አንዲት ትንሽ ልጅ አያቷን እንዲህ ብላ ጠየቀችው፦“ጥርስ አለህ እንዴ አያቴ?”
አያቷም ፈገግ እያለ በረጅሙ ከተነፈሰ በኋላ እንዲህ አላት፦“ልጄ ይህ ህይወት ብዙ አስተምሮኛል፤ ጥርሶች በአጠገብሽ እንዳሉ ጓደኞች ናቸው። አንዳንዴ ይጠቅሙሻል በሌላ ጊዜ ይጎዱሻል። አንቺን እንዲጠቅሙሽ ከፈለግሽ በየቀኑ በደንብ ተቦረሺው እና ደግሞ ሁሌም ቢሆን መንከባከብ መርሳት የለብሽም። አየሽ ቅድም እንዳልኩሽ ነው። ጥርስ እንደጓደኛ ነው። የሚጎዱሽ ውስጣቸው በስብሶ ስታያቸው፤ የሚወዱሽ እንደ ነጭነቱ ልባቸው ንጹህ ሆኖ ታገኚዋለሽ።
የጠፋብሽ ጥርስ ልክ እንደ ጓደኛ ነው። ለተወሰነ ጊዜ ህመም ይሰማሻል ከዚያም ህመሙ ያልፍና ትረሺዋለሽ። ነገር ግን ይህ ባዶነት የማትረሺው ትዝታ ሆኖ ይቀራል። የኔ ትንሽዬ ልጅ እናም እንደምታይኝ ጥርሶቼን በሙሉ አጣሁ። ግን ለምን ጠየቅሽኝ?”
ትንሿ ልጅ ደንፉ እየጫረች መለሰች፦ “በጣም ለፈለፍክ አያቴ!። ባክህ እኔ እስከምመለስ ይሄን ብስኩት አንተጋር ለማስቀመጥ ፈልጌ ነው።”
ያ. ... ፨ ፨..., ፨: ፨ ፨ ፥፥