የኮርፖሬት ጽ/ቤት ኃላፊ ተወካይ የሆኑት ወ /ሮ ፋንታዬ ወንድሙ ዕለቱ በመላ ኢትዮጵያ ያለን ዜጎች በሰንደቅ ዓላማ ፊት ቆመን ቃለ መሃላ በመፈፀም ለሀገራችንና ለሰንደቅ ዓላማችን ያለንን ክብርና ፍቅር ዳግም የምንገልጽበትና የሀገራችንን አንድነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ ቃላችንን የምናድስበት ነው ሲሉ መልእክት አስተላልፈዋል::
17ኛው የብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ "ሰንደቅ ዓላማችን ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ከፍታ!” በሚል መሪ ቃል በዛሬው ዕለት እየተከበረ ነው፡፡