EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት) @effrefe Channel on Telegram

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

@effrefe


This is official telegram chanel of Ethiopian football federation refereeing department.

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት) (Amharic)

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት (EFF Refereeing Departement) ከፋና ብቃት ጋር በትምህርትም በጣም በክለቦች እና በእግር ኳስ ሰልፍ ለማስራራት ከጊዜ ጋር የሚሆኑ ዳኞችን ከታብዩ ደንበኞች ጋር በመዘገብና በመዝገበ ዝግጅት እንዲሰጥ እና መረጃዎችን እንሰጥቷል። በአጭር ፈቃድ የሚታይ ሊሆናቸው ከፈቃዱ በፊት ያልፋል፡፡ ይህ ከታብዩ ለማስራራት የዳኞች ዲፖርትመንት በተናገርኳን መሪ ህዳሳ ጸሃፊ የመስረት ጉዳይ ከሆነ፣ በትክክለኛ የስራ ችግር የሚሰጥ ጥያቄዎችን አገናኝ የሚሆን መረጃዎች ያለው የስማቸው እና ያልሆኑ፣ ለመሆኑ ያበረከተ ጥያቄዎች እና መረጃዎች በመሞከረነት ከተሞላቸው ሊኖሩ ይችላሉ። በዚህ ቦታ በዚህበለይ መረጃዎች እና ጸሃፊ ይሁኑ።

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

05 Feb, 07:21


ለሊግ አንድ የጨዋታ አመራሮች
የአካል ብቃት ፈተና ቀን ስለማሳወቅ

⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️

የሊግ አንድ ውድድር ሁለተኛው ዙር 9/06/2017 ዓ/ም ጀምሮ እንደሚጀምር መገለፁ ይታወቃል። በመሆኑም ማክሰኞ በ04/06/2017 ዓ/ም ከጠዋቱ በ12፡00 ጀምሮ በአበበ ቢቂላ ስታድየም በመገኘት ሁለተኛ ዙር የአካልብቃት ፈተና እንድትወስዱ ስንል ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።


ማሳሰቢያ
#በመጀመሪያው ዙር ጥሪ ላይ ስማችሁ ከተዘረዘረ የጨዋታ አመራሮች ውጭ ለፈተናው የሚመጡትን የማናስተናግድ መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን።
#በመጀመሪያው ዙር ፈተና ያልመጣችሁ የጤና ምርመራ ውጤት ማቅረብ ይጠበቅባችኃል።

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
“አለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ያላቸው የዳኝነት ባለሙያዎች ለመፍጠር እንሰራለን”

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

29 Jan, 12:08


ለወንዶች ከፍተኛ ሊግ የጨዋታ አመራሮች
የፈተና ቀን መቀየሩን ስለማሳወቅ

⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️

ሁለተኛው ዙር የከፍተኛ ሊግ ውድድር የሚጀምርበት ቀን ተራዝሞ 08/06/2017 ዓ/ም እንደሚጀምር ተገልፆልናል። በመሆኑም ማክሰኞ በ27/05/2017 ዓ/ም በማለት ያስተላለፍነው የፈተና ጥሪ ወደ 03/06/2017 ዓ/ም ከጠዋቱ በ12፡00 ጀምሮ የተቀየረ መሆኑን እየገለፅን በተጠቀሰው ቀን በአበበ ቢቂላ ስታድየም በመገኘት ሁለተኛ ዙር የአካልብቃት ፈተና እንድትወስዱ ስንል ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።


ማሳሰቢያ
#በመጀመሪያው ዙር ጥሪ ላይ ስማችሁ ከተዘረዘረ የጨዋታ አመራሮች ውጭ ለፈተናው የሚመጡትን የማናስተናግድ መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን።
#በመጀመሪያው ዙር ፈተና ያልመጣችሁ የጤና ምርመራ ውጤት ማቅረብ ይጠበቅባችኃል።

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
“አለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ያላቸው የዳኝነት ባለሙያዎች ለመፍጠር እንሰራለን”

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

27 Jan, 13:10


ለወንዶች ከፍተኛ ሊግ የጨዋታ አመራሮች
⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️

የከፍተኛ ሊግ ውድድር ሁለተኛው ዙር 30/05/2017 ዓ/ም ጀምሮ እንደሚጀምር መገለፁ ይታወቃል። በመሆኑም ማክሰኞ በ27/05/2017 ዓ/ም ከጠዋቱ በ12፡00 ጀምሮ በአበበ ቢቂላ ስታድየም በመገኘት ሁለተኛ ዙር የአካልብቃት ፈተና እንድትወስዱ ስንል ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።


ማሳሰቢያ
#በመጀመሪያው ዙር ጥሪ ላይ ስማችሁ ከተዘረዘረ የጨዋታ አመራሮች ውጭ ለፈተናው የሚመጡትን የማናስተናግድ መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን።
#በመጀመሪያው ዙር ፈተና ያልመጣችሁ የጤና ምርመራ ውጤት ማቅረብ ይጠበቅባችኃል።

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
“አለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ያላቸው የዳኝነት ባለሙያዎች ለመፍጠር እንሰራለን”

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

19 Jan, 07:51


ለመላው የክርስትና ዕምነት ተከታዮች እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

መልካም በዓል !

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

17 Jan, 11:33


ማስታወቂያ
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆

ከላይ ስማችሁ የተዘረዘረው ከዚህ በፊት ለኢንስትራክተርነት ስልጠና ያወጣነውን ማስታወቂያ ተከትሎ  ለምዝገባ ማስረጃችሁን ያስገባችሁ እና የተመዘገባችሁ መሆኑ ይታወቃል ስለሆነም የመግቢያ ፈተና በመፈተን ፈተናውን ያለፉትን ብቻ በመምረጥ ስልጠናውን ለመስጠት በዝግጅት ላይ እንገኛለን በዚህ መሰረት ከላይ የተጠቀሳችሁ በሙሉ በቅርቡ ለፈተና የምንጠራችሁ ስለሆነ እየተዘጋጃችሁ እንድትጠብቁ እናሳስባለን። ከዚህ በፊት በነበረው የምዝገባ ሂደት ያልተመዘገባችሁ በአዲስ ለመመዝገብ ከዚህ በታች ያለውን መስፈርት የምታሟሉ ብቻ ማስረጃችሁን በመያዝ በፌዴሬሽኑ ዳኞች ዳይሬክቶሬት በማምጣት እስከ 16/05/2017 ዓ/ም ድረስ ብቻ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እያሳውቅን መስፈርቱን የምታሟሉትን ብቻ የመግቢያ ፈተናውን የምንሰጥ ይሆናል። መስፈርቶቹ የሚከተሉት ናቸው።
1.  በአሁኑ ሰዓት ከዳኝነት ስራ ራሱን ያገለለ
3.  የእንግሊዝኛ ቋንቋ ችሎታ ያለው /ያላት
4.  የኮምፒውተር አጠቃቀም ክህሎት ያለው /ያላት
5.  በዳኝነት ሙያ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ላይ ቢያነስ ለ5 ዓመት ያገለገለ/ች

#ማሳሰቢያ
ሙያውን የሚመጥን ጠንካራ የመግቢያ ፈተና የሚሰጥ ስለሆነ ለኢንስትራክተርነት የሚያበቃ አቅም ልምድ እና ችሎታ የሌላችሁ ለፈተና የሚመጣ ሁሉ ወጭውን በራሱ ሸፍኖ መምጣት ስላለበት ለአላስፈላጊ ወጭ እንዳትዳረጉ ስንል በትህትና እናሳስባለን።

ይህ ማስታወቂያ በተለያዬ ጊዜ FUTRO ኮርስ የወሰዳችሁትን አይመለከትም

ማስታወቂያው የአካል ብቃት ኢንስትራክተሮችን አይመለከትም


"ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪ የሆኑ የዳኝነት ባለሙያዎችን ለመፍጠር እንሰራለን"

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

15 Jan, 15:37


የመጪው ዘመን የአፍሪካ እግር ኳስ የጨዋታ አመራሮች ...

የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ለመጀመርያ ጊዜ ያዘጋጀው የታዳጊ ሴቶች የእግር ኳስ ውድድር (GIFT) በታንዛንያ እየተከናወነ ይገኛል። ውድድሩ የታዳጊ እንስት ተጫዋቾችን ችሎታ ከማሳየት በተጨማሪ የጨዋታ አመራሮች እድገት ማሳያ ውድድር ሆኗል።

አማካይ እድሜያቸው 26.6 የሆኑ 17 ወጣት ሴት የጨዋታ አመራሮች ሀገራችን ኢትዮጵያን ጨምሮ ከዘጠኝ ሀገራት ለዚህ ውድድር ተመርጠው ጨዋታዎችን እየመሩ የሚገኙ ሲሆን በቀጣይ ዓመታት የአህጉሪቱን ታላላቅ የጨዋታ አመራሮች ለማግኘት መንገድ የሚጠርግ እንደሆነ ታምኖበታል።

የካፍ ቴክኒካል ልማት ዳይሬክተር ራውል ቺፔንዳ በዚህ ውድድር ላይ ወጣት የጨዋታ አመራሮች እያሳዩ ባለው ብቃት ደስተኛ መሆናቸውን ይናገራሉ። " በዚህ ውድድር ላይ እያሳዩ ባለው ብቃት እና ፕሮፌሽናሊዝም ኩራት ተሰምቶኛል። እያሳዩ ያለው ብስለት እና ክህሎትም በጨዋታ አመራሮች የእድገት መርሐ ግብር ላይ እያስመዘገብን ላለው ጥሩ እምርታ ማሳያ ናቸው። ውድድሩ የሚያሳየን የጨዋታ አመራሮቻችንን ችሎታ ብቻ ሳይሆን የወደፊቱን የጨዋታ አመራርነት ደረጃ የሚበይን ነው። " ብለዋል።

ባሳለፍነው ሳምንት የተካሄደው የታንዛንያው ቲዲኤስ ገርልስ እና የዩጋንዳው ቦኒ ኮንሲሊ ገርልስ ጨዋታ ላይ ኢትዮጵያዊቷ ዋና ዳኛ ዮርዳኖስ ሙሉጌታ ያሳየችው የጨዋታ አመራርነት ብቃት በካፍ "አስደናቂ" ተብሎለታል። ለግሏ የመጀመርያ ኢንተርናሽናል ጨዋታዋ የሆነው ዮርዳኖስ ያሳየችው በሳል ብቃት ቀጣይ የዳኝነት ጉዞዋ ብሩህ ስለመሆኑ አመላካች ነው ሲልም ካፍ በድረገፁ ምስክርነቱን ሰጥቷል።

የ2016 የኢትዮጵያ ሴቶች እግር ኳስ ሊግ ኮከብ ዳኛ በመሆን የተመረጠችው ወጣቷ ዳኛ በካፍ የጨዋታ አመራሮች ዓይን ውስጥ መግባት መቻሏ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በጨዋታ አመራርነት ዘርፍ በአፍሪካ እግር ኳስ ያለውን ቦታ ከፍ ለማድረግ ለሚያደርገው ጥረት አንድ እርምጃ መሆኑን የብሔራዊ ዳኞች ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት የቀድሞው ኢንተርናሽናል ረዳት ዳኛ ሸዋንግዛው ተባባል እምነታቸውን ገልፀዋል።

በተከታታይ ዓመታት ከፊፋ ጋር በመተባበር ለወጣት የጨዋታ አመራሮች ስልጠና እየተሰጠ ከመሆኑ ባሻገር ከዳኝነት ሙያ መመርያ እስከ 10 ዓመት የዳኝነት ሙያ ስትራቴጂክ እቅድ ማዘጋጀት ድረስ ያሉ ስራዎች በዋናነት ወጣት የጨዋታ አመራሮችን ማፍራት ላይ ያተኮረ መሆኑን የኢ/እ/ፌ የዳኞች ልማት እና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ተጠባባቂ ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ ምስጋናው ገልፀዋል።

ካፍ ለወጣት ዳኞች የኢንተርናሽናል የጨዋታ አመራርነት እድል የመስጠት መርሐ ግብርን በአግባቡ በመጠቀም በዚህ የታዳጊ ሴቶች ውድድር ላይ ፌዴራል ዋና ዳኛ ዮርዳኖስ ሙሉጌታ እና ፌዴራል ረዳት ዳኛ ስንታየሁ ደፈርሻ ከመመደባቸው በተጨማሪ ባለፈው የውድድር ዓመት በወንዶች ከ15 ዓመት ውድድር ላይም ፌዴራል ዋና ዳኛ ሄኖክ አበበ እና ፌዴራል ረዳት ዳኛ ወጋየሁ አየለ ተመሳሳይ እድል አግኝተው የዓለም አቀፍ ልምድ ያገኙ የጨዋታ አመራሮች ናቸው።

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

09 Jan, 09:24


ለወንዶች ፕሪሚየር ሊግ የጨዋታ አመራሮች


በአንደኛው ዙር መጠናቀቅን ተከትሎ በሚኖረን የአካል ብቃት ፈተና ጊዜ የግማሽ የውድድር አመቱን አፈፃፀም ከመገምገም በተጨማሪ የጨዋታ ሕግ የፅሑፍ ፈተና እና የተንቀሳቃሽ ምስል ትንተና ፈተና (video analisis test) የምንሰጥ እና ውጤቱንም ለማንኛውም አይነት የምልመላ እና መረጣ ተግባር የምንጠቀምበት መሆኑን እያሳወቅን የጨዋታ አመራሮቻችን ወቅቱ የሚጠይቀውን የእግር ኳስ ዳኝነት ልህቀት እንዲኖራችሁ ራሳችሁ ላይ ሁሌም እንድትሰሩ እያሳሰብን እንደ ዳኞች ኮሚቴ እና ዲፓርትመንት የሚጠበቅብንን ድጋፍ ለማድረግ በማንኛውም ጊዜ እና ሁኔታ ዝግጁ መሆናችንን እንገልፃለን እናንተም ሁልጊዜም ሙያው ለሚጠይቀው ዝግጁነት እንድትሰሩ በጥብቅ እናሳስባለን።

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
"ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ያላቸው የዳኝነት ባለሙያዎች ለመፍጠር እንሰራለን"

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

03 Jan, 09:15


የ2024 የአፍሪካ ሀገራት ዋንጫ (ቻን) ከፌብሩዋሪ 1-28/2025 በታንዛንያ፣ ኬንያ እና ዩጋንዳ የጋራ አዘጋጅነት ይከናወናል። በውድድሩ ላይ ለጨዋታ አመራርነት ከተመረጡት መካከልም ኢትዮጵያዊው ኢንተርናሽናል ረዳት ዳኛ ፋሲካ የኋላሸት አንዱ ሆኗል።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ኢንተርናሽናል ረዳት ዳኛ ፋሲካ የኋላሸት ለቻን ውድድር በመመረጡ ደስታውን እየገለፀ መልካም የውድድር ጊዜን ይመኛል።

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

18 Dec, 10:37


አካል ብቃት ፈተና ጥሪን ይመለከታል
ለሴት የጨዋታ አመራሮች ብቻ
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆

ለሴቶች ሊግ የጨዋታ አመራሮች የመጀመሪያውን ዙር ፈተና የወደቃችሁ እና በተለያዬ ምክንያት ለፈተና ያልመጣችሁ የጨዋታ አመራሮች በድጋሚ የአካል ብቃት ምዘና የሚሰጠው ሐሙስ ታህሳስ 17 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ በአበበ ቢቂላ ስታድየም ሲሆን ባለፈው ለፈተና ያልመጣችሁ የጤና ምርመራ ዉጤት ይዛችሁ በምዘናው ቀን እና ቦታ እንድትቀርቡ እናስታውቃለን።

#ማሳሰቢያ፡-
ባለፈው ተፈትናችሁ ማለፍ ያልቻላችሁ የጤና ምርመራ ውጤት ማምጣት አትገደዱም በተለያዬ ምክንያት ለፈተና ያልመጣችሁ ግን የጤና ምርመራ ውጤት ማምጣት ግዴታ ነው

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
"አለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ያላቸው የጨዋታ እና የውድድር አመራሮች ለመፍጠር እንሰራለን"

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

16 Dec, 10:31


የሐዘን መግለጫ !

በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሊግ አንድ ውድድሮች ላይ በጨዋታ አመራርነት በማገልገል ላይ የነበረው ዘሪሁን በቀለ ዳካ በድንገተኛ አደጋ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

በረዳት ዳኝነት እያገለገለ የነበረው ዘሪሁን በቀለ በሊግ አንድ ውድድር ሮቤ ላይ ጨዋታ ሲመራ ከቆየ በኋላ ትላንት 06/04/2017 ከሮቤ በመነሳት ወደ ትውልድ አካባቢው ወንዶ ገነት በመመለስ ላይ ሳለ ተሳፍሮበት የነበረበት የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ዶዶላ አካባቢ በደረሰት የትራፊክ አደጋ ህይወቱ አልፏል። ሥርዓተ ቀብሩም በትውልድ ቦታው ወንዶ ገነት ወሻ ረቡዕ ማለትም 09/04/2017 ከቀኑ በ6:00 የሚፈፀም ይሆናል። ፌደራል ረዳት ዳኛ ዘሪሁን በቀለ ባለትዳር እና የሶስት ልጆች አባት ነበር።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዳኞች ኮሚቴ እና ዳኞች ዲፓርትመንት በጨዋታ አመራር ዘሪሁን በቀለ ድንገተኛ እና አስደንጋጭ ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ለቤተሰቡ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ፣ ለሙያ አጋሮቹ እና የስፖርት ቤተሰቡ መፅናናትን ይመኛል።

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

11 Dec, 09:52


የ2025 የፊፋ ኢንተርናሽናል የጨዋታ አመራሮች ታወቁ

በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ጨዋታዎችን የሚመሩ ኢትዮጵያውያን የጨዋታ አመራሮች በወንዶች ሰባት ዋና እና ሰባት ረዳት እንዲሁም በሴቶች አራት ዋና እና አራት ረዳት ዳኞች ተመርጠው ለፊፋ ዳኞች ኮሚቴ ተልከው የነበረ ሲሆን ፊፋ ለፌዴሬሽናችን ባሳወቀው መሰረት ከአንድ ወንድ ረዳት ዳኛ (ሲራጅ ኑርበገን) ውጭ ሌሎችን አጩ ዳኞች ለኢንተርናሽናል ዳኝነት ተቀብሏቸዋል።

ፊፋ ያፀደቃቸው ኢትዮጵያዊያን የ2025 ኢንተርናሽናል የጨዋታ አመራሮች ዝርዝር በምስሉ ላይ ተያይዟል።

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

11 Dec, 08:44


Channel photo updated

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

08 Dec, 13:23


Channel photo updated

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

02 Dec, 17:03


ለአዲስ የፌደራል የጨዋታ አመራሮች
⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️

በተለያዬ ጊዜ የፌደራል ዳኝነት ስልጠና ወስዳችሁ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ስር የሚካሄዱ ውድድሮችን መምራት ያልጀመራችሁ በመላ ሀገሪቱ የምትገኙ አዲስ የፌደራል ደረጃ የጨዋታ አመራሮች የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ብቻ:-
የፌደራል ዳኝነት ስልጠና ወስዳችሁ ሰርተፍኬት ያላችሁ
ዕድሜ ከ35 ዓመት በታች የሆናችሁ ብቻ
በየአካባቢያችሁ ጨዋታ እየመራችሁ ያላችሁ
የተስተካከለ የሰውነት አቋም ያላችሁ
የብሔራዊ ዳኞች ኮሚቴ መልምሎ ወደ ስራ ማስገባት ይፈልጋል በመሆኑም የአካል ብቃት ፈተና የሚሰጠው እና ምልመላ የሚደረገው ሐሙስ በ03/04/2017 ዓ/ም በመሆኑ ከጠዋቱ በ12፡00 ጀምሮ በአበበ ቢቂላ ስታድየም የጤና የምርመራ ውጤት እና የ8ኛ ክፍል ካርድ ይዛችሁ በመምጣት የጤና ምርመራ ውጤቱን ለጤና ባለሙያዎች ማረጋገጥ እና በዚያው ቀን 2፡00 ጀምሮ የአካል ብቃት ፈተና በመውሰድ በዚሁ ቀን እንደ አስፈላጊነቱ አካል ብቃት ፈተናውን ያለፋችሁ ብቻ ተግባራዊ ዳኝነታችሁን ለመመዘን እዛው አበበ ቢቂላ ከተጨዋች ጋር በባለሙያዎች ልትገመገሙ ስለሚችል ዝግጅት አድርጋችሁ እንድትመጡ ከወዲሁ እናሳውቃለን።

ማሳሰቢያ
#ከዚህ በፊት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሚያወዳድራቸውን ውድድሮች ስትመሩ የነበረ የጨዋታ አመራሮችን የማናስተናግድ መሆኑን ለማሳሰብ እንወዳለን።
#ለምልመላ ስትመጡ ሙሉ ወጭአችሁን በራሳችሁ የምትሸፍኑ መሆኑን እናሳስባለን።
#ከላይ የተጠቀሰውን መስፈርት በሙሉ የማታሟሉትን የማናስተናግድ ስለሆነ ይህን አውቃችሁ ከአላስፈላጊ የገንዘብ ኪሳራ ራሳችሁን እንድትጠብቁ እናሳስባለን።

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
“አለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ያላቸው የዳኝነት ባለሙያዎች ለመፍጠር እንሰራለን”

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

20 Nov, 10:04


ለ20 ዓመት በታች የጨዋታ አመራሮች
⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️

ከላይ ስማችሁ በዝርዝሩ ውስጥ የተካተተ የጨዋታ አመራሮች የ2017 ዓ/ም የመጀመሪያው ዙር የአካል ብቃት ፈተና የሚሰጠው ማክሰኞ በ17/03/2017 ዓ/ም በመሆኑ ከጠዋቱ በ12፡00 ጀምሮ በአበበ ቢቂላ ስታድየም የጤና የምርመራ ውጤት ይዛችሁ በመምጣት ለባለሙያዎች ማረጋገጥ እና በዚያው ቀን 2፡00 ጀምሮ የአካል ብቃት ፈተና በመውሰድ በዚሁ ቀን ከቀኑ 6:00 ጀምሮ ወደፊት በምናሳዉቀው ቦታ ውይይት እና የውድድር ዝግጅት ገለፃ  ይሰጣል። ስለሆነም በተገለፀው አግባብ ራሳችሁን አዘጋጅታችሁ እንድትገኙ እናሳውቃለን።

ማሳሰቢያ
ስማችሁ በዝርዝሩ ከተጠቀሰው ውጭ የምትመጡ የጨዋታ አመራሮችን የማናስተናግድ መሆኑን ለማሳሰብ እንወዳለን።

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
“አለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ያላቸው የዳኝነት ባለሙያዎች ለመፍጠር እንሰራለን”

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

06 Nov, 13:42


ለሊግ አንድ የጨዋታ አመራሮች
⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️

ከላይ ስማችሁ በዝርዝሩ ውስጥ የተካተተ የጨዋታ አመራሮች የ2017 ዓ/ም የመጀመሪያው ዙር የአካል ብቃት ፈተና የሚሰጠው ሐሙስ በ05/03/2017 ዓ/ም በመሆኑ ከጠዋቱ በ12፡00 ጀምሮ በአበበ ቢቂላ ስታድየም የጤና የምርመራ ውጤት ይዛችሁ በመምጣት ለባለሙያዎች ማረጋገጥ እና በዚያው ቀን 2፡00 ጀምሮ የአካል ብቃት ፈተና በመውሰድ በዚሁ ቀን ከቀኑ 6:00 ጀምሮ ወደፊት በምናሳዉቀው ቦታ ውይይት እና የውድድር ዝግጅት ገለፃ  ይሰጣል። ስለሆነም በተገለፀው አግባብ ራሳችሁን አዘጋጅታችሁ እንድትገኙ እናሳውቃለን።

ማሳሰቢያ
ስማችሁ በዝርዝሩ ከተጠቀሰው ውጭ የምትመጡ የጨዋታ አመራሮችን የማናስተናግድ መሆኑን ለማሳሰብ እንወዳለን።

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
“አለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ያላቸው የዳኝነት ባለሙያዎች ለመፍጠር እንሰራለን”

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

28 Oct, 08:00


ለሴት የጨዋታ አመራሮች
⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️

የ2017 ዓ/ም የመጀመሪያው ዙር የአካል ብቃት ፈተና የሚሰጠው አርብ በ22/02/2017 ዓ/ም በመሆኑ ከጠዋቱ በ12፡00 ጀምሮ በአበበ ቢቂላ ስታድየም የጤና የምርመራ ውጤት ይዛችሁ በመምጣት ለባለሙያዎች ማረጋገጥ እና በዚያው ቀን 2፡00 ጀምሮ የአካል ብቃት ፈተና በመውሰድ በዚሁ ቀን ከቀኑ 6:00 ጀምሮ ወደፊት በምናሳዉቀው ቦታ ውይይት እና የውድድር ዝግጅት ገለፃ  ይሰጣል። ስለሆነም በተገለፀው አግባብ ራሳችሁን አዘጋጅታችሁ እንድትገኙ እናሳውቃለን።

ማሳሰቢያ
በየትኛውም አካባቢ የምትገኙ አዲስ ሴት ፌደራል የጨዋታ አመራሮች ፈተናውን መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን ወጫችሁን በግላችሁ የምትሸፍኑ መሆኑን ለማሳሰብ እንወዳለን።

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
“አለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ያላቸው የዳኝነት ባለሙያዎች ለመፍጠር እንሰራለን”

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

19 Oct, 10:30


ለከፍተኛ ሊግ የጨዋታ አመራሮች
የአካል ብቃት ፈተና ቀን መቀየሩን ስለማሳወቅ
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆

ቀደምሲል የአካል ብቃት ፈተና በ14/02/2017 ዓ/ም እንደሚሰጥ ማሳወቃችን ይታወቃል። ነገር ግን ቀኑን መቀየር ስላስፈለገ አርብ 15/02/2017 ዓ/ም መቀየሩን እያሳወቅን ሙሉ ፕሮግራሙ ከዚህ በፊት በተገለፀው አግባብ የሚካሄድ መሆኑን እንገልፃለን



ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ያላቸው የዳኝነት ባለሙያዎች ለመፍጠር እንሰራለን

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

18 Oct, 13:16


በጤና ምርመራ ውጤት ከዝርዝር ለተቀነሳችሁ ኮሚሽነሮች
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆

ለ2016 ዓ/ም ለውውድር የቅድመ ዝግጅት ስናደርግ በኮሚሽነሮች ዙሪያ ይስተዋሉ ከነበሩ ችግሮች በመነሳት የጤና ምርመራ የተደረገ እና በዚህም የጤና ምርመራውን ማለፍ ያልቻላችሁ ኮሚሽነሮች በውድድር አመቱ የኮሚሽነሮች ዝርዝር ላይ አለመካተታችሁ የሚታወስ ነው። በዚህ መሰረት በተለያዩ ጊዜያት ቅሬታ እያቀረባችሁ የቆያችሁ አና አሁንም ቅሬታችሁን የምታቀርብ መኖራችሁ ይታወቃል። ይሁን እንጅ የብሔራዊ ዳኞች ኮሚቴ በቀረቡት ቅሬታዎች ላይ በሰፊው የተወያየባቸው ሲሆን መሰል ምዘናዎችን በየ ዓመቱ ለማከናዎን ከተለያዩ ጉዳዮች አንጻር አዋጭ አለመሆኑን ስለታመነበት የምዘና ፕሮግራሙን በየ ሁለት ዓመቱ የምናካሂድ መሆኑ ተወስኗል። ስለሆነም በዚህ ዓመት ለ2016 ዓ/ም የውድድር ዓመት ተደርጎ የነበረው የምዘና ውጤትን መሰረት ተደርጎ የሚሰራ ሲሆን ለ2018 ዓ/ም የውድድር ዓመት ዝግጅት ሲደረግ ከጤና ምርመራው በተጨማሪ የጨዋታ ሕግ ፈተናን ጨምሮ ሌሎች አስፈላጊ የምዘና አይነቶችን በመጨመር ምዘናው በድጋሚ ለሁሉም ኮሚሽነሮች ተጠናክሮ የሚሰጥ መሆኑን እና በዚህ መንገድ የሚሰራ መሆኑን እናሳውቃለን።


“አለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ያላቸው የዳኝነት ባለሙያዎች ለመፍጠር እንሰራለን”

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

18 Oct, 07:33


ለወንዶች ከፍተኛ ሊግ የጨዋታ አመራሮች
⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️⚽️

የከፍተኛ ሊግ ውድድር ከጥቅምት 16/2017 ዓ/ም ጀምሮ እንደሚጀምር መገለፁ ይታወቃል። በመሆኑም ሀሙስ በ14/02/2017 ዓ/ም ከጠዋቱ በ12፡00 ጀምሮ በአበበ ቢቂላ ስታድየም የጤና የምርመራ ውጤት ይዛችሁ በመምጣት ለባለሙያዎች ማረጋገጥ እና በዚያው ቀን 2፡00 ጀምሮ የአካል ብቃት ፈተና በመውሰድ በዚሁ ቀን ከቀኑ 6:00 ጀምሮ ወደፊት በምናሳዉቀው ቦታ ውይይት እና የውድድር ዝግጅት ገለፃ  ይሰጣል። ስለሆነም በተገለፀው አግባብ ራሳችሁን አዘጋጅታችሁ እንድትገኙ እናሳውቃለን።

ማሳሰቢያ
ከላይ ስማችሁ ከተዘረዘረ የጨዋታ አመራሮች ውጭ ለፈተናው የሚመጡትን የማናስተናግድ መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን።

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
“አለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ያላቸው የዳኝነት ባለሙያዎች ለመፍጠር እንሰራለን”

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

14 Oct, 07:45


ለሁሉም የጨዋታ አመራሮች
ዝግጅት እንድታደርጉ ስለማሳሰብ
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆

የ2017 ዓ.ም የውድድር ዘመን ሊጎቻችን የሚጀምሩበት ቀናቶች ከዚህ በታች የምናሳውቅ መሆኑን እየገለጽን ሁሉም የጨዋታ አመራሮች ሁለንተናዊ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን፡፡
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ በ16/02/2017
የኢትዮጵያ ሴቶች ኘሪሚየር ሊግ በ24/02/2017
የኢትዮጵያ አንደኛ ሊግ በ30/02/2017
ከ20 ዓመት በታች ወንዶች ኘሪሚየር ሊግ በ10/3/2017
የኢትዮጵያ ሴቶች ከፍተኛ ሊግ በ14/3/2017 የሚጀምሩ መሆኑን እያሳወቅን የአካል ብቃት ፈተና ኘሮግራሞችን በየጊዜው ስለምናሳውቅ እየተዘጋጃችሁ እንድትጠብቁን እናሳውቃለን፡፡

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
“አለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ያላቸው የዳኝነት ባለሙያዎች ለመፍጠር እንጥራለን”

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

04 Oct, 16:17


ከላይ ስማችሁ የተዘረዘረ የጨዋታ አመራሮች ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ በመክፈት መጠይቁን እስከ ቅዳሜ 25/01/2017 ዓ/ም እስከ ሌሊቱ 6:00 ድረስ ብቻ እንድትሞሉ እናሳስባለን።

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://forms.gle/WYH2C8c7BudZghui9

#ማሳሰቢያ
ስማችሁ በዝርዝሩ ውስጥ ያልተካተተ የጨዋታ አመራሮች ሊንኩን እንዳትከፍቱት ብሎም ምንም ነገር እንዳትሞሉ እናሳስባለን።


"ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ያላቸው የዳኝነት ባለሙያዎች ለመፍጠር እንጥራለን"

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

17 Sep, 16:51


የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን እና ጎፈሬ የትጥቅ አምራች ኩባንያ በአይነቱ ልዩ የሆነ የዳኞች ትጥቅ አቅርቦት የአጋርነት ስምምነት ተፈራርመዋል።

ዛሬ በኢሊሊ ሆቴል በተካሄደው ሥነ ስርዓት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ባሕሩ ጥላሁን፣ የጎፈሬ መስራች እና ባለቤት አቶ ሳሙኤል መኮንን፣ የብሔራዊ ዳኞች ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሸዋንግዛው ተባበል እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች እና የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

ለሦስት ዓመታት በሚቆየው በዚህ የአጋርነት ስምምነት ጎፈሬ ለኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ዳኞች አራት አይነት ትጥቆችን ጨምሮ የማሟሟቂያ ፣ የጉዞ እና ቅድመ ጨዋታ ስብሰባ ላይ የሚጠቀሙባቸው ቲሸርቶች እና ቱታ በስፖንሰር መልክ የሚያቀርብ ሲሆን በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ስር በሚካሄዱ ሌሎች ውድድሮች ደግሞ እንደ የደረጃቸው ቅናሽ የተደርገባቸው ትጥቆች የሚቀርቡ ይሆናል።

በመርሐ ግብሩ ላይ ስለ ስምምነቱ ማብራርያ የተሰጠ ሲሆን የጨዋታ አመራሮቻችን የሚጠቀሙባቸው ትጥቆች ለእይታ ቀርበዋል።

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

16 Sep, 14:44


ለፕሪሚየር ሊግ ዳኞች
እያደገ የሚሄድ ዓመታዊ የአፈፃፀም መለኪያ መስፈርትን ስለማሳወቅ


ይህ መስፈርት ለፕሪሚየር ሊጉ መሆኑን እያሳወቅን የምስጉን ዳኛ ምርጫ በዚህ ሂደት የሚያልፍ መሆኑን እንገልፃለን። ለሌሎች ሊጎችም መጠነኛ ማሻሻያ እንደየሊጎቹ ሁኔታ በማድረግ የምናሳውቅ ይሆናል። ማንኛውም አስተያዬት ያለው ሰው ለዲፓርትመንቱ እንዲያቀርብ ይበረታታል።

#ማሳሰቢያ
ይህ የዓፈፃፀም መለኪያ ለፕሪሚየር ሊጉ የሚያገለግል የደረጃ መወሠኛ መሥፈርት ሲሆን በየጊዜው የሚደረጉ ልዩ ልዩ ምርጫዎች በተገኘው የደረጃ ቅደም ተከተል መሠረት ይሆናል።


👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ያለው የዳኝነት ሙያ በሀገራችን እንዲኖር እንሰራለን

EFF Refereeing Departement (የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዳኞች ዲፖርትመንት)

16 Sep, 11:28


ለፕሪሚየር ሊግ ዳኞች
እያደገ የሚሄድ ዓመታዊ የአፈፃፀም መለኪያ መስፈርትን ስለማሳወቅ


ይህ መስፈርት ለፕሪሚየር ሊጉ መሆኑን እያሳወቅን የምስጉን ዳኛ ምርጫ በዚህ ሂደት የሚያልፍ መሆኑን እንገልፃለን። ለሌሎች ሊጎችም መጠነኛ ማሻሻያ እንደየሊጎቹ ሁኔታ በማድረግ የምናሳውቅ ይሆናል። ማንኛውም አስተያዬት ያለው ሰው ለዲፓርትመንቱ እንዲያቀርብ ይበረታታል።

#ማሳሰቢያ
ይህ የዓፈፃፀም መለኪያ ለፕሪሚየር ሊጉ የሚያገለግል የደረጃ መወሠኛ መሥፈርት ሲሆን በየጊዜው የሚደረጉ ልዩ ልዩ ምርጫዎች በተገኘው የደረጃ ቅደም ተከተል መሠረት ይሆናል።


👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ያለው የዳኝነት ሙያ በሀገራችን እንዲኖር እንሰራለን