
ወላ ኒስወቱን ሶበግነ ከበድዐ ጀልአዳ
ሊቱሽቢሀ ለይላ ሱመ አረድነሃ ሊያ

፦ እኔ መቼም ቢሆን ለይላን ከልቤ ላይ ልፍቃት አልችልም፡፡ ምን እንኳን ደህይቼ ብመናኝ ፣ አልያም በነዋይ ብናኝ መቼም ከሷ ፍቅር ልቶብት አልችልም፡፡ ከሷ ፍቅር ... እንኳን ንሰሀ ልገባ ቀርቶ እንደውም ወደርሷ የፍቅር ምንፍስና የሚያደርሰኝን የቤቷን ምሶሶ ሳይቀር እስመዋለሁ፡፡ ምክነያቱም ባንድ ወቅት እሷ ነክታዋለችና ፣ እርሷን ያስታውሰኛልና፡፡ እንዲሁም የፈለገ ውብ ቀዘባዎች ተኳኩለው ተሽቀርቅረው ቢመጡም ፣ ምንም ያክል አቆንጅተው ለይላን አስመስለው ቢያመጡልኝ እንኳን ለይላን ሊያስረሱኝ አይቻላቸውም፡፡ እንዳልረሳት ሁና ከልቤ ላይ ተፅፋለች፡፡ ሲል ጥልቅ የሆነ መውደዱን በግጥም ገለጠ፡፡ የመጅኑንን በአንክሮ የተነዘዘ የፍቅር ኑዛዜ የሰሙት ቤተሰቦቹም የይረሳታል ወሽመጣቸው ተቆረጠ፡፡ ህመሙን የወደደ ልጃቸውን ከአዘኔታ ውጪ ምንም ሊያደርጉለት እንደማይቻላቸው አወቁ፡፡

ከዚያን ቀን ጀምሮ………

ይቀጥላል

t.me/islamawigetem