EBS TV @etv_newss Channel on Telegram

EBS TV

@etv_newss


worldwide news🌍

EBS TV (English)

Welcome to EBS TV, your go-to channel for worldwide news updates! Follow us on Telegram at @etv_newss to stay informed about the latest happenings around the globe. From breaking news to in-depth analysis, we cover a wide range of topics to keep you up-to-date with current events. Whether you're interested in politics, entertainment, sports, or technology, our channel has something for everyone. Join our community of news enthusiasts and never miss a beat. Stay connected with EBS TV on Telegram for real-time updates and exclusive content. Who is EBS TV? We are a reliable source of news, providing accurate and timely information to our audience. What is EBS TV? We are a Telegram channel dedicated to delivering worldwide news straight to your device. Join us today and be part of the conversation. Don't miss out on the latest headlines and trending stories - follow EBS TV on Telegram now!

EBS TV

12 Feb, 11:33


#እንድታውቁት

የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እና ተያያዥ ስብሰባዎች እስከሚጠናቀቁ ድረስ በአዲስ አበባ ከተማ ሞተር ብስክሌት ማሽከርከር ክልክል መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

የመሪዎች ጉባኤ እስከሚጠናቅ ድረስ ባሉ ቀናቶች ውስጥ በየትኛውም የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ሞተር ብስክሌት ማሽከርከር ፍፁም ክልክል መሆኑን ነው ፖሊስ አሳስቧል።

ትእዛዝ በመተላለፍ ሲንቀሳቀሱ በሚገኙ የሞተር አሽከርካሪዎች ላይ ሆነ ባለ ንብረቶች ላይ እርምጃ እንዳሚወሰድ አስገንዝቧል።

@tikvahethiopia

EBS TV

12 Feb, 11:33


#Update

" እያጠፋን በነበርንበት ወቅት የኤሊና እባብ ዝርያዎች ተቃጥለው አግኝተናል። ከ350 እስከ 400 ሄክታር ሳራማ ቦታ ተቃጥሏል ብለን እንገምታለን " - ፓርኩ

በሃላይደጌ አሰቦት እጩ ብሔራዊ ፓርክ ተከስቶ የቆየውና ለቀናት ከቁጥጥር ውጪ ለማድረግ አስቸግሮ የነበረው ቃጠሎ በቁጥጥር ስር መዋሉን ፓርኩና የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ባለስልጣን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።

ይህን ተከትሎም ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ በአደጋው የደረሰው የጉዳት መጠን ምን ያክል እንደሆነ የጠየቀ ሲሆን፣ እንስሳት መቃጠላቸውንና ከ350 እስከ 400 ሄክታር የሚገመት ሳራማ ቦታ መቃጠሉን ሰምቷል። 

የፓርኩ ኃላፊ አቶ አሕመድ እንድሪስ ምን አሉ ? 

" የካቲት 1/2017 ዓ/ም መንስኤው ባልታወቀ ምክንያት የእሳት ቃጠሎ ተነስቶ ነበር። ትላንት 10 ሰዓት በቁጥጥር ስር ተደርጓል። ዛሬም ከጠዋቱ 11 ሰዓት ጀምረን ጫካ ነበርን ሙሉ በመሉ መጥፋቱን አረጋግጠናል።

ተራማጅ የሆኑና መሮጥ የሚችሉ የዱር እንስሳት ብዙዎቹ አምልጠዋል። ግን መራመድ የማይችሉ፣ አዲስ የተወለዱ የዱር እንስሳት ጉዳት ሊያደርስ ችሏል።

እያጠፋን በነበርንበት ወቅት የኤሊና እባብ ዝርያዎች ተቃጥለው አግኝተናል። ግን የጉዳቱን መጠን ሰርቨይ መሰራት አለበት "  ብለዋል።

የፓርኩ ምን ያክል ክፍል እንደተቃጠለ ታውቋል? ለሚለው ጥያቄ በሰጡን ምላሽ፣ " መለካት ያስፈልጋል። ከ350 እስከ 400 ሄክታር ሳራማ ቦታ ተቃጥሏል ብለን እንገምታለን "  የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

" ደረቃማ ሳር ስላለ በትንሹ ነው የሚቀጣጠለውና በሰው ኃይል ለመቆጣጠር አስቸጋሪ አድርጎት፣ በሰው ኃይል ከመቆጣጠር በላይ ሆኖ ነው በግሬደርና፣ ከእሳቱ ርቆ በሎደር የማስራብ ሥራ የተሰራው” ሲሉ አስታውሰዋል።

ፖርኩ ወደ 244 የአእዋፍ ዝርያዎች፣ 42 አጥቢዎችና ሌሎች እንስሳት እንዳሉበት አስረድተው፣ “የተመሰረተው በኬንያና በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኘውን ትልቁ የሜዳ አህያ ለመጠበቅ ነው” ብለዋል።

ኮቪድ ከመከሰቱ በፊት እስከ 200 ሺሕ፣ ኮቪድ ተከስቶ ከቆዬ በኋላ የቱሪስት ቁጥር በመቀነሱ ከ50 ሺሕ እስከ 100 ሺሕ ገቢ የሚገኝበት እጩ ፓርክ መሆኑ ተነግሯል።

ፓርኩ ከአዲስ አበባ በ27ዐ ርቀት ላይ ያለ፣ ኤሪያው 1099 ስኩየር ኪሎሜትር የሆነ፣ ወይራ፣ የሀበሻ ጽድ፣ ዝንባ የመሳሰሉ እፅዋቶች ያሉበት፣ 40 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሜዳ ላይ ያረፈ ሳር ያለበት ነውም ተብሏል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

EBS TV

12 Feb, 07:14


#Update

" እሳቱ በቁጥጥር ስር ውሏል " - የኢትዮጵያ የዱር እንሰሳት ጥበቃ ባለስልጣን 

በሃላይደጌ አሰቦት ዕጩ ብሔራዊ ፓርክ ተከስቶ የነበረው የእሳት ቃጠሎ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ በቁጥጥር ስር እንደዋ ለየኢትዮጵያ የዱር እንሰሳት ጥበቃ ባለስልጣን አሳውቋል።

ላለፉት ሶስት ቀናት በብሔራዊ ፓርኩ ውስጥ ተከስቶ ነበረው የእሳት ቃጠሎ ለመቆጣጠር የኢትዮጵያ የዱር እንሰሳት ጥበቃ ባለስልጣን መ/ ቤቱ  የሃላይደጌ እና የአዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ሠራተኞች፣ የገቢ ራሱ ዞን እና አሚባራ ወረዳ ነዋሪዎችና አመራሮች እንዲሁም የሃላይደጌና አንዲዶ ቀበሌ ነዋሪዎች ርብርብ ማድረጋቸው ተገልጿል።

" እሳቱን ለማጥፋት በተደረገው ርብርብ ትናንት ከሰዓት ጀምሮ በፓርኩ ላይ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ መቆጣጠር ተችሏል " ሲል ባለስልጣን መ/ቤቱ አሳውቋል።

@tikvahethiopia

EBS TV

11 Feb, 20:07


#እንድታውቁት

አዲስ አበባ በሚከናወነው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እና ሌሎች ተያያዥ ስብሰባዎች ምክንያት ከነገ ማለትም ረቡዕ የካቲት 5/ 2017 ዓ.ም ረፋዱ 4፡00 ጀምሮ እስከ መጪው ሰኞ ማለትም የካቲት 10/2017 ዓ.ም ድረስ :-

1. አረቄ ፋብሪካ አጠገብ የነበረው ተርሚናል ወደ ዲያፍሪክ ሆቴል አካባቢ ፤

2. ዋቢ ሸበሌ ሆቴል አጠገብ የነበረው ተርሚናል ወደ ለገሐር ተርሚናል፤

3. በተለምዶ ጠማማ ፎቅ የሚባለው አካባቢ የነበረው ተርሚናል ወደ ሳር ቤት ድልድይ ስር መዘዋወራቸውን እና ስብሰባዎቹ እንደተጠናቀቁ ወደ ቀድሞ ቦታዎቻቸው እንደሚመለዱ የከተማው አስታዳደር አሳውቋል።

@tikvahethiopia

EBS TV

11 Feb, 19:35


" በአደጋው ሁለት ሰዎች ወዲያዉኑ ሲሞቱ ስራ ላይ የነበረ አንድ ተረኛ የፖሊስ አባልን ጨምሮ በሶሰት ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሷል" - የወላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ

ትላንት ምሽት 4 ሰዓት ገደማ መነሻዉን ሻሸመኔ ያደረገ ኮድ (3)  - B311533 AA የሆነ አይሱዙ የጭነት መኪና ሶዶ ከተማ ሲደርስ ባደረሰዉ የትራፊክ አደጋ  በሰዉ ሕይወትና በንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱን የወላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ም/ኮማንደር ሀብታሙ አሰፋ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

እንደ ፖሊስ አዛዡ ገለፃ ከኦሮሚያ ክልል አርሲ አከባቢ የግብርና ምርት / ሙሉ ቲማቲም / ጭኖ የነበረዉ ተሽከርካሪ ሶዶ ከተማ ' ሲዳር ቄራ ' በሚባለዉ አከባቢ በከተማዉ በሞተር ሳይክል ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ሁለት ሰዎችን ገጭቶ ወዲያዉ ሕይወታቸዉ አልፏል።

በተመሳሳይ መልኩ የምሽት ተረኛ የነበረ አንድ የፖሊስ መርማሪም ጥሪ ተደርጎለት በሞተር ሳይክል ጥሪ ወደተደረገለት ስፍራ ሲንቀሳቀስ ይሄዉ ተሽከርካሪ ገጭቶት ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰበት የፖሊስ አዛዡ ገልጸዋል።

አደጋ አድራሹ ተሽከሪካሪ አራት የመብራት ፖሎችን ከገጨ በኋላ ዲች ዉስጥ ገብቶ የቆመ ሲሆን በአሽከርካሪዉና ረዳቱ ላይ ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።

ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰበት የፖሊስ መርማሪ በሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገለት ሲሆን ቀላል ጉዳት የደረሰባቸዉ ሹፌሩና ረዳቱም በኦቶና አጠቃላይ ሆስፒታል በሕክምና ላይ መሆናቸዉን የከተማው ፖሊስ አዛዥ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

አጠቃላይ በአደጋዉ 2 የሞት፣ 1 ከባድና 2 ቀላል የአካል ጉዳት እንዲሁም 7 የንብረት ጉዳት መድረሱን አሳውቀዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia

EBS TV

11 Feb, 19:35


#ExitExam

🔴" የተፈተነው ፈተና ኮንተንቱ(ይዘቱ) ህክምና ያልሆነ ነው በትምህርት ሊገኝ የማይችል ነው " - ተፈታኝ ተማሪዎች

🔵" የተማሩት ነው የሚወጣው የተፈተኑትም ይህን መሰረት አድርጎ ነው " - ትምህርት ሚኒስቴር

ሃገር አቀፍ የመውጫ ፈተና (Exit Exam)  ከጥር 26-30/2017 ዓም በ 87 የፈተና ማዕከላት መሰጠቱ ይታወሳል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ፈተናው ከተጠናቀቀ በኋላ " ፈተናው ለፈተና ዝግጅት ከሚያግዘው ' ብሉፕሪንት ' ውጪ ነው ይዘቱም ከተማርነው ትምህርት ጋር የማይገናኝ ነው " የሚሉ ቅሬታዎችን ከተፈታኞች ተቀብሏል።

ከተለያየ የትምህርት ክፍል ፈተናውን የወሰዱ ተፈታኞች ፈተናውን ከብሉ ፕሪንት ውጪ የመጣ መሆኑን በመግለጽ ትምህርት ሚኒስቴር ምላሽ ይስጠን ብለዋል።

ቅሬታውን ካቀረቡ ተፈኞች መካከል የሆኑ የህክምና ተማሪዎች " የመጣው ፈተና በጣም ከስታንዳርዱ የወጣ የህክምና ተማሪዎችን የማይመጥን ነበር " ብለዋል።

አክለውም " የተፈተነው ፈተና ኮንተንቱ (ይዘቱ) ህክምና ያልሆነ ነው በትምህርትም ሊገኝ የማይችል ነው " ያሉ ሲሆን " የሚመለከተውን አካል ለማናገር ብንሞክርም ከውጤት በፊት ንግግር እንደማይኖር ተነግሮናል " ሲሉ ገልጸዋል።

" ከእኛ በፊት አምና የተመረቁ ተማሪዎች የተፈተኑትን ፈተና ተመልክተናል ሰርተንም ስለገባን እናውቀዋለን ትክክለኛ ፈተና ነበር የተፈተኑት ይዘቶቹም ጥሩ ነበሩ  ዘንድሮ ምን እንደተፈጠረ አናውቅም የወጣው ፈተና ከህክምና ጋር የማይገናኝ ጥያቄ ይበዛው ነበር " ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

በተጨማሪ ከጤና ተማሪዎች ውጭ የፊዚክስ ተማሪዎች ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

የትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር ) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ከብሉ ፕሪንት ውጪ ተፈትነናል የሚለው ቅሬታ " ውሸት ነው " ብለዋል።

" ከስልጠና ፕሮግራም ብቃት (Competency) ውጪ የሚዘጋጅ አንድም ጥያቄ የለም " ያሉት ስራ አስፈጻሚው የተባለው ቅሬታ " ውሸት ነው ሪፖርትም አልቀረበልንም እንደዚህ ብሎ የጠየቀንም የለም ከኮምፒተንሲ ውጭ የሚወጣ ፈተና የለም " ነው ያሉት።

አክለውም "ፈተናው ከብቃት ጋር የተገናኘ ከሁለተኛ ዓመት እስከ መጨረሻ ዓመት የተማሩት ነው የሚወጣው የተፈተኑትም ይህን መሰረት አድርጎ ነው " ብለዋል።

" ጥያቄው ከዚህ ውጪ ወጣ የሚል ቅሬታ ከሱፐር ቫይዘር፣ ፈታኝ ፣ተማሪ እንዲሁም ዩኒቨርሲቲዎች የቀረበልን አንድም ሪፖርት የለም መረጃው የለንም ሪፖርቱም አልቀረበልንም " ሲሉ ገልጸዋል።

በሌላ በኩል ሃገር አቀፉ የመውጫ ፈተና ውጤት ነገ አልያም ከነገ በስቲያ ይፋ እንደሚደረግ ከትምህርት ሚኒስቴር መስማቱን የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪዎች ህብረት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል፡፡

ህብረቱ ፥ ሚኒስቴሩ ከComprehensive Nursing የመውጫ ፈተና ጋር ተያይዞ የቀረበ ቅሬታን እያጣራ እንደሚገኝ አስረድቷል።

ረቡዕ ወይም ሐሙስ አጠቃላይ የመውጫ ፈተና ውጤት ይፋ እንደሚደረግ ሚኒስቴሩ እንደገለጸለት ህብረቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

EBS TV

11 Feb, 19:35


" 4 ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል " - ፖሊስ

በቦንብ ፍንዳታ የተጠረጠሩ 4 ሰዎች በቁጥጥር ስር ማዋሉ ፓሊስ አስታውቋል።

ትናንት የካቲት 3/2017 ዓ.ም በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን እንዳስላሰ-ሽረ ከተማ በአንድ የህዝብ መዝናኛ ስፍራ በተጣለ ቦምብ በ13 ሰዎች ላይ ከባድ እና ቀላል ጉዳት ደርሷል።

ሞት አላጋጠመም።

አደጋው ከተከሰተበት ጀምሮ ከክልል እስከ ወረዳ የተቀናጀ የወንጀል አጣሪ ቡድን አቋቋሞ መንቀሳቀስ መጀመሩ የጠቀሰው ፓሊስ ፤ ከፍነዳታው ጋር በተያያየ 4 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ማዋሉ አስታውቀዋል። 

የቢንጎ ማጫወቻ መሆኑ በተጠቀሰው የህዝብ መዝናኛ ማእከሉ ሰዎች በብዛት እንደሚሰባሰቡበት የጠቀሰው ፓሊስ ባለፈው ጥር ወር በተመሳሳይ ቦንብ ተጥሎ ሳይፈነዳ በመቅረቱ አደጋ አላደረሰም ብሏል።

ፓሊስ " ጥቃቱን አድርሰዋል " በማለት በጠረጠራቸው ሰዎች ላይ ውጤታማ የሆነ የማጣራት በማካሄድ ጉዳዩ ለህዝብ እንደሚያሳውቅ ገልፆ የህዝቡ ትብብር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቋል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            

EBS TV

11 Feb, 19:35


#COC

ጤና ሚኒስቴር የሙያ ብቃት ምዘና ለመውሰድ እየጠበቁ ለሚገኙ የጤና ተመራቂዎች ምዘናው ለመስጠት ዝግጅት ማጠናቀቁን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።

በትምህርት ሚኒስቴር ባለፈው ሳምንት የተሰጠውን የመውጫ ፈተና ወስደው ያለፉ ተማሪዎችን ዝርዝር እየጠበቀ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የመውጫ ፈተና ውጤት መገለፅን ተከትሎ፥ COC የሚወስዱ አመልካቾች (በድጋሜ ተፈታኞችን ጨምሮ) ምዝገባ እንደሚደረግ ሚኒስቴሩ አረጋግጧል።

የCOC ምዘና አመልካቾች ምዝገባ በጊዚያዊነት ከየካቲት 10/2017 ዓ.ም በኋላ ለመጀመር መታቀዱን ሚኒስቴሩ ጠቁሟል።

በዚህም ምዘናውን በየካቲት ወር መጨረሻ ወይም በመጋቢት ወር የመጀመሪያ ሳምንት ለመስጠት በጊዚያዊነት መታቀዱን ከሚኒስቴሩ ሰምተናል።

Via
@tikvahuniversity

EBS TV

11 Feb, 19:35


" 26 ሰዎች ወዲያ ነው ህይወታቸው ያለፈው። ቁጥሩ ሊጨምር ይችላል " - ፖሊስ

በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ፤ ጉዳያ ቢላ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ26 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ።

አደጋው ከሻምቡ ከተማ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ በመገልበጡ ነው የተከሰተው፡፡

በደረሰው አደጋ የ26 ወገኖቻችን ሕይወት ወዲያው ሲያልፍ 42 ወገኖቻችን ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት መድረሱን የዞኑ የትራፊክ ደህንነት ሃላፊ ኢንስፔክተር አስናቀ መስፍን ተናግረዋል፡፡

በአደጋው ሕይወታቸው ያለፉ ወገኖች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችልም ሃላፊው ገልጸዋል፡፡

መረጃው የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ነው።

@tikvahethiopia

EBS TV

02 Feb, 19:31


' በጣም ከፍተኛና ልዩ ስጋት አለብን ! '

“ ኦፊሻል ስላልወጣ እንጂ ከሦስት ሳምንት በፊት ሥራ ቦታ ላይ አንድ የኮሌጁ ባለሙያ ተገድሏል በሽጉጥ ” - የኢትዮጵያ ህክምና ተማሪዎች ማኀበር

የኢትዮጵያ ህክምና ተማሪዎች ማኀበር (ባሕር ዳር) “በጥይት ተገደሉ” በተባሉት በዶክተር አንዷለም ዳኘ ግድያ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጾ፤ “ከፍተኛና ልዩ ስጋት አለብን” ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።

ማኀበሩ ይህን ያለው በኮሌጁ አካላትም ሆነ በኢንተርን ሀኪሞች የግድያና የዘረፋ ሙከራዎች እየተደረጉባቸው መሆናቸውን በመግለጽ ጭምር ነው።

“ ኦፊሻል ስላልወጣ እንጂ ከሦስት ሳምንት  በፊት ሥራ ስራ ቦታ ላይ የነበረ አንድ የህክምና ባለሙያ ተገድሏል በሽጉጥ ” ሲልም አስታውሷል።

ማኀበሩ ስለዶክተር አንዷለም ግድያና ስለስጋቱ ምን አሉ?

“ የዶክተር አንዷለም ዳኘ የቀብር ሥነ ስርዓት በድባንቄ መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል።

ዶክተር አንዷለም ትሁት ሀኪም ነበር። ስለሞተ ሳይሆን እውነታው ይሄው ስለሆነ ነው ይህን የምንለው። ስለሞተ ለመሞጋገስ አይደለም። ከሰውም ሰው ስለነበር እንጂ።

አሟሟቱም ልብ ሰባሪ ነው። ሙያው ሰብ ስፔሻሊስት ነው። አንቱ በሚባልበትና ህዝብን የሚያገለግልበት እድሜ ላይ ነው ያጣነው። እንደ ህክምና ተማሪዎች የእውቀት አባታችንን፤ ወንድማችንን ነው ያጣነው።

ይህን የመሰለ ሰብ ስፔሻሊቲ ሀኪም ማጣት እንደ ሀገርም እንደ ህዝብም በጣም ያማል። መራር ሀዘን ገጥሞናል።

በነገራችን ላይ ተደጋጋሚ ችግሮች አሉ። የሆስፒታሉ ዳይሬክተር ስልክ ተቀምቶ፣ በሽጉጥ ማንገራገር ገጥሞት ነበር፤ በኢንተርን ሀኪሞችም ሙከራ ይደረጋል።

በዚሁ የተነሳ ሰብ ስፔሻሊስቶች አገር እየለቀቁ፤ እየሸሹ ነው። ይሄ ባለበት ሁኔታ ጥበቃ፣ ከለላ አለመደረጉ በጣም ያሳዝናል። በጣም ከፍተኛና ልዩ ስጋት አለብን። የሆስፒታሉ ኃላፊ፣ ኢንተርን ሀኪሞችም ሙከራ ተደርጎባቸል።

የኮሌጁ ኃላፊዎችም ከአቅማቸው በላይ የሆነባቸው ይመስለናል። ምንም ከለላ የለም። ግቢ ያሉ ጥበቃዎችም የተጠናከረ አይደለም። ውጪ ላይ ይቅርና ግቢ ውስጥ ራሱ ከፍተኛ ስጋት አለ። አቤት የምንልበት አጥተን ነው እንጂ ” ብሏል።

በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ያሉ ተማሪዎች መጪውን ጊዜ ለማስተካከል እንዲተጉ፣ ስለመብታቸው ዘብ እንዲቆሙ፣ አንድነት በመፍጠር የመፍትሄ አካል እንዲሆኑ ማኀበሩ አሳስቧል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

EBS TV

02 Feb, 14:47


በትራፊክ አደጋ የ6 ወጣቶች ሕይወት አለፈ።

በሲዳማ ክልል ደቡባዊ ሲዳማ ዞን አለታ ወንዶ ወረዳ " ሽቆ " ተብሎ በሚጠራ አከባቢ ቡና ጭኖ ከሳይት ሲወጣ የነበረ የሠሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3- 18766 ኦሮ የሆነ የጭነት መኪና ተገልብጦ የ6 ወጣቶች ሕይወት አለፈ።

ሁለት ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት መድረሱም ታእላውቋል።

የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የመንገድ ደህንነት ቁጥጥር ዳይሬክቶረት ዳይሬክተር ዋና ኢንስፔክተር ዳንኤል ሽንኩራ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፥ በመኪናዉ ላይ ሹፌርና ረዳቱን ጨምሮ አስር ሰዎች ነበሩ።

ስምንቱ ገዳ ተብሎ በሚጠራዉ ቦታ የቡና ሳይት የሚሰሩ ታዳጊ ወጣቶች እንደነበሩና በአደጋው ወቅት መኪናዉ ሲገለበጥ ቡናዉ በላያቸዉ ላይ በመጫኑ 6ቱ ወዲያዉኑ ሲሞቱ ሁለቱ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዉ የመጀመሪያ ሕክምና በአለታ ወንዶ ሆስፒታል ከተደረገላቸው በኋላ ለከፍተኛ ሕክምና ወደ ሀዋሳ መላካቸውን ዋና ኢንስፔክተር ዳንኤል አስታዉቀዋል።

ዋና ኢንስፐክተሩ ሹፌሩና ረዳቱ በአሁኑ ሰዓት በአለታ ወንዶ ወረዳ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መሆናቸዉን አረጋግጠዋል።

በክልሉ በቡና ምርት ወቅት የሚኖሩ እንቅስቃሴዎች ለትራፊክ አደጋዎች የመጋለጥ ዕድልን ከፍ እንደሚያደርጉ በትራፊክ አደጋ መከላከልና ቁጥጥር ዙሪያ በሁሉም መዋቅሮች ሰፋፊ ስራዎች እየተከናወኑ ቢሆንም በቸልተኝነትና ከልክ ባለፈ በራስ መተማመን በገጠሪቱ አከባቢዎች አደጋዎች እንደሚከሰቱ ከክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ያገኘነዉ መረጃ ያመላክታል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia

EBS TV

02 Feb, 14:47


“ዶክተር አንዷለም ተተኩሶበት ተመትቶ ተገኘ መኪናው ውስጥ። አንድ ሀኪማችንም ተተኩሶበት መኪናው ሁለት፤ ሦስቴ ተመትቶታል” - ጤና ሳይንስ ኮሌጁ

የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጥበበ ግዮን ግቢ ስፔሻላንስድ ሆስፒታል የቀዶ ህክምና አገልግሎት ክፍል ዳይሬክተር ዶክተር አንዷለም ዳኘ በተተኮሰባቸው ጥይት መገዳላቸውን ዩኒቨርሲቲውና ኢንተርን ሀኪሞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ለደህንነታቸው ሲባል ስሜ ከመነገር ይቆይ ያሉ አንድ የዩኒቨርሲቲው ጤና ሳይንስ ኮሌጅ አካል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ ዶክተር አንዷለም ተተኩሶበት ተመትቶ ተገኘ መኪናው ውስጥ። አንድ ሀኪማችንም ተተኩሶበት መኪናው ሁለት፤ ሦስቴ ተመትቶበታል ” ሲሉ አስረድተዋል።

ተኩሱ ከመጀመሩ ከ30 ደቂቃዎች በፊት በአካባቢው እንዳለፉ የገለጹት እኝሁ አካል ስለ ዶክተር አንዷለም ሲገልጹ፣ “ ከሥራ እየተመለሰ በነበረበት ወቅት ቆሸ የሚባለው ሰፈር ተኩስ ተከፈተበት ” ነው ያሉት።

“ አንዷለምን የምናውቀው ደግ፣ ሩህሩህ፣ የሁላችንም ምሳሌ አድርገን ነው። ሰው ነው ከሰውም ሰው ” ሲሉ እያለቀሱ ተናግረዋል።

የገዳዮቹ ማንነት ታውቋል ? የለበሱት ልብስ ምን አይነት ነበር ? ስንል ላቀረብንላቸው ጥያቄ በሰጡን ምላሽ፣ “ እርግጠኛ ሆኖ አሁን መናገር አይቻልም ” ብለዋል።

አክለው፣“ አንድ ከዶ/ር አንዷለም በፊት ሲጓዝ የነበረ ሀኪም ተተኩሶበት ተርፏል። ‘ሦስት የሚተኩሱ ሰዎች ነበሩ፤ የምን እንደሆነ አላውቅም ዩኒፎርም ነገር ለብሰዋል’ ብሎናል ” ሲሉ አስረድተዋል።

በጥበበ ግዮን ግቢ ህክምና ጤና ሳይንስ ኢንተርን ሀኪሞች በበኩላቸው፣ “ ዶክተር አንዷለም ከከተማ ከሥራ ውሎ ሲመለስ ምሽት ላይ ነው የተመታው። ግን ማን እንደመታው የተረጋገጠ ነገር የለም ” ሲሉ ነግረውናል።

“ አስከሬኑም ለፓሊስ ተደውሎ ነው ማታ የተነሳው ” ያሉት ኢንተርን ሀኪሞቹ፣ “ አሁን ሀኪሞቹም፣ ሬዚደንቶቹም ሁሉም የባሕር ዳር ዩኑቨርሲቲ ተማሪዎችና ሠራተኞች ሀዘኑን እየተካፈልን ነው ያለነው ” ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተጨማሪ ማብራሪያ የጠየቃቸው የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት ዶክተር መንገሻ ከሰዓታት በፊት በሰጡን ቃል “ አስከሬን ይዘን ከቤት ወደ ቤተክርስቲያን እየወጣን ነው ” የሚል አጭር ማረጋጠጫ ብቻ ሰጥተዋል።

ስለገዳዮቹ ማንነት የታወቀ ነገር እንዳለ የጠየቅነው የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጸጥታ ክፍል በሰጠን ምላሽ፣ “ ግድያው ከግቢ ውጪ ስለተፈጠረ ምንም ያወቅነው ነገር የለም ” ብሏል።

“ ያወቅነው መረጃ የለንም። እኛም እንደማንኛውም ሰው መሞቱን ብቻ ነው የሰማነው ” ሲል አክሏል።

የሚመለከታቸውን የከተማውን የጸጥታ አካላት ለጉዳዩ ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጡ ጥያቄ የምናቀርብ ይሆናል።

ዶክተር አንዷለም ዳኘ የዩኒቨርሲቲው ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ስፔሻሊስት፤ የጉበት፣ የቆሽት፣ የሀሞት ጠጠር መስመር ሰብ ስፐረሻሊስት ሀኪም፣ እንዲሁም የልጆች አባት እንደነበር ኢንተርን ሀኪሞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። 

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

EBS TV

02 Feb, 14:47


ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚደንት ሆነው ተመረጡ።

የገዢው ብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) የፓርቲው ፕሬዜዳንት አድርጎ በከፍተኛ ድምጽ እንደመረጣቸው ፓርቲው አሳውቋል።

ተመራጩ የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት በጉባኤተኛው ፊት ቃለ መሀላ እንደፈጸሙ ተገልጿል።

በተያያዘ ዜና ጉባኤው አቶ ተመስገን ጥሩነህን እና አቶ አደም ፋራህን የፓርቲው ምክትል ፕሬዚደንቶች አድርጎ ከፍተኛ በሆነ ድምጽ መምረጡ ተነግሯል።

ሁለቱ ምክትል ፕሬዚደንቶች በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት በጉባኤተኛው ፊት ቃለ መሀላ ፈጽመዋል።

@tikvahethiopia

EBS TV

02 Feb, 14:47


" ፍትህ እንሻለን ! " - ቤተሰቦች

በኦሮሚያ ክልል፣ ምዕራብ ሸዋ ዞን ሜታ ወልቂጤ ወረዳ አንዲት ህጻን ከቤት ተወስዳ ከተደፈረች በኋላ ተገድላ መገኘቷ ቁጣ ቀስቅሷል።

" በኛ የደረሰ በማንም አይድረስ " የሚሉት የተጎጂ ቤተሰብ በልጃቸው ላይ ለደረሰው ቀሰቃቂ ወንጀል " ፍትህ እንሻለለን " ብለዋል።

ሲምቦ ብርሃኑ ትባላለች፡፡ የ8 ዓመት ልጅ ስትሆን ገና የአንደኛ ክፍል ተማሪ ነበረች።

ባሳለፍነው ሳምንት ባለፈ ረቡዕ  ጥር 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ከትምህርት ቤት ተመልሳ ምሳ እንደበላች ከመኖሪያ ቤቷ የደረሰችበት ሳይታወቅ ቀርቷል።

በዕለቱ ፍለጋ የወጣው ቤተሰብ ታዳጊዋን ከነሙሉ ጤንነትና በህይወት ለማግኘት ግን አልታደሉም፡፡

ሮጣ ያልጠገበች ፤ ክፉ ከደጉን እንኳን የማትለይ ህፃን ለአዕምሮ በሚከብድ ሁኔታ ከተደፈረች በኋላ " እንዳትናገር በሚል " ከመኖሪያ ቤታቸው ጀርባ በቅርብ ርቀት ላይ ህይወቷ አልፎ መገኘቱን አንድ የቤተሰቧ አባል ለዶቼ ቬለ ሬድዮ ተናግረዋል። 

ህፃኗ ከተገደለች በኋላ ተሰቅላ መገኘቷን የገለጹት የቤተሰብ አባሉ " ጫማዋን ያወለቁባትና የሰቀሏት ቦታ አንድ አይደለም የ50 ሜትር ገደማ ርቀት አለው " ብለዋል።

በወረዳው ኤላ ከተማ በ8 ዓመቷ ልጅ ሲምቦ ላይ የተፈጸመው ጥቃት አባት የመንግስት ሰራተኛ መሆናቸው እና በስራ ቦታ መሆናቸው እንዲሁም እናት የ2 ወር እመጫት በመሆናቸው አጋጣሚውን በመጠቀም እንደነበር የቤተሰቡ አባል ተናግረዋል።

የተጎጂ ቤተሰብ አባል የሆኑት አስተያየት ሰጪ " የህፃኗ ቤተሰብ ቤት በፊት ለፊት በኩል ሆቴል በመሆኑ የሚገባውና የሚወጣው ብዙ ነው፡፡ በጓሮ በኩል ፑል መጫወቻም አለ፡፡ ደፋሪዎችም በዚያው በጀርባ በር እንደወሰዷት ነው የቤተሰብ ስጋት " ብለዋል።

2009 ዓ.ም. የተወለደችው ትንሿ ሲምቦ ገና በ8 ዓመቷ ለዚህ እጅግ ለአሰቃቂ ድርጊት ሰለባ መሆኗ ቤተሰቦቿን ቁጭት ውስጥ ከቷል።

" ባለሙያዎች በሰውነቷ ላይ የታየውን ፈሳሽ በመውሰድ ምርመራ እያደረጉ ነው " ያሉት የቤተሰብ አባል እስካሁን በቁጥጥር ስር የዋለ ተጠርጣሪ  አለመኖሩንም ገልጸዋል፡፡

ባለፈው ረቡዕ ከሰዓት በኋላ 9 ሰዓት ተኩል  የተገኘው የህፃኗ ሲምቦ አስክሬን በትናንትናው እለት ስርዓተ ቀብሩ ተፈጽሟል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የዶቼ ቨለ ሬድዮ ነው።

@tikvahethiopia

EBS TV

02 Feb, 14:47


" ከ10 ሄክታር በላይ የፓርኩ ክፍል በቃጠሎ ወድሟል " - የማዜ ብሔራዊ ፓርክ

ከትናትና በስቲያ ማምሻውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ቁጫ ወረዳ የማዜ ብሔራዊ ፓርክ አከባቢ የተነሳዉ እሳት ሌሊቱን ሙሉ ሳይጠፋ ማደሩንና በፓርኩ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን የማዜ ብሔራዊ ፓርክ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መስፍን ጬማ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

በአከባቢው ከፓርኩ አቅራቢያ ከሚገኝ ሞርካ ቀበሌ አንድ አርሶ አደር የማሳ ዝግጅት በሚያደርግበት ወቅት እያካሄደ ከነበረዉ ቃጠሎ የወጣ እሳት ምሽት 12 ሰዓት አከባቢ በፓርኩ ዙሪያ የሚገኝን 5 ሄክታር ቦታ ካወደመ በኋላ ከሌሊቱ 8 ሰዓት ገደማ የፓርኩን ክፍል ማዉደም መጀመሩን የገለፁት አቶ መስፍን ከወቅቱ ነፋሻማነትና የሰዓቱ ምቹ አለመሆን የእሳት ማጥፋትን ስራ ፈትኖት እንደነበር አስታዉቀዋል።

የእሳት ማጥፋት ስራዉ ከዛሬ ማለዳ ከ12 ሰዓት ጀምሮ በተደራጀ መልኩ በአከባቢው ነዋሪዎች፣ በፀጥታ መዋቅርና በእሳት አደጋ ብርጌድ ርብርብ ሲደረግበት ቆይቶ ከፓርኩ ዉጪ 5 ሄክታር ከፓርኩ ክፍል ደግም 10 ሄክታር በላይ ካወደመ በኋላ ረፋዱ አራት አከባቢ በቁጥጥር ስር መዋሉን አቶ መስፍን አስታዉቀዋል።

አቶ መስፍን አክለዉም እስካሁን በተደረገዉ ማጣራት ከፓርኩ ስነ ምህደር ዉድመት ባሻገር በአራዊቱ ላይ ጉዳት አለመድረሱን ገልፀዋል።

በእሳት ማጥፋቱ ስራ ከተሳተፉት የአከባቢዉ ነዋሪዎች ፣የፀጥታ መዋቅር አባላትና በሃይለማርያምና ሮማን ፋዉንዴሽን የተቋቋመው የእሳት አደጋ ብርጌድ በተጨማሪ ከወላይታ ወደ ሳዉላ ይንቀሳቀሱ የነበሩ የግልና ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች ሕዝቡን በማጓጓዝ ያደረጉት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው ምስጋና አቅርበዋል።

የማዜ ብሔራዊ ፓርክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ እና ጎፋ ዞኖች መካከል ቁጫ ወረዳ አከባቢ የሚገኝ ሲሆን ከአዲስ አበባ 460 ፣ከሐዋሳ 235 እንዲሁም ከጋሞ ዞን አርባምንጭ ከተማ 196 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል።

የፓርኩ አጠቃላይ ስፋት 220 ስኩዌር ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆንበሀገራችን በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኘዉ የስዋይኔ ቆርኬ ጨምሮ አንበሳ፣አቦሸማኔ፣የቆላና ትልልቆቹ አጋዘኖች፣አምባራይሌና ከርከሮን ጨምሮ 39 የተለያዩ አጥቢ እንስሳቶች፣196 የአዕዋፋት ዝርያዎች እና ከ80 በላይ የእፅዋት አይነቶ እንደሚገኙበት ከማዜ ብሔራዊ ፓርክ ያገኘነዉ መረጃ ያመላክታል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia

EBS TV

02 Feb, 14:47


#Update

የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር የአማካሪ ካውንስል ምክር ቤት በይፋ ተመሰረተ።

ምክር ቤቱ ሰብሳቢ እና ምክትል ሰብሳቢ የመረጠ ሲሆን የትግራይ ነፃነት ፓርቲ ሊቀመንበር ደጀን በርሀ (ዶ/ር) በከፍተኛ ድምፅ ምክትል ሰብሳቢ ሆነው ተመርጠዋል። 

የአማካሪ ካውንስል ምክር ቤት የማቋቋም ሃሳብ የክልሉ ምክር ቤት የሚያፈርሰው የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ተከትሎ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ማቋቋምያ ሰነድ ጥር 2015 ዓ.ም ሲፀድቅ የተነሳ ሃሳብ ነው።  

ሃሳቡ በድጋፍ እና በተቃውሞ ለሁለት አመታት ያህል ሲናጥ ቆይቶ ዛሬ ጥር 25/2017 ዓ.ም በይፋ ተመስርቶ መሪዎቹ መርጠዋል። 

በምስረታ ካውንስሉ መልእክት ያስተላለፉት ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ፤ በክልሉ የሚገኙ የኢሮብ እና ኩናማ ብሄረሰቦች የተወከሉበት ካውንስሉ ዘግይቶም ቢሆንም መመስረቱ መልካም ሆኖ አቃፊ ፣ አሳታፊ እና የሃሳብ ብዙህነት የሚንሸራሸሩበት መድረክ መሆን ይገባዋል ብለዋል። 

የአማካሪ ካውንስል ምክር ቤቱ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት የተቀመጡት የትግራይ ህዝብ ጥቅሞች በተሻለ እና በአስተማማኝ እንዲመለሱ አጋዥ ሃይል ለማሰባሰብ አልሞ መቋቋሙን የጠቆሙት ፕሬዜዳንቱ " ልዩነቶቻችን በማጠበብ ለተሻለ ነገ በጋራ መስራት ወቅታዊ የትግራይ ጥያቄ ነው "  ብለዋል። 

የካውንስሉ እድሜ የጊዚያዊ አስተዳደሩ የቆይታ ጊዜ መሆኑ ያስረዱት ፕሬዜዳንት ጌታቸው ይህንን ታሳቢ በማድረግ የትግራይ ፓለቲካዊ ምህዳር ማስፋት እና ለነገ ማመቻቸት ዋነኛ ስራው መሆን እንደሚገባ አክለዋል።   

ካውንስሉ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ስራዎች መሬት ላይ እንዲወርዱ አጋዥ ሚና ከመጫወት በተጨማሪ የትግራይ ተደማጭነት እና የመደራደር አቅም የሚያጠናክር አቅጣጫ መከተል ይገባዋል ብለዋል ፕሬዜዳንቱ። 

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር አማካሪ ካውንስል ምክር ቤት ለመምራት ሰብሳቢ እና ምክትል ሰብሳቢ ሆነው የተመረጡት ቃለ ማህላ ፈፅሟል።

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር አማካሪ ካውንስል ምክር ቤት መመስረት በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት እና ሳልሳይ ወያነ ፓርቲ እና ሌሎች ተቃውሞውታል

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            

EBS TV

18 Jan, 18:21


#ከተራ2017

የ2017 ዓ/ም የጥምቀት ከተራ በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን ዘንድ በቤተክርስቲያኗ ሥርዓት እና ትውፊት ተከብሮ ውሏል።

ዛሬ ታቦታት ከየአብያተክርስቲያናቱ ወጥተው ወደ የማደሪያቸው ባህረ-ጥምቀት ገብተዋል።

በነገው ዕለት በመላው ሀገሪቱ የጥምቀት በዓል ይከበራል።

@tikvahethiopia

EBS TV

18 Jan, 18:19


#Update

🚨“ በጣም ብዙ ችግር ነው እየደረሰባቸው ያለው። ጣታቸው የተቆረጠ አሉ ” - የወላጆች ኮሚቴ

ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ከሰጠው መግለጫ በመነሳት፣ “ አንዳንድ ሚዲያዎች መንግስት በማይናማር የታገቱ ዜጎችን አስለቀቀ ” በማለት መዘገባቸው ስህተት መሆኑን ጉዳዩን የሚከታተሉ የታጋች ቤተሰቦች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

የታጋቾቹ ቤተሰቦች በዝርዝር ምን አሉ ?

“ አጋቾች  ያገቷቸውን ልጆቻችንን ‘መንግስት አስለቀቀ’ መባሉ ትክክል አይደለም።

አጋቾቹ ሲቀጧቸው የተጎዱ፣ በህመም ሳቢያ መስራት የማይችሉ ልጆችን ከካምፕ አውጥተው ታይላንድ ድንበር ሲጥሏቸው ሰብአዊ መብት ላይ የሚሰሩ ኤን.ጂ.ኦ አንስተው ታይላንድ በመውሰድ አሳክመው ህንድ ካለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጋር በመሆን ነው ኢትዮጵያ እንዲገቡ ያደረጓቸው።

አንዳንድ ሚዲያዎች የዘገቡትና መንግስትም ድፍን ባለ መልኩ የሰጠውን መግለጫ መነሻ በማድረግ ማይናማር ያሉ ልጆች የተለቀቁ የመሰላቸው
አድማጮች እንኳን ደስ አላችሁ ’ የሚለን በዝቷል። እውነታው ይሄ አይደለም።

ይህን ጉዳይ ህዝብ ይረዳው። ማይናማር ከታገቱት ልጆች መካከል እንዲለቀቁ በተደረገ ጥረት ማንም አልተለቀቀም።

ታይላንድ ያሉት ናቸው እንጂ ማይናማር ያሉት አይደሉም የወጡት። ዋሽተው ነው። ዜናውን አካብደውታል። እኛን ምንም ተስፋ አልሰጡንም። ‘አትምጡ’ ነው ያሉን ” ሲሉ አስረድተዋል።

የወላጆች ኮሚቴ በበኩሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል ምን አለ ?

በዚህ መልኩ (ታጋቾች ተለቀዋል በሚል) የዘገቡት ሚዲያዎች ሁለት፣ ሦስት ጊዜ ድምፅ እንዲሆኑን ጠይቀናቸው ሳለ ‘ እንከሰሳለን ’ ብለው ነው የፈሩት። አሁን ግን ያልተወራውን ማስተላለፍ ከኢቲክስ ውጪ ነው። በጣም ቅር ብሎናል። እውነታውን አሳውቁልን።

በታይላንድና በማይናማር ድንበር ያሉት ልጆች እንጂ ወጡ የተባሉት ከማይናማር ግዛት ካሉት ጋር እንደማይገናኝ በህንድ የሚገኘው ኢትዮጵያ ኤምባሲ ነግሮናል።

የኤምባሲው ሰዎች ‘እኛ የሚመለከተን ታይላንድ አካባቢ ያለውን ብቻ እንጂ የማይናማሩ የሚመለከተው ቶኪዮ ያለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ነውና ማይናማር ያሉትን አንድም ነገር አልሰራንም’ ብለው ቃል በቃል ነው የነገሩን።

ከኢትዮጵያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር አምባሳደር ነብያት ጌታቸው በመግቢያ ንግግራቸው ያስተላለፉት ትክክለኛውን ‘ታይላንድ አካባቢ ያሉትን’ ብለው ነው።

ነገር ግን አንዳንድ ሚዲያዎች በስቃይ ላይ ያሉ ልጆችን መንግስት እያስወጣ እንዳለ አድርገው ነው መግለጫውን የዘገቡት። ይህ ቅር አሰኝቶናል።


ሌሎች አገራት እኮ ዜጎቻቸውን ያስወጡት ከትራደሽናል ሊደሮች፣ ከኤምባሲዎች ጋር ሆነው በመስራት ነው። የኛዎቹ ግን ይህን ለማድረግ ፈቃደኛ አይደሉም።

አንዱን ኢትዮጵያዊ የመራቢያ አካሉን የዘር ፍሬ ነቅለውታል። በጣም ብዙ ችግር ነው እየደረሰባቸው ያለው። ጣታቸው የተቆረጠ አሉ።

አሁንም ቢሆን የኢትዮጵያ መንግስት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተነጋግሮ በችግር ላይ ያሉ ልጆችንን  ካሉበት ስቃይ እንዲታደጋቸው በአጽንኦት እንጠይቃለን ” ብሏል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

EBS TV

18 Jan, 18:19


ሞሐ የለስላሳ መጠጦች ኢንዱስትሪ አክሲዮን ማህበር፣ ለደንበኞቹ ካዘጋጃቸው በርካታ ሽልማቶች
ውስጥ አንዱ ቢዋይዲ የኤሌክትሪክ መኪና ዕጣ፣ በመቀሌ ለዕድለኛ ወጥቷል፡፡
ዕድለኛው አሸናፊ አቶ የማነ ነጋሽ ፣ ሽልማታቸውን ጥር 10 ቀን 2017ዓ.ም. በመቀሌ ከተማ በተከናወነ
ልዩ የሽልማት ፕሮግራም ተረክበዋል፡፡
ከዚህ በፊት በአዲስ አበባ እና በድሬዳዋ ከተማ ነዋሪ የሆኑ ዕድለኞች ሚሪንዳ እና ፔፕሲ ጠጥተው
ቢዋይዲ የኤሌክትሪክ መኪና ዕጣ ማሸነፋቸው ይታወሳል፡፡

EBS TV

18 Jan, 15:40


#ጎንደር

በታሪካዊቷ እና ጥንታዊቷ ጎንደር ሁሉም ታቦታት ፒያሳ በመገናኘት ወደ ማደሪያ ቦታቸው እየተጓዙ ይገኛሉ።

የጥምቀት ከተራ በዓል በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምዕመናን ዘንድ እየተከበረ ይገኛል።

ጎንደር የጥምቀት በዓል እጅግ በጣም በደማቅ ሁኔታ ከሚከበርባቸው የሀገራችን አካባቢዎች አንዱ ሲሆን ለዘንድሮው በዓል በርካታ እንግዶች በዓሉ ላይ ለመታደም ጎንደር ተገኝተዋል።

ፎቶ፦ ማህበረ ቅዱሳን እና ፋኖስ ፒክቸርስ

@tikvahethiopia

EBS TV

13 Jan, 14:23


" ለ1,523 ቀናት ያህል በፕላስቲክ ቤት መኖር ይብቃን " - ተፈናቃይ ወገኖች

ዛሬ ጥዋት በመቐለ ሰላማዊ ስልፍ ተካሂዷል።

ሰላማዊ ሰልፉ " በቃን ወደ ቄያችን መልሱን " ባሉ የተፈናቃይ መጠለያዎች ውስጥ በሚገኙ ወገኖች አማካኝነት ነው የተደረገው።

የመቐለ ሮማናት አደባባይ የሚወስዱ መንገዶች ከጥዋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ በከተማዋ ፓሊስ ከተሸከርካሪ እና ከእግረኞች እንቅስቃሴ ነፃ  እንዲሆኑ ተደርገው ነበር።

በመቐለ እና ከመቐለ ውጪ ባሉት የተፈናቃይ መጠለያዎች የሚገኙ ወገኖች " ይበቃል !! " በሚል በሦስት አቅጣጫ ወደ ሮማናት አደባባይ ተሰባስበው ድምጻቸውን አሰምተዋል።

ሰልፈኞች በሮማናት አደባባይ እንደደረሱ ፦

- ለ1523 ቀናት በፕላስቲክ ቤት መኖር ይብቃን !
- የፕሪቶሪያ ስምምነት በሙሉነት ይተግበር !
- ወደ ቤታችን መልሱን !
- ጦርነት እንጠየፋለን ፤ ሰላም እንሻለን !
- ዓለም ድምፃችንን ስሚ !
- በመቀጠል ያለው የተፈናቃዮች ሞት ይብቃ !
- ህገ- መንግስት ይከበር !  ... የሚሉ እና ሌሎች መፈክሮች አሰምተዋል።

ተፈናቃዮቹ በተወካያቸው በኩል ባሰሙት መግለጫ ፥ በመላ ትግራይ የሚገኙ ተፈናቃዮች በረሃብ እና መድሃኒት እጦት እየሞቱ መሆናቸው ጠቅሰዋል።

ለማሳያ ከመስከረም 2017 ዓ.ም ወዲህ  ብቻ በክልሉ በሚገኙ የተለያዩ የተፈናቃይ ማቆያ ጣብያዎች ይኖሩ የነበሩ ከ812 በላይ ወገኖች ህይወታቸው ማጣታቸው ገልፀዋል።

መሰል ሰለማዊ ሰልፍ የዛሬን ጨምሮ ለ3 ቀናት እንደሚኖር ተነግሯል። የዛሬው የማስጀመሪያ ስነ-ስርዓት ሰላማዊ ነበር።

የተፈናቃይ ስልፈኞቹን ጥያቄ እና የሚመለከተው የመንግስት አካል ምላሽ ካለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ተከታትሎ ያቀርባል።

#TigraiTV #TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia   

EBS TV

13 Jan, 14:23


" መላው የሎስ አንጀለስ ግዛት በእሳት ስጋት ውስጥ ይገኛል " - ባለስልጣናት

በአሜሪካ ፤ ሎስ አንጀለስ የተነሳው ሰደድ እሳት አሁንም መቆጣጠር ያልተቻለ ሲሆን የሟቾች ቁጥርም ወደ 24 ከፍ ብሏል። 16 ሰዎች ደግሞ የገቡበት አይታወቅም።

በሎስ አንጀለስ ዙሪያ 3 አካባቢዎች መቃጠላቸውን ቀጥለዋል።

በአሁኑ ላይ ትልቁ እሣት ሚገኘው በፓሊሳድስ ሲሆን 9307 ሔክታር መሬትን ሲያቃጥል 11 በመቶውን መቆጣጠር ተችሏል።

የኢቶን እሳት በትልቅነቱ 2ኛ ደረጃ ሲይዝ ከ5665 ሔክታር በላይ አቃጥሏል። 27 በመቶው በቁጥጥር ስር ውሏል።

ከሞላ ጎደል በቁጥጥር ስር በዋለው በሃረስት እሳት 323 ሄክታር መሬት መቃጠሉ ታውቋል።

የእሳት አደጋ ሠራተኞች ትልቁን እሳት መቆጣጠር ቢጀምሩም ባለስልጣናት ግን ቀጣዮቹ ንፋሶች " አደጋ ሊያስከትሉ የሚችሉ የንፋስ ሁኔታዎች ሊሆኑ ይችላሉ መላው የሎስ አንጀለስ ግዛት በእሳት ስጋት ውስጥ ይገኛል " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

እሳቱ በአሜሪካ ታሪክ አውዳሚው ለመሆን መቃረቡ ተገልጿል።

የግል ትንበያ ተቋም የሆነው " አኩዌዘር " በእሳት ቃጠሎ የተነሳ የደረሰው ኪሳራ ግምት ከ250 እስከ 275 ቢሊዮን ዶላር ሊደርስ ይችላል ብሏል።

ለሌላ በኩል ፥ የአደጋ ቀጠና ከሆኑ ቦታዎች ሰዎች እንዲወጡ የታዘዘ ሲሆን የወጡም አሉ።

ነዋሪዎች እንዲወጡ በታዘዙባቸው አካባቢዎች ዝርፊያ ሲፈፅሙ የነበሩ 29 ሰዎች መታሰራቸው ተነግሯል።

ሰዎች ቤታቸው ለቀው ሲወጡ ሲዘርፉ የነበሩ በርካቶች ነበሩ።

ከዚህ ባለፈ ፥ በሰደድ እሳቱን ምክንያት አከራዮች በህገወጥ መንገድ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ላይ ከፍተኛ የሆነ ጭማሬ ማድረጋቸው ተነግሯል።

እሳቱን ተከትሎ ከዚህ ቀደም ይጠየቅበት ከነበረው የቤት ኪራይ በሺዎች በመጨመር እንደተጠየቁ አንዳንዶች ገልጸዋል።

በሰደድ እሳቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ቤታቸው አመድ ሆኗል። በርካታ የተፈናቀሉ ተጎጂዎች " የማይቀምስ የቤት ኪራይ እና የሆቴል ክፍያ እየተጠየቅን ነው " ማለታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።

@tikvahethiopia

EBS TV

12 Jan, 18:55


#ሰርገኛ

ከአገር ውስጥም ሆኑ ከውጪ በበጀትዎ መሰረት ፕሮግራሞ የተሳካ እንዲሆን ሙሉ የማማከር አገልግሎት እንዲሁም የፕሮቶኮል ስራ እንሰራለን።
ለድግስዎ አዳራሽ ፣ ምግብ ፣ ዲኮር ፣ መኪና ፣ ዲጄ ፣ ፎቶ እና ሌሎችንም ከፈለጉ በቀላሉ ከሰርገኛ ያገኛሉ!  ይደውሉልን! +251976085440 | @ChatSergegna

የማህበራዊ ሚዲያ ገፃችንን ፎሎው በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ! www.sergegna.com
Follow Sergegna
👉🏼 Telegram | Facebook | Instagram | Tiktok

@sergegna 💍

EBS TV

12 Jan, 18:55


" ያልተመዘገበ ተማሪ አይፈተንም " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

የ2ዐ17 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ / የ12ኛ ክፍል ፈተና ምዝገባ መጪ ማክሰኞ ጥር 6 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ላይ እንደሚጠናቀቅ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

በተለያየ ምክንያት ያልተመዘገቡ ካሉ በእነዚህ ቀሪ ሁለት ቀናት ላይ ብቻ እንዲመዘገቡ ያሳሰበ ሲሆን " ያልተመዘገበ አይፈተንም " ብሏል።

@tikvahethiopia

EBS TV

12 Jan, 18:55


“ በየፍርድ ቤቱ የሚሰጡ ውሰኔዎች ደካማ፣ ሕጋዊ ውሳኔ ብቻ፣ የመወሰን ስልጣን ስላላቸው ብቻ የሰጧቸው ውሳኔዎች ናቸው ” - የሕግ ባለሙያ ጥጋቡ ደሳለኝ

ጠበቃና የሕግ ባለሙያ ጥጋቡ ደሳለኝ፣ በሴቶችና ህፃናት የወሲብ ጥቃት ፈጻሚዎች ላይ “ ከ15 እስከ 25 ዓመት ጽኑ እስራት ” የሚለው ድንጋጌ ችግሩ እንዲስተካከል ስላላደረገ መሻሻል እንዳለበት ተናገሩ።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከጠበቃና የሕግ ባለሙያው ጋር ያደረገውን ቆይታ ያንብቡ።

Q. ህፃናትን የደፈሩ የስጋ ዝምድና ያላቸው ግለሰቦች ላይ ፍ/ቤቶች የሚጥሉት ቅጣት በማነሱ ድርጊት ፈጻሚዎችን “ አይዟችሁ በርቱ የሚል እየሆነ ነው ” የሚሉ ትችቶች ተበራክተዋል፣ ከሕጉ አንጻር በፍርድ አሰጣጥ ምን መስተካል አለበት ? 

አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ ፦

“ በወንጀል ሕጉ ህፃናት ላይ የሚፈጸሙ የአስገድዶ መድፈር ወንጀሎች የቅጣት ደረጃ ‘ከ እስከ’ የሚል የግርጌና የራስጌ አይነት የቅጣት ስርዓት ነው ያለው። ሰፊ ነው ክፍተቱ።

ለምሳሌ እድሜያቸው ከ13 ዓመት በታች በሆኑ ህፃናት የአስገደድዶ መድፈር ወንጀል የፈጸመ ሰው ከ15 - 25 የሚደርስ፤ ማፈን፣ ማታለል፣ ማነቅ አይነት ተደራራቢ ወንጀል ካለው  የእድሜ ልክም ሞትም ሊሆን ይችላል።

እድሜያቸው ከ14 ዓመት በላይ የሆኑ ህፃናትና አጠቃላይ በሴቶች የሚፈጸም ወሲባዊ ጥቃት ከሆነ ደግሞ እንደ ድርጊቱ አፈጻጸም ከ5 ዓመት እስከ 25 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲፈረድ የሚል ነው።

ዳኞች 10፣ 15 ዓመት ቢፈርዱ ልክ ናቸው በሕገ መንግስቱ አንቀጽ 79 መሰረት ዳኞች የሚሰጧቸው ውሳኔዎች ፍትሃዊ፣ ነጻና ገለልተኛ እንደሆነ ታሳቢ ይደረጋል። 

የእኛ አገር ዳኝነት በተጻፈ ሕግ ብቻ ነው ፍርድ የሚሰጠው። ነገር ግን መሰጠት ያለበት በተጻፈ ሕግ ብቻ ሳይሆን በርትዕ (በሕሊና ፍርድ) ጭምር ነበር።

ነገር ግን ዳኞቻችን ብዙ ጊዜ የሚሰጧቸው ውሳኔዎች የጻፈውን ሕግ እንጂ ርትዕን ታሳቢ አያደርጉም። 

ዳኞቻችን ደግሞ ከምልመላው እስከ ሹመቱ ድረስ ችግር ባለበት ሂደት ነው የሚመጡት። ሕግ የተማሩ ሁሉ ዳኛ አይሆኑም በመርህና በዓለም አቀፍ ደረጃ። 

ኢትዮጵያ ውስጥ ግን ዳኛ ከሆነና በዐቃቢ ሕግም ይሁን በሕግ ባለሙያነት አምስት ዓመት ከሰራና ምልመላውን ካለፈ በምክር ቤት ይሾማል። የዳኞቻችን የውሳኔ አሰጣጥ ችግር አለባቸው። ደካማ ውሳኔ ነው የሚሰጡት።

ሕጋዊ ውሳኔ መስጠትና ፍትሃዊ ውሳኔ መስጠት ይለያያሉ። ሕጋዊ ውሳኔ ማንም የመወሰን ስልጣን ያለው የሚሰጠው ውሳኔ ነው። ለምሳሌ የአንድ ተቋም ጥበቃ ‘ደንበኛ ተፈትሾ ነው የሚገባው’ ቢል ያ የጥበቃው ሕጋዊ ወሳኔ ነው።

በሕግ ደግሞ ፍትሃዊ የሚባለው ከዚህ ውሰኔና አስተሳሰብ ይለያል። የወጡ ሕጎችንና ማስጃዎችን መሠረት ከማድረግ ባሻገር ርትዕን/የህሊና ፍርድን ታሳቢ ያደረገ፣ ተጎጂዎችን ሊክስ የሚችል ጥራት ያለው ውሳኔን ታሳቢ ያደረገ ነው። 

ከፍርድ ቤት የሚጠበቀው ፍትሃዊ ውሳኔ እንጂ ሕጋዊ ውሳኔ አይደለም። በየፍርድ ቤቱ ያሉ ዳኞቻችን የሚሰጧቸው ውሳኔዎች ግን ፍትሃዊ ሳይሆን ሕጋዊ ውሳኔዎች ሆነዋል።

በጥያቄው መሰረት በየፍ/ቤቱ የሚሰጡ ውሰኔዎች ደካማ፣ ሕጋዊ ውሳኔ ብቻ፣ የመወሰን ስልጣን ስላላቸው ብቻ የሰጧቸው ውሳኔዎች ናቸው።

 ነገር ግን ፍትህ በመርህ ደረጃ ፈውስ፣ ህክምና፣ ኢንሹራንስ በመሆኑ ያንን ታሳቢ ያደረገ ጥራትና ብቃት ያለው ውሳኔ ሊሰጡ ይገባል። 

ለምሳሌ አንድ የፍርድ ውሰኔ የሰጠ ዳኛ ቢጠየቅ ‘ሕጉ ከ5 እክከ 25 ዓመት ስለሚል የተጠቀሰበትን አንቀጽ አይቼ፣ የቀረቀውን ማስረጃ መዝኜ፣ የተከሳሹን የቅጣት ማቅለያ ግምት ውስጥ አስገብቼ ተቀናንሶ 13 ዓመት ወሰንኩበት፤ ምን አጠፋሁ?’ ይላል። 

ነገር ግን ኢትዮጵያ ውስጥ በፍርድ ቤቶች በኩል ዳኞች ላይ በጣም መሰራት ያለበት፦ የተጎጂዎቹን እንባ የሚያብስ፣ አጥፊዎችን የሚያርም፣ ሌላውን የሚያስጠነቅቅ ርትዕን ታሳቢ ያደረገ ውሳኔ መስጠት ላይ ነው። 

በፍርድ ቤቶች እየተሰጡ የሚስተዋሉት እነዚህ አነስኛ ቅጣቶች ሕጋዊ እንጂ ፍትሃዊ ውሳኔ አይደሉም። ነገር ግን ዳኞቹ  በቅጡ አይረዱትም እንጂ የዳኞች ውሳኔ ከሕጋዊ ውሳኔ የላቀ መሆን አለበት። ”


Q. ሰሞኑን የሲዳማ ክልል ፍትህ ቢሮ ያወጣው መረጃ የ9 አመት ልጁን የደፈረው አባት በ17 ዓመት እስራት እንደተቀጣና የሌሎቹንም ወንጀልና የቅጣት ውሳኔ በመጥቀስ፣ በአባቷ፣ በእህቷ ባለቤት የተደፈሩት ህፃናት መደፈር ብቻ ሳይሆን በወላጅና በቅርብ ሰው እንደተደፈሩ ጨምር ነው በአእምሯቸው የሚያቃጭልባቸው። ለመሆኑ የቅጣት ውሳኔው አላነሰም ? 

የሕግ ባለሙያ ጥጋቡ ደሳለኝ ፦

“ በአስገድዶ መድፈሩ ተጨማሪ የወንጀል ድርጊት አለ። ለምሳሌ ለህብረተሰቡ ሞራል ተቃራኒ የሆኑ ድርጊቶችን መፈጸም የሚል በወንጀል በህጋችን አለ።

ለህብረተሰቡ ሞራል ተቃራኒ የሆነ ድርጊትን መፈጸም ራሱ ወንጀል ነው። እንግዲህ በተከሳሾቹ ላይ ሁለተኛ ክስ ሆኖ ቀርቦባቸው ይሁን አይሁን ባናውቅም ቢያንስ ግን ሁለት ክስ ሊቀርብ ይገባል። 

የወንጀል ሕጉ መከላከል፣ ወላጅ ልጁን እንዳይደፍር የሚያስተምር፣ የሚያስጠነቅቅ ነው ዓላማው። ስለዚህ ቅጣቱ ዝቅ ሲል እድሜ ልክ ከፍ ሲል የሞት ፍርድ ቅጣት ነው የሚያሰጠው። ነገር ግን 17 ዓመት መሆኑ ተገቢነት የለውም።

የባለቤቱን እህት የደፈረውም ለህብረተሰቡ ሞራል ተቃራኒ የሆነ ድርጊት ፈጽሟል። ዝምድና በሁለት አይነት መንገድ ይፈጠራል በቤተሰብ ሕጉ አንድም በመወለድ አንድም በጋብቻ። 

በዚህ የመደፈር ወንጀል ጋብቻ አለ። ጋብቻ ካለ ደግሞ ዝምድና ተፈጥሯል። ዝምድና ከተፈጠረ ደግሞ በዘመዳሞች መካከል የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ብቻ ሳይሆን በማህበረሰቡ ገደቦች አሉ።

ነገር ግን ይህን የማህበረሰቡን ወግና ባሕል ጥሶ ተላልፎ አስገድዶ መድፈር በባለቤቱ እህት ላይ ከፈጸመ 14 ዓመት የሚለው ፍርድ ያንሳል። በ23 ዓመት ዝቅ ካለ ደግሞ 20 ዓመት መቀጣት ያስፈልገዋል።

ይህም በቂ ነው እያልኩ አይደለም። እድሜ ልክ እስራት ተገቢ ነው። ግን የሚሰጡት ውሳኔ የዘፈቀደ ነው። 

ዳኝነትን ዳኞቻችን እንደሚገነዘቡት ዳኝነት ስራ አይደለም። አገልግሎት ነው እንጂ። ለአገልግሎት የሚሆኑ ጥሩ ሰዎች ተመልምለው ተሹመው በፍርድ ቤት መቀመጥ አለባቸው።

ለሥራ ተብሎ ከሆነ የሚገቡት ሌላ የስራ መስክ መማር አለባቸው። ሰዎች ከስብዕናቸው፣ ከሚኖራቸው ተልዕኮና ጥሪ አንፃር ራሳቸውን መገምገም አለባቸው። ስለዚህ ከላይ የተነሱት ውኔዎች አስተማሪ አይደሉም ማለት ነው። ”

Q. መቼም ዳኞች በተቀመጠላቸው ሕግ መሠረት ነው ፍርድ የሚሰጡት። የቅጣት ውሳኔው ግን አስተማሪ አይደለም። ስለዚህ ችግሩ ያለው ከድንጋጌው አይደለም ? ሕጉ መሻሻል የለበትም?

የሕግ ባለሙያ ጥጋቡ ደሳለኝ ፦

“ የወንጀል ሕጉ ላይ መሻሻል የሚያስፈልጋቸው ነገሮች እየታዩ ነው። አንደኛ ተደራራቢ ወንጀለኞች እየተፈጸሙ ነው። ሁለተኛ ከእስከ (ከ15 ዓመት እስከ 25 ዓመት) የሚለው ስለሰፋ ወንጀለኞችን አላርም አላስተካክል እያለ ነው።

ስለዚህ ከ እስከ የተባለው ነገር ሰፊ ስለሆነ በሴቶችና ሕፃናት ላይ ያለውን ጥቃት ለመቀነስ መሻሻል አለበት ማለት ነው። 

የቅጣት መጠኑ ጠንከር ማለት አለበት። ለምሳሌ በእስራት ከሆነ 25 ዓመት ወይም ዕድሜ ልክ ከዚያም ሲያልፍ ደግሞ የሞት ቅጣት ተብሎ አንደዚህ አይነት ነገሮች በወንጀል ሕጉ መሻሻል አለባቸው
። ”

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

EBS TV

12 Jan, 14:45


#ተፈጸመ : የጉምቱው ፖለቲከኛና የምጣኔ ሃብት (የኢኮኖሚ) ሊቅ አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ስርዓተ ቀብር ተፈጸሟል።

ከስርዓተ ቀብራቸው ቀደም ብሎ በአድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሽ የአስክሬን ሽኝት ተደርጓል።

@tikvahethiopia

EBS TV

12 Jan, 14:45


#Ethiopia #Somalia

የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ዛሬ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።

ለአንድ ቀን ይፋዊ የስራ ጉብኝት ትላንት አዲስ አበባ የገቡት የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ዛሬ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።

ወደ ሀገራቸው ሲመለሱም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ቦሌ ኤርፖርት ተገኝተው ሸኝተዋቸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ " በይፋዊ ጉብኝታቸው ወቅት የሁለትዮሽ ግንኙነቶቻችንን ለማጠናከር ውጤታማ ውይይቶች አድርገናል " ብለዋል።

@tikvahethiopia

EBS TV

10 Jan, 18:05


" ልጆቻችን በሰላም መኖር እንዲችሉ፣ በጦርነት እየተሰቃዩ የሕመማቸውን ልክ መናገር የማይቻለን የኦሮሚያና የአማራ ክልል ነዋሪዎች ሰላምን እንዲያገኙ ጥሪ እናስተላልፋለን " - ቅዱስነታቸው

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክተው አባታዊ የሰላም ጥሪ አስተላለፉ።

ቅዱስነታቸው ፤ በሀገራችን በልዩ ልዩ አካባቢዎች ያሉ ጦርነቶች እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል።

" ልጆቻችን በሰላም መኖር እንዲችሉ፣ በጦርነት እየተሰቃዩ የሕመማቸውን ልክ መናገር የማይቻለን የኦሮሚያና የአማራ ክልል ነዋሪዎች ሰላምን እንዲያገኙ አባታዊ ጥሪ በድጋሚ እናስተላልፋለን " ብለዋል።

ቅዱስነታቸው ፤ በትግራይ ክልል ያለው የአስተዳዳሪዎች አለመግባባት በሕዝቡ ላይ ተጨማሪ ችግርና ጭንቀት እያመጣ መሆኑን ጠቁመዋል።

" በትሕትና መንፈስ እርስ በርስ መገናዘብ ተፈጥሮ ዕረፍት ያጣው ሕዝብ መረጋጋት እንዲችል ታደርጉ ዘንድ አደራችን የጠበቀ ነው " ብለዋል።

በተጨማሪም ቅዱስነታቸው በትግራይ ክልል ስለሚገኙ የሃይማኖት አባቶች ጉዳይ በአባታዊ የሰላም ጥሪ መልዕክታቸው አንስተዋል።

" መበደላችሁን እናውቃለን ፣ በኀዘናችሁ ሰዓት አብረን መቆም ባለመቻላችን ማዘናችሁም እርግጥና ተገቢ ነው " ያሉት ቅዱስነታቸው " ነገር ግን ሁሉም ነገር የሚካሰው በእርቅ ሲሆን እኛ የገፋነውን እርቅ ዓለም ሊቀበለው ስለማይችል፤ በእጃችንም የያዝነው መስቀለ ክርስቶስ የሰላም ዓርማ ነውና ልባችሁን ለሰላም፣ ለአንድነት እንድታዘጋጁ እንጠይቃለን " ብለዋል።

በሌላ በኩል ቅዱስነታቸው በመሬት መንቀጥቀጥ እየተጨነቁ ላሉ እና ስለተጎዱ ልጆቻቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።

" የመሬት መንቀጥቀጥ ባለበት አካባቢ እየተጨነቃችሁ ያላችሁ ልጆቻችን ረድኤተ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር እንዲሆን ቤተ ክርስቲያን በጸሎት የምታስባችሁ መሆኑን እየገለጽን መላው ኢትዮጵያውያን ለጉዳቱ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ለሚኖሩት ወገኖቻቸው አቅማቸው በፈቀደው መጠን ድጋፍ ያደርጉ ዘንድ አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን " ብለዋል።

(የቅዱስነታቸው ሙሉ መልዕክት ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia

EBS TV

10 Jan, 18:05


" በአዲስ አበባ ከተማ ' ቃሊቲ አካባቢ ' ባለ ሰፊ መጋዝን ውስጥ ከጎዳና ላይ የተነሱ በርካታ ሰዎች ይገኛሉ " - ኢመኮ

በጎዳና ላይ ያሉ ሰዎችን ያለፈቃዳቸው መያዝ እና ወደ ማቆያ ማእከላት ማስገባት የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን ስለሚያስከትል ሊቆም እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አሳሰበ።

ኮሚሽኑ " ከጎዳና ላይ ለሚነሱና ወደማቆያ ለሚገቡ ሰዎች ሰብአዊ መብቶችን ያማከለ ዘላቂ መፍትሔ መስጠት ያስፈልጋል "ም  ብሏል።

ኢሰመኮ ዛሬ በላከልን መግለጫ ፥ በሚያዝያ 27 ቀን 2015 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ በጎዳና ላይ ያሉ ሕፃናት በጅምላ ተይዘው የሚቆዩበትን ሁኔታ በተመለከተ እንዲሁም መስከረም 8 ቀን 2016 ዓ.ም. በሸገር ከተማ ገላን ክፍለ ከተማ ሲዳ አዋሽ ወረዳ በሚገኘው ማቆያ ማእከል ተይዘው የነበሩ ውሎና አዳራቸውን በጎዳና ያደረጉ ሰዎችን (በተለምዶ አጠራር ‘‘ ጎዳና ተዳዳሪዎች ’’ ተብለው የሚታወቁ) ሁኔታ አስመልክቶ ክትትል በማድረግ የተለዩ ክፍተቶችንና ምክረ ሐሳቦችን የያዘ መግለጫ ማውጣቱ አስታውሷል።

በታኅሣሥ ወር 2017 ዓ.ም. ባደረጋቸው ክትትሎች ደግሞ በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ “ ቃሊቲ አካባቢ ” ተብሎ በሚጠራው የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ አካባቢ ባለ ሰፊ መጋዝን ውስጥ ከጎዳና ላይ የተነሱ በርካታ ሰዎች መኖራቸውንና ይህ ሰዎችን የመያዝና ወደ ማቆያ ማእከል/ቦታ የማስገባት ድርጊት አሁንም መቀጠሉን አመልክቷል።

ወደ ማቆያው ከገቡት ሰዎች መካከል በማእከሉ ከመቆየት እና የእርሻ ሥራ ከመሥራት እንዲመርጡ በማድረግ፤ የእርሻ ሥራ ለመሥራት የመረጡ ሰዎች በተለያዩ አካባቢዎች ወደሚገኙ እርሻ ጣቢያዎች ተወስደው  እንዲሠሩ እንደሚደረግ ለመገንዘብ መቻሉን ጠቁሟል።

ይህም " የነጻነት መብታቸውን ጨምሮ ሌሎች መሠረታዊ የሰብአዊ መብቶቻቸውን የሚጥስ ነው " ብሏል።

በአዲስ አበባ ከተማ የሚከበሩ ሕዝባዊና ሃይማኖታዊ በዓላት ፣ የሚደረጉ ዓለም አቀፋዊና አህጉራዊ ጉባኤዎች እንዲሁም ከሌሎች ተመሳሳይ ኹነቶች ጋር በተያያዘ ውሎና አዳራቸውን በጎዳና ላይ ያደረጉ ሰዎችን በኃይል በማንሳት በአንድ ስፍራ እንዲቆዩ የማድረግ አሠራር እንዲቆም ፤ ወደመጡባቸው አካባቢዎች የመመለስ እና የመልሶ ማቋቋም ሥራዎች ሰብአዊ መብቶቻቸውን ባከበረ መልኩ ማከናወን እንደሚገባ እና ችግሩ ሁሉ አቀፍ የፖሊሲ ምላሽ የሚያስፈልገው መሆኑን በተለያዩ ጊዜያት በተካሄዱ የኢሰመኮ ክትትሎች መጠቆሙን አስታውሷል።

ኢሰመኮ ለችግሩ ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር  ውትወታ እያደረገ መሆኑን ጠቁሟል።

ጎን ለጎን የነጻነት መብትን ከማክበር እና ከማስከበር አኳያ እንዲሁም በጊዜያዊ ማቆያ ማእከሉ ከንጽሕና እና ከጤና አጠባበቅ ጋር በተያያዘ በሰዎች ሕይወትና ጤና ላይ አደጋ የሚጥሉ ሁኔታዎች እንዳይፈጠሩ ከአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ እንዲሁም ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ጋር ውይይቶችን በማድረግ ጉዳዩን በመከታተል ላይ እንደሆነ በላከል መግለጫ ገልጿል።


#EHRC #Ethiopia

@tikvahethiopia

EBS TV

10 Jan, 17:05


" ከ260 በላይ ቤተሰቦች ጦም ለማደርና ለለልመና ለመውጣት ይገደዳሉ " - ነዋሪዎች

በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ፤ በዋድላ ወረዳ በ11 ቀበሌዎች በተለያዩ ቀናት የሰብል ክምር ላይ ከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ መድረሱ ተሰምቷል።

" ምክንያቱ አልታወቀም " በተባለው የእሳት ቃጠሎ የ154 አርሶ አደሮች እህል ሰብል ክምር መቃጠሉን የዋድላ ኮሚኒኬሽን ገልጿል።

በ03 ቤተሆር ቀበሌ ቀጭኔ ጎጥ ጥር 1/2017 ዓ/ም በደረሰው ቃጠሎ ጉዳት የደረሰባቸው አርሶ አደሮች የቃጠሎው መነሻ በውል አለመታወቁን ገልፀው ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን አስረድተዋል፡፡

በዚህ ቀበሌ ብቻ የ52 አርሶ አደሮች የመህር ሰብል ክምር የተቃጠለ ሲሆን የአንዳንዶቹ ከዚህ ከተቃጠለው ሰብል ውጭ ሌላ ምንም ሰብል/አዝመራ እንደሌላቸው ገልፀዋል፡፡

በዚህ ቀበሌ ብቻ የ52 አርሶ አደሮች የሰብል ክምር ሙሉ በሙሉ ሲቃጠል በቤተሰብ ደረጃም ከ260 በላይ የቤተሰብ አባላት ጦም ለማደርና ለለልመና ለመውጣት እንደሚገደዱ የአካባቢው የህብረተሰብ ክፍሎች ተናግረዋል።

የዋድላ ወረዳ ቅድመ ማስጠንቀቂያ ቡድን መሪ አቶ ምትኩ ሞላ ምን አሉ ?

" በወረዳው በተለያዩ ቀበሌዎች የእሳት ቃጠሎ ተከስቷል።

እስካሁን ባለው መረጃ 770 የሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የጉዳቱ ሰለባ ሆነዋል " ብለዋል።

የዋድላ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ሙሉየ ረታ ምን አሉ ?

" እንደ ወረዳ በ11 ቀበለሌዎች በ152 ክምር ላይ ቃጠሎ የደረሰ ሲሆን 154 አርሶ አደሮች የጉዳቱ አካል ሁናዋል።

የደረሰው ውድመት በኩንታል 4 ሺ 560 ሲሆን ከ32 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት ደርሷል።

አሁንም ቢሆን አርሶ አደራችን የመውቂያ ማሽን ይምጣልን ጥያቄ እያቀረቡ ስለሆነ ማሽኑን መንግስት ቢያቀርብልን አርሶ አደራችን ተጠቃሚ እናደርጋለን።

አሁን ላይ በወረዳችን የደረሰው ጉዳት ከፍተኛ ስለሆነና ወረዳው ይህን የተጎዳ የህብረሰብ ክፍል መረዳት ስለማይችል መረጃውን ለረጅ ድርጅቶች በማጋራትና የምትችሉትን ሁሉ በማገዝ የሰብዓዊነታችሁን ሚና እንድተወጡ " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከዋድላ ወረዳ ኮሚኒኬሽን ነው ያገኘው።

@tikvahethiopia

EBS TV

10 Jan, 17:05


" የቁስ አካላቱ ሞያሌ ላይ አልወደቁም " - ነዋሪዎች

በሰማይ ላይ እየተቀጣጠሉ በከፍተኛ ፍጥነት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የቁስ አካላት ስብስብ  ነገር ሞያሌ ላይ አለመዉደቁን ነዋሪዎች ገለጹ።

ትላንት ምሽት በደቡባዊ የሀገራችን ክፍሎች ሰማይ ላይ ከተለመዱት ተወርዋሪ ኮከቦች በተለየ መልኩ በመጠን የገዘፈና በዘገምተኛ አኳሃን ሲጓዝ እንደነበር የተገለጸው ብርሃናማ የተቀጣጠሉ ቁስ አካላት " ሞያሌ አከባቢ ወድቋል " እየተባለ በማህበራዊ ሚዲያ ምንጫቸው ያልተረጋገጠ መረጃዎች ሲሰራጩ ነበር።

ዛሬ ማለዳ ጀምሮ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሞያሌ ኢትዮጵያ እና ጋምቦ አካባቢዎች ባደረገው ማጣራት ብርሃናማዉ አካል በተመሳሳይ መልኩ በሞያሌ ሰማይ ላይ ወደ ሶማሊያና ምስራቃዊ ኬንያ አቅጣጫ ማለፉንና በአከባቢው አለመዉደቁን ለማወቅ ችሏል።

በሞያሌ ጋምቦ የሚገኘው የመረጃ ምንጫችን ስለጉዳዩ በሰጠው ቃል " በሰሞኑ የመሬት መንቀጥቀጥ አፋር አከባቢ መደጋገሙን ስንሰማ ስለነበር በዚህም ክስተት ሰዉ ሁሉ ደንግጦ ነበር፤ ነገሩ በሞያሌ ሰማይ ላይ ሲያልፍ አይቻለሁ " ብሏል።

አክሎ " ሪችት ይመስላል-ሞያሌ ወደቀ የሚል ነገር ሰምቼ እስከ ማርሳቤትና ናይሮቢ ድረስ ደዋዉዬ አጣራሁ ያሉኝ ነገሩ ናይሮቢ አልደረሰም፤ ነገር ግን የማርሳቤት ሰዎች ሰማይ ላይ አይተነዉ ኡጂሩ በተባለች የኬንያ ድንበር አድርጎ ወደ ሶማሊያ መሄዱን ነግረዉኛል " ሲል ገልጿል።

አንዳንድ ጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡ የስነ ከዋክብትና ስፔስ ሳይንስ አጥኝዎች ይኸው ተቀጣጣይ ነገር " የጠፈር ፍስራሾሽ " ሊሆኑ ይችላሉ ብለዋል።

በኢትዮጵያም ይሁን በኬንያ ተቋማት በኩል ቁርጥ ያለ ነገር ባይነገርም በኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ በኩል ጉዳይን በዝርዝር ለማሳወቅና ለማብራራት ስራዎች እየተሰሩ ነው።

ባሳለፍነው የፈረንጆች ዓመት ማገባደጃ በኬኒያ ሙኩኩ በተባለ ገጠራማ መንደር 500 ኪ.ግ የሚመዝን ቀለበታማ የጋለ ብረት  መውደቁ የተነገረ  ሲሆን የሀገሪቱ ስፔስ ኤጀንሲ ብረቱ በስፔስ ላይ ከሚገኙ ሮኬቶች ተገንጥሎ የወደቀ ሊሆን እንደሚችል ማስታወቁ አይዘነጋም።

#TikvahEthiopiaFamily #Moyalle #Gambo

@tikvahethiopia

EBS TV

10 Jan, 17:05


" የሟሟቱ ሁኔታ በሚመለከታቸው አካላት እየተጣራ ይገኛል " - አክሱም ዩኒቨርሲቲ

በአክሱም ዩኒቨርስቲ የሽረ ካምፓስ ተማሪ ህይወቱ እንዳለፈ ዩኒቨርስቲው አስታወቀ።

" ተማሪያችን ካሕሱ ሃይሉ በእፅዋት ሳይንስ የትምህርት ክፍል የአንደኛ ዲግሪ የሦስተኛ ዓመት ተማሪ ነበር ብሏል " ዩኒቨርስቲው።

ዩኒቨርሲቲው የተማሪው ሕይወት ያለፈው ከካምፓስ ውጪ ሌሊት ባጋጠመ ድንገተኛ ግጭት እንደሆነ ጠቁሟል።

ግጭቱ በምን ምክንያት እንደነበረ ፣ ከምን ጋር እንደሆነ በዝርዝር ያለው ነገር የለም።

የተማሪ ካሕሱ ሃይሉ ሃደራ የሟሟት ሁኔታ በሚመለከታቸው አካላት እየተጣራ ይገኛል ያለው ተቋሙ ውጤቱ በሚመለከታቸው አካላት ይፋ እንደሚደረግ ገልጿል።

@tikvahethiopia

EBS TV

10 Jan, 17:05


በኢትዮጵያ በይፋ የአክሲዮን ግብይት ተጀመረ።

የኢትዮጵያ የሰነድ ሙዓለ ንዋይ ገበያ ዛሬ ዓርብ የአክሲዮን ሽያጭና ግዢ ግብይቱን በይፋ መጀመሩን አስታውቋል።

የአክሲዮን ገበያ ሥራውን በይፋ ያስጀመሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) ፤ " በጉጉት ሲጠበቅ የቆየው የሰነድ ሙዓለ ንዋይ ግብይት በዛሬው ዕለት ጥር 2 ቀን 2017 ዓ.ም የመጀመሪያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ደወል ደውለናል " ብለዋል።

የሰነድ ሙዓለ ንዋይ ገበያው ዋና ዳይሬክተር ጥላሁን ካሳሁን በቀጣዮቹ ዓመታት ውስጥ 50 ያህል ኩባንያዎች በዚህ ገበያ ላይ የአክሲዮን ድርሻዎችን ለግብይት እንደሚያቀርቡ ገልጸዋል።

በተለምዶ ክፍት ገበያ በመባል የሚታወቀው የሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ የተማከለ የፋይናንሺያል ገበያን የሚያመለክት ሲሆን የተዘረዘሩ ኩባንያዎችን የዋስትና ሰነዶች፣ኮሞዲቲዎች ጨምሮ በአክሲዮን ሻጮች እና ገዥዎች መካከል የሚገዙበት እና የሚሸጡበት ማዕከል መሆኑ ይታወቃል።

የመረጃው ባለቤት ካፒታል ጋዜጣ ነው።

@tikvahethiopia

EBS TV

10 Jan, 11:36


#Kenya

ትላንት ምሽት በኢትዮጵያ ደቡብ እና ደቡብ ምዕራብ ክፍሎች በሰማይ ላይ እየተቀጣጠሉ በከፍተኛ ፍጥነት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ብርሃን ያላቸው የቁስ አካላት ስብስብ በኬንያ ሰሜናዊ ምስራቅ ክፍልም ታይተዋል።

እነዚህ ቁስ አካላት በኬንያ ቱርካና፣ ማርሳቢት፣ ሞያሌ አካባቢ መታየታቸውን የኬንያ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ገልጸዋል።

ምንም እንኳን ቁስ አካላቱ " የጠፈር ፍርስራሾች ናቸው በገጠሪቱ የሀገሪቱ ክፍል (ኬንያ - ኢትዮጵያ ድንበር) ወድቀዋል ፤ ሲወድቁም ከፍተኛ ድምጽ ተሰምቷል ፤ ከሚቃጠል ነገር ጭስም ታይቷል ሽታም ነበረው " እያሉ ብዙ ተከታይ ያላቸው የኬንያ ፀሀፊዎች X ላይ ቢፅፉም የኬንያ ስፔስ ኤጀንሲ በይፋ የሰጠው ማረጋገጫ የለም።

እስካሁን የኬንያ ስፔስ ኤጀንሲ ፥ ቁስ አካላቱ ኬንያ ውስጥ ስለመውደቃቸው ማረጋገጫ አልሰጠም ስለ ጉዳዩ መግለጫም አላወዋጣም።

ከሰሞኑን በኬንያ ማኩኒ ካውንቲ ሙኩኩ በተባለች ትንሽዬ መንደር ከሰማይ ወርዷል የተባለ 2 ነጥብ 5 ሜትር ስፋት ያለውና 500 ኪሎግራም ክብደት ያለው ቁስ በርካቶችን አስደንግጦ ነበር።

የኬንያ የስፔስ ኤጀንሲ ሰዎች ቁሱ ወደወደቀበት ስፍ በማቅናት ምንነቱን ለማጥናት የሞከሩ ሲሆን ወደ ህዋ የመጠቀ ሮኬት ቁርጥራጭ ሊሆን እንደሚችል ገምተዋል።

ቀለበት ቅርጹ ከሮኬት ከተነጠለ በኋላ የሚፈረካከስ እንደነበር የተገለጸ ሲሆን የየትኛው ሀገር ወይም ኩባንያ ንብረት እንደሆነ የማጣራት ስራ እየተሰራ ነው። እስካሁን መደምደሚያ ላይ አልተደረሰም።

ተቋሙ " እንደዚህ አይነት ቁሶች (በኬንያ የወደቀው ቀለበት) ወደ ምድር ምህዋር ሲመለሱ ራሳቸውን እንዲያቃጥሉ አልያም ወደ ውቅያኖሶች እንዲገቡ ተደርገው የሚሰሩ ናቸው " ሲል ነው ያብራራው።

እንደ ኒውዮርክ ታይምስ መረጃ ከሆነ ባለፉት ስድስት አስርት አመታት በሀገራት መካከል የሚደረግ የህዋ ላይ ፉክክር መጠናከር ከሰማይ ላይ የሚወድቁ ቁሶች እንዲበራከቱ አድርጓል።

ባለፈው አመት ባወጣ የአውሮፓ የጠፈር ኤጀንሲ መረጃ በዝቅተኛ የምድር ምህዋር ውስጥ ከ14 ሺህ ቶን በላይ ቁሶች እንዳሉ ተገምቷል ፤ ከዚህ ውስጥም ከሲሶ በላዩ ለህዋ ምርምር የማያስፈልጉ ቁሳቁሶች ናቸው።

እንደ መረጀው ፥ በየአመቱ ከ110 በላይ የሳተላይት ማምጠቅ ሙከራዎች ይደረጋሉ ፤ በጥቂቱ 10 ሳተላይቶች እና ሌሎች የምርምር ቁሳቁሶች ወደ ትንንሽ ስብርባሪዎች ይቀየራሉ። ይህም ከህዋ ላይ ወደ መሬት የሚወድቁ ነገሮች እንዲበራከቱ አድርጓል።

መረጃው ከኬንያ የማህበራዊ ትስስር መድረኮች፣ ከኒውዮርክ ታይምስ፣ ከቢቢሲ፣ ከአል አይን ፣ ከኬንያ ስፔስ ኤጀንሲ ነው የተገኘው።

@tikvahethiopia

EBS TV

10 Jan, 11:36


#telebirr

🌟 10% የገንዘብ ስጦታ ከተጨማሪ የዕድል ሽልማቶች ጋር!!

የገናን በዓል አስመልክቶ ከባህርማዶ በቴሌብር ሬሚት እና በአጋሮቻችን በኩል የተላከልዎን ዓለም አቀፍ ሐዋላ በቴሌብር ሲቀበሉ 10% የገንዘብ ስጦታ ያገኛሉ፡፡

💁‍♂️ በተጨማሪም 6ሺህ ብር እና ከዛ በላይ ሲቀበሉ አጓጊ ለሆነው ልዩ የዕድል ጨዋታ ብቁ ይሆናሉ!

1️⃣5️⃣ የቤት ዕቃዎች - እያንዳንዳቸው 100,000 ብር
2️⃣0️⃣ የበግ ስጦታዎች - እያንዳንዳቸው 15,000 ብር
5️⃣0️⃣ የበዓል አስቤዛ - እያንዳንዳቸው 10,000 ብር
3️⃣0️⃣0️⃣ የኪስ ገንዘብ - እያንዳንዳቸው 5,000 ብር
🌍🎁  እንዲሁም በርካታ የሞባይል ዳታ ጥቅሎች

የሚቀበሉት የገንዘብ መጠን ሲጨምር የጨዋታ ዕድልዎም ይጨምራል!
🗓 እስከ ጥር 16 ቀን 2017 ዓ.ም ብቻ!

ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!

#Ethiotelecom #telebirrSupperApp #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #RealizingDigitalEthiopia

EBS TV

02 Jan, 18:32


🔈 #የነዋሪዎችድምጽ

⚫️ " ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ነው ያለብን መኖር አልቻልንም በሳምንት ሶስት እና አራት ቀን መብራት የለንም " - ቅሬታ አቅራቢ

🔴 " ከክረምት በፊት ችግሩ ይቀረፋል ታገሱ " - የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት


በአዲስ አበባ ከተማ ሰሚት ፍርድ ቤት፣ ሰሚት ሳፋሪ፣ ሰሚት ፔፕሲ ፋብሪካ ፣ ፍየል ቤት ፣ ወጂ ሰፈር፣ ሰንራይዝ ሪል ስቴት፣ ፊሊንት ስቶን ሆምስ እና ጎሮ ሚካኤል አካባቢ የሚኖሩ ነዋሪዎች በአካባቢው በተደጋጋሚ እየተከሰተ ያለው የሃይል መቆራረጥ ከፍተኛ የሆነ ምሬት ውስጥ እንደከተታቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

በአካባቢው የሚገኙ በተለይም የፍሊንት ስቶን ትዊን የጋራ መኖሪያ መንደር ነዋሪዎች " ከህዳር 02/03/17 ዓ/ም ጀምሮ የመብራት አገልግሎት ቀንም ለሊትም ሳናገኝ በችግር ላይ እንገኛለን " ሲሉ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ምስራቅ አዲስ አበባ ሪጅን በደብዳቤ ጭምር ቢያሳውቁም " መፍትሄ የሚሰጠን አጥተናል " ብለዋል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በበኩሉ በአካባቢው ለሃይል መቆራረጥ መንስኤ የሆነው በመሬት ውስጥ በሚቀበሩ የሃይል መስመሮች ላይ የሚያጋጥም የመሰረት ልማት ጉዳት እና ስርቆት ምክንያት መሆኑን በመግለጽ ደንበኞቹ የሃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ በትዕግስት እንዲጠብቁ የሚጠይቅ ጽሁፍ በማህበራዊ ትስስር ገጹ ላይ አስፍሯል።

ነዋሪዎች በዝርዝር ምን አሉ ?

" ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ነው ያለብን መኖር አልቻልንም በሳምንት ሶስት እና አራት ቀን መብራት የለንም መብራት አይመጣም ከመጣም ለሊት ነው ከዛ ተመልሶ ይጠፋል መኖር ከብዶናል።

ህመምተኞች አሉ ፤ ፍሪጅ የሚያስፈልጋቸው ሰዎች አሉ ከዚህም በላይ በዚህ ኑሮ ውድነት ምግብ ለመድፋት ተገደናል።

ከህዳር 18 እስከ ታህሳስ 9 ባለው ጊዜ አምስት ጊዜ በተደጋጋሚ በመንገድ ስራ ምክንያት በመሬት ውስጥ ያለ መስመር በኤክስካቫተር እየተመታ ሃይል ተቋርጧል።

መፈጠር አልነበረበትም ቅድመ መከላከል ስራዎች ሊሰሩ ይገባ ነበር ከሆነ በኋላ ግን በተደጋጋሚ መፈጠር አልነበረበትም ተጠያቂነትም ሊኖር ይገባ ነበር።

ከታህሳስ 10 በኋላ ግን አንድ ጊዜ ሲመታ ከ18 ሰዓት እስከ 3 ቀን መብራት ይጠፋ ጀምሯል ከዛ በኋላ መቆራረጡ በከፍተኛ ሁኔታ ባሰ በ24 ሰዓት ጊዜ ውስጥ ለ25 ደቂቃ ብቻ ሃይል የምናገኝበት ጊዜ ሁሉ አለ።

ትልቁ ቆየ ከተባለ 4 ሰዓት ነው ይህም ከእኩለ ለሊት እስከ ንጋት ባለው ጊዜ ውስጥ ነው ሰው ከተኛ በኋላ ለምንም አገልግሎት መዋል በማይችልበት ሰዓት ነው ከሚመጣው።

የመልሶ ግንባታ ስራ ለማከናወን በሚል በወጣው ዝርዝር ውስጥ አካባቢያችን የሃይል አቅርቦት እንደሚቋረጥ የሚገልጸው ከ 3 ሰዓት እስከ 10 ሰዓት ቢሆንም እኛ ከንጋት ጀምሮ እስከ እኩለ ለሊት መብራት አናገኝም።

ችግሩን ማስቆም ሲችሉ ማህበረሰቡ በመሃል እየተቀጣ ነው ልጆች ከትምህርት ቤት መጥተው ማጥናት አልቻሉም ፣በተደጋጋሚ በመጥፋቱም ምክንያት ነዋሪው ለከፍተኛ የኢኮኖሚ ጫና እየተዳረገ ነው " ብለዋል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢ/ር ሺፈራው ተሊላ ምን ምላሽ ሰጡ ?

" ቀን ቀን የፕሮጀክት ስራ አለ በስራው ምክንያት ይቋረጣል ማታ ማታ ይለቁላቸዋል ሙሉ ቀን የማይበራላቸው ብልሽት ሲኖር ነው እንደዛ የሚሆነው ሁሌ አይደለም።

ከሰሚት ጀምሮ እስከ ወረገኑ ድረስ እዛ መስመር ላይ መሰረተ ልማት ስራ እየተሰራ ነው ስራዎች በቅንጅት ነው የሚሰሩት አንዳንዴ ብዙ ስራ ስለሆነ እየተሰራ ያለው ከአቅም በላይ በሆኑ ምክንያቶች ችግሮች ይከሰታሉ።

ለዘለቄታው ለመገልገያ (Utility) የሚሆን ኮሪደር አብሮ እየተሰራ ነው ለተወሰነ ጊዜ ነው የተጠቀሰው አይነት ችግር የሚኖረው በቀጣይ በጣም አስተማማኝ የሆነ መሰረተ ልማት እየተሰራ ነው።

መንገድ በሚሰራበት ጊዜ ከእግረኛና ከአስፋልት መንገድ ጎን የውሃ ፣ የቴሌኮም እና የኤሌክትሪክ መስመር (Utility Corridor) አብሮ እየተገነባ ነው።

ቀደም ሲል የነበረው አካሄድ ብልሽት በሚኖርበት ጊዜ አስባልት ተቆፍሮ ነበር የሚሰራው በአሁኑ አሰራር ደረጃውን በጠበቀ መንገድ ብልሽት ሲኖር መቆፈር እና ማፍረስ ሳያስፈልግ ገብቶ ለመስራት ያስችላል ፣ የመቀየር እና የማሻሻል ስራ ሲያስፈልግ ማሟላት የሚችል የአቅም ማሳደግ ስራ እየተሰራ ነው።

ይህ አይነት ቅንጅት ባለመኖሩ ብዙ ችግሮች ሲከሰቱ ነበር አሁንም የምናየው ችግር የተከሰተው ቀደም ሲል ይህ አይነት ቅንጅት እና የUtility corridor ባለመኖሩ ምክንያት የተከሰተ ነው ።

ይሄንን ችግር ለአንዴ እና ለመጨረሻ ችግሩን ለመፍታት እና ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት እየሰራን ነው።

የተወሰነ ጊዜ መታገስ ነው ለዘመናት የሚያገለግል ስራ ነው የሚሰራው ስራው እስከ 6 ወር ጊዜ ውስጥ የሚጠናቀቅ ነው ከክረምቱ በፊት ያልቃል" ብለዋል።

እስከዛ አሁን ባሉበት አይነት የመብራት ችግር ውስጥ ይቆያሉ ወይ ? ስንል ለዋና ስራ አስፈጻሚው ጥያቄ አንስተናል።

ኢ/ር ሺፈራው ተሊላ

" ሲሪየስ በሆነ ነገር ውስጥ ላይቆዩ ይችላሉ ብዙ ነገር እየተሻሻለ ነው የሚሄደው ብዙ ቁፋሮ አለ ቁፋሮ ካለቀም በኋላ መሰረተ ልማቱ ቦታውን ይይዛል ለስራ ሲባል ሃይል መቆራረጥ ይኖራል ነገር ግን እየተሻሻለ ይሄዳል።

ከመገናኛ ሰሚትም ሲሰራ እንደዚህ አይነት ችግሮች ነበሩ አሁን CMC አካባቢ እንደዚህ አይነት ችግር የለም ከዚህ በኋላ እንደዚህ አይነት ችግሮች አይኖሩም የሁሉም ስራ ያልቃል ከክረምት በፊት ችግሩ ይቀረፋል ታገሱ " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ችግሩን በማቃለል እስከዛ በተሻለ መንገድ ሃይል የሚያገኙበት እድል ይኖራል ወይ ? የሚል ጥያቄም ያነሳንላቸው ሲሆን በምላሻቸውም " እንደዛ እናደርጋለን ከባድ ችግር ስለነበር አንድ ጊዜ ነው እስካሁን ለቀናት በሚባል ደረጃ የተቋረጠው ከዚህ በኋላ እንደዚህ አይነት ነገር እንዳይኖር ጥረት እናደርጋለን " ሲሉ መልሰዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

EBS TV

02 Jan, 17:15


#AAU

ከ600 በላይ ተሳታፊዎች የሚኖሩት የምልክት ቋንቋ ጉባዔ በቅርቡ በአዲስ አበባ ይካሄዳል።

የራሷን የምልክት ቋንቋ የምትጠቀመው ኢትዮጵያ 15ኛውን የምልክት ቋንቋ ዓለም-አቀፍ የምርምር ጉባዔን (TISLR) ከመጪው ጥር 6 እስከ 9 በአዲስ አበባ ታስተናግዳለች።

ከዚህ ቀደም በነበሩት ጉባኤዎች ተሳታፊ የነበረው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተወዳድሮ የዘንድሮውን ጉባዔ እንዲያዘገጋጅ መመረጡን ተከትሎ ከሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ጉባዔውን አዘጋጅቷል።

ይህ በየ 3 ዓመቱ የሚካሄደው የምርምር ጉባኤ በአፍሪካ ሲዘጋጅ የመጀመሪያው መሆኑንና ዓለም አቀፍ የዘርፉ ምሁራንን ጨምሮ ከ600 በላይ ተሳታፊዎች የሚሳተፉበት እንደሚሆን ዛሬ በነበረው የቅድመ ጉባኤ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተገልጿል።

ኢትዮጵያ የምልከት ቋንቋን የብሔራዊ ቋንቋ እንዲሆን ከማድረግ አንጻር ምን እየሰራች ትገኛለች ?

የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚ/ሚኒስትር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ ለዚህ ጥያቄ ምላሽ ሲሰጡ "የቋንቋ ፖሊሲው ለምልክት ቋንቋ እውቅና ይሰጣል ይህንን ሥራ ማድነቅ ያስፈልጋል፤ የብሔራዊ ቋንቋ ለማድረግ ግን ሰፊ ጥናቶች መስራት ይጠበቅብናል።" ብለዋል።

ይሄም ጉባዔም የምልክት ቋንቋዎችን እንደ ህጋዊና አስፈላጊ ቋንቋዎች እውቅና ለመስጠት የሚደረገውን ጥረት የሚደግፍ ይሆናል ነው ያሉት።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕረዚዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በመግለጫው ወቅት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የምልክት ቋንቋ በማስተማር 15 ዓመታትን ማስቆጠሩን ጠቅሰው በጉባዔው በኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታዎች ላይ የተሰሩ ሥራዎች የሚቀርቡበት ነው ብለዋል።

አክለውም፥ የዩኒቨርስቲው ተመራማሪዎች፣ መምህራን፤ ተማሪዎች ተሳታፊ እንዲሆኑ እና ከዓለም አቀፍ አቻዎቻቸው እንዲማማሩ እድል ይሰጣል ያሉት ዶ/ር ሳሙኤል "የምልክት ቋንቋ እውቅና እንዲኖረው የበኩላችንን አስተዋጽኦ የምናበረክትበት ይሆናል" ሲሉ ገልጸዋል።

በዚህ ጉባዔ ኢትዮጵያ ምን የምታቀርበው ነገር አዘጋጅታለች ?

ዶ/ር ኤርጎጌ በዚህ ጉባኤ ከሚቀርቡ የጥናትና ምርምር ሥራዎች በተጨማሪ የተሰሩ ሥራዎችን እንድናቀርብ እድል ይሰጠናል ያሉ ሲሆን፤ በተለይም የመጨረሻ የዝግጅት ምዕራፍ ላይ የሚገኘውን የአካል ጉዳተኞች መብቶች የተጠቃለለ አዋጅን ጠቅሰዋል።

የአካል ጉዳተኞች መብቶች የተጠቃለለ አዋጅ ምን ይዟል?

በዚህ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጡን የጠየቅናቸው የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የአካል ጉዳተኞች ጉዳይ ዳይሬክተር አቶ አሳልፈው አመዲን፥ አዋጁ ተበታትኖ የነበሩትን መብቶች ወደ አንድ በማሰባሰብ በተለይም ተጠያቂነትን የሚያሰፍን እንደሆነ ገልጸውልናል።

ከ90 ያላነሱ አንቀጾችን ይዟል በተባለው በዚህ የተጠቃለለ አዋጅ፥ የምልክት ቋንቋን በተመለከተ መጠቀሱን ያነሱት ዳይሬክተሩ፥ "የምልክት ቋንቋ እንደ አንድ ኢትዮጵያ ውስጥ እውቅና እንደተሰጣቸው ቋንቋዎች ታስቦ ተግባራዊ መደረግ አለበት የሚል ተካቶበታል" ብለዋል።

የምልክት ቋንቋን መጠቀም በኢትዮጵያ አስገዳጅ ነው ?

ይህንን ጥያቄ ያቀረብንላቸው የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የማኅበራዊ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሁሪያ አሊ "በተለይም የመስማት የተሳናቸው ተሳታፊዎች ባሉባቸው መድረኮች እንዲሁም በሚዲያ አዋጁ በግልጽ እንደተቀመጠው የመገናኛ ብዙኃን የምልክት ቋንቋ የመጠቀም ግዴታ ተጥሎባቸዋል" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

የጉባዔው አዘጋጆች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉባዔው መሳተፍ የሚፈልጉ በዚህ http://tislrethiopia.org/registration/ ሊንክ ተጨማሪ መረጃዎችን መውሰድና መመዝገብ እንደሚችሉ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopia
#SignLanguage
#EthSL

@tikvahethiopia

EBS TV

02 Jan, 17:15


“የካሳዋን ጉዳይ አሁንም እየጠበኳት ነው። ግን የለችም” - ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ስላሴ

የሻሸመኔ ኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት ከዚህ ቀደም በታጣቂዎች ከፍተኛ ውድመት እንደደረሰበት የሚታወቅ ሲሆን ፣ አፍርሰው እየሰሩ እንደነበር ሻለቃ ኃይሌ ገ/ስላሴ ገልጸው ነበር።

ከ10 ወራት በፊት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ ሙሉውን አፍርሰን እየሰራን ነው። ከመንግስት ምንም አይነት ማካካሻ አልተሰጠኝም ” ነበር ያሉት።

“ እኔ አላቃጠልኩትም። መንግስት እንደ መንግስት መወጣት ነበረበት ” ብለው፣ “  እኛ ለብዙ አመታት እንግዲህ በኢንቨስትመንት ተሰማርተን እየሰራን ነው ” ማለታቸው አይዘነጋም።

አሁንስ ከመንግሰት ካሳ ተከፈላቸው ?

የሻሸመኔው ሆቴልና ሪዞርት ለደረሰው ውድመት መንግስት ከሳ እንዳልከፈለዎት ገልጸው ነበር፣ ተከፈለዎት ? ተብሎ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬ ጥያቄ ያቀረበላቸው ሻለቃ ኃይሌ አሁንም ካሳ እንዳልተከፈላቸው ተናግረዋል።

“ የካሳዋን ጉዳይ እየጠበኳት ነው ግን የለችም። እሷን ነገር እብቃለሁ ” ነው ያሉት።

የውጪ ኢንቨስተሮች እንዲመጡ እንዲህ አይነት አደጋዎች ሲደርሱ ካሳ ቢከፈል መልካም መሆኑን አስረድተው፣ “ ዞሮ ዞሮ ግን አልሆነም። አልተቀበልኩም ” ብለዋል።

ሆቴሉን ከባለሦስት ወደ ባለአራት ኮከብ አድርገው እየሰሩ መሆኑን ገልጸው፣ “ ህንፃ እያፈረሱ መስሪት ሁለት ሥራ ነው አንደኛ ማፍረስ፣ ሁለተኛ ደግሞ መገንባት አለ ” ሲሉ ተናግረዋል።

“ በአጠቃላይ ግን ስለሆቴልና ሪዞርት ሲወራ እከሌ ሆቴል ከፈተ፣ እከሌ ሪዞርት ከፈተ የሚለው ምንም ፋይዳ የለውም። ማነው የሚተባበረው ? ማነው አብሮት ያለው? ከአዲስ አበባ ከ300 ኪሎ ሜትር ሲመጣ ሴፍ ነው ወይ? የሚሉት ምላሽ የሚፈልጉ ናቸው ” ሲሉም አስገንዝበዋል።

በተያያዘ ዜና በአማራ ክልል በመንግስትና በፋኖ ታጣቂዎች እየተካሄደ ያለውን የተኩስ ልውውጥ ተከትሎ በጎንደር ከተማ ያለው ሆቴላቸው ገቢው እየተቀዛቀዘ መሆኑንም ከዚህ ቀደም መግለጻቸው ይታወሳል።

የጎንደሩ ሆቴል ገቢው በምን ያህል ቀንሷል ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ላቀረበላቸው ጥያቄ ሻለቃ ኃይሌ፣ “ አለ እንዴ ለመሆኑ ቢዝነሱ? 56፣ 57 ሩም ተይዞ 5 ሰዎች ስላሳደርክ ምንድን ነው ገቢው? ” የሚል ጥያቄ አዘል ምላሽ ሰጥተውም ነበር።

አሁንስ የጎንደሩ ሆቴል ገቢ በምን ደረጃ ላይ ይገኛል? በሚል ዛሬ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ ደግሞ፣ “ በጎንደሩ ሆቴል የሚፈለገውን ያህል እየተሰራ አይደለም ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

የቀጣይ የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርቶች መዳረሻ የት እንደሚሆን በዛሬ የጅማ ሪዞርት ምረቃ መርሀ ግብር ላይ ማብራሪያ የሰጡት ሻለቃ ኃይሌ፣ የሻሸመኔውንና የደብረ ብርሃኑን ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፣ “ ድሬዳዋና ሀረርም ቀጣይ መዳረሻችን ይሆናል” ሲሉ ጠቁመዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

EBS TV

02 Jan, 11:29


#Earthquake

ዛሬ በሬክተር ስኬል 5.1 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ እንደነበር የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ገልጿል።

የመሬት መንቀጥቀጡ ከአዋሽ በሰሜን 36 ኪ/ሜ በኩል ነው የተመዝገበው።

የመሬት መንቀጥቀጡ ንዝረት አዲስ አበባ እና ቦታዎችም የተሰማ ሲሆን በተለይ በአዲስ አበባ ንዝረቱ በደንብ ይሰማ ነበር።

አንድ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ፥ " የመሬት ንዝረት እየተሰማ ነው ፤ ያለሁት ቦሌ አካባቢ መኪና ውስጥ ነው ፤ በደቂቃዎች ልዩነት ሁለቴ አጋጥሟል " ሲሉ ቃላቸውን ሰጥተዋል።

ሌላ አንድ የቤተሰባችን አባል  " መኪናዬ ውስጥ ሆኜ ትንሽ ንቅንቅ ስል ተሰምቶኛል ወደ አያት አካባቢ ቆሜ ባለሁበት " ሲል ገልጿል።

ከሰሞኑን የተለያየ መጠን ያላቸው ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቶች እየተመዘገቡ ሲሆን የዛሬው 5.1 ከፍ ካሉት አንዱ ነው።

በሬክተር ስኬል 5.1 ከተመዘገበው የመሬት መንቀጥቀጥ በኃላ በሬክተር ስኬል 4.5 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥም ነበር።

አፋር ላይ በተለይ የመሬት መንቀጥቀጡ አይሎ በሚሰማባቸው ቦታዎች ንብረት ላይ ጉዳት የደረሰ ሲሆን በርካቶችም ከቤታቸው ሸሽተው ሄደዋል።

#TikvahEthiopiaFamily

@tikvahethiopia

EBS TV

02 Jan, 10:31


#HaileResortJimma

“ ወደ 1.7 ቢሊዮን ብር ፈሰስ ተደርጎበታል" - ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ስላሴ

የሻለቃ ኃይሌ ገብረ ስላሴ ሆቴልና ሪዞርት 10ኛ መዳረሻ በኦሮሚያ ክልል ጅማ ከተማ ዛሬ (ሐሙስ ታኀሳስ 24 ቀን 2017 ዓ/ም) ተመርቋል።

ሆቴሉ 3 የመመገቢያ አደራሾች፣ የልጆች መጫወቻ፣ ሞሮኮ ባዝ እንዳሉት፣ ለ210 ሰዎች ቋሚ የሥራ እድል እንደፈጠረ፣ ለወደፊት ደግሞ ወደ 400 ለሚሆኑ ሰዎች የሥራ እድል እንደሚፈጥር ተነግሮለታል።

ሆቴሉ አሁን የተጠናቀቁ ወደ 106 ክፍሎች እንዳሉት፣ ሁሉም ሰጠናቀቁ ደግሞ ወደ 114 ክፍሎች እንደሚኖሩት ተመልክቷል።

በመርሀ ግብሩ የተገኙት ሻለቃ ኃይሌ ባደረጉት ንግግር፣ በአንድ ዓመት ከስምንት ወራት የሆቴሉን ግንባታ በአጭር ጊዜ ላጠናቀቁት ሠራተኞች በሙሉ ምስጋና አቅርበዋል።

ጅማ ላይ የኮንስትራክሽን እቃ ውድ መሆኑን የገለጹት ሻለቃ ኃይሌ፣ “ብሎኬት ከአዲስ አበባ እየተጓጓዘ ነው የተሰራው” ሲሉ ተናግረዋል።

“ኮንስትራክሽኑን ውድ ያደረገው የመንገዱ መበላሸት ነው” ያሉት ኃይሌ፣ “ብሎኬቶች እየተሰባበሩ ነበር። ሁሉ ሰው በአውሮፕላን መጓጓዝ አይችልም” ነው ያሉት።

የሆቴሉን ወጪ በተመለከተ በገለጹበት አውድ ደግሞ፣ “ወደ 1.7 ቢሊዮን ብር ፈሰስ ተደርጎበታል” ብለዋል።

የጅማ ከተማ ከንቲባ አቶ ጣሃ ቀመር በመርሀ ግብሩ ተገኝተው ባደረጉት ገለጻ ደግሞ፣ “ጅማ አባጅፋር ሁሉንም የምታቅፍ ከተማ ናት። ባለሃብቶች ጅማን ለመቀየር ከኅይሌ እንዲማሩ ማሳያ ነው” ሲሉ ተናግረዋል።

የጅማ ከተማ አስተዳደር አቶ ኢጃሌ ናስር፣ “ኃይሌ ሲጠራ እንስቃለን፣ ኃይሌ ሲጠራ እንባችን ይመጣል፣ ኃይሌ እንኳን አገኘንህ” በማለት ደስታቸውን ገልጸዋል።

“ሱልልታ ላይ የኃይሌን ሆቴል ሳይ እንዲህ አይነት ሆቴል ጅማ ላይ ቢገነባ ብዬ ተመኝቼ ነበር። አሁን እንደዚህ ተሰርቶ አየሁትና እንባዬ ነው የመጣው። የተመረቀው ለኃይሌ ሳይሆን ለጅማ ህዝብ ነው” ሲሉ አመስግነዋል።

በ10ሩም የኃይሌ ሆቴሎችና ሪዞርቶች 900  ሩሞች እንዳሉ፣ ለ2500 ሠራተኞች የሥራ እድል እንደተፈጠረ ተመልክቷል።

ፎቶ ፦ በግዛቱ አማረ

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

EBS TV

01 Jan, 18:53


በተአምር የተፈረች ነፍስ !

" ከዚህ ትልቅ አደጋ መትረፌን ማመን አቅቶኛል" - ከቦናዉ የመኪና አደጋ የተረፈችው የኔነሽ ለገሠ


በሲዳማ ክልል ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ቦና ተከስቶ የ71 ሰዎችን ሕይወት ከቀጠፈዉ የመኪና አደጋ የተረፉት 4 ሰዎች ብቻ ናቸው።

ከእነዚህ ዉስጥ ሁለቱ ገና መኪናዉ ወደ ገደል ሳይገባ ዘለዉ በመውረዳቸው መጠነኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል።

ሁለት ሴቶች ደግሞ ተሽከርካሪዉ ወንዝ ዉስጥ ከገባ በኋላ በከፍተኛ ጉዳት በሕይወት ተርፈዉ ከቦና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ለተሻለ ህክምና ወደ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላዝድ ሪፈራል ሆስፒታል መላካቸዉን የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን እና ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን መረጃ ያሳያል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሀዋሳ ቤተሰብ አባል ከዚህ አስከፊ አደጋ የተረፉትን ሁለት ሴቶች በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ለመጠየቅ ወደ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላዝድ ሪፈራል ሆስፒታል አቅንቷል።

ከአደጋው የተረፉት ሁለቱ ሴቶች ስማቸው የነኔሽ ለገሠ እና ከበቡሽ ሃይሌ ይባላሉ።

ከበቡሽ ኃይሌ በአደጋዉ ምክንያት ቀዶ ህክምና ተደርጎላት በመተንፈሻ ማሽን እርዳታ ዉስጥ ትገኛለች።

የኔነሽ ገለሠ ደግሞ በድንጋጤና ከፍተኛ ሕመም ዉስጥ ብትሆንም ማዉራት እና የተፈጠረውን አደጋ በመጠኑም ቢሆን ማስታወስና ከአስታማሚዎቿ ጋርም መግባባት ትችላለች።

ከአደጋው ስለተረፉት ሁለት ሴቶች በምን አይነት የጤንነት ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ማብራሪያ ከሆስፒታሉ የጠየቅን ቢሆንም ሆስፒታሉ ከአደጋው ጋር በተያያዘ " ከፖሊስ በስተቀር መረጃ ለመስጠት እንቸገራለን " የሚል ምላሽ ሰጥቷል።

በወቅቱ የኔነሽ ለገሰን ሲያስታምሙ ያገኘናቸው አቶ ደበበን አሁን ስላለችበት የጤና ሁኔታ ጠይቀናቸዋል።

አቶ ደበበ እንደነገሩን የኔነሽ ስለ አደጋዉ ዝርዝር ጉዳዩ እንዳልተነገራትና በዚህ ዘግናኝ አደጋ ምክንያት አንድ እህቷን እና ሁለት ወንድሞቿን ማጣቷን ነግረውናል።

በሆስፒታሉ በተገኘን ጊዜም የኔነሽ ነቃ ብላ እያወራች ነበር።

አማርኛ ቋንቋን በሚገባ መናገር ባትችልም በሲዳምኛ ቋንቋ ስለ አደጋው ስታስረዳ ማዳመጥ ችለናል።

" አደጋዉ የተከሰተዉ የአጎቴ ልጅ ሚስት ሊያገባ ስለነበር ቤተ-ዘመድ ተሰባስቦ ሙሽራዋን ለመዉሰድ ወደ ወራንቻ ቀበሌ እየሄድን በነበርንበት ወቅት ነዉ" ብላለች።

" እኔ መሃል ነበርኩ፤ ሁላችን በደስታ በዝማሬ ላይ ነበርን ወደ ዋናዉ መስመር ወጥተን ጋላና ወንዝ ስንደርስ በድንገት መኪናዉ ድልድዩን ስቶ ወደ ወንዝ መግባት ሲጀምር በጩኸት ብዛት.... " ንግግሯን መጨረሽ አልቻለችም።

ይኽን በምታወራበት ወቅት እምባ በሁለቱም ዐይኖቿ ይወርድ ነበር።

ከተወሰነ መረጋጋት በኋላ የኔነሽ ስለ አሰቃቂው አደጋ የምታስታውሰውን ማስረዳት ቀጠለች ፤ " አላዉቅም እኔ ዛሬ ነዉ ሀዋሳ መሆኔን እንኳን የተነገረኝ! ሌላዉን አላዉቅም ፤ አጎቴ አብረዉኝ ስለነበሩ አጠቃላይ ስለ ሰርገኛዉ ደጋግሜ ስጠይቀዉ 'እነሱ ቦና ናቸዉ! አንቺ ስለተጎዳሽ ነዉ እዚህ የመጣሽዉ' ይለኛል " በማለት አስታማሚዋ የነበሩት አቶ ከበደ እንደነገሩን ይኽንን መሪር ሀዘን አለመስማቷን አረጋግጣልናለች።

ይህንን በተናገረችበት ቅጽበት አጠገቧ የነበሩት ሁሉ ዝምታን መረጡ ሁሉም እንደተፈራራ ዝም ተባባለ በዚህ ጊዜ አንድ ጥያቄ ቀረበላት "ከቦታዉ አደገኝነት አንፃር በመትረፍሽ ምን ተሰማሽ ? " የሚል።

የኔነሽ ከነበረችበት ትካዜ በመጠኑም ነቃ ብላ " ከቦታዉ አደገኛነትና ከነበረዉ ሁኔታ አንፃር ከዚህ ትልቅ አደጋ መትረፌን ማመን አቅቶኛል " ስትል በመደነቅ ስሜት ገልጻልናለች።

እኛም ፈጣሪ ፈጽሞ እንዲምራትና ብርታቱን እንዲሰጣት ገልጸንላት ተለያየን።

የየኔነሽ አጎትና አደጋዉን ያደረሰው መኪና ባለቤት የሆኑትን አቶ ሀይሌ ሀሮንም አግኝተን ስለ አደጋዉ፣ ስለ መኪናዉ ሁኔታና ስለ ሹፌሩ ጥያቄ አቅርበንላቸው ነበር።

አቶ ሀይሌ ፥ " መኪናዉ አዲስ ነበር። ሹፌሩ ደግሞ የገዛ ወንድሜ ሲሆን ሙሽራዉም የወንድሜ ልጅ ነዉ። መኪናዉ በአባቢዉ ልምድ ከቡና ሳይት ሰራተኞችን የማመላለስ ስራ ይሰራ ስለነበርና አብዛኞቹ የቤተሰቦቻችን አባላት የቡና ስራ ስለሚሰሩ በዕለቱ ሰርገኞችን ጭኖ ወደ ወራንቻ እየሄደ ነበር አደጋዉ የተከሰተዉ " ሲሉ ነግረውናል።

አክለውም ፤ " ከቤተሰቦቻችን ብቻ ከ30 በላይ ሰዎች በአደጋዉ የሞቱ ሲሆን ከዛ ዉስጥ ግማሽ ያህሉ የወንድማማች ልጆች ናቸዉ. . . የቀን ክፉ አንገት አስደፋን ከፍተኛ የልብ ስብራት ነዉ ያጋጠመን ጌታ ብርታቱን ይስጠን " ሲሉ በሀዘን ውስጥ ሆነው አውርተውናል።

በአደጋው ምክንያት ሕይወታቸው ያጡ 71 ሥርዓተ ተቀብራቸዉ የተፈፀመ ሲሆን የሟቾችን ቤተሰብ ለማገዝ ኮሚቴ ተቋቁሞ ወደ ሥራ መግባቱንና የገንዘብና ቁሳቁስ ድጋፍ እየተሰባሰበ እንደሚገኝም ተረድተናል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia

EBS TV

31 Dec, 17:03


" አደጋው የአንድ ቤተሰብና ዘመድ አዝማድ 33 ሰዎችን ከአንድ ቀበሌ የ52 ሰዎችን እንዲሁም ከአንድ ቤት የ4 ወንድማማቾችን ሕይወት የቀጠፈ ነበር " - ማቴ መንገሻ (ዶ/ር)

በቦና ወረዳ በመኪና አደጋ ሕይወታቸውን ያጡ 71 ወገኖቻችን ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ።

ከትላንት በስቲያ አመሻሽ ሲዳማ ክልል ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ቦና ወረዳ የሙሽራዉ ወገን ሰርገኞችን ጭኖ ሲጓዝ የነበረ አይሱዙ ክፍት መኪና የገላና ድልድይ ተብሎ በሚጠራዉ ቦታ መንገድ ስቶ ገደል ውስጥ በመግባቱ የ71 ሰዎች ሕይወት ወዲያውኑ ማለፉ ይታወሳል።

በአደጋዉ ምክንያት ሕይወታቸዉን ያጡ 71 ወገኖች ስርዓተ ቀብር ዛሬ ተፈጽሟል።

በስርዓተ ቀብሩ ወቅት የክልሉ ርዕሰ መስተደድር አቶ ደስታ ሌዳሞና ከፍተኛ አመራሮች፤ ከሁሉም አከባቢዎች የተሰባሰቡ ወዳጅ ዘመዶች ተገኝተው ነበር።

ርዕሰ መስተዳድሩ ፤ " በአንድ ድንገተኛ አደጋ ይህን ሁሉ ሰዉ ማጣት መሪር ሀዘን ነዉ፤ ፈጣሪ መፅናናቱን ይስጠን " ብለዋል።

የምስራቃዊ ሲዳማ ዞን አስተዳዳሪ ማቴ መንገሻ (ዶ/ር) ፥ " አደጋው የአንድ ቤተሰብና ዘመድ አዝማድ 33 ሰዎችን ከአንድ ቀበሌ የ52 ሰዎችን እንዲሁም ከአንድ ቤት የ4 ወንድማማቾችን ሕይወት የቀጠፈ ነበር " ብለዋል።

ከክልሉ መንግስት ጀምሮ መላዉ ሕብረተሰብ የጤናና ፀጥታ መዋቅሩ ላደረገዉ ርብርብ ምስጋና አቅርበዋል።

የሟቹችን ቤተሰቦች ለማፅናናት እና ለማገዝ ኮሚቴ ተቋቁሞ ወደ ስራ መግባቱን ገልጸው በገንዘብና በዓይነት የተሰበሰቡና እየተሰበሰቡም ያሉ ድጋፎችን በቀጣይ ለተጓጂ ቤተሰቦች በአግባቡ የማዳረስ ስራ እንደሚሰራ አስታውቀዋል።

መረጃው ተዘጋጅቶ የተላከው በሀዋሳው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia

EBS TV

31 Dec, 15:57


🚨#እንድታውቁት

" ከሌሊቱ 6:00 እስከ 6:15 ሰዓት ላይ ርችት ይተኮሳል " - ፖሊስ

የፈረንጆች አዲስ ዓመት በዓልን ምክንያት በማድረግ ርችት እንደሚተኮስ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት የደህንነትና ልዩ ኦፕሬሽን ዋና መምሪያ ማስታወቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።

ዋና መምሪያው ለአዲስ አበባ ፖሊስ በላከው ደብዳቤ እንዳስታወቀው ዛሬ ታህሳስ 22 ቀን 2017 ዓ/ም የሚከበረውን የፈረንጆቹን የአዲስ ዓመት ዋዜማ በዓል ምክንያት በማድረግ ከሌሊቱ 6:00 እስከ 6:15 ሰዓት ላይ ርችት ይተኮሳል፡፡

በመሆኑም ህብረተሰቡ ተገቢው መረጃ እንዲኖረው ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

@tikvahethiopia

EBS TV

31 Dec, 15:57


#TPLF : ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህ.ወ.ሓ.ት) ጠቅላላ ጉባዔውን እንዲያደርግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አሳስቧል።

ምርጫ ቦርድ ፤ ህወሓት በኢትዮጵያ የምርጫ የፖለቲካ ፖርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ስነምግባር አዋጅን ለማሻሻል በወጣው አዋጅ ቁጥር መሠረት በልዩ ሁኔታ መመዝገቡን አስታውሷል።

ፖርቲው ከተመዘገበበት ቀን ጀምሮ ባሉት ስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ የፓርቲውን ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርግ እንደሚጠበቅም አመልክቷል።

ምንም እንኳን ፓርቲው በስድስት ወር ውስጥ ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርግ የሚለውን ግዴታ ያለተጨማሪ ማሳሰቢያ መፈፀም እንዳለበት የሚታመን ቢሆንም ቦርዱ ለፓርቲው ነሀሴ 3 ፣ ነሀሴ 20 /2016 ዓ/ም እንዲሁም ጥቅምት 21 ቀን 2017 ዓ.ም በፃፋቸው ደብዳቤዎች አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማከናዎን ጠቅላለ ጉባኤውን እንዲያደርግ ማስታወቁን አመልክቷል።

" ፓርቲው በልዩ ሁኔታ የተመዘገበው ነሀሴ 3 ቀን 2016 ዓ.ም በመሆኑ ጠቅላላ ጉባኤውን እስከ የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲያደርግ ይጠበቃል " ያለው ምርጫ ቦርድ " ለዚሁ የጠቅላላ ጉባኤ ዝግጅት የሚያስፈልገውን የቅድመ ጉባኤ ዝግጅት የተመለከቱ ስራዎችን ቦርዱ መከታተል እንዲችል ፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤውን ከማድረጉ 21 ቀናት በፊት ጉባኤው የሚደረግበትን ቀን ለቦርድ እንዲያሳውቅ ይጠበቃል " ብሏል።

ይሁንና እስከ ዛሬ ድረስ ፓርቲው ከተመዘገበ በ6 ወር ጊዜ ውስጥ ጠቅላላ ጉባኤ ማድረግ የሚያስችለውን እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን ቦርዱ እንደማያውቅ አመልክቷል።

ፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ማድረግ የሚገባው ወቅት ሊገባደድ ከሁለት ወር ያነሰ ጊዜ የቀረው በመሆኑ ፖርቲው ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት በቀረው አጭር ጊዜ የጠቅላለ ጉባኤውን እንዲያደርግ ቦርዱ በጥበቅ አሳስቧል።

ይህ በሕግ ፓርቲው ላይ የተጣለ ግዴታ በወቅቱ ሳይፈፀም ቢቀር ቦርዱ ሕጉን መሠረት በማድረግ ተገቢ ነው የሚለውን ውሳኔ የሚሰጥ መሆኑን አሳውቋል።

ከዚህ ቀደም የህወሓት አመራሮችን ለሁለት የከፈለ ጉባኤ መደረጉ አይዘነጋም።

በወቅቱም ምርጫ ቦርድ ያልተገኘበትን እና ስርዓቱን ያልተከተለ ጠቅላላ ጉባኤ እውቅና እንደማይሰጥ ማስገንዘቡ ይታወሳል።

ምንም እንኳን ምርጫ ቦርድ እውቅና እንደማይሰጥ ቢያሳውቅም በደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ቡድን ጉባኤ አድርጎ አመራሮቹን መርጧል።

አቶ ጌታቸው ረዳን እና ሌሎች ከእሳቸው ጋር የነበሩ ከፍተኛ የፓርቲው አመራሮችን ከቦታቸውን አንስቷል።

በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ቡድንም ለጉባኤው እውቅና የነፈገ ሲሆን ትክክለኛ ቅቡልነት ያለው ጉባኤ እንዲደረግ እየሰራ መሆኑን ማሳወቁ አይዘነጋም።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia

EBS TV

31 Dec, 13:10


#Kesem_Dam

🚨 "በአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ በከሰም ግድብ አከባቢ ያሉ ነዋሪዎች በብዛት እየለቀቁ ነው" - ነዋሪዎች

🔴 " ግድቡ ዲዛይኑ እስከ 7.0 ሬክተር ስኬል የመሬት መንቀጥቀጥ ይችላል ተብሎ ይገመታል " - ጽ/ቤቱ


በተደጋጋሚ እየተከሰተ ባለው የመሬት መንቀጥቀጥ በአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ በተለያዩ ቦታዎች የመሬት መሰንጠቆች በመፈጠራቸውና በተፈጠሩ ስጋቶች ምክንያት ነዋሪዎች ካሉበት አከባቢ ወደ ሌላ አከባቢ እየሸሹ መሆኑን ሰምተናል።

የቲክቫህ ኢትዮጵያ የአፋር ቤተሰብ በትላንትናው ዕለት በአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ አርብሃራ ቀበሌ እና ዶኾ ቀበሌ በመገኘት በመሬት መንቀጥቀጡ ምክንያት እቃቸውን ጭነው ሲጓዙ የነበሩ ነዋሪዎችን አግኝቶ አነጋግሯል።

ኃሳባቸውን የሰጡ የማኅበረሰብ ክፍሎች የመሬት መንቀጥቀጡ እንዲሁም እሱን ተከትሎ የሚሰማው ድምጽ በተለይ ለልጆቻቸው ፍርኃት እንደፈጠረባቸው አስረድተዋል።

ከትላንት በስቲያ ከአርብሀራ ቅርብ ርቀት ላይ በሚገኘው መልካወረር ከተማ የመሬት መንቀጥቀጡ ከፍ በማለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኋላ ነዋሪዎች ለሶላት (ዱኣ ለማድረግ) ወደ መስጂድ እንደገቡ ነው የገለጹት።

በመሬት መንቀጥቀጡ ምክንያት እቃቸውን በሦስት እግር ተሽከርካሪ ጭነው አከባቢውን ሲለቁ ያገኘናቸው ወጣቶች " ብዙ ሰው ለቋል፤ አረ ሁሉም ለቋል እዚያ ሰፈር ያለ ሁሉም እየለቀቀ ነው " በማለት ወደ አዋሽ አርባ እየተጓዙ መሆኑን ተናግረዋል።

የአስፋልት መሰንጠቅ በተከሰተበት ቦታ ያገኘነው አንድ ነዋሪ እንዳስረዳው በርካታ ሰዎች እየለቀቁ ያሉት በወረዳው ከሚገኘው የከሰም ግድብ አከባቢ ያሉ ነዋሪዎች መሆናቸውን ጠቅሷል።

" ከ7 ጀምሮ [በትላንትናው ዕለት] ያለውን ሁኔታ ብታየው በሚገርም ሁኔታ እቃ እየተጫነ ነው፤ በጣም ደግሞ በትናንሽ መኪኖች በባጃጅም ሁሉም እንደ አቅሙ እንደ ኑሮ ደረጃው እቃውን ጭኖ እየወጣ ነው። " ሲልም ነው ያስረዳው።

በተለይም " ግድቡ የመሰንጠቅ አደጋ ደርሶበታል " በሚል የፋብሪካው ሰራተኞች ጨምሮ ነዋሪው በሌሊት ጭምር እቃውን እየጫነ፤ ግመሎቹንና እንስሳቱን እየነዳ ከአከባቢው መሸሹን ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረዳት ችሏል።

ዛሬ ጠዋትም በከሰም ያሉ ነዋሪዎችን ያነጋገርን ሲሆን ትላንት ሌሊት በነበረው የመሬት መንቀጥቀጥ በርካቶች ከቤታቸው ወጥተው አስፓልት ላይ ማደራቸውን ነግረውናል።

የመሬት መንቀጥቀጡ ንጋት ላይም በመቀጠሉ በርካቶች ንብረታቸውን ይዘው ወደ አዋሽ አርባ እየሸሹ መሆኑን ለመረዳት ችለናል። ነዋሪዎች በመንግሥት በኩል በቂ የማረጋጋትም ሆነ ድጋፍ የማድረግ ሥራ በአከባቢው እንዳልተሰራነው የገለጹት።

በአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ እና ዱለቻ ወረዳዎች ለሚገኘው ከሰም ስኳር ፋብሪካ አገልግሎት የሚሰጠው የከሰም ግድብ 500 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ የመያዝ አቅም ያለው ነው።

የግድቡ ባለሞያዎች ነዋሪዎች አከባቢውን ለቀው የሄዱት " ግድቡን ውሃ እየጣሰ ነው " በሚል ሀሰተኛ ወሬ መሆኑን መግለጻቸውን ከአዋሽ ቤዚን አስተዳደር ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

የአዋሽ ቤዚን አስተዳደር ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አደን አብዶ ስለ ግድቡ አሁናዊ ሁኔታ ለቲክቫህ ምን ምላሽ ሰጡ ?

" የግድቡ አካባቢ ላይ ያለውን አሁናዊ ሁኔታ በቅርበት እየተከታተልን ስለሆነ ምንም አይነት ችግሮች የሉም በአሁን ሰዓት ሰላም ነው።

ከግድቡ 30 እና 40 ኪሜ ላይ ነው መንቀጥቀጡ ከበድ ያለው። ቦታው ላይ ካሉ አስተዳደሮች እስካሁን ድረስ ከግድቡ ጋር የተያያዘ የደረሰን መጥፎ መረጃ የለም።

ግድቡ ዲዛይኑ እስከ 7.0 ሬክተር ስኬል የመሬት መንቀጥቀጥ ይችላል ተብሎ ይገመታል እስካሁን እዚህ አልደረሰም ባለሞያዎች እየተከታተሉ ያለውን ስጋት ሪፖርት ያደርጋሉ እኛም ለሚመለከተው አካል እናስተላልፋለን።

በተፋሰስ ውስጥ ያለውን ህብረተሰብ የማንቃት እና ያለውን ሂደቶችን ኮሚቴ ተዋቅሮ መረጃ የሚለዋወጡበት ሂደት ከክልሉ መስኖና ቆላማ ቢሮ እስከ እስከ አደጋ መከላከል ድረስ የቅድመ መከላከል ስራዎች እየተሰሩ ነው " ብለዋል።


#TikvahEthiopiaFamilyAfar

@tikvahethiopia

EBS TV

31 Dec, 13:03


የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ቅሬታ ምንድነው ?

የመቐለ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በግቢያቸው የተፈጠረው አለመረጋጋትና ረብሻ አስመልክቶ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል የወጡት መረጃዎች " ሚዛናዊ አልነበሩም " ሲሉ ተቋውማቸው በፅሁፍ አቅርበዋል።

94 የሚሆኑ የመቐለ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በትግርኛ ቋንቋ ቅሬታቸውን ፅፈው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስገብተዋል።

ምን አሉ ?

እኚህ ተማሪዎች " የነበረውን እና እየቀጠለ ያለው የተማሪዎች ጥያቄ የሚከተለው ነው " ብለዋል።

ችግሩ ከመስከረም 26/2017 ዓ.ም የጀመረ ሆኖ ፦

1ኛ. አሸዋ የተደባለቀበት መግብ አንበላም፤
2ኛ. የፌደራል መንግስት ያወጣውን ሜኑ ይተግበር
3ኛ. ኢንተርፕራይዝ የተባለ አስቤዛ አቅራቢ ድርጅት ከቅጥር ግቢያችን ይውጣ
4ኛ. ያለውን ስለማይወክለን ድምፃችን የምናሰማበት የተማሪዎች ህብረት ለመመረጥ እንድንችል እድል ይመቻችልን 
የሚሉ ናቸው ... ሲሉ ገልጸዋል።

" እነዚህ ያነሳናቸው የመብት ጥያቄዎች ተከትሎ ጥቅምት 7 እና ታህሳስ 14/2017 ዓ.ም ፓሊስ ግቢያችን ድረስ ዘልቆ ከባድ ድብድባ አካሂዶብናል " ብለዋል።

" በተለይ ታህሳስ 14 በ47 ተማሪዎች ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል። የሴቶች የምኝታ ክፍል ሳይቀር በመክፈት ፓሊስ በአስነዋሪ መልኩ በመደብደብ አስፋልት ላይ ጥሎዋቸዋል " ሲሉ አመልክተዋል።

" አንድ አካል ጉዳተኛ ደግሞ ደብድበው ወደ ጉድጓድ ጥለውታል " ሲሉ ጠቁመዋል።

" 14 ተማሪዎች ፣ አንዲት ጥበቃ ፣ አንድ ከዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ ፣ አንድ መምህር በከባድ ግርፋት በአጠቃላይ 17 ሰዎች በዓዲ ሓቂ ግቢ ብቻ በፓሊስ ተቀጥቅጠዋል ታስረዋል " ብለዋል።

" የተደበደቡት ተማሪዎች ህክምና እንዳያገኙ ለሦስት ቀናት በፓሊስ ተከልክለው ከቁሳላቸው ጋር እንዲሰቃዩ ተደርገዋል " ያሉት ተማሪዎቹ " ማንኛውም ተማሪ ለሚድያ ቃሉ እንዳይሰጥ፤ ወደ ማህበራዊ የትስስር ገፅ እንዳይለጥፍ እና እንዳያሰራጭ የተማሪዎች ህብረት እና ፓሊስ አስፈራርተውታል " ብለዋል።

" ቢሆንም ተማሪው የደረሰውን ግፍ በፅሑፍ ፤ በድምፅ እና በቪድዮ ደምፁ ከማሰማት ወደ ኋላ አላለም " ሲሉ ገልጸዋል።

ተማሪዎቹ በወጡት መረጃዎች ላይ ህፀፆች ያሏቸው ምን ምን ጉዳዮች ናቸው ?

" ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ሁኔታን አስመልክቶ ባቀረባቸው ተከታታይ መረጃዎች የሚከተሉት ህፀፆች ነበሩት " ሲሉ ቃላቸውን ሰጥተዋል።

1ኛ. መጀመሪያ በወጣው መረጃ " ሜኑ ይተግበር " ብለን የመብት ጥያቄ ያነሳን ተማሪዎች የፌደራል ሜኑን የተቃወምን በሚመስል መልኩ ነው የቀረበው።

2ኛ. ከታህሳስ 14 /2017 ዓ.ም በፊት በተከታይ ስናቀርበው የነበረውን የመብት ጥያቄያችን አልተካከተልንም።

3ኛ. በፓሊስ የተደበደብን ፣ የታሰርን የተንገላታን እኛ እያለን ፤ ንብረት እንዳወደምን ፣ ሰራተኞች እንደደበደብን ፣ አድማ እንደምታን ተደርጎ የቀረበው መረጃ ፍፁም የተሳሳተ ነው። 

4ኛ. የተማሪዎች ህብረት ያስፈታቸው የታሰሩ ተማሪዎች እንዳሉ ተደርጎ የቀረበው ስህተት ነው እየጠቆመ ተማሪዎች የሚያሳስር ማን ሆነና ነው ? ተማሪዎች እንዲፈቱ ያደረግነው ከኛ ተማሪዎች የተውጣጣ ኮሚቴ ነው። 

5ኛ. ያነሳነው የመብት ጥያቄ ሆን ተብሎ ፓለቲካዊ መልክ እንዲይዝ ተደርገዋል፤ የእኛ ጥያቄ የፓለቲካ ሳይሆን የዳቦ ጥያቄ መሆኑ እንዲታወቅልን እንፈልጋለን።

6ኛ. ድምፃችን እንዲሰማ አዲስ የቴሌግራም ገፅ በከፈቱ ሁለት ተማሪዎች የተማሪዎች ህብረት እስከ አሁን እያስፈራራቸው እንደሚገኝ እንዲታወቅልን እንፈልጋለን።

7ኛ. የምግብ አቅርቦቱ እንደተሻሻለ ፣ የአንዱ ዳቦ ግራም 120 እንዲሆን እንደተደረገ ተደርጎ የቀረበው መረጃ ልክ አይደለም። እስከ ታህሳስ 21/2017 ዓ.ም የተሻሻለ የምግብ አቀራረብና የዳቦ ግራም የለም 50 ግራም የሚመዘን ዳቦ ነው እየቀረበልን ያለው።  

8ኛ. በመልእክት መለዋወጫ ቴሌግራማችን የታፈነ ድምፅ ፣ እንዲጠፋ የተደረገ ድምፅ ፣ የተሰረዘ ተማሪ እንደሌለ ተደርጎ የቀረበውም ውሸት ነው። ጥያቄ ያነሱ በርካታ ተማሪዎች ከቴሌግራም ግሩፕ እንዲወገዱ ተደርገዋል። 

9ኛ. በዓዲ ሓቂ ግቢ በፓሊሶች እንጂ በተማሪዎች የተሰበረ በር እና መስተዋት እንደሌለ እንዲታወቅልን እንፈልጋለን።

10ኛ. በአጠቃላይ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላይ የወጡት መረጃዎች ወደ ዩኒቨርስቲ አስተዳደር ፣ የተማሪዎች ህብረት እና ፓሊስ ያደላ የጉዳዩ ባለቤት የሆነው ተማሪ ድምፅ ያፈነ አቀራረብ ነበር፤ በዚህም እስካሁን ከማስፈራሪያ ከድብደባ ፣ ከህክምና እጦት ፣ ስቃይ እና ረሃብ እንዳንላቀቅ ሆኗል ... ብለዋል።

ቅሬታ አቅራቢዎቹ እኛ የ42 የተማሪ ክፍሎች ፣ 14 በእስር የሰነበቱ፣ 38 በከባድ የቆሰሉ በድምር 94 የመቐለ ዩኒቨርስቲ ዓዲ ሓቂ ግቢ ተማሪዎች እንደሆኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ባስገቡት ደብዳቤ አመልክተዋል።

በተማሪዎች ጉዳይ ዩኒቨርሲቲው፣ ኅብረቱ፣ የፀጥታ ኃይሉ ምንድ ነበር ያሉት ?

ዩኒቨርሲቲው፦

👉 በሜኑው ላይ የሚስተካከሉ ነገሮች ካሉ ብሄራዊ  ሜኑ በይዘትና በጀት ደረጃ እስካልተለየ ድረስ ጥያቄዎች በተማሪዎች ህብረት በኩል ቀርበው ማስተካከል እንደሚቻል
👉 በሃገር ደረጃ ተግባራዊ የሆነውን የምግብ ሜኑ ተቃውሞ የዩኒቨርሲቲውን መሰረተልማት ማጥፋትና የካፊተርያ እና የጥበቃ ሰራተኞች ላይ ጉዳት ማድረስ ተማሪዎችን እንዲሁም ማህበረሰቡን እና ሃገሪቱን የሚጎዳና ተግባር መሆኑን
👉 ተማሪዎች ቅሬታቸውን በሰላማዊ መንገድ መግለጽ እንደሚችሉ ነበር የገለጸው።

የኢትዮጵያ ተማሪዎች ኅብረትና የመቐለ ተማሪዎች ኅብረት፦

‘አንድ ዳቦ፣ ሁለት ዳቦ፣ አሸዋ አለው’ በሚለው ጉዳይ ቅሬታ ተነስቶ ነበር። 120 ግራም ነበር አንድ ዳቦ የሚጋገረው አሁን 60፣ 60 ተደርጎ ወደ ሁለት ሆኗል። ግራሙ ላይ የተጨመረ፣ የቀነሰ ነገር የለም።
የቅሬታ መነሻ አዲሱ የምግብ ሜኑ ትግበራ ነው።
27 የታሰሩ ተማሪዎችን በዲፓርትመንት እና በስማቸው ለይተን ነው ያስፈታናቸው። ግን ካስፈታናቸው በኃላ ሌሊት ላይ ‘ሲቀጠቀጡ ከነበሩ የመለቐ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መካከል አንዱ ሞቷል’ ብለው ፓስት አደረጉ ሄደን ስናጣራ የሞተ ተማሪ የለም። ይህ ሀንድል ከተደረገ በኃላ ‘የታፈኑ ተማሪዎች’ አሉ ወደሚል መጡ፤ ዝርዝር የላቸው ምን የላቸው ይህም ትክክል አይደለም።
ተማሪዎች ተደብድበዋል፣ንብረት ወድሟል፣ በኃላ የታሰሩ ተማሪዎች ተፈትተዋል፤ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ነው.. ያሉት።

የኣዲ ሓቂ ፀጥታ ኃላፊ፦

🔴 የተማሪዎች ኀብረት ማለት የተማሪዎች ተወካዮች ናቸው። እነርሱ ከእኛ ጋር አብረው እየሰሩ ነው።
🔴 ተማሪዎቹ ያደረሱት ጉዳት ትልቅ በመሆኑ ሊፈቱ ባይገባቸውም የጉዳዩ መነሻ እነርሱ ሳይሆኑ ዩኒቨርሲቲው ሊያቀርበው የሚገባውን ነገር ባለማቅረቡ የተነሳ ነው። አስተምሮት ሰጥተን አንድም ልጅ ሳይቀር ፈትተናቸዋል።
🔴 የታሰረ ተማሪ የለንም ለቀናል። አሁንም ድጋሚ የሚሰሩት ስራ አለ እየተከላከልን ነው። 
🔴 ዋና ዋና ለብጥብጡ ተዋናይ የነበሩ ተማሪዎችን ልንለቃቸው አልፈለግንም ነበር።  የተማሪዎች ኀብረት ግን ‘እንደዚህ ከሚሆን እኛው ራሳችን እናስተካክለዋለን’ ስላሉን ለቀናቸው ችግሩ እንዲፈታ እየሰራን ነው።
🔴 ከተማሪዎች ጋር የመጣላት ፍላጎትም የለንም። ተማሪዎቹ መነሻ አይደሉም ለብጥብጡ፣ ለብጥብጡ መነሻው ራሱ ዩኒቨርሲቲው ነው...ብሎ የነበረው።

NB. ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሁሉም ያዘጋጃቸው መረጃዎች ከተማሪዎች የመጡ ቅሬታዎችን መነሻ አድርጎ፤ የሚመለከታቸውን አካላት ምላሽ አካቶ የቀረበ ነው።

@tikvahethiopia

EBS TV

31 Dec, 10:43


#ለጥንቃቄ🚨

የመሬት መንቀጥቀጥ ሲከሰት ምን ማድረግ አለብን ?

➡️ ከቤት ውጭ ከሆኑ ፦ ከዛፎች ፣ ከሕንፃዎች ፣ ከኤሌትሪክ ምሶሶዎች እና ሌሎች ወድቀው ጉዳት ሊያደርሱ ከሚችሉ ነገሮች መራቅ እና ገላጣ ሜዳ አካባቢ መቆየት።

➡️ በቤት ውስጥ ከሆኑ ፦ በበር መቃኖች ፣ ኮርነሮች እና ኮሪደሮች ተጠግቶ ማሳለፍ። ከእሳት ምድጃዎች፣ ከተሰቀሉ ፍሬሞች እና የግድግዳ ጌጦች፣ ከመጽሐፍ መደርደሪያዎች እንዲሁም ከመስኮት አካባቢ መራቅ። የጋዝ ምድጃዎችን በተቻለ ፍጥነት ማጥፋት ካልሆነም ከአካባቢው መራቅ።

➡️ በትልልቅ ሕንጻዎች ውስጥ ከሆኑ ፦ ከሕንጻዎቹ ለመውጣት አለመሞከር ፣ አሳንሰር (ሊፍት) በፍፁም አለመጠቀም። ከደረጃዎች አካባቢ መራቅ።

➡️ መኪና እያሽከረከሩ ከሆኑ ፦ የኤሌትሪክ መተላለፊያ ምሶሶዎችን፣ ዛፎችና ሽቦዎች አካባቢ አለመቆም፣ የኤሌትሪክ መስመር ምሶሶዎች እና ሽቦዎች ተሽርካሪው ላይ ከወደቁ ከመኪናው ለመውጣት አለመሞከር፣ በተቻለ ፍጥነት ገላጣ ወደሆነ አካባቢ መኪናን ማቆም።


#Ethiopia
#የአአእሳትናአደጋስራአመራርኮሚሽን

@tikvahethiopia

EBS TV

31 Dec, 10:43


#Earthquake

ለሊት 7:13 ላይ በሬክተር ስኬል 4.8 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ እንደተከሰተ የጀርመኑ ጂኦ ሳይንስ እና የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ መረጃ ያመላክታል።

የመሬት መንቀጥቀጡ የተመዘገበው ከአቦምሳ 39 ኪ/ሜ ርቀት ላይ ነው።

ይህ ባለፉት ሰዓታት ከተመዘገበው ከፍተኛው ሲሆን በሬክተር ስኬል 4.0 ፣ 4.5 ፣ 4.6 ፣ 4.7 ... የሆኑ የመሬት መንቀጥቀጦች ቀን፣ ምሽት እና ለሊቱን በተከታታይ ተመዝግበዋል።

የነዚህ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቶች አዲስ አበባ እና የተለያዩ የክልል ከተሞች ጠንክረው ተሰምተዋል።

በተለይ በህጻዎች ላይ ያሉ ሰዎች ጠንከር ያለ ንዝረት ተሰምቷቸዋል።

በሌላ በኩል ፤ በመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት በከሰም ቀበና ቤቶች እና ንብረት ላይ ወድመት መድረሱን ነዋሪዎች ጥቆማቸውን በፎቶ አስደግፈው ልከዋል።

@tikvahethiopia

EBS TV

29 Dec, 18:39


አል-ሲሲ ምን እያሉ ነው ?

ኢትዮጵያ እና ሶማሌላንድ ከባህር በር ጋር በተያያዘ የመግባቢያ ስምምነት ከተፈራረሙ ማግስት አንስቶ ከሶማሊያው መሪ ጋር እየተደዋወሉ እና እየተገናኙ ፦
" ° አይዟችሁ እኛ አለን ፤
  ° ከፈለጋችሁ ወታደርም እንልካለን ፣
  ° የጦር መሳሪያ ድጋፍም ይኸው፣
  ° በሰላም ማስከበርም እንሳተፋለን ፣
  ° እናተን ማንም እንዲነካ አንፈቅድም " እያሉ ሲለፍፉ የከረሙት የግብጹ መሪ አብዱል ፈታህ አል-ሲሲ አሁን ደግሞ የአንካራውን ስምምነት " በቅርበት እየተከታተልን ነው ፤ መረጋጋትንም ሊያመጣ ይችላል " የሚል ዲስኩር ይዘው ብቅ ብለዋል።

ድሮውንም የኢትዮጵያ ነገር አይኗን የሚያቀላው ግብፅ ከመግባቢያ ስምምነቱ  (MoU) በኃላ ስለ ኢትዮጵያ ብዙ አሉታዊ ነገር ስታወራ ፣ የማጠልሸት ስራ ስትሰራ ነበር የከረመችው።

ትላንት የግብፁ መሪ አል-ሲሲ በቅርብ ኢትዮጵያ መጥተው ከነበሩትና የኢትዮጵያ የባህር ባር ጥያቄን በይፋ ከደገፉት የፈረንሳዩ ፕሬዜዳንት ማክሮን ጋር የስልክ ውይይት አድርገው ነበር።

በዚህም ወቅት ፥ አል ሲሲ በቱርክ አሸማጋይነት ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ የፈረሙትን ስምምነት ጠቅሰው " በቅርብ እየተከታተልን ነው ፤ ስምምነቱ በአፍሪካ ቀንድ ፀጥታ እና መረጋጋት ሊያመጣ ይችላል " ሲሉ ተናግረዋል።

" ይህ ስምምነት በአፍሪካ ቀንድ መረጋጋት እንደሚያመጣ ተስፋ አለኝ ዓለም አቀፍ ሕግን ተከትሎ ሊሆን ይችላል። በአፍሪካ ቀንድ ያለው መረጋጋት እና የግብፅ ብሔራዊ ጥቅምት የተሳሰሩ ናቸው " ሲሉ እንደገለጹም ተነግሯል።

አል-ሲሲ " ለሶማሊያ ድጋፍ ለማድረግ እንሰራለን ይህ ድጋፍ በሁለትዮሽ ግንኙነት አሊያም በአፍሪካ ሕብረት የሰላም አስከባሪ ሚሽን አማካይነት ነው " ብለዋል።

ግብፅ ፤ ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ቁርሾ ውስጥ በከረሙበት ወራት ስታወጣ የነበረው መግለጫና ስታደርግ የነበረው እንቅስቃሴ ሀገራቱን ወደ መግባባትና ሰላም እንዲመጡ ለማድረግ ሳይሆን ነገሩን ለማጋጋል ፣ ለማባባስ ፣ የለየለት ቀውስና ጦርነት እንዲፈጠር ለማድረግ የታስበ እንደሆነ አመላካች እንደነበር ብዙዎች የሚገልጹት ነው።

#Ethiopia🇪🇹

@tikvahethiopia

EBS TV

29 Dec, 18:39


በሲዳማ ክልል በደረሰ አሰቃቂ የመኪና አደጋ ከ70 በላይ ሰዎች ህይወታቸው አለፈ።

በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን በቦና ዙሪያ ወረዳ ጋላና ወንዝ ተብሎ በሚጠራዉ ድልድይ ላይ ከ70 በላይ ሰርገኞችን ይዞ ወደ በንሳ ወረዳ ሲጓዝ የነበረ አይሱዙ ክፍት መኪና ድልድዩን ስቶ ወንዝ ዉስጥ መግባቱን የበርካታ ሰዎች ህይወት ማለፉን የሲዳማ ክልል መንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታዉቋል።

ቢሮው " እስካሁን ቁጥሩ ያልታወቀ ሰዉ ሕይወት አልፏል " ሲል ገልጿል።

የክልሉ ፖሊስ በሰጠን ቃል 71 ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን አሳውቋል።

የአደጋ መንስኤ እየተጣራ ሲሆን አጠቃላይ የተጠቃለለ መረጃ ይገለጻል።

ነፍስ ይማር !

@tikvahethiopia

EBS TV

29 Dec, 18:39


" የ71 ሰዎች ሕይወት አልፏል " - ፖሊስ

በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን በቦና ዙሪያ ወረዳ ጋላና ወንዝ ተብሎ በሚጠራዉ  አከባቢ 74 ሰዎችን ጭኖ ሲጓዝ የነበረ አይሱዙ መኪና ድልድዩን ስቶ ወንዝ ዉስጥ በመግባቱ የ71 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የክልሉ ፖሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታዉቋል።

የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሽመልስ ቶማስ አደጋዉን አስመልክቶ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለፁት " በመኪናው ላይ የነበሩት የቡና ሳይት ስራ ላይ ቆይተዉ ወደ ከተማ ሲመለሱ የነበሩ ሰዎች ናቸዉ " ብለዋል።

የአደጋዉ መንስኤ የተጣራ ሲሆን 68 ወንዶችና 3 ሴት በድምሩ 71 ሰዎች ሕይወት ማለፉን አረጋግጠዋል።

የተረፉት 3 ሰዎች ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዉ በሕክምና እየተረዱ መሆኑን የገለፁት ኮሚሽነሩ ለሟች ቤተሰቦች መፅናናትን ተመኝተዋል።

ነፍስ ይማር !

@tikvahethiopia

EBS TV

29 Dec, 18:39


#Earthquake አዋሽ ፈንታሌ አካባቢ በተደጋጋሚ እየተከሰተ ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ አሁንም ቀጥሏል።

ንዝረቱ አዲስ አበባ ድረስ የተሰማ በሬክተር ስኬል 5 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ በድጋሚ ተከስቷል።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፤ የጂኦፊዚክስ እና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር የሆኑት ኤሊያስ ሌዊ  (ዶ/ር) ፤ ዛሬ ምሽት 2 ሰዓት ላይ በሬክተር ስኬል 5 ሆኖ የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ በአዲስ አበባ በተደጋጋሚ መሰማቱን ተናግረዋል።

" በአካባቢው ያለው የቅልጥ ዓለት ድንጋይ (ማግማ) እንቅስቃሴ አሁንም ቀጥሏል " ያሉት ኤልያስ (ዶ/ር) " የመሬት መንቀጥቀጥ በተደጋጋሚ እንዲከሰት እያደረገ ያለውም ይኸው ነው " ሲሉ ለብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ተናግረዋል።

@tikvahethiopia

EBS TV

29 Dec, 17:19


የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ገንዘብ እያሰባሰበች ነው ?

👉 " ምዕመናን ፤ ቅዱሳን ገንዘባችሁን እንዳትበሉ ተጠንቀቁ " -  መጋቢ ለወየሁ ስንሻው

" የሚታየው የባንክ አካውንት ሆነ መልዕክት እኛ የማናውቀው ነው " - አገልጋይ ዮናታን አክሊሉ


" በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች ያሉ የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን አጥቢያ ቤተክርስቲያናት ከፓስተር/መጋቢ ዮናታን አክሊሉ ጋር በመተባበር የገቢ ማሰባሰቢያ / ገንዘብ መሰብስበ ስራዎች እየሰሩ ነው " በሚል በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ እንደሆነ ተገልጸ።

የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን በሰጠችው ይፋዊ መግለጫ ፥ የባንክ ቁጥር ጭምር በመግለጽ የተለያዩ ፖስተሮችንም በማሰራት በማህበራዊ ሚዲያ ላይ እየተደረገ ያለው የገንዘብ የማሰባሰብ እንቅስቃሴ ፍጹም የማታውቀው ስራ እንደሆነ ገልጻለች።

የቤተክርስቲያኗ ምክትል ፕሬዜዳንት መጋቢ ለወየሁ ስንሻው ፤ " ከወንድማችን ዮናታን አክሊሉ ጋር በዚህ ስራ ዙሪያ ንግግር አላደርግንም ይህንን መግለጽ እንፈልጋለን " ብለዋል።

የባንክ አካውንቶቹ በአንድ ግለሰብ ስም እንደተከፈቱ እንደተደረሰበትና ቤተክርስቲያኗ በሚመለከተው አካል በኩል ጉዳዩን እንደምትሄድበት ተገልጿል።

ጉዳዩ ቤተክርስቲያንን ያሳሰበና ያስደነገጠ እንደሆነ ተመላክቷል።

መጋቢ ለወየሁ ፤ " ምዕመናን ፣ ቅዱሳን የገንዘብ ማሰባሰቢያ ስራ የተባለው በፍጹም ማታለል እና ማጭበርበር የተሞላበት በመሆኑ በዚህ የማታለል ተግባር ገንዘባችሁን እንዳትበሉ፣ እንዳትሳተፉ " ሲሉ አሳስበዋል።

በተመሳሳይም አገልጋይ ዮናታን አክሊሉ ፥ ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በአዲስ አበባ ዙሪያ ካሉ የሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤተክርስቲያናት እና ከኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል ጋር በመተባበር የገቢ ማሰባሰቢያ እያካሄዱ እንደሆነ የሚገልጹት መልዕክቶች ፍጹም ሀሰተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።

" በስሜ የተከፈተ ለዚህ የሙሉ ወንጌል አገልግሎት የሚውል የባንክ አካውንት እንደሌለ አሳውቃለሁ " ብለዋል።

አካውንቱን ማነው የከፈተው (በማስታወቂያዎች ላይ ያለውን) ስለሚለው ጉዳይም ፤ ማን እንደከፈረው እንደተደረሰበትና የቤተክርስቲያኒቱ እና የእሳቸውም የህግ ክፍል ጉዳዩን እንደሚከታተለው ጠቁመዋል።

" በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የሚታየው የባንክ አካውንት ሆነ መልዕክት እኔን እና ቤተክርስቲያናችንን የአዲስ ካህናት ቤተክርስቲያን የማይመለከት የማናውቀው ነው " ብለዋል።

" እራሳችሁን ከዚህ የማታለል ስራ ጠብቁ ፤ ምንም ተሳትፎም እንዳታደርጉ " ሲሉ አሳስበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

EBS TV

29 Dec, 17:19


" የሰላም ችግር ከሁሉም በፊት ቀድሞ መፍትሔ ማግኘት አለበት " - ፕ/ር መረራ ጉዲና

ባለፈው ሳምንት የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ ፓርቲ (ኦፌኮ) አዲሱን ዋና ፅ/ቤቱን በአዲስ አበባ አስመርቋል።

የቀድሞ ሜክሲኮ የሚገኘው ዋና ፅ/ቤቱ በኮሪደር ልማት ምክንያት በመፍረሱ አዲሱን ቢሮ ቀበና አደባባይ አከባቢ ከፍቶ ስራ አስጀምሯል።

በዚህ ወቅት የኦፌኮ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ንግግር ያደረጉ ሲሆን " አሁንም ሀገራችን ትልቅ ችግር ውስጥ ናት " ብለዋል።

የሰላም ችግር ከሁሉም በፊት ቀድሞ መፍትሔ ማግኘት እንዳለበትም ገልጸዋል። ለዚህ ደግሞ ወደጦርነት የሚመሩትን የፖለቲካ ችግሮች በውይይት መፍታት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።

" የኦሮሞ ህዝብ ፍላጎትም ሆነ የሌሎች ብሔር ብሔረሰቦች ፍላጎት ዘላቂ ሰላም ፣ ጠንካራ የዲሞክራሲ ስርዓት እና በኢኮኖሚ የበለፀገች ኢትዮጵያን ማየት ነው " ያሉ ሲሆን፤ " ይሄን ከግብ ለማድረስ ኦፌኮ'ን ጨምሮ ሌሎች የተቃዋሚ ፖርቲ ህብረቶች ትግላቸውን ማጠናከር አለባቸው " ሲሉ ተናግረዋል።

በወቅቱ ተገኝተው የነበሩ የተለያዩ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች " ህዝቡ ላይ እየደረሰ ያላውን ችግር ለመፍታት ህብረታችንን በደንብ በማጠናከር እና ህዝቡን ከጎን በማሰለፍ አንድላይ መቀጠል ይኖርብናል " ብለዋል።

ኦፌኮ አዲሱን ዋና ፅ/ቤቱን ስራ ባስጀመረበት ወቅት " በአገሪቱ ውስጥ ባለው ወቅታዊ ሁኔታ እና በቀጣዩ ትግል አቅጣጫ ላይ ዝርዝር ውይይት ተደርጓል " ያለ ሲሆን " በዚህ መሠረት በጦርነቱ ጉዳት፣ በኢኮኖሚ ውድቀት ምክንያት የማህበራዊ መቃወስና ወደ መፍረስ እየተኬደ ካለው መንገድ ኢትዮጵያን ለመታደግ ትኩረት ይሰጣል " ብሏል።

#OFC #AddisAbaba

@tikvahethiopia

EBS TV

29 Dec, 14:46


#Update

ማንነታቸው ባልታወቁ  ታጣቃዎች የታገቱት ሦስት የትግራይ ቴሌቪዥን ጋዜጠኞች በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን አስገደ ወረዳ ሜይሊ ተብሎ በሚጠራ ቦታ በሚገኝ እስር ቤት እንደሚገኙ የትግራይ ቴሌቪዥን ማረጋገጡን አስታውቋል።

ጋዜጠኞቹ ከህገ-ወጥ የወርቅ ማዕድን ፍለጋ እና ዝውውር ጋር ተያይዞ ስለሚነሳው ጉዳይ ለማጥራት በተሰማሩበት ነው በታጣቂዎች መታገታቸው የተበገረው።

አሁን ላይ ጋዜጠኞቹ እስር ቤት እንዳሉ ተነግሯል።

@tikvahethiopia

EBS TV

29 Dec, 14:46


#Update : ጅቡቲ የሚገኙት የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞትዎስ (ዶ/ር) ከጅቡቲው ፕሬዚዳንት እስማኤል ኦመር ጊሌ ጋር ተገናኝተው ውይይት አድርገዋል።

የውይይቱ ዓላማ የትውውቅ እና በሁለቱ ወንድማማች ሀገሮች መካከል ያለውን የቆየ ወዳጅነት ለማጠናከር ነው የተባለ ሲሆን በውይይታቸው የሁለትዮሽና አህጉራዊ ጉዳዮችን አንስተው መምክራቸውን በጅቡቲ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የተገኘው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia

EBS TV

29 Dec, 14:46


#Update

" ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቃዎች ታግተዋል " የተባሉት  3 የትግራይ ቴሌቪዥን ጋዜጠኞች ሜይሊ ተብሎ በሚጠራ ቦታ በሚገኝ እስር ቤት እንደሚገኙ የትግራይ ቴሌቪዥን ከደቂቃዎች በፊት ማረጋገጡ ይታወሳል።

አሁን ከስፍራው በተገኘው መረጃ ሦስቱ ጋዜጠኞች ከእስር ተለቀዋል።

የጋዜጠኞቹ መፈታት በማስመልከት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው ፥ ጋዜጠኞቹ መረጃ በማሰባሰብ ስራ እያሉ በአከባቢው በሚገኙ ፓሊስ እና ሚሊሻዎች ነው የተያዙት።

ጋዜጠኞቹ በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ ከወረዳው የፀጥታ እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት መካከል በተደረሰ መግባባት ከሰዓታት እስር ሊለቀቁ ችለዋል። 

ጋዜጠኞቹ በአከባቢው ያለውን ህገ-ወጥ የወርቅ ማዕድን ቁፋሮና ዝውውር የሚመለከት የምርመራ ዘገባ በመስራት ላይ እንደነበሩ ለወረዳው የፀጥታ እና አስተዳደር አካላት የተናገሩ ሲሆን የጋዜጠኞች እስር እና እንግልት በክልሉ ካለው የፓለቲካ ቀውስ ትስስር አለው ተብሏል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
  
@tikvahethiopia 

EBS TV

29 Dec, 13:05


#Tigray

በወርቅ ማዕድን ቁፋሮ እና ዝውውር ዙሪያ መረጃዎች በማሰባሰብ ላይ የነበሩ የትግራይ ቴሌቪዥን ጋዜጠኞች በታጣቂዎች መታገታቸውን ተቋሙ አስታወቀ።

የታገቱት ጋዜጠኞች ብዛት 3 እንደሆነ የገለፀው የሚድያ ተቋሙ ሞባይላቸው ከአገልግሎት ውጪ መደረጉን ጨምሮ ገልጿል። 

ትግራይ ቴሌቪዥን " በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን ከህገ-ወጥ የወርቅ ማዕድን ፍለጋ እና ዝውውር ጋር ተያይዞ የሚነሳው ጉዳይ ለማጥራት የተሰማሩ ጋዜጠኞች ናቸው በታጣቂዎች የታገቱት " ሲል አሳውቋል።

ሦስት አባላት የያዘ የጋዜጠኞች ቡድን ዛሬ ታህሳስ 20/ 2017 ዓ.ም ከረፋዱ 3:00 ጀምሮ በአስገዳ ወረዳ ' ሜይሊ ' ተብሎ ከሚጠራ ልዩ ቦታ በምትገኘው መንደር ነው የታገቱት ተብሏል።

ጋዜጠኞቹ በአከባቢው ስላለው ህገ-ወጥ የወርቅ ማዕድን ቁፋሮ እና ዝውውር በማስመልከት በአካል ቦታው ድረስ በመሄድ የአከባቢው ነዋሪዎች ፣ አርሶ አደሮች እና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ሲያነጋግሩ እንደሰነበቱ የገለፀው የትግራይ ቴሌቪዥን " የጋዜጠኞች ቡድኑ በስራ እያለ በታጣቂዎች ሊታገት እና ሊታሰር ችሏል " ሲል አመልክቷል።

የታገቱት የጋዜጠኞች ቡድን ከረፋዱ 4:00 ጀምሮ ሞባይላቸው ከአገልግሎት ውጪ በመደረጉ ምክንያት ያሉበት ሁኔታ እና ድህንነታቸው ማረጋገጥ እንዳልተቻለ አመልክቷል።

ጋዜጠኞቹን የሚመለከት መረጃ ለመጠይቅ በአከባቢው ለሚገኙ የመንግስት አመራሮች ተደጋጋሚ የስልክ ሙከራ ቢያደርግም እንዳልተሳከለት የትግራይ ቴሌቪዥን አሳውቋል።

እገታውን ስለፈጸሙ ታጣቂዎች ማንነት በዝርዝር የተባለ ነገር የለም።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የትግራይ ቴሌቪዥን ነው።

@tikvahethiopia

EBS TV

03 Dec, 19:00


#Update

" ጊዜያዊ አስታዳደሩ የወሰደው እርምጃ ህዝቡን ወደአላስፈላጊ ቁጣና ግርግር የሚያስገባ ነው " - የመቐለ ከተማ ምክር ቤት አስተባባሪ ቋሚ ኮሚቴ 

የመቐለ ከተማ ም/ቤት አስተባባሪ ቋሚ ኮሚቴ የትግራይ ጊዚያዊ  አስተዳደር ከህዳር 23/2017 ዓ.ም ጀምሮ የሰጠው የመቐለ ከንቲባ ሹመት ከመቃወም አልፎ " ህገ-መንግስት የጣሰ ተግባር " ብሎታል። 

የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ ህዳር 24/ 2017 ዓ.ም ከሰአት በኋላ ባወጣው የአቋም መግለጫ ፥ ህዳር 23/2017 ዓ.ም በመቐለ ከተማ አስተዳደር በምክር ቤት አብላጫ ድምፅ የተሾሙ ከንቲባ በስራ ላይ እያሉ የምክር ቤት እና የህዝብ ሉአላውነት በመጣስ ፓሊስ ስራቸው እንዳይሰሩ አግዷል ብሏል።

" በዚያው ቀን ከሰዓት በኋላ ህጋዊ ያልሆኑ ከንቲባ በአስተዳደሩ አንድ አዳራሽ መግለጫ እንዲሰጡ ተደርገዋል " ሲልም ገልጿል።

" በምክር ቤት በስርዓት የተሾሙ ከንቲባ ወደ ቢሯቸው እንዳይገቡ የመቐለ ፓሊስ ከህግ አገባብ ውጪ ፅህፈት ቤታቸው በማሸግ ህዝብ አገልግሎት እንዳይገኝ አስተጓጉለዋል " ሲል ከሷል።

" የፓሊስ ኢ-ህጋዊ ተግባር  አገልግሎት ያጣ ህዝብ ወዳልተፈለገ ሽብርና ቀውስ እንዲገባ አድርገዋል " ብሏል።

በተጨማሪ የቋም ኮሚቴው በመግለጫ ምን አለ ?

👉 " በህገ-መንግስት የተሰጠ ስልጣን በመቀማት አምባገነን ስርዓት ለመትከል የተፈፀመ ተግባር ነው ይህንን እንኮንናለን። የተፈፀመው አግባብነት የጎደለው ተግባር በአስቸኳይ እንዲታረም ጥሪ እናቀርባለን። "

👉 " የመቐለ ፓሊስ አመራር በህገ-መንግስት የተሰጠው ተግባርና ሃላፊነት ወደ ጎን በመተው የፈፀመው ህገ-ወጥ ተግባር በማስተካከል በምክር ቤት የተሾሙ ከንቲባ ረዳኢ በርሀ (ዶ/ር) ሳይውል ሳያድር  ስራቸው እንዲሰሩ እና አገልግሎት እንዲሰጡ እንዲያደርግ እንጠይቃለን "

👉 " የትግራይ የፀጥታ ሃይሎች የተፈፀመው የህግ ጥሰት በመገንዘብ ህግ እንዲያከብሩ ጥሪ እናቀርባለን "

👉 " የመቐለ ከተማ ህዝብ ህገ-ወጥ ተግባሩ በመቃወም ከምክር ቤቱ ጎን እንዲሰለፍ ጥሪ እናቀርባለን "

👉 " የትግራይ ጊዚያዊ  አስተዳደር የምክር ቤቶች ሉአላዊ ስልጣን በመጣስ የወሰደው እርምጃ ህዝቡ ወደ አላስፈላጊ ቁጣና ግርግር የሚያስገባ መሆኑ በመገንዘብ በዚሁ በህገ-መንግስት ጥሰት የተሳተፉት አካላት በህግ እንዲጠይቃቸው ጥሪ እናቀርባለን "

... ብሏል።



በፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ የተሸሙት አዲሱ ከንቲባ ብርሃነ ገ/የሱስ መደበኛ ህዝባዊ አገልግሎት መስጠት አንደሚጀምሩ ታማኝ ምንጮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ መረጃ ሰጥተውታል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

EBS TV

03 Dec, 19:00


" ልመና አልነበረም ማለት አይደለም ፤ አጉን ግን እየተባባሰ ሄዷል ! ... የኑሮ ውድነቱን መቋቋም አቅቶት ህብረተሰቡ መድረሻ እያጣ ነው " - አቶ አበረ አዳሙ

የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዛሬ 8ኛ መደበኛ ሰብሰባው አድርጎ ነበር።

በዚህም ወቅት ከም/ቤት አባላት ለንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር።

ሚኒስትሩም ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባል የሆኑ አቶ አበረ አዳሙ ምን ጠየቁ ?

" 1. በዓለም አቀፍ ተጨባጭ ሁኔታዎች ምክንያት ከውጭ የሚገቡ ሸቀጦች ዋጋ የኑሮ ውድነቱን እያናረው ከመሆኑንም በላይ በተለይ በሀገር ውስጥ ምርቶች ላይ የሚደረገው ምክንያት የለሽ ጭማሪ የህዝቡን ኑሮ እንዲመሰቃቀል አድርጎታል።

ለምሳሌ ፦
- ጤፍ
- ስንዴ
- ምስር ... ሆነ ሌሎች የአትክልት እና ፍራፍሬ ምርቶች በሀገር ውስጥ የሚመረቱ ቢሆኑም በጥራት እና በብዛት ገበያ ላይ አይገኙም ፤ ቢገኙም ዋጋቸው እጅግ የተጋነነ በመሆኑ በቀላሉ የሚቀመስ አይደለም።

የችግሩ ምንጭ ደግሞ ሰው ሰራሽ መሆኑ አይካድም።

ህጋዊ ነጋዴው በኮንትሮባንድ ነጋዴዎች እና ለደላላ እየተጠለፈ መስራት ከማይችልበት ደረጃ ላይ ደርሷል።

በዚህ የተነሳ ' ልጆቼን የማበላቸው አጣሁ ' የሚሉ አዛውንቶች፣ ' ጋሽዬ ቁራሽ የዳቦ መግዣ ስጠኝ ራበኝ ' የሚሉ አንጀት የሚበሉ በርካታ ህጻናትን ማየት በከተማችን እየተለመደ መጥቷል።

ልመና አልነበረም ማለት አይደለም አሁን ግን እጅግ እየተባባሰ ሄዷል።

ደላላው ዋጋ ይተምናል ፤ ደላላው ዋጋ ይሰቅላል ቢፈልግም ያወርዳል ለዚህም አንድ ወቅት የሱዙኪ መኪና ዋጋን ሰማይ አድርሶ መሬት አስልሶት የነበረበትን አጋጣሚ ማስታወስ ይቻላል።

በአጭር አነጋገር ደላላ የንግዱን ስርዓት /ሲስተም እንደ ተባይ ወሮታል። በዚህም የኑሮ ውድነቱን መቋቋም አቅቶት ህብረተሰቡ መድረሻ እያጣ ነው።

ጥቅሙን የሚያገኘው  በጋ ከክረምት ደም ታፍቶ ያመረተው አርሶ አደሩ ቢሆን መልካም ነበር።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶ ህገወጥ ነጋዴዎች እና ደላላዎችን ስርዓት ሊያሲዝ የሚችል ዘላቂነት ያለው ስራ ከመስራት ይልቅ አልፎ አልፎ ወይም የሆነ አጋጣሚ ሲፈጠር ' ይሄን ያህል የንግድ ድርጅቶችን አሽኩ / ልናሽግ ነው ' እያሉ በመገናኛ ብዙሃን ማስታወቂያዎችን ከማስተጋባት የዘለለ ፦
° የንግድ ተቋማቱ በምን ምክንያት እንደታሸጉ
° ምን አይነት ህጋዊ እርምጃ እንደተወሰደባቸው
° የማሸጉ እርምጃ ምን ውጤት እንዳስገኘ
° የንግድ ድርጅቶቹ ከታሸጉ በኃላ የመጣንው ለውጥ ለህዝቡ ሲያሳውቅ አይታይም።

በኑሮ ላይ ጠብ የሚል ለውጥ አይስተዋልም።

ታዲያ የሀገራችንን ገበያ እየመራ ያለው ንግድ ሚኒስቴር ነው ወይስ ደላላና ህገወጥ ነጋዴ ?

2. ለንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ተጠሪ የሆነው የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ከሚቆጣጠራቸው ተቋማት አንዱ መብራት ኃይል ነው። (በየጊዜው የመዋቅር መቀያየር ለውጥ ካለ ይቅርታ ጠይቃለሁ!)

ይሁን እንጂ የመብራት ተደራሽነት እና አግልግሎት አሰጣጥ በእጅጉ የተበላሸ ነው።

👉 ተደራሽነቱ ፍትሃዊነት የጎደለውና ለማዳረስ የተሞከረው ለረጅም አመታት የተተከሉ ፖሎች ሳይቀር ያለ አገልግሎት የቆሙበት፤

👉 ተዳረሰ የተባለውም በኃይል መቆራረጥ ችግር ተጠቃሚውን የሚያሰቃይ፤

👉 አገልግሎቱን ለማግኘት ያለ እፍረት በእጅ መንሻ / ጉባ ካልሆነ በቀር የማይሰራ ሰራተኛ የበዛበት ነው።

የሚያሳዝነው ደግሞ ጉቦ ወንጀል መሆኑ ቀርቶ መብት እስኪመስል ድረስ ዋጋ ተምነው ' ይህን ያህል አምጣ ' የሚሉ ሰራተኞች መብዛታቸው ነው።

በዚህ ከቀጠለ ምናልባትም ፓርላማውን ' የምቀበለው ጉቦ አንሶኛል እና ህግ አውጡልኝ ' ማለት የቀራቸው ይመስላል።

ይህ የእርሶን ተቋም ብቻ የሚመለከት አይደለም በርካታ ተቋማትን የሚያካትት ነው።

ክቡር ሚኒስትር ለመሆኑ ለእርሶ ተጠሪ የሆነው ባለስልጣን መ/ቤት ህዝቡን እያስለቀሰ የሚቀጥለው እስከመቼ ነው ? ይህንን ተቋም መቆጣጠርና ስርዓቱን ማስያዝ ያልተቻለው ለምንድነው ?

3. የኑሮ ውድነቱን ከሚያባብሱ ምክንያቶች አንዱ ነዳጅ ነው።

የዋጋው ማሻቀብ ምክንያቱ የሚታወቅ ቢሆንም ከዋጋው በላይ ሰልፉ ህዝቡን እያማረረ ይገኛል።

ከእጥረቱም በላይ ነዳጅ ለመቅዳት በሚደረግ ረጃጅም ሰልፍ ምክንያት የስራ ሰዓት ያለ አግባብ እየባከነ፣ የትራፊክ ፍሰቱን እያስተጓጎለ፣ እንዲያውም ሲል በህገወጥ መንገድ ነዳጅ ከሀገር እንዲወጣ ሰፊ በር እየከፈተ መሆኑን እማኝ መጥቀስ የሚያስፈልግ አይመስለኝም።

ክቡር ሚኒስትር ይህንን የተበላሸ አሰራር ስርዓት ማስያዝ የማን ኃላፊነት ይመስሎታል ? እባክዎ ለዚህ የተከበረ ም/ቤት እና ለብዙሃኑ የሀገራችን ህዝብ ተገቢውን መልስ ይስጡ። "

ሚኒስትሩ ምን ምላሽ ሰጡ ? ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-12-03

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia

EBS TV

03 Dec, 13:53


" እኔ ኢየሱስ ክርስቶስን እወደዋለሁ !! "

በሀገራችን ኢትዮጵያ ጨምሮ በመላው ዓለም ላይ በቢሊዮኖች ተመልካች ያለው የእንግሊዝ ፕሪሜየርሊግ ግብረሰዶማውያንን ለመደገፍ በሚል በየአመቱ ዘመቻ ያደርጋል።

ይህንን ዘመቻ የሚያደርገውም በእያንዳንዱ ክለብ አምበል ክንዶች ላይ ግብረሰዶማውያንን የሚገልጸውን ባዲራ / እንዲያደርጉ በማድረግ ነው።

ይህን የሊጉን ተግባር እጅግ በርካታ ሃይማኖተኛ ደጋፊዎች እና ተጫዋቾች ነው የሚያወግዙት።

በዘንድሮው ዓመት የሊጉ ፍልሚያ ኢፒስዊች ታውን የተባለው ክለብ አምበል እና የእስልምና እምነት ተከታዩ ሳም ሞርሲ " እኔ ሃይማኖቴ አይፈቅድልኝም " በማለት የግብረሰዶማውያንን ምልክት ሳያደርግ ቀርቷል።

ከዚህ ባለፈ ግን አንድ የሌላ ክለብ ተጫዋችና አምበል የክርስትና እምነት ተከታይ ክንዱ ላይ ምልክቱን ቢያደርግም ከላይ " እኔ ኢየሱስ ክርስቶስን እወደዋለሁ !! " የሚል ፅሁፍ ፅፎ በመግባቱ የሊጉን አስተዳደሮች እንዳስቆጣ በዚህም ቅጣት ሊጣልበት እንደሚችል ተሰምቷል።

ተጫዋቹ ማርክ ጉሂ ይባላል ፤ እድሜው 24 ሲሆን የአይቮሪኮስት ዝርያ ያለበት የእንግሊዝ ዜጋ ነው።

የሚጫወትለት ክለብ ክርስታል ፓላስ የሚባል ነው።

ይኸው ተጫዋች ነው ባለፈው ቅዳሜ ኒውካስትል ከተባለው ሌላኛው የሊጉ ክለብ ጋር ጨዋታቸውን ሲያደርጉ ግብረሰዶማውያንን የሚደግፈውን ምልክት ክንዱ ላይ ቢያጠልቅም ከላዩ " እኔ ኢየሱስ ክርስቶስን እወደዋለሁ ! " የሚል ፅሁፍ ፅፎበት በመግባት ጨዋታውን አድርጓል።

በዚህም የሊጉን አስታዳዳሪዎች አስቆጥቶ ቅጣት ሊጥሉበት እንደሆነ ተነግሯል።

የእንግሊዝ ፕሪሜየርሊግ ግብረሰዶማውያንን ለመደገፍ በየዓመቱ አምበሎች የግብረሰዶማውያን ምልክት የሆነውን የተለያየ ቀለም ያለው ምልክት በክንዳቸው አጥልቀው እንዲጫወቱ ያደርጋል።

#Guehi #Christian #PremierLeague

@tikvahethiopia

EBS TV

03 Dec, 12:31


" ሃይማኖቴ አይፈቅድልኝም !! "

" ሃይማኖቴ አይፈቅድልኝም ! " ያለው የእግር ኳስ ተጫዋች ግብረሰዶማውያን ለመደገፍ ሲባል ክንድ ላይ የሚጠለቀውን ምልክት ሳያደርግ ቀርቷል።

በዓለም ላይ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ የእግር ኳስ ፍልሚያ አፍቃሪያን እንዳሉ ይታወቃል።

ከየትኛውም ሀገራት በላይ ደግሞ የአውሮፓ ሀገራት ውስጥ የሚካሄዱት ፍልሚያዎች እጅግ ብዙ ተመልካች ያላቸውና ከፍተኛ ተወዳጅነትን ከፉክክር ጋር ያጣመሩ ናቸው።

በተለይም የእንግሊዝ ፕሪሜየርሊግ በሀገራችን ኢትዮጵያ ሳይቀር እጅግ ከፍተኛ ተወዳጅነት ያለውና ብዙ ተመልካች ያለው ነው።

ከህጻን እስከ አዋቂ፣ አዛውንቶች ሳይቀሩ ነው ፍልሚያውን የሚከታተሉት።

ነገር ግን በየዓመቱ ይህ የእግር ኳስ ፍልሚያ የሚደራበት ወር በተለይም ሃይማኖተኛ የሆኑ የእግር ኳስ ተመልካቾችን የሚያስቀይም ነው።

ምክንያት ? ሊጉ ውስጥ ግብረሰዶማውያንን ለመደገፍ ሲባል ዘመቻ ስለሚካሄድበት ነው።

ሰዎቹ " እኩልነትን ለማምጣት " ይበሉት እንጂ በበርካታ ሃይማኖተኛ እግር ኳስ ተመልካቾች እና ተጫዋቾች ዘንድ የሚወገዝ ተግባር ነው የሚፈጽሙት።

የፕሪሚዬር ሊግ ክለቦች ለግበረሰዶማውያን ያላቸውን ድጋፍ ለማሳየት አምበሎቻቸው የግብረሰዶማውያኑን መለያ ምልክት ክንዳቸው ላይ እንዲያጠልቁ ያደርጋሉ።

ይህን ዘመቻ የሚያደርጉትም እኤአ ከኅዳር 29 እስከ ታኅሣሥ 5 ነው።

ከቀናት በፊት በነበረ አንድ ጨዋታ ላይ ግን የአንድ ክለብ አምበል " እኔ ሃይማኖቴ አይፈቅድልኝም " በማለት ምልክቱን ሳያድረግ ቀርቷል።

የተጨዋቹ ስም ሳም ሞርሲ ይባላል ፤ ኢፕስዊች ታውን የተባለው ክለብ አምበል ነው።

በእምነቱም የእስልምና እምነት ተከታይ ሲሆን የግብፅ ዜጋ ነው።

ይኸው ተጫዋች ነው ቡድኑ ኖቲንግሃም ፎረስት ከተባለው ቡድን ጋር በተጫወተበት ወቅት ክንዱ ላይ ምልክቱን " አላጠልቅም " ብሎ ጨዋታውን ያካሄደው።

ክለቡ ባወጣው መግለጫ ምልክቱን ያላደረገው " በሃይማኖቱ ምክንያት ነው ፤ ውሳኔውን እናከብራለን " ብሏል።

ክለቡ አክሎም ፤ የግብረሰዶማውያኑን ምልክት የሚያሳየውን የአምበሎች መለያ በኩራት እንደሚደግፍ ፤ ከግብረሰዶማውያን ማኅበረሰብ ጋር አብሮ እንደሚቆም ፤ እኩልነት እና ተቀባይነት እንዲንሰራፋ እንደሚሰራ ገልጿል።

ከሳም ሞርሲ በስተቀር ሌሎች የፕሪሚዬር ሊጉ አምበሎች የግብረሰዶማውያንን ባንዲራ አጥልቀው ሲጫወቱ ነበር።

#SamMorsy #PremierLeague #Muslim

@tikvahethiopia

EBS TV

03 Dec, 12:31


#ሹመት

የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ከሰሞኑን 6 አዳዲስ ሹመቶች ሰጥተዋል።

ከስድስቱ ሽመቶች ሁለቱ በደብረፅዮን ገ / ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት የተሾሙትን በማንሳት የተሰጠ ነው።

በዚሁ መሰረት ፕሬዜዳንቱ ከህዳር 20/2017 ዓ.ም  ጀምሮ የሚፀና በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት የመቐለ ከንቲባ በመሆኑ የተሾሙት ረዳኢ በርሀ (ዶ/ር) በመሻር በብርሃነ ገ/ዮሱስ ተክተዋል።

የትግራይ ትምህርት ቢሮ ምክትል የስራ ሃላፊ ሆነው ሲያገለግሉ ቆይተው ከህዳር 17/2017 ዓ.ም ጀምሮ በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት የዓዲግራት ከንቲባ በመሆን የተሾሙት ረዳኢ ገ/ሄር ምትክ ኪ/ማርያም ወ/ሚካኤል ምክትል የቢሮ ሃላፊ ሆነው ተሹመዋል።

ፕሬዜዳንቱ በጡሮታ በተገለሉት ሓዱሽ ካሱ ምትክ ዶ/ር ገብሩ ካሕሳይ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ምክትል ፅሕፈት ቤት ሃላፊ አድርገዋቸዋል።

ኮማንደር ተስፋይ ገ/ማርያም በምክትል ኮሚሽነር መዓርግ የወንጀል ማጣራት ሃላፊ ፤ ኮማንደር ጌታቸው ኪሮስን በምክትል ኮሚሽነር መዓርግ የወንጀል መከላከል ሃላፊ እንዲሁም አቶ ሃይላይ ኣብራሃ በምክትል ኮሚሽነር መዓርግ የሰው ሃይል ልማት ዘርፍ ሃላፊ አደርገው ሹመዋል።

በቅርቡ የግድያ ሙከራ እንደተደረገባቸው በተናገሩት የትግራይ ማእከላዊ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሰለሞን መዓሾ ምትክ ጉዕሽ ግደይ ሓድጉ የትግራይ ማእከላዊ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሆነው በፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ደብዳቤ መሾማቸው ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia 

EBS TV

03 Dec, 04:25


" የቀድሞ / ነባር ነኝ አይደለሁም የሚለውን ከፓሊስ እንነጋገርበታለን ፤ ያኔ ግልፅ ይሆንላቸዋል !! " - አቶ ጌታቸው ረዳ

ባለፈው ሳምንት ህዳር 17/2017 ዓ.ም በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በሚመራው ህወሓት ቡድን ምክትል ሊቀ መንበር የሆኑት አቶ አማኒኤል አሰፋ በሰጡት መግለጫ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳን " የቀድሞ ፕሬዜዳንት " ሲሉ ጠርተዋቸው ነበር።

ህዳር 22/2017 ዓ/ም በመቐለ ከተማና ዙሪያዋ ከሚገኘው ደቡባዊ ምስራቃዊ ዞን ከተውጣጡ ወጣቶች ጋር የተወያዩት ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በመድረኩ ለአቶ አማኒኤል ንግግር በስሜትና ኃይለ ቃል በመጠቀም " እሳቸው ለሚገኙበት ቡድን " ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ምን አሉ ?   

" ባለፈው ጊዜ አንድ ሃላፊ ነኝ ባይ በመንግስት ሚድያ ' ነባር / የቀድሞ ፕሬዜዳንት ' ሲል ሰምታቹሃል ? ተልካሻ ነው። የቀድሞ / ነባር ነኝ አይደለሁም የሚለውን ከፓሊስ እንነጋገርበታለን ፤ ያኔ ግልፅ ይሆንላቸዋል።

እነዚህ አንድ ቀን ቁምነገር ሰርተው አያውቁም። መዋቅራቸው ስርቆት ላይ የተሰማራ ነው። አሁን የልዩነት ነጥቡ ፓለቲካ መሆኑ ቀርቷል። 

የኔ ሳምንት ይሁን ወር በዚህ ወንበር መቆየት ያን ያህል አያሳስበኝም ፤ ይህን አደገኛ ቡድን ግን የወንጅል ትስስር (Crime network ) ነው የሚመራው።

በሰሜን ምዕራብ ማእከላዊ ዞኖች ወርቅ ፣ መዳብ እና ሌላ ማዕድናት ያካተተ ዘረፋ የሚያካሄደው ይህን በወንጀል የተሳሰረ ቡድን ነው ፤ ስለሆነም ዞኖቹን ከሱ ቁጥጥር ውጪ እንዲወጡ ፍላጎት የለውም።

ቡድኑ ይህን የዘረፋ ባህሪ አሁን ያመጣው አዲስ ነገር አይደለም ፤ የቆየበት ነው ፤ ሃሜት አይደለም እየነገርኳችሁ ያለሁት ተደራጅቶ እየዘረፈ ነው ያለው።

በስንፍናችን ይሁን ድንገት ወደ ስርቆት ኔትወርክ ያልገባን ሰዎች አለን። ስለሆነም እነዚህን ያለ የሌለ ውሸት ፈጥሮ ስማችን በማጥፋትና በማጠልሸት ' ከጨዋታ ውጪ ማድረግ አለብን ' ብለው ነው በኛ ላይ የዘመቱት።

ስለዚህ ይህንን የቡድኑን ተግባር እንደ ፓለቲካ ሳይሆን እንደ ሌብነት ነው መቆጠር ያለበት፤ ስለሆነም ቡድኑ አንድ እሱን የመሰለ ሌባ አቀፎ ለመያዝ የመጣበት አከባቢ ሳይለይ አባሉ ያደርገዋል " ብለዋል። 


#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

EBS TV

22 Nov, 19:32


🔴 "... አጭበርባሪዎቹ ከቦታው ዘወር ሲሉ በአካውንቱ ላይ ምንም ገንዘብ አይገኝምና እንደ አገር ታንቀው የሞቱ ወገኖች ጭምር እንዳሉ እናውቃለን " - የተወካዮች ምክር ቤት አባል

🔵 " ከማጭበርበር ጋር በተያያዘ ከፍተኛ ሥራ እየደሰራን ነው "  - ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ

የተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በታሪክ ለመጀመሪያ በመስሪያ ቤቱ በአካል በመገኘት የሳፋሪኮም  ኢትዮጵያን የሥራ አፈጻጸምን ገምግሟል።

ኮሚቴው እስከዛሬ ድረስ ድርጅቶችን ሲገመግም የነበረው በሚላክለት ሪፖርት ብቻ የነበረ ከመሆኑ አንጻር የአሁኑ ግምገማ በአካል በመገኘት መሆኑ ግምገማውን ለየት ያለ አድርጎታል።

ድርጅቱ በግምገማው ወቅት፣ የሳፋሪኮም ደንበኞች ወደ ኢትዮ ቴሌኮም ተጠቃሚዎች በሚደውሉበት ወቅት ተጨማሪ ክፍያ እየከፈሉ መሆኑን ጠቅሶ፣ ይኼው ክፍያ እንዲቀርላቸው፣ የታወር ማስፋፊያ ፈቃድ በቅድመ ሁኔታ እንዲሰጥ ኮሚቴው ለመንግስት እንዲያሳስብለት ጠይቋል፡፡

ኮሚቴው በበኩላቸው፣ በቀረበው ጥያቄ ላይ ተወያይቶ ለተጠየቀው የድጋፍም ሆነ የፈቃድ ጥያቄ ምላሽ እንደሚሰጡ ቃል ገብቷል።

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ፣ በሦስት አመታት ውስጥ ከ6 ሚሊዮን በላይ ደንበኞችን እንዳፈራ፣ ከ12 ባንኮች ጋር እየሰራ መሆኑን፣ በዘጠኝ የክልል ከተሞች የኔቶርክ አገልግሎት ተደራሽ ማድረጉን የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዊም ቫንሄልፑት ገልጸዋል፡፡

በግምገማው የተገኙት የምክር ቤት አባላት ስለሳፋሪኮም የሥራ ሁኔታ የቀረበላቸውን ገለጻ ካዳመጡ በኋላ በአጭር አመት ውስጥ ድርጅቱ ያሳየው ውጤት ከፍተኛ መሆኑን በአንክሮ ገልጸው፣ በአንጻሩ ደግሞ የተለያዩ ጥያቄዎችን አንሸራሽረዋል፡፡

የምክር ቤት አባላት ያነሷቸው ጥያቄዎች ምንድን ናቸው ?

➡️ ወ/ሮ ሙሉነሽ የተባሉ የም/ቤት አባል፣ “ ድጅታል ካሽ ፓይመንት ከፋይናንሻል ሰርቪስ አንፃር ለከስተመሩ ምን ያህል ሴኩይር ነው ?

ለምሳሌ በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ ማጭበርበሮች ይከናወናሉ፤ አንዳንድ የንግድ / የሽያጨ ተቋማት ኦንላይን ላይ ሽያጭ ተሽጧል ይባልና ገንዘቡ በአካውንት እንደተላከ የሚያሳይ ጊዜያዊ መልዕክት ይገባል ፤ ከዚያ በኋላ አጭበርባሪዎቹ ከቦታው ዘወር ሲሉ በአካውንቱ ላይ ምን ገንዘብ የማይገኝበት ሁኔታ በመኖሩ እንደ አገር ታንቀው የሞቱ ወገኖች ጭምር እንዳሉ እናውቃለን፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ የተጭበረበሩ እንዳሉም እናያለንና ይህን ጉዳይ ምን ያህል አስተማማኝ ነው ?

ድርጅቱ የሚሰራው ከ12 ባንኮች ብቻ ጋር እንደሆነ ተነግሯል፡፡ ለምን ከቀሪ ባንኮች ጋር አብሮ አልሰራም ? ከሌሎች ባንኮችም ጋር በመስራት ሰርቪሱ ሰፋ እንዳይል ያደረገው ቻሌንጅ ምንድን ነው ? ”
ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

➡️ አቶ ከድር የተባሉ የምክት ቤት አባል ደግሞ ፥ " ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር የምትሰሯቸው ሥራዎች ውጤታማ ናቸው ውይ ? ድርጅቱ ከመንግስት ጋር በገባው ውል አንጻር ተጽዕኖ አለበት ወይ ? ድርጅቱስ በውሉ መሠረት እየሰራ ነው " ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

➡️ ሌላኛው የምክር ቤት አባል ፥ " የድርጅቱ ዓላማ ኢትዮ ቴሌኮም ተደራሽ ባላደረጋቸው አካባቢዎች አገልግሎቱን ተደራሻ ማድረግ ከመሆኑ አንጻር፣ የመሠረተ ልማት ተደራሽነት በሌለባቸው አካባቢዎች በቂና የተለዬ ቴክኖሎጅ ከመጠቀም አንጻር ምን አድርገችኋል?

የኔቶርክ ጥራቱ ከኢትዮ ቴሌኮም የተሻለ ተብሎ ነው የቀረበቀው ነገር ግን አዲስ አበባ ራሱ የኔቶርክ ጥራት አለ ወይ ?
" ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

የሳፋሪኮም በበኩሉ፣ " ከማጭበርበር ጋር በተያያዘ ከፍተኛ ሥራ እየደሰራን ነው " ሲል የኮሚቴ አባል ላነሱት ጥያቄ ምላሽ ሰጥቷል፡፡

'ተጭበረበርን' የሚሉ ሰዎች ሪፖርት እንዳደረጉ ገንዘቡ ሆልድ እንዲሆን እንደሚያደርግ፣ ከዚያ ጉዳዩ በሕግ ታይቶ እርምጃ እንዲወሰድ እንደሚያደርግ ድርጅቱ አስረድቷል፡፡

ከ12 ባንኮች ባለፈ ከሌሎች ባንኮች ጋር ለምን እንዳልተሰራ ለቀረበው ጥያቄ ፥ የባንኮቹ ዝግጅትና የድርጅቱ ዝግጅት የተጣጣመ አለመሆኑን በምክንያት ጠቅሶ፣ ይህ ሲስተካከል ከሁሉም ባንኮች ጋር አብሮ መስራቱ የማይቀር እንደሆነ ጠቁሟል፡፡

ቴሌ ተደራሽ ባላደረጋቸው፣ የመሰረተ ልማት ችግር ባለባቸው አካባቢዎች አገልግሎቱን ተደራሽ ከማድረግ አንጻር ምን እየሰራ እንደሆነ መጠይቅ የቀረበለት ድርጅቱ፣ የተቻለውን ያክል እየሰራ እንደሆነ፣ የጸጥታ ችግር ግን ፈተና እንደሆነበት ተናግሯል።

ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር ያለው ሥራና ውድድር ከባድ ቻሌንጅ እንዳለው የገለጸው ድርጅቱ ከውል ጋር በተያያዘ ለቀረበለት ጥያቄ በእርግጥ በውሉ መሠረት እየሰራ እንደሆነ ገልጿል።

የኔቶርክ ጥራት በተመለከተ ለቀረበለት ጥያቄም፣ የኔቶርክ ጥራቱ የተሻለ እንደሆነ በመጥቀስ ምላሽ ሰጥቷል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

EBS TV

22 Nov, 19:02


🔈 #የመምህራንድምጽ

🔴 “ ‘ለምን ደመወዛችን ተቆረጠ’ ብለው የጠየቁ 66 መምህን  ታስረዋል” - የኮሬ ዞን መምህራን ማኀበር

🔵 “የታሰሩት በመምህራን ላይ ድንጋይ በመወርወር ሌሎቹን በመበጥበጣቸው ነው” - የዞኑ ትምህርት መምሪያ

🟢 “ምቹ ሁኔታ ላይ አይደለሁም። ሥራ ላይ ነኝ ስንት ሰዓት እንደምጨርስ አላውቅም”  - የዞኑ ሰላምና ጽጥታ ቢሮ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ሳርማሌ ወረዳ የሚገኙ መምህራን ደመወዛቸው ያለፈቃዳቸው በመቆረጡ እንዲመለስላቸው በመጠየቃቸው መታሰራቸውን የዞኑና የክልሉ መምህራን ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

የዞኑ መምህራን ማኀበር ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ጭበጮ ለቲክቫህ በሰጡት ቃል፣ “‘ደመወዛችን ለምን ተቆረጠ’ ብለው የጠየቁ 66 መምህራን ታስረዋል” ብለዋል።

“‘የተቆረጠው ደመወዝ ከኛ ፈቃድና ስምምነት ውጪ ስለሆነ ይመለስልን’ የሚል ጥያቄ አቅርበው ነው የታሰሩት። ያለፈቃዳቸው ደመወዛቸው መቆረጡ፤ መታሰራቸው አግባብ አይደለም። አግባብ አለመሆኑን ለሚመለከተው አካል አሳውቀናል” ነው ያሉት።

“ከዞኑ መምህራን ማኀበር የታሰሩትን ለማነጋገር ሂደው የወረዳ አመራሮች የታሰሩት እንዳይጠየቁ ጭምር ከልክለዋል” ያሉት ሰብሳቢው፣ “ጥያቄያቸውን በውይይት መመለስ ሲገባችሁ ማሰር፣ መደብደብ፣ ማንገላታቱ ስህተት ነው” በሚል እየሞገቱ መሆኑን አስረድተዋል።

ስለጉዳየለ ማብራሪያ የጠየቅነው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማኀበር በበኩሉ፣ የመምህራኑ መታሰር ከዞኑ መምህራን ማኀበር ሪፓርት እንደተደረገለት በመግለጽ፣ “ያለአግባብ ማንም ተነስቶ ደመወዝ ቆርጦ መውሰድ ሕገወጥነት ነው” ሲል ወንጅሏል።

ከላይ ላሉት ለሚመለከታቸው አካላት አሳውቃችኋል? በማለት የጠየቅናቸው የማኀበር ፕሬዚዳንት አቶ አማኑኤል ጳውሎስ፣ የመምህራኑን መታሰር አረጋግጠው፣ “ትላንት ነው ከዞኑ ሪፖርት የተደረገልን። ለሚመለከታቸው አካላት አሳውቀናል” ብለዋል።

ያለፈቃዳቸው ደመወዝ መቁረጥና ለምን? ብለው የጠይቁ መምህራኑን ማሰር አግባብ ነው? የሚል ጥያቄ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ የቀረበላቸው የኮሬ ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሰረበ አሻግሬ፣ “ደመወዛቸው የተቆረጠው በፈቃዳቸው” ነው ሲሉ አስተባብለዋል።

ማኀበሩ ለእናንተም እንዳሳወቀ፤ ያለፍቃዳቸው እንደተቆረጠ፣ መምህራኑ እንደታሰሩ ነው የገለጸው፣ ፤ ይሄ ለምን ሆነ? በሚል ላቀረበሰነው ጥያቄ፣ “የሰርማሌ ወረዳ መምህን ጋር ተገናኝቻለሁ። ደመወዛቸው የተቆረጠው አሁን አይደለም፤ ፈቅደውም ነው” ብለዋል።

የኃላፊው ዝርዝር ምላሽ ምንድን ነው?

“ አንድ መፅሐፍ ለአንድ ተማሪ የሚል በሁሉም አካባቢ ወላጅም፣ ሠራተኞችም፣ ተማሪም እንዲተባበር የሚል አገር አቀፍ ጉዳይ አለ። የዞኑ አመራሮች ተስማምተው ነው ወደ ታች የወረደው።

የትምህርት ቤቱ መምህራን ባለሉበት ውይይት ተካሂዷል። ተስማምተው ደመወዛቸው ከተቆረጠ ቆይቷል። ሐምሌና ነሐሴ አካባቢ ነው የተቆረጠው። በተቆረጠ ጊዜ ነበር መቆረጡ ልክ አይደለም ብለው ማመልከት የነበረባቸው።

ተስማምተው ከተቆረጠ በኋላ የሳርማሌ ወረዳ ብቻ ይህንን ተግባሪዊ ሲያደርግ የከተማ አስተዳደርና ጎርካ አላደረገም። ግን ዞን ማዕከሉም ተግባራዊ አድርጓል 25 ፐርሰንቱን።

በመምህራኑ ‘እንዴት ሌሎች አካበቢ ያሉ መምህራን ሳይቆርጡ የኛ ብቻ ተቆረጠ? ስለዚህ ገንዘባችን ይመለስ’ የሚል ጥያቄ ነው የተነሳው መጀመሪያ። ገንዘብ ይመለስ የሚለው ነገር በጋራ እንነጋገራለን።

መምህራን በሁለት ነው የተከፈሉት። ግማሹ ‘እያስተማርን እንጠይቅ’፤ ግማሹ ‘ሙሉ ለሙሉ ትምህርት እናቁም’ የሚል ነው። የተወሰኑት ለማስተማር ክፍል ሲገቡ የተወሰኑት ደግሞ ድንጋይ ይዞ የሚሄድ፤ ተማሪ ይውጣ የሚል አለ።

በመምህራን መካከል ግጭት ተፈጠረ። የተቆረጠው ገንዘብ ይመለስ በመባሉ ሳይሆን በመምህራኑ መካከል በተፈጠረው ግጭት ነው የታሰሩት። ችግር የፈጠሩ ሰባት መምህራን ነበሩ ትላንት የታሰሩት። 

መምህራኑ የታሰሩት ችግር ፈጥረው ነው ሳይፈጥሩ? የሚለውን  እንዲያረጋግጡ ለአራት ዞኑን መምህራን ማኀበር ወደ ታች እንዲወርዱ አሳይመንት ሰጥቻሁ። ትላንት ነበር አሳይመንት የሰጠሁት እነርሱ ግን የወረዱት ዛሬ ነው።

‘እንደገና ደግሞ ሌሎች መምህራን ታስረዋል’ ሲባል በምን ምክንያት ? ስል በፊት የታሰሩት መምህራን ለምን ታሰሩ ? ብለው ሊረብሹ መጥተው ነው የሚል መረጃ አለ። 

አሁን የዞኑን መምህራን ማህበር፣ ትምህርት ጽሕፈት ቤትንም አግኝታለሁ ውይይት ላይ ናቸው። 

የታሰሩት በመምህራን ላይ ድንጋይ በመወርወር ሌሎቹን በመበጥበጣቸው ነው እንጂ ያ በውይይት የሚፈታ ነው። በዚህ ተስማምተናል።
” ብለዋል።

መምህራኑ ለምን ታሰሩ ? በሚለው ጉዳይ ማብራሪያ የጠየቅናቸው የኮሬ ዞን ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተፈራ ቦንደሮ፣ “ ምቹ ሁኔታ ላይ አይደለሁም። ሥራ ላይ ነኝ ስንት ሰዓት እንደምጨርስ አላውቅም ” በማለት ለማብራሪያ ቀጠሮ ከመስጠትም ተቆጥበዋል።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ለጉዳዩ ምላሽ ለመስጠት ቀጠሮ የሰጠ ሲሆን፣ ምላሽ ሲሰጥ፣ ጉዳዩንም እስከመጨረሻው በመከታተል ተጨማሪ መረጃ የምናቀርብ ይሆናል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

EBS TV

22 Nov, 09:50


#Update

ከሳምንታት በፊት በአዲስ አበባ መርካቶ ሸማ ተራ አካባቢ ተከስቶ በነበረው የእሳት አደጋ ሱቅ የተቃጠለባቸው ነጋዴዎችን በጊዜያዊነት መልሶ ለማቋቋም የ20 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አሳውቋል።

በዚሁ ወቅት ከንቲባ አዳነች አቤቤ አካባቢው ደረጃውን በጠበቀ መልኩ መልሶ እንደሚገነባ ጠቁመዋል።

" እስከዛው ሱቅ ለተቃጠለባቸው ነጋዴዎች የመስሪያ ቦታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተገንብቶ እንዲጠናቀቅ ከተደረገው የ20 ሚሊዮን ብር ድጋፍ በተጨማሪ የአይነት እና የቴክኒክ ድጋፎችን እናደርጋለን " ብለዋል።

ከንቲባዋ ፤ " በአካባቢው ያለውን ጥግግትና መጨናነቅ በዘላቂነት በመቅረፍ፣ የተሽከርካሪ መንገድን በማካተት እንዲሁም ለአደጋ ተጋላጭ በማያደርጋቸው መልኩ በዘላቂነት በአክሲዮን ተደራጅተው ደረጃውን የጠበቀ የገበያ ማዕከል መገንባት እንዲችሉ አስፈላጊው ሁሉ ድጋፍ ይደረጋል " ሲሉ ገልጸዋል።

#MayorOfficeofAddisAbaba #Merkato #ShemaTera

@tikvahethiopia

EBS TV

22 Nov, 09:50


#Update

ወጣት እንስቶችን በግፍ ከገደሉ ውስጥ አንዱ በእድሜ ልክ አስራት ሲቀጣ ፤ የተቀሩት ለፍርድ ተቀጥረዋል።

የመቐለ የማእከላዊው ፍርድ ቤት ትላንት ባዋለው ችሎት ኣፀደ ታፈረ በተባለች እንስት ወጣት በተፈፀመ የግድያ ወንጀል በይን የሰጠ ሲሆን ዓድዋ ከተማ ላይ በተገደለችው ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ግድያ ተጠርጣሪዎች ላይ ውሳኔ ለመስጠት ቀነ ቀጠሮ ሰጥቷል። 

ሟች ወጣት ኣፀደ ታፈረን በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደለው ግለሰብ በእድሜ ልክ አስራት እንዲቀጣ  የመቐለ ማዕከላዊ ፍርድ ቤት ህዳር 12/2017 ዓ.ም ወስኗል። 

ገዳይ ወንጀለኛ ቢንያም ገብረሚካኤል ሟች እንስት ኣፀደ ታፈረ በመቐለ ልዩ ስሙ እንዳ ገብርኤል የተባለ ቦታ አንቆ ከገደላት በኋላ በአከባቢው ወደ ሚገኘው ጫካ ወርውሯት እንደሄደ በአቃቤ ህግ የቀረበው የክስ ማስረጃ ያስረዳል።

ገዳይ ወንጀለኛ ቢንያም በፈፀመው አሰቃቂ የግድያ ወንጀል የመቐለ ማእከላዊ ፍርድ ቤት ጥፍተኝቱ አረጋግጦ በእድሜ ልክ አስራት እንዲቀጣ መወሰኑ የመቐለ ፍትህ ፅህፈት ቤት አስታውቀዋል።

ከፍርድ ቤት ውሳኔ በኋላ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አስተያየት የሰጡ ነዋሪዎች ፤ " ገዳይ ወንጀለኛው የእድሜ ልክ አስራት ያንሰዋል ፤ በሞት ፍርድ መቀጣት ነበረበት " ብለዋል። 

በተያያዘ ዜና ፍርድ ቤቱ ባለፈው 2016 ዓ.ም በዓድዋ ከተማ ለወራት ታግታ ተሰውራ ቆይታ ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ ሞታ ተቀብራ አስከሬንዋ የተገኘው እንስት ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ተጠርጣሪዎች ጉዳይ ለሁለተኛ ጊዜ ተመልክቷል።

ፍርድ ቤቱ በማህሌት ግድያ ወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦች ጥቅምት 28/2017 ዓ.ም በአቃቤ ህግ የቀረበላቸው የምስክሮች ማስረጃ እንዲከላከሉ ለህዳር 12/2017 ዓ.ም የቀጠረ ቢሆንም ተጠርጣሪዎች መከላከል ስላልቻሉ የውሳኔ ፍርድ ለመስጠት ለህዳር 23/2017 ዓ.ም ቀነ ቀጠሮ ተሰጥቷቸዋል።  

ባለፈው ጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም በትግራይ የመቐለ እና የውቕሮ ከተሞች በቅርብ የትዳር እና የፍቅር አጋሮቻቸው የተገደሉ ሁለት እንስቶች ጉዳይ ተጠርጣሪ ግለሰቦች ተይዘው የህግ የምርመራ ሂደት መጀመሩ ይታወቃል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia

EBS TV

22 Nov, 09:50


የእውነት ያለቀስነው መቼ ነው ?

አሁን ላይ ጨምሮ ባለፉት ዓመታት ምን ያህል ግፍ ምን ያህል ጭካኔ ሀገራችን ውስጥ እንደተፈጸመ መናገር መቼም ለቀባሪው ማርዳት ነው።

ግን ግን እውነት አብረን ያለቀስንበት ቀን መቼ ነው ? ትዝ የሚለውስ አለ ?

አንዱ በሀዘን ተሰብሮ ሲያለቅስ አንዱ ይስቃል  ይደሰታል ፤ አንዱ ሲደሰት አንዱ ያለቅሳል። ሁሉንም አንድ የሚያደርገው የሰብዓዊነት ስሜትም እየታየ ጠፍቷል ፤ ሞቶ አፈር ለብሷል።

ለማዘን ቅድሚያ ጥያቄው " ማነው ? የትኛው ወገን ነው ? " ብሎ መጠየቅ ተለማምደነዋል። " የኔ " የምንለው ሲሆን ማልቀስ " የሌላው ነው " ብለን ስናስብ ምንም እንዳልተፈጠረ ማለፍ ከዛም ከፍ ሲል ግፉን ኖርማል ለማድረግ መሮጥ ስራችን ሆኗል።

ሌላው ይቅር ግፍና መጥፎ ተግባር ማውገዝ እንኳን ሂሳብ ተሰልቶ ጥቅምና ጉዳቱ ታይቶ፣ ጩኸቱንና የህዝቡን ቁጣ ተመልክቶ ሆኗል።

ከምንም በላይ የሚስፈራው ጭካኔና ግፍ ለሚፈጽሙ ግለሰቦች ያውም ከነማስረስረጃቸው ለሚታዩ ሰዎች ጥብቅና መቆም ለነሱ መከራከር ልምድ እየሆነ መምጣቱ ነው።

" እባካችሁ ነገሩ በደንብ ይጣራ " ማለት አንድ ነገር ሆኖ ሳለ ሰው የግፍ ፈጻሚዎቹ ማንነት የኔ ወገን ነው ብሎ ካሰበ " በፍጹም እንዲህ አያደርጉም ፤ የተፈጠሩበት ተፈጥሮና ስነልቦና አይፈቅድም " ብሎ ድምዳሜ በመስጠት ሌላ ግፍ መፈጸም ተለምዷል።

በኦሮሚያ፣ በትግራይ፣ በአማራ ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ... በሌሎችም ክልሎች በመንግሥት ታጣቂዎች፣ መንግሥትን እንፋለማለን ብለው በወጡ ታጣቂዎች ፣ ፓለቲከኞች በሚሰሩት ጥላቻ የተመረዙ ከማህበረሰቡ በወጡ ሰዎች ለማየት የሚከብድ ብዙ ግፍ ተሰርቶ ያውም በቪድዮ ተቀርጾ ታይቷል ዛሬም እዚሁ መንደር አለ።

ድርጊቶቹ ይፋ ሲወጡ አብሮ በጋራ ከማዘን ፍትህን ከመጠየቀ ይልቅ የፈጻሚዎቹ ደጋፊ ሆነው የሚቀርቡ ሰዎች በዘመቻ ነገሩን ለማራከስ እና እንዳልተፈጸመ ለማሳየት የሚሄዱበት ርቀት እውን ነገ ለወጥ ይመጣል ? የሚል ጥያቄ ያስነሳል።

በሌላኛው ጎራ በንጹህ ሰው ደም ጥቅም ያስገኝልኛል ያለውን ፖለቲካ ይጫወታል። ከበፊትም እጠላዋለሁ የሚለውን አካል መርጦ ሌላ እልቂት ይቀሰቅሳል።

በዚህም መሃል በርካቶች እንደወጡ ቀርተው ፍትህ አላገኙም።

ለማህበራዊ ሚዲያ ሰዎች እና ሰላም ያለበት ከተማ ለሚኖሩ ነገሩ የሁለት ቀን ግፋ ቢል የሶስት ቀን አጀንዳ ሆኖ ያልፋል። ከዛ ሌላ ግፍ ይፈጸማል።

እናት አምጣ የወለደችውን ፤ ለፍታ ያሳደገችውን ልጅ እያሰበች ዘላለም በለቅሶ ትኖራለች። ወዳጅ ዘመድ ግፉን እያሰበ አመለካከቱ ተቀይሮና በመጥፎ ስሜት ተሞልቶ ለሌላው እንዳያዝን ሆኖ ይኖራል።

የስንቱ ቤት በሀዘን ፣ የስንቱ ሰው ልብ በቂምና ቁርሾ ፤ ሳይወድ በግዱ በመጥፎ አመለካከት ተሞልቶ ይሆን ?

ይህ ነገር ማብቃት አለበት። ተስፋ የሚሰጥ ትንሽ ሰብዓዊነት ሊኖር ይገባል። ማንም ይሁን ማን ተጠያቂነት ሊፈጠር፣ ፍትህ ሊሰፍን ይገባል።

እናቶች የሞተው ልጆቻቸውን ባይመልስላቸውም ፍትህ ሲያገኙ ቢያንስ እንባቸው ይታበስ ተስፋቸው ይለመልም ይሆናል።

ፍትህ ሲገኝ ዜጎች በሀገራቸው ተስፋቸው ያብባል።

በምንም አይነት ሁኔታ በግጭት ፣ በጦርነት ሆነ በምንም መንገድ በምድሪቱ ደም አይፈሰስ ፣ ሰው አይበደል ፤ የሰው ደም በፈሰሰ ቁጥር ፤ በደል በተፈጸመ ቁጥር ቂም ጥላቻ፣ አለመተዛዘን እየተወለደ እየተስፋፋ ይመጣል።

ደስታውስ ይቅር እውነት አብረን መቼ ነው በጋራ ያለቀስነው ? ብለን እንጠይቅ። ከልብ እንኮንን፣ ሂሳብ አንስራ ፤ የሰው ደም ላይ ፖለቲካ አንቆምር ፤ ለፍትህ እንታገል ! ካልሆነ የሁላችን እጣ ፋንታ እንደወጡ መቅረት ፍትህ አለማግኘት ይሆናል።

#TikvahEthiopia
#ቲክቫህኢትዮጵያ
#ናውስ

@tikvahethiopia

EBS TV

22 Nov, 04:00


#Bitcoin

የአንድ ቢትኮይን ዋጋ ከ98,000 ዶላር በላይ ሆነ።

" የመጀመሪያው የክሪፕቶ ፕሬዝዳንት " የተባሉትና " አሜሪካን የፕላኔታችን የክሪፕቶከረንሲ መዲና አደርጋታለሁ " ያሉት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት መሆናቸው ከተረጋገጠ በኃላ ቢትኮይን ወደላይ ተተኩሷል።

ዛሬ የተመዘገበው የቢትኮይን ዋጋ በታሪክ ከፍተኛ ሆኗል።

አንድ የቢትኮይን ዋጋ 98,149 የአሜሪካ ዶላር ገብቷል።

ትራምፕ በምርጫ ቅስቀሳቸው ወቅት " በፍጹም ቢትኮይናችሁን አንዳትሸጡ  " ሲሉ ለክሪፕቶ ማህበረሰቡ መልዕክት አስትላልፈው ነበር።

@tikvahethiopia

EBS TV

22 Nov, 04:00


⚫️ #ኢትዮጵያ ⚫️

ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ምን ያልተፈጸም ፤ ምንስ ያልተደረገ ግፍ አለ ?

እጅግ በጣም ሚያስደነግጠው እንዲሁም ፍጹም ከሰውነት ተራ እየተወጣ መሆኑን የሚያሳየው የድርጊቱ ፈጻሚዎች ልክ ጀግንነት ፣ በጎ ተግባር፣ ፍቅርን ለትውልድ የሚያስተላልፉ ይመስል ግፍና ጭካኔያቸውን በቪድዮ ማስረጃ እራሳቸው ቀርጸው ለትውልድ እያስቀመጡ መሆናቸው ነው።

በእርግጥም እንዲህ እየቀረጹ ማስቀመጣቸው ህዝቡን ለሚፈልጉት ዓላማ ለማነሳሳትና እርስ በርስ ለማባላት፣ ህዝቡን ወደ ግጭት ለማስገባት ሊሆን ይችላል።

በጥላቻ የሚፈጽሙት የግፍ ተግባራቸው አላረካ ብሏቸው ፣ " እዩልን ምን ያህል አውሬ እንደሆንን " የሚለውን ለማሳየትም ይሆናል።

በሀገራችን ፦
🔴 ሰው ከነህይወቱ ሲቃጠል
🔴 በድንጋይ ተወግሮ ሲገደል
🔴 በጅምላ በጥይት ተደብድቦ ወደ ገደል ሲከተት
🔴 አስክሬን ሲጎተት
🔴 አስክሬን አደባባይ ላይ ሲጣል
🔴 ተዘቅዝቆ ሲሰቀል
🔴 በስለት ተቀልቶ ሲገደል
🔴 የጥይት በረዶ ሲዘንብበት ... ኧረ ብዙ ብዙ በቪድዮ ተቀርጾ አይተናል።

ይኸው ዛሬ የሰው ልጅ ልክ እንደ ዶሮ " በስመአብ " ተብሎ ሲታረድ በቁማችን አየን።

ይህ ጭካኔ በማስረጃ በቪድዮ ተቀርጾ የወጣ ነው ለመሆኑ ስንት በቪድዮ ያልተቀረጸ ፣ በየአካባቢው የተፈጸመ ግፍ ይኖር ይሆን ?

እነዚህ ግፍ ፈጻሚ ሰዎች ሰይጣናዊ ስራቸውን በቪድዮ ቀርጸው ማስቀረታቸው በቤተሰብ ፣ በህዝብ ላይ የማይረሳ ቂም፣ ቁርሾና ቁስል ለማኖር ይመስላል።

የትም ይሁን ማንኛውም የግፍ ድርጊት ሲፈጸም ግን የሚቀድመው ድርጊቱን ከልብ አዝኖ ማውገዝ  ነው። ፍትህ ተጠያቂነት እንዲሰፍን መጠየቅ ፤ ለፍትህ መታገል ነው።

ልክ ሰው በሞተ ቁጥር ያለ አንዳች ሀዘን እና መከፋት ወደ ፖለቲካ ንትርክ መግባትና የሰው ደም ፈሶ እንዲቀር ለማድረግ መሯሯጥ የግፍ ግፍ ነው።

ከዚህ ቀደም ብዙ ታዝበናል።

ሰው በግፍ ይገደላል ከዛም ሰዎች በየማህበራዊ ሚዲያ ይመጡና " የኔ ወገን ሰው አይገድልም፤ ፍጹም ነው ፣ ፃድቅ ነው ፣ እንዲህ እንዲያደርግ ተፈጥሮው አይፈቅድለትም " እያሉ ድርጊቱ ያራክሱታል።

ሌላው ወገን ይመጣና በሞተው ንጹህ ሰው ደም ፖለቲካ ይሰራል። በጅምላ ጥላቻውን ይተፋል። በዚህ መንገድ የስንት ሰው ደም ፈሶ ቀረ ?

ላለፉት ዓመታት ሰው በግፍ ይገደላል ከዛ የቀናት የማህበራዊ ሚዲያ አጀንዳ ሆኖ ያልፋል፤ ይረሳል። ከዛ ሌላ ግፍ ሌላ ግድያ ይፈጸማል።

አንዳንዱ እውነት ከልቡ አዝኖ ፤ አንዳንዱ ደግሞ የይስሙላ ያዘነ ይመስል ሸፋፍኖ በማህበራዊ ሚዲያው ይጽፋል ፤ ይለፍፋል። ከሰዓታት በኃላ ሁሉም ረስቶት ምንም እንዳልተፈጠረ ወደ ህይወቱ ይመለሳል። ማህበራዊ ሚዲያ ሲገባ ትዝ ሲለው ለቀናት ስሜቱን ይፅፍ ይሆናል።

እስከ ህይወት ፍጻሜ ድረስ በሀዘን የሚቃጠሉትና ልጃቸውን የማይረሱት እናት አባት፣ ወንድም ፣ እህት ቤተሰብ፣ ዘመዶች ናቸው።

በተለይ እናት እና አባት ሲያለቅሱ ነው የሚኖሩት።

ይህ አዙሪት መቆም አለበት። ደመ በፈሰሰ ቁጥር ቁርሾ ቂም እየተወለደ እንጂ ፍቅር አንድነት አይመጣም።

ልጆቹን የተነጠቀ ቤተሰብና አካባቢ እንደሌላው የማህበራዊ ሚዲያ አርበኛ የአንድ ቀን ሀዘን አድርጎ አያልፈውም። የተፈጸመበትን ግፍና በደል መቼም አይረሳውም ! ቂም በውስጡ ያድራል። ይህ በሀገር ህዝብ ትስስር ላይ የሚያሳድረው ተፅእኖ ከባድ ነው።

ከምንም በላይ ለተጎዱ ወገኖች ፍትህ በማስፈን ፣ ሌላ የአንድ ሰው ደም እንዳይፈስ በማድረግ አዙሪቱን ማቆም ካልተቻለ የከፋ ነገር መምጣቱ አይቀርም።

እዚህች ምድር ላይ ነገ ሳይሆን ዛሬ የሰው ልጅ ደም መፍሰስ እንዲቆም ማድረግ ይገባል።

ፍትህ ሊሰፍን ፤ ተጠያቂነት ሊረጋገጥ ይገባል።

ታጣቂም ሆነ አልሆነ ፤ የአካባቢው ፣ የክልሉ የመንግሥት አካል ሆነ አልሆነ ሁሉም በየድርሻው በየደረጃው ሊጠየቅ ይገባል።

እጅግ በጣም አስገራሚው ነገር በምንም አይነት መንገድና ሁኔታ የዜጎችን ደህንነት ማስጠበቅ ቀዳሚ ስራው ሊሆን የሚገባው እና ችግርም ሲፈጠር ለህዝብ የማሳወቅ ኃላፊነት ያለበት መንግሥት የሚፈጸሙ ድርጊቶችን ከማህበራዊ ሚዲያው ጩኸት በኃላ ለመናገር ሲወጣ መታየቱ ነው።

ለመሆኑ የሚፈጸመውን የሚሰማው ከህዝብ ጋር በሚዲያ ነው ? ነዋሪው በሚዲያ ባይጮህ ላያወግዝ ነው ?

ቆይ ልክ እንደማንኛውም ሌላ አካል " አወገዝኩ " ብቻ ነው የሚባለው  ወይስ ስለተፈጸመ ግፍ በዝርዝር አጣርቶ ለህዝብ ወጥቶ መረጃ መስጠት ነው የሚገባው ? የመንግሥት ስራ ድርሻው ምንድነው ? ለስንቱ ፍትህ ለተነፈገ እያነባ ላለ ወገን ፍትህ ሰጠ ? ተጠያቂነትን አሰፈነ ? በደል የደረሰባቸውን ካሰ ? ዳግም ደም እንዳይፈስ ተከላከል ? እኚህ ሁሉ ጥያቄዎች መልስ ይሻሉ።

ህዝብ በሀገሩ የሚሆነውን ሁሉ ያያል ፣ ይታዘባል፣ ይገመግማል ፣ ነጥብም ይይዛል።

በምንም አይነት ሁኔታ የሰው ደም አይፈስስ ፤ ደም ሲፈስ ቂምና ቁርሾ እንጂ ፍቅርና አንድነት አይወለድም።

#ቲክቫህኢትዮጵያ
#TikvahEthiopia
#ናውስ

@tikvahethiopia

EBS TV

21 Nov, 16:25


" ግድያው የተፈጸመበት ወጣት ደረጀ አማረ ተስፋ ይባላል ፤ የ10ኛ ክፍል ትምህርቱን አጠናቅቆ ወደ ቤተሰቦቹ የሄደ ነበር " - ነዋሪዎች

ቁጣን ስለቀሰቀሰው የደራው አሰቃቂ ግድያ ነዋሪዎቹ ምን አሉ ?

ሰሞኑን በሰሜን ሸዋ ደራ ወረዳ አንድ ወጣት በታጣቂዎች ተይዞ በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገደል የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምሥል በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ከታየ በኋላ በርካቶችን አስቆጥቷል።

ጉዳዩን በሚመለከት ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ቃላቸውን የሰጡ የአካባቢው ነዋሪዎች " ግድያው የተፈጸመው በአካባቢው ላይ በሚንቀሳቀሱ የፋኖ ታጣቂዎች ነው " ሲሉ ተናግረዋል

ድርጊቱ የተፈጸመው ከ2 ወራት በፊት እንደሆነም ገልጸዋል።

ግድያው የተፈጸመበት ወጣት ማነው ?

ዳንኤል ገመዳ የተባለው ግለሰብ ወደ ሰሜን ሸዋ ደራ አካባቢ አምርቶ የሟችን ቤተሰቦች ማነጋገሩን ገልጿል።

ግድያው የተፈጸመበት ወጣት ደረጀ አማረ ተስፋ እንደሚባል እና የ10ኛ ክፍል ትምህርቱን አጠናቅቆ ወደ ቤተሰቦቹ የሄደ እንደነበር አስረድቷል።

በአሰቃቂው ቪዲዮ ላይ ከሚታየው የ10ኛ ክፍል ተማሪ በተጨማሪ ጓደኛው ከማል ሁሴን በአንድ ቀን መገደላቸው ተነግሯል።

ጥቃቱ በተፈጸመበት ዕለት የአካባቢው ነዋሪዎች ወደ በከጀማ ተራራ ሸሽተው ነበር። ደረጀ እና ሌሎች ግን በቀያቸው የቆዩት በበረት ታስረው የሚገኙትን እንስሳትን ለመጠበቅ ነበር።

በአካባቢው የነበሩ ታጣቂዎች ደረጀ እና ከማል ላይ ተኩስ መክፈታቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል።

የደረጀ አባት የሆኑትን አቶ አማረ ተስፋ ቶላን አግኝቼ አነጋግሬያለሁ የሚለው ዳንኤል፣ " ያን ቀን አሳድደው እግሩን ተኩሰው መትተው ከያዙት በኋላ ሳርኩላ ወደ ሚባል ቦታ ወሰዱት። እዚያ ቦታ ነው የፋኖ ታጣቂዎች በብዛት የሚንቀሳቀሱት " ይላል።

ደረጀ በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድሎ አስከሬኑ ለአውሬ የተጣለው እዚያ ቦታ መሆኑን የተናገሩት አባትየው፣ የልጃቸውን መገደል ቢሰሙም አስከሬኑን አግኝተው መቅበር አለመቻላቸውን ጨምሮ ገልጿል።

የደረጀ እናት እና አባት በልጃቸው ሞት ምክንያት አእምሮ ጤናቸው መቃወሱ ተገልጿል።

" የደረጀ እናት አእምሮአቸው ተጎድቷል እና አትናገርም። ምን ማድረግ እንዳለባቸው አያውቁም። ለማንም አይመልሱም። " ነው የተባለው።

ደረጀ ለቤተሰቡ ታናሽ ልጅ ሲሆን ወንድሞቹ እና እህቶቹ አግብተው ከቤት በመውጣታቸው እናት አባቱን ለማገዝ በቤት ያለ ብቸኛ ትንሽ ልጅ መሆኑ ተመላክቷል።

የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተቃውሞ ምንድነው ?

የግፍ ግድያውን የተመለከቱ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ዛሬ ሰልፍ ወጥተው ነበር።

ምግባቸውንም ትተው በመውጣት ሀዘናቸውንና ቁጣቸውን ገልጸዋል።

ፍትህ እንዲሰፍን ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ እና ወንጀለኞችም የፍትህ አደባባይ እንዲቀርቡ ጠይቀዋል።

#ኢሰመኮ : የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ጉዳዩን እንደሰማ ገልጾ ማጣራት መጀመሩን እና የደረሰበትን ውጤት ወደፊት እንደሚያሳውቅም ገልጿል።

የደራ ህዝብ እያየው ያለው የከፋ መከራ ምን ይመስላል ?

በደራ ሰላምና ደህንነት ከጠፋ ቆይቷል።

በቀጠናው በሰላም ወጥቶ መግባት ቅንጦት ከሆነ ዓመታት ተቆጥረዋል።

ሰዎች በግፍ ይገደላሉ ፤ የሚጠየቅ አካል ግን የለም።

ለአብነት ከሳምንታት በፊት ገንዳ አረቦ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሀጂ አህመድ መስጅድ ኢማም ሼይኽ ሙሀመድ መኪን ታግተው ከነበሩት 12 የሚሆኑ የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ጋር በሸኔ ታጣቂዎች መገደላቸው መነገሩ የቅርብ ትውስታ ነው።

ሌሎች በርካታ ግፍ እና ግድያዎች ሲፈጸሙም ቆይቷል።

በአካባቢው የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (መንግሥት ሸኔ የሚላቸው) ታጣቂዎች፣ እንዲሁም የፋኖ ታጣቂዎች፣ የመንግሥት ታጣቂዎች  ይንቀሳቀሳሉ።

ህዝቡ ሰላም ከተጠማ ዓመታት አልፈዋል። ግፍ ፣ በደል ፣ ሰቆቃ መመልከት የዕለት ተዕለት ሁኔታው ሆኗል።

ዛሬ ይህ እጅግ አሰቃቂ ቪድዮ ወጥቶ በዚህ ልክ መነጋገሪያ ሆነ እንጂ በአካባቢው የሚፈጸመው ግፍ፣ የሚካሄደው ግድያ እጅግ አስከፊ ነው።

ብዙ ጊዜ ስለ አካባቢው ሁኔታ  ቢነገረም ይህ ነው የሚባል መፍትሄ አልመጣም።

ሰላም ወዳዱ ህዝብ በተለያየ አቅጣጫ በታጣቂዎች የሚያየው መከራ በቃላት የሚገለጽ አይደለም።

የአካባቢው ነዋሪዎች " መንግሥት ተቀዳሚ ስራው የሆነውን የዜጎችን ደህንነት ማስጠበቅ ስራ እየሰራ አይደለም " በሚል ብዙ ጊዜ ቅሬታቸው አቅርበዋል። አሁንም ቢሆን እያቀረቡ ነው።

#Oromia #Dera #BBC_Afaan_Oromoo

@tikvahethiopia

EBS TV

21 Nov, 16:25


🔈 #የመምህራንድምጽ

🔵 " ያለ ፍላጎት እና ያለ አግባብ 'በልማት ሰበብ' ደሞዝ ተቆርጦብናል " - የጎባ ወረዳ መምህራን

🔴 " ከነሱ ጋር ተነጋግረን የምንግባባ ከሆነ እንግባባለን፤ ካልሆነም ብራቸው ይመለሳል " - የጎባ ወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤት


በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጽያ ክልል ጎባ ወረዳ ያሉ መምህራን ለልማት በሚል ሳቢያ " ያለ ፍላጎታችን እና አላግባብ " ደሞዝ ተቆርጦብናል በማለት ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሰምተዋል።

34 ገደማ ይሆናሉ የተባሉት መምህራን በዚህ ምክንያት ስራቸውን አቁመው ከትላንት በስቲያ ተቃውሞአቸውን ለማሰማት ወደ ሚመለከተው አካል በሰልፍ እንደሄዱ የጎባ ወረዳ መምህራን ተወካይ የሆኑት መ/ር ሀብታሙ ታደሴ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

የመምህራኑ ቅሬታ ምንድነው ?

- መምህራኑ እንዲቆረጥ የተወሰነባቸው ደሞዝ በአንድ አመት ውስጥ የአንድ ወር ደሞዝ ሲሆን ደሞዛቸው ያለፍቃድ በጥቅምት መቆረጥ ተጀምሯል።

- የወረዳውን መምህራን ከአንድም ሁለቴ በዚህ ጉዳይ ተወያይተዋል ነገር ግን " በወቅቱ የኑሮ ሁኔታ ምክንያት በየወሩ ከብድር ወደ ብድር እየተሻገርን ባለንበት ወቅት ደሞዝ እንዲቆረጥ አንፈልግም " ብለው ነበር።

- " እኛ ልማት ጠል አይደለንም " ያሉት መምህራኑ " በራሳችን ፍላጎት ልማቱን እንደግፍ እንጂ በግዴታ አይደለም " ሲሉ ነው የገለጹት።

- ከዚህ ቀደም ወረዳው በዚህ ጉዳይ መምህራንን ባወያየበት ወቅት እንደ ወረዳ መምህራን የራሳችን የአቋም መግለጫ አውጥተናል ሲሉ የመምህራኑ ተወካይ መ/ር ሀብታሙ ተናግረዋል።

ተወካዩ አክለው " ወደው፣ ፈቅደው፣ ፈርመው የሰጡት መምህራን እንዲቆረጥባቸው፤ ያልተስማሙት ደግሞ መብታቸው ተከብሮ እንደፍላጎታቸው እንዲደረግ አሳውቀናል" ሲሉም አስረግጠዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለመምህራኑ ቅሬታ ምላሽ እንዲሰጡ የጎባ ወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ የሆኑትን አቶ አስፋቸዉ አቱሞን አነጋግሯል።

አቶ አስፋቸው ምን አሉ ?

በወረዳው ከ400 በላይ መምህራን እንዳሉ የገለፁት አቶ አስፋቸው ወደ ሰባ ደገማ የሚሆኑት  በደሞዝ ቆረጣው እንዳልተስማዉ ገልፀዋል።

" የወረዳ ልማት ተብሎ ሁሉም መንግስት ሰራተኛ ተስማምቶ እየተቆረጠባቸው ነበር " ያሉት አቶ አስፋቸው " የተወሰኑ መምህራኖች ናቸው ችግር እየፈጠሩ ያሉት " ብለዋል።

መምህራኑ የተቆረጠባቸውን ደሞዝ በተመለከተ ከሚመለከተው ክፍል ጋር መነጋገራቸውንም ያስረዱት ኃላፊው " ከነሱ ጋር ተነጋግረን የምንግባባ ከሆነ እንግባባለን፤ ካልሆነም ብራቸው ይመለሳል እንጂ ልማቱ ምንም የሚሆንበት የለም " ሲሉ ተናግረዋል።

ውሳኔውን ብቻቸውን መወሰን እንደማይችሉ የገለፁት ኃላፊው ከሌሎች የወረዳው ባለድርሻ አካላት ጋር እንደሚነጋገሩ አስረድተዋል።

" ከወረዳ ጋር ተነጋግረን መምህራኑ ሊስማሙ ይችላሉ። ካልተስማሙም መመለስ ይችላል " ያሉት አቶ አስፋቸው " ያን ያህል የተጨቆኑበት እኛ ያረግነው የሚካበድ አይደለም። ቀላል ነው። ትንሽም ስለሆኑም የነሱን ባንቆርጥም ልማቱን ወደ ኃላ ሊጎትት አይችልም " ሲሉ ገልፀዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

EBS TV

21 Nov, 16:25


#የሹፌሮችድምጽ

" የታገቱትን ሊፈልግ የሚወጣ የጸጥታ ሃይል የለም ሄዱበት በተባለው መንገድ የሚገባ የለም " - ጣና የከባድ መኪና ሹፌሮች ማህበር

በኢትዮጵያ በርካታ አካባቢዎች የከተማ አቋራጭ እና ሃገር አቋራጭ አሽከርካሪዎች ለእገታ እና ግድያ እየተጋለጡ መሆናቸውን በተደጋጋሚ ሲነገር ይደመጣል።

የጣና የከባድ መኪና ሹፌሮች ማህበር በአራት አመት ጊዜ ውስጥ ከ200 የሚበልጡ አሽከርካሪዎች ቢገደሉም ችግሩን ለመቅረፍ ግን ምንም እንቅስቃሴ እየተደረገ አለመሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ  ገልጿል።

" ሰው ታፈነ ሲባል ሰውን ያህል ነገር ታፍኖ የአካባቢው የጸጥታ ሃይል የት፣እንዴት ታፈነ የሚለውን ጠይቆ እና አነፍንፎ የሚንቀሳቀስ መንግስት አጥተናል" ሲሉ ስሜ አይጠቀስ ያሉ የማህበሩ አመራር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

አክለውም " መታገትህን ትናገራለህ ምንም እንዳልተፈጠረ ዝም ይባላል የታገቱትን ሊፈልግ የሚወጣ ሃይል የለም ሄዱበት በተባለው መንገድ የሚገባ የለም " ነው ያሉት።

አጋቾች የሚደራደሩት በስልክ ነው ገንዘብም የሚገባው በባንክ ነው ያሉ ሲሆን እገታን እዚህ ደረጃ ያደረሰው መንግስት ለሚታገቱ እና ለሚገደሉ ሰዎች የሰጠው ትኩረት በማነሱ ምክንያት ነው ብለዋል።

እንደ ማህበሩ አመራር ገለጻ ህዳር አንድ ላይ አራት አሽከርካሪዎች መተሃራ እና አዋሽ ሰባት መሃል ታፍነው በታጣቂዎች ተወስደዋል።

በተደጋጋሚ የሹፌሮች መታገት እና መገደል የነበረባቸው አንደ ታች አርማጭሆ ያሉ አካባቢዎች ሚሊሻዎችን በየመንገዱ የማሰማራት እና መንገዱን የመጠበቅ እንቅስቃሴዎች መኖራቸውን የጠቀሱ ሲሆን በተጠቀሰው አካባቢ መሻሻል አለ ብለዋል።

" ከአይከል -ጭልጋ- ገንዳውሃ " ያለው መንገድ ግን አሁንም ለሹፌሮች እጅግ አስቸጋሪ ሆኖ መቀጠሉን ገልጸው ከመንግሥት ውጪ የሆነ እና በየመንገዱ የሚሰበሰብ እስከ 20 ሺ ብር የሚደርስ ህገወጥ ቀረጥ ሹፌሮችን እያማረረ ነው ብለውናል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

EBS TV

21 Nov, 16:25


#Update

ዛሬ 320 የትግራይ ተዋጊዎች ትጥቅ አውርደው አስረክበዋል።

የቀድሞ ትግራይ ተዋጊዎች ትጥቅ የማስፈታትና ወደ ተሃድሶ ማዕከላት የማስገባት ስራ በዛሬው ዕለት በይፋ ተጀምሯል።

የኢፌዴሪ ሀገር መከላከያ ሰራዊትም ታጣቂዎች ያወረዷቸውን ትጥቆች ርክክብ አድርጓል።

በዛሬው ዕለት 320 የትግራይ ተዋጊዎች ቀላል መሳሪያዎችን አውርደው በማስረከብ ወደ ተሃድሶ ያስልጠና ማዕከል አቅንተዋል።

እንደ ተነገረው ከሆነ በመጀመሪያው ዙር 75 ሺህ የቀድሞ ተዋጊዎችን ስልጠናና የማቋቋሚያ ድጋፍ በማድረግ ወደ ህብረተሰቡ የመቀላቀል ስራ ይሰራል።

@tikvahethiopia

EBS TV

21 Nov, 16:25


#DDR

" ትጥቅ መፍታት መሸነፍ ፣ መዋረድ ወይም ራስን ዝቅ ማድረግ ማለት አይደለም። ትጥቅ መፍታት ማለት የሀገር አንድነትና ሰላም በፅኑ መሰረት ላይ ከማቆም አንፃር መታየት አለበት " - የኢፌዴሪ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ ወታደራዊ አመራር 

የመጀመሪያ ዙር የትግራይ የቀድሞ ተዋጊዎችን ዲሞቢላይዝድ በማድረግ ወደ  ተሃድሶ ስልጠና ማዕከላት የማስገባት ስራ በይፋዊ ስነስርዓት ተጀምሯል።

ዛሬ በተካሄደ ይፋዊ ስነስርዓት ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ ወታደራዊ አመራር ብርጋዴር ጀነራል ደርቤ መኩሪያው ፤ " የዴሞብላይዜሽን አሰራር ሴት ተዋጊዎችን ፣ አካል ጉዳተኞችን እና በአደረጃጀት ውስጥ ያሉ አመራሮችን በማስቀደም ይፈፀማል " ብለዋል።

በዴሞብላይዜሽን አሰራር በየቀኑ 320 ታጣቂዎች ወደ ስልጠና ማእከላት የማስገባት ስራ እንደሚሰራ ጠቁመዋል።

በመጀመሪያ ዙር 75 ሺህ ታጣቂዎች እንደሚስተናገዱ አክለዋል።

" ማንኛውም ትጥቅ ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ውጭ መያዝ የሀገሪቱ ህገ-መንግስት ይከለክላል ስለሆነም በትግራይ እየተፈፀመ ያለው የዴሞብላይዜሽን አፈፃፀም ህግና ስርዓት ተከትሎ የሚፈፀም ነው " ሱሉ ተናገረዋል።

ብ/ጄነራሉ ፤ " ትጥቅ መፍታት መሸነፍ ፣ መዋረድ ወይም ራስን ዝቅ ማድረግ ማለት አይደለም። ትጥቅ መፍታት ማለት የሀገር አንድነትና ሰላም በፅኑ መሰረይ ላይ ከማቆም አንፃር መታየት አለበት " ብለዋል።

" ትጥቅ ማስረከብ ማለት ያለችን እንዲት ሀገር ከሚጋረጡባት የውጭ ስጋቶች መታደግ መሆኑን መገንዘብ ያሻል " ያሉት ጀነራሉ  " ትጥቅ የማስፈታት ተግባሩ የትግራይ እና በክልሉ ደንበር አከባቢ ያለው የፀጥታ ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት ተፈፃሚ ይሆናል " ሲሉ አሳውቀዋል።

የትግራይ የፀጥታ እና የሰላም ቢሮ ሃላፊ ጀነራል ፍስሃ በበኩላቸው ፤ " ትጥቅ የመፍታቱ ተግባር እርምጃ ለትግራይና ለሀገር ሰላም የተከፈለ ውድ እና ሁሌ በታሪክ ድምቆ የሚታወስ ፍፃሜ ነው " ብለዋል።

ዛሬ ትጥቃቸው ያስረከቡ 320 የቀድሞ ተዋጊዎች ሲሆኑ ወደ ተዘጋጀላቸው የስልጠና ማእከላት ማምራታቸው ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ስነ-ስርዓቱ ከተከናወነበት ቦታ በላከው መረጃ ገልጿል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

EBS TV

20 Nov, 16:11


#Update🚨

“ በሠራተኛዋ እጅ ላይ የተገኘውን ነው እንጂ ያጋራነው ከየት ነው ? የሚል ዝርዝር መረጃ የለውም ፤ እርሱ የሚቀጥል ይሆናል ”  - የአዲስ አበባ ፓሊስ

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ፤ ወረዳ 2 አያት ዞን 1 አካባቢ ተቀጥራ ትሰራበት ከነበረው ቤት 18 ሺሕ የአሜሪካን ዶላርና የህንድ ሩፒን ጨምሮ የተለያዩ የወርቅ ጌጣጌጦች በአጠቃላይ ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት በመስረቅ የተጠረጠችን የቤት ሠራተኛ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የአዲስ አበባ ፓሊስ ከሰዓታት በፊት መረጃ አጋርቶ ነበር።

ፓሊስ ማህበረሰቡ የቤት ሠራተኛ ሲቀጥር ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ መሆን እንዳበት ያሳሰበ ሲሆን፣ መረጃው ከተጋራ በኋላ " ይህን ያህል ዶላር በአንድ ቤት እንዴት ተነኘ ? ይህስ ሌላ ምርመራ አያስፈልገውም ? የሠራተኛዋን መታወቂያ የሰጣት አካልስ ማነው ? " የሚሉ በርካታ ጥያቄዎች ሲንሸራሸሩ ተስተውለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በበኩሉ፣ የዶላሩን ምንጭና ማንነትን በደንብ አያሳይም የተባለውን የቤት ሠራተኛዋን መታወቂያ በተመለከተ ማብራሪያ እንዲሰጡ የአዲስ አበባ ከተማ ፓሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ማርቆስ ታደሰን ጠይቋል።

ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ምን ምላሽ ሰጡ ?

ጥሩ ነው እንደዚህ አይነት መነጋገሪያ መሆኑ ሰው በደንብ እንዲያነበውና ጥንቃቄ እንዲያደርግም ይጋብዛል። ዞሮ ዞሮ አሁን ጥሬ ምርመራ ላይ ያለን ጉዳይ መረጃ ነው ለህብረተሰቡ ያጋራነው።

በጣም በርካታው የከተማው ነዋሪ ሠራተኛ ስለሆነ ሥራውን የሚያቀለው አብዛኛው በሠራተኛ ነው፤ ብዙው ሰው ተሯሯጭ ስለሆነ። ስለዚህ ዞር ብሎ ሠራተኞቻቸውን የሚያዩ፣ ያስያዙትን መታወቂያ ቼክ የሚያደርጉ፣ ፎርጅድ ከሆነም ለምን? ብለው የሚያስይዙ አናሳ ናቸው።

ዞሮ ዞሮ ሠራተኛዋ ላይ ይሄን ያህል ብር እጇ ላይ መገኘቱን ነው ለመግለጽ የሞከርነው። ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ የተባለው ገንዘቡም ንብረቱም ተሰልቶ ነው።

ሠራተኛዋ በተለያዩ ቤቶች ላይ እየዞረች ስትሰራ ነበርና ስለዚህ ተጠርጣሪዋ ከተለያዩ ቦታዎች ሊሆን ይችላል ገንዘብ ያሰባሰበችው፤ ስለዚህ ፈርዘር ነገሮች ገና በምርመራ የሚገኝ ውጤት ነው የሚሆነው።

በአንድ ሰው እጅ ላይ ምን ያህል የአሜሪካን ገንዘብ መኖር አለበት የሚለው በሕግ የተቀመጠ ነገር ነው። ሠራተኛዋ ምናልባት ከእገሌ ቤት ነው ያገኘሁት የምትል ከሆነ ሌላ ፈርዘር ምርመራ ይኖራል።

ዛሬ ያጋራነው ጥሬውን ሀቅ፤ ንብረትና ገንዘብ ተቆጥሮ በእጇ ላይ የተገኘውን ነው። በእጇ ላይ የተገኘውን ነው እንጂ ያጋራነው ከየት ነው? የሚል ዝርዝር መረጃ የለውም፤ እርሱ የሚቀጥል ይሆናል ማለት ነው ”
ብለዋል።

የተጠርጣሪዋን መታወቂያ በተመለከተ ጉዳዩ በሂደት እንደሚጠራ ገልጸው፣ “ ይሄ የቀጣሪዎቹም ክፍተት ነው። ሠራተኛዋ ተያዥ ስታመጣ የራሷን ፎቶ እንዳይታይ፣ ድብዝዝ አድርጋ፣ የሌላ ሰው አስመስላ ነው ያመጣችው ” ብለዋል።

“ የመጨረሻ ኮንሰርናችን በለሚ ኩራ የተፈጸመውን ነገር ህብረተሰቡ አንብቦ ዘወር ብሎ ሠራተኛውን እንዲያይ ነው ” ያሉት ኮማንደሩ፣ “ ይሄኔኮ እየተበዘበዘ ያለ አለ ” ብለዋል።

እንዲህ አይነት ድርጊት የሚፈጽመው “ የቤት ሠራተኛ ብቻ አይደሉም፤ የጥበቃ ሠራተኛ፣ በሌላም ሥራ ላይ ያለም ሊሆን ይችላል ” ብለው፣ የተጠርጣሪ ሠራተኛዋን ተጨማሪ ጉዳይ በቀጣይ ግልጽ እንደሚያደርጉ ጠቁመዋል።

በሌላ በኩል ፤ ኮማንደር በአጠቃላይ ስርቆት የሚፈጸምበት መንገድ ሿሿን ጨምሮ በተለያዬ መልኩ እንደሆነ አስረድተው፣ አንድ ቦታ ላይ የሚያዙት የሿሿ ወንጀል ፈጻሚዎች በድጋሚ በተለያዬ ቦታዎች ላይ እንቅስቃሴ እያደረጉ ስለሆነ የተጠርጣሪዎችን ፎቶ እያጋሩ መሆኑን ተናግረዋል።

ሳይታመሙ የታመሙ መስለው በመለመን ሰዎችን በየዋህነታቸው ፣ በሰጪነታቸው የሚሸውዱ ወንጀለኞች እንዳሉም ሰው መስጠትም ካለበት ሳይጭበረበር ሁነቱን በማጤን ደስ ብሎት መስጠት እንዳለበት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል አስገንዝበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

EBS TV

20 Nov, 16:11


#Update

የትግራይ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በማዕከላዊ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ላይ የተደረገውን የግድያ ሙከራ ወንጀል ማጣራት መጀመሩን አስታውቋል።

ኮሚሽኑ በይፋዊ የማህበራዊ ሚድያ ገፁ በሰጠው ማብራርያ ፤ " ህዳር 8/2017 ዓ.ም ከቀኑ 8 :00 ሰዓት አካባቢ ከአክሱም ወደ መቐለ ከተማ በመኪና በመጓዝ ላይ የነበሩት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ሰለሙን መዓሾ ላይ የተቃጣው የግድያ ሙከራ የሚያጣራ ቡድን ተቋቁመዋል " ብሏል።

አጣሪ ቡድኑ ከፓሊስ እና ከፍትህ አካላት የተወጣጣ እንደሆነ ገልጿል።

የግድያ ሙከራ ወንጀሉ ተፈፅሟል ተብሎ በማህበራዊ ሚድያ የትስስር ገፆች ከተሰራጨበት ደቂቃ ጀምሮ ጥብቅ የማጣራት ስራ መጀመሩ አብራርቷል።

ኮሚሽኑ የማጣራት ሂደቱ እንዲሳካ የህብረተሰቡን ትብብር ጠይቋል። የማጣራት ሂደቱ የሚጎዱ በማህበራዊ ሚድያ የሚነዙ ሁለት ፅንፍ የያዙ አሉባልታዎች እንዲቆሙ አሳስቧል።

የሚደርስበትን የምርመራ ውጤት ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ ቃል ገብቷል።

የግድያ ሙከራ ተደርጎበታል የተባለው ቦታ የማይቅነጣል ወረዳ ሲሆን የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ገብረ ተክለሃይማኖት ለቪኦኤ በሰጡት ቃል ፣ ጉዳዩን ከወረዳው የጸጥታና ፖሊስ አባላት ማጣራታቸውን ገልፀው፣ " መረጃው ከእውነት የራቀ ነው። የተኮሰበት ሰው የለም " ማለታቸው ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia            

EBS TV

20 Nov, 14:27


#ዴሞክራሲ 👏 #ሶማሌላንድ

" የምርጫ ውጤቱን እንቀበላለን " - ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ

ባለፈው ሳምንት በራስ ገዟ ሶማሌላንድ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ መደረጉ ይታወሳል።

በከፍተኛ ብልጫም የተቃዋሚው ዋደኒ ፓርቲ መሪ አብዲራህማን ሞሐመድ አብዱላሂ " ኢሮ " ምርጫውን አሸንፈዋል።

በምርጫው የተሸነፉት ተሰናባቹ ፕሬዜዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ " የምርጫውን ውጤት እንቀበላለን " ብለዋል።

ተመራጩ ፕሬዜዳንትንም " እንኳን ደስ አልዎት ! " ብለዋቸዋል።

" ባስመዘገቡት ድል እንኳን ደስ አልዎት " ያሉት ፕሬዜዳንት ቢሂ " ሰላማዊና የተረጋጋ የስልጣን ሽግግር እንዲደረግ ለማድረግ የተሟላ ድጋፌን አደጋለሁ  " ሲሉ ቃል ገብተዋል።

" የአገልግሎት ዘመንዎ ሰላምን ፣ እድገትን እና ዘላቂ ስኬትን ለሀገራችን እንዲያመጣ እመኛለሁ " ብለዋል።

ተሰናባቹ ፕሬዝዳንት ቢሂ ለህዝቡ ባስተላለፉት መልዕክት " ፕሬዝዳንታችሁ ሆኜ እንዳገለግላችሁ ዕድሉን ስለሰጣችሁኝ አመሰግናለሁ " ሲሉ ገልጸዋል።

" የስልጣን ዘመኔ ማብቂያ ላይ ሆኜ የምለው ነገር ለሀገራችን እድገት ያለኝ ቁርጠኝነት ጸኑ መሆኑን ነው " ሲሉ አክለዋል።

" በአንድነት እና በጋራ ተነስተን ለሶማሌላንድ ብልፅግና እንስራ " ብለዋል።

6ኛው የሶማሌላንድ ፕሬዚዳንት ሆነው የተመረጡት አብዲራህማን ኢሮ " ማንም ተሸናፊ ማንም አሸናፊ የለም ያሸነፈው የሶማሌላንድ ህዝብ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

ሶማሌላንድ እራሷን እንደ ሉዓላዊ ሀገር ምትቆጥር ናት። ከሶማሊያ መንግሥት ጋርም ግንኙነት የላትም። ላለፉት በርካታ ዓመታት ራሷን በራሷ እያስተዳደረች ነው።

እጅግ ሰለማዊ ፣ የተረጋጋ ፣ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ በማድረግ እና ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር በማድረግ ትወደሳለች።

#TikvahEthiopia #ቲክቫህኢትዮጵያ
#Somaliland

@tikvahethiopia

EBS TV

20 Nov, 13:37


#AddisAbaba

" የቤት ሰራተኛ በአጋዥነት ስትቀጥሩ በህጋዊ መንገድ በቂ ተያዥ በማስቀረብ የተያዣቸውን አድራሻና ማንነት በአግባቡ በማጤን ይሁን " - ፖሊስ

በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ ከምትሰራበት ቤት ከ2 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት እና ገንዘብ ሰርቃ የተሰወረች ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር መዋሏን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።

ተጠርጣሪዋ የወንጀል ድርጊቱ የፈጸመችው በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 አያት ዞን1 ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ጥቅምት 22 ቀን 2017 ዓ/ም ነው፡፡

ግለሰቧ በደላላ አማካኝነት በቤት ሰራተኝነት ከተቀጠረችበት መኖሪያ ቤት በ3ኛው ቀን ቆይታዋ ነው ዝርፊያውን የፈጸመችው።

የግል ተበዳይ ስራ በሄዱበት ወቅት አጋጣሚውን በመጠቀም በቤቱ ውስጥ የተቀመጠውን የተለያዩ ሀገራት ገንዘቦች እንዲሁም የተለያዩ የወርቅ ጌጣጌጦችን ሰርቃ በመሰወሯ የግል ተበዳይ የተፈፀመባቸውን የወንጀል ድርጊት ለመሪ ሉቄ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ አመልክተዋል፡፡

ተጠርጣሪዋ የወንጀል ድርጊቱን ከፈፀመች በኋላ የግል ተበዳይ ጋር ከመቀጠሯ በፊት በክፍለ ከተማው ወረዳ 14 አባዶ አካባቢ ኮንዶሚኒየም ቤት ለ3 ወራት ተከራይታ በነበረበት ቤት ተደብቃ በክትትል የፖሊስ አባላት ከሰረቀቻቸው የተለያዩ አልባሳት፣ የተለያዩ የሴትና የወንድ ጫማዎች፣ 18 ሺህ የአሜሪካ ዶላርና የህንድ ሩፒ፣ የተለያዩ የወርቅና ልዩ ልዩ ጌጣጌጦች ጋር በቁጥጥር ስር መዋሏን ፖሊስ ገልጿል።

በ2 የተለያዩ ስሞች የነዋሪነት መታወቂያዎች እንደተገኘባትም ፖሊስ አመልክቷል።

የግል ተበዳይ ተጠርጣሪዋን ለስራ ሲቀጥሯት ያቀረበችው የተያዥ ፎርም የራሷን ፎቶ በትክክል እንዳይለይ አድርጋ የለጠፈች ሲሆን የግል ተበዳይ ይህን ሳያረጋግጡ በእምነት የቀጠሯት መሆኑን ገልፀዋል።

ፖሊስ ፥ ህብረተሰቡ የቤት ሰራተኛ በአጋዥነት መቅጠሩ ተገቢ ቢሆንም በህጋዊ መንገድ በቂ ተያዥ በማስቀረብ የተያዣቸውን አድራሻና ማንነት በአግባቡ በማጤን መቅጠር እንደሚገባ አሳስቧል።

ውድ የሆኑ ንብረቶችን እንዲሁም ገንዘቦችን ደህንነቱ በተጠበቀ ቦታ በማስቀመጥ በተገቢው ሊቆጣጠሩና ንብረታቸውን ከስርቆት ወንጀል ሊታደጉ እንደሚገባም አሳስቧል።

NB. በዚህ የፖሊስ መረጃ ላይ እንዴት አንድ ሰው ቤት ውስጥ ይሄ ሁሉ የአሜሪካ ዶላር በጥሬው ሊቀመጥ እንደቻለ፣ የተገኘው የተጠርጣሪዋ መታወቂያ ከየት እና እንዴት እንደወጣ የተብራራ ነገር የለም።

መረጃውን የተመለከቱ በርካቶች የገለሰቧ መያዝ ትክክል ሆኖ ሳለ እንዴት ይሄ ሁሉ ዶላር ግለሰብ ቤት ተቀምጦ ተገኘ፣ መታወቂያውን የሰጣት አካላስ ማነው ? የሚል ጥያቄ አንስተዋል። ፖሊስ በቀጣይ ስለ ጉዳዩ የሚሰጠው ማብራሪያ ካለ እናቀርባለን።

#AddisAbaba

@tikvahethiopia

EBS TV

20 Nov, 13:37


#አፈሳ

🔵 “ ወጣቶች እየታፈሱ ነው። የሚታፈሱትም ያለ ፍላጎታቸው ወደ ግዳጅ ሊላኩ ነው ” - የኦሮሚያ ክልል ነዋሪዎች

🔴 “ ያገኘናቸው በጣም በርካታ ግኝቶች አሉ ” - ኢሰመኮ


በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ወጣቶች “ በመንግስት ፀጥታ አካላት ” እየታፈሱ መሆኑን፣ በዚህም እንዲህ አይነት ድርጊት በሚፈጸምባቸው ቦታዎች ወጣቶች በነጻነት የመንቀሳቀስ መብታቸው እንደተገደበ ነዋሪዎች በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አቤት ብለዋል።

ነዋሪዎቹ እየተፈጸመ ነው በሚል የተማረሩበት የአፈሳ ድርጊት በይበልጥ እየተካሄደ ያለው በባሌ ሮቤ፣ በሻሽመኔ፣ በአርሲ ነገሌ፣ ባቱ፣ ወንጂ፣ በአዳማ ከተሞችና በዙሪያ ገባው መሆኑም ተመላክቷል።

ነዋሪዎቹ፣ “ ወጣቶች እየታፈሱ ነው። የሚታፈሱትም ያለ ፍላጎታቸው ወደ ግዳጅ ሊላኩ ነው ” ሲሉ ተናግረዋል።

“ ወጣቶቹ ለመዝናናትም ሆነ ለሥራ ሰብሰብ ብለው መንገድ ላይ ሲገኙ ያለምንም ጥያቄ ታፍሰው በመኪና እየተጫኑ ወደ ሌሎች አካባቢዎች እየተወሰዱ ነው ” በማለት ሁነቱን አስረድተዋል።

“ ከዚች ቀደምም አፈሳ ወጣቶች በሚሰበሰቡበት ቦታ ለምሳሌ ዴኤስቲቪ ፣ ፑል ቤት ነበር አሁኑ ግን መንገድ ላይ የሚገኙት ጭምር በገፍ እየተወሰዱ ነው ” ብለዋል።

አንዳንድ ከ15 እስከ 18 ዓመት እድሜ ያላቸው ታዳጊዎችም የተወሰዱበት ሁኔታ አለ ሲሉ ገልጸዋል።

አንድ ቃላቸውን የሰጡ የክልሉ ነዋሪ “ ከሻሸመኔ አንድ የምናውቀው የቤተሰብ ልጅ ተወስዷል። ከሻሸመኔ ተጭነው ወደ ወላይታ ሶዶ አካባቢ መሄዳቸውን ለቤተሰቦቹ ተናግሯል ” ብለዋል።

አንድ የአዳማ ከተማ ነዋሪ ደግሞ ፥ “ ሰው በተለይ ወጣቱ ፈርቷል። ያለውን ወቅታዊ ነገር በመፍራት ስራውን ትቶ በጊዜ ቤት የሚመለስ አለ። ከወጣው እታፈሳለሁ በሚል ስጋት ከቤት የማወጡም አሉ። የጊዜ ገደብ የተቀመጠ ይመስል ውጭ ያለው ሰው 12:00 ስሆን ወደ ቤቱ ለመግባት ይጣደፋል ” ሲል ገልጿል።

“ ሰዎችን ያለምክንያት ይዘው ያስራሉ ሰው ካለው እና 20,000-30,000 መክፈል ከቻለ ይለቃሉ። ያልቻለ ደግሞ ተወስዶ ይሄዳል ” ሲልም አክሏል።

ሰሞኑን አንድ ጓደኛቸው ተይዞ የባንክ ሰራተኛ ነኝ ብሎ ማስረጃ አሳይቶ መለቀቁን ጠቁሟል።

ድርጊቱ በሚፈጸምባቸው አካባቢዎችም ሰዎች ከቤት ለመውጣት፣ ሥራ ለመስራት ከፍተኛ ስጋት እንዳደረባቸው አስረድተው፣ “ የሰው ልጅ መብት ግን ለይስሙላ ነው እንዴ የተጻፈው ? መቼ ነው ይህ መብታችን እንኳ የሚከበረው ? ከዚህ ቀደምም አፈሳ ነበር። ያሁኑ ግን ብሷል ” ሲሉ ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

በርካታ እናቶች ልጆቻቸው ከሚኖሩበት ሰፈር ሳይቀር ተወስደውባቸው በስንት ልመና ከተያዙበት ቦታ ያስወጧቸው አሉ።

በተለይ ወጣቶች ከተያዙ በኃላ የሚወሰዱት ወደ ማቆያ ቦታዎች ነው።

ለቀረበው ቅሬታ ምላሽ ለማግኘት ቲክቫህ ኢትዮጵያ ወደ ኦሮሚያ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ሙከራ ቢያደርግም፣ ስልክ ሆነ የፅሑፍ መልዕክት ለመመለስ ፈቃደኛ አልሆነም።

ከቀናት በፊት የክልሉ መንግሥት “ በክልሉ የጅምላ አፈሳ አለ በሚል የሚሰራጨው መረጃ ሀሰት ነው ” ሲል በፋና ብሮድካስት ኮርፖሬት በኩል ገልጾ ነበር።

እየተፈጸመ ነው የተባለውን የአፈሳ ድርጊት ሰምቶ እንደሆን በሚል የጠየቅነው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ግን አፈሳ እየተፈጸመ ነው የሚለው ቅሬታው ትክክል መሆኑን ነግሮናል።

ወጣቶችን ወደ ‘ግዳጅ ትሄዳላችሁ’ በሚል በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች እየተፈጸመ ነው የተባለውን አፈሰ ኮሚሽኑ ሰምቶ ነበር ? ስንል የጠየቅነው ኢሰመኮ በምላሹ፣ “ አፈሳውን በተመለከተ የሰራነው ብዙ ሥራ አለ።  ፐብሊክ ስቴትመንት ይሰጣል ” ብሏል።

“ ምንድን ነው የሚለውን በሂደት የምናቸው ይሆናል። ግን ጉዳዩ ኦረዲ ብዙ ሥራ ተሰርቶበታል። መግለጫው ሲወጣ ይደርሳችኋል ” ነው ያለው።

አፈሳው ትክክል ነው ? እንዲህ አይነት ድርጊት እየተፈጸመ ነው? ለሚለው የቲክቫህ ጥያቄ ኮሚሽኑ፣ “ በጣም ብዙ የኦሮሚያ አካባቢዎች ላይ ገብተን የሰዎች ማቆያዎችን አይተናል ” የሚል ምላሽ ሰጥቷል።

“ ስለዚህ የማኀበራዊ ሚዲያው አሊጌሽን ምንድን ነው? የሚለው እንዳለ ሆኖ በእኛ በኩል ግን ያገኘናቸው በጣም በርካታ ግኝቶች አሉ ” ሲል አረጋግጧል።

ከክልሉ ጋር የተየጋገርንባቸው፣ እያደረገረግን ያለናቸው ጉዳዮችም አሉ” ሲል ኮሚሽኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

EBS TV

19 Nov, 17:14


ዛሬ ያለመከከስ መብታቸው የተነሳው የልደታ ክ/ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የነበሩት የአ/አ ም/ቤት አባል ሰዒድ አሊ በምንድነው የተጠረጠሩት ?

ዛሬ የአዲስ አበባ ም/ቤት የልደታ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ የነበሩት አቶ ሰዒድ አሊን ያለመከከስ መብት አንስቷል።

ያለመከሰስ መብታቸው የተነሳው በሙስና ተጠርጥረው እንደሆነ በም/ቤቱ የሰላም ፣ ፍትህ እና መልካም አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገልጿል።

ኮሚቴው ምን አለ ?

" ከሜክሲኮ እስከ ቄራ ባለው የኮሪደር ስራ ያልተካተቱ እና በመንግሥት ይፈርሳሉ ተብለው ያልተያዙ የመንግሥት ቤቶችን ከባለሃብት እና ከሰራተኞች ጋር በመመሳጠር ግምታቸው ከ3 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ ኮንዶሚኒየም ቤት እንዲሰጥ አድርገዋል።

የፈረሱት የመንግሥት ቤቶች ግለሰቦች ተከራይተውት የነበረ ነው።

እነዚህን ቤቶች እንዲፈርሱ አስደርገው ይዞታውን ከቤቶቹ አጠገብ ለተሰራው " ዋይልድ አፓርትመንት " ለተባለ ህንጻ ባለቤት  ምቹ በማድረግ ግንባታ እንዲገነባና የግሉ እንዲያደርገው ለማድረግ ተንቀሳቅሰዋል።

አጠቃላይ 6 መኖሪያ ቤቶች እና 1 ንግድ ቤት ፦
- ግለሰቦች እየኖሩበትና ንግድ እየተከናወነ ባለበት፤
- ካቢኔው ይፍረሱ ብሎ ባልወሠነበት
- ፕላን፣ ፎርማት እና የካቢኔ ውሳኔ ባልተያዘበት በ503 ካ/ሜ ላይ ያረፉትን ቤቶች እንዲፈርሱ ሰራተኞችን ሰብስበው በማስወሰንና ትዕዛዝ በመስጠት ፤ ቤቶቹ ያሉበት ቦታ በአካል ጭምር በመሄድ እንዲፈርስ መመሪያና ትዕዛዝ ሰጥተዋል።

የመንግሥት መኖሪያ ቤቶች ውስጥ በኪራይ ይኖሩ ለነበሩት ግለሰቦች አጠቃላይ 3,383,202 ብር ከ77 ሳንቲም የሆኑ 6 የጋራ መኖሪያ ኮንዶሚኒየም ቤቶች እንዲሰጣቸው አድርገዋል።

ይዞታውን ሀጂ በገን ኸይሩ ነጋሽ ለተባሉ  በአካባቢው አፓርትመንት ላላቸው ግለሰብ እንዲሰጥና ግንባታ እንዲገነባበት አድርገዋል።

ተጠርጣሪው ለዚህ ስራ ጉቦ መቀበሉ ማስረጃ አለን ብሏል።

በባለቤታቸው ስም ከባለሃብቱና ከድርጅቱ 6 ሚሊዮን ብር ጉቦ ተቀብለዋል። ይህን ብር ከሌላ ግለሰብ ካተላለፈው 8 ሚሊዮን ብር ጋር በመቀላቀል በባንክ ብድር ለገዙት 30,000,000 ብር ለሚያወጣ ቤት 14,000,000 ብር ለቤቱ ግዥ ብድር ክፍያ ከፍለዋል ፤ በዚህም የሙስናና ህገወጥ ገንዘቡን ህጋዊ አስመስሎ በማቅረብ ወንጀል መፈጸም ምርመራ እየታጣራ ይገኛል " ብሏል።

#AddisAbaba

@tikvahethiopia

EBS TV

19 Nov, 17:14


#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርሲቲ መምህራንን ፈተና ለመፈተን እየተዘጋጀ መሆኑ ተሰማ።

ትምህርት ሚኒስቴር፤ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚያስተምሩ መምህራንን ብቃት ለመመዘን ፈተና ለመፈተን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጿል።

በሚኒስቴሩ የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልግሎት ዳይሬክተር የሆኑት እዮብ አየነው(ዶ/ር ) ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ በሰጡት ቃል ፥ " የመምህራን ፈተና ከዚህ በፊት በአንደኛ ደረጃ በሚያስተምሩት ላይ ተሞክሮ ነበረ በመሆኑም አልተጀመረም ማለት አይቻልም " ብለዋል።

አሁን ግን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራንን ለመፈተን ዝግጅት እየተደረገ እንደሆነ አስረድተዋል።

ዝግጅቱ እንዳለቀ በዚህ ዓመት ወይም በቀጣዩ 2018 ዓመት ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መመህራን ፈተና መሰጠት ይጀምራል ሲሉ ለሬድዮ ጣቢያው ገልጸዋል።

@tikvahethiopia

EBS TV

19 Nov, 17:14


#Update

" መስሪያ ቤቱ መድኃኒት ለመግዛት ገንዘብ እያጠረው ነው " -የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት

የዓይደር ኮምፕረንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ካጋጠመው የመድኃኒትና የህክምና ግብዓቶች እጥረት ጋር በተያያዘ በሆስፒታሉ እና በታካሚዎች ዘንድ በርካታ ችግሮችን እያስከተለ የሚገኝ ሲሆን ተቋሙ ባሉበት ተደራራቢ እዳዎች ምክንያት ችግሩን መቅረፍ ተስኖታል።

ሆስፒታሉ ከኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጋር ባለበት ከፍተኛ ያልተከፈለ እዳ ምክንያት ውዝግብ ውስጥ ገብቷል።

በተቋሙ አጋጥሟል ለተባለ የመድኃኒቶች እጥረት ምክንያትም ያለው ውስን በጀት እና ያለበት ውዝፍ ተጠቃሽ ናቸው።

ካሉበት ችግሮች በተጨማሪ አንዳንድ መድኃኒቶች በመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት በኩልም እያጡ መሆኑን ሆስፒታሉ ለቲክቫህ አሳውቋል። 

ሆስፒታሉ ላቀረበው ቅሬታ እና ስላልተከፈለው ከፍተኛ እዳ የአገልግሎቱን የመቀሌ ቅርንጫፍ አስተባባሪ አቶ አለማየሁ ገብረማርያምን አነጋግረናል።

ያንብቡ : https://telegra.ph/TikvahEthiopia-11-19

@tikvahethiopia

EBS TV

17 Nov, 12:16


ፎቶ፦ ዛሬ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ መርካቶ ጃቡላኒ ህንፃ በተለምዶ " ድንች በረንዳ " እየተባለ በሚጠራው ቦታ ላይ የእሳት ቃጠሎ አደጋ ተነስቶ ነበር።

እሳቱ ከቀኑ 6:30 ሰዓት ላይ የተነሳ ሲሆን ሳይዛመትና የከፋ ጉዳት ሳያደርስ መቆጣጠር እንደተቻለ የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ገልጿል።

ስለ አደጋው ምክንያት የተባለ ነገር የለም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ እሳቱ በተነሳበት ወቅት የእሳትና ከደጋ ሥራ አመራር ኮሚሽንን ለማነጋገር ሞክሮ ነበር። አንድ የኮሚሽኑ አካል በቦታው ሱቆች እየተቃጠሉ እንደነበር ገልጸዋል።

እኚሁ አካል በሥራ እየተጣደፉ ስለነበር ወደ በኃላ ዝርዝር ሁነቱን እንደሚያሳውቁ ገልጸዋል። በቃላቸው ከተገኙ ቀጣይ ተጨማሪ ማብራሪያ የምናቀርብ ይሆናል።

በቅርቡ መርካቶ " ሸማ ተራ " ከፍተኛ የእሳት አደጋ ደርሶ በርካታ ዜጎች ንብረታቸውን ማጣታቸው የሚዘነጋ አይደለም። የዚሁ የአደጋው ምክንያት እና አጠቃላይ የደረሰው ውድመት " ተመርምሮና ተጣርቶና ለህዝብ ይፋ ይደረጋል " ከተባለ ሳምንታት ቢቆይም እስካሁን በይፋ የተባለ ነገር የለም።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

የፎቶ ባለቤት ፦ የአዲስ አበባ እሳት አደጋና ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን

@tikvahethiopia

EBS TV

17 Nov, 10:36


#ትግራይ

የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደተር በ4 ከተሞች የጠራቸው የህዝብ ስብሰባዎች በአንዱ ሲካሄድ በሦስቱ  ተስተጓጉሏል።

ለስብሰባዎች መሰተጓጎል የፀጥታ ስጋት እንደ ምክንያት መቀመጡ አንዳንድ የከተሞቹ ነዋሪዎች ይገልፃሉ።

ባለፈው እሮብ ህዳር 4/2017 ዓ.ም የትግራይ ምስራቃዊ  ዞን ዋና አስተዳዳሪ በመሆን በፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የተሾሙት ሰለሙን ትኩእ በዓዲግራት ከተማ ከዛላኣንበሳ ከተማ ተፈናቃዮች ለመወያየት እና በህዝብ የተመረጠ አዲስ አስተዳዳሪ ለመሾም የጠሩት ስብሰባ ፈተና የበዛበት ነበር።

ስብሰባ ከተከናወነበት አዳራሽ የወጡ የቪድዮ እና ድምፅ ፋይሎች እንደሚያሳዩት የማይናቅ ቁጥር ያላቸው እናቶች በስድብ ፣ ጩኸት እና ዋይታ ሰብሰባው እንዳይካይሄድ ሲከላከሉ ታይተዋል።

ቢሆንም የእናቶቹ ረብሻ በፀጥታ አካላት እንዲረገብ ሆኖ ወይይቱ ተካሂዶ የዛላምበሳ ከተማ አስተዳዳሪ በህዝብ ድምፅ እንዲመረጥ ሆኗል።

በትግራይ ምስራቃዊ ዞን የጉሎመኸዳ ወረዳ ሦስተኛ ከተማ የሆነችው የዛላኣንበሳ ከተማ እስካሁን በኤርትራ ስራዊት ቁጥጥር ስር እንደምትገኝ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ የወረዳው አስተዳዳሪዎችን ዋቢ በማድረግ በተደጋጋሚ  መዘገቡ ይታወሳል።

እሁድ ህዳር 8 /2017 ዓ/ም በትግራይ ምስራቃዊ  እና ማእከላዊ ዞኖች በሚገኙ ውቕሮ ፣ ዓብዩ ዓዲ እና አክሱም ከተሞች በጊዚያዊ አስተዳደሩ የተጠሩ ህዝባዊ ስብሰባዎች መሰረዛቸው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ምንጮች ጠቁመዋል።

ስብሰዎቹ ከፀጥታ ስጋት ጋር በተገናኘ የተሰረዙ እንደሆነ የገለጹ አሉ።

ከዚህ ተቃራኒ አስተያያት የሰጡ ደግሞ " በተለይ በዓብዩ ዓዲ እና አክሱም ከተሞች ሊካሄዱ ታቅተደው የተሰተጓጎሉት ህዝባዊ ስብሰባዎች በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት በዞኑ ያካሄደው የአስተዳደር  የስልጣን ግልበጣ አካል ናቸው " ብለዋል።

ዛሬ ሊካሄድ የታሰበው ስብሰባ የተሰተጓጎለባቸው የውቕሮ ፣ የተምቤን ዓብዩ ዓዲ እና የአክሱም ከተሞች በአሁኑ ሰዓት ከወትሮ የተለየ የፀጥታ ስጋትና መደፍረስ እንደሌለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ወደ ከተሞቹ ስልክ በመደወል አረጋግጧል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

EBS TV

17 Nov, 10:36


#OFC

“ አሁንም ቢሆን ሀገራዊ ምክክሩ በሚሄድበት አቅጣጫ እርካታ የለንም ” - ኦፌኮ

ከዚህ ቀደም በምክክሩ እንደማይሳተው ገልጾ የነበረው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ (ኦፌኮ) አሁንም እየተሳተፈ እንዳልሆነ፣ ኮሚሽኑ በሚሄድበት አቅጣጫ እርካታ እንደሌለው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጿል።

ፓርቲው ከዚህ ቀደም በሀገራዊ ምክክሩ እንዲሳተፍ ቢጋበዝም በምክክሩ እንዳልተገኘ አስታውሷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በበኩሉ፣ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ሥራውን መቀጠሉን እየገለጸ ነው፤ አሁንስ ፓርቲው ከኮሚሽኑ ጋር ተቀራርቦ ለመስራት አላሰበም ? ከምክክሩ የወጣበት ምክንያትስ ምንድን ነው ? ምላሽስ አላገኘም ? ሲል ጥያቄ አቅቧል።

ፓርቲው ምን ምላሽ ሰጠ ?

“ በእርግጥ ከዚህ ቀደምም ጥሪ ተደርጎልን ነበር። ችግሩ ከዝግጅት ጀምሮ ያለው እንቅስቀሴ አሳታፊ አልነበረም።

ሲጀመር የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ተጠሪነቱ 'ለጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ይሆናል’ ተባለ፣ ከዚያ ተመልሶ ‘ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይሆናል’ ተባለ። 

ይሄ ልዩነቱም አልታየንም። ምክንያቱም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም በገዢው ፓርቲ የተሞላ ስለሆነ ገልተኛነቱ ያን ያክል አስተማማኝ እንዳልሆነ ነው የምንረዳው። 

ምክንያቱም የሌሎች ተሳትፎ ወይ የለም ወይ በጣም አናሳ ነው፤ ኢንሲግኒፊካንት የሚባል ደረጃ ማለት ነው።

የኛ ሀሳብ ፓለቲካዊ ውይይቶች በፓለቲካ ኃይሎች መካከል መካሄድ ይኖርባቸዋል፣ ሁሉንም ኃይሎች አካታች መሆን አለበት የሚል ነው።

እኛ ሕዝብ ማወያየትን አንጠላም ወይም አናናንቅም ነገር ግን ከሕዝብ ጋር ከመድረሱ በፊት ወይም እየደረሰም እያለ ሌሎች የፓለቲካ ኃይሎች ሊነጋገሩበትና ሊፈቷቸው  የሚገቡ ነገሮች አሉ። 

ለምሳሌ በተለያዩ አካባቢዎች የኛ ፅሕፈት ቤቶች ተዘግተው ባሉበት፣ አባሎቻችንን ሰብስበን ማነጋገር ባልቻልንበት ሁኔታ፣ ለሀገራዊ ምክክሩ አጀንዳ መፍጠር የሚባለው ነገር ውስጥ መሳተፍ አስፈላጊ አይደለም።

እንደገናም ጦርነት እየተካሄደ ሀገራዊ ምክክር ብሎ ነገር ምንድን ነው? ይሄ እርስ በእርሱ የሚጋጭ ነገር ነው።

ይሄን እርስ በእርስ የሚጋጨውን ነገር የሆነ ጋፕ ስጡት፣ ለመነጋገር፣ ለመወያየት እድል ይሰጠው አገር እየተጠበቀ አገር ቢነጋገርበት ጥሩ ይሆናል በሚል ጥያቄ አቅርበን ነበር።

ይሄን የኛን ሀሳብና ጥያቄ ምንም ከዚህ ግባ አላሉትም። ምናልበት የተሻለ ነገር ቢያመጡ እኛም አጨብጭበን እንቀበላቸዋለንና እንዲሄዱ ነው የተውናቸው።

ኦፌኮ ብቻ ሳይሆን ሌሎች ፓርቲዎች አሉ እንደዚህ ያደረጉ። ጊዜና መነጋገር የሚፈልጉ፣ አንድ ወገንን ብቻ ተጠያቂ ከማድረግ እንድንቆጠብ የሚያደርጉ ነገሮች አሉ።

ስለዚህ ነገሮቹ መፍትሄ ካላገኙና የተወሰነ አቅጣጫ ካልተቀመጠላቸው እንዲያው ለመሳተፍ ተብሎ የምንሳተፍበት ምክንያት አይኖርም። 

አሁንም ቢሆን ሀገራዊ ምክክሩ በሚሄድበት አቅጣጫ እርካታ የለንም። እርካታ ቢኖረንና ብንሳተፍበት ጥሩ ነበር ”
ብሏል።

ለቀረበበት ትችት ምላሽ እንዲሰጥ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን፣ ኮሚሽኑ ለጊዜው በተደጋጋሚ ስብሰባ ላይ መሆኑን በመግለጹ ምላሹን እንደሰጠ የሚቀርብ ይሆናል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

EBS TV

17 Nov, 10:36


#AddisAbaba ዘንድሮ ለ24ኛ ጊዜ የተካሄደው ታላቁ ሩጫ በሰላም መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አሳውቋል።

ፖሊስ " ከአዲስ አበባ እና ከሀገራችን ከተለያዩ አካባቢዎች እንዲሁም የውጭ ሀገር ዜጎች የተሳተፉበት ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በስኬት ተጠናቋል " ብሏል።

@tikvahethiopia

EBS TV

17 Nov, 06:36


#እንድታውቁት

ነገ እሁድ በአዲስ አበባ ከተማ ለ24ኛ ጊዜ የተዘጋጀው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

መነሻና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ነው።

ውድድሩ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ የሚዘጉት መንገዶች ፦

- ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ (ኦሎምፒያ አደባባይ )
- ከጥላሁን አደባባይ ወደ ሳንጆሴፍ መብራት (ጥላሁን አደባባይ ) ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ
- ከአፍሪካ ህብረት መብራት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ (ጥይት ቤት መስቀለኛ )
- ከፓርላማ መብራት ወደ ኮንሰን መታጠፊያ (ፓርላማ መብራት )
- ከኮንሰን መታጠፊያ ወደ ገብርኤል (ኮንሰን መታጠፊያ )
- ከጥይት ቤት ወደ ገብርኤል በጀርባው (ጥይት ቤት መታጠፊያ )
- ከሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ (ሴቶች አደባባይ )
- ከሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ ቶታል (ሴቶች አደባባይ )
- ከ22 አደባባይ ወይም ዘሪሁን ህንፃ ወደ ዑራኤል አደባባይ (ዘሪሁን ህንፃ መስቀለኛ )
- ከፒኮክ አዲሱ መንገድ ወደ ዑራኤል አደባባይ (ፒኮክ መብራት)
- ከጋዜቦ አደባባይ ወደ ደንበል (ጋዜቦ አደባባይ)
- ከቂርቆስ ቤ/ክርስቲያን መስቀለኛ ወደ ለገሃር መብራት (ቂርቆስ ቤ/ክርሰቲያን ነርክ ተራ )
- ከላንድ ማርክ ሆስፒታል መታጠፊያ ገነት ሆቴል ወይም ወደ ገነት መብራት (ላንድ ማርክ ሆስፒታል መስቀለኛ )
- ከጠማማ ፎቅ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ (ጠማማ ፎቅ መስቀለኛ )
- ከአፍሪካ ህብረት መብራት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ (ሜክሲኮ ጥይት ፋብሪካ መስቀለኛ )
- ከፈረሰኛ መብራት ወደ ጨፌ ሜዳ (ፈረሰኛ መብራት )
- ከሞላ ማሩ መስቀለኛ ወደ ጌጃ ሰፈር (ጌጃ ሰፈር መስቀለኛ )
- ከከፍተኛ ፍ/ቤት አደባባይ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ (ከፍተኛ ፍ/ቤት አደባባይ)
- ከሠንጋ ተራ 40/60 ወደ ሠንጋ ተራ መብራት (ሠንጋ ተራ 40/60 መታጠፊያ)
- ከጎማ ቁጠባ መብራት ወደ ብ/ቲያትር (ጎማ ቁጠባ መብራት)
- ከሜትሮሎጂ መታጠፊያ ወደ ፖስታ ቤት መብራት (ሜትሮዎሎጂ መታጠፊያ )
- ከጥቁር አንበሳ ሼል ወደ ኢምግሬሽን (ጥቁር አንበሳ ሼል)
- ከጎላ ሚካኤል መስቀለኛ ወደ ኢምግሬሽን (ጎላ ሚካኤል መስቀለኛ)
- ከቴዎድሮስ አደባባይ ወደ አገር አስተዳደር መብራት (ቴዎድሮስ አደባባይ) ከንጋቱ 11:30 - ሰዓት ጀምሮ ውድድሩ እስከሚጠናቀቅ ይዘጋሉ።

ፖሊስ " ለጋራ ደህንነት ሲባል ፍተሻ ይኖራል " ብሏል።

" ከውድድሩ ዓላማ ውጪ ህገ-ወጥ ተግባራትንና መልእክቶችን ማስተላለፍ የውድድሩን መንፈስ የሚረብሽ ስለሆነ አዘጋጅ ተቋሙ እና ተሳታፊዎች ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው " ሲልም አሳስቧል።

@tikvahethiopia

EBS TV

16 Nov, 15:19


🔈#የዜጎችድምጽ

ችግሩ ቢነገር ቢነገር መፍትሄ ያልተገኘለት በክልሎች ያለው የቤንዚን ጉዳይ !

በክልል ከተሞች ነዳጅ በተለይም ቤንዚን ማግኘት ፈተና እንደሆነ ቀጥሏል።

በርካታ በትራንስፖርት ስራ ላይ የተሰማሩ ወጣቶች ባለው ችግር ምክንያት ሰርቶ መግባት ቤተሰብ ማስተዳደር ከባድ ሆኖባቸዋል።

ከክልል ከተሞች አንዷ የሲዳማ መዲናዋ ሀዋሳ ናት።

በዚህች ከተማ ነዳጅ እንደልብ ማግኘት ከቆመ ዓመታት አልፈዋል።

ያለው ችግር በተደጋጋሚ ቢነገርም በክልል መዲናይቱ ምንም የተቀየረ ነገር የለም። አሁንም ችግሩ እንደቀጠለ ነው። እንደልብ ነዳጅ ማግኘት አይቻልም።

አሽከርካሪዎች " ነዳጅ ማግኘት ከፍተኛ መከራ ሆኖብናል " ሲሉ ድምጻቸውን በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አሰምተዋል።

" ብላክ በኃይላድ እየተሞላ እንደሸቀጥ ዕቃ በየሱቁ አንድ ሊትር  ከ160 እስከ 180 ከዛም በላይ እየተሸጠ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

በከተማው በርካታ ማደያዎች ቢኖሩም ነዳጅ ማግኘት ስቃይ ነው።

ነዳጅ በፕሮግራም ማሸጥ ከተጀመረም በርካታ ወራት አልፈዋል።

ምንም እንኳን በየማደያው ቤንዚን የለም ይባል እንጂ ባጥቁር ገቢያ ነጋዴዎች በከፍተኛ ብር እንደጉድ ይቸበቸባል።

ቤንዚን ከከተማ እስከ ገጠር ድረስ ከጥቁር ገበያው ጠፍቶ አያውቅም።

ጉዳዩ ይመለከታቸዋል የሚባሉት የሥራ ኃላፊዎች " ችግሩ ይቀረፋል እየሰራን ነው " እያሉ ተደጋጋሚ ቃል ከመስጠት ውጪ ያመጡት መሬት ላይ የሚታይ ለውጥ እንደሌለ ነዋሪዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ባለው ሁኔታ ምክንያት " ሰርቶ መኖር በጣም ችግር ሆኖብናል " ብለዋል።

ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ እና ሌሎች ክልሎችም ብንመለከት የቤንዚን ችግር እንደዚሁ ነው።

በየማደያው የለም የሚባለው ቤንዚን ከጥቁር ከገበያ እንደልብ ሲገኝ ይታያል።

ቃላቸውን የሰጡን ነዋሪዎች " ቤንዚን በየሱቁ ፤ በየመንደሩ እንደጉድ ይቸበቸሻል ነዳጅ ማደያ ሲኬድ የለም ነው መልሳቸው " ብለዋል።

" ህዝብ እየተሰቃየ ነው። በተለይ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ዜጎች መከራቸውን እያዩ ነው። ችግሩ በርካታ ጊዜ ቢያልፈውም ለምን ማስተካከል እንዳልተቻለ ሊገባን አልቻለም " ሲሉ አክለዋል።

ከነዳጅ ማደያዎች ሌሊት በሲኖትራክ ሳይቀር ነዳጅ ተጭኖ እንደሚወጣ ፤ በዚህ የጥቁር ገበያና የነዳጅ ሽያጭ ሰንሰለት እጃቸው የረዘመ በመዋቅር ውስጥ ያሉ አካላት ሊኖሩ እንደሚችላ ጠቁመዋል።

በየመዋቅሩ ተጠቃሚ ሰዎች ባይኖሩ እንዴት ይሄን ያህል ጊዜ ችግሩ ይቀጥላል ? ሲሉም ጠይቀዋል።

ለአብነት ወላይታ ሶዶ ከተማ ውስጥ ቤንዚን ማግኘት አይታሰብም።

በጥቁር ገበያ እስከ 200 ብር ድረስ ይቸበቸድረስ

ከዚህ ባለፈ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከነዋሪዎች እንደሰማው አንዳንድ ከከተማ የወጡ ማደያዎች ሳይቀሩ ነዳጅ በድብቅ ይሸጣሉ።

አንድ ሊትር ቤንዚን 92 ብር መሸጥ ሲገባው ከጀርባ በትውውቅ እስከ 220 ብር ድረስ ለመሸጥ የሚደራደሩ አሉ።

ይህ ሁሉ ሲሆን ግን የመፍትሄ እርምጃ ሲወሰድ እና ማስተካከያ ሲደረግ አይታይም።

በአጠቃላይ በክልል ከተሞች በቤንዚን ምክንያት ስራ መስራት ፈተና እንደሆነ ነው። ከከተማ ወጥቶ ለመስራትም እየተቻለ አይደለም።

የዚህ ሁሉ ችግር መጨረሻ የሚወርደው ህዝብ ላይ ነው። " ነዳጅ የለም ተወዷል " በሚል በትራንስፖርት ተገልጋዩ ዜጋ ላይ የሚጨመረው ዋጋ ከፍተኛ ነው ፤ ካለው የኑሮ ውድነት ጋር ይሄ ተጨምሮ የሚያሳድረው ተፅእኖ እንዲሁ በቃላት የሚገለጽ አይደለም።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia

EBS TV

16 Nov, 15:19


🔈 #የጤናባለሞያዎችድምጽ

በአማራ ክልል፣ ደቡብ ወሎ ዞን ቃሉ ወረዳ በዘጠኝ ጤና ጣቢያ ውስጥ የሚሰሩ የጤና ባለሞያዎች ከግንቦት 2016 ዓ/ም ጀምሮ ያልተከፈላቸው  የተጠራቀመ የትርፍ ሰዓት ስራ (ዲዩቲ) ክፍያቸው ሳይከፈላቸው እንደቆየ ተናግረዋል።

ክፍያቸው እንዲፈጸምላቸው ተደጋጋሚ የሆነ ጥያቄ ለወረዳው እና ለጤና ጽ/ቤቱ ሲጠይቁ የቆዩ ሲሆን የወረዳው ጤና ጽ/ቤት ከ6 ወር ክፍያው ውስጥ የ2 ወሩን እንደከፈላቸው ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያቀረቡ የጤና ባለሞያዎች ተናግረዋል።

ቅሬታ አቅራቢዎች የቀረውን የ4 ወር ክፍያ ለመፈጸም ግን ከወረዳው " በጀት የለንም " የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸው ተናግረዋል።

ያነጋገርናቸው የጤና ባለሞያዎች " ወረዳው በክልሉ ካሉ የሰላም ወረዳ (ቀጠና) አንዱ ነው የመንግስት ስራ በሁሉም ሴክተር እየተሰራ ነው ያለው የግብር እና የታክስ መሰብሰብ ስራም በአግባቡ እየተሰራ ነው የበጀት እጥረት አጋጠመን የሚባለው በጭራሽ ከእውነት የራቀ ነው " ብለዋል።

" በዞኑ የሚገኙ አጎራባች ወረዳዎችን፣ ኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር፣ ባቲ ወረዳ፣ አርጎባ ልዩ ወረዳ እና ሌሎችም ወረዳዎች ለባለሙያዎቻቸው የሰሩበትን የትርፍ ሰዓት ክፍያ ከፍለዋል የእኛ በምን ተለይቶ ዘገየ " የሚል ጥያቄን አንስተዋል።

በወረዳው ከሚገኙ ጤና ጣቢያዎች አንዱ ከሆነው " ደጋን " ጤና ጣቢያ ሁለት የጤና ባለሞያዎች ማክሰኞ 03/03/17 ዓም በጸጥታ አካላት ተወስደዋል።

የጤና ባለሞያዎች ለእስር የተዳረጉት ካልተከፈላቸው ክፍያ ጋር በተገናኘ የሰሩበትን የትርፍ ሰዓት ክፍያ እንዲከፈላቸው የሚጠይቅ ጽሁፍ " በሶሻል ሚዲያ አጋርታቹሃል " በሚል ሳይሆን እንዳልቀረ ተነግሯል።

ባለሞያዎቹ ከ4 ቀናት እስር በኋላ ትላንት ምሽት ተፈተዋል።

የቃሉ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ሙህዲን አህመድ ለጤና ባለሞያዎቹ ክፍያው በእርግጥም አለመፈጸሙን አረጋግጠው ያልተከፈላቸው ግን በበጀት እጥረት ምክንያት አለመሆኑን ተናግረዋል።

" ክፍያው የዘገየው በየጤና ጣቢያዎቹ የሚሰጠው አገልግሎት እና የሥራ ጫና የሚለያይ በመሆኑ የሚያድረው የጤና ባለሞያ ቁጥርም ይለያያል በዛ ምክንያት ደረጃ ይውጣለትና በሚሰጡት አገልግሎት እና ባለባቸው የስራ ጫና ልክ ይከፈላቸው ተብሎ ይህንን የሚያጣራ ኮሚቴ ተቋቁሞ በወረዳው በሚገኙ በዘጠኙም ጤና ጣቢያዎች እያጣራ ነው ሪፖርቱን እንዳቀረበ ይከፈላቸዋል " ብለዋል።

በሌሎች ትይዩ ወረዳዎች ላይ ከክፍያ ጋር በተያያዘ ተመሳሳይ ችግር የለም ይህ በቃሉ ወረዳ ለምን ተፈጠረ ለሚለው የቲክቫህ ጥያቄ " የእኛ ወረዳ ከሌሎች የጎንዮሽ ወረዳዎች ጋር ለማነጻጸሪያ ቢቀርብ የተሻለ ከፋይ ነው " ብለዋል።

ታሰሩ ስለተባሉት ባለሞያዎች መረጃው እንደሌላቸው ተናግረው በሌላ ጉዳይ ተጠርጥረው ካልታሰሩ በቀር በክፍያው ጉዳይ አይታሰሩም ብለዋል።

" ከተያዙም ሌላ የጸጥታ ስራ ስላለ በዛ ምክንያት ተጠርጥረው ነው የሚሆነው በተባለው ምክንያት ከሆነ ግን አጣርቼ ልጆቹን ትሪት አደርጋለው " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia

EBS TV

16 Nov, 03:40


" በቴ ምን ያህል ለህዝቡ አስፈላጊ እንደነበር በህዝቡ ሁኔታ፣ በህዝቡ ለቅሶ ተመልክቻለሁ ! " - የፖለቲከኛ አቶ በቴ ኡርጌሳ ባለቤት

ከወራት በፊት መቂ ላይ በግፍ የተገደሉት የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ከፍተኛ አመራር ፖለቲከኛው አቶ በቴ ኡርጌሳ ባለቤት ከልጆቻቸው ጋር ከሀገር ወጥተው አሜሪካ መግባታቸው ተሰምቷል።

ባለቤታቸው ወ/ሮ ስንታየሁ አንበሴ በአጭር ቪድዮ ባሰራጩት ቃላቸው ፥ አሁን ላይ ከልጆቻቸው ጋር አሜሪካ ሀገር እንደሚገኙ ገልጸዋል።

" ባለቤቴ በቴ ኡርጌሳ ከሞተ 7ኛ ወር ሊሞላ ነው። " ብለዋል።

" በዓለም ላይ ያላችሁ ሃዘናችንን የተካፈላችሁ ፣ የኦሮሞ ኮሚውኒቲ ፤ በቴ ምን ያህል ለህዝቡ አስፈላጊ እንዳሆነ በሃዘናችሁ ፤ ባለው ነገር ሁሉ አይተናል " ሲሉ ገልጸዋል።

" እሱ ካረፈበት ቀን ጀምሮ በሀዘናችን ያለቀሳችሁ፣ ከኛ ጋር ያዘናችሁ ፣ በገንዘባችሁ በሃሳባችሁ በጸሎታችሁ የረዳችሁን እግዚአብሔር ይስጥልን ፤ እናመሰግናለን " ብለዋል።

" የኛን ሰላም መሆን ለተጨነቃችሁ ፤ ድምጻችን ሲጠፋ ለተጨነቃችሁ ' ምን ሆናችሁ ነው ? ' ላላችሁን ያለንበትን ለመግለፅ ነው  ፤ አሁን ያለነው አሜሪካ ነው ፤ በሰላም ደርሰናል " ሲሉ ገልጸዋል።

" ኤምባሲዎች በጣም እናመሰግናለን ፤ ያለንበት ቦታ ድምጻችን የጠፋባችሁ ስልካችን እንቢ ያላችሁ ፣ ቤታችን ድረስ ሄዳችሁ ያጣችሁን ምን ሆናችሁ ነው ? ላለችሁን ላደረጋችሁልን ነገር ሁሉ እናመሰግናለን " ብለዋል።

" በቴ ምን ያህል ለህዝቡ አስፈላጊ እንደነበር በህዝቡ ሁኔታ፣ ለቅሶ ተመልክቻለሁ " ያሉት ወ/ሮ ስንታየሁ " እኔ እውነት ለመናገር በቴ ከሞተ በኃላ ነው ህዝቡ እንዴት በቴን ያውቅ እንደነበር የተረዳሁት ምክንያቱም በቴን እንደዚህ አላውቀውም ነበር እውነቱን ለመናገር ከጫፍ ጫፍ ነው ህዝቡ ያዘነው " ሲሉ በእምባ ታጅበው ስሜታቸውን ገልጸዋል።

እምባቸውን 😭 እያፈሰሱ የተናገሩት የበቴ ባለቤት " እሱ የኢትዮጵያ ብቻ አይደለም የዓለም ሰው እንደሆነ አውቃለሁ " ብለዋል።

አሁንም ከጎናቸው ሆነው በብዙ ነገር እየረዷቸው ላሉ በተለይ ለኦሮሞ ኮሚውኒቲ ፣ በውጭ ሆነው በስልክ እየደወሉ እያፅናኗቸው ያሉ፣ በፀሎታቸው ፣ በገንዘብ እየደገፏቸው ላሉ  ሁሉ " እግዚአብሔር ይስጥልን " ሲሉ አመስግነዋል።

ወ/ሮ ስንታየው አንበሴ ፤ ልጆቻቸው ደህንነታቸው የተጠበቀ ቦታ ላይ እንዳሉና ትምህርትም እንደጀመሩ ገልጸዋል።

ወደፊት ጊዜው ሲደርስ ደግሞ ስላሳለፉት ነገር እንደሚገልጹ ቃል ገብተዋል።

ለተደረገላቸው ነገር ሁሉ እያነቡ በልጆቻቸው ስም ምስጋና አቅርበዋል።

የ4 ልጆች አባቱ ፖለቲከኛው በቴ ኡርጌሳ ከወራት በፊት መቂ ላይ በግፍ መገደላቸው ይታወሳል። ከዛ በኃላ " ማጣራት ተደርጎ ስለ ግድያው ዝርዝር ማብራሪያ ለህዝቡ ይሰጣል " ተብሎ ቃል ቢገባም እስከ ዛሬ ስለ ግድያው ሁኔታ ፣ ከግድያው ጋር በተያያዘ ተጠያቂ ስለሆነ አካል በይፋ አንድም የተባለ ነገር የለም።

የፖለቲከኛ አቶ በቴ ኡርጌሳ ጉዳይ " ቄሱም ዝም መፅሃፉም ዝም " እንዲሉ ሆኖ ቀጥሏል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia

EBS TV

06 Nov, 03:48


#አጠቃላይየትምህርትአቂቅአዋጅ

በአገር አቀፍ፣ በክልል ወይም በአካባቢ ደረጃ ያለው የትምህርት ደረጃና ጥራት ከተጠበቀው በታች መወረዱ ሲረጋገጥ የሚመለከታቸው ፦
➡️ የፌደራል፣
➡️ የክልል
➡️ የአካባቢ የትምህርት አስተዳደር ኃላፊዎችን ተጠያቂ የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ ለፓርላማ ቀርቧል።

የአጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ አዋጅ ባለፈው ሳምንት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውይይት ተደርጎበት ለሰው ሀብት ልማት የሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ለዝርዝር ዕይታ በአብላጫ ድምፅ ተመርቷል፡፡

ረቂቁ ምን ይዟል ?

🟢 የትምህርት ደረጃና ጥራት ከሚጠበቀው በታች የወረደ መሆኑ ሲረጋገጥ የትምህርት ተቋሙ፣ ጉዳዩ የሚመለከታቸው መምህራን፣ ሌሎች ለችግሩ አስተዋጽኦ ያደረጉ አካላትና ግለሰቦች ተጠያቂዎች እንደሚሆኑ ተደንግጓል፡፡

🟢 በሒደቱ የትምህርት ደረጃና ጥራት መርማሪዎችን ሥራ ለማሰናከል የሚደረጉ ተግባራት የተከለከሉ መሆናቸው ተደንግጓል።

🟢 የአጠቃላይ የትምህርት ደረጃ ጥራትን በባለቤትነት የሚያስጠብቅ የትምህርት ቁጥጥርና ክትትል አገልግሎት የሚሰጥ መንግሥታዊ ተቋም በትምህርት ሚኒስቴር ሥር እንደሚቋቋም ተካቶበታል፡፡

🟢 የመንግሥት ዋነኛ ተግባር ዕድሜው ለትምህርት የደረሰ ማንኛውም ሕፃን ለአጠቃላይ ትምህርት ያለውን መብት ተግባራዊ ማድረግ፣ ተማሪውም የአንደኛና መለስተኛ ትምህርቱን ለመከታተል ያለበትን ግዴታ መወጣቱን ማረጋገጥ ያስችላል።

🟢 በትምህርት ዘርፍ ለሚሳተፉ ባለሀብቶችና ሌሎች መንግሥታዊ ላልሆኑ አካላት፣ በአገሪቱ የኢንቨስትመንት ሕግና አግባብ ባላቸው ሕጎች መሠረት ማበረታቻ ይሰጣል።

🟢 ስለትምህርት ክፍያ አለመኖር በሚያብራራው አንቀጽ በማንኛውም የመንግሥት አጠቃላይ የትምህርት ተቋም ውስጥ በመደበኛው የትምህርት መርሐ ግብር ከሚማር ተማሪ ከወላጆች ወይም ከአሳዳሪዎች የትምህርት ክፍያ፣ የመማርያ መጻሕፍት ዋጋ ወይም የመመዝገቢያ ክፍያ መቀበል ክልክል ስለመሆኑ ተደንግጓል፡፡

🟢 ክልሎች በሚያወጠት ሕግ መሠረት ለሌሎች የትምህርት መሣሪያዎች የሚውል መጠነኛ ክፍያ ከተማሪ ወላጆች የመክፈል አቅም ጋር በተጣጣመ መንገድ ሊያስከፍሉ እንደሚችሉ ተደንግጓል። ድንጋጌው ቢኖርም ይህንን አላሟላህም ተብሎ ተማሪው ከትምህርት ገበታው እንዲለይ ማድረግ አይቻልም።

🟢 የቅድመ አንደኛ ደረጃ መግቢያ ከአራት ዓመት እስከ ስድስት ዓመት ሲሆን፣ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ዕድሜ ደግሞ ሰባት ዓመት ተደርጓል፡፡

🟢 ተማሪዎች ቢያንስ ሦስት ቋንቋዎችን እንዲማሩ እንደሚደረግ ተደንግጓል። እንግሊዝኛ ቋንቋ ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ እንደ አንድ የትምህርት ዓይነት ይሰጣል። እንዲሁም አንድ ተጨማሪ የውጭ ቋንቋ ክልሉ በሚመርጠው መሠረት ከዘጠነኛ ክፍል ጀምሮ በአማራጭነት እንዲሰጥ ይደረጋል።

🟢 ማንኛውም ሰው ተገቢው የማስተማር ሥራ ፈቃድ ሳይኖርው በአጠቃላይ ትምህርት ተቋማት ውስጥ በመምህርነት ሊሠራ እንደማይችል የተደነገገ ሲሆን፣ ለዚህ የሚረዳና የሥራ ፈቃድ አሰጣጥን የተመለከተ ስታንዳርድ መመርያ በትምህርት ሚኒስቴር በኩል ይወጣል።

🟢 ከቅድመ ሥራ ሥልጠና በኋላ በመምህርነት የሚመደብ ሰው በቅድሚያ የሁለት ዓመት የትውውቅ ሥልጠና የመከታተልና ለዚህም የሚሰጠውን መመዘኛ ፈተና የማለፍ ግዴታ አለበት። ይህን ግዴታ ከተወጣ በኋላ በዚህ አንቀጽ የሥራ ፈቃድ እንደሚሰጠው ተደንግጓል፡፡

🟢 የመምህራን የሙያ ፈቃዱ በየሁለት ዓመቱ መታደስ ያለበት ሲሆን፣ ዕድሳቱ ከማንኛውም የፈቃድ ክፍያ ነፃ ተደርጓል፡፡ ይህ ዕድሳት ለመምህራን ደረጃ ዕድገት እንደሚረዳ ተቀምጧል፡፡

🟢 በውጭ አገር ማኅበረሰቦች የሚቋቋሙ ትምህርት ቤቶች ከሚያስፈልጋቸው በጀት በአገራቸው መንግሥት 30 በመቶ የሚደገፉ እንደሆኑ፣ ቀሪውን 70 በመቶ ራሳቸው መሸፈን የሚችሉ መሆናቸውን የሚያሳይ ማረጋገጫ ማምጣት አለባቸው።

🟢 ኢትዮጵያ ውስጥ በሚቋቋሙ የውጭ አገር ማኅበረሰብ ትምህርት ቤቶችና ዓለም አቀፍ ትምህርት ቤቶች የሚያስተምሩ መምህራን ከሚመለከተው አገር የሥራ ፈቃድ ማምጣት እንደሚገባቸው ተደንግጓል፡፡ (ሪፖርተር ጋዜጣ)

@tikvahethiopia

EBS TV

05 Nov, 14:00


#Ethiopia #USA

አሜሪካ በአማራ ክልል እየተባባሰ የሄደው ግጭት እንዳሳሰባት ገለጸች።

የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒዮ ብሊንከን " የርስ በርስ ግጭቶች እልባት ያገኙ ዘንድ የፖለቲካ ውይይቶች መደረግ አለባቸው " ብለዋል።

አንቶኒ ብሊንከን ይህንን ያሉት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር ባደረጉት የስልክ ውይይት እንደሆነ ተነግሯል።

ብሊንከን "በአማራ ክልል የቀጠለው ግጭት ያሳስበኛል" ሲሉ የተናገሩ ሲሆን ሌሎች በኢትዮጵያ ውስጥ የሚካሄዱ ግጭቶችን ጨምሮ የውስጥ ግጭቶችን ለመፍታት የፖለቲካ ውይይት እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ ከጠቅላይ ሚንስትር አቢይ ጋር በነበራቸው የስልክ ቆይታ " በፕሪቶሪያው ስምምነት እና አፈጻጸሙ ዙሪያ " መነጋገራቸውን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

ኢትዮጵያ ስምምነቱን ተግባራዊ ለማድረግ የምታደርገውን ጥረት የሀገራቸው እገዛ እንደማይለያት የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ ተናግረዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒዮ ብሊነክን በአፍሪቃ ቀንድ ቀጣና እየተባባሰ ነው ያሉት ውጥረት እንዲረግብም በዚሁ ጊዜ መጠየቃቸውን ተዘግቧል።

#AFP #DW

@tikvahethiopia

EBS TV

05 Nov, 14:00


ፎቶ ፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነው በአፍሪካ የመጀመሪያው ኤርባስ ኤ350-1000 አውሮፕላን ዛሬ ኢትዮጵያ ገብቷል።

#EthiopianAirlines🇪🇹

@tikvahethioia

EBS TV

05 Nov, 06:27


#US

ነገ በአሜሪካ ከሚደረገው ኦፊሴላዊ የድምፅ መስጫ በፊት ባሉት ጥቂት ቀናት ብቻ ከ78 ሚሊዮን በላይ ሰዎች " ለሀገራችን ይሆናታል ፣ ይበጃታል " ያሉትን መርጠዋል።

አሜሪካ እና ዜጎቿ በዓለም ከሚታወቁባቸው ጉዳዮች አንዱ የምርጫ ስርዓታቸው ነው።

የሀገሪቱ ዜጎች በምርጫ ጉዳይ ቀልድና ፌዝ አያውቁም ምክንያቱም የነገ ዕጣፋንታቸው የሚወስነበት ስለሆነ።

ለዚህ ነው በነቂስ እየተሳተፉ " ይሆነናል ፣ ለሀገራችን ይጠቅማል " የሚሉትን ተመራጭ የሚመርጡት።

በዘንድሮው ምርጫ ካማላ እና ትራምፕ አንገት ለአንገት የሚተናነቁበት እጅግ ብርቱ ፉክክር ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።

@tikvahethiopia

EBS TV

05 Nov, 06:27


#ቦትስዋና👏

ከሰሞኑን በቦትስዋና በተካሄደው ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ መሸነፋቸውን ያመኑት ሞከዌትሲ ማሲሲ ለአዲሱ ተመራጭ ፕሬዜዳንት ዱማ ቦኮ በይፋ በሰላም ፤ አቅፈዋቸውን ስልጣናቸውን አስረክበዋል።

ላለፉት 58 ዓመታት በሥልጣን ላይ የቆየው ' የቦትስዋና ዲሞክራቲክ ፓርቲ ' ህዝቡ በድምጹ ቀጥቶት ከባድ ሽንፈት አስተናግዶ መሪነቱን ተነጥቋል።

ይህ ፓርቲ አፍሪካ ውስጥ ረጅም ዓመታትን በግዢነት የቆየ ነው።

ተቃዋሚ ፓርቲ የነበረው ' አምብሬላ ፎር ዲሞክራቲክ ቼንጅ ' በከፍተኛ ብልጫ በማሸነፍ ፕሬዜዳንታዊ ስልጣኑን ተቆጣጥሯል።

ተሰናባቹ ፕሬዝዳንት በምርጫ መሸነፋቸውን ካመኑ በኃላ መላው ህዝብ በአንድነት አዲሱን የመንግሥት አስተዳደር እንዲደግፍ ጥሪ አቅርበዋል።

ቦትስዋና አፍሪካ ውስጥ በተረጋጋ ሰላም እና ዴሞክራሲያዊ ስርዓቷ በቀዳሚነት ትጠቀሳለች።

#ዴሞክራሲ #ምርጫ

@tikvahethiopia

EBS TV

04 Nov, 13:58


" ከገጠመን ችግር ውስብስብነት የተነሳ በየቦታው የምናየው ተስፋ የመቁረጥ ስሜት ይመስላል " - ዶ/ር ዳንኤል በቀለ

ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም መታሰቢያ ፋውንዴሽን 4ኛ ዓመታዊ ጉባኤውን ትላንት እሁድ በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ አካሂዷል።

ጉባኤው ትኩረቱን ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ከተቋቋመበት እና ስራ ከጀመረነት ጌዜ አንስቶ ምን ምን አብይ ጉዳዮችን አከናወነ ? ምን እንቅፋቶች ገጠሙት? ለእንቅፋቶቹስ ምን መፍትሄ ሰጠ የሚለውን ዋና የመወያያ አንጀዳ አድርጎ ነበር።

በዚሁ መድረክ የቀድሞ የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ  (ዶ/ር) ንግግር አድርገዋል።

ዳንኤል (ዶ/ር) ፤ " ትልቁ ጥያቄ መሆን ያለበት ሰላም እንዴት ይምጣ ? የሚለው ነው " ብለዋል።

መንግስትም ሲጠየቅ " ሰላም እፈልጋለሁ፣ ሽማግሌ ልክያለሁ ሞክሬያለሁ፣ ሰላም አጥተናል ሰላም እንዲሆን እመኛለሁ " ይላል።

ታጣቂ ቡድኖችም ሲጠየቁ " እኛም ሰላም እንፈልጋለን ተገደን ነው ወደዚህ ነገር ውስጥ የገባነው " ይላሉ።

ስለዚህ ሁለቱም ሰላምን እንፈልጋለን የሚሉ ወገኖች ናቸው ሰላምን እንዴት እናጸናለን የሚለው ግን ከባድ ጥያቄ ሆኖብናል ኢትዮጵያ ውስጥ ሲሉ ገልጸዋል።

" ይሄ የሰላም ጥያቄ ለመንግሥት እና ለተፋላሚ ወገኖች ብቻ የሚተው መሆን የለበትም " ብለዋል።

ተመሳሳይ የሆነ የግጭት ዓውድ ውስጥ ባለፉ ሃገሮች ልምድ መሰረት ዘላቂ ሰላም እንዲመጣ የሚከተሏቸው ስልታዊ እና ተቋማዊ ሂደቶች አሉ እነዚህም የሃገራዊ ምክክር እና የሽግግር ፍትህ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

እነዚህ ሁለት መፍትሄዎች ቀደም ብለው ተጀምረው ተግባራዊ እየሆኑ መሆኑን ተናግረው የተዓማኒነት ጥያቄ ግን እየተነሳባቸው መሆኑን አንስተዋል።

" ሂደቱ በተቻለ መጠን ሁሉን አሳታፊና ተዓማኒ እንዲሆን ይፈለጋል፤ ነገር ግን በተዓማኒነታቸው ላይ ጥያቄ ምልክት ተነስቶባቸዋል። ይህ አይነቱ የተዓማኒነት ጥያቄ ግን በኢትዮጵያ ብቻ የተነሳ ጥያቄ አይደለም ተመሳሳይ ሂደት በተከተሉ ሃገሮች በሙሉ ጥያቄ ተነስቶባቸዋል " ሲሉ ገልጸዋል።

" የተዓማኒነት ጥያቄው የኢትዮጵያ ብቻ ችግር ባይሆንም በቀላሉ የሚታይ ግን አይደለም ነው " ያሉት።

" አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ከገጠመን ችግር ውስብስብነት የተነሳ በየቦታው የምናየው ተስፋ የመቁረጥ ስሜት ነው " ያሉት ዶ/ር ዳንኤል፤ " ከችግሩ ክብደት አንጻር ላይገርም ይችላል ነገር ግን ብዙ ነገሮች እየመጡ ሲያልፉ አይተናል አሁን ያለውም ችግር ከኢትዮጵያውያኖች አቅም በላይ ነው ብዬ አላስብም " ብለዋል።

#TikvahEthiopiaAddisAbaba

@tikvahethiopia @tikvahethmagazine

EBS TV

04 Nov, 13:58


የREMEDIALፕሮግራም ምደባ ይፋ ሆነ።

በ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የREMEDIAL ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ይፋ ተደርጓል።

ከአሁን ሰዓት ጀምሮ ተማሪዎች ምደባቸውን ፦
➡️ በዌብሳይት : https://placement.ethernet.edu.et 
➡️ በቴሌግራም : https://t.me/moestudentbot ላይ መመልከት እንደሚችሉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

ተማሪዎች ተቋማት በሚያስተላልፉት ጥሪ  መሰረት የREMEDIAL ፕሮግራሙን እንዲከታተሉ ተብሏል።

ትምህርት ሚኒስቴር የተቋም ይቀየርልኝ ጥያቄ የማያስተናግድ መሆኑን ገልጿል።

@tikvahethiopia

EBS TV

31 Oct, 19:12


#ቅዱስሲኖዶስ

" በጦርነትና በግጭት የመጣ ሰላም፣ የተገነባ ሀገር የለም !! ... ችግሩ በእርቅ እንዲፈታ ለሁሉም ወገኖቻችን የሰላም ጥሪ እናቀርባለን " - ቅዱስ ሲኖዶስ

የጥቅምት 2017 ዓ/ም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ስብሰባ ተጠናቋል።

ምልዓተ ጉባኤው ከጥቅምት 11 እስከ ጥቅምት 20 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ መደበኛ ስብሰባውን ሲካሄድ ሰንብቷል፡፡

ቅዱስ ሲኖዶስ በመንፈሳዊ፣ በማኅበራዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ ማሳለፉ ተገልጿል።

የስብሰባውን መጠናቀቅ ተከትሎ በቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ተሰጥቷል።

ከመግለጫው የተወሰደ ፦

" በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች እየተከሰተ ባለው የሰላም እጦት፣ የእርስ በርስ ግጭት ምክንያት የሰው ሕይወት እየተቀጠፈ፣ አካል እየጎደለ፣ ማኅበራዊ ትሥሥር እየተናደ፣ ሰብአዊ ክብር እየተጎዳ፣ መብት እየተጣሰ፣ በዜጎች ላይ ሥጋትና አለመረጋጋት እየበዛ ሀብትና ንብረት እየወደመ ስለሆነ ጉዳዩ አስቸኳይ መፍትሔ የሚያስፈልገው መሆኑ አጠያያቂ አይደለም፡፡ 

ስለሆነም በጦርነትና በግጭት የመጣ ሰላም፣ የተገነባ ሀገር የለምና በሀገራችን እያጋጠመ ያለውን ችግር ለመፍታት ካለፈው በመማር በጥበብ፣ በማስተዋልና በሰለጠነ አካሄድ በሰላማዊ መንገድ በመወያየት ችግሩ በእርቅ እንዲፈታ ለሁሉም ወገኖቻችን ቅዱስ ሲኖዶስ የሰላም ጥሪውን በአጽንኦት ያቀርባል፡፡ "


(ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት)

/ ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል /

@tikvahethiopia

EBS TV

31 Oct, 19:12


#NBE : ዛሬ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፤ ባንኮች እርስ በርሳቸው የሚበዳደሩበት የገንዘብ ግብይት ይፋ አድርጓል።

ንግድ ባንኮች የአጭር ጊዜ ማለትም ለአንድ ቀን ወይም ለሰባት ቀናት መቆየት የሚችል ገንዘብ መበደርና ማበደር የሚችሉ መሆናቸውንም አብስሯል።

በባንኮች መካከል የሚደረግ የገንዘብ ግብይት መጀመሩ ፦

➡️ ባንኮች የአጭር ጊዜ የገንዘብ ጉድለትን በመሸፈን ወይም ትርፍ ገንዘብን ለሌሎች ባንኮች በማበደር የገንዘብ ፍሰትን በብቃት እንዲያስተዳደሩ ያስችላቸዋል።

➡️ የገንዘብ ግብይቱ የአጭር ጊዜ ማለትም የአንድ ቀን ወይንም የሰባት ቀናት የመክፈያ ጊዜ ያላቸው ብድሮችን ያካትታል ፤ ይህ ባንኮች የአጭር ጊዜ የገንዘብ ጉድለትን በመሸፈን ወይም ትርፍ ገንዘብን ለሌሎች ባንኮች በማበደር የገንዘብ ፍሰትን በብቃት እንዲያስተዳደሩ ያስችላቸዋል።

➡️ የገንዘብ እጥረት ስጋትን በመቀነስና በተረጋጋ የወለድ ተመን ለደንበኞች የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት ያስችላል ሲል ብሔራዊ ባንክ አሳውቋል።


በባንኮች መካከል የሚደረግ የገንዘብ ግብይት በኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ የግብይት መድረክ ላይ ብቻ እንዲሆ ብሔራዊ ባንክ ፈቅዷል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

#NBE

@tikvahethiopia

EBS TV

31 Oct, 18:24


#DStvEthiopia

ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓም በኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት አዳራሽ ( ወመዘክር ) በተከናወነው “የአቦል አዳዲስ ይዘቶች ማስተዋወቂያና የአፋፍ ቴሌኖቬላ ማጠናቀቂያ” የአቦል አዳዲስ ተከታታይ ድራማዎች አዘጋጆች በመድረኩ ልምዳቸውንና የአቦልን አስተዋፅኦ ያጋሩ ሲሆን ይዘቶቻቸውንም አስተዋውቀዋል።

አንተህ ኃይሌ ስለ “የእሳት እራት” ቴሌኖቬላ፣ ኑር አክመል ስለ “አሻራ” ቴሌኖቬላ፣ ፌቨን ከተማ ስለ “የልቤ” ድራማ እንዲሁም ኡስማን አወል ስለ ማዲ አቦል ይዘቶች ገለፃ አድርገዋል።

የአቦል አዳዲስ ተከታታይ ድራማዎች አዘጋጆች በመድረኩ ልምዳቸውንና የአቦልን አስተዋፅኦ ያጋሩ ሲሆን ይዘቶቻቸውንም አስተዋውቀዋል።

አንተህ ኃይሌ ስለ “የእሳት እራት” ቴሌኖቬላ፣ ኑር አክመል ስለ “አሻራ” ቴሌኖቬላ፣ ፌቨን ከተማ ስለ “የልቤ” ድራማ እንዲሁም ኡስማን አወል ስለ ማዲ አቦል ይዘቶች ገለፃ አድርገዋል።

መርሃግብሩ አስተዋፅኦ ላደረጉና በአፋፍ የዝግጅት ሂደት ለተሳተፉ ባለሙያዎች የዕውቅና የምስክር ወረቀት በመስጠት ተጠናቋል።

#ሁሉምያለውእኛጋርነው

EBS TV

31 Oct, 18:24


ዛሬም ድረስ አንዳንድ ተቋማት ኢ-ህገመንግስታዊ የሆኑ የአለባበስ (ድሬሲንግ) ኮዶችን በመጥቀስ ብዙ ሙስሊሞችን በትምህርት፣ በስራ ገበታ ላይ አስተዋፅኦ እንዳያደረጉ እንቅፋት እየሆኑ እንዳሉ የፓርላማ አባሉ ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ ተናግረዋል።

ይህንን ያሉት ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተገኙበት የምክር ቤቱ ስብሰባ ላይ ነው።

ዛሬ እንኳን አሉ ኡስታዝ " ዛሬ እንኳን እኛ እዚህ ቁጭ ብለን ተማሪዎች በኒቃባቸው በሂጃባቸው ምክንያት ከትምህርት ገበታቸው ተገለው አንዳንድ አካባቢዎች እስከ ሁለት ዓመት ድረስ የሄዱ በሺህ የሚቆጠሩ ተማሪዎች አሉ " ሲሉ ተናግረዋል።

ይህ አይነት ድርጊት እጅግ ጎጂ መሆኑን በማንሳት መንግሥት መሰል ድርጊቶች እንዲታረሙ እንዲያደርግ የሚያስገነዝብ ሃሳብና ጥያቄ በይፋ አቅርበዋል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia

EBS TV

31 Oct, 18:24


#AddisAbaba

የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ ቤት ሰሞኑን በከተማው በሚገኙ አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ከሙስሊም ሴት ተማሪዎች አለባበስ ጋር በተያያዘ የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት በመዋቅሮቹ አማካኝነት በየደረጃው ተከታታይ ውይይቶችን ሲያደርግ መቆየቱን ገልጿል።

ትላንትና የከፍተኛ ምክር ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች እና ስራ አስፈፃሚዎች የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ፓሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር እንዲሁም የትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች በተገኙበት  በጉዳዩ ላይ ውይይት መደረጉን ተገልጿል።

በዚሁም መሰረት ችግሩ በተደጋጋሚ እየተከሰተ ያለና ዘላቂ መፍትሔ የሚያሻው ከመሆኑ አንጻር ከፍተኛ ም/ቤቱ ከፌደራል መጅሊስ እንዲሁም ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ጋር በመሆን በጉዳዩ ላይ ዘላቂ እልባት የሚያመጣ የመፍትሔ ሀሳብ እንዲያቀርብ ከስምምነት መደረሱ ተነግሯል።

ከወሩ መጀመሪያ አካባቢ ጀምሮ ከትምህርት ገበታ የተገለሉ ተማሪዎችን በተመለከተ ግን በጊዜያዊነት ከመገለላቸው በፊት ይስተናገዱ በነበረበት ሁኔታ ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱና ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ  ከስምምነት መደረሱን ምክር ቤቱ ይፋ አድርጓል።

@tikvahethiopia

EBS TV

31 Oct, 18:24


#መቐለ

መቐለ ከተማ ውስጥ በጭካኔ የተገደለች እንስት አስከሬንዋ ከ2 ቀን በኋላ መገኘቱን ፓሊስ አስታውቋል።

የጭካኔ ተግባሩ የት ፣ መቼ ፣ እንዴት ተፈፀመ ?

የጭካኔ ተግባሩ በትግራይ ፣ መቐለ ሓወልቲ ክፍለ ከተማ ዓዲሓ ተብሎ በሚጠራው ልዩ ሰፈር በሚገኝ የአንድ ሆቴል ክፍል ነው የተፈፀመው።

ሓበን የማነ የ19 ዓመት ወጣት ስትሆን በሆቴል ክፍል #በቢላዋ ተገድላ መገኘትዋና ጥቅምት 20 /2017 ዓ.ም ከሰአት በኋላ የቀብርዋ ስነ-ሰርዓት መከናወኑ ተሰምቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል የጭካኔ ተግባሩ የሚመለከት ተጨባጭ መረጃ ለማግኘት ወደ ሓወልቲ ክፍለ ከተማ ፓሊስ ፅህፈት ተጉዟል።

ፓሊስ የጭካኔ ተግባሩ የሚመለከት ዝርዝር መረጃ በማሰብባሰብ ላይ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የጭካኔ ግድያ ተግባሩ በፍቅኛሞች መካከል መፈፀሙን እና በግድያ ወንጀል የተጠረጠረ ዳዊት ዘርኡ የተባለ ግለሰብ በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውል ህዝቡ ጥቆማ በመስጠት እንዲተባበር ጠይቋል። 

በተያያዘ በያዝነው ወር የመጀመሪያ ሳምንት ውቕሮ ከተማ ላይ እሁድ ጥቅምት 5 ተድራ ሓሙስ ጥቅምት 7/2017 ዓ.ም በባሏ በጭካኔ የተገደለችው ሙሽሪት ሊድያ ጉዳይ ተጣርቶ ወደ አቃቤ ህግ መተላለፉን የወቕሮ ከተማ ፓሊስ ማስታወቁ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አክሎ ዘግቧል።

@tikvahethiopia

EBS TV

31 Oct, 16:28


#RedSea

" ዓለም ዛሬ ይስማ የቀይ ባህር አክሰስ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ኢትዮጵያ ያስፈልጋታል " - ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)

🟢 " ወይ እኛ ወይም ልጆቻችን ይህንን ያሳኩታል "🟢

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)  ጠቅላይ ሚኒስትሩ " ኢትዮጵያ የማይናወጥ ብሔራዊ ጥቅም አላት ዓለም ዛሬ ይስማ የቀይ ባህር አክሰስ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ኢትዮጵያ ያስፈልጋታል " ሲሉ በዛሬው ፓርላማ ላይ ተናግረዋል።

ይህንን ሲናገሩ የፓርላማ አባላት ዘለግ ያለ ከፍተኛ ጭብጨባ አሰምተዋል።

" በዚህ (ቀይ ባህር) ጉዳይ የምንደብቅ የሚመስለው ካለ ተሳስቷል " ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ " በጦርነት ፣ በኃይል አንፈልግም በቂ ሪሶርስ ነው በማንኛውም ህግ በማንኛውም የሀገር ልምምድ ኢትዮጵያ ይገባታል " ብለዋል።

" ብዙዎች እኮ ይላሉ 120 ሚሊዮን ህዝብ መቆለፍ ነውር ነው ይላሉ ፤ አንዳንድ የተገዙ ኢትዮጵያውያን ባይገባቸውም ወይ እኛ ወይ ልጆቻችን ያሳኩታል ፤ ይሄ ምንም ጥርጥር የለውም እውነት ስለሆነና ሎጂካል ነገር ስለሆነ " ሲሉ ተደምጠዋል።

" ይህንን አስታኮ ' ነገ ውጊያ ይነሳል ' ብለው የሚያስቡ ሰዎች አንዋጋም ከማንም ጋር የመዋጋት ፍላጎት የለንም " ሲሉ ተናግረዋል።

" ' ኢትዮጵያን ሊወሩ ይችላሉ ሀገራት ' የሚል ስጋት ያለባቸው ሰዎች አልፎ አልፎ ስለሚነሱ ኢትዮጵያን ማንም ሰው ዛሬ በኃይል መውረር አይችልም ማንም !! " ሲሉ ገልጸዋል።

" ለመመከት የሚያስችል በቂ አቅም አለን። ስንገዛ ስንሸምት የነበርናቸውን በውጊያ ክፍተት የገጠሙንን ነገሮች ማምረት ጀምረናል። እናመርታለን ፣ ሰው አለን ጀግኖች ነን ከነኩን ግን ለማንም አንመለሰም " ብለዋል።

ይህንን ሲናገሩም የፓርላማ አባላት በጭብጨባ አቋርጠዋቸው ነበር።

ኢትዮጵያ የወረራ ስጋት እንደሌለባት የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ " በአጼ ሚኒሊክ ዘመነ መንግሥት ብዙ አቅም ባልነበረበት ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን አድዋ ላይ ሄደው አሸንፈው ነጻነት ማስከበር ከቻሉ ያኔ 5 ሚሊዮን ነበሩ ዛሬ 120 ሚሊዮን ነው የጀግንነት ደሙ እንዳለ ነው ስጋት አይግባችሁ ማንም ቢመጣ አሳፍረን እንመልሳለን እኛ ግን ማንንም አንነከም " ብለዋል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia

EBS TV

23 Oct, 18:49


" አደጋው በሸገር የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ላይ ነው የደረሰው ፤ እስካሁን የአንድ ሰው ህይወት አልፏል " - ፖሊስ

በአዲስ አበባ በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 7 ' አዲሱ ገበያ ' አካባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ እስካሁ የአንድ ሰው ህይወት ማለፉን የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።

አደጋው በሸገር የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ላይ መድረሱን ፖሊስ ጠቁሟል።

በአደጋው የተጎዱ ሰዎችን ህይወት ለመታደግ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ እንደሆነ ገልጿል።

" እስካሁን በአደጋው የ1 ሰው ህይወት አልፏል " ያለው ፖሊስ " የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ ነው " ብሏል።

ፖሊስ ከአደጋው ጋር የተያያዙ ዝርዝር መረጃዎችን በቀጣይ ለህዝብ እንደሚገልጽም ለብሔራዊ ቴሌቪዥን በሰጠው ቃል አሳውቋል።

@tikvahethiopia

EBS TV

23 Oct, 18:35


#SafaricomEthiopia

🌍በሳፋሪኮም ሮሚንግ ጥቅሎች የውጭ ሃገር ቆይታችንን ያለስጋት እናሳልፍ! በአፍሪካ ፣ በአውሮፓ ፣ በእስያ እና በሰሜን አሜሪካ ወዳሉ የተመረጡ ሃገራት ስንጓዝ ሳፋሪኮም አብሮን ነው! ከዳር እስከ ዳር አለምን ከአስተማማኙ ኔትወርክ ጋር እንቃኝ!

የቴሌግራም ቦታችንን https://t.me/official_safaricomet_bot በመጠቀም የአየር ሰዓት ወይንም ልዩ ልዩ ጥቅሎችን እንግዛ!
ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://t.me/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

#1Wedefit #Furtheraheadtogether

EBS TV

23 Oct, 18:35


#ኢትዮጵያ

መደበኛ ባልሆነ ማቆያ ቦታ፣ ያሉበት ሳይገለጽ እንዲቆዩ የተደረጉ እና አስገድዶ መሰወር ሁኔታን ሊያቋቁም በሚችል ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ተጎጂዎች እና የተጎጂዎች ቤተሰቦችን በተመለከተ ተጠያቂነት ሊረጋገጥ እና ፍትሕ ሊሰጣቸው  እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን አሳስቧል።

ኮሚሽኑ ከዚህ ጋር በተያያዘ አንድ ሪፖርት ልኮልናል።

ከሪፖርቱ ውስጥ የተገኘ ማሳያ ፦

(የአስገድዶ መሰወር ሁኔታን ሊያቋቁም በሚችል ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ተጎጂዎች)

🔴 አቶ መንበረ ቸኮል ምስጋናው፣ የግንባታ ባለሙያ፣ የ7 እና የ4 ዓመት ዕድሜ ያላቸው 2 ሕፃናት ልጆች አባት ሲሆኑ፣ ግንቦት 9 ቀን 2016 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ “ሰፈራ” ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ በጸጥታ አካላት ሰሌዳ በሌለው ተሽከርካሪ የተወሰዱ ሲሆን፣ ያሉበት ቦታ እና ሁኔታ የማይታወቅ በመሆኑ ቤተሰቦቻቸው ለከፍተኛ ጭንቀትና ሥነ ልቦናዊ ጉዳት ተጋልጠው ይገኛሉ።

🔴 አቶ ዘላለም ግሩም ፍላቴ፣ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባልና አሽከርካሪ ሲሆኑ፣ ኅዳር 19 ቀን 2016 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ፣ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ፣ ልዩ ስሙ “ዲቦራ ትምህርት ቤት” ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ በጸጥታ አካላት ሰሌዳ ቁጥሩ ባልታወቀ ተሽከርካሪ ከተወሰዱ ጀምሮ፣ ያሉበት ቦታ እና ሁኔታ የማይታወቅ በመሆኑ ቤተሰቦቻቸው በከፍተኛ ጭንቀትና ሥነ ልቦናዊ ጉዳት ውስጥ ይገኛሉ።


(በተለያየ መደበኛ ባልሆኑ ቦታዎች ወይም ያሉበት ሳይታወቅ በተራዘመ እስር ሁኔታ ቆይተው የተለቀቁ)

አቶ አማረ ግዳፍ፣ ባለ3 እግር ተሽከርካሪ በተለምዶ “ባጃጅ” በማሽከርከር ሥራ ላይ የተሰማሩ ሲሆኑ መጋቢት 11 ቀን 2016 ዓ.ም. ከረፋዱ 5፡00 ሰዓት አካባቢ በአዲስ አበባ ከተማ፣ የካ ክፍለ ከተማ፣ በተለምዶ “ወሰን መስቀለኛ” ተብሎ በሚጠራው አካባቢ 6 የሲቪል ልብስ እና 1 የመከላከያ ሰራዊት የደንብ ልብስ በለበሱ ሰዎች እና ሰሌዳ በሌለው ተሽከርካሪ ተወስደው፣ ላለፉት 6 ወራት ያሉበት ቦታ ሳይታወቅ ቆይተው በጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም. ተለቀዋል።

አቶ ዓለማየሁ ከፈለ ተሰማ የተባሉ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ ነሐሴ 20 ቀን 2015 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ፣ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ፣ ወረዳ 1 በተለምዶ “ፍላሚንጎ” በሚባለው አካባቢ ሲቪል ልብስ ለብሰው መታወቂያ በያዙ 6 የፌዴራል ፖሊስ አባላት ተወስደው፣ በሚያዝያ ወር 2016 ዓ.ም. ተለቀዋል።

አቶ መቼምጌታ አንዱዓለም፣ ባለትዳርና የ2 ሕፃናት ልጆች አባት፣ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ ሲሆኑ ነሐሴ 27 ቀን 2015 ዓ.ም. ከቀኑ 11፡00 ሰዓት አካባቢ “ብስራተ ገብርኤል” ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የታክሲ አገልግሎት ከሚሰጡበት አካባቢ ከነተሽከርካሪያቸው የሲቪል ልብስ በለበሱ የጸጥታ አካላት ተወስደው፣ በተለምዶ “ራሺያ ካምፕ” ተብሎ በሚጠራው የመከላከያ ሰራዊት አባላት መኖሪያ ለ7 ወራት ከቆዩ በኋላ መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ.ም ተለቀዋል።

ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ አንድ የቤተሰብ አስተዳዳሪ እና የልጆች አባት የሆኑ ተጎጂ፣ ነሐሴ 15 ቀን 2015 ዓ.ም. ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ገደማ ከግል የሥራ ቦታቸው ሲቪል እና የደንብ ልብስ ለብሰው ቀይ ቦኔት ባደረጉ የጸጥታ አባላት ተይዘው፣ ሰሌዳ በሌለው ተሽከርካሪ ጦር ኃይሎች አካባቢ በተለምዶ “ራሺያ ካምፕ” ተብሎ በሚጠራው የመከላከያ ሰራዊት አባላት መኖሪያ እንደቆዩ አስረድተዋል። ከዚያ ቀን ጀምሮ ቤተሰቦቻቸው በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ በርካታ የአዲስ አበባ ከተማ እና የፌዴራል ፖሊስ ጣቢያዎች ቢያፈላልጓቸውም በምን ምክንያት እንደተያዙ ለማወቅ ሳይቻል፣ ለ2 ወራት ከቆዩ በኋላ ጥቅምት 18 ቀን 2016 ዓ.ም. ተለቀዋል።

ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ሌላው ተጎጂ ነሐሴ 19 ቀን 2015 ዓ.ም. ከሚሠሩበት አካባቢ ሲቪል እና የደንብ ልብስ ለብሰው ቀይ ቦኔት ባደረጉ የጸጥታ አካላት በተለምዶ “ፓትሮል” በሚባል ተሽከርካሪ በግዳጅ ተወስደው ባልታወቀ ቦታ ከቆዩ በኋላ፣ መስከረም 28 ቀን 2016 ዓ.ም. ተለቀዋል።

ሌላ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ተጎጂ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ እና ባለትዳር ሲሆኑ፣ ታኅሣሥ 24 ቀን 2016 ዓ.ም.  እኩለ ቀን ላይ በተለምዶ “ስታዲየም” በሚባለው አካባቢ ከሚሠሩበት ቦታ ሲቪል በለበሱና ሽጉጥ በታጠቁ፣ እንዲሁም የመከላከያ ሰራዊት የደንብ ልብስ በለበሱና ቀይ ቦኔት ባደረጉ የጸጥታ አካላት ሰሌዳ ቁጥር በሌላቸው ዳለቻ ቀለም እንደሆኑ በተገለጸና በተለምዶ “ሎንግቤዝ” እና “ፓትሮል” ተብለው በሚጠሩ መኪናዎች ተጭነው ተወስደው፣ ከ6 ወራት እስር በኋላ ሰኔ 22 ቀን 2016 ዓ.ም. ተለቀዋል።  

በተመሳሳይ ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ ተጎጂ ከግል የሥራ ቦታቸው የተወሰኑት ሲቪል እና ሌሎች የደንብ ልብስ በለበሱና በታጠቁ የጸጥታ አካላት መጋቢት 30 ቀን 2016 ዓ.ም. ከተያዙ በኋላ፣ ዐይናቸውን በጨርቅ ተሸፍነው ተወስደው ያሉበት ሳይታወቅ እስከ ጳጉሜን 5 ቀን 2016 ዓ.ም. ከቆዩ በኋላ፣ በድጋሚ ዐይናቸውን በጨርቅ ተሸፍነው አዲስ አበባ ከተማ፣ “ኃይሌ ጋርመንት” ተብሎ በሚጠራው አካባቢ እንዲወርዱ መደረጋቸውን አስረድተዋል።


(ሙሉ ሪፖርቱ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia

EBS TV

23 Oct, 18:35


“ ጡረታ፣ ህክምና ይከበርልን። እኛ ወድቀናል፤ ከስረናል፤ ከሽፈናል። ቢያንስ እንደ ዜጋ እንታከም ” - የሶማሌ ክልል ቀድሞ ሰራዊት አባላይ

ሰሞኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሶማሌ ክልል ከሚገኙ ባለድርሻ አካላት ጋር የአጀንዳ ማሰባሰብ የውይይት መድረክ አድርጎ ነበር።

በዚህ መድረክ ከተሳተፉት ባለድርሻ አካላት መካከል አንዱ የሶማሌ ክልል የቀድሞ ሰራዊት አባላት ነው።

ኮሚሽኑ ስለቀድሞ ሰራዊት ጉዳይ ምን ማተኮር እንዳለበት፣ ስለታጠቁ ኃይሎችና የመንግስት አካሄድ የተመለከቱ ጥያቄዎች ያቀረብንላቸው የክልሉ የቀድሞ ሰራዊት አባላት ሊቀመንበር ሻለቃ ሴባ ቶንጃ ምላሽ ሰጥተዋል።

ምን አሉ ?

ሥርዓት ሲወድቅ የሚወድቅ ሥርዓት ሲነሳ የሚነሳ ሰራዊት ካለ ሀገርና ሕዝብ ዋስትና የለውም። ማንም እንደገባ ከዚያም ከዚህም ያዋክበዋል፤ ህዝብ ጉዳት ያደርስበታል።

ቀጣዩ ትውልድ እንዴት ይኑር? ለምን በባንዲራ እንጨቃጨቃለን? ከጥንት ጀምሮ ቅድመ አያቶቻችን ያወረሱን ነው እዚህ ላይ ያለው ስህተት ምንድን ነው? ለምን በአድዋ ድል እንጨቃጨለን? ስህተት ካለ ተመካክረን እናስተካክል እንጂ ለምን እንጋደላለን ?... በሚል ለሀገር የሚጠቅም አጀንዳ እየቀረጽን ነው።

ጡረታ ያልተከበረልን ነን፤ ጡረታ ይከበርልን፤ እንደዜጋ ለሀገር አገልግለናል፤ ሜዳ ላይ መውደቅ የለብንም። አሁንም እየተጠራን እየተሳተፍን ነው።

እኛ ለሀገር አሁንም ዝግጁ ነን፤ አላኮረፍንም፡፡ ሁሉም በእኩልነት ይታይ፡፡ የተወሰኑትን ብቻ መዞ ይዞ የተወሰነው ጭራሽ እስከነመፈጠሩም ይረሳል፡፡

ጡረታ ይከበርልን፤ ህክምና ይከበርልን፤ እኛ ሁሉን ትተን ለሀገር ብለን ስለንዘምት የነበረ ተማሪ አሁን ዶክተር ፕሮፌሰር ነው። እኛ ወድቀናል፤ ከስረናል፤ ከሽፈናል። ቢያንስ እንደ ዜጋ እንታከም። እኛ ስንዋጋ ተምረው ዶክተር የሆኑ ያክሙን።

መንግስት የሕክምና፣ የጡረታ ዋስትና ይስጠን። ከራሳችን ገንዘብ ተቆርጦ ገቢ ሲሆን የነበረውን ተከልክለናል። ይህ ይስተካከል።

እንደዜጋ በክብር እንኑር። በመስሪያ ቤቶች ተቀጥረን ጥበቃ ለመስራት እንኳ የታገደበት ሁኔታ ነበር፤ ‘እንዳይቀጠሩ’ የሚል። ዜጋ ነን፣ ይሄ ያሳምጻል ነገር ግን አላመጽም በሀገራችን አናምጽም፤ ህዝብ ይበጠበጣል ብለን።

ችግራችንን አምቀን ይዘን አሁንም ለህዝባችን ደኀንነት እየታገልን ነው።

ሀገሪቱ ውስጥ ያሉ ግጭቶች በአያያዝ ስህተት የተፈጠሩ እንደሆኑ እናምናለን። በአጠቃላይ የእርስ በእርስ ግጭት የወንድማማቾች እልቂት አንደግፍም። 

እገሌ እገሌ የሚል ስያሜ መንግስት ይስጠው እኛ የወንደማማቾች ግጭት አንደግፍም፡፡ ግን መጥተው ህዝቡን እንዲጨፈጭፉና ተቋም እንዲያወድሙም አንፈልግም፡፡ 

ይልቁንም ወደ መድረክ እንዲመጡ እንፈልጋለን፡፡ ለዚያ ደግሞ መንግስት በሆደ ሰፊነት ቀረብ ብሎ መሳብ ያስፈልጋል። ግጭት እስከወዲያኛው ይቁም።

አሁን የተፈጠረው ግጭት በአያያዝ ስህተትነው የተፈጠረው አይፈጠርም ነበር፡፡ ለምሳሌ ጊዜውን መጠበቅ ሲገባ ያልበሰለ አጀንዳ ወደ ህዝብ ይለቀቃል፡፡ 

በሚስጥር ተይዞ ቆይቶ በኋላ ሁኔታው ሲፈቅድ መልቀቅ ነው እንጂ ጊዜውን ያልጠበቀ አጀንዳ ከለተለቀቀ ግጭት ይፈጥራል፡፡ ጊዜውን ያልጠበቀ አጀንዳ መዓት ነገር ነው፡፡ 

ለምሳሌ ፦ ለመጥቀስ የፋኖም ራሱ ጊዜውን ያልጠበቀ አጀንዳ ሆኖ በግድ ስለተኬደበት እንጂ አይዋጉም ነበር፡፡ ትላንትና ራቁቱን የተባረረውን መካላከያ ሰራዊትን ያዳኑ እነርሱ አይደሉምን ?

አሁን የተፈጠረውን ብቻ ኮንነን መንግስት ይውደደን ብዬ አልናገርም፡፡ ሚዛናዊ ህሊና አለኝ፡፡ አሁን የሚሰሩት ሥራ ጥሩ ነው እያልኩ ሳይሆን ወደ መጥፎ ተገፋፍተው በእልህ የተገፉት ነገር ጥሩ ስላልሆነ ነው፡፡ 

በእርግጥ አሁን መንግስት ጥረት እያደረገ ነው በዚሁ ይቀጥል፡፡ ወደ ሰላም ቢያመጣቸው ጥሩ ነው፡፡ 

መጪው ትውልድ በሰላም እንዲኖር ከእንግዲህ በአገራችን የወንድማማቾች ጦርነት እንድናይ፣ እኛ ያየነው ችግር በእነርሱ ላይ እንዲደርስ አንፈልግም፡፡

ሁሉም የበኩል ድርሻ ተቀብሎ መንግስትም ያለውን ስህተት አርሞ ብለድርሻ አካላት በሙሉ ለሰላም አስተቃጽኦ አድርገው ከተንቀሳቀሱ ሰላም ይመጣል፡፡ ይህ ካልሆነ ከዚህ በባሰ እንጠፋፋለን፡፡ አሁን በዚህ ውይይት መፈታት አለበት ከዚህ ካለፈ አካሄዱ አያምርም፡፡

ከተሞክሯችን ተነስተን ነው መልዕከት የምናስተላልፈው፡፡ እሳት የጎረሰ መሳሪያ ይዘን ውሃ ጠምቶን ለምነን እየጠጣን ነበር፡፡

ከደረሰብን ጉዳት አንጸር እኛ ለመሸፈት ነበርን ቅርብ፡፡ አሁንም ቢሆን አኩርፈን ለመሄድ እኛ ነን ቅርብ፡፡ ጸጉራችንን ተላጭተን እድሜያችንን የጨረስነው በርሃ ውስጥ ነው፡፡

በውጊያ አውድ ያሉ አካላት እርግጥ ምክንያት ኖሯቸው ትግል ቢጀምሩም የትኛውም ግጭት ሂዶ ሂዶ በስምምነት መጠቃለሉ አይቀርም፡፡ ዞሮ ዞሮ ሰላም ይመጣል፤ በእድሜያችን እያየን ያለነው ይሄው ስለሆነ፡፡ ከብዙ መተላለቅ ይልቅ ለስምምነቱ፣ ለእርቁ፣ ለውይይቱ እድል ቢሰጡ ጥሩ ነው"
ብለዋል።

ምን ያክል ቀድሞ ሰራዊት አባላት አሉ ለሚለው የቲክቫህ ጥያቄ በምላሻቸው “ ባለንበት አካባቢ በርካታ የቀድሞ ሰራዊት አባላት አሉ፡፡ ወደ 5 ሺሕ የሚሆኑ አሉ ” ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

EBS TV

22 Oct, 18:16


ትላንትና መርካቶ ሸማ ተራ እሳት አደጋ ሲከሰት እጅግ በሚያሳፍር ሁኔታ አንዳንድ ህሊና የሌላቸው ሰዎች ዝርፊያ ላይ ተሰማርተው ነበር።

በዛ ጭንቅ ሰዓት፣ ሁሉም እሳቱን ለማጥፋ ሲረባረብ እነሱ ግን የራሳቸው ሃቅ ያልሆነን የሰው ንብረት ሲዘርፉ ነበር።

ከአሳዛኙ የእሳት አደጋ በተጨማሪ ይህ የዝርፊያ ተግባር የአካባቢው ነሪዎችን አሳዝኗል።

ዛሬ የአዲስ አበባ ፖሊስ ይፋ ባደረገው መረጃ ፥ አደጋውን እንደ ምቹ ሁኔታ በመጠቀም የስርቆት ወንጀል የፈፀሙ 33 ተጠርጣሪዎችን ይዞ ምርመራ እያጣራ ይገኛል።

በሌላ በኩል ከአደጋው ጋር በተያያዘ በ7 ሰዎች ቀላል በ2 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት  መድረሱን አሳውቋል።

የአደጋውን መንስኤ የለማጣራት ከፌዴራል ፖሊስ የፎረንሲክ ምርመራ ቡድን ጋር በመቀናጀት ምርመራ መጀመሩን አመልክቷል።

Photo Credit - Yeraguel Baria

@tikvahethiopia

EBS TV

22 Oct, 18:16


አንድ እንጀራ 30 ብር በገባበት ወቅት 450 ብር ለምን ይጠቅማል ? ለቤት ኪራይ፣ ወይስ ለቀለብ ነው የሚሆነው? ” - የኢትዮጵያ መምህራን ማኀበር።

የመምህራን የስልጠና ክፍያ እጅግ አነስተኛ መሆን ከኑሮ ውደነት ጋር ተያይዞ ፣ ዩኒቨርሲቲዎች ሲሰጡት የነበረውን የሙያ ስልጠና አለመስጠታቸው የትምህርት ጥራት ቀውስ ውስጥ እንዲገባ እያደረገ በመሆኑ ትኩረት እንዲሰጠው የኢትዮጵያ መምህራን ማኀበር በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ጠየቀ።

ከማኀበሩ የተሰነዘሩ ቅሬታዎች ምንድን ናቸው ?

“ ከትምህርት ሥርዓት አንጻር በአሁኑ ሰዓት የትምህርት ጥራት ችግር ብቻ ልንለው አንችልም። የትምህርት ቀውስ ነው። ቀውስ ውስጥ ገብተናል። ወደ መምህራን ችግሩን የመግፋት ነገር ይታያል። ይሄ ትክክል አይደለም። 

ሲጀመር የመምህርት ስልጠና ዋጋ አልተሰጠውም። ለምላሌ ፦ የአንደኛ ደረጃ ት/ቤት እጩ መምህራን ከተወሰኑ ኮሌጆች ውጪ 450 ብር ተሰጥቷቸው ውጪ ሆነው እንዲማሩ የሚደረጉት።

አንድ እንጀራ 30 ብር በገባበት ወቅት 450 ብር ለምን ይጠቅማል ? ለቤት ኪራይ ወይስ ለቀለብ ነው የሚሆነው ? ችግሩ እዚያ ጋ ነው የሚጀምረው። 

እጩ መምህራን ወደ ኮሌጅ ውስጥ ሲገቡ 450 ብር ይከፈላቸዋል። ፍላጎታቸውን ስለማይሟላ ትምህርት ላይ ትኩረት ሳያደርጉ ፍላጎታቸውን ለሟሟላት ይንቀሳቀሳሉ። ይሄ የመምህርነትን ሙያ ጥራቱን ቀንሶታል። ስለዚህ ጉዳዩ ሊታረብበት ይገባል።

የኢትዮጵያ መምህራን ማኀበር ጥናት አጥንቷል። በዚያ መልኩ ተግባራዊ ሊደረግ ይገባል


በሌላ በኩል ፥ ወደ መምህርነት ሙያ ሴንተር ኦፍ ኤክሰለንሲ ተብለው እነዚህ የመቐለ ፣ ባሕር ዳር፣ የአዲስ አበባ፣ ጅማና ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲዎች መምህራንን የሚያሰለጥኑ ነበሩ ለ2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች። 

ነገር ግን ላለፉት ሦስትና አራት ዓመታት ምንም አይነት ተማሪ ወደ መምህርነት ሙያ እንዲገባ እያሰለጠኑ አይደለም። 

ይሄ ደግሞ በቀጣይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶቻችንን በድጎማ መምህር ልናስይዝ አይደለም ወይ ! ይሄ ወዴት እየሄደ ነው ?


በተያያዘ፣ የመፅሐፍት ስርጭት ችግሮች አሉ። ችግር መኖር ብቻ ሳንሆን አንደኛ ደረጃ ት/ቤቶች ላይ በአንድ ላይ ኮምባይን የሆኑ ትምህርት ቤቶች አሉ። 

ለምላሌ ፦ ኬሚስትሪ፣ ፊዚክስና ባይሎጂ አንድ ላይ ናቸው። በአንድ መምህር ነው የሚሰጡት። ይህም መምህራን ኬሚስትሪውን ፓርት ያስተምሩና ፊዚክስና ባይሎጂው የተመረቁበት ስለማይሆን ለማስተማር እየተቸገሩ ነው። 

በሌሎች የትምህርት አይነቶችም ተመሳሳይ ችግር አለ። መምህር ያልተዘጋጀባቸው ሥርዓተ ትምህርቶች አሉ። የትምህርት ጥራቱን እየጎዳው ያለው አንዱ ችግር ይሄ ነው። አጠቃላይ ትምህርቱ ሴክተሩ በቂ ትኩረት አላገኘም። በቂ ፋይናንስ እየተመደበለት አይደለምና ሊመደብለት ይገባል።

መምህራንም የተለያዬ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ሲፈጠሩ መብታቸውን ለማስከበር ወደ ሕግ ተቋማት ስለሚሄዱ የትምህርት ጊዜ ይዘጋል። ይሄ ደግሞ የትምህርት ጥራት ላይ ችግር አምጥቷል። ”


እነዚህ ቅሬታዎች የትምህርት ሚኒስቴር በተገኘበት መድረክ እንደቀረቡ ማኀበርሩ ገልጾልናል።

የሚመለከታቸው አካላት ለጉዳዩ በቂ ትኩረት እንዲሰጡ ያሳሰበው ማኀበሩ፣ ትምህርት ሚኒስቴር በተነሱት ቅሬታዎች ዙሪያ መፍትሄ ለማምጣት አሳይመንት ይዞ እንደሄደ አመላክቷል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

EBS TV

22 Oct, 14:59


#ኦርቶዶክስተዋሕዶ

" ...አለመግባባት በዝቷል፤ ማኵረፍና መቀያየም ሰፍቷል ፤ ነገሩ ሁሉ ግራ የሚያጋባና የተመሰቃቀለ ሆኖ ይታያል፡፡ ችግሩ ከሕዝብ አልፎ የአምልኮ ስፍራዎችንና የአምልኮው ፈጻሚዎችን ዒላማ ያደረገ እግዚአብሔርን መዳፈር እየተለመደ መጥቷል " - ቅዱስነታቸው

የጥቅምት 2017 ዓ/ም የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ተጀመረ።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተወሕዶ ቤተክርስቲያን ሁለንተናዊ አገልግሎትና የስራ አፈጻጸም ላይ ለመምከርና ለመወሰን ኃላፊነት ያለው ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ መደበኛና ዓመታዊ ጉባኤውን ጀምሯል።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የጉባኤውን መጀመረ አስመልክተው መልዕክት አስተላልፈዋል።

ከመልዕክታቸው ፦

" የሰው ልጆች በዚህ ዓለም ሲኖሩ የተሟላ ሰላምና ጣዕመ ሕይወት ሊኖራቸው የሚችለው በመንፈሳዊ ኑሮአቸው የተሻለ ነገር ስላገኙ ብቻ አይደለም፡፡

ሰዎች ከሥጋዊ ክዋኔም ጭምር የተፈጠሩ እንጂ እንደመላእክት ሥጋ የሌላቸው መንፈስ ስላይደሉ ለኑሮአቸውና ለሥጋዊ ክዋኔአቸው የሚሆን ነገር ያስፈልጋቸዋል፡፡

በዚህም ዓለማዊው አስተዳደር የተመቻቸ መደላድል ሊፈጥርላቸው ግድ ነው፤ ዓለማዊው አስተዳደርም የመለኮትን ተልእኮ ለመፈጸም የተሾመ ሹመኛ እንደመሆኑ የእግዚአብሔርን ሕዝብ በትክክል መምራት ይጠበቅበታል፡፡

ምንም ቢሆን የተቀበለው ኃላፊነት የእግዚአብሔር ነውና በሚሰራው ሁሉ በሿሚው አምላክ ከመጠየቅ አያመልጥም፡፡

እኛም በዚህ ዓለም የእግዚአብሔር ወኪሎች ስለሆንን ቢሰሙንም ባይሰሙንም ዓለማውያን ሹማምንትን የማስተማርና የመምከር ኃላፊነት አለብን፡፡

ይህ የሁለታችን ኃላፊነት እንደ እግዚብሔር ፈቃድ ስንፈጽም የሕዝብ ሰላምና በረከት፣ ፍቅርና አንድነት፣ ዕድገትና ልማት በአስተማማኝ ሁኔታ ይረጋገጣል፡፡

ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ በሀገራችንም ሆነ በአካባቢያችን እየሆነ ያለው ይህ አይደለም፤ አለመግባባት በዝቶአል፣ ማኵረፍና መቀያየም ሰፍቶአል፤ ነገሩ ሁሉ ግራ የሚያጋባና የተመሰቃቀለ ሆኖ ይታያል፡፡

ችግሩ ከሕዝብ አልፎ የአምልኮ ስፍራዎችንና የአምልኮው ፈጻሚዎችን ዒላማ ያደረገ እግዚአብሔርን መዳፈር እየተለመደ መጥቶአል፤ ይህ ለአንድ ሀገር ወይም ሕዝብ የውድቀት ምክንያት ከሚሆን በቀር ከቶውኑም የዕድገት ምልክት ሊሆን አይችልም፡፡

ከሁሉም በላይ የሚያሳዝነው ደግሞ ይህ ክፉ ድርጊት እየተፈጸመ ያለው በእኛው ልጆች በኢትዮጵያውያን መሆኑ ነው፤ ስለሆነም በከተማም፣ በጫካም፣ በገጠርም በየትኛውም ስፍራ የምትገኙ ልጆቻችን ምንም ይሁን ምን ሀገርንና ሕዝብን ከመጉዳት ተቆጠቡ፡፡

በተለይም ከቤተ ክርስቲያንና ከሀገር እንደዚሁም ሕዝቡን ከሚያገለግሉ ካህናትና ሲቪል ሰራተኞች እባካችሁ እጃችሁን አንሡ፤ ቤተ ክርስቲያን እኮ የእናንተና የሕዝቡ ሁሉ እናት ናት፤ በእናታችሁ ላይ መጨከንን እንዴት ተለማመዳችሁት ? አሁንም ንስሐ ግቡ ያለፈው ይበቃል፡፡

ልብ በሉ ከእግዚአብሔር ጋር መጣላት አይበጅም፤ ሰውን መጉዳትና እግዚአብሔርን መዳፈር አቁሙ፤ የእግዚአብሔር ገንዘብ የሆነውን ሥርዓተ አምልኮም ያለቦታው አታውሉ፤ ጥያቄአችሁን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ዕድል ስጡ፡፡

በእግዚአብሔር ስም ለመላው ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንና ልጆቻችን የምናስተላፈው ወቅታዊ መልእክታችን ይህ ነው፡፡ "

(የቅዱስነታቸው ሙሉ መልዕክት ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia

EBS TV

19 Oct, 18:42


" እኛ እኮ ትርፍ ነገር አልጠየቅንም ፤ የኑሮ ውድነቱ የሚታወቅ ነው በደሞዝ ብቻ መኖር አልቻልንም ፤ ለልጆቻችን የምንቋጥረው ምግብ ከአቅም በላይ ሆኖብናል።

መሰረታዊ ፍላጎታችንን እናሟላ የሰራንበተን ክፈሉን ነው እያልን ያለነው።

በህክምና ሞያ ብቻ ከ10 ዓመት በላይ ተምረናል ፤ እድሜያችን ወደ ጎልማሳነት ተጠግቷል ቤተሰብ ማስተዳደር ፣ ለልጆቻችን ወተት እና ዳይፕር መግዣ እስከ ማጣት ድረስ ነው ያቃተን። "

➡️ የ4 ወር ዲዩቲ (የትርፍ ሰዓት ስራ ክፍያ)፣
➡️ የ14 ወር የኦቨር ሎድ ክፍያ (Over load)፣
➡️ የ2016 የአንዋላይዜሽን (Annualization) ክፍያ እስካሁን አልተከፈለንም ያሉ በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ውስጥ የሚያስተምሩ ሐኪሞች ድምጽ !

@tikvahethiopia

EBS TV

19 Oct, 17:40


" በግቢ ውስጥ ብዙ የአእምሮ ህሙማን ፤ አረጋውያን አሉ በእነሱ ላይ ምንም አይነት ጉዳት አልደረሰም " - አቶ ንጋቱ ማሞ

ዛሬ ቀን ላይ አዲስ አበባ ለሚኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 3 መቆዶኒያ የአእምሮ ህሙማንና የአረጋዊያን መርጃ ማህበር እያስገነባ ባለዉ አዲስ ህንጻ ስር ባለ መጋዘን ላይ የእሳት አደጋ ተከስቶ ነበር።

የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ " በደረሰን ጥሪ መሰረት የአደጋ ጊዜ ሰራተኞቻችን ከሁለት ቅርንጫፍ ወደ ቦታዉ ፈጥነዉ በመድረስ እሳቱ ሳይስፋፋ በፍጥነት ተቆጣጥረውታል " ብለዋል።

በእሳት አደጋዉ በመጋዘን ዉስጥ የነበሩ ልዩ ቁሳቁሶች ላይ መጠነኛ ጉዳት ከመድረሱ በስተቀር በሰዉ ላይ ምንም ጉዳት እንዳልደረሰ ተናግረዋል።

አቶ ንጋቱ ማሞ ፤ " ግቢ ውስጥ ብዙ የአእምሮ ህሙማን፣ አረጋውያን አሉበት በእነሱ ላይ ምንም አይነት ጉዳት አልደረሰም። አካባቢው ላይ ካሉ ፀጥታ ኃይሎች፣ ከግቢው ማህበረሰብ ጋር በመሆን እሳቱን በቀላሉ መቆጣጠር ተችሏል " ሲሉ አስረድተዋል።

መጋዘን ውስጥ የነበሩ ልዩ ልዩ ቁሳቁሶች ላይ ግን መጠነኛ ጉዳት እንደደረሰ ጠቁመዋል።

የአደጋውን ምክንያት ፖሊስ እያጣራው ነው።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

EBS TV

19 Oct, 17:40


#EarthQuake

" በኢትዮጵያ በስምጥ ሸለቆ ውስጥ ለ22 ቀናት ወደ መሬት ለመውጣት ተፈጥሯዊ እንቅስቃሴ ሲያደርግ የነበረው ቅልጥ አለት የመወጠር ሁኔታ አሁን ረገብ ብሏል " ሲሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂዮ ፊዚክስ ስፔስ ሳይንስና አስትሮኖሚ ተቋም ዋና ዳይሬክተር ኤልያስ ሊዊ ለብሔራዊ ቴሌቪዥን/ኢቲቪ ተናግረዋል።

" አሁን ባለን መረጃ ቅልጥ አለቱ ወደታች እየወረደ ነው ፤ በዚህም ምክንያት ባለፉት 2 ቀናት የተመዘገበው የመሬት መንቀጥቀጥ ዝቅተኛ ነው " ብለዋል።

" ቀደም ሲል የነበረው ስጋት ባለፉት ቀናት ቀንሷል " ያሉት ኤልያስ ሌዊ (ዶ/ር) ፥ " ነገር ግን በስምጥ ሸለቆ ውስጥ የምንገኝ እንደመሆናችን ስጋቱ ተመልሶ ሊመጣ ይችላል " ሲሉ ተናግረዋል።

" ስምጥ ሸለቆ እና አካባቢው በተፈጥሮ ለመሬት መንቀጥቀጥ ተጋላጭ መሆኑ የማይቀየር ተፈጥሯዊ እውነታ ስለሆነ እንደ ሀገር፣ እንደ ህዝብ የራሳችንን ጥንቃቄና ዝግጀት ማድረግ ያስፈልጋል " ሲሉ ለቴሌቪዥን ጣቢያው በሰጡት ቃል አስገብዝበዋል።

ባለፉት ቀናት እና ሳምንታት በአፋር ፣ ፈንታሌ አካባቢ ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ እየተከሰተ እንደነበር ይታወቃል። የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ እስከ አዲስ አበባ እና ሌሎችም ከተሞች ዘልቆ የተሰማ ነው።

@tikvahethiopia

EBS TV

19 Oct, 17:40


" የጥቅምት ወር ደመወዝ ክፍያ በአዲሱ የተሻሻለው ስኬል መሆን ይጀምራል " - አቶ አህመድ ሽዴ

የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ፤ የጥቅምት ወር ደመወዝ ክፍያ በአዲሱ የተሻሻለው ስኬል መሆን እንደሚጀምር አሳውቀዋል።

" ከጥቅምት ወር ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ ደመወዝ በካቢኔ ተወስኗል። ባለፉት ሳምንታት በገንዘብ ሚኒስቴር በኩል ቅድመ ዝግጅቱ አልቋል ፤ በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽንም በኩል ቅድመ ዝግጅት አልቋል ፤ የአፈጻጸም መመሪያ ተዘጋጅቷል " ብለዋል።

የጥቅምት ወር ደመወዝ ክፍያም በአዲሱ ስኬል ይሆናል ሲሉ ገልጸዋል።

" ዝቅተኛ ተከፋይ ለሆነው የመንግሥት ሰራተኞች ፣ ለጸጥታ ተቋም አባላት ፤ በየደረጃው ባሉ የመንግሥት ተቋማት በክልልም በፌዴራልም ተግባራዊ ማድረግ ይጀምራል " ብለዋል።

" ይሄ በመላው ሀገሪቱ የሚፈጸም ነው። ክልሎችም ለሰራተኞቻቸው / የደመወዝ ተከፋዮቻቸው የሚመጣውን ደመወዝ ከጥቅምት ወር ጀምሮ የክልል ድርሻ በፌዴራል መንግሥት የሚሸፈን ሆኖ በገንዘብ ሚኒስቴር በኩል ለክልሎች ይላካል " ሲሉ ገልጸዋል።

@tikvahethiopia

EBS TV

19 Oct, 17:40


#እድታውቁት #አዲስአበባ

አጠቃላይ በ571 የአዲስ አበባ ከተማ አካባቢዎች " የተለያዩ ሥራዎች (ጥገናና የመልሶ ግንባታ ስራ) ለማከናወን ሲባል የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እንደሚቋረጥ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አሳውቋል።

በተለዩት አካባቢዎች ላይ የኤሌክትሪክ አገልግሎት የሚቋረጠው እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ሲሆን የሚቋረጥበትን ሰዓት እንዲሁም ቀናት በዝርዝር ይፋ አድርጓል።

@tikvahethiopia

EBS TV

19 Oct, 16:17


ተፈጸመ !

የሊቀ ትጉኃን ባሕታዊ አባ መፍቀሬ ሰብእ ኪዳነወልድ የቀብር ስነ-ስርዓት በሐይቅ ቅዱስ እስጢፋኖስ እና አቡነ ኢየሱስ ሞዓ አንድነት ገዳም ተፈጽሟል።

የቀብር ስነ-ስርዓታቸው የደሴና አካባቢው የተለያዩ እምነት ተከታዮች በተገኙበት ነው የተፈጸመው።

የፎቶ ባለቤት ፦ የደቡብ ወሎ ኮሚኒኬሽን

@tikvahethiopia

EBS TV

19 Oct, 14:34


“ የሞቷ ምክንያት ምን እንደሆነ ፓሊስ እያጣራ ነው ” - ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ

የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጂ የቱሪዝም ትምህርት ክፍል ሁለተኛ ዓመት ተማሪ የነበረችው ሩት ማርሻ ከዚህ ዓለም በሞት እንደተለየች ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ከቀናት በፊት አሳውቋል።

ዩኒቨርሲቲው በማኀበራዊ ትስስር ገጹ ተማሪዋን፣ “ በድንገት ከዚህ ዓለም ድካም አርፋለች ” ከማለት ውጪ ስለአሟሟቷ የጠቀሰው ግልጽ ማብራሪያ የለም።

ይህ በእንዲህ እያለ “ ተማሪዋ ከወንድ ጓደኛዋ ጋር በመጣላቷ ከፎቆ ተወርውራ ነው የተገደለችው ” የሚሉ ወሬዎች እየተዘዋወሩ ነው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ያሰራጫችሁት ፅሑፍ ተማሪዋ በድንገት ከዚህ ዓለም ድካም እንዳረፈች ከመግለጽ ውጪ ስለአሟሟቷ አያብራራም፤ በሌላ ወገን ደግሞ ተማሪዋ የሞተችው “ ከፎቅ ተወርውራ ” እንደሆነ እየተገገረ ነው፣ እውነታው ምንድን ነው ? ሲል ዩኒቨርሲቲውን ጠይቋል።

ከዩኒቨርሲቲው የሕዝብና ዓለም ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ቢሮ ምላሽ የሰጡን አቶ ማቲዎስ ጪናሾ፣ “ በፃፍነው ላይ ድንገት ሕይወቷ አለፈ ነው የሚለው። አሁን ደግሞ የሞቷ ምክንያት ምን እንደሆነ ፓሊስ እያጣራ ነው ያለው ” ብለዋል።

“ እርሷ ጋር የነበረ ልጅም አለና ከእርሱ ኢንቬስቲጌት እያደረጉ ስለሆነ መረጃውን ፓሊስ ይፋ ሲያደርግ እኛም ይፋ እናደርጋለን ብለን ነው እየጠበቅን ያለነው ” ነው ያሉት።

እስካሁን የተገኘ ፍንጭ አለ ? ከፎቅ ተወርውራ ስለመገደሏ አመላካች ጉዳዮች፤ የአሟሟቷ ሂደት እንዴት ነው ? ሲል ቲክቫህ ላቀረበው ጥያቄ ፣ “ የአሟሟት ሂደቱን እኛ አሁን ይሄ ነው ብለን መናገር አንችልም ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

“ ምክንያቱም ጉዳዩን የያዘው ፓሊስ ነው። የሞቷ ምክንያት ይሄ ነው ብሎ ይፋ ሲያደርግ ነው ይፋ ማድረግ የምንችለውና አሁን እኛም የተረዳነው ነገር የለም ” ሲሉም አክለዋል።

“ ዝም ብለው ወሬዎቹ አሉ። ወሬዎቹ የተለያዩ ናቸው” ያሉት አቶ ማቲዎስ፣ “ ‘ከ4ኛና 5ኛ ፎቅ ወድቃም’ ይባላል፤ ‘ሰው አንቋትም’ ይባላል፤ የተለያዬ ወሬ ነው ያለውና ያንን አሁን እንደ ምክንያት አንቀበልም። መቀበል የምንችለው የተጣራ መረጃ ሲገኝ ነው ” ብለዋል።

አደጋው የደረሰው ከቀናት በፊት ከምሽቱ 4 ሰዓት ገደማ እንደሆነ፣ አስከሬኑ አዲስ አበባ ወደሚመለከተው ሆስፒታል ሌሊት ተወስዶ፣ በማግስቱ ሀዋሳ ከቤተሰብ እንደደረሰ፣ ቤተሰብ የቀብር ሥነ ሥርዓት እንደፈጸመ፣ ዩኒቨርሲቲውም ትላንት የሻማ ማብራት ሥነ ሥርዓት እንዳካሄደ አቶ ማቲዎስ ተናግረዋል።

በተጨማሪ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ስለጉዳዩ የጠየቀው የወላይታ ሶዶ ዞን ፓሊስ ለጊዜው ማብራሪያ ከመስጠት የተቆጠበ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ህብረት ደግሞ ጉዳዩን እንደሚያጣራ ገልጿልናል።

(ጉዳዩን እስከመጨረሻው በመከታተል ተጨማሪ መረጃ እናደርሳችኋለን)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

EBS TV

19 Oct, 11:04


ፎቶ ፦ የሁሉ አባት የሆኑት የአባ መፍቀሬ ሰብእ ክቡር አስከሬን ሌሊቱን በርዕሰ አድባራት ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ጸሎተ ሰዓታት ፣ ማኅሌት ሲደረስ አድሮ ፣ በክብር አሸኛኘት ወደ ደሴ ደብረ ቤቴል ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል በመድረስ በአሁኑ ሰዓት ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ የምዕራብ ካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት ጸሎተ ፍትሐት እየተደረገ እንደሚገኝ ከተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል የተገኘው መረጃ ያሳያል።

የደሴ አድባር ፣ የሁሉ አባት፣ የሁሉ አለቃ፣ የሁሉ መካሪ፣ የሁሉ ዘካሪ፣ የሀገር ምሰሶ፣  የቤተ ክርስትያን ድምቀት እና  የአውደ ምህረት ጌጥ እንደነበሩ የተገለጸላቸው ሊቀ ትጉሀን ባህታዊ አባ መፍቀሬ ሰብዕ በ96 አመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸው ይታወሳል።

Photo Credit - ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል/ TMC

@tikvahethiopia

EBS TV

19 Oct, 11:04


" በተፈጸመባት ግርፋት ክፉኛ ተጎድታለች፤ የአካሏ ግራ ክፍል አይሰራም። የራስ ቅሏ ተሰብሯል " - የቤተሰብ አባል

በኦሮሚያ ክልል ፣ በምስራቅ ቦረና ዞን ዋጪሌ ወረዳ ' የሽማግሌዎችን ትዕዛዝ አላከበረችም ' በሚል ከዛፍ ጋር ታስራ በባለቤቷ ክፉኛ የተደበደበችና የተገረፈች የ3 ልጆች እናት በአስጊ ጤና ሁኔታ ላይ እንደምትገኝ የቤተሰብ አባሏ ተናገሩ።

በአሁኑ ወቅት በሐዋሳ ሆስፒታል በህክምና ላይ የምትገኘው ኩሹ ቦናያ የተባለችው እናት በደረሰባት ግርፋት ክፉኛ ተጎድታ " የአካሏ ግራ ክፍል አይሰራም። የራስ ቅሏ ተሰብሯል " በማለት የቤተሰብ አባሏ ገልጸዋል።

የአካባቢው አቃቤ ሕግ በበኩላቸው ግርፋቱን መፈጸማቸው የተጠረጠሩ ባለቤቷን ጨምሮ 8 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ መካሄዱን ተናግረዋል።

በቁጥጥር ስር ከዋሉ ግለሰቦች መካከል የቅጣት ውሳኔውን አስተላልፈዋል የተባሉት ሽማግሌዎች የዋስትና መብታቸው ተከብሮ ሲለቀቁ ባለቤቷ ግን አሁንም በቁጥጥር ስር እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ጃርሶ ቡሌ (ዘመዷ) ምን አሉ ?

" ኩሹ ቦናያ የ3 ልጆች እናት ናት።

ገበያ ላይ አስሮ የመግረፉ ድርጊት የተፈጸመው ባለፈው ወር መስከረም 9/ 2017 ዓ.ም. ነው።

ግርፋቱ የተፈጸመባት ባለቤቷ ገልገሎ ዋሪዮ ይባላል።

ኩሹ እና ባለቤቷ ገልገሎ በትዳር 12 ዓመት ቆይተዋል

በኑሯቸው ችግር ውስጥ ሲወድቁ ባለቤቷ ወደ ውትድርና ይገባል። በውትድርና 4 ዓመት ያህል ቆይቷል።

እሷ ልጆቿን ለማሳደግ ብቻዋን ስትጥር ነው የቆየችው።

ገልገሎ ከውትድርና ከተመለሰ በኋላ ግን ባለቤቱን መደብደብ ይጀምራል።

በተደጋጋሚ ወደ ቤተሰቦቿ እየሸሸችም ሁኔታዎች ሲረጋጉ ወደ ቤቷ ትመለስ ነበር።

ገልገሎ ከውትድርና ከተመለሰ በኋላ ከባለቤቱ ጋር መስማማት አለመቻሉም ፤ ዘወትር ባለቤቱን እና ልጆቹን ይደበድብ ነው።

በአገር ባህል መሰረት ሽማግሌዎች በባለትዳሮቹ መካከል የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት በተደጋጋሚ ለሽምግልና ተቀምጠዋል።

ችግሮች ሳይፈቱ ሲቀሩ ወደ አባቷ ቤተሰብ ሸሸች። ሽማግሌዎች ተነጋግረው ባለቤቷ ጠባዩን እንዲያሻሽል እርሷም ወደ ቤቷ እንድትመለስ መከሯት።

እርሷ ግን ነገሩን በደንብ እንዲያጤኑት ወደ ቤቷ ብትመለስ አንደሚገላት’ ተናገረች።

የሽማግሌዎቹን ቃል አላከበረችም በሚል ሽማግሌዎቹ ታስራ እንድትገረፍ ወስነውባታል።

የሽማግሌዎቹ ውሳኔ የቦረናን ባሕል አይወክልም ፤ ይህ የጥቂት ሰዎች ውሳኔ ነው።

በሚኖሩበት አካባቢ ባለ ዛፍ ላይ አሰሯት። ይህንን ያደረጉት ልጇ እያለቀሰ፣ ሌሎች ቆመው እያዩ ነው።

በስፍራው ተገኝተው የነበሩ በሙሉ ፎቶ እንዳያነሱ፣ ቪድዮ እንዳይቀርጹ ተከልክለው ነበር።

ስትገረፍ ከዋጪሌ ዱብሉቅ አንድ መኪና በድንገት መጣ።

አንድ ልጅ ከመኪናው ወርዶ ቪድዮ መቅረጽ ጀመረ ፤ በዚህም የተፈጸመውን ወንጀል ሌሎች ሊያዩት ይችለዋል።

የሦስት ልጆች እናት የሆነችው ኩሹ በዛፍ ላይ ታስራ በባለቤቷ ግርፋት ከደረሰባት በኋላ ክፉኛ ተጎድታለች።

የአካሏ ግራ ክፍል አይሰራም። የራስ ቅሏ ተሰብሯል።

የቤተሰብ አባላቶቿ የደረሰባትን ወድያውኑ አልሰሙም ነበር። ለሳምንት ያህል ሕክምና ሳታገኝ ቆይታለች።

ወንጀሉ አንደተፈጸመ ወድያውኑ ቪድዮው አልተለቀቀም ነበር። ከሳምንት በኋላ ነው ሰው ያየው። ወላጆቿም የሆነውን ያዩት ከቪድዮው ላይ ነው።

መጀመርያ በአሬሮ ሆስፒታል በኋላም ወደ ያቤሎ ሆስፒታል ሄዳ ሕክምና የተከታተለች ቢሆንም የተሻለ ሕክምና በማስፈለጉ ወደ ሐዋሳ ሆስፒታል ተልካለች። "


የዋጪሌ ወረዳ አቃቤ ሕግ ኃላፊ የሆኑት አቶ ጉዮ አሬሮ ጥቃቱ በቃቃሎ መንደር መፈጸሙን እና ከተፈጸመ ከሳምንት በኋላ ሪፖርት መደረጉን ተናግረዋል።

" መረጃው እንደደረሰን የምርመራ ቡድን በማዋቀር መረጃ መሰብሰብ ጀምረናል " ብለዋል።

ተጠርጣሪዎቹ በቁጥር ስር ውለው ፍርድ ቤት ከቀረቡ በኋላ ሽማግሌዎቹ የዋስትና መብታቸው ተከብሮ ሲለቀቁ ባለቤቷ ግን አሁንም በእስር ላይ እንደሚገኝ ጨምረው ተናግረዋል።

" ክስ ለመመስረት የሕክምና ማስረጃ እንፈልጋለን። አሁንም የሕክምና ክትትል እያደረገች በመሆኑ መረጃው ገና ተጠናክሮ አልቀረበልንም። ሕጋዊው ጉዳይ ግን ሂደቱን ጠብቆ ይቀጥላል " ሲሉ ተናግረዋል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የቢቢሲ አማርኛው አገልግሎት ነው።

ቪድዮ፦ ከማህበራዊ ሚዲያ

@tikvahethiopia

EBS TV

17 Oct, 17:03


" ታፍኖ ከተወሰደ ከ5 ቀናት በኋላ ተገድሎ አስክሬኑ ወንዝ ተጥሎ ተገኝቷል " - የትግራይ ነፃነት ፓርቲ

የትግራይ ነፃነት ፓርቲ የአመራር አባሉ ታፍኖ ከተወሰደ በኃላ ተገድሎ አስከሬኑ ወንዝ ተጥሎ እንደተገኘ ገለፀ።  

ፓርቲው ታፍኖ የተወሰደውን የአመራር አባሉን ላለፉት ከ5 ቀናት ሲፈልግ የቆየ ቢሆን ተገድሎ አስክሬኑ ወንዝ ተጥሎ ማግኘቱ አሳውቋል።

የፓርቲው ሊቀ-መንበር ዶ/ር ደጀን መዝገበ " አሰቃቂ ድርጊቱ የተፈፀመው በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን አስገደ ወረዳ ነው " ብለዋል።

ተገድሎ የተገኘው የፓርቲው አመራር አባል በወረዳው የፓርቲው አስተባባሪ መሆኑን ገልጸው ፥ " ታፍኖ ከተወሰደ ከ5 ቀናት በኋላ ተገድሎ ሬሳው በወንዝ ተጥሎ ተገኝቷል ይህ ጭካኔ የተሞላበት አረመንያዊ ድርጊት ነው " ሲሉ አውግዘውታል። 

ሊቀ-መንበሩ በዞኑ የሚገኙ አባላቱ " ' ፓርቲው መደገፍ ህወሓት መቃወም አቁሙ አለበለዚያ ትገደላላችሁ ' የሚል ማስፈራርያ ደርሶዋቸዋል " ሲሉ ' ህወሓትን ክሰዋል።

ህወሓት ለቀረበበት ክስ እስካሁን የሰጠው መልስ የለም። 

" ተግባሩን የህወሓት አባላት ነው እየፈፀሙ የሚገኙት " በማለት ያቀረቡትን ክስ ያጠነከሩት የፓርቲው ሊቀመንበር " በ19 የፓርቲው አባላት አፈና ፣ ደብደባና ግድያ ደርሷል " ማለታቸው ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            

EBS TV

17 Oct, 16:26


#AddisAbaba

ትናንት ምሽት 5 ሰዓት ተኩል ገደማ በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ ከተማ ወረዳ 7 ኢንዱስትሪ መንደር እየተባለ በሚጠራው አካባቢ አንድ ግለሰብ በማሽን ተይዞ በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወቱ አልፏል።

እንደ አዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን መረጃ ፤ ከሜድሮክ ድርጅቶች በአንዱ ውስጥ ሰራተኛ የሆነው ሟቹ ትናንት ምሽት አሸዋ በሚፈጭ ማሽን ላይ ስራውን እያከወነ በነበረበት ወቅት በማሽኑ ተይዞ ወዲያው ህይወቱ አልፏል።

አስከሬኑን ከማሽኑ ለማላቀቅ አልተቻለም ነበር፡፡

የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች አስከሬኑን ከማሽኑ አላቀው ማውጣት የቻሉት ለ2 ሰዓት ከፈጀ ጥረት በኋላ ነው።

የትናንቱ በማሽን ላይ የደረሰው አደጋ ጉዳይ በህግ ተይዟል ተብሏል።

በሌላ በኩል ፤ ትላንት በሸገር ከተማ አሸዋ ሜዳ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ተቆፍሮ ክፍቱን በተተወና ወሀ ባቆረ ጉድጓድ ውስጥ ሁለት ወጣቶች ህይወታቸው አልፏል።

ሟቾቹ ዕድሜያቸዉ 19 እና 23 ነው።

የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች አንደኛውን ወጣት አስክሬን አውጥተዉ ለፖሊስ ያስረከቡ ሲሆን እድሜው 19 ዓመት የሆነው ወጣት አስክሬን የአካባቢው ህብረተሰብ አስቀድሞ አውጥተውታል።

ክፍት የተተወው ጉድጓድ ውሃ ያለበት በመሆኑ አንደኛው ግለሰብ ለመታጠብ ብሎ ገብቶ ተንሸራትቶ ወደ ውሃው ውስጥ ይገባል ፤ የዚህን ሰው መግባት የተመለከተው ሌላው ግለሰብ ደግሞ እርሱን ለማውጣት ሲል ወደ ጉድጓዱ በመግባቱ የሁለቱም ህይወት ወዲያው አልፏል፡፡

#ShegerFM102.1

@tikvahethiopia

EBS TV

17 Oct, 16:26


#Tigray

" ጠቅላይ ሚንስትሩ ያስቀመጡት የመፍትሄ አቅጣጫ ተግባራዊ አልሆነም " - የትግራይ የንግድ ማህበረሰብ ግብረ ሃይል ተወካዮች

የትግራይ የንግድ ማህበረሰብ ግብረ ሃይል ተወካዮች ከሰሞኑን ውይይት ተቀምጠው ነበር።

በዚህም ወቅት ፤ " ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አህመድ በትግራይ ከነበረው ጦርነት ጋር በተያያዘ የተከማች የብድር ወለድና ቅጣት መልክ እንዲይዝ ባለፈው ዓመት የሰየሙት የመፍትሄ አፈላላጊ ቡድን እስካሁን ያስቀመጠው ተጨባጭ ነገር የለም " ብለዋል።

" ጠቅላይ ሚንስትሩ በሰጡት የአመራር አቅጣጫ የገንዘብ ሚንስቴር ፣ የብሄራዊ ባንክና ልሎች ከፍተኛ የፌደራል መንግስት የስራ ሃላፊዎች ያካተተ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ቢቋቋምም እስከ አሁን የሚዳሰሰ የሚጨበጥ ለውጥ አልመጣም " ሲሉ ገልጸዋል።

ተወካዮቹ ፥ " ከ7 ወራት በፊት በ2016 ዓ.ም ጠቅላይ ሚንስትሩ ወደ አዲስ አበባ ከጋበዟቸው የንግድ ማህበረሰብ ያካተተ ልኡክ ጋር ባካሄዱት ውይይት ማጠቃለያ በጦርነቱ ጊዜ የተከማቸው የብድር ወለድና ቅጣት ተሰልቶ ፓለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ መፍትሄ እንዲሰጠው አቅጣጫ ቢያስቀምጡም እስከ አሁን ጠብ የሚል መፍትሄ አለመጣም ይህም በጣም አሳዝኖናል " ብለዋል።

አበዳሪ የፋይናንስ ተቋማት የሰጡት የብድር ወለድ ከነቅጣቱ እንዲመለስ የንግድ ማህበረሰቡ ማስጨነቅ እንደጀመሩ በዚሁ ውይይት ወቅት ተነግሯል።

ተግባሩ በጦርነት ምክንያት የደቀቀው የክልሉ ኢኮኖሚያዊ አቅም ይበልጥ ጉልበት የሚያሳጣ መሆኑ በመገንዘብ አገራዊ የፓሊሲና የፓለቲካ መፍትሄ ሊሰጠው ይገባል ተብሏል።

ጉዳዩ ጊዜ የሚሰጥ አይደለምና " አስቸኳይ ትኩረት እና መፍትሄ " እንደሚያሻው አፅንኦት ተሰጥቷል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች የፌደራል መንግስት የትግራይ የንግድ ማህበረሰብ የሚታደግ የመፍትሄ እርምጃ እንዲያስቀመጥ ተጠይቋል።

#TikvahEthiopiaMekelleFamily

@tikvahethiopia

EBS TV

17 Oct, 14:22


#ትኩረት🚨

ከሰሞኑን በርካታ ሰዎች በተለይ ትንንሽ ህጻናት በጉንፋን እና በጉንፋን መሰል የመተንፈሻ አካላት ህመም እየተያዙ ይገኛሉ።

ይህንን ወቅታዊ ሁኔታ አስመክቶ ጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና እንስቲትዩት ያጋራ መግለጫ ልከዋል።

ምን አሉ ?

➡️ የጉንፋን ሕመም በተፈጥሮ የላይኛውን የመተንፈሻ የሰውነት ክፍሎች ማለትም አፍንጫን፣ ጎሮሮን እና የአየር መተላለፊያ ባንቧን የሚያጠቃ ተላላፊ ሕመም ነዉ።

➡️ ሪኖ ቫይረስ ለጉንፉን መከሰት ዋና ምክንያት ሲሆን፣ ኮሮና፣ ኢንፍሉዌንዛ፣ ፓራ ኢንፍሉዌንዛ፣ አር ኤስ ቪ(RSV) ቫይረሶች ደግሞ ለጉንፉን መሰል ህመሞች መከሰት ዋና ዋና ምክንያቶች ናቸዉ። ከተጠቀሱት ቫይረሶችም ለጉንፋን ሕመም መከሰት 50 በመቶ ድርሻውን የሚይዘው ሪኖ ቫይረስ ነው፡፡ በደረቅ ነፋሳማ ወቅት የአፍንጫ የውስጠኛው ስስ ሽፋን “ ሙከስ መምብሬን ” ስለሚደርቅ የጉንፋን ሕመም እና ተላላፊነቱ ይጨምራል፡፡

➡️ የክረምት ወራት ወይም የዝናብ ወቅት ማብቃቱን ተከትሎ መስከረምን ጨምሮ በጥቅምትና ህዳር ወራት እንደዚህ አይነት ጉንፋን መሰል ህመም የሚጠበቅ ነው፡፡

➡️ ሕመሙ ከሰው ወደ ሰው የሚተላለፈው በቫይረሱ የተጠቃ ሰው በሚያስልበት ወይም በሚያስነጥስበት ጊዜ እንደሆነና በተጨማሪም ሰዎች ቫይረሱ ያረፈበትን የበር እጀታ፣ ጠረጴዛ ወይም በሕመምተኛው የተነካካንን ሰው እጅ ከነኩ በኋላ አፋቸውንና አፍንጫቸውን ሲነካኩ ቫይረሱ ለመተላለፍ በሚፈጠርለት ምቹ ሁኔታ ነው።

➡️ የጉንፋን ሕመም የመጀመሪያ ምልክቱ ከመጀመሩ አንድ ቀን በፊት ተላላፊ ሊሆን ይችላል፤ ሕመሙ ከጀመረ ከ 5 እስከ 10 ባሉት ቀናት ደግሞ ሕመምተኛው ቫይረሱን ያስተላልፋል።

➡️ ህመሙ አብዛኛዉን ጊዜ እስከ 2 ሳምንት ሊቆይ ይችላል። ምልክቶቹም እንደ ፦
° የአፍንጫ ፈሳሽ መብዛት፣
° ሳል፣
° ትኩሳት፣
° ራስ ምታትና ጉሮሮን መከርከር፣
° ማስነጠስ፣
° አይን ማሳከክ እና መቅላት፣
° ማስታወክ፣
° ከፍ ሲልም የትንፋሽ ማጠር፣
° ከፍተኛ ድካምና የምግብ ፍላጎት መቀነስ ዋና ዋናዎቹ ናቸዉ።

➡️ ከመስከረም ወር ጀምሮ መሰል ህመም ተሰምቷቸው ወደ ጤና ተቋማት በመሄድ ናሙና ከሰጡት ታካሚዎች ውስጥ አር ኤስ ቪ የተገኘባቸዉ ቁጥር የመጨመር ሁኔታ ያሳያል፡፡ በዚሁ ወቅት የተከሰተው ጉንፋን መሰል ህመም (አር ኤስ ቪ) በተለይ በህጻናት ላይ በብዛት የተከሰተ ሲሆን ለዚህም ወቅቱ ትምህርት ቤት የተከፈተበት በመሆኑ ለበሽታው መስፋፋት አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡

➡️ ባለፈዉ 1 ወር ዉስጥ ተመርምረዉ አር ኤስ ቪ ከተገኘባቸዉ ታካሚዎች መካከል 84% ያክሉ እድሜያቸዉ ከ5 አመት በታች ነዉ። እንደዚሁም ባለፈዉ ሳምንት ለአር ኤስ ቪ ከተመረመሩት 81 ናሙናዎች 49 (60.5%) ያህሉ ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል።

➡️ አስፈላጊው ጥንቃቄ ካልተደረገ በሽታው የመዛመት እድሉ ከፍ ሊል እንደሚችል፤ በተለይ ቀዳሚ ተጎጅ ሊሆኑ የሚችሉ እንደ ህጻናትና አረጋውያን ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎች አና ተጓዳኝ የጤና ችግር እንደነ አስም፣ የስኳር በሽታ፣ ካንሰር እና ሌሎች ሥር የሰደዱ በሽታዎች ያሉባቸው ሕሙማን ከፍተኛ ጥንቃቄ ልናደርግላቸው እና ወደ ጤና ተቋማት በመሄድ አስፈላጊዉን ምርመራና ህክምና ሊያደርጉ ይገባል።

➡️ የጉንፋን ሕመም የጆሮ ኢንፌክሽን እና የሳንባ ምች ሕመምን ጨምሮ ለተለያዩ ሕመሞች ተጋላጭ ሊያደርግ ይችላል፡፡

ጉንፋን መሰል በሽታን የምንከላከልባቸው መንገዶች ምንድናቸው ?
° የእጅ ንጽህናን መጠበቅ፣
° ሰዎች በተሰበሰቡበት ቦታ የአፍና አፍንጫ ጭምብል(ማስክ) ማድረግ
° በዕለት ኑሯችን የምንጠቀምባቸውን በከባቢዎቻችን የሚገኙ ቁሳቁሶችን ማጽዳት
° የብዙሃን ማጓጓዣ ትራንስፖርት ላይ መስኮቶችን በመክፈት በቂ የአየር ዝዉዉር እንዲኖር በማድረግ የበሽታዉን የመተላለፍ ዕድል መቀነስ ይቻላል፡፡


#ማሳሰቢያ ፦ ህብረተሰቡ አስፈላጊውን የጥንቃቄ እርምጃዎችን እንዲወስድና ጠንከር ያለ የበሽታው ምልክት የሚታይበት ሰው በፍጥነት በአቅራቢያው ወደሚገኝ የጤና ተቋም በመሄድ አስፈላጊውን የህክምና ምክር አና ዕርዳታ ማግኘት አለበት፡፡

#MoH #EPHI

@tikvahethiopia

EBS TV

17 Oct, 10:21


🔈 #የሰራተኞችድምጽ

" ኑሮን መቋቋም አቃተን ! " - ሰራተኞች

በተለይ በተለይ አዲስ አበባ ከተማ ነዋሪነታቸውን ያደረጉና ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ በተለያዩ የመንግሥት እና የግል ተቋማት ውስጥ ተቀጥረው የሚሰሩ ሰራተኞች ኑሮን መቋቋም ፈተና እንደሆነባቸው ገልጸዋል።

ቃላቸውን ከሰጡት ውስጥ የልጆች እናት መሆናቸውን የገለጹ አንዲት እናት " መሃል ከተማ ያለውን የማይቀመስ የቤት ኪራይ ሽሽት ከከተማ ጥግ ብገባም በየጊዜው በእያንዳንዱ ነገር ላይ በሚታየው ጭማሪ ኑሮን መቋቋም አልቻልኩም " ብለዋል።

" እኔ የዛሬ አመት ይከፈለኝ የነበረ ደመወዝ ዛሬም እዛው ነው ትምህርት ቤት፣ የምግብ ግብዓት፣ አልባሳት፣ ትራንስፖርት ሌሎችም ነገሮች ጨምረዋል ፤ ነገር ሁሉ ነው ግራ ያጋባኝ " ሲሉ በሃዘን ስሜት ያሉበትን ሁኔታ ገልጸዋል።

ሌላኛዋ ወጣት በአንድ የግል ድርጅት ውስጥ ተቀጥራ የምትሰራ ፥ " ከተመረቅኩ ይኸው 5 ዓመቴ ነው ፤ ደህና ደመወዝ የለኝም። የምሰራው ቀን ሙሉ ነው ደመወዜ እዛው ሆኖ ያልጨመረ ነገር የለም " ብላለች።

" ቤት ኪራይ ብቻዬን መክፈል ስለማልችል ከጓደኛዬ ጋር ነው የምኖረው ፤ እንደዛም ሆኖ የወር ጊቢዬን ምኑን ከምን እንደማደረገው አላውቅም ይኸው ልክ እንደ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ አንዳንዴ ቤተሰቦቼ ገንዘብ ይልኩልኛል ፤ ሁኔታዎች እንዲህ ከሆኑ እዛው ቤተሰቤ ጋር ሄጅ ሻይ ቡናም ቢሆን እየሰራው ብኖር ይሻለኛል " ስትል ተናግራለች።

ሌላ ቃላቸውን የሰጡ አንድ አባት ፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በየአገልግሎቱ ላይ የሚታዩት ጭማሪዎች እሳቸውና ሌሎችም ሰራተኛ ዜጎች ቼይ ከፍተኛ ጫና እንደሚያሳድር ገልጸዋል።

" አንዳንድ የመንግሥት ተቋማት ሳይቀሩ ለአገልግሎት የሚያስከፍሉትን ጭማሪ አድርገዋል ፤ ትራንስፖርት ዋጋው ጨምሯል እኔም ሆንኩኝ ሌላው ሰራተኛ ወርሃዊ ደመወዙ እዚህ ግባ የማይባል ነው ፤ ታዲያ ኑሮ የሚኖረው  ፤ ልጆችን ማሳደግ የሚቻለው እንዴት ነው ? " ሰሉ ጠይቀዋል።

አዲስ አበባ ከተማ በርካታ ዜጎች የሚኖሩባት ሲሆን የቤት ኪራይ ዋጋ የማይቀመስባት በመሆኑ በርካቶች ከሚሰሩበት ርቀው ከከተማ ዳር ዳር ተከራይተው ለመኖር ይገደዳሉ።

በርካቶች ጥዋት ማታ ለፍተው ተንከራተው የሚያገኙት ገቢም እዚህ ግባ የማይባል ፤ ያሰቡትን ለማሳካት ይቅርና ኑሮን ለመግፋት የማያስችል ነው።

በተለይ ወርሃዊ ደመወዝ የሚያገኙ ዜጎች በኑሮ ውድነቱ እጅግ በጣም ነው የሚፈተኑት።

ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ ወጣቶች በክልል ከተሞች ያለው ብሔር እየመረጡ ፣ በትውውቅ በሙስና ሰዎችን ስራ መቅጠር ፣  አስተማማኝ የሆነ ሰላምና ደህንነት ሁኔታ አለመኖር ፣ ብዙ ድርጅት እና ተቋማት አለመኖር ፣ የሰፋ የስራ እድል አለመኖር ፣ በአንዳንድ ከተሞችም ያለውን እንቅስቃሴ እጅጉን መዳከም ሳቢያ በአንጻራዊነት አዲስ አበባን ለኑሮና ስራ እንዲመርጧት እንዳደረጋቸው ጠቁመዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

EBS TV

17 Oct, 10:21


" የታይ-ታይ ከረሜላ በህጋዊ መንገድ የተመዘገበ እና የተረጋገጠ ጤናማ እና ደህንነቱ የተጠበቀ ነው " -ቪታ ፉድ ኢንዱስትሪ ኃ.የተ.የግ.ማ

መሰረቱን በቱርክ ያደረገው እና እ.ኤ.አ ከ 2019 ጀምሮ በኢትዮጵያ ታይ ታይ የተሰኙ ከረሜላዎችን በማምረት ለተጠቃሚዎች እያደረሰ የሚገኘው ቪታ ፉድ ኢንዱስትሪ ኃ.የተ.የግ.ማ ምርቶቼ በህጋዊ መንገድ በኢትዮጵያ በአምራችነት የተመዘገቡ እና ጥራታቸውን የጠበቁ መሆናቸውን ሊሰመርበት ይገባል ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ ገልጿል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በገበያ ላይ በመንግስት ያልተመዘገቡና የምስክር ወረቀት የሌላቸው ተመሳስለው የተሰሩ ምርቶች መኖራቸውን አስተውለናል ያለው ድርጅቱ እነዚህ ምርቶች በህገ ወጥ መንገድ ስለሚመረቱ ምንም አይነት የአምራች መረጃም ሆነ አድራሻ የላቸውም ብሏል።

ተቋሙ ጉዳዩን ለአዲስ አበባ ጤና ቢሮ እና ለኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን በተደጋጋሚ ማሳወቁን በመግለጫው ገልጿል።

የአዲስ አበባ ጤና ቢሮም እነዚህን ህገወጥ ምርቶች የመለየት ስራ የሰራ ሲሆን የኢትዮጵያ ምግብ እና መድኃኒት ቁጥጥር ባለሥልጣንም ምርቶቹን በመገናኛ ብዙሃን በማሳወቅ ከገበያ አግዷቸዋል።

ሆኖም እኚህ የታገዱ፣ በህገወጥ መንገድ የተመረቱ እና ተመሳስለው የተሰሩ ምርቶች የእኛን ምርቶች አመሳስለው ስለሚገለብጡ ደንበኞቻችን ምርቶቹን ከእኛ(ከህጋዊ ምርቶች)መለየት ባለመቻላቸው ምርቶቻችን ታግደዋል የሚል ብዥታ እንደተፈጠረ ተናግሯል።

ድርጅቱ የታይ-ታይ ከረሜላ በህጋዊ መንገድ የተመዘገበ እና የተረጋገጠ ጤናማ እና ደህንነቱ የተጠበቀ እንዲሁም በህጋዊ መንገድ በኢትዮጵያ በአምራችነት የተመዘገበ መሆኑን ሊሰመርበት ይገባል ብሏል።

እነዚህ ምርቶች (ከረሜላዎች) በተለይም ልጆች የሚጠቀሟቸው በመሆኑ ሁሉም ሰው ከመግዛቱ በፊት የምርቶቹን ደህንነት ግምት ውስጥ ማስገባት እንደሚኖርበት አሳስቧል።

@tikvahethiopia

EBS TV

17 Oct, 10:21


" የቅልጥ ዓለቱ እንቅስቀሴ እስከቀጠለ ድረስ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቱ የመቀጠል እድል አለው " - ኤልያስ ሌዊ (ዶ/ር)

በዛሬው ዕለት ከቀኑ 6 ሰዓት አከባቢ በ 'አዋሽ ፈንታሌ' የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል።

ንዝረቱ በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ አካባቢዎች ተሰምቷል፡፡

ትናንት ምሽት የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት መሰማቱ ይታወሳል።

አሁንም ዳግም የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ መከሰቱ ታውቋል።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦፊዚክስና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር ዶ/ር ኤሊያስ ሌዊ ለብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጡት ቃል፥ " ከቀኑ 6 ሰዓት ከ10 ደቂቃ ከ9 ሰኮንድ በአዋሽ ፈንታሌ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል በሬክተር ስኬል 4.6 አካባቢ ነው " ብለዋል።

የዛሬው የመሬት መንቀጥቀጥ የተከሰተው ባለፈው በተከሰተበት አዋሽ ፈንታሌ አካባቢ ሲሆን በአካባቢው ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ እንቅስቃሴ አሁንም እንዳልቆመ ተናግረዋል።

" አሁን የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ የንዝረት መጠኑ አነስተኛ ነው " ሲሉ ገልጸው " በአዋሽ ፈንታሌ እና ሳቡሬ ከተማ መካከል ላይ ያለው የቅልጥ ዓለት እንቅስቀሴ እስከቀጠለ ድረስ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቱ የመቀጠል እድል አለው "  በማለት ለብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ አስረድተዋል።

@tikvahethiopia

EBS TV

17 Oct, 03:33


#Update

እንደ ' አሜሪካ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ ድረገጽ ' ዛሬ ምሽት ልክ 5:11 ላይ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ ነበር።

የመሬት መንቀጥቀጡ ከአዋሽ በሰሜን በኩል 17 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ነው።

በሬክተር ስኬል 4.6 የተመዘገበ እንደሆነ ጠቁሟል።

የመሬት መንቀጥቀጡ ንዝረት በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች እና በተለያዩ የክልል ከተሞች ተሰምቷል።

አዋሽ አካባቢ ባለፉት ሳምንታት ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ እየተከሰተ ሲሆን አዲስ አበባ ድረስ የዘለቀ ንዝረት ሲሰማ ይህ በቀናት ልዩነት ለ3ኛ ጊዜ ነው።

ከቀናት በፊት አዋሽ ፈንታሌ አካባቢ በሬክተር ስኬል 4.6 የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ ከዛ በፊት ደግሞ በሬክተር ስኬል 4.9 የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ ንዝረቱ አዲስ አበባና ሌሎች ከተሞች ላይ መሰማቱ ይታወሳል።

@tikvahethiopia

EBS TV

17 Oct, 03:33


#Alert🚨

ከደቂቃዎች በፊት በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች የመሬት መንቀጥቀጥ ንዘረት እንደሰሙ ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ጠቁመዋል።

" በተለይም ፎቅ ላይ በደንብ ይታወቅ ነበር " ብለዋል።

ጎተራ፣ አያት ፣ ባልደራስ ፣ ሰሚት ፣ መካኒሳ ፣ ጀሞ ፣ ኮዬ ፣ ጣፎ ፣ ቱሉ ዲምቱ ፣ ጦር ኃይሎች ፣ ቀጨኔ፣ ጎፋ ... እንዲሁም ከሌሎች በርካታ አካባቢዎች ቲክቫህ ኢትዮጵያ ንዝረቱ መሰማቱን የሚመለከቱ መልዕክቶችን ተቀብሏል።

ይህ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት በቀናት ውስጥ ለሶስተኛ ጊዜ ነው።

ሰሞኑን በአዋሽ ፈንታሌ አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ እየተከሰተ መሆኑ ይታወቃል።

ይህም የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ አዲስ አበባ እና ሌሎች ከተሞች ድረስ እየተሰማ ነው።

@tikvahethiopia

EBS TV

16 Oct, 16:40


#ኢትዮቴሌኮም : ዛሬ የኢትዮ ቴሌኮም 10 በመቶ የአክሲዮን ሽያጭ ይፋ ሆኗል።

ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በተካሄደ ሥነ-ስርዓት የኢትዮ ቴሌኮም 10 በመቶ የአክሲዮን ሽያጭ ይፋ ተደርጓል።

የአክሲዮን ሽያጭ ጊዜው ከዛሬ ጥቅምት 6 ጀምሮ እስከ ታኅሣስ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ይቆያል ተብሏል፡፡

ዝርዝር መረጃ ፦

- በ2016 በወጣው የሂሳብ ሪፖርት የድርጅቱ ካፒታል ➡️ 100 ቢሊዮን ብር ነው።

- በዓለም አቀፍ የ3ተኛ ወገን የገበያ ተመን መሰረት ድርጅቱ የሚያወጣው ዋጋ ➡️ 300 ቢሊዮን ብር ነው።

- በመጀመሪያው ዙር መደበኛ የአክሲዮን ሽያጭ የቀረበው ➡️ 100 ሚሊዮን ሼር ነው።

- የአንድ ሼር ዋጋ ➡️ 300 ብር ነው።

- 100 ሚሊዮን ሼር በ300 ብር ሲሸጥ ኢትዮ ቴሌኮም ከሼር ሽያጭ ➡️ 30 ቢሊዮን ብር ያገኛል።

- ዝቅተኛ መግዛት የሚቻለው የሼር መጠን  ➡️ 33 ሼር ሲሆን ይህን በገንዘብ ሲቀመጥ 9,900 ብር ይሆናል።

- ከፍተኛው መግዛት የሚቻለው የሼር መጠን 3,333 ሲሆን ይህን በገንዘብ ሲቀመጥ ➡️999,900 ብር ይሆናል።

- መግዛት የሚቻለው ከዛሬ ጥቅምት 6 እስከ ታህሳስ 25 ድረስ ይሆናል።

- የሼር አባላቱ የሚታወቁት ➡️ ጥር 23/2017

- ሽያጩ በቴሌብር ብቻ የሚደረግ ይሆናል።

- ክፍያውን በ48 ሰዓት ውስጥ መክፈል ይቻላል።

- አንድ አክሲዮን ግዢ ሲፈጸም ከአክስዮኑ ዋጋ በተጨማሪ 1.5% የአገልግሎት ክፍያ እና ተጨማሪ እሴት ታክስ የሚከፍል ይሆናል።

- ከከፍተኛው የአክሲዮን መጠን በላይ መግዛት አይቻልም።

- ግብይቱ የሚካሄደው በኢትዮጵያ ብር ብቻ ነው።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

EBS TV

16 Oct, 12:44


#AddisAbaba 🛬 #DireDawa

በዛሬው ዕለት ከአዲስ አበባ ወደ ድሬዳዋ በመጓዝ ላይ የነበረ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር ET248 ድሬዳዋ አውሮፕላን ማረፍያ ለማረፍ በዝግጅት ላይ ሳለ በአውሮፕላኑ ውስጥ #ጢስ መታየቱን አየር መንገዱ አሳውቋል።

አውሮፕላኑ በድሬዳዋ አውሮፕላን ማረፍያ በሰላም እንዳረፈም ገልጿል።

መንገደኞችን በተለመደው መልኩ ከአውሮፕላኑ ማውረድ መቻሉን ገልጾ አየር ጢሱ የተነሳበትን ምክንያት በማጣራት ላይ እንደሚገኝ ጠቁሟል።

ለተፈጠረው ክስተት መንገደኞቹን ይቅርታ ጠይቋል።

ከዚህ ቀደም (ከወራት በፊት) ከሀዋሳ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበረ አውሮፕላን ውስጥ ጭስ መታየቱን ፤ ነገር ግን አውሮፕላኑ በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፍያ በተመደበለት የመንገደኞች ማስተናገጃ በር ያለ ምንም እክል መቆሙ መንገዶኞቹም ከአውሮፕላን ላይ ደህንነታቸው እንደተጠበቀ መወርዳቸው መገለጹ የሚዘነጋ አይደለም።

በወቅቱም ጢሱ ከእሳት ወይም ከሌላ ነገር ጋር የተያያዘ ሳይሆን አዉሮፕላን ዉስጥ ያለዉ ዘይት ተቃጥሎ የተፈጠረ መሆኑን ይህም አልፎ አልፎ የሚያጋጥም ችግር እንደሆነ አስረድቶ ነበር።

ዛሬ ከአዲስ አበባ ወደ ድሬዳዋ በመጓዝ ላይ በነበረውና ድሬዳዋ አውሮፕላን ማረፍያ ለማረፍ በዝግጅት ላይ በነበረው አውሮፕላኑ ውስጥ የታየው #ጢስ ምክንያት ምን እንደሆነ #እያጣራ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አሳውቋል።

@tikvahethiopia