ELIAS MESERET @eliasmeserett Channel on Telegram

ELIAS MESERET

@eliasmeserett


Journalist-at-large

ELIAS MESERET (English)

Are you looking for reliable and up-to-date news from all around the world? Look no further than ELIAS MESERET, the Telegram channel run by journalist-at-large Elias Meseret. With years of experience in journalism, Elias Meseret provides insightful and in-depth coverage of the latest news, events, and developments happening globally. Whether it's politics, business, technology, or culture, you can trust ELIAS MESERET to keep you informed and engaged. Join the channel today and stay ahead of the curve with the most accurate and unbiased news reporting. Don't miss out on any important stories - subscribe to ELIAS MESERET now!

ELIAS MESERET

29 Jan, 17:45


በዛሬው እለት የታጠቁ ግለሰቦች መቐለ ኤፍኤም 104.4 ሬድዮን ለመቆጣጠር ሙከራ አርገው ነበር ተባለ

(መሠረት ሚድያ)- በትግራይ ክልል ባለስልጣናት መሀል እየተካረረ የመጣውን ውዝግብ ተከትሎ በዛሬው እለት የታጠቁ ግለሰቦች የመቐለ ኤፍኤም 104.4 ሬድዮን ለመቆጣጠር ሙከራ አርገው እንደነበር ታውቋል።

ሙከራው የተካሄደው በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል በሚመራው ቡድን አባላት መሆኑን ምንጮቻችን ጠቅሰው ሙከራው ግን ያልተሳካ ነበር ብለውታል።

"ታጣቂዎቹን ወደ ሬድዮ ጣቢያው ይዞ የገባው በእነ ዶ/ር ደብረፅዮን የተሾመ ዘመንፈስ ቅዱስ ፍስሃ የተባለ ግለሰብ ነው" ያሉት ምንጫችን ድርጊቱ ሲከሽፍ የኤፍኤም ሬድዮ ጣቢያውን ማህተም ይዘው ሲወጡ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ጠቁመዋል።

ምን ያህል ታጣቂዎች ወደ ሬድዮ ጣብያው እንደገቡ እንዲሁም አላማቸው ምን እንደነበር እስካሁን የተገለፀ ነገር የለም።

መረጃን ከመሠረት!


@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

28 Jan, 19:42


ከሁለት ኢትዮጵያዊ አንዱ፣ ወይም 60 ሚልዮን ገደማው ኤሌክትሪክ አያገኝም

መንግስት 13 ሀገራትን በኤሌክትሪክ ለማስተሳሰር እየሰራ ነው።

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

26 Jan, 17:19


ከመንግስት ጋር ለመደራደር የተዘጋጀው የፋኖ ክንፍ ንግግሩ በአሜሪካ ወይም በአውሮፓ እንዲሆን ጠየቀ

(መሠረት ሚድያ)- ከሰሞኑ ታዛቢዎች በተገኙበት ከመንግስት ጋር ውይይት እንዳደረገ እና ለድርድር ዝግጁ እንደሆነ የገለፀው በእስክንድር ነጋ የሚመራው የፋኖ ክንፍ ድርድሩ በውጭ ሀገራት እንዲሆን እየጠየቀ መሆኑ ታውቋል።

የመሠረት ሚድያ ምንጮች እንደተናገሩት ታጣቂ ክንፉ ድርድሩ በአውሮፓ አልያም በአሜሪካ እንዲደረግ ቅድመ ሁኔታ አስቀምጧል።

መንግስት በዋናነት በእስክንድር ከሚመራው የፋኖ  ክንፍ  ጋር በቅርቡ በቴክኒክ ኮሚቴ ደረጃ እንደተወያየ እስክንድር ከኢትዮ 360 ጋር ባደረገው ቃለ መጠይቅ ገልፆ ነበር። አክሎም በድርድሩ ላይ የኢጋድ፣ የአውሮፓ ህብረት፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአሜሪካ ተወካዮች መገኘታቸውን ገልፆ ነበር።

በውይይቱ ላይ በፋኖ ክንፉ በኩል የተነሱ ነጥቦች መከላከያ አካባቢውን በግዜያዊነትም ቢሆን ለቆ መውጣት፣ ክልሉን ማስተዳደር፣ በፌደራል መንግስቱ በስልጣን መወከል፣ የድሮን ጥቃት ማቆም፣ ለተጎዳው ህዝብ ለህይወት ሳይቀር ካሳ መክፈል እና የመሳሰሉት ናቸው ተብሏል።

በመንግስት በኩል ደግሞ ትጥቅ በመፍታት ወደ ማሰልጠኛ መግባት፣ ጎጃም አካባቢ ላይ ያለውን ነገር ማስተካከል፣ በየከተማው ያለውን አደረጃጀት መረጃ መቀበል፣ ተጠያቂ የሚሆኑ አባላቱን አሳልፎ መስጠት እንዲሁም በምክክር ኮሚሽኑ ውስጥ መካተት ናቸው ተብሏል።

"በመንግስት ዝግ ስብሰባ ላይ ሲያጨቃጭቅ የነበረው የነእስክንድር ክንፍ አቅም ጉዳይ ሲሆን ግምገማውም በሀገር ውስጥና በውጭ ተቀባይነትን ለማግኘት መነጋገሩ እንደ  አማራጭ ተወስዷል" ያሉን ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቁ ምንጫችን ሸዋ ላይ ድርጅቱ የተሻለ አቅም እንዳለው፣ ነገር ግን ጎጃም ላይ የለም የሚባል ደረጃ ላይ እንደደረሰ መረጃ ቀርቦ ንግግር ተደርጎበታል ብለዋል።

"ቢያንስ ሸዋን ማቃለሉ እንደ ጥሩ እድል በመታየቱ እና የድርድር ዝርዝር መረጃም የሚቀበሉ አለም አቀፍ ተቋማትም በመንግስት የንግግሩ ቦታ ስለተጓጓዙ ውይይቱ ተደርጓል" በማለት ሂደቱን አስረድተዋል።

"ነገር ግን አሳሳቢው ጉዳይ አሁንም ልክ እንደነ ጃል ሰኒ እንዳይሆን ነው፣ ሙሉ ሰላም ለማምጣት የተወሰነ ቡድን ሳይሆን ሁሉንም አካታች መሆን አለበት" ያሉን ደግሞ በጉዳዩ ዙርያ አስተያየት የሰጡን ተንታኝ ናቸው።

"መንግስት ነገሮችን ያቀሉልኛል ብሎ እየሄደበት ያለው ይህ ነው። ሁሉም ወደ ንግግሩ መግባት አለበት፣ አልያ እንደ  ኦሮምያ አይነት ሁኔታ ይፈጠራል፣ ይባስ ብሎም በቀረው ፋኖ ታጣቂ እና በመንግስት መካከል የሚኖረው ሁኔታ ይባስ ሊካረር ይችላል" በማለት ለሚድያችን ተናግረዋል።

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

26 Jan, 06:57


#FactCheck የኢትዮጵያ ሰብዐዊ መብቶች ኮሚሽን በርካታ ታዳጊዎች ከመንገድ እየታፈሱ ወደ እርሻ ጣቢዎች በግድ እየተወሰዱ እንደሆነ መግለፁ ይታወቃል

"እርሻዎቹ የት ይሆኑ?" ብላችሁ ለጠየቃችሁ እና ማጣራት ለምትፈልጉ፣ ዋና መዳረሻው በሚድሮክ ሆራይዘን ፕላንቴሽን ስር የሚተዳደረው የበበቃ ቡና እርሻ ልማት ነው። "ሚድሮክ ፈቅዶ ነው ወይ ተገዶ ነው?" ለሚለው ምላሽ ቢሰጥበት ጥሩ ነው።

ሚድሮክ በዚህ ዙርያ አስተያየት እንዲሰጥ ደጋግሜ ብጠይቅም ምላሽ ከመስጠት ተቆጥቧል፣ ህዝብ ግን ልጆቹ የት እየተወሰዱ እንደሆነ የማወቅ መብት አለው።

በነገራችን ላይ ታፍሰው እየተወሰዱ ያሉት የጎዳና ላይ ልጆች ብቻ ሳይሆኑ እንደ ሊስትሮ፣ ፍራፍሬ መሸጥ፣ የጉልበት ስራ በመስራት፣ መኪና በማጠብ ወዘተ የሚተዳደሩ እና ቤተሰብ ያላቸው ልጆች ጭምር ናቸው።

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

25 Jan, 14:45


#የህዝብድምፅ ከህዝብ በጥቆማ መልክ ደርሰውን ትክክኝነታቸው የተረጋገጡ 5 መረጃዎች

1. የሲዳማ ክልል አስተዳደር በያዝነው ሳምንት የአፈር ማዳበሪያ ዋጋ ላይ ከ100 ፐርሰንት በላይ ጭማሪ አድርጓል፣ ይህም አርሶ አደሩን ከፍተኛ ስጋት ውስጥ ከቷል። ዳፕ ማዳበሪያ ከዚህ በፊት በኩንታል 3,980 ብር ሲሸጥ የነበረ ሲሆን ከነበረበት ባሳለፍነው ማክሰኞ በተወሰነው መሰረት ዋጋው እስ 8,047 ብር እንዲሆን ተደርጓል። "ምንም አይነት ገቢ የሌለው አርሶ አደር ለማዳበሪያ 8,074 ብር ከየት ያመጣል? ቢገዛ እንኳ ከምርቱ ምንን ሊያተርፍ ይችላል? የሚለው በጣም አሳሳቢ ጉዳይ እንደሆነባቸው ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።

2. የኢሚግሬሽን ባህር ዳር ቅርንጫፍ በርካታ ሰዎችን ለአሻራ እየቀጠረ ተስተናጋጆች ሲሄዱ "አዲስ አሰራር ስለመጣ ተቃጥሏል፣ ከእንደገና ለአዲስ 5,000 ብር እና የሚያስቸኩል ጉዳይ ካላችሁ ደግሞ 20,000 ብር ከፍላችሁ መመዝገብ ትችላላችሁ" እየተባሉ መሆኑን ለሚድያችን ጠቁመዋል። የከፈሉት ገንዘብ እና ያቃጠሉት ግዜን በተመለከተ ሲጠይቁም ምላሽ እንዳላገኙ ተናግረዋል።

3. በኦሮሚያ ክልል "ሚዛን ጀምረናል" በሚል ምክንያት ከ12 ሜትር ኪዩብ በላይ የሆኑ እንደ ሲኖ ያሉ መኪናዎች መንቀሳቀስ እንዳልቻሉ ታውቋል፣ ይህም የኮንስትራክሽን ግብዐት የሆኑት እንደ ጠጠር እና አሸዋ ዋጋቸው በእጅጉ እንደጨመረ መሠረት ሚድያ ሰምቷል። ይህ የሰሞኑ "ሚዛን" የተባለ አሰራር የተወሰኑ የአሸዋ እና ጠጠር አምራቾችን ለመጥቀም እንደሆነ የተናገሩት ምንጮች ከዚህም በተጨማሪ በየቦታው የኬላ ክፍያ እንዳሰለቻቸው ጠቁመዋል።

4. በሀዋሳ ከተማ የሚስተዋለው የቤንዚን እጥረት ተባብሶ መቀጠሉ ታውቋል። ማደያዎች አሁንም ቤንዚን መሸጥ ያቆሙ ቢሆንም አሽከርካሪዎች እስከ 300 ብር ከጥቁር ገበያ ከመግዛት እየተገደዱ መሆኑን ያስረዳሉ። "ብዙ ማደያ አለ፣ ነገር ግን ቤንዝን የለም። የሆነ ቀን አንዱጋ አለ ከተባለ አዳር ተሠልፈን ሳናገኝ እንበተናለን። በየመንገዱ ከየት እንደሚያመጡ የማይታወቁ አንድ ሊትር 300 ብር እየሸጡልን ነው" ብለው ነዋሪዎች ጠቁመዋል።

5. በመጨረሻም፣ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ለበዓል የወጡ በርካታ ወጣቶች የፋኖን ስም ጠርታችሁ ጨፍራችኋል ተብለው እየታደኑ በመታሰር ላይ እንደሚገኙ ታውቋል። ወጣቶቹ አሁን ላይ የታሰሩበት ቦታ እንደማይታወቅ የጠቆሙት ምንጮቻችን ቁጥራቸው በርካታ በመሆኑ ፖሊስ ጣብያ ስለማይችለው ምናልባት ወደ ወታደራዊ ካምፕ ተወስደው ሊሆን እንደሚችል ጠቁመዋል። "ሚካኤል ታቦቱ ወደ ማደሪያ ሲመለስ ጨፍራችሀል የተባሉት ወጣቶች እስከዛሬ ቀን ድረስ ታፍሰው የት እንደታሰሩም አይታወቅም፣ በየፖሊስ ጣቢያውም የሉም፣ በቁጥር በጣም ብዙ ናቸው" ያሉን በስፍራው ያሉ ምንጮቻችን ናቸው።

መረጃን ከመሠረት!



@EliasMeserett

ELIAS MESERET

25 Jan, 06:27


#መሠረትሚድያ

በጀት= 0 ብር

የሰራተኛ ብዛት= 1

በጎ ፈቃደኞች= 3

ተፅእኖ= 100 ፐርሰንት

ሁሌ እኮራለሁ!

መረጃን ከመሰረት


@EliasMeserett

ELIAS MESERET

23 Jan, 19:16


የትራንስፖርት ዋጋ መጨመር ያስከተለው ምስቅልቅል እና ምሬት

(መሠረት ሚድያ)- ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ፣ በተለይ ደግሞ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻ ከተደረገ ወዲህ የኑሮ ውድነት ተባብሶ ቀጥሏል።

የመገበያያ ዋጋቸው እጅግ እየጨመሩ ከመጡ ምርቶች አንዱ ነዳጅ ነው። የዛሬ ሁለት አመት በዚህ ወቅት ቤንዚን በሊትር 61 ብር ነበር፣ ነጭ ናፍጣ በሊትር 67 ይሸጥ ነበር፣ ኬሮሲንም በሊትር 67 ብር ነበር።

አሁን ላይ ቤንዚን 101 ብር ከ47 ሳንቲም ገብቷል፣ ናፍጣ ደግሞ በሊትር 98 ብር ከ98 ሳንቲም ሆኗል፣ በሌሎች የነዳጅ ምርቶች ላይም በትንሹ ከ8 ብር በላይ ተጨምሯል።

ታድያ የዚህ የነዳጅ ዋጋ ማሻቀብ የህዝብ ትራንስፖርቱ ዋጋም በእጅጉ እንዲያሻቅብ ምክንያት ሆኗል። በተለይ በተለይ በአዲስ አበባ ዳርቻ አካባቢዎች በሰፈሮችና በኮንዶሚኒየምዎች የሚኖሩ ዜጎች ለትራንስፖርት የሚያወጡት ወጪ እጅግ በጣም ጨምሮ ኑሮን እንዳከበደባቸው ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።

ለምሳሌ በኮዬ ፈጬ፣ በአራብሳ፣ በቂሊንጦ፣ በቱሉዲምቱ ወዘተ... የሚኖሩ ዜጎች ከነዚህ መኖሪያ መንደሮች እስከ መገናኛ እንኳን ለመድረስ በአውቶብስ 20 ብር፣ በታክሲ ደግሞ 50 ብር መክፈል ይጠበቅባቸዋል።

"ወቅታዊ ታሪፉ ደርሶ መልስ በአውቶቡስ 40 ብር፣ በታክሲ 100 ብር ነው መገናኛ ድረስ ብቻ። እኛ ግን አልፈን ሄደን መሀል ከተማ ነው የምንሰራው፣ ለትራንስፖርት ብቻ በቀን እስከ 130 ብር በትሹ እናወጣለን" በሚል አስተያየት የሰጡት እነዚህ ዜጎች ይህንንም ለማግኘት ብዙ ተሰልፈው እና ተንገላተው እንደሆነ ያስረዳሉ።

"ይሄ እጅግ በጣም ኑሮአችንን አክብዶብናል፣ ከአቅማችን በላይ ሆኖብናል። አቤቱታችንን በሚዲያችሁ አስተላልፉልን፣ የሚመለከተው አካል መፍትሔ ሊሰጠን ይገባል" የሚሉት እነዚህ ዜጎች የነዳጅ ድጎማ ቀስ በቀስ መነሳት ላልተጠበቀ እና እጅግ አቅምን ለሚፈታተን ከባድ ወጪ እንደዳረጋቸው በምሬት ይናገራሉ።

"በአንድ ቤት ውስጥ ብቻ ስራ ለመሄድ፣ ልጆችን ት/ቤት ለማድረስ እንዲሁም ሌሎች የቤተሰብ አባላትን እንቅስቃሴ ሳይጨምር ለአንድ ሰው  ይሄን ያህል ወጪ በቀን እያወጡ እንዴት መኖር ይቻላል?" በማለት አስተያየታቸውን በጥያቄ ቋጭተዋል።

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

21 Jan, 14:18


ከእዳ ወደ ምንዳ ወይስ ከእዳ ወደ እዳ?

የተቃርኖ ዘመን!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

21 Jan, 13:43


የትብብር ጥያቄ!

አቶ ገብረማርያም መለስ እድሜያቸው 85 ሲሆን ጥር 9/2017 ዓ/ም ከሰአት ላይ ጠፍተዋል፣ መጨረሻ የታዩበት ቦታ ወሰን 02 አካባቢ ነው። በሰአቱ ለብሰውት የነበረ ልብስ ጥቁር ጃኬት ነው፣ ከዘራም ይዘው ነበር። 

አቶ ገብረማርያምን ያየ ሰው በዚህ ስልክ ቁጥር ቢጠቁመን ብለው ቤተሰብ ተማፅኖ አቅርበዋል:

0920581054

ELIAS MESERET

19 Jan, 04:56


እንኳን ለደማቁ የጥምቀት በአል አደረሳችሁ፣ አደረሰን!

መልካም በዓል!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

17 Jan, 18:35


በጥምቀት በዓል መዳረሻ በርካታ ወጣቶች በአዲስ አበባ ከተማ እየታፈሱ መሆኑ ታወቀ

(መሠረት ሚድያ)- በአዲስ አበባ ከተማ በርካታ ስፍራዎች በተለይ በደማቁ የጥምቀት በአል ወቅት ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የሚታወቁ ወጣቶች እየታፈሱ መሆኑ ታውቋል።

መሠረት ሚድያ የደረሰው መረጃ እንደሚያሳያው እንደ ሽሮ ሜዳ፣ ፈረንሳይ፣ ካዛንችስ፣ ሳሪስ፣ አዋሬ ወዘተ ባሉ ስፍራዎች የሚገኙ ወጣቶች በብዛት በቁጥጥር ስር እየዋሉ ነው።

ሽሮ ሜዳ አካባቢ ትናንት ማታ ከ30 በላይ ወጣቶችን የሽሮ ሜዳ ፖሊስ አፍሶ እንደወሰዳቸው የአይን እማኞች ተናግረዋል። ወጣቶቹ የቤተክርስቲያን ጥምቀት አስተባባሪዎች እና ምንጣፍ የሚሸከሙ ልጆች መሆናቸው ታውቋል።

በሌላ በኩል በዛሬው እለት ሳሪስ አዲስ ሰፈር እና ብሄረ ፅጌ አካባቢ ለጥምቀት በአል የተሰቀሉ ማስዋቢያዎችን ፖሊስ በሀይል ያነሳ ሲሆን ሰቅላችኋል የተባሉ አንዳንድ ወጣቶችም እንደታሰሩ ታውቋል።

ከዚህ በፊት በየመንገዱ የሚሰቀሉ እና የኦርቶዶክስ አርማ ያለበት ባንዲራ ጭምር በፖሊስ በበርካታ ስፍራዎች እንዲወርድ እየተደረገ መሆኑን ሰምተናል።

ማምሻውን ከፖሊስ ምላሽ ለማግኘት ያረግነው ሙከራ አልተሳካም።

ፎቶ: ፋይል

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

17 Jan, 14:12


ኦሮሚያ ውስጥ ወታደሮች አንድ የሲቪል ልብስ የለበሰ ወጣትን እጁን ወደኋላ አስረው በጭካኔ ሲረሽኑ የሚያሳይ ቪድዮ ማህበራዊ ሚድያ ላይ ተለቋል

ቆይ፣ ይህ በቪድዮ የተቀረፀ ነው። እንዲህ ተቀርፆ ለህዝብ ያልደረሰ ምን ያህል ግፍ በየቀኑ ይፈፀማል?

ነፍስ ይማር ወንድሜ!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

17 Jan, 14:07


የመርካቶ ነጋዴዎች የተጠየቁትን ከፍተኛ ታክስ ቢከፍሉም ቦታቸው እንደሚወሰድባቸው እንደተነገራቸው ተሰማ

(መሠረት ሚድያ)- መርካቶ ከጣና ህንፃ ጎን በንግድ ስራ የሚተዳደሩ ነጋዴዎች ከዚህ ቀደም ራሳቸው ቦታው ላይ እንደሚያለሙ ተነግሯቸው እና ተደራጅተው እየተንቀሳቀሱ ባሉበት ወቅት ይህ በምስሉ ላይ የሚታየው ደብዳቤ ደርሷቸው ለስብሰባ መጠራታቸው ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።

ደብዳቤው በአዲስ አበባ መስተዳድር የመሬት ልማት ፅ/ቤት የተፃፈ ሲሆን ስፋታቸው 3,984 እና 14,466 ካሬ ሜትር የሆኑ እነዚህ መሬቶች ለመንግስታዊው የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ተላልፎ እንዲሰጥ የከተማው ካቢኔ መወሰኑን ይገልፃል። 

"የሚገርመው ነገር ከዚህ ቀደም ከነበረው ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ የሆነ ግብር እንድንከፍል ተደርገን እና ፍቃድ አድሰን እፎይ ስንል ይህ መሆኑ ነው" ይላሉ የሚሉት ነጋዴዎቹ ውሳኔውን እንደማይቀበሉ ገልፀው ፍትህ እንደሚሹ ተናግረዋል።

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

16 Jan, 15:54


የዘርፉ ባለሙያዎች አስረዱን!

ታሪካዊ ቅርስ ሲታደስ በዚህ መልኩ የቀድሞ መልኩን እስኪቀይር እንዲህ ይደረጋል? ወይስ አለም አቀፍ ተሞክሮዎችም ይህንኑ ያሳያሉ?

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

16 Jan, 13:34


ከጥቂት ሳምንታት በፊት መሠረት ሚድያ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የመንግስት ሰራተኞች ከስራቸው ሊቀነሱ እንደሆነ መረጃ አቅርቦ ነበር

መረጃው በወጣ በነጋታው የመንግስት ሀላፊዎች ተሯሩጠው "ውሸት ነው፣ አዲስ የፀደቀው የሰራተኞች አዋጅ ተቋማት ተልዕኳቸውን በብቃት እንዲፈፅሙ የሚያስችል ብቻ ነው" ብለው ነበር።

ዛሬስ?

እንደ አንበሳ አውቶቡስ አገልግሎት፣ ፖስታ አገልግሎት፣ የተለያዩ የክፍለ ከተማ ፅህፈት ቤቶች... ወዘተ በመቶዎች እና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ማሰናበት ጀምረዋል።

በዚህ ሳምንት ብቻ 450 የፖስታ አገልግሎት ሰራተኞች "በሪፎርም ምክንያት" በሚል ከስራቸው ተነስተው በሌሎች ተተክተዋል፣ ድርጊቱ በዘመድ፣ በእውቅ እና በብሄር ተለይቶ እንደሆነ ሰራተኞቹ ነግረውኛል።

አሁን በዚህ የኑሮ ውድነት የእነዚህ ሰራተኞች እና ቤተሰብ እጣ ምንድን ነው? ጎዳና ላይ መውጣት?

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

15 Jan, 18:48


ሀረር ከተማ መግቢያ ላይ ባለ ፍተሻ የኦሮሚያ መታወቂያ ያላቸው ሰዎች እየተለዩ እንዲመለሱ እየተደረጉ እንደሆነ ታወቀ

(መሠረት ሚድያ)- ካለፉት ጥቂት ቀናት ጀምሮ የሀረር መግቢያ ላይ በሚደረግ ፍተሻ ወቅት የኦሮሚያ ፖሊስ ልብስ የለሰቡ የፀጥታ አካላት የኦሮሚያ መታወቂያ ያላቸውን ሰዎች ለይተው እየመለሱ እንደሆነ ታውቋል።

መሠረት ሚድያ እየደረሰው ያለው መረጃ እንደሚያመለክተው ሰዎቹ ተመላሽ እየተደረጉ ያሉት ከሰሞኑ ካለው አፈሳ ጋር ተያይዞ እንደሆነ ይጠቁማል።

"ዛሬ በስራ አጋጣሚ ወደ ጅግጅጋ እየሄድኩ ሃረር ከተማ መግቢያ ላይ የኦሮሚያ ፖሊስ ለፍተሻ ካስወረደን በኋላ የኦሮሚያ ክልል ተወላጅ የሆኑትን ብቻ ከባስ አስወርደው ሲያስቀሯቸው ተመልክተናል" ያለው አንድ የአይን እማኝ በግምት 6 የሚሆኑ ፖሊሶች ድርጊቱን ፈፅመዋል ብለዋል።

"የተሳፈርነው ጊዎን ባስ ነበር፣ የሁላችንንም መታወቂያ ካዩ በኋላ የኦሮሞ ተወላጅ መታወቂያ ያላቸውን መሰብሰብ ጀመሩ። ልጆቹንም ለብቻቸው እንዲቆሙ አደረጓቸው፣ ከዛ እኛ ወደ ባሳችን ተመልሰን ስንገባ ወጣቶቹ ግን አልገቡም" ያለው ሌላ ምንጫችን ባስ ውስጥ ከነበሩት ጋር ሲነጋገሩ ከአፈሳ ጋር የተያያዘ ሊሆን እንደሚችል እና ልጆቹን ለስልጠና ፈልገው እንደሆነ ሰምተናል ብሏል።

ከሰሞኑ ኦሮሚያን ጨምሮ በበርካታ የሀገሪቱ ክፍሎች ወጣቶች ከመንገድ እና ከስራ ቦታ ጭምር ታግተው ተወስደው ወደ ወታደራዊ ካምፕ እየገቡ መሆኑን መሠረት ሚድያ በተደጋጋሚ መዘገቡ ይታወሳል።

ፎቶ: ፋይል

መረጃን ከመሠረት!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

15 Jan, 18:15


ኒያላ ኢንሹራንስ ከሰራተኞቹ ከፍተኛ ቅሬታ እና ክስ ቀረበበት

- "13.6 ሚልዬን ብር በቦነስ ስም ለድርጅቱ ስራ አስፈፃሚ ብቻ እንዲከፈል ተደርጓል"

(መሠረት ሚድያ)- ኒያላ ኢንሹራንስ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የህዝብ ሃብት ምዝበራ እና የመልካም አስተዳደር ችግር እንዳለ ሰራተኞች ለብሄራዊ ባንክ እና ለጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት በፃፏቸው ደብዳቤ ማሳወቃቸውን ሰምተናል።

በሃገሪቱ ካሉ እና በብሄራዊ ባንክ ፈቃድ አግኝተው በስራ ላይ ከሚገኙ 17 የኢንሹራንስ ኩባንያዎች ውስጥ የሚመደበው ድርጅቱ ከቅርብ ግዜ ወዲህ ከፍተኛ የሆነ የመልካም አስተዳደር ችግር እና ውንብድና በኩባንያው ከፍተኛ አመራሮች በተደጋጋሚ እየተፈፀመ የህዝብ ሃብት እና
ንብረት በማን አለብኝነት እየተመዘበረ ይገኛል ብለዋል።

ለዚሁ ማሳያ ይሆን ዘንድ ሰራተኞቹ የተለያዩ ማስረጃዎችን ለእነዚህ ሁለት አካላት እንዳሳወቁ መሠረት ሚድያ የደረሰው ሰነድ ያሳያል።

ለምሳሌ ኢትዮጵያ በሂሳብ አያያዝ እና አቀራረብ አዋጅ ቁጥር 847/2006 ዓ.ም መሰረት የአለም አቀፍ የሂሳብ አያያዝ (IFRS) ህግን ከ 2006 ዓ.ም ጀምሮ በይፋ ተቀብላ እየተገበረች ቢሆንም እ.ኤ.አ በ January 1, 2023 ጀምሮ ድርጅቱ በሂሳብ አመቱ እንዳልተገበረ በውጭ ኦዲተሮች ተረጋግጧል ብለዋል።

በሁለተኛነት የቀረበው አቤቱታ ደግሞ "ይህ በIFRS መርህ መሰረት ያልተዘጋጀ እጅግ የተጋነነ ትርፍ ተገኘ በማለት ባለአክሲዬኖችን እና ባለድርሻ አካላትን በማሳሳት በህገወጥ መንገድ እ.ኤ.አ በ 2023/24 አመት ብቻ የትርፍ ምጣኔ የተሰላ 3% የትርፍ ድርሻ 13.6 ሚልዬን ብር በቦነስ ስም ለድርጅቱ ስራ አስፈፃሚ ብቻ እንዲከፈል ተደርጓል" ይላል።

ከዚህም በተጨማሪ እ.ኤ.አ በ 2021/22 የበጀት አመት ብቻ የብሄራዊ ባንክ መመሪያ ቁጥር SB/46/2018 ለኩባንያው የቦርድ አባላት በአመት ሊከፈል የሚገባው ማንኛውም ክፍያ ከብር 150 ሺህ መብለጥ የለበትም ብሎ ቢደነግግም ይህን መመሪያ በሚፃረር መልኩ ከ6 ሚልየን ብር በላይ በቦነስ ስም ለኩባንያው ቦርድ አባል እንዲከፈል ተደርጓል ብለዋል።

"ለ20 አመታት በላይ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳንል በሰራንበት የኢንሹራንስ ሴክተር በቂም በቀል በሌሎች የኢንሹራንስ ኩባንያዎች ውስጥ ሰርተን እንኳን ቤተሰቦቻችንን እንዳናስተዳድር ሆነ ተብሎ የኢንሹራንስ ኩባንያዎቹ እኛን እንዳይቀጥሩ ከፍተኛ የስም ማጥፋት ዘመቻ እና ጫና እያሳደሩ ይገኛሉ። ይህ ደግሞ ህጋዊ ስራ ሰርቶ የመኖር ፣ በየትኛውም ቦታ ተዘዋውሮ የመስራት እና ንብረት የማፍራት ህገ-መንግስታዊ መብታችንን የሚጋፋ የማን አለብኝነት ድርጊት ነው" በማለት ቅሬታቸውን ለብሄራዊ ባንክ እና ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አስገብተዋል።

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

15 Jan, 17:07


ኢሚግሬሽን አላማው ለህዝብ አገልግሎት መስጠት ነው ወይስ ለትርፍ መስራት?

ኧረ የህዝብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን ሚና እንኳን እየለየን?!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

15 Jan, 16:15


አንዳንድ ግዜ እነዚህ እኔ ላይ ሲደረጉ የነበሩ ዘመቻዎችን መለስ ብዬ ሳስብ ይገርመኛል!

መንግስት በወቅቱ 'ታጋሽ' ሆኖ ይሁን እነዚህ የ 'እሰሩት' ጥሪዎች ውሸት እንደሆኑ ተገንዝቦ ባላውቅም እኔ ላይ አልደረሱም። የሚገርመው ደግሞ እነዚህ የውጭ ጋዜጠኞችን በአካልም፣ በኢሜይልም፣ ወይም በሌላ መንገድ አናግሬያቸው የማላውቅ ናቸው። አግኝቼ አስተርጓሚ ብጠቁማቸውም ምንም ችግር የሌለበት ትብብር ነበር።

ግዜ ደጉ፣ ይህን ለእኔ ሲመኙ የነበሩት አሁን የት ናቸው?

አንዱ ሳውዲ ለእስር ተዳርጎ፣ በቅርቡም ተላልፎ ተሰጥቶ ሀገር ቤት እስር ላይ ይገኛል። አንደኛው የጦርነት አራራው ወጥቶለት ይመስለኛል የስፖርት ተንታኝ ሆኗል።

ለሱሌማን አብደላ ሳይታሰር በፊት በአንድ ጉዳይ ሊያናግረኝ ደውሎ ስህተት እንደሰራ ነግሬ ለውሸቱ ወቅሼዋለሁ፣ አሁንም ትክክለኛ ፍትህ እንዲያገኝ እና ለቤተሰቡ እንዲበቃ እመኛለሁ።

#Karma

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

15 Jan, 14:17


ተቀጣሪ ወይም ነጋዴ ሆነህ ቤት ብትገነባ
- ከገቢህ 35% የገቢ ግብር
- የመሬቱ ሊዝ
- የጣራና ግድግዳ ግብር
- ለግንባታው የባንክ ብድር ወለድ
- በምትከፍለው እያንዳንዱ ትራንዛክሽን ባንክ ቻርጅና ቫት
- አሁን የንብረት ግብር
- በሁሉም ክፍያ ላይ ቫት
- ከሆነ ባለሥልጣን ጋር ከተነጃጀስክ ውርስ
- 30% ግሽበት
- ያለምክንያት መዋጮ
- ያለዕድሜህ ሽበት
- የማይቆም ጦርነት

=> መፍትሔ:- ባገኘኸው የትኛውንም safe መንገድ ስደት

Via Abdulkadir Hajj Nureddin

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

15 Jan, 13:58


የዛሬ 14 አመት>>> የህዳሴ ግድብን ጀምሮ ለማጠናቀቅ 80 ቢልዮን ብር ይፈጃል

ዘንድሮ>>> የግድቡ 97.6 ፐርሰንት ግንባታ ቢያልቅም ቀሪውን 2.4 ፐርሰንት ለመጨረስ 80 ቢልዮን ብር ያስፈልጋል

ይህ በራሱ መገበያያ ገንዘባችን ብር ምን ያህል እየወደቀ እንደሆነ ማሳያ ቢሆንም 2.4 ፐርሰንት ስራ ለመጨረስ ይህን ያህል ገንዘብ ያስፈለገበትን ምክንያት የሚመለከታቸው አካላት ለህዝብ በግልፅ ሊያስረዱ ይገባል።

Figures via Sheger FM

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

14 Jan, 05:00


ኦቪድ የተባለው ድርጅት የዛሬ አመት ገደማ በሸጣቸው ቤቶች ላይ ቅሬታ ያላቸው ቤት ገዢዎች ለመሠረት ሚድያ ተከታታይ መረጃ ሲልኩ ነበር

የቅሬታቸው መሰረትም ቃል በተገባላቸው መሰረት የቤቶቹ ግንባታ እየተካሄደ አይደለም የሚል ነበር፣ ለዚህም የሳይቶቹ የምስል እና የቪድዮ ማስረጃ አለ።

ይሁንና በዚህ ያልተደሰቱት ኦቪዶች ሁለት ነገር አደረጉ: አንደኛው የመሠረት ሚድያ ፕላስ (Meseret Media+) የዩትዩብ ቻናል ሞኒታይዜሽንን ሪፖርት አርገው አዘጉ፣ በሌላ በኩል እኔን አናገሩ።

ቻናሉን ማዘጋታቸው ትክክል እንዳልሆነ ነግሬያቸው (እንዳዘጉ የተናገሩበት የድምፅ ቅጂ/ሪከርድ ሙሉው አለ) በዜናው ላይ ማንኛውም አይነት ቅሬታ እና ትክክል አይደለም ብለው የሚያስቡት ነገር ካለ ላኩት እና አጣርተን ስህተት ከሆነ ሌላ የእርምት ዜና እንሰራለን አልኩ።

እሺ ተባብለን ከጨረስን በሗላ ግን "በአምስት ቀን ውስጥ የመረጃዎቻችሁን ምንጭ አምጡ፣ ወይም እንከሳለን" ብለው ማስፈራርያ መሰል 'ድንፋታ' በኢሜይል ላኩ 🙂

ማስፈራርያው መሠረት ሚድያ ላይ እና ኢትዮ ፎረም ላይ እንደሆነ በሶሻል ሚድያ ገፆቻቸው ፅፈው አየሁ።

የሚገርመው ዜናው መሠረት ሚድያ ላይ ከወጣ በኋላ ቤት ገዢዎችን ጠርተው መዘግየት የተፈጠረው በአዲሱ 'ሴት ባክ' ህግ ወዘተ እንደሆነ እና በቅርቡ ግንባታ እንደሚጀመር ራሳቸው ተናግረዋል።

ዜናው ውሸት ነው ብለው ካሰቡ ቀላሉ ማስረጃ በዜናው ላይ የተጠቀሱትን የጉለሌ እና የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ሳይቶቻቸውን በምስል እና ቪድዮ አስደግፈው አቅርበው የመሠረት ሚድያ ዜናን ውሸት ማጋለጥ ነበር፣ ግን አላረጉም።

ሁሉ በእጃቸው እና በደጃቸው የሆነ መስሏቸው ይሁን መንግስት አዲስ አበባ ሊያገኝ ያልቻላቸውን ጋዜጠኞች በዚህ በባለቤትነቱ ዙርያ ብዙ ህዝብ ጥያቄ በሚያቀርብበት ድርጅት በኩል ድምፅ ማፈን የሚችል መስሎት አይታወቅም ይህን ተግባር ፈፅሟል።

አንድ ነገር ማለት ይቻላል... በዚህ ዘመን የህዝብን እውነት እና የሚድያን ስራ ማፈን አይቻልም። የፈለገ ያህል ሀብት ያለህ የቢዝነስ ድርጅት ሁን፣ ቱባ ባለስልጣን ሁን።

You are selling properties to the public so you remain in the public eye, and no authority can silence criticism or dissenting voices.

The voice of the people cannot be suppressed!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

11 Jan, 16:09


ይህ በምስሉ ላይ የሚታየው ማጎርያ ካምፕ ከቃሊቲ ማሰልጠኛ ውሀ ልማት ጀርባ የሚገኝ ሲሆን በርካታ በዝቅተኛ ስራ የሚተዳደሩ ታዳጊዎች እና የጎዳና ተዳዳሪዎች እየታፈሱ የሚገቡበት ነው

መሠረት ሚድያ የዛሬ ሁለት ሳምንት በሰራው ዘገባው እድሜያቸው ከ15 አመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች ጭምር በየግዜው እየገቡበት እንደሆነ እና ካምፕ ውስጥ ከገቡ በኋላም ህይወታቸው ያለፈ እንዳሉ ጠቁሞ ነበር።

መንግስታዊው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ትናንት ባወጣው መግለጫው ድርጊቱ በቦታው እየተፈፀመ መሆኑን ያረጋገጠ ሲሆን ከጎዳና ላይ የተነሱ በርካታ ሰዎች መኖራቸውን እና ድርጊቱ አሁንም መቀጠሉን አረጋግጧል።

"ወደ ማቆያው ከገቡት ሰዎች መካከል በማእከሉ ከመቆየት እና የእርሻ ሥራ ከመሥራት እንዲመርጡ በማድረግ የእርሻ ሥራ ለመሥራት የመረጡ ሰዎች በተለያዩ አካባቢዎች ወደሚገኙ እርሻ ጣቢያዎች ተወስደው  እንዲሠሩ እንደሚደረግ ለመገንዘብ ተችሏል። ይህም የነጻነት መብታቸውን ጨምሮ ሌሎች መሠረታዊ የሰብአዊ መብቶቻቸውን የሚጥስ ነው" በማለት ኢሰመኮ አስታውቋል።

አሁን በደረሰኝ መረጃ መሰረት ከእነዚህ ዜጎች መሀል 3,700 የሚሆኑት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በአንድ የግል የቡና እርሻ ድርጅት ውስጥ በግዳጅ አምጥተው አስፈረዋቸዋል። ከእነዚህ የጎዳና ላይ ወጣቶች መሀል ህይወት ከብዷቸው አሁን ላይ እራሳቸውን ያጠፉ በርካቶች እንደሆኑ ታውቋል።

በዚህ ቃሊቲ ማሰልጠኛ አካባቢ ባለው ስፍራ ታስረው የተለቀቁ ዜጎች "መኝታ እና ምግብ ብሎ ነገር የለም፣ ጤነኛ ሆኖ የገባው ህይወቱ አልፎ ሲወጣ አይተናል" በማለት ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።

የእኔ ጥያቄ:

ህዝባዊ እና ሀይማኖታዊ በአላት ሲደርሱ፣ እንደ አፍሪካ ህብረት ያሉ ስብሰባዎች ሲካሄዱ፣ ከተሞች በልማት ሲፀዱ እንዲሁም ግጭቶች ሲከሰቱ ድሀውን ማህበረሰብን ለምን ይሰቃያል? ምን ያድርጉ?

የሚያሳዝነው አንድ ግለሰብ በቅርቡ "ፒያሳን አይታችሁታል? ኮተት ሁሉ ተጠራርጎ ወጥቶ እብድ ራሱ ጠፋ" ብሎ ማህበራዊ ሚድያ ላይ በተሰራጨ ቪድዮ ላይ ሲሳለቅ ነበር።

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

10 Jan, 20:02


ከሰሞኑ አንድ፣ ሁለት ወይም ሶስት የሚሆኑ በመንግስት የተሰሩ ስራዎች ትክክል መስለው ስለታዩኝ 'መልካም ነው' ብዬ ከመፃፌ አንዳንዶች 'ምን ነክቶህ ነው?' እና 'ተቀላቀልካቸው እንዴ?' የሚል መልእክት አድርሰውኛል 😊

ድሮም ሆነ አሁን አስተያየት፣ ጥቆማ እና ትችት የማቀርበው ሊጠቅም ከቻለ በሚል ነው... ጥቅም ሲሰጥም ስላየሁበት። የማቀርባቸው መረጃዎች ደግሞ ለሀገር እንደ አንድ የሚድያ ባለሙያ ግዴታ ከመወጣት እና ለህዝብ ድምፅ ከመሆን አንፃር ነው።

ከዛ ውጪ በትግራይ ይደርስ የነበረውን ግፍ ስፅፍ 'ጁንታ' የተባልኩት ግለሰብ ዛሬም በአማራ ክልል የሚደርሰውን ሰቆቃ ለህዝብ ሳቀርብ 'ጃዊሳ' እየተባልኩ ነው፣ አንድ ሰሞን በኦሮሚያ ሰላማዊ ዜጎች ተገደሉ የሚል ዜና ሰርቼ 'ሸኔ' የሚል ስም ተሰጥቶኝም ነበር። ስም ልጠፋው ስለለመድኩት እና ስለማይደንቀኝ አጠናክሮ መቀጠል ይቻላል። 

ነገር ግን እኔ እዛው የድሮ አቋሜ ላይ እገኛለሁ፣ የማንም ደጋፊ ወይም ተቃዋሚ አይደለሁም። ያለሁበት ይህ ቦታ ስለተመቸኝ ወደፊትም መገኛዬ እዛው ነው 📍

መልካም ምሽት።

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

10 Jan, 18:22


መሠረት ሚድያ ቃሊቲ አካባቢ ስለሚገኝ የወጣቶች ማጎርያ ካምፕ በቅርቡ ያወጣውን ዜና የሚያረጋግጥ መግለጫ ኢሰመኮ ሰጠ

(መሠረት ሚድያ)- መንግስታዊው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) መሠረት ሚድያ ታህሳስ 19/2017 ዓ/ም ቃሊቲ ማሰልጠኛ አካባቢ ስለሚገኝ የወጣቶች ማጎርያ ካምፕ ያወጣውን ዜና የሚያረጋግጥ መግለጫ ማምሻውን አውጥቷል።

ሚድያችን በዚህ ዘገባው በአዲስ አበባ ከቃሊቲ ማሰልጠኛ ውሀ ልማት ጀርባ በሚገኘው እና ምስሉ ላይ በሚታየው ማጎርያ ካምፕ ውስጥ እድሜያቸው ከ15 አመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች ጭምር በየግዜው እየገቡበት እንደሆነ ጠቁሞ ነበር።

ለውዝ አዟሪ፣ ሊስትሮ፣ የሀይላንድ እቃ ሰብሳቢ፣ መንገድ ላይ የሚለምኑ፣ የቀን ሰራተኞች ወዘተ መንገድ ላይ እየተያዙ ያለምንም ጥያቄ ተጭነው እየተወሰዱ እንደሚገኙም መረጃ አጋርተን ነበር።

ኢሰመኮ ዛሬ ባወጣው መግለጫው በታኅሣሥ ወር 2017 ዓ.ም. ባደረግኳቸው ክትትሎች በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ 'ቃሊቲ አካባቢ' ተብሎ በሚጠራው የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ሰፈር ባለ ሰፊ መጋዝን ውስጥ ከጎዳና ላይ የተነሱ በርካታ ሰዎች መኖራቸውንና ይህ ሰዎችን የመያዝና ወደ ማቆያ ማእከል/ቦታ የማስገባት ድርጊት አሁንም መቀጠሉን ተገንዝቤያለሁ ብሎ የመረጃውን እውነትነት አረጋግጧል፡፡

"ወደ ማቆያው ከገቡት ሰዎች መካከል በማእከሉ ከመቆየት እና የእርሻ ሥራ ከመሥራት እንዲመርጡ በማድረግ፤ የእርሻ ሥራ ለመሥራት የመረጡ ሰዎች በተለያዩ አካባቢዎች ወደሚገኙ እርሻ ጣቢያዎች ተወስደው  እንዲሠሩ እንደሚደረግ ለመገንዘብ ተችሏል። ይህም የነጻነት መብታቸውን ጨምሮ ሌሎች መሠረታዊ የሰብአዊ መብቶቻቸውን የሚጥስ ነው" በማለት ኢሰመኮ አስታውቋል።

አክሎም "በአዲስ አበባ ከተማ የሚከበሩ ሕዝባዊና ሃይማኖታዊ በዓላት፣ የሚደረጉ ዓለም አቀፋዊና አህጉራዊ ጉባኤዎች እንዲሁም ከሌሎች ተመሳሳይ ኹነቶች ጋር በተያያዘ ውሎና አዳራቸውን በጎዳና ላይ ያደረጉ ሰዎችን በኃይል በማንሳት በአንድ ስፍራ እንዲቆዩ የማድረግ አሠራር እንዲቆም፤ ወደመጡባቸው አካባቢዎች የመመለስ እና የመልሶ ማቋቋም ሥራዎች ሰብአዊ መብቶቻቸውን ባከበረ መልኩ ማከናወን እንደሚገባ እና ችግሩ ሁሉ አቀፍ የፖሊሲ ምላሽ የሚያስፈልገው መሆኑን በተለያዩ ጊዜያት በተካሄዱ የኢሰመኮ ክትትሎች ተጠቁሟል" ብሏል።

በዚህ ስፍራ ታስረው የተለቀቁ ዜጎች "መኝታ እና ምግብ ብሎ ነገር የለም፣ ጤነኛ ሆኖ የገባው ህይወቱ አልፎ ሲወጣ አይተናል" በማለት ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

10 Jan, 17:57


#GoodNews ዛሬ በይፋ ስራ የጀመረው የኢትዮጵያ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ (Ethiopian Securities Exchange) ትልቅ እምርታ ነው

ሩቅ ሳንሄድ እዚሁ ጎረቤት ሀገሮች እንኳን ዜጎቻቸው ለስቶክ ገበያ ክፍት የሆኑ ድርጅቶችን በግልፅ ገበያ ሼር በመግዛት እና በመሸጥ ይነግዳሉ፣ ያተርፋሉ፣ ኑሯቸውን ይገፋሉ።

የውጭም ሆነ የሀገር ውስጥ ኢንቨስተሮችን ለመሳብም ሁነኛ መንገድ እንደሆነ የሚታመንበት ይህ Securities Exchange በቅርብ ወራት 50 የሀገር ውስጥ ኩባንዎች ይካተቱበታል ተብሏል።

በአሜሪካ ሀገር እንዳለው Securities and Exchange Commission (SEC) ያለ ጥብቅ ቁጥጥር የሚያደርግ አካል ግን እንደሚያስፈልገው ግልፅ ነው።

አለበለዛ ገበያው በቀላሉ ሊጭበረበር እንደሚችል በቅርብ በሌላ ሀገራት የተከሰቱ እንደ Insider Trading,  Pump and Dump እና Ponzi Scheme ያሉ ወንጀሎችን ማየት ይቻላል።

በጅማሮው ተስፋ አድርገን መልካሙን ሁሉ ለተገበያዮች ተመኘን።

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

10 Jan, 09:44


ትናንት ምሽት በደቡባዊ ኢትዮጵያ ስለታየው ክስተት መረጃ ለማግኘት እንደ ናሳ፣ የአውሮፓ ስፔስ ኤጀንሲ፣ የሩስያ ጠፈር ድርጅት እና የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ ያሉ አካላትን ታግ በማድረግ እና ኢሜይል በመላክ ለማግኘት ሙከራ አድርጌ ነበር

የአውሮፓ ስፔስ ኤጀንሲ ከደቂቃዎች በፊት ምላሹን ያሳወቀኝ ሲሆን ክስተቱ የሰው ሰራሽ ጠፈር ስብርባሪ ወደ ምድር ንፍቀ ክበብ ሲመለስ የተፈጠረ መሆኑን አስታውቋል፣ ስብርባሪውም የቻይና ሺጂያን-19 መንኩራኩር ሊሆን እንደሚችል ጠቁሟል።

ሙሉ መረጃውን መሠረት ሚድያ ላይ ያገኙታል ⤵️

https://t.me/meseretmedia/765

ELIAS MESERET

10 Jan, 05:37


አሜሪካንን ታላቅ ሀገር ካደረጋት አንዱ ይህ የፖለቲካ ልምምዳቸው ነው

ምንም ያህል በፖለቲካው ቢጠላለፉ፣ ቢጠላሉ እና ቢጋጩ በሀገራዊ እና እንዲህ በግል ጉዳያቸው ላይ 'ለአሜሪካ ቅድሚያ' ብለው ይነሳሉ፣ የግል ፀባቸውን ያለዝባሉ እንዲሁም በህዝብ ዘንድ እንዲህ ይታያሉ። ይህ ምስል ትናንት በጂሚ ካርተር የሽኝት ፕሮግራም ላይ የተነሳ ነው።

እኛ ጋር ቢሆንስ?

በእውነት ያስቀናል።

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

09 Jan, 19:20


ዛሬ ከምሽቱ 1:30 ገደማ በደቡብ ኢትዮጵያ ባሉ በርካታ ዞኖች ይህ በቪድዮ ላይ የሚታየው ግዙፍ 'ነገር' ከሰማይ ላይ ሲወድቅ በአካባቢ ያሉ ሰዎች መመልከታቸውን እያሳወቁኝ ይገኛሉ

ምዕራብ ጉጂ ዲምቱ አካባቢ ያለ አንድ ነዋሪ "በጣም አስፈሪ የሆነ ግዙፍ ነገር ከሰማይ ሲወርድ ነበር፣ ግቢ ውስጥ ያለነው ሰራተኞች በግርምት ተሰባስበን ነው ያየነው። እየተቀጣጠለ ሚወርድ ነው ሚመስለው፣ ክስተቱ የሕዋ ከሆነም ብታጣሩልን" በማለት ገልፆታል።

ቪድዮው ላይ የሚትልየው ምን እንደሆነ የዘርፉ ባለሙያዎች ብታሳውቁን በሚል አጋራሁት።

በቅርብ ቀናት የጠፈር ስብርባሪ ኬንያ ውስጥ ባለ አንድ ገጠራማ ቦታ መውደቁ ይታወሳል።

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

09 Jan, 15:01


ምነው ጋሼ 😅

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

09 Jan, 11:41


በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ያሉ መምህራን፣ የጤና ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎች በርካታ የመንግስት ተቀጣሪዎች ደሞዝ ለወራት ሳይከፈላቸው ቀርቶ ለመንገድ ዳር ልመና እና ለጉልበት ስራ ጭምር የተዳረጉ እንዳሉ የሚደርሱኝ መረጃዎች ይጠቁማሉ

እዚህ ጋር ደግሞ በ3.5 ቢልየን ብር (ሚልየን አይደለም) የጢያ ትክል ድንጋይን ለማልማት እቅድ ወጥቶ ወደ ስራ እየተገባ ነው ይለናል ይሄ ዘገባ።

የቱሪዝም ሀብትን አልምቶ መጠቀም ይበል ያሰኛል፣ ግን ቅድሚያ የሚሰጠው የቱ ነው? ይሄ በመላው ሀገሪቱ የሚታየው ቅድሚያ የሚሰጠውን ነገር አለማወቅ ወይም ሆን ብሎ ማዛባት አይነተኛ ማሳያ ነው።

Misplaced priorities!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

09 Jan, 07:21


ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃባቸውን ለብሰው መማር መቻል አለባቸው

በአክሱም የሚገኙት እነዚህ ተማሪዎቹ እየጠየቁ ያሉት መብታቸውን ነው፣ ያውም ሀይማኖታቸው የሚያዛቸውን ለመፈፀም። ያለን መንግስት አለማዊ (secular) ነው፣ የሁሉንም ሀይማኖቶች መብት ያከበረ መሆን አለበት።

በዚህ ዙርያ የመሠረት ሚድያ ዘገባ ⬇️

"የአክሱም ከተማ ሙስሊም ነዋሪዎች ችግር እልባት ያልተሰጠበት እና ወደባሰ ሁኔታ እየሄደ ነው"--- የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት

(መሠረት ሚድያ)- የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የአክሱም ከተማ ሙስሊም ነዋሪዎች ለዘመናት የነበረባቸውን የእምነት ነፃነት፣ የመስገጃ ቦታ ችግር እና የቀብር ቦታ ችግር እልባት ያልተሰጠበት እና ወደባሰ ሁኔታ እየሄደ ነው አለ።

ምክር ቤቱ መግለጫውን ያወጣው በከተማው የሚገኙ ሴት ተማሪዎች ሂጃባቸውን አድርገው ትምህርት መከታተል እንዳልቻሉ ከሰሞኑ መሰማቱን ተከትሎ ነው።

"በዚህ ዘመን በጋራ እምነቶች ተከባብረው በሚኖሩበት አገር እሴቱን የሚሸረሽር ተግባር መፈፀሙን በፅኑ እናወግዛለን" ያለው ምክር ቤቱ የሙስሊሙ ማህበረሰብ መብቶች ሳይሸራረፉ ተግባራዊ እንዲደረጉ እና መንግስትም ይህን እንዲያስፈፅም ጥያቄ አቅርቧል።

መረጃን ከመሠረት!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

08 Jan, 16:29


ኢቢሲ ዛሬ ባስነበበው አንድ ዘገባው "... ኢትዮጵያ ነዳጅን በዝቅተኛ ዋጋ በመሸጥ ከአፍሪካ ሀገራት በ8ኛ ደረጃ፣ ከዓለም በ28ኛ ደረጃ ላይ ነች" የሚል መረጃ የሆነ ድረ-ገፅን ዋቢ አድርጎ አጋርቷል።

እውነታው ግን በእነዚህ ሀገራት ያሉ ዜጎች ከእኛ ጋር ለንፅፅር ሊቀርቡ አይችሉም፣ ምክንያቱም በብዙ እጥፍ የመግዛት አቅማቸው የተሻለ ነው።

ዜናው በገራሚነት እንደምሳሌ አሜሪካንንም ጠቅሷል፣ በአሜሪካ አንድ ሌትር ነዳጅ 0.897 ዶላር ሲሸጥ በኢትዮጵያ ደግሞ 0.805 ዶላር (ተመሳሳይ ሊባል የሚችል ነው)።

ታድያ ኢቢሲ በአሜሪካ ያለ ህዝብ ገቢው ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር አንድ ነው እያለን ይሆን? እንደ IMF መረጃ በአሜሪካ የነፍስ ወከፍ ገቢ 89,600 ዶላር ሲሆን በኢትዮጵያ ደግሞ 1,100 ዶላር ነው።

ለዛ ነው 'መንግስት' የሚባል አካል የህዝቡን የመግዛት አቅም አገናዝቦ ድጎማም ሆነ ሌላ ዋጋ መቀነሻ መፍትሄ የሚያበጀው። ለግዜው የተያዘው አካሄድ ግን 'በርካሽ እየሸጥን ነው' እያሉ ህዝቡን ማደንዘዣ መውጋት ነው።

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

06 Jan, 17:09


በጣም ያምራል፣

እንኳን ለገና በዓል አደረሳችሁ።

#የአእላፋትዝማሬ

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

06 Jan, 14:43


"አገር ከፖለቲካ ፓርቲዎች በላይ ናት"

አቶ ቡልቻ ደመቅሳን ለዜና ግብዐትነት በርካታ ግዜ የማነጋገር እድል ገጥሞኝ ነበር። ግልፅ እና ለቆሙለት አላማ የቻሉትን ያህል የሚሞግቱ ሰው ሰው የሚሸቱ ፖለቲከኛ ነበሩ።

በአንድ ወቅት ፓላማ ላይ "... እንዴት ኢትዮጵያ ይህን ያህል አደገች ይባላል?" ብለው ሲሞግቱ እንደተለመደው የፓርላማ አባሎች ግርርር ብለው ሲስቁ ብዙዎቻችን አይተናል።

እውነታው ግን እሳቸው እኛ የማናውቀውን አውቀው ስለነበር ነው ብዬ አስባለሁ፣ መረጃ በመንግስታት እንደሚቀነባበር ስለሚገባቸው። የአለም ባንክ የኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር ሆነው እ.አ.አ ከ1970- 1974 እንደሰሩ ልብ ይሏል።

ነፍስ ይማር!

Photo: Dagu

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

04 Jan, 16:58


በአዋሽ ፈንታሌ እና ሌሎች አካባቢዎች የሚገኙትን ወገኖች በመሬት መንቀጥቀጡ ምክንያት ሊከሰት ከሚችለው አደጋ ለማዳን በሚካሄደው እንቅስቃሴ ላይ የመከላከያ  ተሽከርካሪዎች በስፋት እየተሳተፉ እንደሆነ ታውቋል 🙏🏽

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

04 Jan, 16:15


የከሰም ስኳር ፋብሪካ በሚታየው መልኩ በመሬት መንቀጥቀጡ ተጎድቷል፣ ከ400 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር በላይ ውሀ የያዘው እና ለስኳር ፋብሪካው ግብአት የሚሆነውን የሸንኮራ አገዳ ለማልማት የተሰራው ግዙፉ የከሰም ግድብ ያለበት ሁኔታ ግልፅ አይደለም

የዛሬ ሶስት ወር ገደማ የፃፍኩትን መልሼ ላጋራው ⬇️

ከሰሞኑ ከሚያባንኑኝ ጉዳዮች አንዱ በቅርብ ቀናት አዋሽ አካባቢ የተከሰተው ርዕደ መሬት እና አያድርስ እና ከፍ ያለ መጠን ያለው መንቀጥቀጥ ቢከሰት በአካባቢው ያሉ ግድቦች ላይ መደርመስ አስከትሎ ዜጎች ላይ ሊያደርስ የሚችለው ጉዳት ነው።

በአካባቢው ያለው ግዙፉ የከሰም ግድብ ላይ ጉዳት ቢደርስ ሊለቀው የሚችለው ግዙፍ የውሀ መጠን በታችኛው ተፋሰስ ላይ ያሉ ዜጎችን ሊውጥ ይችላል።

"ግድቡ በክረምቱ ወቅት ግዙፍ የውሀ መጠን ይዞ ይገኛል፣ አደጋ ቢከሰት ሊያደርስ የሚችለውን ጉዳት ለማሰብ ይከብዳል" ያሉኝ አንድ ባለሙያ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች አሁንም ለአደጋው ተጋልጠው ይገኛሉ ብለዋል።

አደጋ ከደረሰ በኋላ "ብዬ ነበር" ማለት ወይም ከንፈር መምጠጥ ዋጋ የለውም፣ ስለዚህ ሌላው አለም ላይ እንደሚደረገው ቢያንስ ሁኔታው በደንብ እስኪጠና ተጋላጭ ወገኖችን ወደ ሌላ ቦታ ማስፈር ቢቻል እጅግ መልካም ነው። 

እባካችሁ የሚመለከታችሁ አካላት ትኩረት፣ ትኩረት፣ ትኩረት!

Photo: Tamiru Huliso

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

04 Jan, 05:14


የዚህ የመሬት መንቀጥቀጥ ጉዳይ እጅግ አሳሳቢ እየሆነ መጥቷል፣ ዛሬ ለሊት በሬክተር ስኬል የተመዘገበው 5.8 ደርሷል

መንግስት አሁን ላይ ከምንም በላይ ከፍተኛ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል፣ ሚድያው እና የሚመለከታቸው አካላት በአደጋ ወቅት ሊወሰዱ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች እና ዝግጅቶች ሊያስቡበት ይገባል።

ለረጅም ሳምንታት እየተከሰተ ስለቆየ ህዝቡ የተላመደው ይመስላል፣ ይህ አደገኛ ነው። ጥንቃቄ፣ ጥንቃቄ፣ ጥንቃቄ በዚህ ዙርያ መሠረት ሚድያ ከአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ አንድ ባለሙያ ጋር ቃለመጠይቅ አድርጎ ያቀርባል።።

ፈጣሪ ሀገራችንን እና ህዝባችንን ይጠብቅ!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

02 Jan, 17:10


ለቢሾፍቱ ኮሪደር ልማት እያንዳንዳቸው 1 ሚልየን ብር አምጡ የተባሉት ኤጀንቶች

(መሠረት ሚድያ)- በኦሮሚያ ክልል ቢሾፍቱ ከተማ ለሚገኙ ፋብሪካዎች እና ኢንደስትሪዎች ግብዐት በማቅረብ እና ምርት በመቀበል ስራ ላይ የተሰማሩ ድርጅቶች እና ኤጀንቶች ለኮሪደር ልማት የሚውል እያንዳንዳቸው 1 ሚልየን ብር እንዲያዋጡ መታዘዛቸው ታውቋል።

መሠረት ሚድያ የተመለከተው በከተማው ምክትል ከንቲባ አቶ ገዛኸኝ ደጀኔ የተፈረመ እና ለድርጅቶቹ የተሰጠ ደብዳቤ እንደሚጠቁመው በከተማው መስተዳድር እና በአየር ሀይል አስተባባሪነት ለሚካሄደው የኮሪደር ልማት ብሩን እንዲያዋጡ የተወሰነው መስከረም 11/2017 ነበር።

"እያንዳንዱ ኤጀንት 1 ሚልየን ብር ለመክፈል መስማማቱ እንደሚከፍል መስማማታችን ይታወቃል... ስለሆነም ሁሉም የየኢንደስትሪው ወይም ፋብሪካ ባለቤት ይህንን አውቃችሁ በስራችሁ የሚገኙትን ኤጀንቶች በእናንተ በኩል እንድታስከፍሉ በጥብቅ እናሳስባለን" የሚለው ደብዳቤው ገንዘቡ ገቢ የሚደረግበትን የአዋሽ ባንክ የአካውንት ቁጥር አስቀምጧል።

መሠረት ሚድያ ሐምሌ 2016 ዓ/ም ባቀረበው አንድ ዘገባው የቢሾፍቱ ከተማን 'በምስራቅ አፍሪካ የቱሪዝም ማዕከል' ለማድረግ እየተሰራ ካለው ስራ ጋር በተያያዘ በርካታ የከተማው ቦታ ለተባበሩት አረብ ኤምሬቶች (UAE) ባለሀብቶች ሊሰጥ እንደሆነ መረጃ አቅርቦ ነበር።

እነዚህ ነዋሪዎች "እስከ 80 ፐርሰንት የሚደርስ የከተማው ቦታ ለኤምሬትስ ኢንቨስተሮች ሊሰጥ ነው የሚል መረጃ አለ፣ በዛ ላይ ትንሽ የቤት እድሳት ለማድረግ እንኳን ስንሞክር በከተማው አስተዳደር 'እዚህ ብዙ ስለማትቆዩ ማደስ አትችሉም' እየተባልን ነው" ብለው ነበር።

ይህን በተመለከተ መሠረት ሚድያ የቢሾፍቱ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሀላፊ የሆኑትን አቶ ገብሬ ዳቢ አነጋግሮ "እኔ የከተማው ኢንቨስትመንት ቦርድ ውስጥ አባልም ነኝ፣ ግን በዚህ ደረጃ እንዲህ አይነት ኢንቨስትመንት ይመጣል የሚል መረጃ የለኝም" ብለው ተናግረው ነበር።

ነዋሪዎቹ ግን ትነሳላችሁ የሚለው ቃል ከመንግስት እስካሁን ባይወጣም ወደፊት ግን ሊነሱ እንደሚችሉ ስጋታቸውን ገልፀዋል።

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት አዲስ ባወጣው የከተሞች የተቀናጀ ፕላን ቢሾፍቱ ከተማን በሦስት ክፍለ ከተሞች እንዲሁም በአስር ወረዳዎች እንድትደራጅ ማድረጉ ይታወሳል፡፡

via Meseret Media


@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

31 Dec, 15:08


ባለሀብቱ በራቸው ላይ በተተኮሰባቸው ጥይት ተገደሉ

(መሠረት ሚድያ)- ታዋቂው የአክሰስ ኮም ኩባንያ ባለቤት እና የሸበል በረንታ ሲሚንቶ ፋብሪካ ስራ አስኪያጅ አቶ ቢረሳው ምናለ ትናንት ምሽት 1:30 ላይ ቤታቸው በር ላይ በጥይት ተመትተው እንደተገደሉ ታውቋል።

መሠረት ሚድያ የደረሰው መረጃ እንደሚጠቁመው ባለሀብቱ በለሚ ኩራ፣ ወረዳ ዘጠኝ 'አትሌቶች መንደር' መውረጃ አስፓልት አጠገብ በሚገኝ መኖሪያ ቤታቸው በር ላይ መኪና ውስጥ ሆነው የግቢው በር እንዲከፈት ክላክስ እያደረጉ ባሉበት ወቅት በጥይት ጥቃት ተፈፅሞባቸዋል።

"በሰዓቱ የአስፓልቱና የአካባቢው መብራት ጠፍቶ ነበር" የሚሉት የአካባቢው ነዋሪዎች በአካባቢው ምንም የፀጥታ አካል አልነበረም፣ በስፍራው የደረሱትም ነግቶ ነው ብለዋል።

የምስራቅ ጎጃም ቢቸና ወረዳ ተወላጅ የሆኑት እና የ 'ምናሉ ሆቴል' ባለቤት አቶ ቢረሳው የቀብር ስነስርዐት በዛሬው እለት በሳሊተ ምህረት ቤተክርስቲያን ተፈፅሟል።

መሠረት ሚድያ የአዲስ አበባ ፖሊስን በግድያው ዙርያ መረጃ የጠየቀ ሲሆን "መረጃው አልደረሰንም" የሚል ምላሽ አግኝቷል።


via Meseret Media


@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

26 Dec, 18:33


በአዲስ አበባ ከተማ የመንገድ ዳር አበባ እና ሳር ለማጠጣት የሚውለው የመጠጥ ውሀ በመሆኑ ህዝቡ መቸገሩ ታወቀ

(መሠረት ሚድያ)- በአዲስ አበባ ከተማ በተለይ በቅርብ ግዜያት ከተሰሩ የኮሪደር ልማቶች ጋር ተያይዞ ለተተከሉ የመንገድ ዳር አትክልትና ሳር ለማጠጣት የሚውለው ውሀ ለነዋሪዎች መጠጥ ከሚያገለግል የውሀ መስመር በመሆኑ ህዝቡ ውሀ መቸገሩ ታወቀ።

በኮሪደር ልማት ለተተከሉት አትክልትና ሳር ጠዋትና ማታ ውሀ የሚያጠጡት ተሽከርካሪዎች ለነዋሪው ለመጠጥ ከሚያገለግል የውሀ መስመር ሀይድራንቶች ላይ እንደሚቀዱ መሠረት ሚድያ ከአዲስ አበባ ውሀ እና ፍሳሽ ባለስልጣን ምንጮቹ አረጋግጧል።

ሀያ ሺህ ሊትር ገደማ የሚይዙ ትልልቅ ቦቴዎች ለመጠጥ ከሚውል የውሀ ሀይድራንቶች እየቀዱ አትክልት ማጠጣታቸው ወትሮም የውሀ እጥረት ላለባት ከተማ ፈተና እንደሆነ ታውቋል።

"በሳምንት አንድ ቀን ውሀ ሲያገኝ የነበረው የኮዬ ፈጬ ኮንዶሚኒየም እና ሌሎች ተመሳሳይ አካባቢዎች ያሉ ነዋሪዎች የውሀ ፈረቃቸው በሁለት ሳምንት አንዴ እየሆ ነው" ያሉት የመረጃው ባለቤት በእነዚህ ቦታዎች ያሉ ነዋሪዎች በውሀ እጥረት ክፉኛ እየተጎዱ ነው ብለዋል።

"ቤቶቹ የሽንት ቤቶቻቸው ሽታ ሳሎን አያስቀምጡም፣ የውሀ እጥረት ስላለ ፎቅ ላይ አይወጣም" ያሉን አንድ የኮዬ ፈጬ ነዋሪ "ስንት ወንዝ ባለበት ከተማ ከዛ ውሀ ቀድተው ለአትክልት መጠቀም ሲችሉ ነዋሪውን በውሀ ችግር ማሰቃየታቸው ሚያሳዝን ነው" ብለዋል።

Via meseret media

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

22 Dec, 04:56


Journalism is not just about speaking to those in power; it is about speaking truth to power ✊️

#Journalism

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

21 Dec, 13:22


የመንግስት ሚድያዎች የትናንቱን የአሜሪካ ኤምባሲ መግለጫ ዜና እንዳይሰሩ እንደተነገራቸው ታወቀ

(መሠረት ሚድያ)- አሜሪካ በሰሜን ወሎ ቡግና ወረዳ ለተከሰተው ድርቅ እና የምግብ እጥረት ምግብ እየተላከ መሆኑን አዲስ አበባ በሚገኘው ኤምባሲዋ በኩል በትናንትናው እለት ያሳወቀችበትን መረጃ የመንግስት ሚድያዎች እንዳይዘግቡ እንደተነገራቸው ታውቋል።

በሁለት የተለያዩ የመንግስት ሚድያዎች ውስጥ የሚሰሩ የሚድያ ባለሙያዎች ስማችን አይጠቀስ ብለው ለመሠረት ሚድያ እንደተናገሩት "ከላይ በመጣ ትእዛዝ" የአሜሪካ ድጋፍ ማድረግ እንዳይዘገብ ትእዛዝ ተላልፏል።

"ዜናውን መስራት ጀምረን ነበር፣ በኤዲተራችን በኩል ግን ተዉት ተብለናል" ያለው አንደኛው ምንጫችን ጉዳዩ "የመንግስትን የሰብል ምርት ስኬት ያኮስሳል" ተብሎ እንደተነገረው ገልጿል።

ሌላኛው ጋዜጠኛ ደግሞ "ጉዳዩ ለሀገር ገፅታ አንፃር ይቅር" እንደተባለ ተናግሯል።

የአሜሪካ ኤምባሲ ትናንት በኦፊሴላዊ የፌስቡክ ገፁ እንዳስታወቀው በወረዳው ድርቅ እንደተከሰተ ከሰሞኑ እየወጡ ያሉ ሪፖርቶች ላይ ክትትል አድርጌያለሁ ብሏል።

"የኢትዮጵያ ህዝብን ለመደገፍ አጋሮቻችን ምግብ እና አልሚ ምግቦችን ወደተጠቁት ስፍራዎች እየላኩ ነው" ያለው ኤምባሲው ሁኔታውን በቀጣይም በመከታተል ችግሩን ለመቅረፍ እንደሚሰራ አስታውቋል።

መሠረት ሚድያን ጨምሮ አንዳንድ ሚድያዎች ከሰሞኑ በሰሜን ወሎ ቡግና ወረዳ ስለተከሰተው ድርቅ ሲዘግቡ ቆይተዋል።

በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የምግብ እጥረት እንዳጋጠማቸው እና በርሀብ እጅግ የተጎዱ ህፃናት ምስልም በማህበራዊ ሲዘዋወር ነበር።

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

20 Dec, 19:40


"ከ30 ሺህ ብር እስከ 250 ሺህ ብር የሚያወጣ ዲም ላይት ገዝታችሁ ህንፃችሁን አስውቡ ተብለናል"--- የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች

(መሠረት ሚድያ)- በሀዋሳ ከተማ እየተካሄደ ከሚገኘው የኮሪደር ልማት ጋር በተያያዘ እጅግ ከፍተኛ ወጪ የሚያስወጡ ዲምላይት/መብራቶችን ገዝተው ህንፃዎቻቸው እና ቤታቸው ላይ እንዲገጥሙ መታዘዛቸውን ነዋሪዎቹ ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።

በከንቲባው አቶ ሙኩሪያ መርሻዬ ጭምር በቀጥታ ስልክ እየተደወለ ማስጠንቀቂያ እየደረሳቸው እንደሆነ የተናገሩት ነዋሪዎች ከኑሮ ውድነት እና ከስራ መቀዝቀዝ ጋር ተደምሮ ግራ በመጋባት ላይ እንዳሉ ጠቁመዋል።

"በህንፃዎች ዙሪያ የመብራት መስመሮች ወይም ዲምላይት ለመዘርጋት በትንሹ እስከ 30 ሺህ ከዚያም በላይ እስከ 250 ሺህ ወጪ ይጠይቃል" የሚሉት ነዋሪዎቹ በተጨማሪውም ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ዲምላይት ማብራት እንዳለባቸው የመንግስት አካላት ሲያስጨንቁን ይውላሉ ብለዋል።

በሌላ ዜና ቢሾፍቱ ላይ የግዳጅ በሆነ አካሄድ ነዋሪዎች የግቢያቸውን አጥርም ሆነ ግንብ ነጭ ቀለም እንዲቀቡ መታዘዛቸው ታውቋል። ቀለም ገዝቶ መቀባት ያቃታቸው ነዋሪዎች ኖራ ገዝተው በመቀባት ከቅጣት ለማምለጥ እየሞከሩ እንደሆኑ ጠቁመዋል።

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

20 Dec, 16:39


Thank you, America!

የእነዛ በርሀብ የተጎዱ ምስኪን ህፃናት ምስል ከአእምሮ አይጠፋም።

https://t.me/Eliasmeserett/990

ELIAS MESERET

20 Dec, 16:36


አሜሪካ በሰሜን ወሎ ቡግና ወረዳ ለተከሰተው ድርቅ እና የምግብ እጥረት ምግብ እየተላከ መሆኑን አስታወቀች

(መሠረት ሚድያ)- አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ቡግና ወረዳ የተከሰተውን ድርቅ እና የምግብ እጥረት ተከትሎ እርዳታ ወደ ስፍራው እየተላከ መሆኑን አስታውቋል።

ኤምባሲው በኦፊሴላዊ የፌስቡክ ገፁ እንዳስታወቀው በወረዳው እንደተከሰተ ከሰሞኑ እየወጡ ያሉ ሪፖርቶች ላይ ክትትል አድርጓል።

"የኢትዮጵያ ህዝብን ለመደገፍ አጋሮቻችን ምግብ እና አልሚ ምግቦችን ወደተጠቁት ስፍራዎች እየላኩ ነው" ያለው ኤምባሲው ሁኔታውን በቀጣይም በመከታተል ችግሩን ለመቅረፍ እንደሚሰራ አስታውቋል።

መሠረት ሚድያን ጨምሮ አንዳንድ ሚድያዎች ከሰሞኑ በሰሜን ወሎ ቡግና ወረዳ ስለተከሰተው ድርቅ ሲዘግቡ ቆይተዋል።

በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የምግብ እጥረት እንዳጋጠማቸው እና በርሀብ እጅግ የተጎዱ ህፃናት ምስልም በማህበራዊ ሲዘዋወር ነበር።

መረጃን ከመሠረት!

via Meseret Media

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

19 Dec, 18:01


"ጠንካራ ዲፕሎማሲ... " ብሎ ለኮመተ ክፍያ ተጀመረ እንዴ?

አንዳንዴ እኮ አንሰማም፣ የሰማችሁ አሳውቁን።

#የሚድያሰራዊት

Via Inbox

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

19 Dec, 14:08


አቶ ሰርፀ ፍሬስብሀት ከንቲባ አዳነች አቤቤ በፃፉት ደብዳቤ ከስራቸው ተሰናበቱ

(መሠረት ሚድያ)- የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የባህል፣ ኪነጥበብ እና ቱሪዝም ቢሮ የኪነጥበብ ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሀላፊ ሆነው ላለፉት ስድስት አመታት ያገለገሉትን አቶ ሰርፀ ፍሬስብሀትን ከስራቸው ማሰናበታቸውን መሠረት ሚድያ የደረሰው መረጃ ያሳያል።

አቶ ሰርፀ ከስራቸው የተነሱት በከንቲባዋ ህዳር 23/2017 ዓ/ም በተፃፈ ደብዳቤ ሲሆን ምክንያቱ ግን በደብዳቤ ላይ አልተገለፀም።

ይሁንና ሚድያችን ከውስጥ አዋቂዎች የደረሰው ተከታታይ ጥቆማ እንደሚያሳየው ጉዳዩ በከተማ አስተዳደሩ ሊደረግ ከታሰበው የሰራተኛ ቅነሳ ጋር የተያያዘ ነው።

በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ባህልና ቱሪዝም ስር በሚገኙት 4 ቴአትር ቤቶች ማለትም የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ፣ አገር ፍቅር፣ ራስ ቴአትር እና ሕጻናትና ወጣቶች ቴአትር በስራቸው 800 ሰራተኞች አሉ።

ከእነዚህ ሰራተኞች 50 ከመቶው እንዲቀነሱ እንደተወሰነ የደረሰን መረጃ የሚጠቁም ሲሆን በምትካቸው ማለትም 50 ከመቶ የሚሆኑ ከተለያዩ የክልል አካባቢዎች በመጡ ሰዎች በቴአትር ቤቶቹ ምደባ ተከናውኗል ተብሏል።

ይህን ውሳኔ ያልተቀበሉ ላይ ወይም ተቃውሞ ያሰሙ ሰዎች ላይ ከስራ የማንሳት እርምጃ እየተወሰደ እንደሆነ የታወቀ ሲሆን የአቶ ሰርፀ ጉዳይም ከዚህ ጋር የተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ተጠቁሟል።

ሚድያችን ከሰሞኑ በተደጋጋሚ በሰራዎች ዘገባዎቹ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የመንግስት ሰራተኞች በቅርቡ ከስራ ሊቀነሱ እንደሆነ መዘገቡ ይታወሳል።

Via meseret media


@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

17 Dec, 13:20


የበርካታ ባለሐብቶች የባንክ ሂሳብ እየታገደ እንደሆነ ታወቀ

(መሠረት ሚድያ)- በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የተሻለ ቢዝነስ ያንቀሳቅሳሉ የሚመባሉ የበርካታ ባለሐብቶች የባንክ ሂሳብ እየታገደ እንደሆነ ታውቋል።

እነዚህ በአብዛኛው የአማራ ተወላጅ የሆኑ ባለሀብቶች እየተመረጡ ተንቀሳቃሽ ሒሳባቸው በህግ እየታገደ ወይም Legal Restriction እየተደረገባቸው እንደሆነ የባንኮች ምንጮቻችን ተናግረዋል።

መሠረት ሚድያ ባደረገው ማጣራት በአማራ ክልል ከቀጠለው ግጭት ጋር በተያያዘ ለታጣቂዎች ድጋፍ ሊያደርጉ ይችላሉ የተባሉ ሁሉ 'ከላይ በመጣ ትእዛዝ) በሚል በጥርጣሬ ባንካቸው እየታገደባቸው ይገኛል።

ንግድ ባንክ ላይ ብቻ ቢያንስ 200 የሚሆኑ የእነዚህ ባለሀብቶች አካውንቶች እንደታገዱ ታውቋል፣ የግል ባንኮች ላይ በተመሳሳይ ቁጥራቸው ያልታወቀ እገዳዎች መደረጋቸው ታውቋል።

"አብዛኞቹ የፍርድ ቤት እግድ እንኳን የሌለባቸው ናቸው፣ በጥርጣሬ በሚል በርካታ አካውንቶች ተዘግተዋል" ያሉት ምንጫችን ሁኔታው የዛሬ ሶስት እና አራት አመት በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ወቅት የትግራይ ባለሀብቶች ላይ ከተደረገው ጋር ተመሳሳይነት አለው ብለዋል።

ሚድያችን በዚህ ዙርያ አካውንታቸው የታገደባቸውን አንድ ነጋዴ እነጋግሯል።

"አካውንቱ መታገዱን የሰማሁት ከቢሮዬ ተደውሎ ክፍያ መፈፀም አልቻልንም ሲሉኝ ነው" የሚሉት እኚህ ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ ነጋዴ ወደ ንግድ ባንክ ሄደው ሲያጣሩ "ለግዜው እንቅስቃሴ እንዳያደርግ እግድ ተጥሎበታል ተባልኩ፣ ሌላው ቀርቶ በወረቀት ላይ የተፃፈ ማብራርያ ወይም ለእግዱ ማረጋገጫ አልሰጡኝም" በማለት አስረድተዋል።

በተመሳሳይ እርሳቸው የሚያውቋቸው የአራት የአማራ ተወላጅ የቢዝነስ ባለቤቶች አካውንታቸው እንደታገደባቸው እንደሰሙ ጠቅሰው ወንጀል ባልፈፀሙበት እና ክስ እንኳን ባልቀረበበት ጉዳይ ለ40 አመት የሰሩበትን የንግድ ስራ እንዲያቆሙ እንደተገደዱ ተናግረዋል።

በጉዳዩ ዙርያ ከብሄራዊ ባንክም ሆነ ከሌላ የመንግስት አካል የተሰጠ መግለጫም ሆነ ማብራርያ የለም።

via መሰረት ሚዲያ

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

17 Dec, 13:01


አሁን ድረስ የቀጠለው በቦሌ አየር ማረፊያ መንገደኞች ላይ የሚፈፀሙ እንግልቶች እና የሙስና ተግባሮች

(መሠረት ሚድያ)- በቦሌ አየር ማረፊያ በኩል የሚገቡ እና የሚወጡ መንገደኞች ላይ የሚደርሱ እንግልቶች እና የሚፈፀሙ የሙስና ወንጀሎች እንደቀጠሉ ናቸው።

ለማሳያነት ለመሠረት ሚድያ የደረሰው የአንዲት መንገደኛ አዲስ አቤቱታ እንደሚያሳየው ህዳር 16/2017 ዓ/ም ከአዲስ አበባ ወደ ዋሽንግተን በነበረ በረራ ተሳፋሪ የነበረች አንዲት መንገደኛ 400 ዶላር በግዴታ እንድትከፍል ተደርጋለች።

መንገደኛዋ የማታ በረራውን ለማድረግ በአየር ማረፊያው በተገኘችበት ወቅት የበረራ አስተባባሪዎቹ በግልፅ አራት መቶ ዶላር ካላመጣች መብረር እንደማትችል እንደነገሯት እና እሷን ከጉዞዋ ላለመስተጓጎል ክፍያውን እንደፈፀመች ታውቋል።

መንገደኛዋን ዶላሩን ካልከፈለች ልትታሰር እንደምትችል ሲነግሯት እርሷም "ምን አጥፍቼ ነው የምታሰረው?" ብላ ስትሞግት ምንም ሳይፈሩ "እናስርሻለን፣ ማንም አያድንሽም" እንዳሏት ታውቋል።

በመጨረሻም በረራው እንዳያመልጣት በመፍራትና ከህገወጥ እስር ለመዳን ስትል ከፍላ ወደ አሜሪካ መመለሷ ታውቋል።

በተመሳሳይ መልኩ የዛሬ አመት አንዲት ተጓዥ ወደ አየር ማረፊያ ለአሜሪካ ጉዞ በሄደችበት ወቅት "የያዝሽውን ብር እና ወርቅ አካፍዩን" ተብላ እንደነበር ማህበራዊ ሚድያ ላይ መረጃ መውጣቱን ተከትሎ በካሜራ የታገዘ ማጣራት ተደርጎ ሁለት የኤርፖርት ሰራተኞች በቁጥጥር ስር ውለው እንደነበር ይታወሳል።

ይህን ተከትሎም የመንገደኞች የቅሬታ ማቅረቢያ ስርዐት ተዘርግቶ ለችግሩ ተገቢው ትኩረት እንደተሰጠው ተገልጾ ነበር።

ጉዳዩ የውጭ ተጓዦችን ብቻ ሳይሆን አሁን አሁን የሀገር ውስጥ መንገደኞችንም እያጉላላ እንደሆነ መሠረት ሚድያ በቅርቡ ተመሳሳይ መረጃ ማቅረቡ ይታወሳል።

በቅርቡ በሰራነው አንድ ዘገባችን ከጎንደር የመጣ አንድ ተጓዥ አዲስ አበባ ቦሌ አየር ማረፊያ ተይዞ የጉቦ ገንዘብ አምጣ ተብሎ አልከፍልም በማለቱ ሁለት ቀን ኤርፖርት ግቢ ውስጥ ባለ አንድ ፖሊስ ጣብያ ታስሮ እንደተለቀቀ መረጃ አቅርበን ነበር።

በተያያዘ ዜና የኤርፖርት እና ድንበር አስተዳደር ትራንስፎርሜሽን ፕሮግራም ስርዓት የትብብር ስምምነት ከአራት ቀን በፊት መፈረሙ ታውቋል። ስምምነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያለውን ታላቅ ስምና ዝና ለማስቀጠል እንዲሁም የድንበር ደህንነትን ይበልጥ ለማሳደግ ያስችላል ተብሏል።

የስምምነቱ ዋነኛው ምክንያት የኢትዮጵያ አየር መንገድን ክብርና ዝና ማስቀጠል መሆኑ የተለፀ ሲሆን ይህም በቅርብ ጊዜያት አየር ማረፊያው ላይ የሚፈፀሙ የህገወጥ ድርጊቶች መበራከት አንዱ ምክንያት እንደሆነ ታውቋል።

via Meseret Media

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

17 Dec, 04:00


1. "30 አመት ውጪ ሀገር ታክሲ እየሰራህ እዚህ መጮህ አይቻልም..."

2. "ዛሬ የአሜሪካንን ድሪም ኢትዮጵያ ውስጥ መኖር ችለናል..."

... አለ አፍሪካን የሚወክል ሚድያ አዲስ አበባ ላይ ላቋቁም ነው ብሎ ከመንግስት በተሰጠው ሁለት ሰፋፊ ቦታ ከባድ ጆካ የተጫወተው ወንድማችን... አሜሪካን ሀገር Seattle ከተማ ላይ ደግሞ የገዛውን ጭውቴ እናውቃለን።

#የዛሬይቱኢትዮጵያ 

በሰፊው እመለስበታለሁ...

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

16 Dec, 18:54


የቀድሞው ምክትል ጠ/ሚር አቶ ደመቀ መኮንን አፍሪካ ውስጥ ያሉ ህፃናትን መቀንጨር የሚከላከል ድርጅት እንዳቋቋሙ ዛሬ ሰማን

ድርጅታቸው ለግዜው አፍሪካን ትቶ እሳቸው የወጡበት የአማራ ክልል ውስጥ እንዲህ በርሀብ እየተጎዱ ያሉ ህፃናት ላይ ትኩረት ቢያደርግ እላለሁ።

ይህ የ1977 ድርቅ ሳይሆን አሁን ላይ የኢትዮጵያ ህፃናት ምንም በማያውቁት እያለፉበት ያለ ስቃይ ነው፣ አንዳንዱ ህዝባችን ደግሞ "ጦርነት አቁሙ በሏቸው፣ ወይም ርሀቡ ይቀጥላል" እያለ በህፃናቱ መሳለቅ ይዟል።

እንደ ህዝብ መጨረሻችን ይህ መሆኑ ያሳዝናል።

Photo: Belay Manaye

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

16 Dec, 18:11


በተለይም አሁን አገራችን በምትገኝበት እጅግ የተመሰቃቀለ  ውስጣዊ ሁኔታ ይህንን ውሳኔ መወሰን እንዝላልንት ነው::

የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምም አደጋ ላይ የሚጥል እንጂ የሚያስከብር እንደማይሆን እሙን ነበር:: ሄዶ ሄዶ እንዳየነው የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በተለይም የGCC እና የአረብ ሊግ አባላት ስምምነቱን ከመነሻው ነበር የተቃወሙት። መንግስት ከሱማሊያም ጋር የተካረረ አለመግባባት ውስጥ ገባ።

በአጠቃላይ የኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ ዓለም አቀፍ ውግዘትን አስተናገደ ። በመጨረሻም በቱርክ አንካራ በብዙ ጫና  የሱማሊያን ግዛታዊ አንድነት ለማክበርና አጨቃጫቂ ጉዳዮችን ላለማንሳት ተስማማ። ይህም ሱማሌላንድን እንደ አገር ለመቆጠር ከተፈራረመው የቀድሞ መግባቢያ ሰንድ ጋር በቀጥታ ስለሚቃረን የቀድሞውን ስምምነት ዋጋ አልባ ያደርገዋል።

(በነገራችን ላይ ቱርክ በሶማልያ የአገር ውስጥ ፖለቲካም የሶማልያን የማዕከላዊ መንግስት በመደገፍ የምትታወቅ እና ከሶማሊላንድ ጋርም በጥርጣሬ የተሞላ ግንኙነት ያላት አገር ናት)።

እነዚህ ከላይ ለማሳያነት ያነሳዃቸው አበይት ጉዳዮች የዲፕሎማሲያችን አሁናዊ ቁመና በትንሹም ቢሆን ያሳያሉ የሚል እምነት አለኝ። ትንሽ የዲፕሎማሲ ስህተት ትልቅ ብሔራዊ ጥቅም ያሳጣል። የብሔራዊ ጥቅም መነካት ደግሞ ወደ ለየለት ጦርነት ያስገባል። 

በመሆኑም ኢትዮጵያ ተለዋዋጭ የሆነውን የቀጠናውን እና  ዓለማቀፋዊ ሁኔታውን የዋጀ በሳል ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መመስረት ከምን ጊዜውም በላይ ያሻታል። ተቋማት ከአደርባይ ካድሬዎች ይልቅ በሙያተኞች ይጠናከሩ ። መሪዎችም ቢያንስ ለአገርና ለስማቸው ሲሉ ሙያተኛን ይስሙ። ጉዳዩ የአገር ልኡዋላዊነትና ህልውና ነውና!

*** የፅሁፉ ባለቤት አቶ ቢንያም እሸቱ ናቸው። አቶ ቢንያም የቀድሞው የጠ/ሚር ልዩ ጽ/ቤት ባልደረባ የነበሩ ናቸው። ለአስተያየታቸው መሠረት ሚድያ ከፍ ያለ ምስጋና ያቀርባል።

በዚህ አጋጣሚ ለአቶ ቢንያም እሸቱ ምላሽ የሚሆን ወይም የተቃርኖ ሀሳብ ያለው የመንግስት ተቋምም ሆነ አመራር ካለ ፅሁፉን ለማስተናገድ በራችን ክፍት መሆኑን ለመግለፅ እንወዳለን።


via MeseretMedia

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

16 Dec, 18:11


#አስተያየት "ኢትዮጵያ ተለዋዋጭ የሆነውን የቀጠናውን እና  ዓለማቀፋዊ ሁኔታውን የዋጀ በሳል ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መመስረት ከምን ጊዜውም በላይ ያሻታል"--- አቶ ቢንያም እሸቱ

(መሠረት ሚድያ)- አገራት ከፍተኛ ውጥረት እና ፉክክር በተሞላበት ዓለም አቀፋዊ ሁኔታ ውስጥ ብሔራዊ ጥቅማቸውን ለማስጠበቅ የሚያስችሉ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶችንና አጋርነቶችን መመስረት የግድ ይላቸዋል። ማንኛውም አገር ከዓለም አቀፉ ስርዓት ተነጥሎ ሊኖር   አይችልምና!  

ዲፕሎማሲ በአብዛኛው ሕግ-ተኮር (rule-based ) ሲሆን በዓለም አቀፍ  ሕግጋት (International Law) እና  በተለምዷዊ አሰራሮች (Norms and principles) ይመራል። የሁለትዮሽ (Bilateral) እና ባለብዙ  ወገን (Multilateral) ስምምነቶች ደግሞ የዓለም አቀፍ ግንኙነቶች ዋነኞቹ መልህቆች ናቸው።

አገራችን ኢትዮጵያ ከውጫሌ ስምምነት አንስቶ እስከ አሁን በርካታ ባለብዙ ወገን  እና የሁለትዯሽ ስምምነቶችን ተፈራርማ የውጪ ግንኙነቷን ስታከናውን ቆይታለች። የውጫሌን ስምምነት በተለየ ሁኔታ ያነሳሁት የመጀመሪያው መደበኛ ዓለማቀፍ ስምምነት ስለሆነ እንጂ ኢትዮጵያ ከሌሎች ዓለማት ጋር ታደርግ የነበረውን ዘመን ጠገብ ግንኙነት ለማሳነስ እንዳልሆነ ልብ ይሏል።

እነዚህ ስምምነቶች በአገር ውስጥ ያሉ መንግስታት በተቀያየሩ ቁጥር የሚለዋወጡ ሳይሆን ዘመን ተሻጋሪ  ናቸው። ስለዚህ የትኛውም መንግስት የሚፈራረመው ስምምነት ብሔራዊ ጥቅምን ያስከበረ እና ለመጪው ትውልድ እዳን ትቶ የሚያልፍ አለመሆኑን በአግባቡ መፈተሽ ይኖርበታል።

እዚህ ጋር በኢሕአዴግ መንግስት ወቅት የፋይናንስ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ሱፊያን አህመድ የደርግ መንግስት ከሰሜን ኮሪያ መንግስት ጋር የተፈራረመውን የብድር ስምምነት እዳ አከፋፋል አስመልክቶ ለውይይት ወደ ፒዩንግ ያንግ (Pyongyang ) ባቀኑበት ወቅት የገጠማቸውን ሁኔታ ያጫወቱኝ ትዝ ይለኛል። ልብ በሉ የደርግ መንግስት የገባውን እዳ የኢሕአዴግ መንግስት ሲከፍል ማለት ነው። 

ሰሞንኛው የአንካራ ስምምነት የመንግስትን የውጪ ግንኙነቱን አካሄድ ድክመቶች እና አደገኛ መዘዞች በግልጽ  ያሳየ ሆኗል። ባለፉት 6 ዓመታት የኢትዮጵያ መንግስት ለቀጣዩ ትውልድ ጭምር ሊተላለፉ የሚችሉ በርካታ ዲፕሎማሲያዊ ስህተቶችን እንደሰራ በርካታ ማስረጃዎችን ማቅረብ ይቻላል። ለዚህ ጽሑፍ ሲባል ሶስቱን አበይት ስህተቶች ብቻ እንመልከት:

- የኢትዮ-ኤርትራ ግንኙነት:
የብልጽግና መንግስት አስተዳደር ገና ከጅምሩ ከኤርትራ ጋር ለዘመናት የቆየውን አለመግባባት ለማርገብ ጥረት ማድረጉ በምልዓተ ህዝቡ ተወዶለት ነበር ። ሆኖም  ከኤርትራ መንግስት ጋር እንደ አዲስ የመሰረተው ግንኙነት የሚመራበት ይህ ነው የሚባል ስምምነት ወይም መርሆ አልነበረም። ሌላው ቢቀር የአልጀርስን የድንበር ኮሚሽን ውሳኔ  አፈፃፀም አስመልክቶ እንኳን የተደረሰበት ስምምነት በግልጽ አይታወቅም። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስምምነቱን ሙሉ በሙሉ ተቀብለናል ሲሉ ከዚህ በፊትም የሁለቱ አገራት ውጥረት ዋና እምብርት የነበረው የአልጀርስ ስምምነቱ የአረዳድ እና የአፈፃፀም ልዩነቶች ተለይተው አልተፈቱም። ስምምነቱ ይተግበር ቢባል እንኳ እነዚህ ልዩነቶች ስላሉ ወደፊትም ሌላ ውጥረት እንደሚነግስ እሙን ነው። አለባብሰው ቢያርሱ በአርም ይመለሱ ነውና ነገሩ ብዙም ሳይቆይ እየተቀየረ መጥቷል። ዛሬም ድረስ የአንድ ወቅት ዋነኛ የቀጠናው አጀንዳ የነበረው የኤርትራና የኢትዮጵያ መንግስት ግንኙነት መሰረት በተለምዶ የጂዳው መግለጫ ከተሰኘው ሰነድ በቀር ይህ ነው የሚባል ስምምነት አልነበረም። ይሁን እንጂ የግንኙነታቸው አድማስ በጣም ጥብቅ የሆነ ወታደራዊ ትብብርንም ይጨምር እንደ ነበር የትግራዩ ጦርነት አሳይቷ አልፏል። ግንኙነቱ ግልጽ በሆነ መንገድ ባለመመራቱም በአንድ ወቅት ተሟሙቆ የነበረው ግንኙነት ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ተቋርጧል። በአሁኑ ወቅት የሁለቱ አገራት የተካረረ ግንኙነት ወደ ግጭት እንዳይገባ ከፍተኛ ስጋት ተፈጥሯል።

- የኢትዮጵያ እና የተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች ግንኙነት:
ሌላኛው አወዛጋቢ ግንኙነት በኢትዮጵያና በተባበሩት አረብ ኢምሬትሶች ጋር ያለው መርህ አልባ ግንኙነት ነው። የኢትዮጵያ እና ኢሚሬቶች አሁናዊ ግንኙነት የሚመራበት ይህ ነው የሚባል ግልጽ ስምምነት ማቅረብ አዳጋች ነው። ከቤተ መንግስት ማስዋብ አንስቶ በርካታ ሜጋ የአስተዳደሩ ፕሮጀክቶች ከኢሚሬትሶች በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ እየተከናወኑ እንደሆነ በተደጋጋሚ ቢገለጽም ድጋፉ በምን ስምምነት እንደተገኘ ማስረጃ ማቅረብ የሚቻል አይመስለኝም። ችግሩ የሚመነጨው መሪው አገሪቱን የጋራችን ሳትሆን የግል ንብረታቸው አድርገው ከመቁጠራቸው የተነሳ  ይመስላል። አለበለዚያማ ማንኛውም የብድር ወይም የእርዳታ ስምምነት ሲፈጸም የህዝብ እንደራሴዎች ፊት ቀርቦ በይፋ እንዲጸድቅ ይደረግ  ነበር (የኢፌዲሪ ሕገ-መንግስት አንቀጽ 55 (12)። ፓርላማውም በስምምነቱ መሰረት አፈፃፀሙን ሊከታተልም  ይገባ ነበር። ሆኖም በአንድ ወቅት ጠ/ሚኒስትሩ አራሳቸው ለምነው በሚያመጡት ገንዘብ ማንም ሊጠይቃቸው እንደማይችል የፓርላማ አባላት ፊት ሲናገሩ ታዝበናል። ለመሆኑ ኢትዮጵያ እስካሁን ከኢሚሬቶች መንግስት ምን ያህል ገንዘብ አገኘች? ገንዘቡ በእርዳታ ነው ወይስ በብድር የተገኘው? ጠቅላይ ሚኒስትሩ በግሌ ነው የለመንኩት ሲሉ በግላቸው ማን ናቸው? እነዚህ ጥያቄዎች መልስ ያሻቸዋል።

- የኢትዮ-ሶማሊላንድ ስምምነት: 
ከቀይ ባህር 60 ኪሜ  (37 miles) ርቀት ላይ ብቻ የምትገኘው አገራችን ኢትዮጵያ ከወደብ አልባ አገራት ተርታ መሰለፏ  የሁሉም አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ቁጭት ነው። በተለይም ታሪካዊውን የአሰብ ወደብ ያለአግባብ እንድታጣ የተደረገበት መንገድ ብዙዎችን አንገት አስደፍቷል። ይህንን ጠንቅቀው የሚያውቁት የአገሪቱ መሪ በሕዝብ ያጡትን ቅቡልነት መልሶ ለማግኘት ይሁን ለአጀንዳ ለማስቀየር  ይህንኑ የውሃ አጀንዳ ወደ ፊት ያመጡት የዛሬ ዓመት ገደማ ነበር። ነገር ግን ማንም ኢትዮጵያዊ ባልገመተው መንገድ እንደ አገር እውቅናን ለማግኘት ከምትውተረተረው የሱማሌላንድ ግዛት ጋር በተፈረመ ስምምነት አገራችን የወደብ ባለቤት መሆኗን የሚያበስር ዜና በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት አሰራጩ። በዓለም አቀፍ ህግ መሰረት አንዲት እንደ አገር እውቅና  ያላገኘች አገር የሁለትዮሽ ስምምነት ለመፈረም የሚያስችል ችሎታ (international legal personality ) ስለሌላት ከማንም ልኡዋላዊ አገር ጋር የምታደርገው ማንኛውም ስምምነት ከመነሻው እንዳልተደረገ ይቆጠራል /void ab initio /(የVienna Convention on the Law of Treaties አንቀጽ 46) ። ሱማሌላንድም በዚህ ረገድ ሲታይ እንደ አገር የምትቆጠር ስላልሆነ ይህ የህግ ድንጋጌ ተፈፃሚ የማይሆንባት ምክንያት አይኖርም። ስምምነቱ አስገዳጅ ሳይሆን  የመግባቢያ ሰነድ ብቻ ነው ቢባል እንኳን  የአፈፃፀም ልዩነት ካልሆነ በቀር በችሎታ ደረጃ  ውጤቱ ተመሳሳይ ነው።

የስምምነቱ ህጋዊነት አጠያያቂነት እንዳለ ሆኖ በውጤትም ደረጃ የኢትዮጵያ መንግስት ያሰበውን ያሳካ አይመስልም። የኢትዮጵያ ብሔራዊ  ጥቅም ቢያስገድድ እና ለሶማሊላንድ እውቅና መስጠት ቢያስፈልግ እንኳ ጊዜ እና ሁኔታን ጠብቆ በጥልቀት የሁኔታዎችን ግምግማ ጥናት ላይ ተመስርቶና አስፈላጊውን ሁሉ ቅድመ ዝግጅት አድርጎ የሚገባበት እንጂ ተዘሎ የሚገባበት አልነበረም።

ELIAS MESERET

14 Dec, 15:48


ኦሮሚያ ባንክ ከአውሮፓ አገኘሁ ያለው ሽልማት እና የሸላሚው አካል ማንነት

(መሠረት ሚድያ)- ኦሮሚያ ባንክ እያስመዘገበ ባለው የማይዋዥቅ የላቀ አገልግሎት ምክንያት ከአውሮፓ ሶሳይቲ ፎር ኳሊቲ ሪሰርች (ESQR) ህዳር 30/2017 ዓ.ም በኦስቲሪያ፣ ቪየና በተካሄድ ፕሮግራም ላይ ሽልማት መቀበሉን አስታውቆ ነበር።

በዚህ ወቅት የባንኩ ሀላፊዎች "ባንካችን ወደ ዓለም አደባባይ በስፋት በመውጣት ተወዳጅ ዓለም-አቀፍ  ብራንድ እየሆነ መጥቷል" ብለው ተናግረው ነበር።

በዚህ ሽልማት ዙርያ መሠረት ሚድያ ባደረገው ማጣራት የአውሮፓ ሶሳይቲ ፎር ኳሊቲ ሪሰርች (ESQR) የተባለው ሸላሚ ተቋም ከ4 ሺህ ዩሮ ጀምሮ ክፍያ ለሚፈፅሙ ተቋማት ሽልማት በማከፋፈል ከዚህ በፊት የሚታወቅ መሆኑን ለማወቅ ችለናል።

የዛሬ ሁለት አመት ናሚቢያ ውስጥ የሚገኙ ሁለት ተቋማት እያንዳንዳቸው 4,200 ዩሮ ከፍለው ይህን ተመሳሳይ ሽልማት ተቀብለው እንደነበር አንድ የሀገሪቱ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት አጋልጦ ነበር (ሊንክ: https://www.facebook.com/share/v/19pn9HpsZS/)

በተጨማሪም አለም አቀፉ የተደራጁ ወንጀሎች እና የሙስና ተግባሮችን አጣሪ እና ሪፖርት አቅራቢ ተቋም (OCCRP) የዛሬ አስር አመት ባወጣው ሪፖርቱ የአውሮፓ ሶሳይቲ ፎር ኳሊቲ ሪሰርች (ESQR) እና ሌሎች ተመሳሳይ በሽልማት ስም የሚያጭበረብሩ ድርጅቶች ምንም አይነት ውድድር ሳይደረግ እና የማሸነፊያ መመዘኛዎችን ሳያስቀምጡ ገንዘብ ለከፈሉ ሁሉ ሽልማት እንደሚሰጡ ጠቅሶ ነበር (ሊንክ: https://www.occrp.org/en/investigation/what-price-honor)

አሁን አሁን ብዙ የሽልማት ፍላጎት እየበዛ የመጣው ከታዳጊ ሀገራት እንደሆነ ሪፖርቱ ገልፆ ማንኛውም ገንዘብ መክፈል የቻለ ተቋም ከ ESQR እና መሰል ድርጅቶች ሽልማት ማጋበስ እንደሚችሉ ጠቅሟል።

ኢትዮጵያ ውስጥ ከኦሮሚያ ባንክ በተጨማሪ የንግድ እና ኢንደስትሪ ሚኒስትር፣ የጉምሩክ ኮሚሽን እንዲሁም ሌሎች ሽልማት እየተበረከተላቸው እንደሆነ በተደጋጋሚ መረጃዎችን ሲያጋሩ ቆይተዋል።

እነዚህ African Leadership Magazine፣ African Governance Award፣ The African Women Awards፣ Africa Respected Professionals Award ወዘተ የተባሉ ሽልማቶች በተለይ ጋና እና ናይጄርያ መቀመጫቸውን ባደረጉ ጋዜጠኞች እየተዘጋጁ የሽልማት ፍላጎት ላለባቸው ሀገራት ገንዘብ በማስከፈል እንደሚሰጡ ታውቋል።

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

10 Dec, 18:16


በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሱሉልታ ወረዳ የወረዳው ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ለገሰ ሥዩም ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ በሚጠራው አማጺ ቡድን መገደላቸውን ዋዜማ ከምንጮቿ ሰምታለች።
ከፖሊስ አዛዡ በተጨማሪ የወረዳው የብልፅግና ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት ሲሳይ በሻዳ ተመትተው ጫንጮ ሆስፒታል መግባታቸውን ሰምተናል፡፡

በጥቃቱ ሁለት የመከላከያ ሠራዊት አባላትና አንድ የኦሮሚያ ፖሊስ አባል በድምሩ አራት ሰዎች ሕይወታቸው ማለፉን ዋዜማ ማረጋገጥ ችላለች።
አማጺ ቡድኑ ጥቃቱን የፈጸመው ዛሬ ታህሳስ 1 ቀን ጠዋት 3 ሰዓት አካባቢ ልዩ ስሙ ሮብ ገበያ በተባለ ስፍራ መሆኑን የገለጹት ምንጮች፣ ፖሊስ አዛዡና የጸጥታ ኃይሎቹ ወዲያው ሕይወታቸው ሲያልፍ፣ የብልጽግና ጽ/ቤት ኃላፊው ወደ ጫንጮ ሆስፒታል መወሰዳቸውን ለዋዜማ አረጋግጠዋል።

አማጺ ቡድኑ <<የክልሉ መንግሥት ያቀረበውን የሰላም ጥሪ ተቀብለናል>> በማለት ቀድመው ማሳወቃቸውን ተከትሎ አመራሮቹና የጸጥታ ኃይሎቹ ወደ ስፍራው ማቅናታቸውን ምንጮች ጠቁመዋል።

ሆኖም በስፍራው ሲደርሱ በአማጺ ቡድኑ በኩል በተከፈተባቸው ድንገተኛ የእሩምታ ተኩስ የፖሊስ አዛዡና የጸጥታ አባላቱ ሕይወታቸው ማለፉት ምንጮች ተናግረዋል።
ታጣቂዎቹ ጥቃቱን ከፈጸሙ በኋላ አመራሮቹ ሲንቀሳቀሱበት የነበረውን ፓትሮል ተሽከርካሪ አቃጥለው ከጥቅም ውጪ ማድረጋቸውንም ዋዜማ ሰምታለች።

አማጺ ቡድኑ ከዚህ ቀደምም የውጫሌ ወረዳ ዋና አሥተዳዳሪና ከሃምሳ በላይ የጸጥታ አባላትን መግደሉን ዋዜማ መዘገቧ የሚታወስ ሲሆን፣ ከአንድ ዓመት በፊትም የሱሉልታ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ በተመሳሳይ በታጣቂዎቹ መገደላቸው ተጠቁሟል፡፡

ድርጊቱ የተፈጸመው የክልሉ መንግሥት በቅርቡ ከአማጺ ቡድኑ አንድ ክንፍ ጋር አደረኩት ባለው የሠላም ስምምነት በርካታ የቡድኑ ታጣቂዎች ወደ ተሃድሶ ማዕከላት እየገቡ እንደሆነ እየተገለጸ ባለበት ወቅት ነው።


Via ዋዜማ
@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

10 Dec, 16:01


በቱሉ ቦሎ ከተማ እርቅ የፈፀሙ የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አባላት ወደ ሰማይ ሲተኩሱ ባመለጣቸው ጥይት አንድ ታጣቂ እና ሹፌር ህይወታቸውን አጡ

(መሠረት ሚድያ)- ከሰሞኑ በአንዳንድ የአዲስ አበባ አካባቢዎች ከመንግስት ጋር እርቅ ፈፀሙ የተባሉ የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አባላት በመሀል ከተማ ጥይት እየተኮሶ ማለፋቸው አነጋጋሪ ሆኖ መቆየቱ ይታወሳል።

በዚህ ተኩስ ምክንያት መገናኛ አካባቢ አንዲት ሴት በጥይት ተመትታ ህይወቷ ማለፉ የሚታወስ ሲሆን በተመሳሳይ በአምቦ ከተማ በታጣቂዎቹ በተተኮሰ ጥይት ሁለት ሰዎች በተባራሪ ተመትተው እንደሞቱ መዘግባችን ይታወሳል።

ዛሬ በደረሰን መረጃ ደግሞ በተመሳሳይ መልኩ በምዕራብ ሸዋ ዞን ቱሉ ቦሎ ከተማ ባለፈው ሳምንት አርብ እለት እርቅ ፈፅመው ወደ ሰማይ እየተኮሱ ካምፕ ሲገቡ የነበሩ የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አባላት ባመለጣቸው ጥይት አንድ ታጣቂ እና ሲሄዱበት የነበረውን ተሽከርካሪ ሲነዳ የነበረ ሹፌር ህይወታቸውን ማጣታቸው ታውቋል።

"ታጣቂዎቹ በፒካፖች ተጭነው ከተማ ሲገቡ ወደላይ እየተኮሱ ነበር" ያለው አንድ የአይን ምስክር እንዳጋጣሚ መኪናው ጉድጓድ መሰል ነገር ውስጥ ገብቶ ሲዘል ሲተኮስ የነበረው መሳሪያ አቅጣጫ በመቀየሩ ሶስት አመት አብረው ከነበሩ ታጣቂዎች መሀል አንዱ እና ሹፌሩ ህይወታቸውን ወዲያው ማጣታቸውን ለመሠረት ሚድያ ተናግሯል።

ድርጊቱን ተከትሎ ታጣቂዎቹ ተኩስ እንዳይተኩሱ ማሳሰቢያ ቢሰጣቸውም በነጋታው ወደ ሰማይ እየተኮሱ ሲሄዱ እንደታዩ ሌላ ምንጫችን ጠቁመዋል።

ፎቶ: ፋይል



@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

10 Dec, 15:49


ቤተል አደባባይ ላይ ተሽከርካሪዎች በግድ እንዲቆሙ እየተደረጉ ሰዎች እየታገቱ መሆኑ ታወቀ

(መሠረት ሚድያ)- ከቅርብ ወራት ወዲህ ቤተል አደባባይ ላይ በተለይ ዘመናዊ የሚባሉ መኪናዎችን የሚያሽከረክሩ ሰዎች በሁለት ሌሎች መኪናዎች መንገድ ተዘግቶባቸው በጠራራ ፀሀይ እየታገቱ እንደሆነ ምንጮቻችን ጠቁመዋል።

እነዚህ ግለሰቦች በዚህ መልኩ ታግተው ከተወሰዱ በኋላ እስከ 5 ሚልዮን ብር እየተጠየቀባቸው እንደሆነ ለመሠረት ሚድያ የሚደርሰው ጥቆማ ያሳያል።

አንድ የጉዳዩ ሰለባ የሆኑ ግለሰብ ድርጊቱን ለማንም እንዳይናገሩ ማስፈራርያ ስለሚደርሳቸው እንጂ በዚህ መልኩ በርካታ ዜጎች ታፍነው እየተወሰዱ ገንዘብ ከፍለው እየተለቀቁ እንደሆነ ተናግረዋል።

ሁለት ሚልየን ብር ከፍለው እንደወጡ የሚናገሩት ግለሰቡ ያገቷቸው ሰዎች የፀጥታ አካላት እንደሆኑ እንደደረሱበት ጨምረው ተናግረዋል።

"ህዝብን ይጠብቃሉ ተብለው የሚመደቡ አካላት ህዝብ ላይ እንዲህ በደል ሲያደርሱ ማየት እጅግ ያሳዝናል" ያሉን ግለሰቡ በዚህ ምክንያት ከሀገር ለመውጣት እንደተገደዱ ተናግረዋል።

በተያያዘ ዜና ከውጭ ሀገራት ወደ ሀገር ቤት ለዘመድ ጥየቃ፣ ለመዝናናት እና ለስራ የሚሄዱ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የእገታ ሰለባ እየሆኑ እንደሆነ ታውቋል።

ሰዎች ከውጭ እንደመጡ ሲታወቅ በክትትል ኢላማ ውስጥ እንዲገቡ እንደሚደረጉ የተጠቆመ ሲሆን በተለይ ሀብትና ንብረት እንዳላቸው የሚታወቁ የዲያስፖራ ኮሚኒቲ አባላት እገታ እንደተፈፀመባቸው የደረሰን መረጃ ይጠቁማል።

አንዳንዶች ካረፉበት ሆቴል እና አፓርትመንት ጭምር "ትፈለጋለህ" በሚል ምክንያት እንደሚወሰዱ እና በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ ግን የገንዘብ ድርድር እንደሚጀመር ታውቋል።

በዚህም እስከ 2 ሚልየን ብር ከፍለው የተለቀቁ የዲያስፖራ ኮሚኒቲ አባላት እንዳሉ እና ይህም በኤምባሲዎች እና በፖሊስ ተቋማት በኩል ጭምር እንደሚታወቅ ጨምሮ ተገልጿል።

በክፍላተ ሀገራት ይፈፀሙ የነበሩ የእገታ ወንጀሎች አሁን አሁን በጠራራ ፀሀይ በመሀል አዲስ አበባ እየተፈፀመ መሆኑ በብዙዎች የሚታወቅ ቢሆንም መረጃው እንዳይወጣ በሚፈፀም ማስፈራራት ወደ ሚድያ እንደማይወጣ ታውቋል።

via Meseret Media

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

08 Dec, 14:20


በአዲስ አበባ የሚሰማው ተኩስ ምንድን ነው?

- በተኩሱ አንድ ሴት መገናኛ አካባቢ ተመትታ ህይወቷ አልፏል

(መሠረት ሚድያ)- ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ እንደ ገርጂ፣ ጃክሮድ፣ ሾላ፣ 6 ኪሎ፣ መነን፣ ጎሮ ወዘተ ያሉ አካባቢዎች ከፍተኛ ድምፅ ያለው ተኩስ ሲሰማ ነበር።

በርካታ ነዋሪዎች በድምፁ ተደናግጠዋል፣ መረጃ የሰጠ የመንግስት አካልም የለም።

መሠረት ሚድያ በዚህ ዙርያ ባደረገው ማጣራት ተኩሱ ከሰሞኑ ከመንግስት ጋር እርቅ ፈፀሙ በተባሉት የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አባላት የተተኮሰ ነው።

መገናኛ አካባቢ አንዲት ሴት በተኩሱ ምክንያት በጥይት ተመትታ ህይወቷ ማለፉም ታውቋል።

ታጣቂዎቹ የኦነግን ባንዲራ በመያዝ ከሸገር ከተማ በመነሳት ወደ አዲስ አበባ ሲገቡ ወደ ሰማይ እየተኮሱ እንደገቡ የደረሰን መረጃ ያሳያል።

"ታጣቂዎቹ በቅጥቅጥ አና በሃይሉክስ መኪና ተጭነው ሾላ ፖሊስ ጣቢያ አካባቢ ሲደርሱ ወደ ሰማይ ተኩስ አየተኮሱ እየተጓዙ ነበር" ያለን አንድ የአይን ምስክር በሁኔታው በርካቶች እንደተደናገጡ ገልጿል።

ህዝብ በሚንቀሳቀስበት ጎዳና ላይ ድርጊቱ መፈፀሙ እንዳሳዘናቸው የገለፁት ነዋሪዎች ህዝብን በዚህ ሁኔታ፣ በተለይ ቀድሞ ባልተገለፀበት ሁኔታ ማሸበር አግባብ እንዳልሆነ ተናግረዋል።

መሠረት ሚድያ ሾላ ፖሊሲ ጣቢያ ከሚገኙ አንድ የፖሊስ አባል ድርጊቱን ያረጋገጠ ሲሆን አንዳንዶች ከተኮሱ ቦታ በድንጋጤ ሲሸሹ ይታይ እንደነበር ገልፀዋል።

ፎቶ: ፋይል

መረጃን ከመሠረት!

via MeseretMedia

@eliasmeserett

ELIAS MESERET

25 Nov, 13:29


ፒያሳ 'ቻይና ግቢ' የእሳት አደጋ ተከሰተ

(መሠረት ሚድያ)- ፒያሳ ከቲያትር ቤቱ ፊት ለፊት በተለምዶ 'ቻይና ግቢ' ተብሎ በሚጠራው ስፍራ ዛሬ ከሰአት 9 ሰአት ገደማ የእሳት አደጋ እንደተከሰተ ምንጮች ከስፍራው ለመሠረት ሚድያ ጠቁመዋል።

"ዘጠኝ ሰአት የተነሳው እሳት አሁንም አልጠፋም፣ የእሳት አደጋ ሰራተኞች በስፍራው ተገኝተዋል" ያለው አንድ በስፍራው የሚገኝ ግለሰብ እሳቱ እየቆየ የቀነሰ ይመስል እና እንደገና ይጨምራል በማለት ተናግሯል።

የእሳት አደጋው 'ጃንጉሲ ኮንስትራክሽን' በተባለ ድርጅት ውስጥ እንደተነሳ ታውቋል።   

ከሰሞኑ በተመሳሳይ በመርካቶ በቀናት ልዩነት ሁለት ግዜ ከባድ የእሳት አደጋዎች መከሰታቸው ይታወሳል።

መረጃን ከመሠረት!

via MeseretMedia

ELIAS MESERET

25 Nov, 12:04


#ከዜናዎቻችን| ኢትዮጵያዊያን ስደተኞችን ከአውሮፓ አስገድዶ ወደትውልድ ሀገር የመመለስ የተቀናጀ ዘመቻ ተከፍቷል ተባለ

(መሠረት ሚድያ)- በኖርዌይ የክርስቲያን ካውንስል የስደተኖች አማካሪ የሆኑት አቶ ለማ ደስታ ለመሠረት ሚድያ የላኩት ፅሁፍ እንዲህ ይነበባል ⤵️

"በሀገራችን ኢትዮጲያ ለረዥም ጊዜ ተንሰራፍቶ በነበረው ግጭቶችና ጦርነቶች፣ የብሄርና የማንነት ተኮር ጥቃቶች፣ ኢ-ፍትሓዊ አሰራር ፣ ከፓለቲካ መብትና ነጻነት፣  ከመልካም አስተዳደር እጦት የተነሳ ለህይወታቸው በመስጋት ቤተሰብን፣ ሀገርንና መንደርን ጥለው  ወደጎረቤትና ወደሩቅ ሀገሮች በመሸሽ የፖለቲካ ጥገኝነት መጠየቅ የቅርብ ዘመን ታሪካችን አካል ነው።

የወገኖቻችን የስደት ጥያቄ አዎንታዊ መልስ አግኝቶ የፓለቲካና የስብዕና ከለላ የተሰጣቸው ብሎም በተጠለሉባቸው ሀገር ቋሚ ነዋሪና ዜጋ የሆኑ ብዙ ወገኖቻችን በዉጪ ሀገሮች ይኖራሉ። ከሚኖሩበት ሀገርም በገንዘብ፣ በእውቀት፣ በዲፕሎማሲና በሌሎች ሁሉ መልኮች ቤተሰባቸውንም ሆነ ሀገራቸውን በመርዳት ትልቅ ገንቢ ሚና የሚጫወት ሀገር ወዳድ ዲያስፖራ ያለን ሀገር ለመሆን በቅተናል።

በተቃራኒው የስደት ጥያቄዎቻቸው በፍትሓዊና በአጥጋቢ ሁኔታ  ሳይታይ በጥቅሉ ውድቅ የተደረገባቸውና  አሉታዊ መልስ ተሰጥቶኣቸው የሰብዓዊና ፍትሓዊ መብት ሙግት ውስጥ ሆነው  ለረጀም ዓመታት በብዙ ድካምና መከራ ያሰለፉ ወገኖቻችን በየሀገሩ አሉ።

ጥቁሮችን፣ የደሃ አገር ዜጎችን ጠል ጎጠኝነት እየተስፋፋ ባለበት በአሁኑ ወቅት፣ አዎንታዊ መልስ ያላገኙ ኢትዮጲያዊን ስደተኞችን የዓለም አቀፍ የስደተኞችና የሰብዓዊነት ህግና መርህ ባልተከተለ መልኩ  አስገድዶ ወደ ትውልድ ሀገር የመመለስ የተቀናጀ ዘመቻ ከተከፈት ወራቶችን አስቆጥሯል። ዘመቻውም ባለፉት ጥቂት ዓመታት  የአውሮፓ መንግስታት ኢትዮጲያ ስደተኞችን መልሳ እንድትቀበል በልዩ ትኩረት ለመደለልም ካልተቻለም ለማስገደድ  የተወሰነው መመሪያ አካል ነው።

እንዲያውም በህብረቱ የተቀመጠውን በተለይም ኢትዮጲያዊያን ስደት ጠያቂዎችን በከፍተኛ ቁጥር ለመመለስ የታሰበው እቅድ ለማስፈጸም  ከሀገር ቤት ጭምር ተወካዮችንና ባለሙያዎችን በመላክ የትውልደ ኢትዮጲያዊን ስደቶች ሰብዓዊ መብት በማያከብር መልኩ ተባባሪ ሆኖ እየተስተዋለ ነው።

ለዚህም አንድ ማሳያ በቅርቡ  አርቲስት አለማየሁ ሂርጶን ጨምሮ ከአስር በላይ ኢትዮጲያዊያን ስደተኞች ከኖርዌይ ወደ ኢትዮጲያ ተወስደዋል። ከሁለትና ሶስት አስርት ዓመታት ልፋት፣ ቆይታ እና ድካም በኋላ በአሳዘኝ ሁኔታ ባዶ እጃቸውን ያለውዴታቸው ወደ ሀገር ቤት ተወስደዋል። ተመልሰውም ወደ ሸንገን ሀገሮች ቢያንስ ለአስር ዓመት እንዳይገቡ ስማቸው፣ ፎቶግራፈቸውና አሻራቸው ተመዝግቧል።

እነ ዓለማየሁን የሚያክል ታዋቂ ሰዎች በህዝባዊ ድጋፍ እጅ መሆናቸው የታየ ቢሆንም የተቀሩት ወንድምና እህቶቻችን ከብዙ ዓመታት በኋላ የት እንደወደቁ አናውቅም። ይሄ በደል ነው። ሀገራችን ኢትዮጲያ ከፈረመቻቸዉ አህጉራዊውም ሆነ አለም አቀፋዊ የስደተኞች ውል በተለያዩ ምክንያቶች ከሀገራችን ተሰደው በሌላ ሀገር የጥገኝነት ጥያቄ ያቀረቡ በወንጀል የማይፈለጉ ዜጎችን ያለፈቃደቸው ወደ ትውልድ ሀገር እንዲመለሱ ማስገደድን አጥብቆ ይቃወማል። በአንጻሩ ደግሞ የሀገራችን ህገመንግስት የዜግነት መብቶች፣ ሌሎች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች እንደሚጠበቁ ይደነግጋል።

ሀገራችን ኢትዮጲያ በአህጉራዊውም ሆነ አለም አቀፈ የስደተኞች ችግር ለማቃለል እየሰሩ ካሉና ቀዳሚ ሚና ከሚጫወቱ ሀግሮች አንዷ ናት።  በመሆኑ ማንኛዉም ሰው ያለፈቃዱና ኢሰብዓዊ በሆነ መንገድ ተገዶ እንድመጣ የኢትዮጲያ መንግስት ይደግፋል ብዬ አላምንም። በስደት የቆዩ ወገኖቻችንን ጥያቄ በአንድ በኩል የመብትና የፍትሕ ጥያቄ ሲሆን፣ በሌላ መልኩ የሰብዓዊነት ጥያቄ ነው። ከአብዛኞቹ አውሮፓ አገራት እንዲመለሱ እየተገደዱ ያሉ ስደተኞች በኢትዮጲያ ውስጥ በነበረው ሁኔታ ተሰደው የመጡና፣ የስደት ጥያቄ በቀረቡባቸዉ ሀገሮች ተገቢውን ምላሽ በተገቢው ጊዜ ባለማግኛት ለብዙ ፈተናና መከራ ተጋልጠው የኖሩ ናቸው።

በድብቅ የጉልበት ሥራ እየሰሩ፣ ራሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን እየረዱ፣ ሲታመሙ እንኳን በአግባቡ ሳይታከሙ፣ ዘዎትር በፍርሃትና በስጋት ኖረዋል። አንዳዶቹ እንደማንም በጊዜ ትዳር መስርተው ቤተሰብ መፍራት አልቻሉም። ትዳር ኖሮኣቸው የመጡትም ከሚወዱትና ከሚናፍቁት ቤተሰባችው ጋር ሳይገናኙ ለመኖር ተገደዋል። በስደት የተንከራተቱትና መልስ በመጠበቅ ህይወታቸው በአንድ ስፍራ ተገትሮ ያሳለፉት ያ ሁሉ የመከራ ግዜ ከምንም ሳይቆጠር ዜጎቻችን ኢሰብኣዊ በሆነ ሁኔታ ተገደውና በዶ እጃቸውን እንዲመለሱ እየተደረገ ነው።

ተመልሰውም ኑሮን እንደገና አዲስ ለመጀመር የሚገደዱ ሲሆን፣ በዚህ መልክም ለራሳቸው፣ ለቤተሰባቸውና ለሀገርም ሽክም መሆኑ ግልጽ ነው። ይሄም አሳሳቢ ድርጊት የብዙ ወገኖቻችንን ኑሮ እያቃወሰ እንደሆነ መታወቅ አለበት። የብዙዎች ሰብዓዊ መብትና ጥቅም ተጥሶ ለአደጋ እንዲጋለጡ እያደረገ ይገኛል። በመሰረቱ በሀገራችን በተለምዶ ስለስደት ማዉራት ውርደት መስሎ ስለሚታይ ስደት የጠየቁ ዜጎቻችን የሚጠብቃችው ስነልቦናዊ ሸክምም ቀላል አይደለም። የአውሮፓ ሀገራት ከቅርብ ዓመታት ጀምሮ እየተከተሉ ያሉትን ስደተኞችን የአለመቀበል ቢቻልም የዓለም አቀፍ የስደት ሸክም ባለበት እንዲቆይ የማድረግ ህልማቸውን ከግብ ለማድረስ እየተጉ ይታያሉ፡፡ ከዚህ የፖለቲካ አላማ የተነሳም በ November 2015 በማልታ ዋና ከተማ ቫሌታ ለይ ከኢትዮጲያ መንግስት ጋር ስምምነት እንደተፈራረሙ የሚታወስ ሲሆን ስምምነቱ የታለመለትን ኢትዮጲያውያንን በገፍ መመለስ ሳይቻል ቆይቷል።

በ December 2017 በአውሮፓ ህብረት መቀመጫ በሆነችው በብራሴልስ ከተማ ሌላ ተጨማሪ ስምምነት ስደተኞችን በገፍ የመመለስ ውል ተፈራረመዋል። አዲሱ የስምምነት ውልም በአውሮፓ ፓርላማ ጥያቄ ያስነሳ ነበር። የአዉሮፓ ሀገሮችና መንግስታቶቻቸዉ ለሀገራችን ልማት የሚያደርጉትን ድጋፍ የማደንቅ ቢሆንም በስደተኞች ለይ የሚያሰዩትን ጭካኔ ግን የሚያሳዝን ነው። ከዚህም የተነሳ የኢትዮጲያ መንግስት ኢትዮጲያዊያን በስደተኞችን መልሶ እንዲቀበል ማስገደድ የአውሮፓ መንግስታት ትልቅ የፖለቲካ አቅጣጫ መሆኑን ከግምት ውስጥ በማስገባት ፣ የኢትዮጲያ መንግስት ከአውሮፓ ሀገሮች ጋር የገባውን የኢትዮጲያዊያን የስደተኞችን መብትና ጥቅም ያለገናዘብ ዉል ዳግም እንዲያጤነው እጠይቃለሁ።

በተለይ ኖርዌይ ያሉ ብዙ የቆዩ የስደት ጥያቄ አቅራቢ ኢትዮጲያዊያን ዜጎቻችን ፈጣን እርዳታና ምላሽ በመስጠት በመንግስታችሁ በኩል ትብብር እንድታድርጉ ትህትና እጠይቃለሁ በማለት አቶ ለማ ደስታ ፅሁፋቸውን አጠቃለዋል።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

Via meseretmedeia


@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

24 Nov, 14:12


#ውጤት ትናንት ላቀረብነው ምስልን የመፈተሽ (image searching) ጥያቄ በርካቶች ትክክለኛ መልስ የሰጡ ሲሆን በመጀመርያ የመለሰው ደግሞ 'Belay Afework' ነው። የመሠረት ሚድያ ሎጎ ያረፈበት ኩባያ እና የ1ሺህ ብር ተሸላሚ ይሆናል።

ማህበራዊ ሚድያ ላይም ሆነ ሌሎች ቦታዎች የሚለጠፉ ምስሎች ለመፈለግ በርካታ ዘዴዎችን መጠቀም ይቻላል። ለምሳሌ:

1. በመጀመርያ ስልክ ወይም ኮምፒውተር ላይ ምስሉን በማስቀመጥ (save በማድረግ) ከዛም እንደ ጉግል፣ ያንዴክስ እና ቲን አይ ባሉ መገልገያዎች መፈለግ

2. በምስሎች ላይ የሚታዩ ጠቋሚ ፅሁፎችን (indicators) በመመልከት እና እንደ ጉግል ማፕ ባሉ መተግበርያዎች ላይ በመፈለግ አካባቢውን ማወቅ ናቸው።

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

23 Nov, 15:31


#ይሸለሙ በየሳምንቱ ቅዳሜ እንደምናደርገው ለማስታወሻ የሚሆን የመሠረት ሚድያ ሎጎ የታተመበትን ኩባያ (mug) እና የ1,000 ብር ሽልማት ለማግኘት ይህን ጥያቄ ይመልሱ:

ይህ ምስል የት ሀገር፣ ምን የሚባል መንገድ ላይ ይገኛል?

መልሱን እዚህ የፌስቡክ ሊንክ ላይ ያስቀምጡ (https://www.facebook.com/61562533862014/posts/pfbid0tw9ozZNKkYdEGYdgWYtfuaW3MPg3H4JGQyivJYNwFyQLEWYt1TFTiCg3tnG3dTmMl/)

*** ቀድሞ የመለሰ ይሸለማል። ምስሎች ላይ ምርመራ የማድረግ ክህሎት ማህበራዊ ሚድያ ላይ የሚሰራጩ ፎቶዎችን ለማጣራት ይጠቅማል፣ እርስዎም ራስዎን ይፈትሹ።

ELIAS MESERET

21 Nov, 17:02


#ከዜናዎቻችን| በሲዳማ ክልል እና በወላይታ ዞን የመንግስት ባለስልጣናት ከህገወጥ የነዳጅ አዘዋዋሪዎች ጋር እየሰሩ እንደሆነ ተጠቆመ

(መሠረት ሚድያ)- ወላይታ ሶዶን ጨምሮ አጠቃላይ በደቡብ ህዝቦች ክልል እንዲሁም በሀዋሳ ከተማ ቤንዚን ከጠፋ በርካታ ቀናት ማለፉ የሚታወቅ ሲሆን ለነዳጅ እጥረቱ እንደ ዋና ምክንያት እየተነሳ ያለዉ የህገወጥ ንግድ መበራከት ነዉ ቢባልም የችግሩ ጥልቀት ከዛም ያለፈ እንደሆነ ምንጮቻችን ጠቁመዋል።

ከወደብ ተጭኖ የሚመጣ ነዳጅ ከማደያ ባለቤቶች፤ ከፀጥታ አካላት፤ ከንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት እንዲሁም ከደላሎች ጋር ባለ የጥቅም ትስስር በጥቁር ገበያ ከ150-200 ብር በጅምላ እየተሸጠ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።

ዛሬ ላይ በጥቁር ገበያዉ በድብቅ ቤንዚን በችርቻሮ እስከ 250 ብር እየተሸጠ እንደሆነ የተረጋገጠ ሲሆን ለበርካታ ወጣቶች የስራ ዕድል በመፍጠር፤ ቤተሰብ ማስተዳደሪያነት የሚጠቀሙ ባለ3 እግር ባጃጅና ባለ2 እግር ሞተሮች ሙሉ በሙሉ ማለት በሚያስችል ሁኔታ አገልግሎት መስጠት አቁመዋል።

ስሜ አይጠቀስ ያሉ አንድ የወላይታ ሶዶ ባለ ሶስት እግር ባጃጅ አሽከርካሪ "በዚሁ ስራ ራሴን እና ቤተሰቤን የማስተዳደር ነበርኩ፣ ነገር ግን በቤንዚን ምክንያት እኔም ሆነ ሌሎች ጓደኞቼም ሥራ መሥራት ተቸግረናል" ያለ ሲሆን በሶዶ ከተማ ያሉ ማደያዎች በጠቅላላ ቤንዚን የለም የሚል ማስታወቂያ እየለጠፉ ይገኛሉ ብሏል።

አክሎም "ነገር ግን ቤንዚን በሁለት ሌትር የውሃ ሃይላንድ በከተማዋ መንገዶች ይቸበቸባል። ከየት የመጣ ነው ሲባል እነዚህ ማደያዎች በህገወጥ መንገድ ለቸርቻሪዎች እየሸጡ ሁሉም አይነት አሽከርካሪዎች ከነዚህ ቸርቻሪዎች 1 ሌትር በ 200 ብር እየገዙ ይጠቀማሉ" ብሏል።

በዚህ ምክንያት አሽከርካሪዎች እንዲሁም ተጠቃሚዎች ለከፋ ችግር ተዳርገናል፣ ለማን አቤት እንበል? ማደያዎች አልቋል ባሉት ማግስት በየሜዳው የሚሸጠው ከየት የመጣ ነው? በማለት ለመንግስት ጥያቆያቸውን አቅርበዋል።

በተመሳሳይ በሲዳማ ክልል፣ ሀዋሳ ከተማ እጥፍ ዋጋ በማስከፈል ነዳጅ በየመንገዱ እየተሸጠ እንደሆነ ታውቋል። መንገድ ላይ መሸጡ ብቻ ሳይሆን እንደ ውሀ ያለ ባእድ ነገር ተቀላቅሎ እየተሸጠ እንደሆነ ጠቁመው የመንግስት ሀላፊዎች እንዳሉበት እንደሚሰሙ ጠቁመዋል።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

via MeseretMedia


@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

21 Nov, 16:58


#ከዜናዎቻችን| በኦሮሚያ ክልል የመንግስት ሰራተኞች ደሞዝ በሲንቄ ባንክ በኩል ብቻ እንዲከፈል መደረጉ የህግ ጥያቄ አስነሳ

(መሠረት ሚድያ)- በክልሉ ያሉ የመንግስት ሰራተኞች ደሞዝ በግዴታ በሲንቄ ባንክ በኩል እንዲከፈል የክልሉ መንግስት ባስተላለፈው ትዕዛዝ መሰረት ደሞዝተኞች በስንቄ ባንክ በኩል ደሞዝ መከፈል ከጀመሩ ሁለተኛውን ወር መያዙ ታውቋል።

ከዚህም በተጨማሪ ማንኛውም በፌደራል መንግስት በጀት የሚንቀሳቀሱ ፕሮጄክቶች፣ የካሳ ክፍያዎች እና የመሳሰሉት አገልግሎቶች በግዴታ በሲንቄ ባንክ ከኩል መደረግ ከጀመሩ ሰነባብተዋል ያሉት ምንጮቻችን ይህም የዛሬ ሶስት አመት ገደማ የገንዘብ ሚኒስቴር ያወጣውን ማንኛውም የፌደራል መንግስት በጀት እና በፌደራል መንግስት ለሚሰሩ ልማቶችን የተመለከቱ ክፍያዎች ለፌደራል መንግስት ተጠሪ በሆኑት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወይም በኢትዮጵያ ልማት ባንክ በኩል ብቻ ተፈፃሚ እንዲሆኑ የሚደነግገውን አዋጅ ይጥሳል ተብሏል።

አዋጁ በሰዓቱ ሲታወጅም አንዳንድ ክልሎች የፌደራል መንግስትን በጀት ከህግ ውጪ በሆነ አሰራር በግል ባንኮች እያንቀሳቀሱ እንደሆነ ጠቅሶ የግል ባንክ ውስጥ የተቀመጠ የፌደራል መንግስት በጀት ባስቸኳይ ወደ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ይመለስ የሚል ድንጋጌም ተካቶበት ነበር።

ይሁንና በተለይ ከሌሎች ክልሎች በተለየ በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት እየተስተዋሉ ያሉ ተደጋጋሚ የህግ ጥሰቶች ከመቀነስ ይልቅ ተባብሰው ሲታዩ የተለያዩ ጥያቄዎችን አጭረዋል።

ከእነዚህም መሀል የኦሮሚያ ክልል ለፌደራል መንግስት የማይታዘዝ ክልል ሆኖ ነው ወይ? የፌደራል መንግስቱ ለአንዱ ክልል አባት፤ ለሌላኛው ክልል የእንጀራ አባት ነው ወይ? የገንዘብ ሚኒስቴርስ የአዋጁን አፈፃፀም ሳይከታተል ቀርቶ ነው ወይስ ጫና ተደርጎበት? የሚያስብሉ እና ሌሎችንም ጥያቄዎች እንድንጠይቅ ያደርገናል በሚል አንድ የባንክ ባለሙያ አስተያየታቸውን ለመሠረት ሚድያ አጋርተዋል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ አሁን ደሞዛቸው በግድ በሲንቄ ባንክ እንዲሆን የተደረጉ ሰራተኞች መስተጓጎል እንዳጋጠማቸውም ታውቋል፣ አንዱ ምክንያት ደግሞ የሚከፈለው ደሞዝ ከእጅ ወደ አፍ የሆነበት ህዝብ ደሞዙን ለማውጣት ሲሄድ የፈለገውን ያክል እንዳያወጣ የሚደረግበት ጫና መሆናቸው ታውቋል።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

via MeseretMedia


@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

21 Nov, 16:54


#ከዜናዎቻችን| በጅማ ከአባ ጅፋር ቤተመንግስት እድሳት ጋር በተያያዘ 150 አባዋራዎች ከመኖርያቸው እንደፈናቀሉ ተናገሩ

(መሠረት ሚድያ)- በከተማው ጅሬን ቀበሌ የሚገኘው ቤተመንግስቱ እድሳት ከተጀመረ ወዲህ ከ40 ሄክታር መሬት በሚበልጥ ቦታ ላይ ይኖሩ የነበሩ እነዚህ ከ150 በላይ አባወራዎች መፈናቀላቸውን ተናግረዋል።

"ከአባቶቻችን ጀምሮ ከ100 አመት በላይ ከኖርንበት ቄያችን ያለምንም ካሳና ምትክ ቦታ ተፈናቅለን በግለሰቦች ቤት ተጠልለን እንገኛለን" ያሉት እነዚህ ዜጎች ህዝብ ጉዳታችንን ይወቅልን ብለዋል።

በመጀመሪያ ዙር 60 ቤቶች ክረምት ላይ፣ ማለትም ከሐምሌ እስከ ነሃሴ 2016፣ በሁለተኛ ዙር ደግሞ ከጥቅምት ሁለት 2017 ጀምሮ 90. ቤቶች እየፈረሱ እንደሆነ ታውቋል።

"መሬትና ቤት እየለኩ ይገኛሉ፣ ለማፍረስ ሲዘጋጁ እንኳን ከሶስት ቀን በላይ አይሰጡም" ያሉት የጅማ ነዋሪዎች ስለፈረሰበት ቤት እና ንብረት መረጃ ስጡኝ ብሎ የጠየቀ ሰዉ "የልማት ፀር" ተብሎ ይደበደባል አሊያም ይታሰራል ብለዋል።

ከአባ ጅፋር ቤተመንግስት እድሳት በተጨማሪ በጅማ ዞን፣ ጌራ ወረዳ 'ከሚሴ' በምትባል ትንሽ ከተማ ውስጥ 'ለኮሪደር ልማት' በሚል ከሀምሳ በላይ ቤቶች እንደፈረሰ መሠረት ሚድያ በቅርቡ ዘግቦ ነበር።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

via MeseretMedia


@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

21 Nov, 16:50


#ከዜናዎቻችን| በሶማሌ ክልል ውጫሌ ከተማ የስልክ እና ኢንተርኔት አገልግሎት ከተቋረጠ ወር እንደሞላ ታወቀ

(መሠረት ሚድያ)- ከዚህም በተጨማሪ በሶማሊላንድ እና በኢትዮጵያ ድንበር ላይ በምትገኘው ቶጎጫሌ ከተማ የኢንተርኔት አገልግሎት ከተቋረጠ ሁለት ሳምንት እንዳለፈው ታውቋል።

በርካታ የአካባቢው ነዋሪዎች በዚህ ምክንያት ስራ መስራት እና ቤተሰቦቻቸውን ማግኘት እንዳልቻሉ ለመሠረት ሚድያ የጠቆሙ ሲሆን በርካቶች አሁን ላይ የኢትዮ ቴሌኮም ኔትዎርክን መጠቀም ባለመቻላቸው የሶማሊላንድ የስልክ ኔትዎርክ እየተጠቀሙ እንደሆነ ተናግረዋል።

ቶጎጫሌ እና ውጫሌ በንግድ እንቅስቃሴ የሚታወቁ አካባቢዎች ከመሆናቸው አንፃር ካለምንም ማስጠንቀቂያ እና ማብራርያ ኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቱን ማቋረጡ ህይወታቸውን ፈታኝ እንዳደረገባቸው ከስፍራው የሚደርሰን ተከታታይ መረጃ ይጠቁማል።

በጉዳዩ ዙርያ ከኢትዮ ቴሌኮም ማብራርያ እስካሁን አልተሰጠም።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

via MeseretMedia

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

21 Nov, 16:46


#ከዜናዎቻችን| ዋልታ ስራ አስፈፃሚውን አሰናብቶ ምርመራ ጀምሯል

(መሠረት ሚድያ)- የዋልታ ሚዲያ እና ኮሚኒኬሽን ኮርፖሬት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መሀመድ ሀሰን ከሀላፊነት መነሳቱን መሠረት ሚድያ አረጋግጧል።

አቶ መሀመድ ከሀላፊነት የተነሳው ለኪሳራ  የተዳረገው ዋልታን ፋና ብሮድካስቲንግ በመጠቅለሉ ምክንያት ነው ተብሏል።

ከ2 ዓመታት በፊት ወደ ሀላፊነት የመጣው አቶ መሀመድ ለስራ ማስኬጃ ወደ 500 ሚሊዮን ብር ከመንግስት ተበጅቶ የነበረ ቢሆንም በአጭር ጊዜ ውስጥ ይህን ከፍተኛ ገንዘብ ላልተበጀተ ጉዳይ በማዋሉ ቅሬታ ሲቀርብበት ቆይቷል።

ሀላፊው ዋልታን ለመምራት ከተረከበ በኋላ በርካታ የቅርብ ጓደኞቹን እና የቤተሰብ አባሎቹን ወደ ተቋሙ በመቀላቀል ከሌላው ሰራተኛ በተለየ መልኩ ልዩ እና ከፍተኛ ተከፋይ እንዲሆን አድርገዋል በሚል ከነባር ሰራተኞች ቅሬታ ሲቀርብበት ነበር።

አቶ መሀመድ በተቋሙ የነበረውን ማኔጅመንት ሙሉ በሙሉ በመበተን በወዳጆቹ እንዲተካ እንዳደረገ የታወቀ ሲሆን በዋልታ በዜና እና በዶክመንተሪ ስራዎች ከፍተኛ ልምድ ያካበቱ አመራሮችም ከስራቸው እንዲሰናበቱ አድርጓል በሚል ክስ ሲቀርብበት ቆይቷል። 

በመፀዳጃ ቤት እና በሌሎች መጠነኛ የቢሮ እድሳት ሰበብ ግልፅ ባልሆነ አካሄድ ገንዘብ በማባከን የሚወቀሰው አቶ መሀመድ በአማካሪነት ስም ቤታቸው ቁጭ ብለው እስከ 90 ሺህ ብር ከዋልታ የሚከፍላቸው ግለሰቦች ስለመኖራቸውም ከዋልታ ሰራተኞች የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ላለፉት ዓመታት በተለይ በነባር ሰራተኞች ላይ ከፍተኛ የአስተዳደር በደል እና የሙስና ወንጀል ሲፈፀም ቆይቷል የሚሉት ምንጮቹ በወንጀል የተጠረጠሩ አመራሮች በህግ አግባብ ምርመራ ተደርጎባቸው ተጠያቂ እንደሚሆኑም እምነታችን ነው ብለዋል።

አቶ መሀመድ የተቋም ንብረቶችን ለግል የዩትዩብ ሚዲያው ሲጠቀም መቆየቱም ታውቋል።

"ሰውየው" በሚል ርዕስ ጠቅላይ ሚ/ር አብይ አህመድን በተመለከተ መፅሀፍ የፃፈው አቶ መሀመድ ከቀናት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትሩን የሚተች ፅሁፍ በፌስቡክ ገፁ ላይ ለጥፎ መልሶ ማንሳቱ ታውቋል።

አሁን ላይ ዋልታን የጠቀለለው ፋና ብሮድካስቲንግ "ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን" በሚል ስም ተመስርቶ የሀላፊነት እና የንብረት ርክክብ ማድረግ ጀምሯል። የነባሩ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አድማሱ ዳምጠው አዲሱን ግዙፍ ሚዲያም በዋና ስራ አስፈፃሚነት እንደሚመሩት ታውቋል።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

via MeseretMedia

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

21 Nov, 16:43


#ከዜናዎቻችን| በአምስት አመት ውስጥ አንድም ተማሪ ለዩኒቨርስቲ ያላሳለፈው ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት

(መሠረት ሚድያ)- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ዳዉሮ ዞን፣ ማሪ-ማንሳ ወረዳ ውስጥ ካሉ ከሦስት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ አንዱ የሆነው የአሰሊ-መንድዳ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከ2012 ዓ/ም ጀምሮ ለዩኒቨርሲቲ መግቢያ ካስፈተናቸው ተማሪዎች ውስጥ አንድም ተማሪ እንዳላለፈ ታውቋል።

የትምህርት ቤቱ አመራሮች እና ወላጆች ለመሠረት ሚድያ እንደተናገሩት የተማሪዎች የመማሪያ ክፍሎች በቅጡ አለመዘጋጀት፣ የመማሪያ መጽሐፍት አለመኖር፣ የተማሪ መቀመጫ እና ወንበር እጥረት፣ የቤተ-መጻህፍት አለመኖር፣ ትምህርት ቤቱ በአጠቃላይ ለተማሪ በሚመጥን መልኩ አለመሥራቱ እና ሌሎች ምክንያቶች ለዝቅተኛው ውጤት ምክንያት ሆነዋል ብለዋል።

ከዚህም በተጨማሪ እስካሁን ድረስ የኢኮኖሚክስ ትምህርት የሚያስተምር መምህር ካለመኖሩና ካለመመደቡ የተነሳ ተማሪዎች የትምህርት ዓይነቱን ሳይማሩ ፈተና እንዲፈተኑ እየተደረጉ እንደሆነ ታውቋል።

የICT (ወይም የኮምፒውተር) ትምህርት በቲዎሪም ሆነ በተግባር እስካሁን እየተማሩ አለመሆናቸው በተማሪዎች ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ እያሳደረ ነው ተብሏል።

ጉዳዩን ለሚመለከተው አካል ብናቀርብም እስካሁን ድረስ ምላሽ ሊሰጥ ባለመቻሉ ተማሪና ትምህርት ቤቱ ከፍተኛ ችግር ዉስጥ ወድቋል ብለው ተናግረዋል።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

via MeseretMedia

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

21 Nov, 16:36


በርካቶችን ያስቆጣው የደራ ወረዳው የግድያ ወንጀል

(መሠረት ሚድያ)- በሰሜን ሸዋ ደራ ወረዳ አንድ ወጣት በታጣቂዎች ተይዞ በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገደል የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምሥል በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ከታየ በኋላ በርካቶችን መስቆጣቱን ቀጥሏል።

ጉዳዩን በሚመለከት ቢቢሲ ኦሮምኛ ያነጋገራቸው ግለሰቦች ግድያው የተፈጸመው በአካባቢው በሚንቀሳቀሱ “የፋኖ ታጣቂዎች” መሆኑን ይናገራሉ።

ነገር ግን ይህንን ክስ በተመለከተ ከፋኖ ቡድን የተሰጠ ምላሽ የለም፤ ቢቢሲም በአካባቢው ይንቀሳቀሳል ከተባለው ቡድን ምላሽ ለማግኘት ያደረገው ጥረትም አልተሳካም።

ድርጊቱ የተፈጸመው ከሁለት ወራት በፊት ነው የሚለው ዳንኤል ገመዳ ወደ ሰሜን ሸዋ ደራ አካባቢ አምርቶ የሟችን ቤተሰቦች ማነጋገሩን ለቢቢሲ ገልጿል። ግድያው የተፈጸመበት ወጣት ደረጀ አማረ ተስፋ እንደሚባል እና የ10ኛ ክፍል ትምህርቱን አጠናቅቆ ወደ ቤተሰቦቹ የሄደ እንደነበር ዳንኤል ጨምሮ አስረድቷል።

በሰሜን ሸዋ ደራ ወረዳ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት እንዲሁም የፋኖ ታጣቂዎች የሚንቀሳቀሱ ሲሆን፣ በተለያየ ጊዜ ከመንግሥት ኃይሎች ጋር ይጋጫሉ። ቢቢሲ ከኦሮሚያ ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ፣ የደራ ወረዳ አስተዳደር እና የፀጥታ ኃላፊዎች ግድያውን በተመለከተ ምላሽ ለማግኘት ያደረገው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም።

የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ ሐሙስ በሰጡት መግለጫ በሰሜን ሸዋ ደራ ከተፈጸመው ድርጊት ጋር “አሸባሪ እና ጽንፈኛ ቡድኖች በንጹሀን ዜጎች ላይ የሚፈጽሙት” የጭካኔ ድርጊት ነው በማለት አውግዘዋተል።

ኃላፊው ጨምረውም ቡድኖቹ “የተለያየ ቋንቋ ይናገሩ እንጂ ድርጊታቸው ተመሳሳይ ነው” በማለት ድርጊቱ በሕዝቡ መካከል ጥርጣሬ እንዲፈጠር የተፈጸመ ነው ብለዋል።

መንግሥት ሸኔ የሚለው ቡድን በተለያዩ አካባቢዎች የሕዝብ ደኅንነት አደጋ ላይ እንዲወድቅ እና ልማት እንዲደናቀፍ እያደረገ ነው ያሉት አቶ ኃይ፤ኡ፤ ፋኖ ደግሞ ኦሮሚያ እና አማራ ክልሎች በሚዋሰኑባቸው አካባቢዎች በንጹሃን ላይ ጉዳት እያደረሰ ነው ብለዋል።

የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደሪ አቶ ከፋለው በበኩላቸው ይህ ድርጊት ወደ ተፈጸመበት ስፍራ በመሄድ ሁኔታውን አጣርተው እንደሚናገሩ ለቢቢሲ ኦሮምኛ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ጉዳዩን እንደሰማ ገልጾ ማጣራት መጀመሩን እና የደረሰበትን ውጤት ወደፊት እንደሚያሳውቅም ገልጿል። ቢቢሲ ቪዲዮው መቼ እና የት እንደተቀረፀ ከገለልተኛ ወገን ማጣራት አልቻለም።

የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት አባላትን ትመግባላችሁ በሚል ጥቃት ያደርሱብናል በማለት ፍርሃት እንዳለባቸው ይናገራሉ።
በተጨማሪም የፋኖ እና የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ታጣቂዎች ከመጡ ደግሞ ቤት ያቃጥላሉ፣ ይዘርፋሉ፣ ይገድላሉ ሲሉ ነዋሪዎች መናገራቸውን ዳንኤል ይናገራል።

ለዚህም ማሳያ አንድ የአካባቢው ነዋሪ “ፋኖ ታጣቂዎች” ወደ ቤታቸው መጥተው አንደነበር ገልጸው “ባለቤቴ እና አማቴ ቤት ነበሩ። አማቴ ልጄን ደብቃ ከአባቷ ጋር ወጥታለች ብላ አሸሸቻት። እርሷን መትተዋት ባለቤቴን ይዘዋት ወጡ” ይላሉ።

ግለሰቡ ባለቤታቸውን ለማስለቀቅ 10 ሺህ ብር ቢከፍሉም ከቀናት በኋላ ግን ባለቤታቸው በታጣቂዎች መደፈራቸውን መስማታቸውን ለቢቢሲ ኦሮምኛ ተናግረዋል።
“መጀመሪያ አንደተደፈረች ደብቃ ነበር። ነገር ግን የአካባቢው ሰዎች ማውራት ሲጀምሩ ነው ለእኔ የነገረችኝ።

እኔ እንዲለቋት ብዬ 10 ሺህ ብር ከፍዬ ነበር።”
በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ከሚፈጽሙት የንብረት ውድመት እና ዘረፋ በተጨማሪም በተደጋጋሚ የመድፈር ጥቃቶች ይፈጽማሉ ሲሉ ነዋሪዎች ይከሳሉ።

ሌላ በአካባቢው በሚገኝ መስኪድ ውስጥ ከሰኔ ወር ጀምሮ ተጠልለው የሚገኙ አንድ ነዋሪ “መውጫ መንገድ የለም። ለመንግሥት ይግባኝ ለማለት ምንም መንገድ የለም። መንገድ ዘግተው ያሉት እነርሱ [የፋኖ ታጣቂዎች] ናቸው” ይላሉ።

በአካባቢው የሚንቀሳቀሱት ታጣቂዎች አርሶ አደሮቹ ያመረቱትን ዘርፈው፣ የተረፈውን በማቃጠላቸው በአሁኑ ጊዜ የሚበላ ነገር በእጃቸው አለመኖሩን ይናገራል።

“በፊት በዘር እና በሃይማኖት ሳንከፋፈል አብረን እንኖር ነበር” የሚሉት እኚሁ ግለሰብ፣ “በጾም ወቅትም አብረን ጾምን ነበር። በኢሬቻ ጊዜ እንኳን ከአማራ ተወላጆችጋር አክብረናል” ሲሉ በአካባቢው የሚኖረው ማኅበረሰብ የነበረበትን ትስስር ይገልጻሉ።

“አሁን ግን እነዚህ ታጣቂዎች መጥተው አብረን የምንኖረውን ሰዎች በእኛ ላይ አነሳሱብን” በማለት የተለያዩ ሰቅጣጭ ጥቃቶች እና ግድያዎች መፈጸማቸውን ለቢቢሲ ኦሮምኛ በዝርዝር አስረድተዋል።

ሌላው የደራ ወረዳ ነዋሪ በበኩላቸው ከፍርሀት የተነሳ ማገዶ ለመልቀም እንኳ የምንሄደው በጋራ ነው ይላሉ።
ለዚህም ምክንያታቸውን ሲያስረዱ “ምናልባት አንዱ እንኳ ቢያዝ ጮኽን ለማስለቀቅ በሚል ነው በጋራ የምንሄደው።”
ቢቢሲ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች በቀን አንድ ጊዜ እንኳ ለመመገብ እንደሚቸገሩ ይገልጻሉ።

ባለፈው ዓመት መንግሥት የእርዳታ እህል ወደ ስፍራው ቢልክም በአካባቢው በሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች እጅ መግባቱን ይናገራሉ። መንግሥት ጉዳዩን በሚመለከት እስካሁን ድረስ ያለው የለም።

በኦሮሚያ የተለያዩ አካባቢዎች በታጣቂዎች በሚደርሱ ጥቃቶች የተነሳ በርካቶች ተገድለዋል፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ደግሞ ተፈናቅለዋል። የፌደራል መንግሥት ከኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ጋር የገባውን ግጭት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ለሁለት ዙር በታንዛኒያ ያካሄደው ድርድር ያለውጤት መጠናቀቁ ይታወሳል።

Via ቢቢሲ

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

20 Nov, 14:58


#ቃለመጠይቅ በአሜሪካ የዶናልድ ትረምፕ በመመረጥን ተከትሎ በኢሚግሬሽን ጉዳይ ዙርያ የተለያየ መረጃ እየተሰራጨ ይገኛል

ህገወጥ ኢትዮጵያውያን ሊባረሩ ነው፣ ዲቪ ሊቆም ነው፣ ጥገኝነት (asylum) መስጠት ሊቆም ነው ወዘተ የሚሉ መረጃዎች በስፋት እየተሰራጩ ነው።

በዚህ ዙርያ በአሜሪካ ሀገር በኢሚግሬሽን የህግ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው Mulu Law LLC ባልደረባ አቶ ሙሉአለም ጌታቸውን ባልደረባችን ጋዜጠኛ ኤልያስ መሠረት አነጋግሯል። ይከታተሉት:

https://youtu.be/bW0VdKHE5yw?si=OdnWO1Jolcx2EmaT

ELIAS MESERET

20 Nov, 12:27


እጅግ አሳዛኝ፣ አፀያፊ እና ሁላችንም ልናወግዘው የሚገባ ድርጊት ሰላሌ ላይ እንደተፈፀመ ታውቋል

የሰው ልጅ ላይ የዚህን ያህል ጭካኔ ለምን? ምን እየሆንን ነው? የነዚህ ግፎች መጨረሻ መቼ ይሆን?

ነፍስ ይማር!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

19 Nov, 19:40


ይህ የ40/60 ህንፃ ቦሌ አያት 2 ብሎክ 38 ይባላል

ዕጣ ከወጣበት ሁለት አመት ሊሞላው ሲሆን ባለ 13 ፎቁ "ህንፃ" በሚያሳፍር እና አደገኛ በሆነ ሁኔታ ተሰርቶ ቆሟል። እስካሁን ከ8ኛ በላይ ያለው የውስጥ ለውስጥ partition የሌለው፣ መወጣጫ ደረጃው ያላለቀ፣ የውስጥ ልስን የሌለው እና ጣራው ያልተመታ ነው። ህዝብ ግን የንግድ ባንክ ክፍያውን ቤት አገኝ ብሎ እየከፈለ ነው።

እርግጥ ነው ኮንትራክተሩ ከመንግስት ጋር ያላቸው ትስስር ይታወቃል፣ ግን ህንፃው ውስጥ ሰው ገብቶ አስከፊ አደጋ ሳያደርስ በፍጥነት መፍትሄ ያስፈልገዋል።

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

19 Nov, 15:07


#FactCheck የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ኮ/ል መንግስቱ ኃይለማርያም የመኪና መገጣጠሚያ ሲያስመርቁ ያሳያል ተብሎ የተጋራው ቪዲዮ የተሳሳተ ነው

ከ7 ሺህ በላይ ተከታዮች ያሉትና ‘UNO’ የሚል ስያሜን የሚጠቀም የቲክቶክ አካውንት የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ኮ/ል መንግስቱ ኃይለማርያም የመኪና መገጣጠሚያ ሲያስመርቁ ያሳያል ያለውን ቪዲዮ ማጋራቱን ተመልክተናል።

ቪዲዮውም በድምሩ ከ12,000 በላይ ግብረ-መልሶችን ያገኘ ሲሆን በቪዲዮው ላይ የሚታዩት ሰው ፕሬዝደንት መንግስቱ ናቸው ብለው ያመኑ በርካታ ሰዎች አስተያየት ሲሰጡም ተመልክተናል።

ሆኖም ኢትዮጵያ ቼክ ባደረገው ማጣራት በቪዲዮው ላይ የሚታዩት ሰው ፕሬዝደንት መንግስቱ አለመሆናቸውን አረጋግጧል። በቪዲዮው ላይ የሚታዩት ሰው በጋና የሚገኝ አሳንቲ ብሔር ባህላዊ ንጉስ ሲሆኑ የንግስና ስማቸውም ዳግማዊ ኦቶሙፉ ናና ኦሲ ቱቱ (Otumfuo Nana Osei Tutu II) ነው።

ንጉሱ ከንግስናቸው በተጨማሪ የኩዋሜ ኑኩሩማህ ሳይንስና ቴክኖሎጅ ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር በመሆንም ያገለግላሉ።

ከላይ የተጋራው ቪዲዮ የተቀረጸውም ዳግማዊ ኦቶሙፉ ናና ኦሲ ቱቱ ከሶስት ቀናት በፊት ዞንዳ የተባለን በጋና የሚገኝ የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ በጎበኙበት ወቅት ነበር። ትክክለኛውን ቪዲዮ ይህን ማስፈንጠሪያ በመከተል ማግኘት ይቻላል:
https://vm.tiktok.com/ZMhnCy44V/

ከአውድ ውጭ ተወስደው የሚጋሩ ቪዲዮዎች ለሀሰተኛ እና አሳሳች መረጃዎች ሊያጋልጡን ስለሚችሉ ከማጋራታችን በፊት ተገቢዉን ማጥራት እናድርግ።

via ኢትዮጵያ ቼክ

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

19 Nov, 14:40


አዲስ አበባ ገና ፓሪስን አልመሰለችም፣ ወደፊት ግን ልትመስልም... ልትበልጥም ትችላለች!

ግን ኢቢሲ ህዝብ በሚሊዮኖች በሚራብበት፣ በሚገደልበት፣ በሚፈናቀልበት እና በሚሰደድበት ወቅት የቁንጅና ውድድር ይመስል ከተማ ለከተማ መልክ ሲያወዳድር የሚውል ሚድያ ሆኖ አረፈው?

ይህ ነው የኢቢሲ 'አዲሱ አቀራረብ' ተብሎ በስፋት ሲተዋወቅ የከረመው?

#ሙያውንአታርክሱት

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

19 Nov, 13:32


የ33 አመት እድሜ ያላት ሶማሊላንድ ነፃና ፍትሀዊ ምርጫ አድርጋ አዲስ ፕሬዝደንት መርጣለች

እኛ የ3 ሺህ አመት ስልጣኔ ያለንስ?

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

18 Nov, 17:07


ከውጭ ጉዳይ እንዳጋራው የተላከልኝ ነው

የእንግሊዘኛ፣ ፈረንሳይኛና ዓረብኛ ቋንቋዎችን መናገርና መጻፍ የምትችሉ እና ዕድሚያችሁ ከ18-30 የሆነ ኢትዮጵያዊና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን መመዝገብ ትችላላችሁ

ELIAS MESERET

18 Nov, 16:35


No comment!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

18 Nov, 11:46


#ከዜናዎቻችን| የቢሾፍቱ ከተማ ለዱባይ ባለሀብቶች በሊዝ ሊሰጥ መሆኑን መረጃ ማቅረባችንን ተከትሎ ነዋሪዎች አዲስ መረጃ ከመንግስት ተነገረን አሉ

(መሠረት ሚድያ)- መሠረት ሚድያ ባሳለፍነው ሳምንት ባጋራው መረጃው ቢሾፍቱ ከተማ ለዱባይ ባለሀብቶች በሊዝ እንደተሸጠ ለነዋሪዎች እንደተነገራቸው ጠቁሞ ነበር።

በዚህም ምክንያት ነዋሪዎች በአንድ ሳምንት ከመኖርያ እና የስራ ቦታቸው እንዲነሱ መታዘዛቸው መታወቁን ዘግበን ነበር።

ይህን ተከትሎ በደረሰን መረጃ መሰረት ደግሞ የቢሾፍቱ ከተማ አመራሮች ባሳለፍነው ሳምንት መባቻ ነዋሪዎችን ሰብስበው የአየር ካርታ ላላቸው ነዋሪዎች በምትኩ 105 ካሬ ቦታ እንሰጣለን ማለታቸው ታውቋል።

"በተመሳሳይ ለገበሬዎች 105 ካሬ እና የሊዝ ዋጋ ካሳ እንከፍላለን ብለውን ሄደዋል" በማለት ተናግረዋል።

ቢሾፍቱን 'በምስራቅ አፍሪካ የቱሪዝም ማዕከል' ለማድረግ እየተሰራ ካለው ስራ ጋር በተያያዘ በርካታ የከተማው ቦታ ለተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ሊሰጥ እንደሆነ በመጀመርያ የተሰማው የዛሬ ሁለት ወር ገደማ ነበር።


(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

via MeseretMedia

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

18 Nov, 09:01


ከሳምንት በኋላ ዛሬም የመርካቶ ሱቆች በአብዛኛው ዝግ ሆነዋል

(መሠረት ሚድያ)- በዛሬው እለት በርካታ የመርካቶ ነጋዴዎች ሱቆቻቸውን ዝግ እንዳደረጉ ታውቋል፣ ምክንያቱ ደግሞ ከሰሞኑ በመንግስት አካላት እና በነጋዴዎች መካከል ውዝግብ የፈጠረው የገቢዎች የደረሰኝ አጠቃቀም ጉዳይ መሆኑ ታውቋል።

ነጋዴዎች እየተጠየቁ ያሉት የደረሰኝ ቅጣት እና የቅጣት አፈፃፀም ከአቅማቸው በላይ መሆኑን ሲናገሩ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በበኩሉ በደረሰኝ እንዲገበያዩ የሚጠበቅባቸው ነጋዴዎች በደረሰኝ ግብይት እንዲፈጽሙ በመደረጉ ያነሱት ጉዳይ ነው ብሏል።

"በግምት ከዘጠና ፐርሰንት በላይ ሱቆች ዛሬ ዝግ ናቸው" ያለው አንድ ነጋዴ የመንግስት ባለስልጣናት ጭምር የተሳተፉባቸው የኮንትሮባንድ ምርቶች ወደ ገበያ ያለደረሰኝ እየተበተኑ ነጋዴውን ደረሰኝ ቁረጥ ማለት አግባብ አይደለም ብሏል።

ሌላ አንድ ስሜ አይጠቀስ ያለ የመርካቶ ነጋዴ የሱቅ መዝጋት አድማው "እስከ ስድት ቀን ሊቆይ ይችላል፣ እየተነጋገርን ነው" በማለት ለመሠረት ሚድያ ተናግሯል።

መንግስት ያለደረሰኝ ግብይት ሲፈፅም የተገኘ ነጋዴ ንብረቶቹ ይወረሳሉ በሚል 'ሀሰተኛ መረጃ' አንዳንድ ባለንብረቶችና ነጋዴዎች ሱቃቸውን የመዝጋትና እቃዎችን የማሽሽ ሁኔታዎች አሉ ቢልም ነጋዴዎቹ የዛሬ ሳምንት ገደማ ይርጋ ሀይሌ የገበያ ማዕከል ደረሰኝ አልተቆረጠም በሚል ምክንያት ከ200 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጡ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችን ደንብ አስከባሪዎች እንሰወሰዱባቸው ተናግረዋል።

መረጃን ከመሠረት!

via MeseretMedia

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

18 Nov, 08:31


ሰው ሁሉ ይበላል፣ ይጠጣል፣ ይጨፍራል። የአሸናፊነት ስሜት ላይ ነበሩ። እኔ አለቅሳለሁ፣ እለምናለሁ. . . ሰሚ አልነበረም። ሁኔታቸው ምርኮ ይዞ እንደመጣ ጀግና ነበር።
ኩራዝ ብቻ የበራበት ጨለማ ክፍል ውስጥ አስገቡኝ። ጠባቡ ክፍል ውስጥ ሊወቅድ የደረሰ አልጋ ተቀምጧል። አሁን ላይ ክፍሉን ሳስበው መቃብር መስሎ ይታየኛል። እያለቀስኩ፣ እየጸለይኩ ሌሊቱ ነጋ።
በማግስቱ ዋነኛው ጠላፊ የኋላመብራት እና አባሪዎቹ ቤቱ ደጅ ላይ ስብሰባ መሰል ነገር አድርገው ሲጨርሱ አስጠሩኝ።
“ከዚህ በኋላ የኋላመብራት ሚስት ነሽ። ሽማግሌዎችን አዘጋጅተናል። ለቤተሰቦችሽ ትደውያለሽ። ሽማግሌዎችን ይቀበሏቸዋል” ብለው በእኔ ላይ ያጸቀዱትን ውሳኔ ነገሩኝ። ያዘዙኝን ለመፈጸም ወደ ቤተሰቦቼ ደወልኩ።
ቤተሰቦቼ መጥፋቴን አውቀው ስለነበር፤ ያወሩኝ የነበረው በድንጋጤ ነበር። የት እንዳለሁ ለማወቅ በጥያቄ እያጣደፉኝ ስልኩ ተዘጋ። እኔንም መልሰው ወደዚያች ክፍል አስገቡኝ።
በዚህ ምሽት ነበር በትንሿ መስኮት ወጥቼ ለማምለጥ የሞከርኩት። እዚህ ውሳኔ ላይ የደረስኩት ሌላ አማራጭ እንደሌለኝ በመረዳቴ ነው።
በራሱ ውሳኔ ሚስቱ ያደረገኝ ጠላፊ ግን ነጻ የመውጣት መፍጨርጨሬን የቆጠረው ክብሩ ላይ እንደተቃጣ ጥቃት ነበር። የማምለጥ ሙከራዬ ከሽፎ፤ ተሸክመው ወደ ቤት በሚመለስሱኝ ሰዓት በእልህ እሳት የነደዱ ዓይኖቹን አያቸው ነበር።
“እንዴት ታመልጫለሽ?... ልታዋርጂኝ ነው?... ከእጁ ሴት አመለጠች ልታስብዪኝ ነው?... ማንም ከእኔ እጅ አያመልጥም” ደጋግመው ከአፉ የሚወጡ ቃላት ነበሩ።
ተሸክመው ወደ ቤት የመለሱኝ ሰዎች ሳሎን ውስጥ እንደተቀመጡ ወዳመለጥኩባት ጨለማ ክፍል ይዞኝ ገባ። እንዳይሆንብኝ የፈራሁት ከባዱ ነገር ሊሆንብኝ ሆነ።
እዚያች ክፍል ውስጥ ተደፈርኩ።
ከባድ ነበር . . . በእልህ ነበር . . . ወንድነቱን ለማሳየት በትግል ነበር። አቅሜ ተፈተነ።
ራሴን በመጠበቅ ውስጥ ነበር ያቆየሁት። ከዚህ በፊት ወንድ አላውቅም ነበር። በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ለማግባት ዝግጅት ላይ ነበርኩ።
ከዚህ ድርጊት በኋላ ሲመሽ የሚሆነው እያሰብኩ ቀኑን ሙሉ ሳለቅስ እውላለሁ። በመሸ ቁጥር ወንድነቱን ይጠቀም ነበር።
“ምግብ በልታለች ወይ? ተጨንቃለች? እያለቀሰች ነው” የሚል ርህራሄ የለውም። በተደጋጋሚ ይደፍረኝ ነበር። ራሴን እስክስት ድረስ ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ ይጠቀመኝ ነበር።
ለቀናት በዚህ ሁኔታ ወስጥ እያለፍኩ ምንም ማድረግ አልቻልኩም። ቤት ውስጥ ያለው ሰው ሁሉ ተባብሮ ጨካኝ ሆኖብኛል። እጮሃለሁ፣ እርዳታ እጠይቃለሁ፤ ህመሜን የሚረዳ አልነበረም።
ሰው መሃል ሆኜ ሁሉም ሰው ጨካኝ ሆኖብኝ ነበር።
“ተው” የሚል ከልካይ፣ “ምን እየሆነች ነው?” የሚል ጠያቂ አልነበረም። በየቀኑ ብዙ ሰዎች ወደ ቤቱ ቢመጡም ስለ እኔ ሁኔታ ግድ አላላቸውም።
መሽቶ በነጋ ቁጥር ያስፈራል። እጠባበቅ የነበረው መውጣቴን ነው።

በአንዱ ቀን ምግብ እንድታበላኝ የተላከችን ልጅ “ያለንበት ሰፈር ምን ያባላል” ብዬ አግባብቼ ጠየቅኳት። “ቡርሳ” ብላ ነገረችኝ።
ይህንን ከነገረችኝ ከሰዓታት በኋላ እንዴት እንደሆነ በማላውቀው ሁኔታ አጠገቤ የተረሳ ስልክ አገኘሁ። ለሰከንዶች እጄ በገባው ስልክ “ቡርሳ” የሚል መልዕክት ወደ ቤተሰቦቼ ላክሁ። መልዕክቱን ከስልኩ ላይ አጠፋሁት።
ቤተሰቦቼ መልዕክቱ የደረሳቸው ለጉዳዩ ትኩረት የሚሰጥ አጥተው፤ በራሳቸው ላይ ታች በሚሉበት ጊዜ ነበር። መሥሪያ ቤት ውስጥ አብራኝ የምትሠራው ልጅ ስለ እኔ መጥፋት ስትጠየቅ “የኋላመብራት እንደወሰደኝ” በመናገሯ ጠላፊው የፖሊስ አባል እንደሆነ አውቀዋል። ጉዳዩ ይመለከታቸዋል ያሏቸው ቢሮዎችን ደጅ እየጠኑ ነበር።
በኢትዮ ቴሌኮም ትብብር መልዕክት የተላከበት ቁጥር አድራሻው “ቡርሳ” እንደሆነ አወቁ። መልዕክቱ ያለሁበት ቦታ ስም መሆኑን ስለተረዱ ያገኙትን መረጃ ለፖሊስ አቀረቡ።
በማግስቱ ምሽት ሁለት ሰዓት ገደማ ፖሊሶች እና ወንድሜ ቡርሳ ፖሊስ ጣቢያ ደረሱ። እስከ አራት ሰዓት ድረስ አጋቹን በምን ዓይነት መንገድ ይዘወት ነጻ እንደሚያወጡኝ እያቀዱ ነበር። የአካባቢውን ሰዎች አጠያይቀው ወደ ነበርኩበት ቤት ሲደርሱ ግን እኔም ሆነ ጠላፊዬ አልነበርንም።
የኋላመብራት፤ ፖሊሶች አካባቢው ላይ ስለመድረሳቸው አስቀድሞ መረጃ ደርሶት ነበር። እነሱ ወደ ቤቱ ከመድረሳቸው በፊት ከአካባቢው ይዞኝ ሸሽቷል። ሰውነቴ ቁስል ሆኖብኝ ብደክምም፤ ረጅም መንገድ በእግር እና በሞተር ሳይክል እንጓዝ ነበር።
በሽሽት ያስቀመጠኝ አካባቢ ላይ ፖሊሶች በተቃረቡ ቁጥር የሚያስፈሩ መንገዶችን በሌሊት፣ በጉም እንድጓዝ ተገድጄ ነበር። ምንም እንኳ የርሃብ ስሜት ባይሰማኝም፤ እየተመገብኩ ስላልነበር ሰውነቴ ዝሏል።
በጣም በሚያሰቅቀው ደግሞ በዚያ ሁኔታ ውስጥ ሆኜ እንኳ ወንድነቱን ይጠቀም ነበር። እኔ ላይ ስቃዩን በማብዛት ቤተሰቦቼ ጋር ደውዬ “ሽማግሌ ተቀበሉ፤ የሚሏችሁን አድርጉ” ብዬ እንድናገር ይደረግ ነበር።

ቀናት እየገፉ፣ የእኔም ድምፅ እየጠፋ ሲመጣ ቤተሰቦቼ በተጠለፍኩ በሰባተኛው ቀን ጉዳዩን ወደ ማኅበራዊ ሚዲያ አወጡት። ጉዳዩ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ መውጣቱ እና መነጋገሪያ መሆኑ ፖሊሶች በጠላፊው ላይ ጫና እንዲፈጥሩ አደረጋቸው። የየኋላመብራት ቤተሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋል ጀመሩ።
እነዚህ የፖሊስ እርምጃዎች እርሱ ላይ ጫና ስለፈጠረ ሽማግሌዎች ተሰብስበው ጠለፋውን እንድቀበል ሊያግባቡኝ ሞከሩ። ለማሳመን ሲያቅታቸው፤ “እንለቅሻለን፣ ወደ ቤተሰቦችሽ ትሄጃለሽ። ከዚያ ግን በእርቅ ያልቃል” አሉኝ። ጉዳዩ በእርቅ እንደሚያልቅ ለማረጋጋጥ መሃላ እንደምፈፅም አስረዱኝ።
የመሃላ ሥነ ሥርዓቱ በንጋታው ጠዋት እንዲፈጸም ተቀጥሮ እያለ ፖሊሶች ወደነበርኩበት ከተማ እንደደረሱ ለየኋላመብራት መረጃ ደረሰው። እኔን ቤት ውስጥ ትቶኝ ሸሸ።
በማግስቱ ሌሎቹ ሰዎች የትራንስፖርት ብር አስይዘው ወደ መናኸሪያ ወሰዱኝ። እንዴት የተለያዩ መኪናዎችን ተሳፍሬ ሐዋሳ ከተማ እንደምደርስ ነገሩኝ። ሐዋሳ ከተማ ስቃረብ ለቤተሰቦቼ እንድደውል ሲም ሰጥተው ለቀቁኝ።
ሰውነቴም፣ አዕምሮዬም አቅማቸውን ስጨረሱ አድርጊ የሚሉኝን አደርግ ነበር። በደመነፍስ ጽፈው በሰጡኝ መሠረት ሦስት መናኸሪያዎች ውስጥ እየወረድኩ፣ እየተሳፈርኩ ወደ ሐዋሳ ተቃረብኩ። ቤተሰቦቼ ጋር ደውዬ “ተለቅቄያለሁ እየመጣሁ ነው፤ ሐዋሳ መግቢያ ላይ ጠብቁኝ” አልኩ።
ሐዋሳ መግቢያ ላይ ስደርስ ከባድ ፍተሻ ነበር። ብዙ የፖሊስ መኪኖች ቆመው፣ የሚመጣው ሰው ሁሉ ከመኪና እየወረደ ይፈተሻል። የነበርኩበት መኪናም ቆሞ ስወርድ ፖሊሶች ጠሩኝ።
“የምንፈልገው አንቺን አይደል እንዴ” ብለው ከጎን እና ከጎን እንደ ወንጀለኛ ይዘው የፖሊስ መኪና ውስጥ ሊያስገቡኝ ሲሉ “ቤተሰቦቼን ሳላገኝ አልገባም” አልኩ። በስልክ አገናኝተውኝ፤ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ወሰዱኝ።

ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ ባለሥልጣናት እና የፖሊስ ኃላፊዎች ተሰብስበው ከየት እንደመጣሁ፣ እንዴት እንደተለቀቅኩ ጠየቁኝ። የተነሳሁበትን ቦታ እንደማላውቅ አስረድቼ አቆራርጬ የመጣሁባቸውን ቦታዎች ነገርኳቸው።

ELIAS MESERET

18 Nov, 08:31


ከዚያ በኋላ ወደ ማረፊያ ክፍል ላኩኝ። ከትንሽ ቆይታ በኋላ ደግሞ መልሰው ጠሩኝ።
“ያገኘንሽ እኛ ነን። ከተለቀቅሽበት ቦታ ጀምሮ እየተከታተልንሽ ነበር። ሐዋሳ እስከምትገቢ የጠበቅነው ሌላ ግርግር ላለመፍጠር ነው” አሉኝ። እኔ ወደ ሐዋሳ ስመጣ እነሱ ካሳፈሩን በተጨማሪ በራሴ ሁለት መናኸሪያዎችን አቋርጫለሁ። ጉዞ የጀመርኩት መኪና እስኪሞላ እየጠበቅኩ ነበር።
የመጀመሪያው መናኸሪያ ላይ “ግርግር ላለመፍጠር ነው” ተብሎ ከታሰበ ቀጣዮቹ ሁለቱ መናኸሪያዎች ላይ ራሳቸው ፖሊሶች ይዘውኝ ሊመጡ ይችሉ ነበር።
ኃላፊዎቹ ይህንን ብለውኝ ወደ ማረፊያ ክፍሉ ተመለስኩ። ትንሽ ቆይቶ ወንድሜ ዜና ሲሰማ “በተቀናጀ ኦፕሬሽን እሷን ይዘናት እርሱ ጫካ ገባ” ይላል። እኔ የወጣሁት ግን ተሸኝቼ ነበር።
ቆይቶ ወደ ሆስፒታል ተወስጄ ምርመራ ተደረገልኝ። ምርመራው ሲያበቃ አብረውኝ የነበሩትን የፖሊስ አባላትን ወደ ቤቴ ለመሄድ እንዲለቁኝ ብጠይቅም ምላሻቸው እንደጠበቅሁት አልነበረም። ቃል መስጠት እንዳለብኝ ነግረው ወደ ጣቢያው መለሱኝ። ፍራሽ የተነጠፈባት አንዲት ቢሮ መሰል ክፍል ውስጥ አስገቡኝ።
ደጅ ላይ ወንድ እና ሴት ጥበቃዎች በተደረገበት በዚያ ክፍል ውስጥ ለአራት ቀናት ቆየሁ። ከክፍሉ መውጣት አልችልም ነበር። መጸዳጃ ቤት የምሄደው በፖሊሶች ታጅቤ ነው። ወደ ክፍሉ የሚገቡ ሰዎችን የሚፈቅዱ እና የሚከለክሉት ፖሊሶች ናቸው።
በራሴ ፍቃድ እዚያ ክፍል ውስጥ ያደርኩት በአራተኛው ዕለት ብቻ ነበር። በዕለቱም ያደርኩት ከቀኑ አስር ሰዓት እንድወጣ ሲነገረኝ ወደ ቤተሰቦቼ ቤት የምመለስበት ትራንስፖርት ባለማግኘቴ ብቻ ነበር።
ጠለፋ እና አስገድዶ መድፈር የፈጸመብኝ ዋና ሳጅን የኋላመብራት ወልደማርያም በቁጥጥር ስር የዋለው እኔ ከተለቀቅኩ ከአምስት ቀናት በኋላ ነበር። ከሰባት ወራት በኋላ ደግሞ የሐዋሳ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የሴቶች እና ሕጻናት ችሎት በ16 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ወሰነ

ቅጣቱ ከተላለፈ ከሦስት ወራት በኋላ የፍርድ ቤት ሰነዶችን ለማግኘት በምጠይቅበት ጊዜ ግን በማላውቀው ሁኔታ የተሰጠው ፍርድ መሻሻሉን ሰማሁ። የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የሰጠው የ16 ዓመት ፍርድ፤ በይግባኝ ወደ አስር ዓመት ተቀንሷል። ይህ ውሳኔ መቼ እና እንዴት እንደተሻሻለ አላወቅኩም። ይህ ውሳኔ ሲተላለፍ ያሳወቀኝ ዐቃቤ ሕግም አልነበረም።
የመጀመሪያውን ውሳኔ የተቀበልኩት “የሕግ ባለሙያዎች መሄድ ያለባቸውን ርቀት ተጉዘዋል” ብዬ በማሰብ ነበር። በሕግ ቋንቋ “ተመጣጣኝ ቅጣት” የሚል አገላለጽ ቢኖርም፤ በየትኛውም ሁኔታ ለተጠቂዋ ተመጣጣኝ የሚሆን ቅጣት ይኖራል ብዬ አላስብም።
ብዙ ሰው የሚያስተውለው በዚያች ደቂቃ በመደፈር ውስጥ ያለውን ስቃይ ብቻ ነው። ከዚያ በኋላ ያለውን ሥነ ልቦናዊ ጉዳት የማያስተውሉ ብዙዎች ናቸው። መደፈር የዚያች ደቂቃ ጉዳይ ብቻ የሚሆነው ምናልባት ለአጥቂው ነው። ለተጠቂዋ ግን እድሜ ልኳን የሚከተላት ህመም ነው።
በሥነ ልቦናዊ ጉዳት በጣም ተሰቃይቻለሁ። እስካሁን ድረስ ህክምና እከታተላለሁ።
የተጋፈጥኩት የእነዚያ የዘጠኝ ቀናት ስቃይ ብቻ አይደለም። እነዚያ ቀናት ምናልባትም ወደፊትም ጭምር ሕይወቴን የሚጎዳ ጠባሳ ትተውብኛል። የደረሰብኝ ጥቃት ማኅበራዊ ግንኙነቴን፣ መንፈሳዊ ሕይወቴን፣ ለራሴ ያለኝን አመለካከት ጭምር ጎድቶብኛል።
ነጻ እንደወጣሁ ቀጥታ ወደ ሥነ ልቦና ህክምና ነበር ያመራሁት። በዚያ ፍጥነት ህክምና አግኝቼ እንኳ እስከ አሁን የምሰቃይባቸው፣ በጣም ብዙ ቀኖቼን በለቅሶ እንዳሳልፍ ያስገደዱኝ ህመሞች አሉኝ።

ቤተሰቦቼ በእኔ ጉዳይ ከመጠን በላይ ተጨንቀው ስለነበር እነሱ ላይ ሌላ ጭንቀት እንዳልሆን፤ ተደብቄ ብዙ ከባድ ቀናትን አሳልፌያለሁ። ከጥቃቱ በፊት የነበረችውን ፀጋ መልሶ ማግኘት ቀርቶ፤ ትንሽ ጠንከር ያለችውን ፀጋ ለማግኘት ታግያለሁ።
ይህንን ሁሉ እያሳለፍኩ ባለሁበት ምንም ሳይነገረኝ የመጀመሪያው ውሳኔ በመቀየሩ እርዳታ ፍለጋ ወደ ማኅበራዊ ሚዲያ ወጣሁ። ፍትህ መዛባቱን እንዲሁም ከዚያም በፊት ታስሬ እንደነበር ጠቅሼ ቲክ ቶክ ላይ ቪድዮ ለቀቅኩ። የእኔ ጉዳይ በድጋሚ ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ትኩረት ሳበ።
የለቀቅኩት ቪድዮ ግን በሐዋሳ ከተማ ፖሊስ ዘንድ በመልካም አልታየም። የሐዋሳ ከተማ ፖሊስ “የከተማውን ስም እያጠፋሽ ነው። ከድርጊትሽ ተቆጠቢ” የሚል መግለጫ አወጣ።
የተናገርኩት የደረሰብኝን ነው። የጠየቅሁት ስለ ተዛባብኝ ፍትህ ነው። ከዚህ ንግግሬ በኋላ ተጨማሪ ነገር ብናገር . . . ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶኛል። በመጠበቅ፣ ቃል በመቀበል ሰበብ መልሰው ወደ እስር ሊያስገቡኝ ይችላሉ ብዬ ሰጋሁ ።
ይብዛም ይነስ በተደረገልኝ ህክምና፣ እግዚአብሔርም ረድቶኝ በተወሰነ ጥንካሬ ላይ ነኝ። ከዚህ በኋላ እንደ እኔ ጥቃት ለደረሰባቸው ሴቶች ድምፅ መሆን፣ ክፍተቶችን መናገር አለብኝ።
ይህንን ሳደርግ ግን የሚከተለኝ ነገር አስቀድሞ በማስጠንቀቂያ ከተነገረኝ፣ ከዚያ በላይ ሀገር ውስጥ መቆየት አልችም ነበር። ያገኘሁትን አጋጣሚ ተጠቅሜ ከሀገር ለመውጣት ተገደድኩ።
ከሀገር ከወጣሁ ግንኙነት የፈጠርኩት ከዓለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋም አምነስቲ ኢንተርናሽናል ጋር ነበር። በእነርሱም አማካኝነት የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ከለላ ፕሮግራም ውስጥ ታቅፌ ሥልጠናዎችን እየወሰድኩ እና ድጋፍ እያገኘሁ ነው።
ከባዱን ጊዜ አልፌያለሁ። ጉዳቴ ጨርሶ ባይሽርም በተደረገልኝ እገዛ ቢያንስ አሁን እዚህ ቆሜያለሁ። ከዚህ በኋላ ግን ለብዙ ሺህዎች ድምፅ እሆናለሁ። የመሰበር ምልክት መሆን አልፈልግም። አልፌ አሳያለሁ። እጠነክራለሁ። በጥቃት ውስጥ ላለፉ እና ለሚያልፉ ሴቶች የጥንካሬ ምሳሌ እሆናለሁ።

ሴት ልጅ ከተደፈረች በኋላ “ዋጋዋ እንደበፊቱ አይደለም” ተብሎ ይታሰባል። ተፈትኖ የወጣ ወርቅ ግን ምን ያህል ውድ እንደሆነ ማሳየት አለብን።
በሌላ አቅጣጫ ሳይሆን በራሱ በሰበረኝ ነገር ላይ እጠነክራለሁ። እኔን የሰበረኝ መደፈር ነው። እኔን የሰበረኝ ፆታዊ ጥቃት ነው። በዚሁ እኔን በመታኝ ነገር ላይ ለብዙዎች መፍትሔ እሆናለሁ።
ለየትኛውም ፆታዊ ጥቃት “እምቢ” በማለት ውስጥ ያለው ማሸነፍ የሚታይበት ሕይወት እቀጥላለሁ ብዬ አስባለሁ። የደረሰብኝን ነገር፣ ያለፉኩበትን ሁኔታ የሚያሳይም መፅሀፍ እያዘጋጀን ነው።
ከዚህ በፊት በነበሩ ጠለፋዎች፣ ፆታዊ ጥቃቶች ላይ ተገቢው ቅጣት ተሰጥቶ ቢሆን ኖሮ በእኔ ላይ የደረሰው አይፈጸምም ነበር። እነዚህ የሕግ ክፍተቶች ለእኔ ጥቃት ምክንያት ሆነዋል።
ከዚህ በኋላ እነዚህን ክፍተቶች ለመቅረፍ ለሴቶች መብት እሟገታለሁ። በአሁኑ ሰዓት የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ለመሆን የሚያስችሉኝን ሥልጠናዎች እየወሰድኩ ነው።
የሰብዓዊ መብት ተሟጋችነትን ለራሴ በመቆም ጀምሬያለሁ። ከዚህ በኋላ ፍላጎቴ፤ በእኔ የደረሰው ነገር በሌሎች ኢትዮጵያውያን ሴት እህቶቼ ላይ እንዳይደርስ መሟገት ነው።
* ፀጋ በላቸው ከጠለፋ የወጣችበትን መንገድ በተመለከተ ከቢቢሲ ጥያቄ የቀረበለት የሲዳማ ክልል ሠላም እና ፀጥታ ቢሮ በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥቧል። የቢሮው ኃላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቲዮስ፤ በወቅቱ ድርጊቱ ጋር የተያያዙ መረጃዎች መስጠታቸውን አስታውሰው፤ “በድጋሚ የምንሰጠው ማብራሪያ የለም” ብለዋል።

Via BBC Amharic

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

04 Nov, 19:18


አንዳንዴ የሀገራችን መሪዎች ለጥቂት ደቂቃ በኢንቦክስ የሚላኩ ቅሬታዎችን፣ ጥቆማዎችን፣ የእርዱኝ ተማፅኖን እና የድረሱልኝ ጥሪን አብረውኝ ቁጭ ብለው ባዩት ብዬ እመኛለሁ

ይሄ ከባለፈው አንድ እና ሁለት ቀን በጥቂቱ ነው።

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

04 Nov, 18:20


ኢትዮጵያ ካላት 120 ሚልዮን ህዝብ 86 ሚልየኑ በድህነት ውስጥ እንደሚኖር አንድ ጥናት አረጋገጠ

(መሠረት ሚድያ)-  የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና ኦክስፎርድ በጋራ ያዘጋጁት ይህ ጥናት እንደጠቆመው ህንድ 234 ሚልዮን በድህነት የሚኖሩ ዜጎችን በመያዝ በአለም በአንደኝነት ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።

ፓኪስታን በ93 ሚልዮን ሁለተኛ፣ ኢትዮጵያ በ86 ሚልዮን ሶስተኛ፣ ናይጄርያ በ74 ሚልዮን አራተኛ እንዲሁም ዴሞክራቲክ ኮንጎ በ66 ሚልዮን አምስተኛ ደረጃን ይዘዋል።

እነዚህ አምስት ሀገራት ከአለማችን 1.1 ቢልዮን ድሀ ህዝቦች መሀል 48 ፐርሰንቱን እንደሚይዙ የተጠቀሰ ሲሆን ከእነዚህ የአለማችን ህዝቦች መሀል 455 ሚልዮኑ ጦርነት በሚካሄድባቸው ሀገራት ይገኛሉ ብሏል።

ኢትዮጵያ ካላት 120 ሚልዮን ህዝብ 86 ሚልየኑ ወይም 72 ፐርሰንት ገደማው በድህነት ውስጥ እንደሚኖር ቢረጋገጥም ከመንግስት የሚወጡ ተከታታይ ሪፖርቶች ኢኮኖሚው እንዳደገ የሚጠቁሙ ናቸው።

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

04 Nov, 18:16


በ1.8 ቢልየን ብር ከቦታቸው ሳይፈናቀሉ ቤት ይሰራላችኋል ተብለው የነበሩት የለገሀል ኤግል ሂልስ ፕሮጀክት ሳይት ነዋሪዎች በሶስት ቀን ቤታቸውን ለቀው እንዲወጡ ተነገራቸው

(መሠረት ሚድያ)- ከስድስት አመት በፊት የለገሀር ኤግል ሂልስ ፕሮጀክት የመሰረት ድንጋይ ሲጣል በ1.8 ቢልዮን ብር የመኖርያ ቤት ተገንብቶላቸው እዛው እንደሚኖሩ ተነግሯቸው የነበሩት የአካባቢው ነዋሪዎች በሶስት ቀን ውስጥ እቃቸው አውጥተው የካዛንችስ ነዋሪዎች ወደሄዱበት ቦታ እንዲሄዱ እንደተነገራቸው ገለፁ።

"ዶ/ር አብይ የመሰረት ድንጋይ ሲያስቀምጡ ባደረጉት ንግግር በአካባቢው ላይ እየኖሩ ለሚገኙ 1,650 አባወራዎች እዛው ፕሮጀክቱ አካባቢ ሰርተን በዘመናዊ ቤት ኑሮ እንዲኖሩ እናደርጋለን፣ ለዚህም የኤግል ሒልስ ባለቤቶች 1.8 ቢልየን ብር ሰጥተውናል ብለው ተናግረው ነበር" የሚሉት ነዋሪዎች አሁን አዲስ ዱብዳ የሆነ መረጃ ተነግሮናል ብለዋል (ለንግግሩ ቪድዮውን ይመልከቱ)።

ባሳለፍነው ቅዳሜ ጥቅምት 23/2017 ዓ/ም የቂርቆስ ክፍለ ከተማ እና በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የወረዳ 10 የመሬት አስተዳደር ኃላፊዎች የተወሰኑ ነዋሪዎችን ሰብስበው በሶስት ቀናት ውስጥ እጣ አውጥታችሁ የካሳንችስ ነዋሪዎች የሔዱበት አካባቢ ትገባላችሁ፣ ተዘጋጁ ብለው ለነዋሪው ማስጠንቀቂያ ሰጥተው እንደሄዱ ለመሠረት ሚድያ የደረሰው ጥቆማ ያሳያል።

"ነዋሪው በጣም ተደናግጧል፣ እስቲ ብትዘግቡልን እና ህዝብ ቢያውቅልን ስንል አደራ እንላለን" ያሉት ነዋሪዎች ተስፋ አድርገው ለአመታት ቢጠብቁም ቃል ታጥፎ ከከተማ ውጭ እንዲሄዱ መደረጋቸው እንዳሳዘናቸው ተናግረዋል።

ይህ ከአልሚው ኢግል ለተነሺዎች ቤት መገንቢያ ተብሎ ተሰጥቶ የነበረው 1.8 ቢልዮን ብር የት እንደደረሰ በመንግስት የተባለ ነገር የለም።

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

04 Nov, 11:31


#ከዜናዎቻችን| በቤተመንግስት ተገኘ ስለተባለው 400 ኪ/ግ ወርቅ ተጨማሪ መረጃ ለመሠረት ሚድያ ደርሷል

(መሠረት ሚድያ)- ጠ/ሚር አብይ አህመድ ባሳለፍነው ሳምንት ሀሙስ እለት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደራሴዎች ማብራርያ በሰጡበት ወቅት የቤተመንግስት እድሳት በተደረገበት ወቅት ተቆልፎበት ተቀምጦ የነበረ 400 ኪ/ግ ወርቅ ለብሄራዊ ባንክ ገቢ እንደተደረገ ለፓርላማ አባላት መናገራቸው ይታወሳል።

"ባደረግነው የቤተመንግስት ዕድሳት ተቆልፎበት የተቀመጠ 400 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ አስገብተናል" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ "ወርቁ የፊውዳል አይደለም፣ የኢትዮጵያ ነው" ከማለት ውጪ ዝርዝር መረጃ ባያቀርቡም በቅርስ ዙርያ የሚሰሩ ሰዎችን እና መላው ኢትዮጵያውያንን ግን ጉዳዩ ማስደንገጡን ቀጥሏል።

"ከወርቅ፣ ከብር እና ከነሀስ የተሰሩ በርካታ የሀገር ሀብት የሆኑ ታሪካዊ ቅርሶች በትልቁ ቤተመንግስት ይገኛሉ" ያሉት አንድ የቅርስ ጥበቃ ምንጫችን እነዚህ ቅርሶች የንጉሳዊ ስርዐቱን በጣለው በደርግ ስርዐት ወቅት ጭምር የኢትዮጵያ ታሪክ አካል እንደሆኑ ታምኖባቸው፣ ሌሎቹ ደግሞ ተደብቀው ቆይተው አሁን ላለው ትውልድ በቅብብሎሽ የደረሱ ናቸው ብለዋል።

"ደርግ ከሶቪየት ህብረት የጦር መሳርያ እንጂ ገንዘብ አያገኝም ነበር፣ ብዙ የገንዘብ ችግር ነበረበት ነገር ግን እነዚህ ቅርሶች እንዳሉ እያወቀ ወደ ሽያጭ አልሄደም" ያሉት እኚህ ምንጭ ጉዳዩ እንዳስደነገጣቸው ተናግረዋል። 

ታድያ እነዚህ እንደ ተራ ወርቅ ለሽያጭ ሊቀርቡ የማይችሉ ታሪካዊ ቅርሶች አሁን ላይ ለገበያ እንዲውሉ ወደ ብሄራዊ ባንክ መላካቸው እጅግ እንዳሳዘናቸው እና እንዳስደነገጣቸው ጨምረው ገልፀው ይህ ከታሪክ ማጥፋት የማይተናነስ ድርጊት ነው ብለውታል።

ሌላ ስሜ አይጠቀስ ያሉ የመረጃ ምንጫችን ደግሞ ለብሄራዊ ባንክ ቀረበ የተባለው ወርቅ 400 ኪ/ግ ነው የመባሉን ትክክለኛነቱን በመጠራጠር ምንም ያህል ይሁን ምን ድርጊቱ አሳዛኝ ነው ብለዋል።

"ምናልባት 40 ኪ/ግ ለማለት ተፈልጎ እንደሆን እንጃ፣ በደርጉ ፍቅረስላሴ ወግደረስ መጽሀፍ ላይም የእነዚህ ወርቆች መገኘት ተገልጿል፣ መጠኑ ግን እንደተባለው አይደለም" ያሉት እኚህ ቤተመንግስት በአንድ ወቅት የሰሩ ግለሰብ አብዛኛው ከብር የተሰራ፣ ሌላው ከነሀስ የተሰራ የቤተመንግስት መገልገያ በብዛት እንደሚገኝ ያብራራሉ።

"እርግጥ ነው በግዢ እና ከሌሎች መንግስታት በስጦታ መልክ ሀገር ውስጥ ያሉ በርካታ የወርቅ ቁሳቁስ እና መገልገያዎችም አሉ፣ ከሁሉም ያስደነገጠኝ ግን ወደ ሙዚየም ሳይሆን ወደ ብሄራዊ ባንክ ተላኩ መባሉ ነው" በማለት ሀዘኔታ በተሞላበት ሁኔታ ተናግረዋል።

በዚህ ዙርያ ያነጋገርናቸው አንድ ሌላ የቅርስ ባለሙያ ጉዳዩን እንደሚያውቁ በመጥቀስ "ማንም ደፍሮ 'ለምን?' የሚል የለም፣ ማንም ይሄ የሀገር ቅርስ ነው አይነካ አይልም" በማለት በጉዳዩ ዙርያ የሚሞግት አካል እንኳን እንደሌለ በአፅንኦት ተናግረዋል።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

03 Nov, 17:36


#Update ቅድም ለፍለጋ ያጋራሁትን የህፃን ልጅ ፎቶ ተከትሎ በርካታ በዱባይ እና በኢትዮጵያ የሚገኙ ሰዎች መረጃ ሰጥተዋል

እናት ልጇን ካለ ጋብቻ ዱባይ ውስጥ ከወለደች በኋላ ለአንድ አመት በክፍሏ በመደበቅ (ክትባትም ሳታስከትብ) አቆይታት ነበር። አባትም ስላልታወቀ ፓስፖርቷን ተነጥቃ በአንድ የመውጫ (exit) ዶክመንት ወደ ኢትዮጵያ ከሶስት ቀን በፊት ተጠርዛ ተላከች። ከዛም ነው ትናንት ምሽት ልጇን ሆሳዕና ውስጥ የጣለቻት።

"ቤተሰቦቼ ይገሉኛል ስትል ሰምተናል" ብለው ከዱባይ አንዳንድ ጉዳዩን የሚያውቁ ሰዎች ተናግረዋል።

ከዚ በሁዋላ ጉዳዩ እና የተገኘው ዶክመንት ለፖሊስ ይተላለፋል፣ የግለሰቧም ማንነት ስለታወቀ የሆሳዕና ፖሊስ በቅርቡ እንደሚያሳውቀን ተስፋ አረጋለሁ።

መልእክቱን አይታችሁ ላስቀመጥኳቸው ቁጥሮች (ለሚሚ እና ለአቶ ምስክር ሺበሺ) በመደወል ላሳወቃችሁ ሁሉ ምስጋና ይድረሳችሁ።

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

30 Oct, 16:18


የዛሬ የመሠረት ሚድያ ዘገባዎች:

1. የፋኖ አመራሮችን ኢላማ ያደረጉ የድሮን ጥቃቶች ተፈፅመዋል? ዝርዝሩን ይዘናል

2. በአለም ገና ከተማ አንድ አነጋጋሪ ዘረፋ ተፈፅሟል፣ በዚህ ዙርያም መረጃ አለን

3. የጤና ባለሙያዋን በባህር ዳር ምን አጋጠማት?

4. "ሙሉ የከተማ ህዝብ እያስለቀሰ ነው" የተባለለት የሰሜን ሸዋ፣ ደራ ወረዳ ሰሞንኛ ግጭት

5. በአዳማ ከተማ ተጧጡፎ ስለቀጠለው የፀጥታ አካላት ድርጊት

6. በጫንጮ ከተማ ስለተፈፀመው እገታ እና ከፍቼ ከተማ ስለተሰማው ክስተት፣ እንዲሁም

7. ብዙዎችን እያነጋገረ ስላለው የመከላከያ አመሯሯ ንግግር መረጃዎችን ይዘናል። በዩትዩብ ቻናላችን ማምሻውን ይጠብቁን ⤵️

https://youtube.com/@meseretmedianews?si=u0Wqzt1fh_0Bo_Kx

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

30 Oct, 16:14


#ከዜናዎቻችን| የኮሪደር ፕሮጀክት ለአምስት አመት እንደሚቆይ ተረጋገጠ

(መሠረት ሚድያ)- አነጋጋሪው እና ለበርካቶች ከቤት እና ከስራ መፈናቀል ምክንያት እየሆነ የሚነገርለት ፕሮጀክቱ በአዲስ አበባ በርካታ ስፍራዎች፣ አሁን በቅርቡ ደግሞ በክልል ከተሞች እና በገጠራማ ስፍራዎች ጭምር እየተተገበረ ስላለው ወይም ሊተገበር እቅድ እየተያዘለት እንደሆነ ይታወቃል።

መሠረት ሚድያ የደረሰው አዲስ መረጃ እንደሚጠቁመው የኮሪደር ፕሮጀክት ለአምስት አመት የሚቆይ እና በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ያሉ አብዛኞቹን የጭቃ ቤቶች በማንሳት በአዳዲስ የፕሮጀክቶች ሳይቶች ለመተካት ያለመ መሆኑ ታውቋል።

የኮሪደር ልማት ሥራው ህዝብ በጉጉት ሲጠብቀው የነበረ እና ካረጁ እና ከተጎሳቆሉ ቤቶች ህብረተሰቡን አውጥቶ የተሻለ አኗኗርን የሚያስገኝ እንደሆነ በመንግስት ተደጋግሞ ይነገራል።

የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቱ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለይ በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች መካሄድ ከጀመረ በኋላ መንገዶች አምረዋል፣ ህንፃዎች አሸብርቀዋል፣ አዳዲስ የመዝናኛ እና ማረፍያ ስፍራዎች ተገንብተዋል።

ወትሮውን ጽዳት የሚጎድላት ከተማ ተደርጋ ስትወሰድ የነበረችው የአፍሪካ መዲናዋ አዲስ አበባ እንደስሟ አዲስ የሚያስመስሏት ስራዎች ተሰርተዋል፣ ይህን ደግሞ ፕሮጀክቶቹን በአንድም ይሁን በሌላ መልኩ የሚተቹ እና የሚነቅፉ ሁሉ የሚመሰክሩት ሀቅ ነው።

ይሁንና ከዚህ ባለ ብዙ ቢልዮን ብር ፕሮጀክት ጋር ተያይዞ እየተካሄዱ ያሉ በርካታ የመኖርያ ቤቶች፣ የህንፃዎች፣ የመንገዶች እና የመሰረተ ልማት አውታሮች ጭምር የጅምላ ፈረሳ የሀገራችንን ህዝብ በቅርብ አመታት ታይቶ በማይታወቅ ግርታ ውስጥ ከቶታል።

ነገ ተራው ደርሶኝ ፈራሹ ቤት የኔ ይሆን ወይ? ነገ የተከራየሁት ቤት ፈርሶ መንገድ ዳር እወድቅ ይሆን ወይ፣ የስራ ወይም የንግድ ቦታዬ ፈርሶ ቤተሰቤን ማስተዳደር ያቅተኝ ይሆን ወይ? የሚሉ ጥያቄዎች የህዝብ የእለት ተእለት ጭንቀት፣ ሮሮ እና ሀሳብ ከሆኑ ሰነባብተዋል። 

ይህ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀሳብ አመንጪነት እንደተጀመረ ተደጋግሞ የሚነገርለት የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ከአዲስ አበባ ተሻግሮ እንደ ቢሾፍቱ፣ አዳማ፣ መቀሌ፣ ጅማ፣ ሀረር፣ ድሬዳዋ፣ ሀዋሳ ወዘተ ያሉ ከተሞች መስፋፋትም ጀምሯል።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

30 Oct, 16:11


#ከዜናዎቻችን| ባንዲራ ይዘው የኢትዮጵያን ብሄራዊ መዝሙር ሲዘምሩ የነበሩ ታዳጊዎች ከትምህርት ቤታቸው ታፍሰው ተወስደው እንደተደበደቡ ታወቀ

(መሠረት ሚድያ)- ጀሞ 1 የሚገኘው የሳውዝ ዌስት አካዳሚ ተማሪዎች የሰንደቅ አላማ ቀንን ለማክበር እያንዳንዳቸው አረንጓዴ፣ ቢጫ እና ቀይ ለየብቻ፣  ማለትም አንዱ ተማሪ አረንጓዴ ሌላው ቀይ ሌላው ቢጫ ለብሰው እና የጥላሁን ገሰሰን "ኢትዮጵያ" መዝሙር ሲዘምሩ ቆይተው ኋላ ላይ ግን ለምን ይህን ቀለም ያለበት ልብስ ለበሳችሁ ብለው የፀጥታ አካላት የጅምላ እስር እንደፈፀሙባቸው መሠረት ሚድያ ያሰባሰበው መረጃ ያሳያል።

በሶስት መኪናዎች ተጭነው የመጡት የፖሊስ አባላት ባለ ኮከቡን የኢትዮጵያ ባንዲራ ጭምር ይዘው ሲዘምሩ የነበሩ 30 ገደማ ታዳጊ ተማሪዎችን ጭነው በመውሰድ በቁጥጥር ስር ካዋሉ በኋላ ድብደባ እንደፈፀሙባቸው ታውቋል።

ከተደበደቡት ተማሪዎች መሀል ቢያንስ ሁለቱ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ምንጮቻችን ጠቁመዋል። 

እነዚህ የ10ኛ ፣የ11ኛ እና የ12 ኛ ክፍል ተማሪዎች እንዲሁም ዳይሬክተሩ ሀሙስ እለት ካሰሩዋቸው በኋለ አርብ የተወሰኑትን ከፈቱዋቸው በኋላ ዳይሬክተሩን እና የተወሰኑ ተማሪዎች አስረው አቆይተዋል ተብሏል።

"የራሱን የመንግስት በአል ማክበር ያሳስራል ወይ? በጣም ነው ያዘንነው" ያሉት አስተያየት ሰጪዎች የኢትዮጵያ ህዝብ ልጆቻችን ላይ የደረሰውን ግፍ እና በደል ይወቅልን ብለዋል።

ባንዲራ ከመልበሳቸው ጀርባ የሆነ አላማ አለ በሚል ጥርጣሬ እስሩ እና ድብደባው እንደተፈፀመ ምንጮቻችን ጠቅሰው የወረዳ አመራሮች የልጆቻቸውን ከእስር መፈታት ሊጠይቁ ሲሄዱ "የፈለገ በክላሽ መግጠም ይችላል፣ ምላሽ እንሰጣለን" የሚል አሳዛኝ ምላሽ እንደተሰጣቸው ተናግረዋል።

ማርያም ሰፈር በሚገኘው ፖሊስ ጣብያ በታዳጊዎቹ ላይ የተፈፀመው ድብደባ ልባቸውን የሰበረው ወላጆች "ፖለቲካ ምንድን ነው ቢባሉ እንኳን ምላሽ የሌላቸውን የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች አጉሮ መደብደብ የግፍም ግፍ ነው" ብለው በምሬት ተናግረዋል።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

30 Oct, 16:09


#ከዜናዎቻችን| ኢትዮጵያ ውስጥ 10 ቢልየን ብር የሚፈጅ የጦር ሙዚየም ሊገነባ መሆኑ ተሰምቷል

(መሠረት ሚድያ)- ከ2010 ጀምሮ ኢትዮጵያ የጦር ሙዚየም እንዲኖራት እቅድ ተይዞ እንደነበር ለዋልታ የተናገሩት ብርጋዲየር ጀነራል ደሳለኝ ዳቼ አሁን ላይ ይህ በርካታ ቢልዮን ብሮችን ይፈጃል የተባለ ሙዚየም ዲዛይን ተሰርቶ እንዳለቀ ተናግረዋል።

የመከላከያ ወታደራዊ ቅርስ ጥናት እና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር እና ከፍተኛ አማካሪ የሆኑት ዶ/ር ሀሰን ሰይድ በበኩላቸው የሙዚየሙ ግንባታ ለዘመናዊ መከላከያ ግንባታ አበርክቶ አለው በሚል እሳቤ ሀሳቡ እንደቀረበ ጠቁመው ዘመናዊ መከላከያ ከታሪክ መማር ስላለበት ፕሮጀክቱ አስፈላጊ ነው ብለዋል።

ዶ/ር ሀሰን አክለውም ሙዚየሙ ከአክሱም ዘመነ መንግስት ጀምሮ እስከ አሁን ያለውን የመከላከያ ታሪክ ከትቦ የሚይዝ መሆኑን አስረድተው ለንግባታው 7 ሄክታር መሬት መያዙን ተናግረዋል።

"ከዚህ በኋላ ፈንድ አፈላልጎ ወደ ስራ መግባት ብቻ ይቀረናል" ያሉት ባለሙያው ገንዘቡ ከየት ከየት እንደሚገኝ ግን ከመግለፅ ተቆጥበዋል።

የስምንት አስርት አመታት ያህል ዕድሜ እንዳለው በሚነገርለት የዘመናዊ የኢትዮጵያ ሙዚየም ታሪክ ውስጥ ይዘቱና ትኩረቱ በሌሎች ዘርፎች ላይ በማድረጉ፣ ነባሩን የጦር ኃይሉን የሚያሳይ የገዘፈ ክንፍ እንኳን አልነበረውም ይባላል፡፡

በሌላ በኩል ከቅርብ ዓመታት ወዲህ መከላከያ ሚኒስቴር የራሱን የውትድርና ቅርስ ጥበቃ ማዕከልና ወታደራዊ ሙዚየም ለማቋቋም ሲጥር ታይቶ ነበር፡፡

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

30 Oct, 11:07


#ከዜናዎቻችን| በኢትዮጵያ እየተከሰተ ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ ለ10 ሺህ ገደማ ሰዎች የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ ስጋት እንደሆነ ተጠቆመ

(መሠረት ሚድያ)- 'Gelology Hub' በሚል የሚታወቀው እሳተ ገሞራዎችን እና የመሬት እንቅስቃሴዎችን በተመለከተ ትንታኔ የሚያቀርበው ድርጅት እንዳለው በአለም ዙርያ ትኩረት የተነፈገው ይህ አደገኛ ክስተት የእሳተ ገሞራ ፍንዳታን ሊያስከትል የመቻል እድሉ ከፍተኛ ነው።

በኢትዮጵያ እየተካሄዱ ያሉ ግጭቶች እና ጦርነቶች ይህ ተፈጥሮአዊ አደገኛ ክስተት ብዙ ትኩረት እንዳያገኝ አድርጎታል የሚለው Geology Hub ይህን መረጃ ለህዝብ ማድረስ የፈለገው የሰው ህይወት ለማትረፍ ነው ብሏል።

ከመስከረም ወር ጀምሮ ከፍተኛ የሆነ የቀለጠ አለት ክምችት እየታየ መሆኑን ገልጾ እስካሁን ከአደጋው አካባቢ 700 ገደማ ሰዎች እንዲነሱ መደረጉን ገልጿል።

በዚህ አደገኛ ስፍራ የሚገኙ 10 ሺህ ገደማ ሰዎች በአስቸኳይ ከስፍራው እንዲነሱ መደረግ እንዳለባቸው የሚገልፀው Gelology Hub ይህን ጉዳይ በዋሽንግተን ዲሲ ለሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እና ለአሜሪካው የጂኦሎጂካል ሰርቬይ ማሳወቁን ጨምሮ ጠቅሷል።

21 ኪ/ሜ ርዝመት ያለው ይህ የእሳተ ገሞራ ግፊት በመካከለኛ ኢትዮጵያ አዋሽ አካባቢ እንቅስቃሴው እንደቀጠለ የታወቀ ሲሆን ከዚህ ጋር ተያይዞ ከዚህ በፊት በአካባቢው ያልነበሩ አዳዲስ ሙቅ ውሀዎች መፍለቅ መጀመራቸውም ታውቋል።

ለአራተኛ ግዜ በአዋሽ ፈንታሌ እስከ 4 ነጥብ 7 ሬክተር ስኬል የተመዘገበ የተለያየ ደረጃ ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን ሠመራ ዩኒቨርሲቲ አስታውቆ ነበር።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

30 Oct, 11:06


#ከዜናዎቻችን| "በጽኑ የታመሙ ህሙማን ለተሻለ ህክምና ወደ ሌላ ቦታ መሄድ በመከልከሉ ያላቸው አማራጭ ሞትን ቤታቸው ሆኖ መጠባበቅ ሆኗል"

(መሠረት ሚድያ)- በአማራ ክልል በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ስር የሚገኙ እና በከፍተኛ ደረጃ በተፈጥሮ የተራቆቱ ተብለው የሚታወቁት ከ6 መቶ ሺህ በላይ የ4 ወረዳ ህዝብ ሙሉ ለሙሉ መድሀኒት፣ ምግብ እና ነዳጅን ጨምሮ ሸቀጣሸቀጦች እንዳይገባላቸው ተደርጎ ወባ እና ኮሌራን ጨምሮ በርሀብና በበሽታ ሰው እየሞተ እንደሚገኝ ታውቋል።

ምስራቅ በለሳ፣ ምዕራብ በለሳ እና ስላሪ ወረዳዎች አፋጣኝ መፍትሄ ካልተገኘላቸው ተጨማሪ ህዝብ እንዳያልቅ ስጋት እንዳላቸው ነዋሪዎች ተናግረዋል።

ሶስት ወር ሙሉ የትራንስፖርት ክልከላ ተደርጓል የሚሉት ነዋሪዎቹ ሰራተኛ ደሞዝ አልተከፈለውም፣ ህዝብ የሚበላው አጥቷል ብለዋል።

በሌላ በኩል በአማራ ክልል በተስፋፋው ጦርነት ምክንያት በጦርነቱ ከሚሞተው ህዝብ በተጨማሪ መንገድ በመዘጋቱ ምክንያት በህክምና እጦት የሚሞተው ሰው በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ መሆኑ ታውቋል።

እናቶች ቤት ለመውለድ ተገደው በወሊድ ምክንያት እየሞቱ መሆናቸውን እና ከባለፈው ነሀሴ ወር መጨረሻ ጀምሮ ከደቡብ ጎንደር አምስት ወረዳዎች (ማለትም ከእስቴ፣ አንዳቤት፣ ስማዳ፣ ሙጃ እና ታች ጋይንት) መከላከያ ለቆ የወጣ ሲሆን ላለፉት ሁለት ሳምንታት ደግሞ ወደ እነዚህ ወረዳዎች የሚደረግ ሁሉም አይነት ትራንስፖርት በፀጥታ ሀይሎች መከልከሉ ህዝቡ ለከፍተኛ ስቃይ መዳረጉ ታውቋል።

ወደ ቀጠናው ምንም ዓይነት የሸቀጥም ይሁን የመድሀኒትና እና ሌሎች የህክምና ግብአቶች መግባት ያልቻሉ ሲሆን በዚህም የመንግስት ሆስፒታሎች እና ጤና ጣቢያዎች እንዲሁም የግል ጤና ተቋማት አገልግሎት መስጠት እያቆሙ ነው ተብሏል።

"በጽኑ የታመሙ ህሙማን ለተሻለ ህክምና ወደ ሌላ ቦታ መሄድ በመከልከሉ ያላቸው አማራጭ ሞትን ቤታቸው ሆኖ መጠባበቅ ሆኗል" ያሉት ነዋሪዎች ሸቀጥ ወደየወረዳው እንዳይገባ በመከልከሉም ሰው ለከፍተኛ የኑሮ ቀውስ ተጋልጧል።

በአምስቱም ወረዳዎች መከላከያ ለቆ ከወጣ ጀምሮ የመንግስት ሰራቸኞች ደመወዝ ባለመከፈሉ ከፍተኛ ችግር ላይ ናቸው ተብሏል።

ፎቶ: ፋይል

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

30 Oct, 10:50


#ከዜናዎቻችን| በከምባታ ዞን ዳምቦያ ወረዳ፣ ፉንጦ ከተማ ውስጥ ወጣቶች በጭካኔ በፀጥታ አካላት ሲደበደቡ የሚያሳየው ምስል አነጋጋሪነቱ ቀጥሏል

(መሠረት ሚድያ)- ከአካባቢው ነዋሪዎች የደረሰን መረጃ እንደሚጠቁመው በአካባቢው ውሃ እና መብራት ከወራት በላይ ጠፍቶ ህዝቡ በስቃይ እያሳለፈ ይገኛል።

በዚህ ጉዳይ ላይ መንግስትን በኮሚቴ ሆነን ሄደን እንጠይቅ ብለው የተሰበሰቡ ወጣቶች በክልሉ ልዩ ሀይል ክፉኛ ድብደባ እንደተፈፀመባቸው እና ሶስቱ ደግሞ በጥይት ተመትተው እንደቆሰሉ ታውቋል።

"ለዚህ ጉዳይ ወጣቶች ከተማ ውስጥ ተሰብስበው ምን እናድርግ ብለው እየተወያዩ ባሉበት ሁኔታ ላይ የክልሉ ልዩ ሀይል ለምን ተሰባስባችሁ በማለት ይህን ዓይነት ድርጊት ፈፅሞባቸዋል" ያለን አንድ የከተማው ነዋሪ ነው።

ሌላ የከተማው ነዋሪ ደግሞ ድብደባ ከተፈፀመባቸው ወጣቶች መሀል ሁለቱ ክፉኛ ተጎድተው ወደ ሆስፒታል እንደተወሰዱ መስማቱን ተናግሯል።

የከምባታ ዞን መዲና ከሆነችው ዱራሜ ወጣ ብላ በ20 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው ፉንጦ ከተማ ላይ የህዝብን ሰቆቃ ለህዝብ እናሳውቅ ባሉ ወጣቶች ላይ የተፈፀመው ድርጊት የብዙዎች መነጋገርያ ሆኗል።

የአካባቢው ነዋሪዎች ለፉንጦ ከተማ ትኩረት ተሰጥቶ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ የክልል አመራሮች ጉዳዩን በአስቸኳይ እንዲከታተሉና ለህዝቡ ተገቢውን ምላሽ እንዲሰጡ ጠይቀዋል።

''15 ቀናትን ያለ ውሃ እና መብራት ማነው የሚኖረው?" ብለው ጥያቄ እያነሱ የሚገኙት ነዋሪዎች የጉድጓድ ውሃ እየጠጣ የሚታመመውንና ለሞት ሰለባ የሆነውንስ ቤቱ ይቁጠረው ብለዋል።

ከአካባቢው ካሰባሰብነው መረጃ መሀል "እኛ ብርሃን እንወዳለን፣ መብራት እንፈልጋለን" ብለው ለችግሩ ፍትህ ፍለጋ በወጡበት ሦስት ሰዎች በጥይት መመታታቸው ታውቋል፣ ሌሎች ደግሞ ከቤታቸው እንዲወጡ እየተደረጉ እንደተደበደቡ ሰምተናል።

በዚህ ዙርያ ከከምባታ ዞን አመራሮች ተጨማሪ መረጃ እና ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

28 Oct, 19:04


የሚድያ ሰራዊት...?!

በዚህ መልኩ የሚገኝ ላይክ፣ ኮመንት እና ሼር ጥቅሙ ምን ይሆን?

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

28 Oct, 17:10


#ከዜናዎቻችን| ዝነኛው ፈንድቃ የባህል ማዕከል ፈረሰ፣ ምትኩ በስፍራው ሊገነባ እንደሆነም ተሰምቷል

(መሠረት ሚድያ)- ለካዛንችስ አካባቢ ለአመታት ድምቀት ሆኖ የቆየው ፈንድቃ በኮሪደር ልማት ምክንያት መፍረሱ ታውቋል።

የባህል ማእከሉን ለማፍረስ ከ2015 ጀምሮ በከተማ አስተዳደሩ የተለያዩ እንቅስቃሴዎች ሲደረጉ ቢቆዩም በስተመጨረሻ ባሳለፍነው ሳምንት እንደፈረሰ ታውቋል።

ከ1990ዎቹ ጀምሮ ፈንድቃ የትዝታ ቦታ ብቻ ሳይሆን የበርካታ ኢትዮጵያውያን አርቲስቶች፣ ሙዚቀኞች እና ተወዛዋዦች መኖሪያ መሆኑ የሚነሳ ሲሆን በርካቶች ትዝታቸውን ያሳለፉበት ስፍራም ነበር።

"ፈንድቃ በካዛንቺስ ውስጥ አስፈላጊ የኢኮኖሚ ሞተር ነበር፣ በየዓመቱ ወደ 200 ሺህ ጎብኚዎች ወደ አካባቢው ይመጣሉ" የሚለው የባህል ማእከሉ ባለቤት አርቲስት መላኩ በላይ በጣሊያን ስታር 2022፣ በቲኤዲ ኅብረት 2022፣ በፕሪንስ ክላውስ ሎሬት 2020፣ ለሙዚቃ ቪዛ 2019 እና በፈረንሣይ ሜዳሊያ 2015 መሸለሙን ገልጿል።

"አዲስ አበባ ልማት እንደሚያስፈልጋት በመረዳት በፈንድቃ ደመቅ ያለ ኢትዮጵያዊ ባህል እየተጋራን አካባቢውን ለማልማት የቢዝነስና የሕንፃ ፕላን አዘጋጅተን ነበር" ብሎ ከዚህ በፊት ለሚድያዎች ተናግሮ የነበረው አርቲስት መላኩ አሁን ላይ ካዛንቺስ በተመሳሳይ ቦታ ፈንድቃን እንዲገነባ መንግስት ፍቃድ እንደሰጠው በፌስቡክ ገፁ አስታውቋል።

በተያያዘ ዜና በፈንድቃ ባህል ማዕከል ላይ የተሰራው  "Take Me to Fendika" የተሰኘ ደክመተሪ ፊልም በአሜሪካ ቴክሳስ፣ ሂዩስተን በተደረገው 2ኛው የአፍሪካ የባህል ፊልም ፌስቲቫል (AFFRICUFF) ላይ በምርጥ ደክመንተሪ ዘርፍ አሸናፊ መሆኑ ታውቋል።

ዳይሬክተሩ ሲስኮ ብራድሌይ "ይህ እውነተኛ የቡድን ጥረት ነበር፤ በፈንድቃ የባህል ማዕከል ላሉ አርቲስቶች በሙሉ ፍቅር እና ምስጋና ይድረሳቸው ። እንደገና ለመገንባት በዚህ ትግል ውስጥ ቆመናል፣ አስተዋጽኦ ላደረጉ ሁሉ እናመሰግናለን።" ሲል በማህበራዊ ድረገጹ ጽፏል።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

28 Oct, 17:08


#ከዜናዎቻችን| በክፍለ ሀገራት የሚሰሩ የኮሪደር ልማቶችን ተችተው የነበሩት የፓርላማ አባል ፅሁፋቸውን አጥፍተው ሚድያዎችን ከሰሱ

(መሠረት ሚድያ)- የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት ዶ/ር ኬፈና ኤፋ "ደጋግሜ ብጽፍም አትሰልቹኝ" በማለት የዛሬ ሳምንት ገደማ ባቀረቡት ፅሁፋቸው በክልሎች በኮሪደር ልማት ስም የሚተገበረው ፕሮጀክት እንደ ደርግ የመንደር ምስረታ አደገኛ እየሆነ መጥቷል ብለው ነበር፡፡

ዶ/ር ኬፈና አያይዘውም "ወፍ እንኳን ጎጆ አላት፣ ምነዉ ክቡር የሆነውን የሰዉ ልጅ ከወፍ አሳነስን? እኔ ፀረ-ልማት አይደለሁም። የመንግሥትን የልማት አቅጣጫ ለማደናቀፍም አይደለም። አጉል ተወዳጅነትም ለማትረፍ አልሞክርም፣ ተረዱኝ" ብለው አቤቱታቸውን አሰምተው ነበር።

የፓርላማ አባሉ በአዲስ አበባ እየተተገበረ ያለውን የኮሪደር ፕሮጀክት እደግፋለሁ ያሉ ሲሆን "በክልሎች ያለው ግን እኔ አጅግ አላማረኝም፡፡ ሀገር እየፈረሰ ነዉ፡፡ በልማት ስም እየተኬደበት ያለ መንገድ ለዜጋ ሲኦል ሆኗል" ብለው መረጃ አጋርተው ነበር።

ይሁንና ዶ/ር ኬፈና ይህን ፅሁፍ ማጋራታቸውን ተከትሎ መሠረት ሚድያን ጨምሮ በርካታ ሌሎች ሚድያዎች ጉዳዩን መዘገባቸው ከመንግስት ጫና እንዳስከተለባቸው ሰምተናል።

በመጀመርያ ፅሁፉን ያቀረቡበትን የፌስቡክ አካውንታቸውን የቆለፉ ሲሆን ቆይተው ደግሞ ይህን ከላይ ያቀረብነውን አቋማቸውን ከገፃቸው ላይ ማጥፋታቸውን ተመልክተናል።

ከአምስት ቀን በፊት ደግሞ መሠረት ሚድያን እና ሌላ አንድ ሚድያን በስም በመጥቀስ ወቅሰዋል።

"ማሳበቅ የጋዜጠኝነት ሥነምግባር አይደለም" በማለት ፅሁፋቸውን የፌስቡክ አካውንታቸው ላይ ያሰፈሩት የፓርላማ አባሉ "ከሰሞኑ በሰጠሁት አስተያየት ከጋዜጠኝነት ሥነ-ምግባር ውጭ ፅሑፌን ሆን ብለው ለራሳቸው እንዲመቻቸው አድርጎ በሚዲያቸው በማቅረብ ችግር ለመፍጠር ያደረጉት እኩይ ተግባር ተነጋግረንበታል" በማለት በጉዳዩ ዙርያ ከመንግስት አካላት ጋር ንግግር እንዳደረጉ ጠቁመዋል።

አክለውም "ኢትዮ ፎረምና መሠረት ሚዲያ የሚባሉ ሚዲያዎች የሠራችሁት ሥራ እጅግ ትክክል እንዳልሆነ መቀበል አለባችሁ። ዘመኑ ሐሳብ በነፃነት የሚንሸራሸርበት የብልፅግና ዘመን እንጂ እንዳለፉት ዘመናት ሰበብ አስባብ እየተፈለገ የአይንህ ቀለም አላማረኝም ተብለህ የሚትሰወርበት፣ የምትታሰርበት፣ የምትሰቃይበት ዘመን አይደለም" ያሉት አቶ ኬፈና "ጊዜው የሐሳብ ዘመን ነው። በኃላፊነት መንፈስ የምትንቀሳቀስበትና ስህተት እንኳን ከተፈጠረ እርስ በርስ የምትተራረምበት ዘመን እንጂ የደርግ ወይም ኢህአዲግ ዘመን አይደለም" ብለዋል።

ዶ/ር ኬፈና ይህንን ሚድያዎች የተቹበት ፅሁፍ በድጋሜ ከፌስቡክ ገፃቸው ላይ ማጥፋታቸውን ተመልክተናል።

ዶ/ር ኬፈና በዚህ ሁሉ ፅሁፋቸው ውስጥ ግን በምን መልኩ መሠረት ሚድያም ሆነ ሌሎች ሚድያዎች ሀሳባቸውን እንዳዛቡባቸው አልገለፁም፣ ወይም ያልፃፍኩትን አቀረቡ ብለው በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውንጀላ አላቀረቡም።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

28 Oct, 17:05


#ከዜናዎቻችን| "አብያተ እምነት የሰማያዊ መንግሥት ተልዕኮ ማስፈጻሚያ ኤምባሲዎች በመሆናቸው ጥበቃ ሊደረግላቸው ይገባል"

(መሠረት ሚድያ)- እናት ፓርቲ አብያተ እምነት የሰማያዊ መንግሥት ተልዕኮ ማስፈጻሚያ ኤምባሲዎች በመሆናቸው ጥበቃ ሊደረግላቸው ይገባል ብሎ መግለጫ አውጥቷል።

መንግሥት የወንዝ ዳር፣ ጫካ፣ ኮሪደር… ወዘተ ፕሮጀክት በሚሉ መጠሪያዎች የሚያከናውነውን ፈረሳና የማፈናቀል ተግባር አስመልክቶ በቅርቡ የአገራችን የበላይ ሕግ የሆነውን ሕገ መንግሥትና የሚመለከታችውን አዋጆች ጠቅሰን በትብብር ፓርቲዎች የጸና አቋማችንን መግለጻችን ይታወቃል ያለው ፓርቲው ከዚኹ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ጋር ተያይዞ በአዲስ አበባ ከተማና ዙሪያዋ በሚገኙ ከተሞች የአምልኮ ሥፍራዎች ሕጋዊ ይዞታዎች ድንበር በማን አለብኝነት እየፈረሰ እንዳለና እንደሚፈርስ ማስጠንቀቂያ እንደደረሳቸው መገንዘብ ችለናል ብሏል።

ፓርቲው አክሎም እየፈረሱ ካሉት በዋቢነት የሰበታ ጌቴሴማኒ ቤተደናግል ጠባባት የሴቶች ገዳም ይዞታ ከክብር በወረደ አኳኋን እንዲፈርስ ተደርጓል በማለት የከሰሰ ሲሆን ከየካቲት 12 አደባባይ ከፍ ብሎ ያለውና ከአምስቱ ዓመት የፋሽስት ጣልያን ወረራ ወቅት ጋር ቀጥተኛ ተያያዥ ታሪክ ያለው የአገር ባለውለታው የምስካዬ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም ይዞታም ጠባብ የሆነውን ዐውደ ምሕረት የበለጠ በማጥበብ ከፊት ለፊቱ የገዳሙና የገዳሙ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ፈረሳ እንደሚከናወንባቸው ፓርቲያችን መረጃ ደርሶታል ብሏል።

እናት ፓርቲ በመግለጫው ባለፉት ጥቂት ተከታታይ ዓመታት በአብያተ ክርስቲያናት፣ በመስጅዶች እና በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች የደረሱ ቃጠሎዎች፤ በአገልጋዮችና ምእመናን ላይ የደረሱ አሰቃቂ ግድያዎች በኢትዮጵያ በትልቁ አገራዊ እሴታችን በሆናው ሃይማኖት ላይ የተጋረጠውን ኹለንተናዊ ጥቃት ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል ብሏል።

ከዚኹ የቀጠለ በሚመስል አኳኋንና በተቀናጀ መልኩ በአዲስ አበባና አካባቢው አብያተ ክርስቲያን ይዞታዎች ላይ እየተወሰደ ያለው የማፍረስ ተግባር ከውጭና ከውስጥ ተናቦ የሚተገበር መኾኑን መጠርጠር አያዳግትም በማለት ፓርቲው አቋሙን አጋርቶናል። 

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

28 Oct, 17:01


#ከዜናዎቻችን| በርካታ ነዳጅ የሚጠቀሙ ቅንጡ እና ውድ መኪናዎች ወደ ሀገር ውስጥ እየገቡ እንደሆነ ታወቀ

(መሠረት ሚድያ)- በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ በታገደበት በአሁኑ ወቅት በርካታ ነዳጅ የሚጠቀሙ ቅንጡ እና ውድ መኪናዎች ወደ ሀገር ውስጥ እየገቡ እንደሆነ መሠረት ሚድያ ያደረገው ምርመራ ያሳያል።

ታድያ ከሁሉም በላይ መነጋገርያ የሆነው በታዋቂው የንግድ ሰው አቶ ሻቃ ጉርሜሳ ወደ ሀገር ውስጥ ሊገቡ ፕሮሰስ ላይ የሚገኙት 700 ይደርሳሉ የተባሉት V8 መኪናዎች ጉዳይ ነው። 

የ Shaka Mall ባለቤት የሆኑት አቶ ሻቃ መኪና በማስመጣት እና በመሸጥ ከበርካታ አመታት በፊት ጀምሮ ልምድ ያላቸው ቢሆኑም በዚህ ወቅት በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን በብዛት ማስገባት መቻላቸው ለብዙዎች እንቆቅልሽ እንደሆነ ሰምተናል።

በቅርቡ 700 V8 ላንድ ክሩዘር መኪናዎችን ሊያስገቡ ሂደት ላይ እንደሆኑ የታወቀ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ ከ40 በላይ የሚሆኑት በአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት ላይ ጥሩ የአመራር ብቃት ላሳዩ የመንግስት ተሿሚዎች በስጦታ መልክ የሚበረከቱ መሆናቸው ተሰምቷል።

"መድሃኒት ፈልጎ ማግኘት ከባድ በሆነበት፣ ብታገኝም ዋጋው በማይቀመስበት አገር እንዲህ አይነት የሃብት ብክነት እየተፈፀመ ይገኛል" ያሉት አንድ ጉዳዩን የሚያውቁ የመረጃ ምንጫችን ናቸው።

የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን የተሽከርካሪ አጠቃቀም አስመልክቶ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የዛሬ ስድስት አመት ያወጣው መመሪያ በበርካታ ተቋማት እየተተገበረ አለመሆኑ ተደጋግሞ እየተነሳ ይገኛል።

በመመሪያው ቁጥር 4 ንዑስ ቁጥር 1 ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ወጪ ቆጣቢና ውጤታማ የፋይናንስ አጠቃቀም እንዲኖር ለከተማ ውስጥ ስራ አውቶሞቢል ተሽከርካሪዎችን እንዲጠቀሙ ተደንግጓል።

በዚህ መሰረት የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ቪ8፣ ቪ9፣ ፕራዶና ፓጃሮ ተሽከርካሪዎችን ከሚጠቀሙ ይልቅ አውቶሞቢል ተሽከርካሪዎችን ቢጠቀሙ ከፍተኛ ወጪ በመቀነስ ውጤታማ አገልግሎት መስጠት እንደሚቻል ተገልፆ ነበር።

ይሁንና አሁን ድረስ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ቪ8 እና ሌሎች ተመሳሳይ መኪናዎችን ከተማዎች ውስጥ እንደሚጠቀሙ መሠረት ሚድያ በቅርቡ መዘገቡ ይታወሳል።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

28 Oct, 16:58


#ከዜናዎቻችን| የአፋር ክልል አመራሮች አለመግባባት ወደ መንገድ መዝጋት ተሸጋግሮ እንደነበር ተሰማ

(መሠረት ሚድያ)- በክልሉ የብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት ሃላፊ በአቶ ኢሴ አደም እና በክልሉ ፕሬዚዳንት ሀጂ አወል አርባ መካከል ያለው አለመግባባት የክልሉን ከፍተኛ አመራሮችን ለሁለት የከፈለ መሆኑ የታወቀ ሲሆን ባሳለፍነው ሳምንት አቶ ኢሴ አደምን ከስልጣን በማንሳት ብዙ ስራ ወደሌለው በምክትል ፕሬዚዳንት ማአረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪነት ለማውረድ ሙከራ በመደረጉ ውጥረት ተነስቶ እንደነበር ታውቋል።

በኋላም የክልሉ የብልፅግና ፓርቲ ሃላፊ የነበሩት አቶ ኢሴ አደም በምክትል ር/መስተዳድር ማአረግ የማህበረዊ ክላስተ አስተባባሪ ሲደረጉ የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት እና የስራ ክህሎት ቢሮ ሃላፊ አቶ ኤለማ አቡበከር እስካሁን እጣ ፈንታቸው አልታወቀም።

የሀጂ ኢሴ ደጋፊ ነበሩ የሚባሉት የክልሉ የመንገድ ልማት እና የትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊ የነበሩት አቶ አደን ሀባናን ከስልጣናቸው ዝቅ በማድረግ በቅርቡ በምክር ቤት የተቋቋመው የአካባበቢ ጥበቃ ባለስልጣን ሃላፊ ተደርገዋል።

የክልሉ የብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት ሃላፊ የነበሩ አቶ ኢሴ አደም ሹም ስሩ የተካሄደበትን የካቢኔ ስብሰባ ረግጠው የወጡ ሲሆን "ይህ ሴራ ነው፣ አልቀበለው" እንዳሉ የታወቀ ሲሆን ለፌዴራል መንግስት አቤቱታቸውን ማቅረባቸው ታውቋል።

ይህንን ሹም ሽር የተቃወሙ የኡንዳፎቶ ቀበሌ ነዋሪዎች የኢትዮ- ጀቡቲ አስፋልት መንገድን ባሳለፍነው ሀሙስ ከጠዋት ጀምሮ ዘግተው እንደነበር ታውቋል፣ ቆይቶም መከፈቱን ሰምተናል።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

28 Oct, 13:00


#ሁለቱግፎች በቅርብ ቀናት ከሰማኋቸው የግፍ ድርጊቶች ሁለቱን ላጋራችሁ:

አንደኛው ጀሞ አካባቢ በሚገኛው ሳውዝ ዌስት አካዳሚ የተፈፀመ ነው። የኢትዮጵያን ባንዲራ ይዘው ሲዘምሩ እና የጥላሁንን "ኢትዮጵያ" ዘፈን ሲዘፍኑ የነበሩ ከ30 በላይ ታዳጊዎች (ከ10- 12ኛ ክፍል ተማሪዎች) ታፍሰው ተወስደው ክፉኛ ተደብድበዋል። ሁለቱ ላይ የደረሰው ድብደባ እጅግ የከፋ ነበር የተባለ ሲሆን፣ የልጆቻቸውን ከእስር መፈታት ሊማፀኑ ወደ 'ማርያም ሰፈር' የሚገኝ ፖሊስ ጣብያ የሄዱ ወላጆች "ከፈለጋችሁ በክላሽ እናናግራችሗለን" እንደተባሉ ነግረውኛል።

ሁለተኛው ደግሞ በከምባታ ዞን ፉንጦ ከተማ የተፈፀመ ሲሆን ከሁለት ሳምንት በላይ መብራት በመጥፋቱ በኮሚቴ ሆነን መንግስትን እንጠይቅ ብለው ሲመክሩ የነበሩ ወጣቶች በልዩ ሀይል ተይዘው ክፉኛ ተቀጥቅጠዋል፣ የድብደባውን መጠን የሚያሳይ ቪድዮም ተለቋል።

ሙሉ መረጃውን መመልከት ከፈለጉ: https://youtu.be/4-mTXuOxJjg?si=TU42M6bYuv3cqgGE

#StopAtrocities

ELIAS MESERET

27 Oct, 16:57


ይሄ ቁጭት ሲንጋፖርን እና ማሌዥያን መምሰል እና አለመምሰል ሳይሆን እንዴት በዚህ ክፍለ ዘመን አንድ የሀገሬ ዜጋ ምግብ አጥቶ ይራባል፣ ፖለቲከኞች በሚቆሰቁሱት እሳት ይለበለባል፣ በልማት ስም ከቤቱ ተጎትቶ ወጥቶ መንገድ ላይ ይጣላል... ወዘተ ቢሆን በወደድኩ።

እኔ እንኳን እንደ አንድ ተራ ግለሰብ ምናልባት ድምፅ ከሆነን በሚል ከህዝብ የሚደርሰኝ አሰቃቂ እና ዘግናኝ ሁኔታ እንቅልፍ ይነሳኛል።

አያውቁትም ወይስ አያገባኝም?

ወይስ ሌላ?

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

26 Oct, 19:45


#ከዜናዎቻችን| በትግራይ የተገደሉ የእርዳታ ሰራተኞችን ሞት ሲያጣሩ የነበሩ ባለሙያዎች ስራቸውን እንዲያቆሙ በአንድ የመንግስት ባለስልጣን ታዘዙ

(መሠረት ሚድያ)- ማሪያ ሄርናንዴዝ፣ ቴዎድሮስ ገብረማርያም እና ዮሃንስ ሃለፎም የድንበር የለሽ የሀኪሞች ቡድን ወይም MSF ሰራተኞች ሲሆኑ ሰኔ 24 ቀን 2013 ዓ/ም ትግራይ ውስጥ ለሰብአዊ ስራ ሲንቀሳቀሱ የኢትዮጵያ የመንግስት ወታደሮች ናቸው በተባሉ አካላት መገደላቸው ይታወሳል።

ከአንድ ወር ተኩል ገደማ በፊት ይህን ግድያ እንደ አዲስ ለመመርመር ወደ ስፍራው ያቀኑ የፍትህ ሚኒስቴር ባለሙያዎች ምርመራቸውን ጨርሰው አዲስ አበባ ሲመለሱ የፍትህ ሚኒስቴር ዴኤታው አቶ ተስፋዬ ዳባ የቃል ማስፈራርያ በመስጠት ምርመራቸውን እንዲያቆሙ ማድረጋቸውን ምንጮች ለመሠረት ሚድያ ጠቁመዋል።

ድንበር የለሽ የሀኪሞች ቡድን አሁን ድረስ የኢትዮጵያ መንግስት በዚህ ሆን ተብሎ የተደረገ ነው በተባለ ግድያ ግልጽ ምላሽ እንዲሰጠው እየጠየቀ ይገኛል።

"ከባልደረቦቻችን አሰቃቂ ሞት ጀምሮ፣ MSF ከእነዚህ ግድያዎች በስተጀርባ ያለውን ሁኔታ ለመረዳት እና የኃላፊነት እውቅና ለማግኘት ያለ እረፍት ሲጥር ቆይቷል፡፡ ለኢትዮጵያ ባለስልጣናት ያጋራነውና የድርጅታችን የውስጥ ምርመራ የመጀመሪያ ደረጃ ግኝቶች ወንጀለኞቹ እነማን እንደሆኑ እና አላማቸውን በእርግጠኝነት አላረጋገጡልንም" የሚለው የእርዳታ ድርጅቱ ግድያው በተፈፀመበት አካባቢ ያሉትን ሁለቱን ወገኖች ማለትም የሀገር መከላከያ ሀይል እና ህወሓትን በማሳተፍ በጉዳዩ ላይ ያላቸውን ተሳትፎ በተመለከተ የተለያዩ ጥያቄዎችን አቅርበናል ብሏል።

ይሁንና የእነርሱን የምርመራ ውጤት እና ግምገማ ከእኛ እና ከማሪያ፣ ቴድሮስ እና የዮሐንስ ቤተሰቦች ጋር እንዲያካፍሉ ብንጠይቅም እስከዛሬ ድረስ ለግድያው መንስኤ የሆኑት ሁኔታዎች ወይም ለኃላፊነት እውቅና ስለሰጡን ሁኔታዎች ምንም ግልጽነት ያለው ምላሽ አልሰጡንም ብሎ ቅሬታውን አቅርቧል።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

26 Oct, 19:20


#ከዜናዎቻችን| አንዳንድ የእሳት አደጋ ሰራተኞች በመርካቶው አደጋ ወቅት እሳት ማጥፋት ከመጀመራቸው በፊት ከተጎጂ ነጋዴዎች ጋር ገንዘብ ሲደራደሩ እንደነበር ታውቋል

- ሰራተኞቹ በበኩላቸው በገንዘብ ሊደልሉን የሞከሩት ባለሱቆቹ ናቸው ብለዋል

(መሠረት ሚድያ)- ሰኞ እለት በመርካቶ ሸማ ተራ ተከስቶ በነበረው የእሳት አደጋ ወቅት የታዩ ሁለት አሳዛኝ እና አሳፋሪ ክስተቶች እንደነበሩ የአይን እማኞች ለመሠረት ሚድያ ጠቁመዋል።

አንደኛው ድርጊት አንዳንድ የእሳት አደጋ ሰራተኞች እሳት ማጥፋት ከመጀመራቸው በፊት ከተጎጂ ነጋዴዎች ጋር ገንዘብ ሲደራደሩ እንደነበር የደረሰን የተረጋገጠ መረጃ ነው።

በስፍራው የነበሩ በርካታ ምንጮች እንደጠቆሙን አደጋው እንደተከሰተ የእሳት አደጋ መኪናዎች በአካባቢው የደረሱት ፈጥነው ነበር።

ይሁንና በስፍራው ከደረሱ በኋላ እሳቱን ከማጥፋት ይልቅ "ማንን ነው ምናናግረው?" በማለት ለረጅም ደቂቃዎች ማጥፋት እንዳልጀመሩ ታውቋል።

"ማለት የፈለጉት ብር እንዲሰጣቸው ከማን ጋር ነው ምንደራደረው ነው። ይህ ነገር የተለመደ ቢሆንም ይሄ ሁሉ ንብረት እስኪወድም ግን በዚ ደረጃ አይመስለኝም ነበር" ያለ አንድ የአደጋው ተጎጂ ቤተሰብ ይህን መረጃ በስፍራው የነበሩ በርካታ ሰዎች እንደሚያውቁ ተናግረዋል።

መሠረት ሚድያ በደረሰው መረጃ በስፍራው ቀድመው በአምቡላንስ የደረሱ የእሳት አደጋ ቡድን አባላት 4 ሚልዮን ብር ለመቀበል በድርድር ተስማምተዋል።

"የደረሰው የእሳት አደጋ ካለፈ በኋላ ምንም ባይጠቅምም ለወደፊት እንኳ ትምህርት ቢሆን ህዝብ ማወቅ አለበት" ያሉ አንድ አስተያየት ሰጪ ደግሞ መጀመሪያ እሳቱ የተያያዘው ሸማ ተራ የገበያ ማዕከል ላይ እንደነበር ያስረዳሉ።

አክለውም "ነገር ግን በጊዜው የዛ ህንፃ ባለቤቶች ቀርበው ተደራድረው፣ ማለትም 4 ሚሊዮን ብር ከፍለው እሳቱን ቶሎ መቆጣጠር ችለዋል" ያሉ ሲሆን ይህን ጉዳይ ማንም በስፍራው ተገኝቶ ማጣራት እንደሚችል ተናግረዋል።

እኚህ የመረጃ ምንጫችን እንደሚሉት የተቃጠለው "ነባር የገበያ ማእከል" ግን በጊዜው ብር የሚከፍል ሰው ባለመቅረቡ በዛ መልኩ ሊወድም ችሏል ብለዋል።

በርካታ ጉዳዩን የሚያውቁ ግለሰቦች በሰጡን መረጃ መሰረት ብር ከፋዮቹ በጊዜው የነበሩ የሱቅ ባለቤቶች ሲሆኑ የብዙ ሚሊዮን ብር ንብረት ሱቆቹ ውስጥ ላይ ስለነበራቸው የተጠየቁትን ለመክፈል አላቅማሙም ነበር። ጠያቂዎቹ ደግሞ በጊዜው አምቡላንስ ይዘው የመጡ የእሳት አደጋው ሰራተኞች ናቸው ተብሏል።

ይህ መረጃ ከወጣ በኋላ የእሳት አደጋ ሰራተኞች ለመሠረት ሚድያ በሰጡት ቃል "በሸማ ተራ አደጋው ወቅት ሱቅ ያላቸዉ እና ባልደረቦቻችንን የሚያቁ አንዳንድ ነጋዴዎች ስልክ ደውለው ሰራተኞችን የፈለጋችሁትን እንከፍላለን፣ የኛን ሱቅ መጀመሪያ አጥፉልን እያሉ በገንዘብ ሰራተኛዉን ለመደለል የሞከሩ ነጋዴዎችም እንዳሉ ሰምተናል" ብለዋል።

መሠረት ሚድያ ይህን መረጃ ካወጣ በኋላ የተቋሙ አመራሮች ባሳለፍነው ሀሙስ እለት ለግምገማ መቀመጣቸው ተሰምቷል።

"አደጋዉ ወደ ተቋማችን የመጣዉ ምሽት ወደ 12 ሰአት ከ28 ደቂቃ አካባቢ ነበር" ያሉት ሰራተኞች ወደ ተቋማቸው ጥሪ ከተደረገ በኋላ የአደጋዉ መኪና በ4 ደቂቃ ዉስጥ ቦታዉ ላይ ደርሶ ነበር ብለዋል።

ይሁንና የከባድ የእሳት አደጋ ማጥፋት ስራ ሲሰራ የአደጋ አመራር እዝ በአመራሮቹ መዘርጋት ነበረበት የሚሉት ሰራተኞች ማን ምን ይሰራል የሚል ስርአት ያስፈልግ ነበር ብለው "ይህ በአመራሩ አልተዘረጋም፣ ሁሉም በየራሱ ዉኃ እየረጨ ሲሄድ ነበር፣ የተተራመሰ አደጋ ነበር፣ የሚመራዉ አካል ራሱ አይታወቅም ነበር፣ ይህ የዚህ አደጋ መስፋፋት አንዱ ችግር ነበር" ብለዋል።

በዚህ ሁሉ መሀል ግን አብዛኞቹ ሰራተኞች አደጋው ከጀመረ ግዜ አንስቶ እስከ ጠዋት 2 ሰአት ተኩል ድረስ ዉኃ እንኳን ሚሰጣቸዉ አጥተዉ ሲሰሩ የነበሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በሌላ በኩል አደጋው በደረሰበት ወቅት በርካታ ከየት የመጡ እንደሆነ የማይታወቁ ግለሰቦች እቃ እየጫኑ ሲወስዱ እንደነበር ድርጊቱን የተመለከቱ ሰዎች ተናግረዋል፣ ይህም የእሳት አደጋውን አስታኮ ከፍተኛ ዝርፊያ እንደተፈፀመ እንዲገምቱ እንዳደረጋቸው ጠቁመዋል።

በተለይ አንዳንዶች "እቃችንን እያወጣን ነው" በማለት የሌላ ሰው ንብረት እየጫኑ ሲወስዱ እንደነበር ታውቋል። ከዚህ ጋር ተያያዞ የስርቆት ወንጀል የፈፀሙ 33 ተጠርጣሪዎች መያዛቸው የታወቀ ሲሆን የአዲስ አበባ ፖሊስ በአደጋው በ7 ሰዎች ቀላል፤ በ2 ሰዎች ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል ብሏል።

ይሁንና በስፍራው የነበሩ የአይን እማኞች አንድ ከእሳቱ ለማምለጥ ከፎቅ ላይ የዘለለ ግለሰብ ህይወቱ በስፍራው ማለፉን ተናግረዋል።

የአደጋውን መንስኤ የሚያጣራ የፎረንሲክ ምርመራ ቡድን በማቀናጀት ምርመራ መጀመሩን ፖሊስ ቢያስታውቅም እነዚህ ገንዘብ ሲጠይቁ የነበሩ የእሳት አደጋ ሰራተኞች በምርመራው ውስጥ ይካተት አይካተት እስካሁን አልታወቀም።

የእሳት አደጋውን በፍጥነት ለማጥፋት ያልተቻለው አካባቢው የአደጋ ተሽከርካሪዎችን ለማስገባት አመቺ ባለመሆኑ በከተማው አስተዳደር አመራሮች ተገልፆ ነበር። በሄሊኮፕተር የታገዘ የእሳት ማጥፋት ለማድረግ እንደሚሞከርም በባለስልጣናት ቢነገርም ምንም አይነት ሄሊኮፕተር በስፍራው እንዳልነበር ታውቋል።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

26 Oct, 18:05


#ከዜናዎቻችን| የኤርትራ መንግስት በኢትዮጵያ አየር መንገድ ላይ የ3.5 ሚልዮን ዶላር ክስ መሰረተ

(መሠረት ሚድያ)- የኤርትራ መንግስት በኢትዮጵያ አየር መንገድ ላይ የ3.5 ሚልዮን ዶላር ክስ መመስረቱን መሠረት ሚድያ ያገኘው አንድ ዶክመንት ጠቁሟል።

የኤርትራ ሲቪል አቪየሽን ባለስልጣን የኢትዮጵያ አየር መንገድን የከሰሰው በጉዞ ወቅት ጠፍተዋል ባላቸው 450 ሻንጣዎች ምክንያት እና  ከዛሬ 27 አመት በፊት ያልተከፈለኝ ገንዘብ አለ በማለቱ ነው።

በዚህም መሰረት ጠፍተዋል ለተባሉት የኤርትራውያን መንገደኞች 450 ሻንጣዎች 3.45 ሚልዮን ዶላር ገደማ፣ እንዲሁም ኤርትራ ለአየር መንገዱ እኤአ በ1997-1998 ዓ/ም ለሰጠሁት የኤር ናቪጌሽን እና over flying አገልግሎት ያልተከፈለኝ 576,000 ዶላር ክፍያ እንዲከፍለኝ ብሎ በክስ ማመልከቻው ላይ አስፍሯል።

ክሱን በአስመራ ፍርድ ቤት ክስ የመሰረተው የኤርትራው ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የሻንጣዎቹ ግምት እንዴት እንደተሰላ እንዲሁም ከ27 አመት በፊት ሰጠሁት ላለው አገልግሎት አሁን ለምን ለመጠየቅ እንደፈለገ ግልፅ አላደረገም።

መሠረት ሚድያ የተመለከተው የክስ ዶክመንት እንደሚያሳየው ክሱ መጀመርያ ወደ ፍርድ ቤት የቀረበው እአአ በኦገስት 25/2024 ዓ/ም ነበር።

የኤርትራ ኤርፖርት ባለስልጣን ለአየር መንገዱ የ 576,000 ዶላር ክፍያ ክፈሉኝ ብሎ ጥያቄ ያቀረበው እአአ በኦገስት 5/2024 መሆኑ ተመላክቷል።

አየር መንገዱ የዛሬ ሁለት ወር ገደማ ወደ አስመራ መብረር ማቆሙ የሚታወስ ሲሆን በወቅቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጠው መግለጫ የአስመራ ቅርንጫፍ የሂሳብ ደብተሩ ሙሉ በሙሉ መታገዱ ወደ ከተማዋ ያደርገው ለነበረው በረራ መቋረጥ አንዱ ምክንያት መሆኑን ተገልፆ ነበር።

አየር መንገዱ ኤርትራ ውስጥ የናቅፋ እና የውጭ ገንዘቦች አካውንት እንዳለው የጠቀሱት ዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ መስፍን ጣሰው ይህን ገንዘቡን በፈለገው ጊዜ የማንቀሳቀስ መብት እንዳለው ገልፀው ነበር።

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ግን ይህን ገንዘቡን እንዳያንቀሳቅስ በኤርትራ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን መከልከሉን ጠቅሰው በዚህም አየር መንገዱ ገንዘቡን ማንቀሳቀስ እና ለተለያዩ ወጪዎች መጠቀም ባለመቻሉ በረራውን ለማቋረጥ መገደዱን አስታውቀው ነበር።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeseret

ELIAS MESERET

26 Oct, 16:05


#ከዜናዎቻችን| ማህበራዊ ሚድያን በመጠቀም በአርቲስቷ ላይ ወንጀል ፈፅሟል የተባለው ግለሰብ በሌለበት በ13 አመት እስራት ተቀጣ

(መሠረት ሚድያ)- በአርቲስት ሄለን በድሉ እና በቤተሰቦቿ ላይ ላለፉት አምስት አመታት በርካታ ተደራራቢ ወንጀሎችን ሲፈፅም ነበር የተባለው ግለሰብ በሌለበት በ13 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ የፍርድ ውሳኔ መተላለፉ ታወቀ።

አሸናፊ ከበደ ብዙወርቅ፣ ወይም በፌስቡክ ስሙ ጴጥሮስ አሸናፊ ከበደ በሚባል ስም የሚታወቀው ግለሰብ በግል ተበዳይ በኩል  ክስ ቀርቦበት የህግ ተጠያቂነት ሲመጣበት ለበቀል በሶሻል ሚድያ ላይ ሰዎችን በግልፅ መልምሎ ወንጀለኞችን በማደራጀት እና ስምሪት በመስጠት ለአካለ መጠን ያልደረሱ በወቅቱ እድሜአቸው 5 እና 7 የነበሩትን የግል ተበዳይ ህፃናት ልጆች ላይ ጉዳት ለማድረስ ታስቦ የተሞከረውን የእገታ ወንጀል አቀናባሪ እና አስፈፃሚ በመሆን ክስ ቀርቦበት እንደነበር ከክሱ ዝርዝር ተመልክተናል።

ይሁንና ከሀገር ውጪ የሚገኘው ተከሳሹ ለተከሰሰበት የወንጀል ድርጊቱ ምላሽ እንዲሰጥ እና በተደጋጋሚ ፍርድ ቤት እንዲቀርብ ከጥር 25/2015 ዓ/ም ጀምሮ በተደጋጋሚ በጋዜጣ የታወጀ እንዲሁም በህግ እንደሚፈለግ በተለያዩ የመገናኛ ብዙሀን በሰፊው የተዘገበ ቢሆንም ፍርድ ቤት አለመቅረቡ ታውቋል።

ይሁንና ጥቅምት 7/2017 ዓ/ም በዋለው ችሎት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከይግባኝ ባይ የፌደራል አቃቤ ህግ የተደራጁ እና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ዐቃቤ ሕግ  የቀረበለትን ግንቦት 13/2016 ዓ/ም  በከፍተኛ ፍርድ ቤት  የተሰጠውን የ 8 አመት ከ 5 ወር ፍርድ ላይ አቃቤ ህግ ያቀረብውን የይግባኝ አቤቱታ በመመርመር ጥፋተኛውን  ያርማል፣ ሌሎችንም ያስተምራል በማለት እንዲሁም ሌላውም የማህበረሰብ ክፍል ከእንደዚህ አይነት ወንጀል ድርጊት እንዲጠነቀቅ ለማድረግ የ13 አመት ፅኑ እስራት ውሳኔ በአሸናፊ ከበደ ብዙ ወርቅ ላይ ማሳረፉ ታውቋል።

በተጨማሪም ግለሰቡ በኢንተርፓል ተይዞ ማረሚያ ቤት እንዲወርድ ፍርድ ቤት  ትእዛዝ ሰጥቷል።

ይህን ተከትሎ አስተያየት የሰጠው የአርቲስቷ ባለቤት አቶ ሚካኤል መኮንን "በተፈፀመብን ተደራራቢ ወንጀል ምክንያት ያጋጠመውን የልጆቼን ስነልቦናዊ እና አካላዊ ጉዳት ባይጠግንም በተመሳሳይ ድርጊት ላይ እየተሳተፉ ያሉ ወንጀለኞችን እና ሌላው የማህበረሰብ ክፍል ከእንደዚህ አይነት ወንጀል ድርጊት እንዲጠነቀቅ እና ወንጀለኞች አደብ እንዲገዙ የሚያደርግ አስተማሪ የሆነ የ13 አመት ፅኑ እስራት ውሳኔ ተላልፎበታል" በማለት ቃሉን ሰጥቷል።

ጴጥሮስ አሸናፊ ከበደ "የአርቲስት ሄለን በድሉ ባለቤት የጄነራል ክንፈ ዘመድ ነው፣ የሀብታቸው ምንጭም ግለሰቡ ነው፣ በመኖሪያ ቤታቸውም ጊዜያዊ ባንክ ቤት አለ" የሚል መረጃ በአንድ ወቅት በገፁ አሰራጭቶ እንደነበር ተመልክተናል።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

@eliasmeserett

ELIAS MESERET

26 Oct, 16:00


#ከዜናዎቻችን| በአዲስ አበባ በአስተማሪነት ለመቀጠር የሚጠየቀው የ70 ሺህ ብር ጉቦ

(መሠረት ሚድያ)- አንዳንድ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አመራሮች አስተማሪዎችን ለመቅጠር እስከ 70,000 ብር ጉቦ እንደሚጠይቁ የደረሱን ጥቆማዎች ያሳያሉ።

በተለይ በቅርቡ አውጥቶ ለነበረው የአስተማሪዎች ቅጥር በርካታ አመልካቾች ዶክመንታቸው ቢያስገቡም በውስጥ በሚደረግ ድርድር 70,000 ብር የከፈሉ ግለሰቦች ቅጥር እየተፈፀመላቸው መሆኑ ታውቋል።

ቅጥሩ ትክክለኛ እንዲመስል ዶክመንታችሁን አምጡ፣ እውነተኝነቱን እናጣራለን በሚል አስፈላጊ ዶክመንቶችን ከሰበሰቡ በኋላ በውስጥ ለውስጥ ግንኙነት ሰዎች በብዛት እንደሚቀጠሩ የተናገሩት መረጃ ሰጪዎች በዚህ መልኩ ከሚቀጠሩት ውስጥ አንዳንዶቹ ሀሰተኛ ዶክመንት ያላቸው እንደሆኑ እንሰሚያውቁ ጠቁመዋል።

"ይህ ድርጊት አዲስ አይደለም፣ በአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የቅጥር አሰራር ውስጥ ያለፈ ሁሉም ሰው ያውቀዋል" ያሉን በዚሁ ተቋም ውስጥ የሚሰሩ አንድ ጥቆማ ሰጪ ብር ከፍለው የተቀጠሩ ሰዎች በቅርበት እንደሚያውቁ ተናገረዋል።

የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ በስሩ ለሚገኙ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የስራና ተግባር ትምህርት የመምህራን ቅጥር ማስታወቂያ ነሀሴ 21/2016 ማውጣቱን የተመለከትን ሲሆን ይህ የስራ ቅጥርም አንዱ ዋነኛ የሙስና ድርጊት የተፈፀመበት መሆኑን ጥቆማ ሰጪዎቻችን ጨምረው ገልፀዋል።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

@Eliasmeserett

ELIAS MESERET

23 Oct, 14:29


💠.10| በአንድ ወቅት ለህዝብ ተደጋግመው ተነግረው የነበሩ፣ አሁን ላይ ግን ደብዛቸው ከጠፉ 10 ጉዳዮች መሀል

(መሠረት ሚድያ)- 10ኛ: "የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ስቴሽን ዋገን ቪ 8፣ ቪ 9፣ ፕራዶና ፓጃሮ ተሽከርካሪዎችን ከተማ ውስጥ መጠቀም አይችሉም"

የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን የተሽከርካሪ አጠቃቀም አስመልክቶ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የዛሬ ስድስት አመት ያወጣው መመሪያ በበርካታ ተቋማት እየተተገበረ አለመሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር በተደጋጋሚ ማስታወቁ ይታወሳል።

በመመሪያው ቁጥር 4 ንዑስ ቁጥር 1 ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ወጪ ቆጣቢና ውጤታማ የፋይናንስ አጠቃቀም እንዲኖር ለከተማ ውስጥ ስራ አውቶሞቢል ተሽከርካሪዎችን እንዲጠቀሙ ተደንግጓል።

በዚህ መሰረት የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ስቴሽን ዋገን ቪ 8፣ ቪ 9፣ ፕራዶና ፓጃሮ ተሽከርካሪዎችን ከሚጠቀሙ ይልቅ አውቶሞቢል ተሽከርካሪዎችን ቢጠቀሙ ከፍተኛ ወጪ በመቀነስ ውጤታማ አገልግሎት መስጠት እንደሚቻል ተገልፆ ነበር። ይህም ተግባራዉ እንዲሆን መመርያዎች ተላልፈው ነበር።

ይሁንና አሁን ድረስ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ቪ 8 እና ሌሎች ተመሳሳይ መኪናዎችን ከተማዎች ውስጥ እንደሚጠቀሙ ይታያል።

እንደ ሀረሪ ያሉ ክልሎች መሪዎች ደግሞ ከዚህም ላቅ እንደ ሊንከን ናቪጌተር የመሳሰሉ እስከ 50 ሚልዮን ብር የሚሸጡ መኪናዎችን መጠቀም እንደጀመሩ በቅርቡ ዘግበን ነበር።

መሠረት ሚድያ!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

23 Oct, 14:18


💠.9| በአንድ ወቅት ለህዝብ ተደጋግመው ተነግረው የነበሩ፣ አሁን ላይ  ደብዛቸው ከጠፉ 10 ጉዳዮች መሀል

(መሠረት ሚድያ)- 9ኛ: "ላዳ ታክሲዎች በአንድ ዓመት ውስጥ ሙሉ ለሙሉ በአዲስ መኪናዎች ይተካሉ"

በተለምዶ ሰማያዊ ላዳ ታክሲዎች የሚባሉት ተሽከርካሪዎች በአንድ ዓመት ውስጥ ሙሉ ለሙሉ በአዲስ እንደሚተኩ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ባለሥልጣን የዛሬ አራት አመት አካባቢ አስታውቆ ነበር።

በአዲስ አበባ ከተማ 10,500 የላዳ ታክሲዎች ባለንብረቶች መኖራቸውንና አስተዳደሩ ባመቻቸላቸው ዕድል ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተገኘ የብድር አገልግሎት መሠረት የሚቀየሩ መሆኑን፣ የወቅቱ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ባለሥልጣን ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ በድሉ ሌሊሳ ለሪፖርተር ተናግረው ነበር።

ኢቲቪ በበኩሉ ታክሲዎቹን በአዳዲስ ለመተካት ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ ከንግድ ባንክ ብድር መመቻቸቱን ጠቅሶ በወቅቱ ዘግቦ የነበረ ሲሆን አዳዲሶቹ ታክሲዎች በሚቀጥሉት 4 ወራት ወደስራ እንደሚገቡ ይጠበቃል ብሎ ነበር።

የብድር አገልግሎቱ የመጀመርያ ክፍያ 20 በመቶ መሆኑን የገለጹት አቶ በድሉ፣ ጠቅላላ ክፍያው በአምስት ዓመታት ውስጥ እንዲያጠናቅቁ እንደሚደረግ ተናግረው ነበር።

ባለንብረቶቹ በአንድ ዓመት ውስጥ የሚቀይሩት አዲስ መኪና ዓይነቶች በአገር ውስጥ የሚገጣጠሙ ተሽከርካሪዎች መሆናቸውን ምክትል ሥራ አስኪያጁ ተናግረው ነበር።

ባለታክሲዎች ከታኅሳስ 24 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዝግ የቁጠባ ደብተር በአምስት ቅርንጫፎች እንዲከፍቱ የተደረጉ ሲሆን የቅየራው የመጀመርያው ምዕራፍ እንደሚሆንም ጠቁመው ነበር።

ይሁንና ይህ ብዙ የተባለለት እቅድ የትም ሳይደርስ ተግባራዊ ሳይደረግ አራት አመት ሞልቶታል።

መረጃን ከመሠረት!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

23 Oct, 14:14


💠.8| በአንድ ወቅት ለህዝብ ተደጋግመው ተነግረው የነበሩ፣ አሁን ላይ ግን ደብዛቸው ከጠፉ 10 ጉዳዮች መሀል

(መሠረት ሚድያ)- 8ኛ: "የኮሮና መድሀኒትን በኢትዮጵያ ሰርተን በአጠረ ግዜ ለህዝብ እናቀርባለን"

የኮሮና ቫይረስ በኢትዮጵያ ገባ በተባለበት ሰሞን የወቅቱ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር አብርሀም በላይ የኮሮና መድሀኒት በኢትዮጵያ የመገኘት ተስፋን አስመልክተው አንድ ንግግር አድርገው ነበር።

በዚህ ንግግራቸው ላይ በኢትዮጵያውያን ተመመራማሪዎች እየተካሄደ የነበረው የምርምር ስራ እና የተገኘው ውጤት በጣም አበረታች ብቻ ሳይሆን በአጠረ ጊዜ ቀሪ ስራዎች በማጠናቀቅ ለህዝቡ የጀመርነውን የምንጨርስ እና ያልነውን የምናደርግ መሆኑን እናሳያለን ብለው ነበር።

የምርምሩ ቀሪ ስራዎች ማለትም የአኒማል ቶክሲስቲ እና ክልኒካል ቴስት ስራዎች በተፋጠነ መንገድ እየተሰሩ የሚገኘውን ውጤት ለህዝባችን እንገልፃለን ብለውም ነበር።

ይሁንና ይህ ንግግር ህዝቡን እንዲዘናጋ ሊያደርገው ይችላል ተብሎ ትችት ሲቀርብበት ባለስልጣኑ "እንዴት በኢትዮጵያውያን ይህ ሊሆን ይችላል በሚሉ፣ ሃገራቸውን እነሱ የሚያውቁዋትን ያህል እውቀት ብቻ ያላት በሚመስላቸው እና ይህ ስራም ፖለቲካዊ ገፅታ ሰጥተው፣ እኛ ያላወቅነው እንዴት ይሆናል በሚሉ አካላት ባልሆነ መንገድ ተርጉመው እያቀረቡ ያሉት ትርክት ነው" ብለው አጣጥለውት ነበር።

ዶ/ር አብርሀም አክለውም "የለመዱትን የአሉባልታና የውሸት ዜና መስራት መቅረቱን ያልተረዱ እና ሀገራችን ለችግር ግዜ የሚደርሱ አዋቂዎችና ተመራማሪዎች እንዳሉዋት የማያውቁ ወይም ማወቅ የማይፈልጉ ሰዎች ናቸው፣ እና የነሱ ማላዘን ይቀጥላል ሃገራችን እና ህዝቦችዋ ወደ ከፍታ ማማ ይጓዛሉ" በማለት ትችቱን አጣጥለው ነበር።

ይሁንና መድሀኒቱ በኢትዮጵያ እንደሚኝ የተሰጠው ተስፋ እውን ሳይሆን ቀርቷል፣ በአለማችን ላይም እንደ አሜሪካ፣ እንግሊ፣ ሩስያ እና ቻይና ካሉ ጥቂት ሀገራት ውጪ ለክትባት የሚሆን መፍትሄ ማዘጋጀት የቻሉ ሌሎች ሀገራት አልነበሩም።

መረጃን ከመሠረት!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

23 Oct, 14:11


💠.7| በአንድ ወቅት ለህዝብ ተደጋግመው ተነግረው የነበሩ፣ አሁን ላይ ግን ደብዛቸው ከጠፉ 10 ጉዳዮች መሀል

(መሠረት ሚድያ)- 7ኛ: "በ 8.8 ቢሊዮን ብር በደጀን ከተማ ላይ የሲሚንቶ ፋብሪካ ሊገነባ ነው"

ቀጣዩ ጉዳይ ደግሞ በ 8.8 ቢሊዮን ብር በደጀን ከተማ ላይ የሲሚንቶ ፋብሪካ ሊገነባ ነው በሚል የዛሬ ስድስት አመት ተነግሮ የነበረው መረጃ ነው።

ጥር 16/2011 ዓ.ም አባይ ኢንዱስትሪያል የልማት ማህበር በአማራ ክልል ደጀን ከተማ ላይ ሲሚንቶ ፋብሪካ ለመገንባት ሥምምነት ተፈራርሞ ነበር፡፡

የልማት ማህበሩ ከቻይናው HY እና ከዴንማርኩ FLF ኩባንያዎች ጋር ነበር የውል ሥምምነቱን የተፈራረመው፡፡ ፋብሪካው በ 8.8 ቢሊዮን ብር እንደሚገነባና ግንባታውም በ 24 ወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ይፋ ተደርጎ ነበር፡፡

የደጀን ሲሚንቶ ፋብሪካ በቀን 5 ሺህ ቶን እንዲያመርት ታቅዶ የነበረ ሲሆን ለዚህም 655 ሰዎችን በቋሚነት ይቀጥራል ተብሎ ተነግሮለት ነበር፣ በሙሉ አቅሙ ሥራ ሲጀምር ደግሞ የሰራተኞቹን ቁጥር ወደ 1 ሺህ ያሳድጋል ተብሎ ነበር ፡፡

ሸራተን ሆቴል በተፈረመው ስምምነት ላይ የወቅቱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ የወቅቱ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ገዱ አንዳርጋቸው እና የአባይ ኢንዱስትሪያል የልማት ማህበር የቦርድ ሰብሳቢ አቶ መላኩ አለበል ተገኝተው ነበር።

ይሁንና ይህ ፕሮጀክት ከፊርማ በዘለለ ወደ ተግባር ለመለወጥ አንዳንድ ስራዎች ተጀምረው የነበረ ቢሆንም ከስድስት አመት በኋላም ስራ ሳይጀምር ፕሮጀክቱ ተቋርጦ ይገኛል።

መረጃን ከመሠረት!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

23 Oct, 13:54


💠.6| በአንድ ወቅት ለህዝብ ተደጋግመው ተነግረው የነበሩ፣ አሁን ላይ ግን ደብዛቸው ከጠፉ 10 ጉዳዮች መሀል

(መሠረት ሚድያ)- 6ኛ: "በኢትዮጵያ ውስጥ የለሙ ዋትሳፕና ዙምን የሚተኩ የተግባቦት ፕላትፎርሞች  ወደ ስራ ሊገቡ ነው"

በኢትዮጵያ ውስጥ የለሙ ዋትሳፕና ዙምን የሚተኩ የተግባቦት ፕላትፎርሞች  ወደ ስራ ሊገቡ እንደሆነ ከዛሬ አራት አመት በፊት ተነግሮ ነበር።

ኢትዮጵያ ፌስቡክን እና ትዊተርን ቢያንስ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመጠቀም በሚስያችል ሀገራዊ የማህበራዊ ትስስር ገጽ የመቀየር እቅድ እንዳላትም የወቅቱ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሹመቴ ግዛው አስታውቀው ነበር።

ዶ/ር ሹመቴ ከአል አይን ጋር በነበራቸው አንድ ቆይታ አንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎች ለፖለቲካ ሀይሎች መጠቀሚያ ሆነዋል፤ አሁን ባለንበት ሁኔታም ፌስቡክ እና ትዊተርን ለአብነት ማንሳት ይቻላል ብለው ነበር።

“ኢትዮጵያዊ የሆኑ እና እውነትን የያዙ በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የሚሰራጩ እና ተጽእኖ ሊፈጥሩ የሚችሉ መልእክቶች ካሉ ፌስቡክ በአስቸኳይ እንዲጠፉ እያደረገ ነው” ያሉት ዶ/ር ሹመቴ፤ ትዊተርም አሁን ጀምሯል ሲሉ ከሰው ነበር።

“የሚያዋጣን ነገር የራሳችን የሆነ ፌስቡክን እና ትዊተርን ሊተካ የሚችል እንዲሁም ቢያንስ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመጠቀም የሚስያችል የማህበራዊ ትስስር ገጽ መፍጠር ነው” በሚል እየተሰራበት መሆኑን ያስታወቁት ሀላፊው በኢትዮጵያ ውስጥ የለሙ ዋትስ አፕ እና ዙምን የሚተኩ የተግባቦት (ወይም የኮሙዩኒኬሽን) ፕላትፎርሞች ወደ ሙከራ መግባታቸውንም ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረው ነበር።

ከእነዚህም ውስጥ ለስብሰባ የሚሆኑ፣ የኮሙዩኒኬሽን እንዲሁም የመረጃ መለዋወጫ መተግበሪያዎች የለሙ እና በሙከራ ደረጃ እየተሰራባቸው ያሉ መሆኑን ጠቅሰውም ነበር።

አስፈላጊው መሰረት ልማት ተሟልቶላቸው በቅርቡ ሙሉ ለሙሉ ለኢትዮጵያ ህዝብ የሚለቀቁ መሆኑን ዶክተር ሹመቴ በወቅቱ ቢገልፁም ከአራት አመታት በኋላ ዛሬ ድረስ እነዚህ ፕላትፎርሞች አልተለቀቁም፣ ምን ደረጃ ላይ እንዳሉም አልታወቀም።

መረጃን ከመሠረት!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

23 Oct, 13:04


💠5| በአንድ ወቅት ለህዝብ ተደጋግመው ተነግረው የነበሩ፣ አሁን ላይ ግን ደብዛቸው ከጠፉ 10 ጉዳዮች መሀል

(መሠረት ሚድያ)- 5ኛ: "በአፍሪካ ትልቁ ሆቴልና ሪዞርት በአርባ ምንጭ ሊገነባ ነው"

ቀጣዩ ጉዳይ ደግሞ በአፍሪካ ትልቁን ሆቴልና ሪዞርት በአርባ ምንጭ ለመገንባት መንግስት ተዘጋጅቷል ተብሎ የነበረው ጉዳይ ነው።

ግዜው ሀምሌ 2011 አ/ም ነበር፣ ጠ/ሚ ዐብይ አህመድ ፓርላማ ላይ ንግግር ባደረጉበት ወቅት በአፍሪካ አህጉር ገቢ በማመንጨት አቅሙ፣ በስፋቱ እና በዘመናዊነቱ ትልቁን ሆቴልና ሪዞርት በአርባ ምንጭ ለመገንባት መንግስት መዘጋጀቱን አንስተው ነበር።

መሪው በንግግራቸው በሁለት ትላልቅ ሐይቆች በተከበበችው አርባ ምንጭ ከተማ የሚገነባው ሆቴልና ሪዞርት ሁሉንም አገልግሎቶች ያሟላና በአፍሪካ ግንባር ቀደም የቱሪስቶች መዳረሻ ከሆነችው ሲሸልስ ጋር አርባ ምንጭ ከተማን ሊያተካክል የሚችል ነው ብለው ነበር።

ግንባታውን በተመለከተ ድርድር ሲደረግ መቆየቱን ያነሱት ጠ/ሚር ዐብይ አሁን ላይ ዝግጅቶች በመጠናቀቃቸው በቅርቡ ይጀመራል ብለው ነበር።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ከመናገራቸው ከ4 ወር በፊት አርባ ምንጭን በጎበኙበት ወቅት መንግስታቸው ለሠላም ወዳዷና ውቧ አርባ ምንጭ ትልቅ ዕቅድ እንዳለው ገልፀው ነበር።

ይህ ፕሮጀክት ግን እስካሁን ተግባራዊ ያልሆነ ሲሆን በርካታ የአርባ ምንጭ ነዋሪዎች "መንግስት ቃል ከገባልን ውስጥ ይህን ጉዳይ ተግባራዊ ማድረግ አልቻለም" ብለው እስካሁን ቅሬታ እያሰሙ ይገኛሉ።

መረጃን ከመሠረት!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

23 Oct, 12:50


💠 4| በአንድ ወቅት ለህዝብ ተደጋግመው ተነግረው የነበሩ፣ አሁን ላይ ግን ደብዛቸው ከጠፉ 10 ጉዳዮች መሀል

(መሠረት ሚድያ)- 4ኛ: "በስራ ሰዓት ማንኛውም ስብሰባ እንዳይካሄድ"

ሌላኛው የዛሬ ሰባት አመት ገደማ ተግባራዊ እንዲሆን በርካታ ባለስልጣናት ትእዛዝ ያስተላለፉበት ጉዳይ በስራ ሰዓት ማንኛውም ስብሰባ እንዳይካሄድ እና ስብሰባዎች ሲያስፈልጉ ቅዳሜ እና እሁድ ወይም ከስራ ሰአት ውጪ እንዲካሄዱ የሚል ነበሩ።

ለምሳሌ የትራንስፖርት ሚኒስቴር በወቅቱ የስራ አፈጻጸሙን ከ 11፡30 በኃላ ማለትም ከመደበኛ ስራ ሰአት ውጪ ባለው ግዜ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ ገምግሞ እንደነበር የተሰራውን ዜና ማግኘት ችለናል።

በተመሳሳይ የአዲስ አበባ የከንቲባ ቢሮ በወቅቱ የከተማዋን አመራሮች ሠብስበው "ከዚህ በኋላ በመንግስት የስራ ሰአት ስብሰባ አይካሄድም" ብለው ተናግረው ነበር።

የአዲስ አበባ የብልፅግና ቢሮም በፌስቡክ ገፁ ልክ የዛሬ ስድስት አመት "ከዚህ በኋላ በመንግስት የስራ ሰአት ስብሰባ አይካሄድም!" ብሎ ነበር።

የጠ/ሚር ፅ/ቤት ሀላፊ የነበሩት ወ/ሮ ደሚቱ ሀምቢሳም ሚያዝያ 18/2010 በፃፉት አንድ ደብዳቤ "የቦርድ ስብሰባዎች ሁሉ ከመንግስት ሰአት ውጪ እንዲደረጉ ተወስኗል" ብለው የፈረሙበትን ደብዳቤም ተመልክተናል።

ይሁንና አሁን ላይ ይህ አሰራር ተረስቶ በብዙ መስሪያ ቤቶች ስብሰባ ቅዳሜ እና እሁድ ወይም ከስራ ሰአት ውጪ የማይታሰብ ሆኗል።

መሠረት ሚድያ አምስት የሚሆኑ የመንግስት ቢሮዎች ላይ ይህ አሰራር እየተተገበረ ይሆን ብሎ የጠየቀ ሲሆን ሁሉም ላይ ተግባራዊ ሆኖ እንደማይገኝ ታውቋል።

መረጃን ከመሠረት!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

23 Oct, 12:45


💠3| በአንድ ወቅት ለህዝብ ተደጋግመው ተነግረው የነበሩ፣ አሁን ላይ ግን ደብዛቸው ከጠፉ 10 ጉዳዮች መሀል

(መሠረት ሚድያ)- 3ኛ: "አሊባባ ግሩፕ ከኢትዮጵያ ጋር በኤሌክትሮኒክስ የታገዘ የንግድ ማዕከል ለመገንባት ተፈራረመ"

ቀጣዩ ጉዳይ ደግሞ አሊባባ ግሩፕ ከኢትዮጵያ ጋር በኤሌክትሮኒክስ የታገዘ የንግድ ማዕከል ለመገንባት ተፈራረመ በሚል የዛሬ አምስት አመት ወጥቶ የነበረው መረጃ ነው።

በኢትዮጵያ አለም አቀፍ በኤሌክትሮኒክስ የታገዘ እና አለም አቀፍ የንግድ አጋርነት በኤሌክትኒክስ የሚያስተሳስር ማዕከልን ለመገንባት አሊባባ ግሩፕ ከኢትዮጵያ ጋር ተፈራረመ ተብሎ በስፋት ተዘግቦ ነበር።

eWTP የተባለው እና በኢትዮጵያ እንደሚገነባ ስምምነት ላይ ተደርሶበት የነበረው ማዕከል አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን በማካተት ድንበር ተሸጋሪ ግብይቶችን በማዘመን የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣም ተገልጾ ነበር።

ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ፣ የአሊባባ ግሩፕ መስራች ጃክ ማ እና Ant የተባለው አለም አቀፍ ገንዘብ ተቋም ሊቀመንበር ኢሪክ ጂንግ በተገኙበት የመግባቢያ ሰነዱ ተፈርሞ ነበር።

ኢትዮጵያ አዲሱን የቴክኖሎጂ የንግድ መገኛ ማዕከል ስታስገነባ ከአፍሪካ ከሩዋንዳ በመቀጠል ኹለተኛዋ አገር እንደምትሆን ተነግሮም ነበር።

አዲሱ አጋርነት በኢትዮጵያ ተግባራዊ የሚሆነው በእስያ ቻይና እና ማሌዥያ እንዲሁም በአውሮፓ ቤልጀም እና በአፍሪካ ደግሞ ሩዋንዳ ተግባራዊ ተደርጎ በኹለት ዓት ውስጥ እምርታ በማሳየቱ እንደሆነ አዲስ ማለዳ ዘግቦ ነበር።

የማእከላቱ የሚደረገው የንግድ ግብይት ሲጨምር ነጋዴዎችም ገበያ ላይ የሚኖራቸው ዕድልም እንደሚሰፋ ተጠቁሞ የነበረ ቢሆንም ይህ የንግድ ማዕከል ከአምስት አመት በኋላ እስከ ዛሮ ድረስ አልተገነባም።

መረጃን ከመሠረት!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

23 Oct, 12:40


💠 2| በአንድ ወቅት ለህዝብ ተደጋግመው ተነግረው የነበሩ፣ አሁን ላይ ግን ደብዛቸው ከጠፉ 10 ጉዳዮች መሀል

(መሠረት ሚድያ)- 2ኛ: "በኢትዮጵያ ነዳጅ ተገኝቷል፣ ለውጭ ገበያ መቅረብ ሊጀምር ነው"

በቀጣይነት የምንመለከተው ብዙዎች ስለሚያስታውሱት የነዳጅ በኢትዮጵያ መገኘት ጉዳይ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደ ስልጣን በመጡ ማግስት አንድ መልካም ዜና ለህዝብ ተናግረው ነበር፣ ኢትዮጵያ ነዳጅ ለውጪ ገበያ ማቅረብ ልትጀምር ነው የሚል። 

ህዝቡም ዜናው ከተነገረው ስድስት አመት ቢሆነውም ጠብ ያለ ነገር ባለማየቱ የተባለው ነዳጅ የት ደረሰ እያለ በመጠየቅ ላይ ነው።

ጠ/ሚሩ በወቅቱ የተናገሩት አንደኛው በቀዳማዊ ሃይለስላሴ ግዜ በኦጋዴን የተገኘውን የጋዝ ክምችት ፖሊ ጂሲ ኤል የተባለው የቻይና ኩባንያ የጋዝ ማስተላለፊያ ጅቡቲ ድረስ ዘርግቼ ኤክስፖርት አደርጋለው በማለቱ ይህን ተመርኩዘው ኢትዮጵያ ከኤክስፖርቱ በአመት ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ እንደምታገኝ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል እንደሚፈጠር ገልፀው ነበር።

ፕሮጀክቱ ከ5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ኢንቨስትመንት የሚጠይቅ በመሆኑ የቻይናው ኩባንያ ፕሮጀክቱ የሚፈልገውን ከፍተኛ መዋለ ነዋይ ማግኘት ባለመቻሉ ተግባራዊ ሊያደርገው አልቻለም።

ፖሊ ጂሲ ኤል በአለም አቀፍ የነዳጅ ኢንዱስትሪ ውስጥ የማይታወቅ እና በዘርፉ ልምድ የሌለው፣ አስተማማኝ የገንዘብ ምንጭ የሌለው በመሆኑ እና ከዚህ ቀደም በሱማሌ ክልል በካሉብ እና ሂላላ የሚገኘውን የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ለማልማት በተለያዩ የውጪ ኩባንያዎች የተደረጉ ስምምነቶች ፍሬ ሳያፈሩ በመምከናቸው መንግስት ህዝቡን በተስፋ ባይሞላ ጥሩ ነበር። ፕሮጀክቱ እስካሁን በእንጥልጥል ላይ ይገኛል።

ሁለተኛው ጠቅላይ ሚኒስትሩን በተስፋ የሞላቸው በካሉብ እና ሂላላ መካከል ዶሃር በተባለ ስፍራ ፖሊ ጂሲ ኤል ያገኘው የተፈጥሮ ዘይት ጉዳይ ነበር።

በወቅቱ ለነዳጅ ፍለጋ በተቆፈረ ጉድጓድ ውስጥ የታየው የዘይት ፍሰት ተስፋ ሰጪ ቢሆንም ተጨማሪ የፍለጋ ጉድጎዶች ተቆፍረው የክምችቱ መጠን ምን ያህል ነው? ኮሜርሺያል ነው? አዋጪ ነው? ተብሎ የአዋጭነት ጥናት ሳይሰራ ለህዝብ ዜናው ይፋ መደረጉ በወቅቱ የማእድን ሚኒስቴር የፔትሮሊየም ባለሙያዎችን አሸማቋል።

ምክኒያቱም በአለም አቀፍ የነዳጅ ፍለጋ አሰራር በአንድ የፍለጋ ጉድጎድ ውስጥ የዳጅ ፍሰት ሲታይ በሚስጥር ተይዞ ተጨማሪ ጉድጎዶች ተቆፍረው የተለያዩ ሙከራዎች (well testing) ተሰርቶ የክምችት ግመታ ስራ እና የአዋጭነት ጠናት ተከናውኖ የክምቱ መጠን እና አዋጭነት ከተረጋገጠ በኋላ ነው ዜናው የሚበሰረው። 

"የእኛው ግን ገና በአንድ ጉድጎድ ውስጥ የነዳጅ ፍሰት በመታየቱ ከላይ የተዘረዘሩት ጥናቶች ሳይሰራ ከነገ ጀምሮ ኢትዮጵያ በቀን 450 በርሜል የነዳጅ ምርት ማምረት ትጀምራለች ተብሎ ተነገረ፣ ይህ ትልቅ ስህተት ነበር" የሚለው የመሠረት ሚድያ የፅሁፍ አቅራቢ እና የዘርፉ ተንታኝ ቃለየሱስ በቀለ "በቀጣይ በተካሄደው የሙከራ ምርት እንደታሰበው የነዳጅ ፍሰት ማግኘት ሳይቻል ቀርቷል፣ ህዝቡ ግን የተነገረውን መልካም ዜና ይዞ እስካሁን ነዳጁ የት ደረሰ ብሎ ይጠይቃል" ብሏል።

ግማሹም "ኢትዮጵያ ውስጥ አናዳጅ እንጂ ነዳጅ የለም" እያለ መዘዛበቻ አድርጎታል፣ መልካም ዜናውን ያበሰሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩም ሆኑ ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለስልጣናት ወይም ባለሙያዎች የተፈጠረውን ችግር ለህዝብ ባለማስረዳታቸው እንቆቅልሽ ሆኖ ቀርቷል።

በህዝብ ዘንድ ታማኝነት የሚያሳጣ በመሆኑ መንግስት የምስራቹን እንደተናገሩ ሁሉ በቀጣይ ምን እንደተፈጠረ ቢያስረዳ መልካም ነበር የሚለው ቃለየሱስ ይህን እንደ ትምህርት ወስዶ ለወደፊቱ ተመሳሳይ የነዳጅ እና የመአድን ፍለጋ እና ልማት ፕሮጀክቶች ጥናቶች ተሰርተው ሳይጠናቀቁ ዝርዝር መረጃዎችን ከመስጠት መቆጠብ ይገባል ብሏል።

መረጃን ከመሠረት!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

23 Oct, 12:32


💠1| በአንድ ወቅት ለህዝብ ተደጋግመው ተነግረው የነበሩ፣ አሁን ላይ ግን ደብዛቸው ከጠፉ 10 ጉዳዮች መሀል

(መሠረት ሚድያ)- 1ኛ: "የአፍሪካ ዋካንዳ በባህር ዳር ሊገነባ ነው"

በአንደኛ ደረጃ የምንመለከተው በባህር ዳር አካባቢ ይገነባል ተብሎ በስፋት ተነግሮለት ስለነበረው የአፍሪካ ዋካንዳ ፕሮጀክት ነው።

የዛሬ ስድስት አመት ገደማ ዋካንዳን በባህር ዳር እገነባለሁ ብሎ የተነሳ ሀብ ሲቲ ላይቭ የተባለ አንድ ድርጅት ነበር። ይህ ድርጅት አለኝ የሚለው ምዝገባም ሆነ የፋይናንስ ምንጭ ከመጀመርያው ጀምሮ አጠራጣሪ ነበር።

ታድያ ይህ ምናባዊውን ዋካንዳ በአማራ ክልል ጭስ አባይ አካባቢ ዕውን ያደርጋል የተባለው ፕሮጀክት የት ደረሰ?

‘ምንጩ’ ወይም The Source በሚል ስያሜ በጭስ አባይ ፏፏቴ አቅራቢያ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መንደር ሊገነባ እንደነበር በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን በወቅቱ ሲዘገብ ነበር፡፡

ይገነባል ተብሎ የታሰበው የቴክኖሎጂ መንደር ባለቤት ሀብ ሲቲ ላይቭ የተባለ የአሜሪካ ድርጅት ሲሆን፤ እ.አ.አ በ2018 በሆሊውድ ፊልም መንደር ተሠርቶ ለዕይታ የበቃው የ‹‹ብላክ ፓንተር›› ፊልም ምናባዊ ከተማ ዋካንዳን መሠረት አድርጎ እንደሚገነባ  ነበር በወቅቱ የተገለጸው፡፡

ሀብ ሲቲ ላይቭ የተባለው ድርጅት ሥራ አስኪያጅ ሚካል ካሚል ከዋልታ ቲቪ ጋር በወቅቱ በነበራቸው ቆይታ የፕሮጀክቱ ስያሜ ‘ምንጩ’ እንደሚባልና ለ20 ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር፣ ኢትዮጵያንም በዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ዘርፍ የተሻለ ደረጃ እንደሚያሰጣት ነበር የተናገሩት፡፡

ፕሮጀክቱ እስከ 20 ቢሊዮን ዶላር ወጪ እንደሚጠይቅና ሦስት ቢሊዮን ዶላር በወቅቱ ተመድቦ እንደነበርም መናገራቸው ይታወሳል፡፡

ቀሪው በጀት በዋናነት ከአሜሪካ ባንኮች እንደሚገኝም ሥራ አስኪያጁ ጠቁመው ነበር፡፡  ወደ ኢትዮጵያ ከመምጣታቸው በፊት ፕሮጀክቱን እና ተያያዥ ሥራዎችን ሲሰሩ መቆየታቸውንም በቃለ መጠይቁ አስረድተው ነበር፡፡

ባሕር ዳር  የጣና ሐይቅ እና የጭስ የአባይ መገኛ ውብ ከተማ በመሆኗ ተመራጭ አድርጓታል፤ ከታሪክ አንፃርም የዓለም ትልቁ ስልጣኔ መነሻ ከዚህ አካባቢ ነው ተብሎ ስለሚታመን ምናባዊ ዋካንዳ የቴክኖሎጂ ከተማን ለመገንባት አካባቢውን እንደመረጡት ሥራ አስኪያጁ እንደመረጡት መናገራቸውም ይታወሳል።

ጉዳዩ ይበልጥ ትኩረት እንዲስብ አድርጎት የነበረው ደግሞ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ከተማን የመስራት እቅዱን አስመልክቶ የሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከባለድርሻዎች ጋር ውይይት ማድረጉን ተከትሎ አብዛኞቹ የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን የዘገባ ሽፋን መስጠታቸው ነበር፡፡

ሀብ ሲቲ ላይቭ የተባለው ድርጅት ሥራ አስኪያጅ ሚካል ካሚል እውነተኛውን የዋካንዳ ፕሮጀክት በጭስ ዓባይ ፏፏቴ አቅራቢያ ገንብቶ ለመጨረስ ከስምንት እስከ አስር ዓመታት እንደሚወስድ፣ ፕሮጀክቱንም አጠናቅቀው ዕውን እንደሚደርጉት ገልጸው ነበር፡፡

‹‹ሀሳባችን በኢትዮጵያ መንግስት ተቀባይነት አግኝቷል፡፡ ለምንጠይቀው ሁሉ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገልን ነው›› ብለውም ነበር፡፡ ይሁንና ከጥቂት ወራት በኃላ ‹ዕውን ይሆናል የተባለው ምናባዊው ዋካንዳ› የት ደረሰ? በማለት የወቅቱ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ ሲጠየቁ “የአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ የፕሮጀክቱ እውን መሆን ለክልሉ የቱሪዝም እንቅስቃሴ ወሳኝ በመሆኑ ተገቢውን ድጋፍ እንድናደርግ ደብዳቤ ፅፎልን እንጅ በኛ በኩል ስለ ፕሮጀክቱ የምናውቀው ነገር አልነበረም” ብለዋል፡፡

በተፃፈለት የድጋፍ ደብዳቤ መሠረት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በንድፈ ሀሳቡ ዙሪያ ከአጋር አካላት ጋር ውይይት ማድረጉንም አስታውሰው ውይይቱም ፕሮጀክቱ ለሀገሪቱ የቴክኖሎጂ ሽግግር በሚኖረው ፋይዳ ዙሪያ እንደነበር እና አሁን በምን ደረጃ ላይ እንዳለ እውቅና እንደሌላቸው ተናግረው ነበር፡፡

ከዛ ወዲህ የሀብ ሲቲ ላይቭ ሰዎች ወደ ኢትዮጵያ መጥተው እንደማያውቁ የታወቀ ሲሆን ያ ብዙ የተወራለት የዋካንዳ ፕሮጀክትም የውሀ ሽታ ሆኖ ቀርቷል።

መረጃን ከመሠረት!


@EliasMeserett

ELIAS MESERET

21 Oct, 23:06


💠"እሳቱ ሙሉ በሙሉ አልጠፋም፣ እሳት ያልደረሰባቸው ሱቆች በተጨማሪ እንዳይቃጠሉ ስጋት አለን"

(መሠረት ሚድያ)- ዛሬ ማምሻውን መርካቶ ሸማ ተራ ከጃቡላኒ የንግድ ማዕከል ጀርባ ከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ መነሳቱን ተከትሎ አሁን ድረስ (ከለሊቱ 6:39) እሳቱ ሙሉ በሙሉ እንዳልጠፋ በስፍራው የሚገኙ የአይን እማኞች ለመሠረት ሚድያ ተናገረዋል።

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ከንቲባ አዳነች አቤቤን በመጥቀስ እሳቱ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር መሆኑ የተገለፀው የተሳሳተ ነው ያሉት በስፍራው ያሉ ግለሰቦች፣ እሳቱ የመቀነስ አዝማሚያ ቢኖረውም ሙሉ በሙሉ አልጠፋም ወይም በቁጥጥር ስር አልዋለም።

"በቃጠሎው ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት የነባር የገበያ ማእከል ውስጥ ካሉ ስቆች ውስጥ እስከ አሁን ድረስ እሳት ያልደረሰባቸው የተወሰኑ ሱቆች ነበሩ፣ ነገር ግን ሙሉ በሙሉ እሳቱን ማጥፋት ባለመቻሉ የቀሩትም ሱቆች በእሳቱ የመውደም አደጋ አንዣቦባቸዋል" ያሉት ጥቆማ ሰጪዎች አደጋው አሁንም አንዣቦ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

በመንግስት ሀላፊዎች ሄሊኮፕተር ለመጠቀም ጥረት ተደርጎ ነበር ቢባልም በስፍራው እንዳልተገኘ ገልፀዋል።

በሌላ በኩል አደጋው በደረሰበት ወቅት በርካታ ከየት የመጡ እንደሆነ የማይታወቁ ግለሰቦች እቃ እየጫኑ ሲወስዱ እንደነበር ድርጊቱን የተመለከቱ ሰዎች ተናግረዋል፣ ይህም የእሳት አደጋውን አስታኮ ከፍተኛ ዝርፊያ እንደተፈፀመ እንዲገምቱ እንዳደረጋቸው ጠቁመዋል።

መረጃን ከመሠረት!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

21 Oct, 18:38


💠መርካቶ ሸማ ተራ ከጃቡላኒ የንግድ ማዕከል ጀርባ ከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ ተነሳ

(መሠረት ሚድያ)- መርካቶ ሸማ ተራ ከጃቡላኒ የንግድ ማዕከል ጀርባ ወይም ሽንኩርት በረንዳ የሚባለው ሥፍራ ላይ ከበድ ያለ የእሳት አደጋ እንደተከሰተ ታውቋል።

የእሳት አደጋ ሰራተኞች እሳቱን ለማጥፋት፣ የሰውን ሕይወት ለማትረፍ እና ንብረት ለማዳን ከፍተኛ ጥረት እያረጉ እንደሚገኙ በስፋራው ካሉ የመሠረት ሚድያ ተከታታዮች የደረሰን መረጃ ይጠቁማል።

በዚህ ዙርያ ተጨማሪ መረጃ እንደደረሰን እናቀርባለን።

መረጃን ከመሠረት!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

21 Oct, 16:24


#የዕለቱዜና| የጥቅምት 11/2017 ዓ.ም የመሠረት ሚድያ የምሽት ዜና ዘገባዎች:

https://youtu.be/fj2SbYPLGew?si=8quXjMSKFfmRGXfS

ELIAS MESERET

21 Oct, 14:36


💠የዛሬ የጥቅምት 11/2017 ዓ/ም የመሠረት ሚድያ የዜና ዘገባዎች

1. "ልማት የሰውን ልጅ ሲያፈርስ በዓይኔ አየሁት" በማለት አርቲስት አዜብ ወርቁ ታሪካቸውን ስለፃፈችላቸው የእድሜ ባለፀጋ አዲስ መረጃ ይዘናል

2. ከሰሞኑ ለህዝብ ይፋ ሆኖ ብዙዎችን ያስደነገጠው 'ሴት ባክ' የተባለው የግንባታ መመርያ አዲስ ማሻሻያ ተደርጎበታል 

3. የሸገር ከተማ አመራሮች አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ አነጋጋሪ የሆነ ጥቅማጥቅም እየተሰጣቸው ስለመሆኑ መረጃ ይዘናል

4. ከኢትዮጵያ ወደ ኤርትራ የነበረው የስልክ ግንኙነት የተቋረጠው ከየት በኩል ስለመሆኑ ምንጮች ጠቁመውናል

5. በኮሪደር ልማት ምክንያት የፈረሰው ገዳም የደረሰበትን ጉዳት ዝርዝር ይፋ አድርጓል

6. ተሸላሚዎችን ገንዘብ የሚቀበል አንድ የጋናውያን ስብስብ በአዲስ አበባ ሽልማት እያዘጋጀ መሆኑን መስማታችንን የተመለከቱ መረጃዎችን እና ሌሎች ጥቆማዎችን ይዘናል

በዩትዩብ ቻናላችን ዛሬ ምሽት ይጠብቁን ⤵️

https://youtube.com/@meseretmedianews?si=r3CbiYkjigdRWUIr

https://t.me/Eliasmeserett

ELIAS MESERET

21 Oct, 14:09


💠ወደ ደቡብ አሜሪካ ከሚጓዙ ዜጎች ቦሌ ኤርፖርት ላይ እስከ ግማሽ ሚሊዮን ብር ጉቦ ሲጠይቅ የነበረው ግለሰብ ከስራ ታግዶ ምርመራ እየተደረገበት መሆኑ ታወቀ

(መሠረት ሚድያ)- ወደ ደቡብ አሜሪካ የሚጓዙ ዜጎች ቦሌ ኤርፖርት ላይ እስከ ግማሽ ሚሊዮን ብር ጉቦ እየተጠየቁ እንደሆነ መሠረት ሚድያ ከባለፈው አርብ ጀምሮ ሲዘግብ መቆየቱ ይታወሳል። 

በርካታ ጥቆማ ሰጪዎች በሰጡን መረጃ መሠረት በተለይ ወደ ብራዚል የሚጓዙ ዜጎች ለጉዞ ማድረግ ያለባቸውን ፕሮሰስ ሁሉ ጨርሰው እና ከብራዚል ኤምባሲ ቪዛ ተመቶላቸው በበረራ ሰአታቸው ቦሌ አየር ማረፊያ ሲደርሱ "በዛው ልትጠፉ ነው፣ ስለዚህ እንድትሄዱ እንድንፈቅድላችሁ 500 ሺህ ብር አምጡ እየተባልን ነው" ብለዋል።

አንድ ጥቆማ ሰጪ ደግሞ ወደ አንድ የአየር ማረፊያው ቢሮ ሀላፊ በመግባት ሁኔታውን ሲያስረዳ "እዛው ጨርስ" እንደተባለ ተናግሯል።

በዚህ ዙርያ ዛሬ ከአየር መንገዱ አዲስ መረጃ የደረሰን ሲሆን ሚድያችን ለአየር መንገዱ በሰጠው ጥቆማ መሰረት ይህን ድርጊት ሲፈፅም የነበረው ግለሰብ ከስራ ታግዶ ምርመራ እንደተጀመረበት ታውቋል።

ውጤቱም በቅርቡ ለህዝብ ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።

መረጃን ከመሠረት!

https://t.me/Eliasmeserett

ELIAS MESERET

21 Oct, 13:35


💠በአጋሮ ከተማ ከኮሪደር ልማት ጋር ተያይዞ ግለሰቦች አጥራቸውን ለማሳመር  እስከ 100 ሺህ ብር እንዲያወጡ እየተገደዱ መሆኑን ተናገሩ

(መሠረት ሚድያ)- የአጋሮ ከተማ እንደ እድሜ ጠገብነቷ ዕድገቷ ውስን ሆኖ መቆየቱን የሚናገሩት ነዋሪዎች ሆኖም ከኮሪደር ልማት መጀመር ጋር ተያይዞ ጥሩ ነገሮች ይኖሩታል የተባለለት ሥራ መልኩን ቀይሮ 'ምነው በቀረብን' የሚያስብል ደረጃ ላይ ደርሷል ብለዋል።

"ምንም አይነት የካሳ ክፍያ ሳይሰጥ ቤቶች ፈርሰዋል፣ እንዲሁም ህዝቡ በፈቃዱ ቤቱን ወደኋላ ቢያስጠጋም በኮሎን እና ግንብ ካልሆነ ትነሳላችሁ የሚል ማስፈራሪያ እየደረሰን ነው" ብለው ለመሠረት ሚድያ ቃላቸውን የሰጡት ነዋሪዎች አብዛኛው የቀበሌ ቤት ነዋሪ ስለሆነ በፍራቻ የቻለ ከኪሱ ያልቻለ ዘመድ አስቸግሮና ለምኖ የተባለውን እያረገ ነው ብለዋል።

በዚህ ቢቆም ጥሩ ነበር የሚሉት ነዋሪዎች ነገር ግን ቀለም ለማስቀባት እና የተለያዩ መብራቶችን ለመስቀል ህብረተሰቡ እንዲማረር ሆኗል ይላሉ።

"እኚህ ሒሳቦች ሲሰሉ ከ80 ሺህ እስከ100 ሺህ ብር ይሆናሉ። እኔ እንኳን በግሌ ከ80 ሺህ በላይ አውጥቻለሁ" ያሉት አንድ ነዋሪ በየሰአት ልዩነት የቀበሌ ሰዎች እየመጡ የማሸግ እና የማስፈራራት ድርጊት እየፈፀሙብን ነው ብለዋል።

አቅማችን ተሟጧል፣ ሰው በጣም ያለውን ገንዘብ በማውጣት ጎድቷል የሚሉት ነዋሪዎች ህዝብ ጉዳታችንን ይወቅልን ብለዋል።

መረጃን ከመሠረት!


https://t.me/Eliasmeserett

ELIAS MESERET

21 Oct, 09:59


💠AddisAbaba #ኮንዶሚኒየም

🔵 " ከ97 ጀምሮ የቆጠቡ ሰዎች መቼ ነው የሚደርሳቸው ፤ መቼ ነው የሚኖሩበት ? ሳይኖሩበት ሊሞቱ ነው እኮ ! " - አቶ አበበ አካሉ

" የ97 ደግሞ የሚባል የለም። እኛ እስከምናውቀው ዘግተናል " - ከንቲባ አዳነች አቤቤ


ከአዲስ አበባ የኮሪደር ስራ ጋር በተያየዘ በርካቶች በልማት ተነሺነት ከኖሩበት አካባቢ ተነስተው ወደ ተለያዩ ጋራ መኖሪያ ቤቶች እንዲገቡ እየተደረገ ነው።

ምንም እንኳን ተነሺዎቹ መግባታቸው ላይ ቅሬታ ባይፈጥርም ከ97 አንስቶ ሲቆጥቡ የኖሩ ነዋሪዎች መፍትሄ ሳያገኙ መቅረታቸው እና አሁን ላይ አስተዳደሩ ቤት የተሰጠ መሆኑ ቅሬታ አሳድሯል።

ከሰሞኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተገኙበት በተካሄደ የኮሪደር ስራውን በሚመለከት የውይይት መድረክ ላይ ይኸው ቅሬታና ጥያቄ ተነስቷል።

ጥያቄውን ካነሱት አንዱ ፖለቲከኛው አቶ አበበ አካሉ ናቸው።

" ሲቆጥቡ የኖሩ ሰዎች ጉዳይ ምን ደረሰ ? አሁን ማህበረሰቡ ምን ያማል ከተማ አስተዳደሩን ' እኛ በቆጠብነው ገንዘብ ነው የልማት ተናሺዎችን እያሰፈረ ያለው ' የሚል ሮሮ አለ።

ለዚህ ምንድነው ምላሻችሁ ?

ከ97 ጀምሮ የቆጠቡ ሰዎች መቼ ነው የሚደርሳቸው ፤ መቼ ነው የሚኖሩበት ሳይኖሩበት ሊሞቱ ነው እኮ ! " ሲሉ ገልጸዋል።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ ምን መለሱ ?

" የኮንዶሚኒየም ቤት እስኪ ከየት አምጥታችሁ ነው በዚህ ደረጃ ያላችሁ ኃላፊዎች ' በቆጡት ገንዘብ ነው የሚሰራው ' የምትሉት።

እነ ንግድ ባንክ ናቸው ብሩን የሚያቀርቡት እስቲ እንነጋገር ትንሽ ወደ መረጃው ጠጋ ብላችሁ ብናወራ ምናለበት።

ኮንዶሚኒየም በብድር ነው የሚሰራው። የከተማ አስተዳደሩ በጀቱን አስይዞ ነው የሚበደረው።

ለምንድነው የሚቆጥቡት ? ከተባለ ዕጣ የደረሳቸው ዕለት የሚከፍሉትን እንዳያጡ ነው። እንጂ ቤቱን መገንቢያ አይደለም። ልክ ቤቱ ሲገነባ ብሩን ይከፍሉታል።

ሁለተኛ እንዴት ነው እኛ ብቻችንን የምንጠየቅበት ? ቤት ባልተዘጋጀበት በሚሊዮኖች መዝግቦ ቆጥቡ ብሎ ኃላፊነት ወስዶ የሰራ አካል እያለ ለምንድነው እኛ የምንወቀሰው ?

ቤት ሳያዘጋጅ ዜጎችን ልክ እንደ ማታለያ በሚሊየን መዝግቦ የበተነ እያለ ለምንድነው እኛ የምንወቀሰው ?

የኮንዶሚኒየም ቤት አጠቃላይ አንድ ቦታ እጅብ ብሎ ስለተሰራ ብዙ ይመስላችኋል እንጂ እስካሁን እስካጠናቀቅነው ያለው 300,000 ነው። የተመዘገበው በሚሊዮን ነው። በየጊዜው ተስፋ ቆርጦ፣ ተጣርቶ ተጣርቶ እኛ የደረስንበት 600,000 ነው። አክተቭ ይቆጥብ የነበረው። ግን ቤት ማግኘት እንዳለባቸው እናምናለን። ቤት ማግኘት አለባቸው።

ካለቁት ኮንዶሚኒየሞች ብራቸው ተዘርፎ፣ ቀድሞ ተከፍሎ ያልተሰራ 80 ህንጻ ብር ተከፍሎበት ጥለው ሄደዋል። በብዙ ውጣውረድ ነው 139,000 ቤቶችን የጨረስነው። የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ብቻ።

አሁንም ቢሆን ግን የከተማችን ነዋሪዎች ቤት ማግኘት አለባቸው። ለዚህም በኮንዶሚኒየም ብቻ አይደለም እንደ ቀድሞ በሚፈለገው ደረጃ ብድር ማግኘት አልቻልንም ከባንክ። ኮንዶሚኒየም መጥፎ ስለሆነ አላቆምነውም።

ከተማ አስተዳደሩ ዕዳ እየከፈለ ነው። ንግድ ባንክ የሚያበድረው የባለሃብትን ገንዘብ ነው አይደል ? 56 ቢሊዮን የኮንዶሚኒየም ዕዳ ነው የተረከብነው ዋስትና የሚሰጠው ከተማ አስተዳደሩ ስለሆነ ክፈሉ ተባልን ተገደድን በለውጥ ዘመኑ 30 ቢሊዮን ከፍለናል የኮንዶሚኒየም ዕዳ።

ይህ ሁሉ ዕዳ አንደኛ በከፍተኛ ሰብሲዲ ስለሚሰራ ነው ፤ ሌላው ያልተሰሩ ቤቶች የተከፈለባቸው አሉ። ሳይከፍሉ ሲሸጡ በተለያየ መንገድ ሲተላለፉ የነበሩ ቤት ውስጥ ያገኘናቸው ሰዎች ከግለሰብ የገዙ ናቸው፤ ሊገደዱ አይችሉም የኮንዶሚኒየም ክፈሉ ተብለው። አጣርተን እኮ በሚዲያ ነግረናችኋል ፤ ያጋጠመንን።

አሁን በግልና በመንግሥት አጋርነት ወደ 100,000 ቤቶች አስጀምረናል። የቁጠባ ቤቶችንም እየሰራን እያከራየን ነው። በሪስልቴትም በግል የሚሰሩትን እንደ ከተማው ፕሮጀክት ጠጋ ብለን እያገዝን ቶሎ እንዲጨርሱ እያደረግን ነው።

እስካሁን የቆጠቡትን አሁን በግልና መንግሥት ትብብር ከምንሰራው  ውስጥ ቅድሚያ ሊያገኙ የሚችሉበትን አግባብ እየተከተልን ነው። ሁለተኛ ደግሞ ተደራጅተው በማህበር እንዲሰሩ ...እስካሁን ለተደራጁት መሬት አስረክበናል።

መነገጃ አታድርጉት፤ ከእውነታው ውጭ መነጋጃ ማድረጉ አይጠቅምም።

የ97 ደግሞ የሚባል የለም። እኛ እስከምናውቀው ዘግተናል። ባለፈው ያስጨረስናቸውን ኮንዶሚኒየም ቤቶች ቅድሚያ 97 አክቲቭ ቆጣቢዎች ሁሉ ዕጣ እንዲወጣላቸው ተደርጓል።

እነሱ ከወጣላቸው በኃላ ዲአክቲቬት ያደረገውን አካውን አክቲቬት ያደረገ ካለ እሱ ስለቆጠበ ቤት ስለሚፈልግ ለሚቀጥለው ጊዜ ሊታይ ይገባል ፤ እንጂ በዚህ መንገድ መቅረብ የለበትም " ሲሉ መልሰዋል።

via tikvah

https://t.me/Eliasmeserett

ELIAS MESERET

20 Oct, 20:14


💠የብሔራዊ ባንክ ገዢ ዛሬ በዋሽንግተን ዲሲ ተገኝተው ዲያስፖራዎችን እያወያዩ ነው

(መሠረት ሚድያ)- የብሔራዊ ባንክ ገዢ አቶ ማሞ ምህረቱ ወደ አሜሪካ አቅንተው በዛሬው እለት በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ያሉ ዲያስፖራዎችን እያወያዩ እንደሆነ መሠረት ሚድያ ማምሻውን የደረሰው መረጃ ያሳያል።

በአቶ ማሞ የተመራው ቡድን ዋና አላማው የዲያስፖራው ማህበረሰብ አባላት በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ያላቸውን አስተዋፅኦ ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ለማወያየት እንደሆነ ሰምተናል።

ከብሔራዊ ባንክ ገዢው እና ከልኡክ ቡድናቸው በተጨማሪ የበርካታ የኢትዮጵያ የንግድ ባንኮች ዋና ስራ አስፈፃሚዎች አብረው ወደ አሜሪካ እንደተጓዙ እና ይህ ዜና እየተፃፈበት ሰአት ድረስ ስብሰባው እንደቀጠለ ታውቋል። መሠረት ሚድያ የስብሰባውን ውጤት ከስብሰባው መጠናቀቅ ይዞ የሚቀርብ ይሆናል።

የቀድሞው በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ፍፁም አረጋ በቅርቡ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ሆነው መሾማቸው ይታወሳል።

መረጃን ከመሠረት!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

20 Oct, 17:58


💠ከዜናዎቻችን| በደቡባዊ ኢትዮጵያ በርካታ ስፍራዎች የወባ በሽታ ዜጎችን እያረገፈ እንዳለ ተሰማ

- በሽታው እያደረሰው ያለውን ጉዳት ገፅታ እንዳያበላሽ በሚል ይፋ እንዳልተደረገ የጤና ባለሙያዎች ተናግረዋል

(መሠረት ሚድያ)- በደቡባዊ ኢትዮጵያ በርካታ ስፍራዎች የወባ በሽታ ዜጎችን እያረገፈ እንዳለ ተሰምቷል። በተለይ በወላይታ ዞን ባሳለፍነው ወር ብቻ ከ6,000 ሰዎች በላይ በበሽታው የተጠቁ ሲሆን ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ሰዎች ደግሞ ህይወታቸው እንዳለፈ አንድ በዞኑ የሚሰሩ እና ስሜ አይጠቀስ ያሉ የጤና ባለሙያ ተናግረዋል።

"አሁን ወባ በወረርሽኝ ደረጃ ተከስቷል፣ ከስድስት ሺህ በላይ አዳዲስ ታማሚ አለ፣ ይህ ደግሞ በግል ተቋማት ታመው ያሉትን እና ወደ ጤና ተቋም ያልሄዱትን ሳይጨምር ነው" ያሉት የጤና ባለሙያው በአንድ መንደር ብቻ ባሳለፍነው ሀሙስ እለት አራት ሰው በወባ እንደሞተ በአካል ሄደው እንዳረጋገጡ ተናግረዋል።

ሀላፊው ጨምረው ለዞኑ ገፅታ ጥሩ አይደለም በሚል መረጃው በአብዛኛው ተድበስብሶ እየቀረ ነው በማለት ተናግረዋል።

ከወላይታ ዞን በተጨማሪ በሽታው በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያም ከፍተኛ የሰው ህመም እና ሞት እያስከተለ መሆኑ ታውቋል። ባለፉት ሁለት ወራት ምርመራ ከተደረገላቸው 370 ሺህ ዜጎች ውስጥ ከ240 ሺህ በላይ ዜጎች በወባ በሽታ መያዛቸውን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታውቋል፡፡

በሌላ በኩል መንግሥት ቶሎ መድረስ ካልቻለ የሀዲያ ዞን ህዝብ በወባ ወራርሽን እያለቀ መሆኑን የሚደርሱን መረጃዎች ይጠቁማሉ። እጅግ አስጊ በሚባል ደረጃ ላይ ይገኛል የተባለው የዞኑ የበሽታ ምጣኔ በየቀኑ በርካቶችን እየቀጠፈ እንደሚገኝ ሰምተናል።

ከነዚህ በተጨማሪም በከምባታ፣ በጉራጌ፣ በምስራቅ ወለጋ፣ በዳውሮ፣ በከፋ እና ቤንች ዞኖች እና አዋሳኝ ስፍራዎች አደጋው የከፋ ሁኔታ ላይ መድረሱን መሠረት ሚድያ ያሰባሰበው መረጃ ይጠቁማል።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

20 Oct, 17:53


💠ከዜናዎቻችን| ወደ ደቡብ አሜሪካ የሚጓዙ ዜጎች ቦሌ ኤርፖርት ላይ እስከ ግማሽ ሚሊዮን ብር ጉቦ እየተጠየቁ እንደሆነ ተናገሩ

(መሠረት ሚድያ)- ወደ ደቡብ አሜሪካ የሚጓዙ ዜጎች ቦሌ ኤርፖርት ላይ እስከ ግማሽ ሚሊዮን ብር ጉቦ እየተጠየቁ እንደሆነ ለመሠረት ሚድያ በሰጡት ጥቆማ ተናግረዋል።

በርካታ ጥቆማ ሰጪዎች በሰጡን መረጃ መሠረት በተለይ ወደ ብራዚል የሚጓዙ ዜጎች ለጉዞ ማድረግ ያለባቸውን ፕሮሰስ ሁሉ ጨርሰው እና ከብራዚል ኤምባሲ ቪዛ ተመቶላቸው በበረራ ሰአታቸው ቦሌ አየር ማረፊያ ሲደርሱ "በዛው ልትጠፉ ነው፣ ስለዚህ እንድትሄዱ እንድንፈቅድላችሁ 500 ሺህ ብር አምጡ እየተባልን ነው" ብለዋል።

አንድ ጥቆማ ሰጪ ደግሞ ወደ አንድ የአየር ማረፊያው ቢሮ ሀላፊ በመግባት ሁኔታውን ሲያስረዳ "እዛው ጨርስ" እንደተባለ ተናግሯል።

በቦሌ አየር ማረፊያ ላይ በርካታ የመብት ጥሰቶች እና ሙስና እንደሚፈፀም ከዚህ በፊት ተደጋግሞ መነሳቱ ይታወሳል። ይሁንና በአየር ማረፊያው የፍተሻ እና ጥበቃ አካላት አንድ ተጓዥ ላይ በየካቲት 2016 ዓ/ም ዝርፊያ እና እንግልት ከተፈፀመ በኋላ ጉዳዩ ወደ ማህበራዊ ሚድያ በመምጣቱ መንግስት ምላሽ ሰጥቶበት ነበር።

በወቅቱ አንድ ትውልደ ኢትዮጵያዊት ግለሰብ በፍተሻ ወቅት "ሻንጣሽን ከፍተሽ አሳዪን፣ ማሽኑ የሆነ ነገር ያሳየናል" በማለት ሻንጣዎቿን አስከፍተዋት በዚህ ወቅት የያዘችውን የግል መገልገያ ጌጣጌጥ እና በህጋዊ መንገድ የያዘችውን ዶላር አካፍዪን ማለታቸው ይታወሳል።

ይህን መረጃ ተንተርሶ በተደረገ ማጣራት ድርጊቱን ፈፃሚዎች በካሜራ ክትትል ተይዘው ለእስር ተዳርገው ነበር።

እንዲህ አይነት ኤርፖርት ላይ በፀጥታ እና ኢሚግሬሽን ሰራተኞች የሚፈፀም ድርጊት በተለይ ወደ አረብ አገራት የሚሄዱ ዜጎች የበረታ እንደሆነ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

በኤርፖርት ያሉ እንዲህ አይነት ጉዳዮች ሲነሱ አንዳንዶች በቀጥታ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር የሚያያይዙት ቢሆንም የኤርፖርት ጥበቃ እና ፍተሻ የሚከናወነው በአየር መንገዱ ሳይሆን በሌሎች የመንግት የደህንነት እና የፅጥታ አካላት መሆኑን ለማሳሰብ እንወዳለን።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

17 Oct, 04:06


💠"የመሬት መንቀጥቀጡ እና ተያያዥ ንዝረቶች በተለይ ለአዲስ አበባ ትላልቅ ህንፃዎች ስጋት ናቸው"

(መሠረት ሚድያ)- የዛሬ ምሽቱን ጨምሮ ከሰሞኑ ብቻ ሶስት ግዜ የተከሰቱትን የመሬት መንቀጥቀጦች ተከትሎ ለአዲስ አበባ ትላልቅ ህንፃዎች ስጋት እንዳላቸው አንድ የዘርፉ የመንግስት ሀላፊ ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።

በጉዳዩ ዙርያ ለሚድያዎች መረጃ ለመስጠት ፈቃድ እንደሌላቸው በመግለፅ ስሜ አይጠቀስ ያሉት እኚህ የስራ ሀላፊ እንደሚሉት የአዲስ አበባ በርካታ ህንፃዎች ሲገነቡ ከፍተኛ የመሬት መንቀጥቀጥን እና በተፈጥሮ ሊከሰቱ የሚችሉ ከባድ ተያያዥ ንዝረቶችን መከላከል እንዲችሉ ታሳቢ ተደርገው አይደለም።

"ስለሆነም አዲስ አበባ እና እንደ አዋሽ ካሉ የመርዕደ መሬት በከፍተኛ ደረጃ ሊያጠቃቸው ከሚችሉ ቦታዎች አቅራቢያ ያሉ ህንፃዎች ለአደጋ እጅግ ተጋላጭ ናቸው፣ አያድርስ እና በሬክተር ስኬል ከ5.5 በላይ ርዕደ መሬት ቢከሰት አደጋ መድረሱ አይቀርም" ያሉት ሀላፊው ይህ ሟሟረት ሳይሆን ሊሆን የሚችለውን ነገር መረጃን በማስደገፍ መተንተን እና መፍትሄ ማስቀመጥ ያስፈልጋል ብለዋል።

መስከረም 26 ቀን ምሽት ላይ በበርካታ የአዲስ አበባ እና አጎራባች ከተሞች እንዲሁም በአዋሽ ዙርያ እና አቅራቢያ ባሉ ስፍራዎች የመሬት ንዝረት መከሰቱ ይታወሳል። በዚህ የተደናገጡ በርካታ ሰዎች ቤታቸውን ጥለው ወደ ውጪ ሲሯሯጡ ታይተው ነበር።

ይህ 4.9 ሆኖ የተመዘገበ የመሬት ርዕደትን ተከትሎ በሳምንቱ ጥቅምት 3 ቀን 4.6 ሆኖ የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ አዋሽ አካባቢ ተመዝግቦ ነበር። ዛሬ ምሽትም 4.6 ሆኖ የተመዘገበ ርዕደ መሬት አዋሽ ላይ ተከስቶ ንዝረቱ እስከ አዲስ አበባ ተሰምቷል።

ሀላፊው "ወደፊትም ተመሳሳይ እና መጠናቸው ዝቅ ወይም ከፍ የሚሉ የመሬት መንቀጥቀጦች ሊከሰቱ ስለሚችሉ የመንግስት ተቋማት፣ ሚድያዎች፣ የአደጋ ምላሽ ሰጪ ድርጅቶች ወዘተ ህብረተሰቡ ላይ የማንቃት ስራ እና የአደጋ ምላሽ አሰጣጥ ላይ ትኩረት ማድረግ ይገባል" ብለዋል።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጂኦ ፊዚክስ ስፔስ ሳይንስ እና አስትሮኖሚ ዳይሬክተር ዶ/ር ኤልያስ ሌዊ በመዲናዋ የተከሰተው የመሬት ንዝረት በአዋሽ ፈንታሌ ተራራ አካባቢ በተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ ሞገድ አማካይነት የተፈጠረ መሆኑን ደጋግማው መግለፃቸው ይታወሳል።

የፈንታሌ አካባቢ ለመሬት መንቀጥቀጥ የተጋለጠ አካባቢ መሆኑን የገለፁት ዶ/ር ኤልያስ፤ አካባቢው ብዙ ነዋሪ የሌለበት መሆኑንም ተናግረዋል።

ተቋሙ ተጨማሪ መረጃዎችን የማሰባሰብ ስራ እየሰራ መሆኑንም ነው የተናገሩት ዶ/ር ኤልያስ በቀጣይ ዝርዝር መረጃዎችን ተቋሙ እንደሚያቀርብ እና እንዲህ ያለ አደጋ ሲያጋጥም የቤት ቋሚዎች በተለይ ኮንዶሚኒየም ህንጻ ላይ ያሉ ሰዎች ኮለኖች አካባቢ መጠጋት፣ ጠረጴዛ ስር መግባት፣ ሊፍት አለመጠቀም፣ ውጪ ላይ የመብራትና መሰል ምሶሶዎችን አለመጠጋት እንደሚያስፈልግ መክረዋል።

መረጃን ከመሠረት!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

16 Oct, 18:45


💠 ኢትዮቴሌኮም : ዛሬ የኢትዮ ቴሌኮም 10 በመቶ የአክሲዮን ሽያጭ ይፋ ሆኗል።

ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በተካሄደ ሥነ-ስርዓት የኢትዮ ቴሌኮም 10 በመቶ የአክሲዮን ሽያጭ ይፋ ተደርጓል።

የአክሲዮን ሽያጭ ጊዜው ከዛሬ ጥቅምት 6 ጀምሮ እስከ ታኅሣስ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ይቆያል ተብሏል፡፡

ዝርዝር መረጃ ፦

- በ2016 በወጣው የሂሳብ ሪፖርት የድርጅቱ ካፒታል ➡️ 100 ቢሊዮን ብር ነው።

- በዓለም አቀፍ የ3ተኛ ወገን የገበያ ተመን መሰረት ድርጅቱ የሚያወጣው ዋጋ ➡️ 300 ቢሊዮን ብር ነው።

- በመጀመሪያው ዙር መደበኛ የአክሲዮን ሽያጭ የቀረበው ➡️ 100 ሚሊዮን ሼር ነው።

- የአንድ ሼር ዋጋ ➡️ 300 ብር ነው።

- 100 ሚሊዮን ሼር በ300 ብር ሲሸጥ ኢትዮ ቴሌኮም ከሼር ሽያጭ ➡️ 30 ቢሊዮን ብር ያገኛል።

- ዝቅተኛ መግዛት የሚቻለው የሼር መጠን  ➡️ 33 ሼር ሲሆን ይህን በገንዘብ ሲቀመጥ 9,900 ብር ይሆናል።

- ከፍተኛው መግዛት የሚቻለው የሼር መጠን 3,333 ሲሆን ይህን በገንዘብ ሲቀመጥ ➡️999,900 ብር ይሆናል።

- መግዛት የሚቻለው ከዛሬ ጥቅምት 6 እስከ ታህሳስ 25 ድረስ ይሆናል።

- የሼር አባላቱ የሚታወቁት ➡️ ጥር 23/2017

- ሽያጩ በቴሌብር ብቻ የሚደረግ ይሆናል።

- ክፍያውን በ48 ሰዓት ውስጥ መክፈል ይቻላል።

- አንድ አክሲዮን ግዢ ሲፈጸም ከአክስዮኑ ዋጋ በተጨማሪ 1.5% የአገልግሎት ክፍያ እና ተጨማሪ እሴት ታክስ የሚከፍል ይሆናል።

- ከከፍተኛው የአክሲዮን መጠን በላይ መግዛት አይቻልም።

- ግብይቱ የሚካሄደው በኢትዮጵያ ብር ብቻ ነው።

via tikvah

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

16 Oct, 18:34


💠አንድ ሰው ከኢትዮ ቴሌኮም የገዛውን አክሲዮን ድርሻ ማዘዋወር፤ አትርፎ መሸጥ ፤ እንደ ማሲያዣ መጠቀም ቢፈልግ ይችላል ወይ ?

አትዮ ቴሌኮም አሁን የሚጀመረው የአክሲዮን ሺያጭ የመጀመሪያው ምዕራፍ እንደሆነ አስታውቋል።

በዚህ ምዕራፍ ዜጎች የአክሲዮን ድርሻ ብቻ መግዛት የሚችሉ ይሆናል።

ዜጎች ድርሻቸውን ማዘዋወር ፤ አትርፎ መሸጥ ፤ እንደ ማሲያዣ መጠቀም የሚችሉት ኢትዮ ቴሌኮም ሁለተኛ ምዕራፍ ብሎ ባስቀመጠው ሲሆን ይህም ገና በሂደት ላይ እንዳለ ተጠቅሷል።

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ ቴሌኮም በ " listing " ሂደት ላይ እንደሚገኝ እና ይህም በአጭር ጊዜ እንደሚጠናቀቅ የጠቀሱ ሲሆን ይፋዊ ቀን ግን አልተቆረጠለትም።

የሁለተኛው ዙር አክሲዮን ሽያጭ ሲጀመር ደግሞ ዜጎች ድርሻ ማዘዋወር ፣ አትርፎ መሸጥ ፤ እንደ ማሲያዣ መጠቀም ያስችላቸዋል።

እንዴት ነው አክሲዮን የሚገዛው ?

በቴሌብር ላይ ነው መግዛት የሚቻለው። ቴሌብር ላይ ሲገቡ አክሲዎን ለመግዛት የሚል አማራጭ ይገናኛል (ልክ ላውንች ሲደረግ) በዛ አማካኝነት ነው መግዛት የሚቻለው። በዛ ዝርዝር መረጃ ይገኛል፤ የደብንበኝነት ውልን ስለሚኖር አንብቦ መቀጠል ይችላል ከተስማሙ።

(እስካሁን ድረስ ቴሌብር ላይ ይህ የአክሲዎችን ሽያጭ አማራጭ አልመጣም ልክ ሲመጣ እናሳውቃችኃለን)

ፎርሙን በ48 ሰዓት ውስጥ ማስተካከል  ይቻላል ፤ በተመሳሳይ ክፍያም በ48 ሰዓት ውስጥ መከፈል አለበት። ከ48 ሰዓት በኃላ ፎርሙን ማስተካከል አይቻልም።

ፎርሙን መጀመሪያ በመደበኛ መታወቂያ፣ መንጃ ፍቃድ ፣ ፓስፖርት መሙላት የሚቻል ሲሆን መጨረሻ ላይ የሼር ባለቤት ለመሆን የናሽናል አይዲ (ፋይዳ) ያስፈልጋል።

ሼር ገዢ ተመዝጋቢዎች ቁጥር ለሽያጭ ከቀረበው ሼር በላይ ከመጣ ከዛ ውስጥ እነማን የሼሩ ባለቤት ይሆናሉ የሚለውን ለመለየት የሚያስችል አሰራር ተቀምጧል። (በቀጣይ በዚህ ላይ መረጃ እናቀርባለን)

➡️ ሼር መግዛት ማመልከይ የሚችለው ኢትዮጵያዊ ዜጋ እና እዚሁ ሀገር ውስጥ በአካል ያለ ነው።

2016 ዓ/ም በወጣ የሂሳብ ሪፖርት የድርጅቱ የካፒታል 100 ቢሊዮን ብር ሲሆን በዓለም አቀፍ የ3ተኛ ወገን የገበያ ተመን መሰረት ድርጅቱ የሚያወጣው ዋጋ 300 ቢሊዮን ብር ነው።

በመጀመሪያ ዙር መደበኛ የአክሲዮን ሽያጭ የቀረበው ደግሞ 100 ሚሊዮን ሼር ነው። የአንድ ሼር ዋጋም 300 ብር ነው። ዝቅተኛ መግዛት የሚቻለው የሼር መጠን  33 ሼር ሲሆን ይህን በገንዘብ ሲቀመጥ 9,900 ብር ይሆናል። ከፍተኛው መግዛት የሚቻለው የሼር መጠን 3,333 ሲሆን ይህን በገንዘብ ሲቀመጥ 999,900 ብር ይሆናል።


via tikvah


@EliasMeserett

ELIAS MESERET

16 Oct, 17:07


#የዕለቱዜና| የጥቅምት 6/2017 ዓ.ም የመሠረት ሚድያ የምሽት ዜና ዘገባዎች:

https://youtu.be/15mM0f3vPpA?si=OGOcEcoqaQmpqyv0

ELIAS MESERET

16 Oct, 16:12


💠ከወንድም ጌጡ ተመስገን እና ጓድ ታደለ አሰፋ ጋር በአፍሪካን ኢምፓክት አዋርድ ፕሮግራም

Was fun.

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

15 Oct, 17:20


💠ለግልፅነት ከሚሰራበት ቦታ ተባሮ እና የሚኖርበት ቤት እንደሚፈርስ ሲነገረው ራሱን ስላጠፋው አዲሱ ካሳሁን ትናንት አንድ መረጃ እና የድጋፍ ጥሪ አቅርቤ ነበር

እስከ አሁኑ ሰአት ድረስ ብቻ 520,000 ብር (አምስት መቶ ሀያ ሺህ ብር) በባለቤቱ የቀጥታ የባንክ አካውንት ድጋፍ ተደርጎላታል።

ድጋፍ ላደረጋችሁ እንዲሁም መረጃውን በአካውንታችሁ እና ገፃችሁ መልሳችሁ ሼር ላደረጋችሁ ሁሉ ምስጋና ይድረሳችሁ።

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

15 Oct, 15:54


💠አሁን ህዝቡ በጣም ገቢው አድጎ ስለበለፀገ አምና በሳንቲሞች ይጨምር የነበረው የትራንስፖርት ዋጋ አሁን እስከ እጥፍ በሚሆን ጭማሪ አሳይቷል...

የመዓት ግዜ!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

15 Oct, 14:53


#ትንታኔ| የኮሪደር ልማት አወዛጋቢ ሆኖ ቀጥሏል፣ አንዳንድ የተቃውሞ ድምፆችም መሰማት ጀምረዋል

ፕሮጀክቱ ከአዲስ አበባ ወደ ክልል እና የገጠር ስፍራዎች ጭምር እየተስፋፋ ነው፣ የህዝቡ እጣ ፈንታ ምን ይሆን?

በዚህ ዙርያ ያቀረብነው ዳሰሳ ይመልከቱ:

https://youtu.be/ClFkAlwSzaA?si=dhuPuOxQ5gW3jEkP

ELIAS MESERET

15 Oct, 14:40


💠በአማራ ክልል እየተፈፀሙ ባሉ ተደጋጋሚ የድሮን ጥቃቶች በርካታ ዜጎች እንደተገደሉ እንደሆነ ታወቀ

(መሠረት ሚድያ)- ባለፉት አምስት ቀናት ውስጥ በአማራ ክልል የተለያዩ ስፍራዎች እየተፈፀሙ ያሉ የድሮን ጥቃቶች በርካታ ዜጎችን ለሞት እየዳረጉ እንደሆነ የክልሉ ነዋሪዎች ለመሠረት ሚድያ እየተናገሩ ይገኛሉ።

የአይን እማኝ የሆኑ እነዚህ ዜጎች ባደረሱን መረጃ መሰረት በዛሬው እለት ባህር ዳር አቅራቢያ በሚገኘው ሜጫ ወረዳ፣ አማሪት ቀበሌ ተደጋጋሚ የድሮን ጥቃቶች ተፈፅመው ንፁሀን ዜጎች ጭምር ተገድለዋል።

በሌላ በኩል በዳጋሞት ወረዳ፣ ፈረስ ቤት ከተማ እንዲሁ በደረሰ ጥቃት በርካታ ሰዎች ለሞት እና መቁሰል እንደተዳረጉ የደረሰን መረጃ ይጠቁማል።

ከዚህ በተጨማሪ በዛሬው እለት ከሞጣ ከተማ በ34 ኪሜ ርቀት ላይ በምትገኘው አስተሪዮ ከተማ መንግስት በተመሳሳይ የድሮን ጥቃት መፈፀሙ ታውቋል።

መንግስት በሚፈፅማቸው የድሮን ጥቃቶች ዙርያ ማብራርያ የማይሰጥ ሲሆን ከዚህ በፊት ግን ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ የኢትዮጵያ ጦር ድሮን የታጠቀው አለኝ ለማለት ሳይሆን ሊጠቀምበት እንደሆነ መግለፃቸው ይታወሳል።

ይሁንና በአማራ ክልል በቀጠለው ጦርነት ሰለባ እየሆኑ ያሉ ንፁሀን ዜጎች ቁጥር እየጨመረ እንደሆነ እየወጡ ያሉ አንዳንድ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

መረጃን ከመሠረት!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

15 Oct, 14:35


💠ከዜናዎቻችን| የደሞዝ ማሻሻያ ረቂቅ ሰነድን አሾልካችሁ አወጣችሁ የተባሉ ሰራተኞች መታሰራቸው ታወቀ

(መሠረት ሚድያ)- በቅርቡ ይፋ የሆነውን የደሞዝ ማሻሻያ ረቂቅ ሰነድን አሾልካችሁ አወጣችሁ የተባሉ ሰራተኞች መታሰራቸውን መሠረት ሚድያ ሰምቷል።

የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙን ተግባራዊ መሆን ተከትሎ በመንግስት ቃል የተገባው የመንግስት ሰራተኞች የደሞዝ ጭማሪ ለበርካታ ሳምንታት ምንም መረጃ ሳይሰጥበት መቆየቱ ይታወሳል።

ይሁንና የዛሬ ወር ገደማ ጳጉሜ 1/2016 ዓ/ም አንድ የደሞዝ ጭማሪውን ያሳያል የተባለ ዶክመንት ማህበራዊ ሚድያ ላይ በስፋት ሲሰራጭ እንደነበር ይታወሳል።

መሠረት ሚድያም በወቅቱ ዶክመንቱ ትክክለኛ መሆኑን መዘገቡ ይታወሳል።

አሁን በደረሰን መረጃ መሰረት ደግሞ ይህን የደሞዝ ማሻሻያ ረቂ ሰነድን አሾልካችሁ እንዲወጣ አድርጋቹሃል የተባሉ የገንዘብ ሚኒስተር ሰራተኞች ተይዘው መመርመራቸውን እና ወደ ቃሊቲ እስር ቤት ተወስደው እንዲቆዩ መደረጋቸው ታውቋል።

እነዚህ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የፅህፈት ቤት ሀላፊ እና የመዝገብ ቤት ሰራተኞች መንግስቱ ጉዳዩን ይፋ ሳያደርግ በስልክ ፎቶ በማንሳት በማህበራዊ ሚድያ በመልቀቅ ተጠርጥረው ነው መታሰራቸው የተሰማው።

ይህ ሰነድ ማህበራዊ ሚድያ ላይ ከወጣ በሗላ ከፍተኛ ቅሬታ በህዝብ ዘንድ በመፈጠሩ መንግስት ጉዳዩን ይፋ ከማድረግ ተቆጥቦ ቆይቶ ነበር።

ይሁንና ጉዳዩ ለሳምንታት ያዝ ከተደረገ በኋላ ከመስከረም ወር ጀምሮ ታሳቢ የሚደረግ የደመወዝ ጭማሪ በሚኒስትሮች ምክር ቤት መጽደቁን የገንዘብ ሚኒስትሩ ባሳለፍነው ሳምንት ገልፀው ነበር።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

15 Oct, 14:28


💠ከዜናዎቻችን| ዶ/ር አርከበ እቁባይ የፃፉት አዲስ መፅሀፍ ሊወጣ መሆኑ ታወቀ

(መሠረት ሚድያ)- "The Oxford Handbook on the Greening of Economic Development" የተባለው ይህ አዲስ መፅሀፍ የሚታተመው በኦክስፎርድ ዩኒቨርስቲ ሲሆን የኢኮኖሚ እድገትን ከአረንጓዴ ኢኮኖሚ ጋር እንዴት ማስተሳሰር እንደሚቻል እንደሚያትት መሆኑ ተጠቁሟል።

ይህ 160 ፓውንድ የሚሸጠው መፅሀፍ ለዶ/ር አርከበ ዘጠነኛቸው ሲሆን ከዚህ በፊት ከፃፏቸው መፅሀፎች በተለይ "Made in Africa" የሚለው ከፍተኛ ተቀባይነትን አግኝቶ እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ።

ዶ/ር አርከበ የኢትዮጵያው ጠ/ሚር አብይ አህመድ የኢኮኖሚ አማካሪ ሆነው እስከ ቅርብ አመታት ያገለገሉ ሲሆን አሁን ላይ በ SOAS የለንደን ዩኒቨርስቲ አለም አቀፍ ፕሮፌሰር በመሆን እየሰሩ መሆኑን የደረሰን መረጃ ያሳያል።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

15 Oct, 14:25


💠ከዜናዎቻችን| ኤርትራ በሶማልያ ጦሯን ለማስፈር በድብቅ ስምምነት ላይ መድረሷ ተሰማ

(መሠረት ሚድያ)- ይህ የተሰማው የኤርትራው መሪ ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ የግብፅ እና ሱማልያ መሪዎችን በሀገራቸው ጋብዘው ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ ባገኙበት ወቅት ነው።

ሶስቱ ሀገራት በጋራ ያወጡት መግለጫ ላይ ይህ የኤርትራ ጦርን በሶማልያ የማስፈር ጉዳይ ባይጠቀስም 12,000 የኤርትራ ጦር አባላትን ሶማልያ ላይ ለማስፈር ስምምነት ላይ መደረሱን የዲፕሎማቲክ ምንጮቻችን ነግረውናል።

በይፋ የተነገረው መግለጫ ላይ ሶስቱ ሀገራት የግዛታዊ ሉአላዊነታቸውን በጥብቅ እንደሚያስከብሩ እንዲሁም በሀገሮቻቸው ጣልቃ ገብነትን እንደማይታገሱ መግለፃቸው ተሰምቶ ነበር።

ከዚህም በተጨማሪ ሀገራቱ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቻቸው የሚመራ የፖለቲካ ምክክር ኮሚቴ አቋቁመው በየግዜው እየተገናኙ ለመምከር ቀጠሮ ይዘዋል።

የቀጠናው ተንታኞች የእነዚህ ሶስት ሀገራት ምክክር ኢትዮጵያን ከሁሉም አቅጣጫ በመክበብ ከማስጨነቅ የመነጨ እንደሆነ በመግለፅ አካሄዱ አደገኛ እና ቀጠናውን ወደ ግጭት አውድማ ሊቀይር የሚችል እንደሆነ እያሳሰቡ ይገኛሉ።

ይሁንና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቢሮ ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ኢትዮጵያ ከኤርትራ ጋር ያላት ግንኙነት ሰላማዊ መሆኑን ጠቅሰው "በነበረት ቀጥሎ ይገኛል" ብለዋል።

ቃል አቀባዩ ሁለቱ ሀገራት አሁን ላይ መልካም ጉርብትና እና ወዳጅነት አላቸው ቢሉም ግንኙነታቸው በቅርብ ወራት ውጥረት የተሞላበት እንደሆነ የተለያዩ ክስተቶች እያሳዩ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አስመራ ሲያደርገው የነበረው በረራ ከወር በፊት የተቋረጠ ሲሆን አሁን ደግሞ የስልክ ግንኙነት እንዲቋረጥ እንደተደረገ ተሰምቷል። በድንበር የማይገናኙት ግብፅ፣ ሱማልያ እና ኤርትራ አስመራ ላይ መጣመራቸውን የኢትዮጵያ መንግስት ከማጣጣል ይልቅ በትኩሩት ሊመለከተው እንደሚገባ ተንታኞች እየገለፁ ይገኛሉ።

(#ከዜናዎቻችን በሳምንቱ በቪድዮ ዩትዩብ ላይ ያቀረብናቸውን የተመረጡ መረጃዎች ቆየት ብለን በድጋሜ በፅሁፍ የምናቀርብበት አምድ ነው)

መረጃን ከመሠረት!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

14 Oct, 15:54


💠"በፈረሱ አካባቢዎች ላይ እየገነባችሁ ያላችሁ ባለሀብቶች የተፈናቀለ ወገናችሁ አንድ ቀን ተመልሶ እንደሚመጣ አድርጋችሁ ማሰብም መሥራትም እንዳለባችሁ እንድታውቁት ለማሳሰብ እንወዳለን"- የፖለቲካ ፓርቲዎች

(መሠረት ሚድያ)- መኢአድ፣ ኢሕአፓ፣ ዐማራ ግዮናዊ ንቅናቄና እናት ፓርቲ "አሻራ የሚቀመጠው ታሪክን በመደምሰስና በሕዝብ ሰቆቃ ላይ አይደለም" በሚል ባወጡት የጋራ መግለጫ በኮሪደር ልማት ዙርያ ተቃውሞ እና ትችታቸውን አጋርተዋል።

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአዲስ አበባ ከተማ በመጀመሪያ የወንዝ ዳር ልማትና የጫካ ፕሮጀክት በሚል ተጀምሮ አኹን ላይ የኮሪደር ልማት በሚል መጠኑንና አድማሱን አስፍቶ ሙሉ ከተማ ወደማፍረስ የተሸጋገረው ሥራ አሻራ በማሳረፍ ሰበብ የመቶ ሺህዎችን ሕይወት እያመሰቃቀለ ነው ያሉት ፓርቲዎቹ በድንገት ቤታቸው የፈረሰባቸውና የይፈርሳል መርዶው ሲነገር ለጠና ሕመም የተዳረጉ፣ ከለመዱት ማኅበራዊ መሠረት የተናጠቡ፣ ሥራቸው ሙሉ ለሙሉ የተቋረጠና ለከፋ ችግር የተዳረጉ፣ ቍጥሩ በውል ያልታወቀ በድንጋጤም የሞቱ እንዳሉ ለመረዳት ችለናል ብለዋል፡፡

"ከዋና ባለቤቶች/ባለይዞታዎች ባልትናነሰ ተከራዮች ከፍ ላለ ስቃይ እንደተዳረጉ፣ አካል ጉዳተኞችና አቅመ ደካሞች የከፋ ችግር ላይ መውደቃቸውን ታዝበናል፡፡ ይዋል ይደር እንጂ ይህ የሕይወት መመሰቃቀል የማይነካው የከተማዋ ነዋሪ እንደማይኖር ለመገመት ነቢይ መሆን አይጠይቅም" ያሉት ፓርቲዎቹ የማፍረሻ ምክንያት እየፈለጉ የከተማዋን ነዋሪ በማፈናቀልና በአንድ ጀምበር ኑሮውን ወደ ሲዖልነት መለወጥ ፍጹም ተቀባይነት የሌለው አለፍ ሲልም ሀገር የምትተዳደርበትን ህግ በመሠረታዊነት የጣሰና ይጠብቀው ዘንድ ሓላፊነቱን በተቀበለ መንግሥት እየተፈጸመ የሚገኝ ከፍተኛ ወንጀል ነው ብለዋል።

ፓርቲዎቹ አክለውም መንግሥት በሕገ መንግሥቱ የተደነገገውን የዜጎች መብት እንዲያከብርና ማኅበረሰቡን መሠረታዊ በሆነ መልኩ ከሚያናጋ በልማት ሽፋን የሚተገበር ደባ እንዲያቆም፤ የፈረሳው ሰለባ የሆነው የአዲስ አበባ ነዋሪ ባገኘው አጋጣሚ ኹሉ ድርጊቱን በሰላማዊ መንገድ በመቃወም ሕገ መንግሥታዊ መብቱን እንዲያስከብር፤ ከቦታቸው የተፈናቀሉ ዜጎች የነበሩበትን ቦታ ካርታና መሰል የነዋሪነት/ባለ ይዞታነት/ ማስረጃዎች በጥንቃቄ እንዲያስቀምጡ እንዲሁም አዲስ በፈረሱ አካባቢዎች ላይ እየገነባችሁ ያላችሁ ባለሀብቶች የተፈናቀለ ወገናችሁ አንድ ቀን ተመልሶ እንደሚመጣ አድርጋችሁ ማሰብም መሥራትም እንዳለባችሁ እንድታውቁት ለማሳሰብ እንወዳለን ብለዋል።

መሠረት ሚድያ!

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

14 Oct, 12:48


💠አዲሱ ካሳሁን በአዲስ አበባ ከተማ ከኡራኤል ቤተክርስቲያን ወደ አትላስ ሆቴል በሚወስደው መንገድ አካባቢ በሚገኘው 'በፀጋህ ሆስፒታል' ፊት ለፊት ባለ አንድ ግቢ ነዋሪ ነበር።

አዲሱ ነጠላ ከሚሸጥበት ኡራኤል ቤተከርስቲያን አካባቢ ስራ እንዳይሰራ ሶስት ግዜ በደንብ አስከባሪዎች ተባሮ እና ንብረቱም ተወስዶበት እንደነበር ባለቤቱ እንዲሁም ጓደኞቹ ይናገራሉ።

ከዚህም በተጨማሪ ከአምስት ቀን በፊት ምሽት ወደ ቤቱ ሲገባ ተከራይቶ የሚኖርበት ቤት በነጋታው ጠዋት እንደሚፈርስ ሲነገረው ተስፋ በመቁረጥ ስሜት እዛው ግቢ ውስጥ ራሱን እንዳጠፋ ባለቤቱ በእንባ እየታጠበች ነግራኛለች።

"የዛን እለት ብዙ ሲጨናነቅ ነበር፣ ቤት ሲያጠያይቅ 13 ሺህ እና 15 ሺህ ሲሉት ነበር፣ በዛ ላይ ቤተሰብ ያለው አናከራይም እያሉት። ሊነጋጋ ሲል ራሱን አጥፍቶ አግኝተነዋል፣ አሁን የት እንደምሄድ እና ምን እንደማረግ እንዳለብኝ አላውቅም" በማለት ነግራኛለች።

የሁለት የልጅ አባት የሆነው አዲሱ (አንደኛው ገና 5 ወሩ ነው) ባሳለፍነው አርብ እለት ስድስት ሰአት ላይ በኡራኤል ቤተክርስቲያን ቀብሩ ተፈፅሟል።

ባለቤቱን እማኑሽ ፈንታን በቻልነው አቅማችን እንደግፍ፣ ለማስጀመርያ እንዲሆን እኔም በግሌ የአቅሜን ድጋፍ አደርጋለሁ።

እማኑሽ ፈንታ
ስልክ: +251920660393

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000334824652


@EliasMeserett

ELIAS MESERET

14 Oct, 12:36


#ውጤት 'Remzi Mohammed' በዚህ ሳምንት ለማስታወሻ የሚሆን የመሠረት ሚድያ ሎጎ የታተመበት ኩባያ (mug) የሚበረከትለት ሆኖ ተመርጧል

ጥያቄው "መሠረት ሚድያ መረጃ ማቅረብ ከጀመረበት ሐምሌ 25/2016 ጀምሮ ምን ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት፣ ምን መስተካከል እንዳለበት በአጭሩ ያስቀምጡልን" የሚል ነበር።

በሚቀጥለው ቅዳሜ ሌላ ጥያቄ እና ሽልማት ይዘን እንመለሳለን።

መረጃን ከመሠረት!


@EliasMeserett

ELIAS MESERET

14 Oct, 09:49


💠ጌታቸው ረዳን በሚተኳቸው ተሿሚ ዙሪያ ከፌደራል መንግስቱ ጋረ እየተነጋገርን ነው”  ፈትለወርቅ ገ/እግዚአብሔር

በደብረጺዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ህወሓት የጽህፈት ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገብረግዚአብሔር ፓርቲያቸው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳን ማንሳቱን አስታውሰው እሳቸው በሚተካ ተሿሚ ዙሪያ ከፌደራል መንግስቱ እና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተነጋገር ነው ሲሉ አስታውቀዋል።

“ሁለታችንም ያመንበት ነው የሚሆነው፣ አንዳችን ካላመንበት አይሆንም” ብለዋል፤ ማን ይተካ በሚለው ዙሪያ መነጋገር አለብን ሲሉ ጠቁመዋል።

ህወሓት በግዜያዊ አስተዳደሩ ያለው ኮታ በመጠቀም የካቢኔ ተሿሚዎቹ ላይ ምደባ በማድረጉ ጊዜያዊ አስተዳደሩን ሊያፈርስ ነው በሚል የሚሰራጨው መረጃ ፍጹም ሀሰት ነው ማለታቸውንም ፓርቲው ባጋራው መረጃ ላይ አመላክቷል፤ የጊዜያዊ አስተዳደሩ አጠቃላይ 27 ወንበሮች አሉት ሲሉ ገልጸው ህወሓትን የሚመለከተው 14ቱ ብቻ ናቸው ሲሉ ጠቁመዋል።

የጊዜያዊ አስተዳደሩን የመሰረቱት ከትግራይ ሰራዊት፣ ከምሁራን እና ከተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ የተመደቡ 13 የካቢኔው ተሿሚዎች አሁንም በቦታቸው አሉ ሲሉ ያብራሩት ዋና ጻሃፊዋ የህወሓትም ቢሆን በጊዜያዊ አስተዳደሩ ምስረታ ወቅት የተመደቡ 6 ተሿሚዎች ቀጥለዋል ሲሉ አስታውቀዋል።

ይህም በጊዜያዊ አስተዳደሩ ያሉ እና የቀጠሉ የካቤኒ አባላትን 19 ያደርሰዋል ሲሉ ጠቁመው ከዚህ ውጭ ደግሞ 3 የሚሆኑ የካቢኔ አባላት ቀደም ብለው ቦታውን በመልቀቃቸው በነሱ ምትክ ነው ሰው የተመደበው ብለዋል።

via አዲስ ማለዳ

@EliasMeserett

ELIAS MESERET

14 Oct, 04:29


💠የዘንድሮው የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ስነ ስርአት ሜሪላንድ በሚገኘውና ኢትዮጵያዊያን በባለቤትነት በሚያስተዳድሩት ሜትሮ ፖይንትስ ሆቴል ዛሬ፣ እሁድ ኦክቶበር 13/2024 ምሽት በደማቅ ዝግጅት እየተካሄደ ነው፣ እኛም በስፍራው ተገኝተናል

በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ የተመሰረተውና ለትርፍ ያልተቋቋመው ኖቫ ኮኔክሽን ያዘጋጀው የ2024 አፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ የዘንድሮ የክብር የሽልማት ሥነ ስርዓት እየተከናወነ ነው።

ይህ አመታዊ የእውቅና ሽልማት ስነ ስርአት በአሜሪካና በአፍሪካ በሙያቸው ታላቅ ሥራ የሰሩ ግለሰቦችን ለማክበር የተዘጋጀ ነው።

በየአመቱ ከስፖርት፣ ከስነ ጥበብና ከስራ ፈጠራ ዘርፎች ለማህበረሰቦቻቸው ላበረከቱት አስተዋፅኦና ለለውጥ ላደረጉት የላቀ ተሳትፎ ከየዘርፉ ተመርጠው የሚሸለሙበት መድረክ ነው።

አፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ እስካሁን ለአራት ጊዜያት ተካሂዷል። ዘንድሮም በተለያዩ ዘርፎች ለአምስት ተፅዕኖ ፈጣሪ ኢትዮጵያዊያንን የክብር እውቅና እየሰጠ ይገኛል።

የዘንድሮ ተሸላሚዎች አርቲስት አስቴር አወቀ፣ ጋዜጠኛ መአዛ ብሩ፣ አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ፣ ወ/ሮ ሬቤካ ሀይሌ እና አትሌት ትግስት አሰፋ ናቸው።

ለግብዣው ዶ/ር ጋሻው አበዛን አመሰግናለሁ።

@EliasMeserett