Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC)

@etbcinfo


Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC)

14 Oct, 10:26


የኢትዮጵያ ንግድ ስራዎች ኮርፖሬሽን በዋና መ/ቤትና በዘርፍ የሚገኙ አመራር እና ሰራተኞች ብሄራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀንን አከበሩ::

የኮርፖሬት ጽ/ቤት ኃላፊ ተወካይ የሆኑት ወ /ሮ ፋንታዬ ወንድሙ ዕለቱ በመላ ኢትዮጵያ ያለን ዜጎች በሰንደቅ ዓላማ ፊት ቆመን ቃለ መሃላ በመፈፀም ለሀገራችንና ለሰንደቅ ዓላማችን ያለንን ክብርና ፍቅር ዳግም የምንገልጽበትና የሀገራችንን አንድነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ ቃላችንን የምናድስበት ነው ሲሉ መልእክት አስተላልፈዋል::

17ኛው የብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ "ሰንደቅ ዓላማችን ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ከፍታ!” በሚል መሪ ቃል በዛሬው ዕለት እየተከበረ ነው፡፡

Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC)

21 Sep, 07:14


የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ባለፉት ሁለት ወራት የገበያ ዋጋ መናርን ለመከላከል በግዥና በስቶክ ያለ ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ገበያውን ለማረጋጋት ጥረት አድርጓል፡፡ በዚህ ረገድ ኮርፖሬሽኑ ያከናወናቸው ዋና ዋና ተግባራት እንደሚከተለው ቀርበዋል፡፡

>> ለመንግሥት ሠራተኛው፣ ለማረሚያ ቤቶችና ሌሎች ሸማች የህብረተሰብ ከፍሎች 3,054 ኩንታል ጤፍ በብር 37,589,371

>> 7,294 ኩንታል አትክልትና ፍራፍሬ በብር 51,529,544

>> 601,800 ሊትር የምግብ ዘይት በብር 64,442,446

>> 7,198 ኩንታል ስኳር በብር 51,215,171

>> 16,344 ኩንታል ልዩ ልዩ የፍጆታ ሸቀጦች በብር 117,643,868 ለህብረተሰቡ በማሰራጨት የገበያ ዋጋ ለማረጋጋት ጥረት ተደርጓል፡፡

በተጨማሪም በግንባታው ዘርፍ እየገጠመ ያለውን ከፍተኛ የሆነ የስሚንቶ አቅርቦት እጥረትና ዋጋ መናር ለመከላከል ከፋብሪካዎች 1,600 ኩንታል በቀጥታ በመረከብ ለተጠቃሚው በተመጣጣኝ ዋጋ ማስራጨት ተችሏል፡፡

በአጠቃላይ ኮርፖሬሽኑ ባለፉት ሁለት ወራት ለገበያ ባቀረበው ምርት በወቅታዊ ገበያ ቢሸጥ ብር 1, 292, 871, 759 ሊያገኝ የሚችለውን በብር 1, 182, 584, 964 በመሸጥ 110, 286, 795 ብር ከገበያው ቅናሽ በማድረግ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ አድርጓል፡፡

Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC)

20 Sep, 13:03


የኮርፖሬሽኑ ያለፉት ሁለት ወራት አፈጻጸም ተገመገመ

የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ያለፉትን ሁለት ወራት ማለትም የሐምሌና ነሐሴ ወራት ዋና ዋና የእቅድ አፈጻጸም ተግባራትን በማኔጅመንት ደረጃ መስከረም 10/ 2017 ዓ.ም ገመገመ፡፡

የእቅድ አፈጻጸም መድረኩን የመሩት የኮርፖሬት ፋይናንስ ዘርፍ ም/ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አለበል ሞላ እና የኢንዱስትሪና የግብርና ውጤቶች ንግድ ዘርፍ ም/ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ቀጸላ ሸዋረጋ ሲሆኑ ባለፉት ሁለት ወራት በግዢና ሽያጭ ክንውን ከእቅድ በታች አፈጻጸም መታየቱ ተመልክቷል፡፡

ኮርፖሬሽኑ በ2017 በጀት ዓመት የሐምሌና ነሐሴ ወራት 63ሺ 832 ኩንታል የእህል፣ ቡና፣ ፍጆታ እቃ፣ አትክልትና ፍራፍሬ ምርት በብር 312, 218, 960 ግዢ ያካሄደ ሲሆን ሽያጭን በተመለከተ በሁለት ወራት 232ሺ 844 ኩንታል ምርት በብር 1, 603, 237, 188 ሽያጭ ፈጽሟል፡፡

በውይይት መድረኩ ለታየው ዝቅ ያለ አፈጻጸም ከነባራዊ ውጫዊ ምክንያቶች ባለፈ ወደ ውስጥ ማየትና ክፍተቶችን በትክክል መለየት እንደሚገባ የተገለጸ ሲሆን በቀጣይ ጊዜያት የማካካሻ እቅድ በማውጣት የተቀመጠውን እቅድ ለማሳካት ርብርብ ማድረግ እንደሚያስፈልግ አጽንኦት ተሰጥቷል፡፡

በተለይም በየደረጃው ያለው አመራር የመሪነት ሚናውን በአግባቡ እየተወጣ ስለመሆኑ ራሱን ሊፈትሽ እንደሚገባና ሁሉም ፈጻሚ ከአዲሱ መዋቅርና ምደባ ጋር ራሱን በማዋሃድ ወደ ስራ መግባት እንዳለበት ማሳሰቢያ ተሰጥቷል፡፡

Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC)

13 Sep, 07:00


የእህልና ቡና ንግድ ዘርፍ በአዳማ ግብይት ማዕከል ለሚገኙ 217 የጉልበት ሰራተኞች አዲሱን ዓመት በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ ስጦታ አበርክቷል፡፡

የማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችችን በመቀላቀልና ድረገጻችንን በመጎብኘት የምርትና አገልግሎት መረጃዎችን በቀላሉና በፍጥነት ያግኙ፡፡
ድረገጽ፡- https://www.etbc.com.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/etbcofficial
ቴሌግራም፡- https://t.me/etbcinfo
አስተያየትዎን በኢሜይል አድራሻችን [email protected] ያድርሱን፡፡

Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC)

10 Sep, 12:47


የኢንሥኮ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አቻ ደምሴ የ2017 አዲስ ዓመት መልዕክት

የማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችችን በመቀላቀልና ድረገጻችንን በመጎብኘት የምርትና አገልግሎት መረጃዎችን በቀላሉና በፍጥነት ያግኙ፡፡
ድረገጽ፡- https://www.etbc.com.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/etbcofficial
ቴሌግራም፡- https://t.me/etbcinfo
ዩትዩብ ቻነል፡- https://www.youtube.com/@etbcinfocom4858
አስተያየትዎን በኢሜይል አድራሻችን [email protected] ያድርሱን፡፡

Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC)

10 Sep, 12:02


የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን እና የራስ ቴአትር አመራርና ባለሙያዎች የ2017 አዲስ ዓመትን በማስመልከት ጳጉሜ 4 ቀን 2016 ዓ/ም በጋንዲ፣ ዘውዲቱ፣ የካቲት 12፣ ራስ ደስታና እና ምኒልክ ሆስፒታሎች በመገኘት ለወላድ እናቶችና ህሙማን የእንኳን አደረሳችሁና ስጦታ የማበርከት ሥነ ሥርዓት አካሂደዋል፡፡

የማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችችን በመቀላቀልና ድረገጻችንን በመጎብኘት የምርትና አገልግሎት መረጃዎችን በቀላሉና በፍጥነት ያግኙ፡፡
ድረገጽ፡- https://www.etbc.com.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/etbcofficial
ቴሌግራም፡- https://t.me/etbcinfo

አስተያየትዎን በኢሜይል አድራሻችን [email protected] ያድርሱን፡፡

1,310

subscribers

583

photos

10

videos