Southwest Communications @debubmierab Channel on Telegram

Southwest Communications

@debubmierab


https://www.facebook.com/sowestcommunication?mibextid=ZbWKwL


www.southwestcomunications.gov.et

Southwest Communications (English)

Southwest Communications is a leading Telegram channel that brings you the latest news and updates from the Southwest region. As a trusted source of information, Southwest Communications covers a wide range of topics including politics, business, culture, and more. With a dedicated team of reporters and editors, this channel is committed to providing accurate and timely news to its subscribers.

Who is Southwest Communications? Southwest Communications is a reliable news outlet that aims to keep you informed about the latest developments in the Southwest region. Whether you are interested in local politics, business trends, or cultural events, this channel has you covered.

What is Southwest Communications? Southwest Communications is a Telegram channel dedicated to providing high-quality news and information to its audience. By following this channel, you can stay up-to-date on important events and stories happening in the Southwest region. From breaking news to in-depth analysis, Southwest Communications delivers the news that matters to you.

Join Southwest Communications today to stay informed and connected with the Southwest region. Follow us on Telegram @debubmierab and visit our Facebook page at https://www.facebook.com/sowestcommunication for more updates. You can also visit our website at www.southwestcomunications.gov.et for additional information and resources. Don't miss out on the latest news - join Southwest Communications now!

Southwest Communications

18 Feb, 15:05


በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የቦንጋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የ2017 በጀት ዓመት የ6 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ተገመገመ

የቦንጋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የ2017 በጀት ዓመት የ6 ወራት ዕቅድ ክንውን ሪፖርት በጣቢያው የልማት ዕቅድ ዳይሬክተር በሆኑት በአቶ ክንፈ ገብሬ ቀርቦ ውይይት ተደርጓበታል።

በመድረኩ የተሳተፉ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ባለሙያዎች እንዳነሱት የሚቀረጹ ይዘቶች ተደማጭነትና የስርጭት አድማስ በማስፋት ሊሠራ እንደሚገባ ገልፀዋል።

ተቋሙ አንዳንድ ከሰው ሃይል፣ ከበጀትና ከሚዲያ ቁሳቁስ እጥራት ጋር ያሉ ችግሮችን መፍታት እና ከተለያዩ ተቋማት ጋር ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር የውስጥ ገቢውን ለማሣደግ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባም አንስተዋል፡፡

ያረጁ የሚዲያ ቴክኖሎጂ ዕቃዎች እንዲቀየሩ ጠይቀዋል።

ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ ተደማጭ ሆኖ እንዲቀጥል ከወትሮው የበለጠ ለመስራት የበኩላቸውን ሚና ለመወጣት ዝግጅ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

የቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ምክትል ሥራአስኪያጅና የይዘት ዘርፍ አስተባባሪ አቶ አሸናፊ አየለ እንደገለጹት በጣቢያው የሚሰሩ ዜናዎችና ፕሮግራሞች ከወትሮው በተሻለ ጥራት ደረጃ እየተሰሩ በመሆናቸው ተደማጭነቱ በዚያው መልኩ እየተሻሻለ መምጣቱን ተናግረዋል።

ከሰው ሃይል፣ ሚዲያ ቴክኖሎጂ ቁሳቁሶችና የውስጥ ገቢ አቅሙን ለማሣደግ በሚደረገው ጥረት ጣቢያው በቀጣይ የበለጠ ውጤታማ ለመሆን በልዩ ሁኔታ እየተሰራ ነዉ ብለዋል።

የጽሕፈት ቤቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ስንታየሁ ሳልልህ በበኩላቸው የቦንጋ ሬድዮና ቴሌቪዥን ጣቢያ ዜናዎችን፣ ፕሮግራሞችንና ወቅታዊ ጉዳዮችን የማምረት ስራ የሚሰራ ተቋም መሆኑን ጠቅሰው በሚዲያው ዘርፍ የተሻለ ሥራዎችን ለመሥራት እንዲቻል በጽሕፈት ቤቱ በኩል ጥረት እየተደረገ ይገኛል።

የተቋሙ ተግባራት ዘለቄታዊ የሆነ እይታ የሚጠይቅ በመሆኑ ለዚህም የተጀመሩ ስራዎች መኖራቸውንና ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አንስተዋል፡፡

የክልሉ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ምክትል ኃላፊና የኮሙኒኬሽንና ሚዲያ ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ በረከት ኢዮብ ቢሮው አጀንዳ የሚመግብ ተቋም በመሆኑ ከቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ጋር አብሮ መስራት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ በርካታ ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመው አንዳንድ የሚታዩ ችግሮችን በማረም በቀጣይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት የሚጠበቅበት መሆኑን ተናግረዋል።

የክልሉን ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችሉ ይዘቶች በተቋሙ ተቀርጸውና ተገቢው ትኩረት ተሰጥቷቸው ሊሰሩበት እንደሚገባም ጠቁመዋል።

የክልሉ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ የሺዋስ ዓለሙ በበኩላቸው ጣቢያው በ6 ወር ወስጥ የተሻለ አፈፃፀም መኖሩን ገልጸው በቀጣይ የክልሉ ሕዝብ የመረጃ ተደራሽነት ለማስፋት የተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮችን መጠቀም ይገባል ብለዋል።

ተቋሙ ከኮሙኒኬሽን ተቋማት ጋር ቅንጅታዊ አሰራርን በመጠናከር መረጃዎችን በተሻለ በጥራት ደረጃና በወቅታዊነት መሥራት እንደሚገባም ገልጸዋል።

ቅርንጫፍ ጣቢያዉ የውስጥ ገቢ አቅሙን የበለጠ ለማሳደግ የአየር ሰዓት ሽፋኑን በመጨመርና የተለያዩ አማራጭ መንገዶች በመከተል መስራት እንዳለበት ገልፀዋል።

የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ እያደረገ ያለዉን ሁሉን አቀፍ ድጋፍ የሚያጠናክር መሆኑንም አንስተዋል።

የቦንጋ ቅርንጫፍ ጣቢያ ተደማጭነቱን ለማሳደግ ቅንጅታዊ አሰራርን በመጠናከር መረጃዎችን በተሻለ በጥራት መሥራት እንደሚገባም አሳስበዋል ፡፡

በተከተል ወ/ሚካኤል

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.xn--facebook-f86aoi9fn7aq6e.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

18 Feb, 14:15


በኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ለመደገፍ ያለመ ስምምነት ተፈረመ

ኢትዮጵያ ታዳሽ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ለመደገፍ ከመላው አፍሪካ የንግድና ኢንቨስትመንት መድን ድርጅት የአፍሪካ ንግድ መድን ኤጀንሲ (ኤቲአይዲአይ) ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመች፡፡

ስምምነቱ ኢትዮጵያ የውጭ ኢንቨስትመንቶችን ወደ ታዳሽ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች በመሳብ የምታደርገውን ሽግግር ያፋጥናል መባሉን የገንዘብ ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል ሲል ኤፍኤም ሲ ዘግቧል፡፡

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

18 Feb, 14:14


ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ስራው እንዲሳካ መንግስት ቁርጠኛ ነው

የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ስራው እንዲሳካ መንግስት ቁርጠኛ መሆኑን የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ ቤልጅጌ (ዶ/ር) ገልፀዋል።

ኮሚሽኑ በሀገሪቱ ለረጅም ጊዜ የተከማቹ ቅሬታዎችንና ችግሮችን ይፈታል ተብሎ የታመነበትና በብዙ ዜጎች ቅቡልነት ያገኘ እና ተስፋ የተጣለበት ተቋም መሆኑን አብራርተዋል።

ኮሚሽኑ በገለልተኛነት ለሚያከናውናቸው ተግባራት መንግስት ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር ቁርጠኝነቱን እያሳየ መሆኑንም አስረድተዋል።

ለአብነትም በቅርቡ የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበል ትጥቅ የፈቱ ታጣቂ ሀይሎች በሀገራዊ የምክክር መድረክ መሳተፋቸውን ጠቅሰዋል።

በቀጣይም ከጠመንጃ ውጪ በጠረጴዛ ዙሪያ እነጋገራለሁ ለሚል ማንኛውም አካል መንግስት በሩን ክፍት እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

ለስኬቱም ሁሉም አካል ከሚያራርቁ ሀሳቦች ይልቅ በሚያቀራርቡ ጉዳዮች አተኩሮ መስራት እንዳለበት መግለጻቸውን የምክር ቤቱ መረጃ ያመለክታል።

የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የካቲት 14 ቀን 2017 ዓ.ም. የስራ ዘመኑ የሚጠናቀቀውን የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የስራ ዘመን ለአንድ አመት እንዲራዘም ለምክር ቤቱ የውሳኔ ሀሳቡን አቅርቧል።

ምክር ቤቱም በቀረበው የውሳኔ ሀሳብ ላይ ከተወያየ በኋላ የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የጀመራቸውን ታላላቅ ሀገራዊ ስራዎችን እንዲያጠናቅቅ የስራ ዘመኑን በሶስት ተቃውሞ በአብላጫ ድምፅ ለአንድ ዓመት አራዝሟል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

18 Feb, 14:13


በፀጥታና ደህንነት በኢኮኖሚና በፖለቲካው መስክ የተከናወኑ ተግባራት ሀገር አሻጋሪ ናቸው:-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

በፀጥታና ደህንነት በኢኮኖሚና በፖለቲካው መስክ የተከናወኑ ተግባራት ሀገር አሻጋሪ መሆናቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።

የጠቅላይ ሚኒስትር ተጠሪ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያው አጋማሽ አፈጻጸም የግምገማ መድረክ እየተካሄደ ነው።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በመክፈቻ ንግግራቸው፥ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያው አጋማሽ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚና ሌሎችም መስኮች በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።

በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የለውጡ መንግሥት ከተመሠረተ በአጭር ጊዜ ውስጥ የላቁ ተግባራትን ማከናወኑንም ጠቅሰዋል።

በተለይም በፀጥታና ደህንነት በኢኮኖሚና በፖለቲካው መስክ የተከናወኑ ተግባራት ሀገር አሻጋሪ ናቸው ብለዋል።

ብዙ ፈተናዎች ቢገጥሙንም እየተሻገርናቸው ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ በቀጣይም ፈተናዎችን ለተሻገረ ድል መትጋት ወሳኝ ነው ብለዋል።

በግማሽ ዓመቱ ከልማት ሥራዎች ባሻገር በርካታ ሀገራዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ሁነቶችንና ጉባኤዎችን ማስተናገድ መቻሉንም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያን ገፅታ የቀየሩና ስሟን በበጎ ያስጠሩ ስራዎች መከናወናቸውን በማንሳት፥ በዓመቱ በዓለም ከፍተኛ የቱሪስት መዳረሻ ከሆኑ ሀገራት አንዷ ሆናለች ብለዋል።

በድህነትና ኋላቀርነት ትታወቅ የነበረችው ሀገራችን ዓይን ገላጭ ሥራዎችን በመተግበር በበርካታ መስኮች አስደማሚ ለውጥ አምጥታለች ብለዋል።

ለተገኙ ተስፋ ሰጪ ስኬቶች የጠቅላይ ሚኒስትር ተጠሪ ተቋማት የመሪነት ድርሻቸው የላቀ እንደሆነም ገልጸዋል።

የእስካሁን ሥራዎች ጅምር እንጂ የተሟላ የስኬት ደረጃ ላይ አልደረሱም ያሉት አቶ ተመስገን፥ የዓለም ነባራዊ ሁኔታን ታሳቢ ያደረገ ሥራ ከፊታችን ይጠብቀናል ብለዋል።

ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ ራሷን እንድትችል እና በአፍሪካ የብልፅግና ተምሳሌት እንድትሆን የተቀናጀና እረፍት የለሽ ሥራ የግድ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የጠቅላይ ሚኒስትር ተጠሪ ተቋማት ከራሳቸው ባለፈ ለሌሎች ተቋማት ግብ መሳካት ጉልህ አስተዋፅኦ ማበርከት እንዳለባቸውም ገልፀዋል።

በተለይ አገልግሎት አሰጣጥን ማዘመን፣ ወጪ ቆጣቢ መሆን፣ ቅንጅታዊ አሠራርን ማጠናከር እና ተፅዕኖ መፍጠር ላይ ተጠሪ ተቋማቱ የትኩረት ማዕከል መሆን አለባቸው ብለዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

15 Feb, 18:36


ማህሙድ አሊ ዩሱፍ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሆነው ተመረጡ

የጅቡቲ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል።

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ለመሆን ሶስት እጩዎች ከፍተኛ ፉክክር ሲያደርጉ ቆይተዋል።

በዚህም በስራ ላይ ያሉትን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሀመት ለመተካት በተካሄደው ምርጫ የጅቡቲው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ 33 ድምፅ በማግኘት ምርጫውን አሸንፈዋል።
ኢቢሲ

Southwest Communications

15 Feb, 13:29


ተመራቂ ተማሪዎች ከመንግስት ተቀጣሪነት ይልቅ ለስራ ፈጣሪነት ትኩረት ማድረግ እንደሚገባቸው ተገለጸ

ተመራቂ ተማሪዎች ከመንግስት ተቀጣሪነት ይልቅ ለስራ ፈጣሪነት ትኩረት ማድረግ እንደሚገባቸው የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪያል ፓርኮች ልማት ዋና ስራ አስፈጻሚ እና የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ የቦርድ ሰብሳቢ ዶክተር ፍሰሀ ይታገሱ ተናገሩ።

ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በመጀመሪያ እና በድህረ ምረቃ ፕሮግራም ያስተማራቸውን 394 ተማሪዎቹን ለ17ኛ ጊዜ አስመርቋል።

ሁለተኛ ትውልድ እየተባሉ ከሚጠሩት ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ አንዱ የሆነው የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ፥ ከዛሬ አስራ ስምንት አመት በፊት 200 መቶ ተማሪዎችን ተቀብሎ አስተምሮ ያስመረቀ ሲሆን ዘንድሮም በተለያዩ የትምህርት መስኮች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ 394 ተማሪዎችን በድህረ ምረቃ እና በመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራም ማስመረቁን ነው የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ዋቆ ገዳ የተናገሩት።

ዩኒቨርስቲው በዘንድሮ 2017 የትምህርት ዘመን በ54 ቅድመ እና በ42 ድህረ ምረቃ ፕሮግራሞችን እያስተማረ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

በዩንቨርስቲው የነበሩ ተግዳሮቶችን ለመፍታት እንደ ሀገር ትምህርት ሚኒስቴር የሰራው ሀገራዊ የሪፎርም ስራ የዩኒቨርስቲ አመራር ቦርዶች በአዲስ በመተካቱ የነበሩ ጉድለቶችን በማረም ያሉትን ጥንካሬዎች በማስቀጠል በተሰሩት ስራ ተጨባጭ ለውጥ መመዝገብ ተችሏልም ብለዋል።

ዩኒቨርስቲው በ2017 የትምህርት ዘመን ከ80 በመቶ በመረጡት የትምህርት ዘርፍ መደልደል መቻሉን ጠቁመው ተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና የተሻለ ውጤትም እንዲያስመዘግቡ በመምህራኖች በሚሰጣቸው ድጋፍም የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ማድረጉን ገልጸዋል።

በምረቃው ስነ-ስረአት ላይ የተገኙት የዩኒቨርስቲው የቦርድ ሰብሳቢ እና የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪያል ፓርኮች ልማት ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ፍሰሀ ይታገሱ በበኩላቸው፥ የሀገራችን መንግስት በትምህርቱ ዘርፍ የነበሩ ስብራቶችን ለመጠገን በርካታ የሪፎርም ስራዎችን መስራቱን ጠቁመው፥ በአጭር ጊዜ ቀላል የማይባሉ ለውጦች መመዝገብ ችሏል ብለዋል።

ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ላለፉት አመታት በሀገር አቀፍ የመውጪያ ፈተና ያስመዘገበው አመርቂ ውጤት የዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ እና መምህራን የጋራ ውጤት በመሆኑ ሊመሰገኑ ይገባል ብለዋል።

ምሩቃን ተማሪዎች ወደ ሰፊው ማህበረሰብ ስትቀላቀሉ ከመንግስት ተቀጣሪነት አስተሳሰብ ይልቅ ለስራ ፈጣሪነት ትኩረት ማድረግ ይገባችኋል ብለዋል።

ዩኒቨርስቲው ከምሩቃኑ ተማሪዎች መካከል ከፍተኛ ነጥብ ላመጡ ሁለት የጤና ተመራቂ ተማሪዎች ነጻ የትምህርት እድል ሰጥቷል።

ከፍተኛ ውጤት አምጥተው የተመረቁ ተማሪዎችም ዩኒቨርስቲው በሰጣቸው ነጻ የትምህርት እድል መደሰታቸውን ጠቁመው ህብረተሰባቸውን በሰለጠኑበት ሙያ ለማገልገል ቃል ገብተዋል።

እንዲሁም በመንግስት የትምህርት እድል ተጠቃሚ የሆኑ እና በድህረ ምረቃ የተመረቁ የአመራር አካላቶችም ባገኙት እውቀት ይበልጥ ህብረተሰባቸውን ለማገልገል ቃል ገብተዋል።
ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

15 Feb, 13:26


ርዕሰ መስተዳድር ኢ/ር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ከኢፌዲሪ ከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የድጋፍ ቡድን ጋር ተወያዩ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ከኢፌዴሪ ከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ከ አመራሮች ጋር የክልሉን የከተማ ልማት ስራዎች ላይ ያተኮረ ዉይይትላይ በጽህፈት ቤታቸው አድርገዋል፡፡

የኢፌዲሪ ከተማ መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች በክልሉ የከተማ መሬት በምዳባና በጨረታ በማስተላለፍ ሰነድ አልባ የከተማ መሬቶችን ወደ ህጋዊ መስመር ከማስገባት ጥሩ ጅምር ስራዎች መኖራቸውን ገልጸው ለቀጣይነቱ የፖለቲካ አመራር ቁርጠኝነት ይጠይቃል ነው ያሉት ፡፡

የሱፐርቪዥን ቡዱኑ በአጠቃላይ በክልሉ የገጠርና ከተማ ኮሪደር ተግባራት ጥሩ ጅምር ስራዎች አይተናል ያሉ ሲሆን ከከተማ ጽደት አንፃር የከተማ ቆሻሻ መልሶ ከመጠቀም አንፃር በቀጣይ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባም አንስተዋል፡፡

የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር የማታለም ቸኮል የከተሞች ኮሪደር ልማትን የተሻለ ለማድረግ ህብረተሰቡንና ባለሃብቶችን በማሳተፍ የተጀመሩ ጥሩ ጅምር ስራዎች መኖራቸውን ገልጸው ይህንን አጠናክሮ ማስቀጠል የሚያስፈልግ መሆኑን አንስተዋል፡፡

የከተሞች አረንጓዴ ሽፋንን ለማሳደግ ለከተማ እንደ ክልል ከተማ ልማትና ኮንሰትራክሽን ቢሮ ሰፊ ስራዎች እየተሰራ ነው ቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም በውይይቱ መድረኩ ላይ አብራርተዋል፡፡

በውይይት መድረኩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ፤ የፌዴራል የሱፐርቪዥን ቡድን በየወቅቱ በክልላችን በተጨባጭ መሬት ላይ ያሉ ተግባራትን ምልከታ በማድረግ በየጊዜው የሚሰጠው ግብረ መልስ ለክልሉ ትልቅ አቅም የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል።

እንደ ክልል የኮሪደር ልማት ስራ ዘግይቶ የተጀመረ ቢሆንም ከሌሎች ከተሞች ጋር በተመሳሳይ ጊዜ ለማጠናቀቅ የተጀመሩ በርካታ ጥሩ ጅምር ስራዎች መኖራቸውንና ስራውን ውጤታማ ለማድረግ ህብረተሰቡን በማሳተፍ ትኩረት ተሰጥቶ የሚሰራ ተግባር መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ከከተማ ገቢ አንፃር በከተሞች አካባቢ በርካታ የገቢ መሠረቶች መኖራቸውን ያነሱት ርዕሰ መስተዳድሩ በሚፈለገው መልኩ ሰብስቦ ልማት ላይ ከማዋል አንፃር በቂ አይደለም በቀጣይ ከተሞች በልዩ ትኩረት መስራት የሚፈልግ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

ከከተማ ማዘጋጀ ቤታዊ አገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን በሁሉም ከተሞች የተጀመሩ ስራዎች መኖራቸውን ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሂሩት ዮሐንስ፤ በክልሉ ኮሪደር ልማት ስራ በሚመለከት ጥሩ ጅምር ስራዎች ያለው ቢሆንም ባለሀብቱንና ህብረተሰቡን እንዲሁም የተለያዩ ግብረ ሰናይ ድርጅት በኮሪደር ልማት ስራው ማሳተፍ አጠናክሮ መስራት ያስፈልጋልም ብለዋል፡፡

ከመሠረተ ልማት አኳያ የተጀመሩ ጥሩ ስራዎች ያሉ ቢሆንም አሁንም በመንገድ መሠረተ ልማት ዘርፍ ያለውን ችግር በመለየት ትኩረት ተሰጥቶ መስራት የሚጠይቅ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በተከተል ወ/ሚካኤል

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

15 Feb, 11:06


አፍሪካ ሙሉ የብልፅግና አቅሟን እንድትጠቀም አንድነት እንጂ መከፋፈል አይጠቅምም - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አፍሪካ ሙሉ የብልፅግና አቅሟን እንድትጠቀም አንድነት እንጂ መከፋፈል እንደማይጠቅም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በ38ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ ላይ የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል፡፡

በንግግራቸውም “የጉባኤው ተሳታፊዎች የፓን አፍሪካኒዝም መሰረት እና የአፍሪካ የነጻነት ቀንዲል ወደ ሆነችው ኢትዮጵያ እንኳን በደህና መጣችሁ” ብለዋል።

ተለዋዋጭ በሆነው የዓለም ሥርዓት ውስጥ ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ አፍሪካውያን አንድነታቸውን ማጎልበት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል፡፡

በአህጉሪቱ ሰላም እና ልማትን ለማረጋገጥ ቀጣናዊ ውጥረቶችን መፍታት፣ ታሪካዊ ክፍፍሎችን ማስወገድ እና በአንድነት እሳቤ መነሳት እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡

ጉባኤው አፍሪካውያን በታሪክ የደረሰባቸው በደል የሚሽርበትን አይነተኛ መፍትሄ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ የምንቀይስበት ሊሆን ይገባልም ብለዋል።

“በታሪክ ለደረሰብን በደል የምንጠይቀው ካሳ እርዳታ ወይም ችሮታ ሳይሆን ፍትህን ነው“ ሲሉም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አበክረዋል ሲል ኢቢሲ
ዘግቧል።
ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

15 Feb, 06:05


የአፍሪካ መሪዎች በምን ጉዳይ ላይ ይመክራሉ?

የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ዛሬ በአዲስ አበባ ሲጀመር ቀደም ሲል በተጠናቀቀው የሚንስትሮች ጉባኤ ላይ ተመስርቶ ነው የሚካሄደው።

በስኬት እንደተጠናቀቀ የተገለጸው የሚንስትሮች ጉባኤ ለውይይት የሚሆኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን በመለየት ለመሪዎች እንዲቀርብ ይደረጋል።

በዘንድሮው የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ላይ መሪዎች ዓለም አቀፋዊ እና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ በመምከር ውሳኔ እንደሚያሳልፉ ይጠበቃል።

የአፍሪካ ህብረት ተቋማዊ ማሻሻያዎች፣ የማካካሻ ፍትህ፣ አህጉራዊ ሰላምና ደህንነት ውይይት የሚደረግባቸው አጀንዳዎች እንደሆኑ ተጠቁሟል፡፡

የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና አፈጻጸምና አህጉራዊ የንግድና ኢኮኖሚ ትስስር፣ ግብርናና የአየር ንብረት ለውጥ፣ ሰብዓዊ መብቶች፣ ስርዓተ ጾታና ወጣቶችን ማብቃት እንዲሁም የተቋማት አደረጃጀቶች ላይም ጉባኤው ይወያያል።

አፍሪካ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ለማግኘት እየተደረጉ ያሉ እንቅስቃሴዎችን በተመለከተም ህብረቱ የሚወያይበት እንደሚሆን ይፋ ተደርጓል።

የሥራ ዘመናቸውን በጨረሱት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ቦታ የአዲስ ኮሚሽነር ምርጫ ማካሄድም ከዚህ ጉባኤ የሚጠበቅ ነው።

ኢቢሲ

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

14 Feb, 09:12


የሲሚንቶ ግብይት ላይ በተወሰደ የአሰራር ስርዓት ማሻሻያ ዋጋው በግማሽ ቀንሷል - ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)

የሲሚንቶ ግብይት ላይ በተወሰደ የአሰራር ስርዓት ማሻሻያ የተረጋጋ አቅርቦትና ግብይት እንዲኖር ከማድረግ ባሻገር ዋጋው በግማሽ እንዲቀንስ መደረጉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው÷ የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ አጋማሽ የፌደራልና የክልሎች የንግድ ዘርፍ ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ ዛሬ አካሂደናል ብለዋል፡፡

በ6 ወራት በሀገር አቀፍ ደረጃ 2 ሚሊየን 50 ሺህ በላይ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት በኦንላይን መሰጠቱን ገልጸዋል፡፡

ከጠቅላላው ሀገራዊ የወጪ ንግድ 3 ነጥብ 28 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ገቢ መገኘቱን ገልጸው፤ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር 1 ነጥብ 71 ቢሊየን ዶላር ብልጫ እንዳለው ጠቁመዋል።

የቅዳሜና እሁድ ግብይት ማዕከላትን 1 ሺህ 213 ማድረስ መቻሉንም ተናግረዋል።

የሲሚንቶ ግብይት ላይ በተወሰደ የአሰራር ስርዓት ማሻሻያ የተረጋጋ አቅርቦትና ግብይት እንዲኖር ከማድረግ ባሻገር ዋጋው በግማሽ እንዲቀንስ መደረጉንም ጠቅሰዋል፡፡

በስድስት ወሩ ዓለም አቀፍ ጥራቱን የጠበቀ የጥራት መንደር በ7 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ ተገንብቶ ወደ ስራ መግባቱን ጠቅሰው÷ በተቋሙ ቅጥር ግቢ 730 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ የወጪ ንግድ ማሳያ ማዕከል ተገንብቶ የኢትዮጵያን የንግድና ኢንቨስትመንት አቅሞችን በማስተዋወቅ ላይ እንገኛለን ብለዋል፡፡

ዓለም አቀፍ የንግድ ትስስርን በማጠናከር አስተማማኝ የገበያ እድል ከመፍጠር አንጻር የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ ንግድ ቀጣና ስምምነትን ተግባራዊ ለማድረግም እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል፡፡ ኤፍ ኤም ሲ

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

14 Feb, 09:07


በክልሉ በሁሉም ዞኖች በሁለተኛው የብልጽግና ፓርቲ ውሳኔዎችና የቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ ከዞን ማዕከል አጠቃላይ አመራሮች ጋር ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

14 Feb, 07:49


በፓርቲያችን ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ የተቀመጡ ውሳኔዎች እና አቅጣጫዎች እንዲሳኩ አመራሩና አባሉ በቁርጠኝነት መስራት ይገባቸዋል፦ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግሥት ብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ''ከቃል እስከ ባህል''በሚል መሪ ቃል በሁለተኛው የብልጽግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ የተቀመጡ ውሳኔዎች እና አቅጣጫዎች ዙሪያ እየተወያዩ ነው።

ውይይቱ በጉባዔው በተላለፉ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ላይ የጋራ ግንዛቤ በመያዝ ወደ ትግበራ ለመግባት ዓላማ ያደረገ ነው።

የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ እና የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ብልጽግና ባለፉት ጥቅት ዓመታት የገመጡትን ፈተናዎች በመሸጋገር የማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ፖለቲካዊ እና ዲፕሎማሲያዊ በርካታ ውጤቶችን ማስመዝገብ የቻለ ፓርቲ ነው ብለዋል።

ፓርቲው በመጀመሪያው መደበኛ ጉባኤ ያስተላለፋቸው አንኳር ጉዳዮች እስከ ሁለተኛ ጉባኤ በገባው ቃል መሠረት በመፈጸም የህዝቡን የሰላም፣የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ማረጋገጥ ችሏል ስሉ ተናግረዋል ።

በዚህም ሀገሪቱ የገጠማትን የኢኮኖሚው ስብረት መጠገን የሚያስችሉ ፖሊሲ እና ሪፎርም ተግባራዊ በማድረግ በግብርናው፣በቱሪዝም፣ኢንዱስትሪና በሌሎች ዘርፎች ትኩረት አድርጎ መስራቱንም ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል።

ፓርቲው በማህበራዊ ዘርፍ በጤና እና በትምህርት እንዲሁም በሌሎች ማህበራዊ ጉዳዮች የሚያጋጥሙ ችግሮችን ከመፍታት ባሻገር የባህር በር ጥያቄ በሰላማዊ መንገድ ለማግኘት የሄደበት አካሄድ ለቀጣይ ለብልጽግና ጉዞ ምቹ ምቹ መደላድል እየፈጠረ ይገኛል ነው ያሉት።

ዶክተር ነጋሽ ዋጌሾ በፓርቲው ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ የተቀመጡ ውሳኔዎች እና አቅጣጫዎች እንዲሳኩ አመራሩና አባሉ በወጥነት ተግባሩን ማከናወን እንደሚኖርበትም በአጽንኦት ተናግረዋል።

የብልጽግና ፓርቲ ምክር ቤት አባልና የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን በበኩላቸው በፓርቲው ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ የተቀመጡ ውሳኔዎች እና አቅጣጫዎች እንዲሳኩ አመራሩ ፣አባሉና ህዝቡ ከፓርቲው ጎን እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል።

በውይይት የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እየተሳተፉ ነው።

በፍቅር ከበደ

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

13 Feb, 10:56


4ኛው የክልል አቀፍ ባህል ስፖርቶች፣ ባህል ፌስቲቫል እና 1ኛዉ የአትሌቲክስ ውድድር ከየካቲት 8/2017 ጀምሮ በኮንታ ዞን አመያ ከተማ ይካሄዳል።

''ባህላዊ ስፖርቶቻችንን ለአንድነታችንና ለሠላማችን'' በሚል መሪ ቃል ከየካቲት 8_13/2017 ዓ.ም በኮንታ ዞን በአመያ ከተማ የሚካሄደው 4ኛው የክልል አቀፍ የባህል ስፖርቶች፣ የባህል ፌስቲቫል እና የአትሌቲክስ ውድድር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች የተጠናቀቁ መሆናቸውን የክልሉ የባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ሃላፊ አቶ ፋንታሁን ብላቴ ገልጿል።

የቢሮ ኃላፊው አክለውም የባህል ስፖርቶችና የባህል ፌስቲቫል ውድድር የህዝቦች ትስስር በመፍጠር የማህበረሰቡ ቱባ ባህላዊ እሴቶች እንዲጎለበቱና እንዲታወቁ ድርሻው ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።

አያይዘውም አቶ ፋንታሁን ውድድሩ በህዝቦች መካከል ህብረ-ብሔራዊ ወንድማማችነትን በመትከልና ክልላዊ አንድነቱን በማጽናት ክልሉን ወክለው በፌዴራል ደረጃ የሚወዳደሩ ብቁ ልዑካኖችን ለማገኘት ታስቦ የተዘጋጀ ውድድር እንደሆነ አብራርተዋል።

የክልሉ የባህል ስፖርቶች ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አፈወርቅ ዳና የባህል ስፖርቶቻችን ውድድርና የባህል ፌስቲቫል የክልሉ ህዝቦች ነባር ባህላዊ ኩነቶችንና ወጎችን በአደባባይ ለማስተዋወቅና በህዝቦች መካከል ያለዉን ህብረ-ብሔራዊ ወዳጅነት ለማሳየት ምቹ አውድ በመሆን እያገለገለ እንደሆነም ገልጿል።

ውድድሩ በ11 የተለያዩ የባህላዊ የስፖርቶች ዓይነቶች ማለትም በሻህ፣ በቡብ፣ በገበጣ ባለ12 ጉድጓድ፣ በገበጣ ባለ 18 ጉድጓድ፣ በኮርቦ፣ በትግል፣ በፈረስ ጉግስ፣ በፈረስ ሽርጥ፣ በቀስት እንዲሁም በድብልቅ ቀስት በአጠቃላይ በሁሉም የስፖርት ዓይነቶች በሁለቱም ፆታዎች ከ400 በላይ ስፖሮተኞችና የፌስቲቫል ተሳታፊዎችን የሚያሳትፍ ነው ሲል አቶ አፈወርቅ አክለዋል።

አትሌቲክስ ውድድር በክልሉ የመጀመሪያ መሆኑን በመጥቀስ በውድድሩ ስድስቱም ዞኖች የሚሳተፉ ሆኖ በግልም የሚሳተፉ የአትሌቲክስ ክለቦችና የሚዛን አማን አካዳሚ ጨምሮ እንደሚገኙ የቢሮ ምክትል ሃላፊና የስፖርት ዘርፍ አቶ አህመዲን አወል ተናግሯል።

በውድድር የሚሳተፉ ልዑካኖች የስፖርታዊ ጨዋነት በመላበስ ብቁ ውድድር እንደያደርጉም አቶ አህመዲን መናገራቸዉን የክልሉ የባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ መረጃ ያመለክታል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

13 Feb, 08:16


ክልላዊ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን ከሰው ንክኪ ውጭ በሆነ በቴክኖሎጂ እንዲታገዝ መደረግም አለበት።ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር)

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወራት ዕቅድ አፈጻጸምና የቀጣይ ወራት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር በታርጫ ከተማ እየመከረ ነው ።

በምክክር መድረኩ የተገኙት ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ባስተላለፉት መልዕክት በግማሽ ዓመቱ የተሻለ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል ።

በገቢ አሰባሰብ ሂደት ውስጥ የተገኘውን ጥንካሬ ማስቀጠልና በድክመት የታየውን በመቅረፍ ባለድርሻ አካላት ለገቢ ውጤታማነት የድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል ።

ገቢን መሰብሰብ የሚያስችል አቅም እያለ በአቅም ልክ መሰብሰብ ያልቻልንበትን ችግሮች በመለየትም ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ በትኩረት መሰብሰብ ይገባልም ብለዋል።

ክልላዊ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን ከሰው ንክኪ ውጭ በሆነ በቴክኖሎጂ እንዲታገዝ መደረግም አለበት ብለዋል ርዕሰ መስተዳድሩ።

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን ተከትሎም የደረጃ ለውጥ የሚያስፈልጋቸውን ግብር ከፋዮች በመለየት በትኩረት ሊሰራበት ይገባል ብለዋል።

በገቢ አሰባሰብ ሂደት ውስጥ የህግ የበላይነትን በማስፈን የፖለቲካ አመራሩ፣የፍትህ እና የፖሊስ አካላት ተቀናጅተው ሊሰሩም እንደሚገባ ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል ።

ክልላዊ የገቢ ዕቅድ 10.07 ቢሊዮን ብር ለማሳካት የተለያዩ የገቢ አማራጮችን በመጠቀም ማሳካት ይገባናል ብለዋል።

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ህይወት አሰግድ በበኩላቸው የክልሉን ህዝብ የልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ 60 ከመቶ በውስጥ ገቢ ለመሸፈን ግብ ተጥሎ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

በክልሉ ግብርን በቴክኖሎጂ በመታገዝ የማዘመን ስራዎችን ዕውን ለማድረግም በ66 የታክስ ማዕከላት ሲሰራ መቆየቱንም ወ/ሮ ህይወት ተናግረዋል ።

በክልል ቢሮዎች የሚሰበሰበውን ገቢ የኢታክስ ስርዓት በመዘርጋት ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።

የክልሉን የገቢ ዕቅድ ውጤታማ ለማድረግ በአንዳንድ ተቋማት ልልነት የታየበት አሰራር መኖሩ በሚፈለገው ልክ ገቢን ለመሰብሰብ ተግዳሮት በመሆኑ ህግን በማስከበር የሚፈለገውን ገቢ ስኬታማ ለማድረግ ባለድርሻ አካላት ተቀናጅተው ሊሰሩ እንደሚገባ ገልጸዋል ።

ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት የክልሉ ገቢዎች ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የቀጣይ ወራት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ የአፈጻጸም ሪፖርት በቢሮ የልማት ዕቅድ ዳይሮክቶሬት በሆኑ በአቶ ጂብሪል አባጊሳ ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት ነው።

በታጠቅ አበበ

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

08 Feb, 16:09


የብልፅግና ፓርቲ በሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ካስቀመጣቸው ስምንት የትኩረት አቅጣጫዎች መካከል አንዱ የሆነው ገቢር ነበብ ፐብሊክ ሰርቪስ ሪፎርም የአገልግሎት አሰጣጥ በቴክኖሎጂ እንዲታገዝ በማድረግ በዘርፋ የነበሩ ችግሮችን ይፈታል

በብልፅግና ፓርቲ ዋና ስቱዲዮ በመገኘት ፓርቲው ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በሲቪል ሰርቪስ ዙሪያ እየተደረገ ስለሚገኘው ገቢር ነበብ የፐብሊክ ሰርቪስ ሪፎርም ማብራሪያ የሰጡት የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ የሰለጠነና ቀልጣፋ፣ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አገልግሎት ለማቅረብ የማስፈፀም አቅም ማጎልበት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ነው ብለዋል::

በፌደራል እና በክልል መንግሥታት የሚሰሩ ስራዎች የአደረጃጀት እና የአገልግሎት አቅርቦት የተሳለጠ እንዲሆን እየተሰራ ነው ያሉት ዶክተር መኩሪያ ኃይሌ የስራ ሂደቱን የተቀላጠፈ ለማድረግ፣ ብቃት ያለውን የሰው ኃይል በማፍራት በሀገር ደረጃ የመንግስት ሰራተኛው አስተማማኝ አቅም እንዲኖረው የሚመዘንበት ስርአት እየተዘረጋ ነው ብለዋል።

በተጨማሪም የመንግስት ሰራተኛው በፌደራል ተቋማት ያለው ብዝሃነትንና አካታችነትን የጠበቀ የሚሆንበት ዘመናዊ የሆነ የሰው ኃይል ስምሪት በቴክኖሎጅ የታገዘ ለማድረግ በመሰራት ላይ እንደሆነ ገልጸው እነዚህ ሰዎች ሲሰሩ በፅንሰ ሀሳብ፣ በፖሊሲ፣ በስትራቴጂ ብቻ ሳይሆን በተግባር ማሳየት እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል።

ሪፎርሙ ገቢር ነበብ አካሄድ በመከተል ተግባርን መሰረት በማድረግ ችግሮችን የሚፈታ እና ተጨባጭ ሁኔታዎችን አገናዝቦ አመራር የሚሰጥበት ስርዓት የሚፈጥር ነው ብለዋል ዶክተር መኩሪያ ኃይሌ::
በኢትዮጵያ ዘመናዊ አሰራር በመዘርጋት አገልግሎት በማሻሻል ህዝብ በቋንቋው የሚገለገልበት፣ በተለያየ አማራጭ አገልግሎት የሚያገኝበት ሁኔታ ለመፍጠር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ያነሱት ኮሚሽነሩ የመንግስት ሰራተኛው በአግልግሎት አቅርቦትና ምርታማነት ላይ ያለውን ችግር ለመፍታት ትልቅ አቅም እንዳለው መረዳት መቻል እንዳለበት አስገንዝበዋል::

በኢትዮጵያ 2.5 ሚሊዮን በሲቪል ሰርቪስ የተመዘገበ የመንግስት ሰራተኛ መኖሩን ያወሱት ኮሚሽነሩ በሪፎርም መንግስት ሰራተኛው በሰራው ልክ የሚጠቀም መሆኑን ተረድቶ ራሱን ማዘጋጀት አለበትም ብለዋል::

#prosperity

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

08 Feb, 16:08


የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ባለፋት ስድስት ወራት 169 የDNA ምርመራ አከናውኗል

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በ2017 በጀት ዓመት ባለፋት ስድስት ወራት 169 የDNA ምርመራ ማከናወኑን ገልጿል።

ውጤቱ የተመዘገበው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዘመናዊ የDNA ምርመራ ላቦራቶሪ በማደራጀትና በዘርፉ ተገቢው ሙያዊ ዕውቀት ያላቸው ባለሙያዎችን በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር አሰልጥኖ ወደ ሥራ በማሰማራቱ መሆኑን ተቋሙ አስታውቋል።

ከለውጡ በፊት በሀገር ውስጥ የDNA ምርመራ አገልግሎት የሚሰጥ ተቋም ባለመኖሩ ናሙና ወደ ውጭ ሀገር እየተላከ በከፍተኛ ወጪ ሲመረመር እንደነበር አስታውሶ ይህን አሠራር በማስቀረት በሀገር ውስጥ የDNA የምርመራ አገልግሎት መስጠት መቻሉን ገልጿል፡፡

የDNA ምርመራ ለፍትህ ሥርዓት መረጋገጥ ያለው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሶ በተለይ የሰዎችን ማንነት ለመለየት፤ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ለማረጋገጥ፣ ከተወላጅነት ጋር ለሚነሱ ክርክሮችና ቤተሰባዊ ጉዳዮችን ለመመርመር የሚያስችል አቅም እንደተፈጠረም ከተቋሙ የተገኘው መረጃ ያመላክትል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

08 Feb, 14:01


በክልሉ እየተሰሩ ያሉ የግብርና የልማት ሥራዎች አበረታች ናቸው። ግርማ አመንቴ (ዶ/ር)

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በተቋማት እየተከናወኑ ያሉ የግብርና ልማት ስራዎች አበረታች መሆናቸው የኢፌዴሪ ግብርና ሚኒስትር ሚኒስቴር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ተናገሩ።

ሚኒስትሩ ከክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እና ከሌሎች የፌዴራልና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በቦንጋ ግብርና ምርምር ማዕከል እና በቦንጋ ዩኒቨርስቲ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝቷል።

ሚኒስትሩ በጉብኝታቸው በቦንጋ የግብርና ምርምር ማዕከል እየተከናወኑ ያሉ የተለያዩ የዘር ብዜት ስራዎች እና የተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት የጎበኙ ሲሆን በተቋሙ እንደ ማነቆ የቀረቡ ጉዳዮችን ደረጃ በደረጃ ለመፍታት ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በበኩላቸው በተቋማቶቹ እየተሰራ ያለው ተግባር ተስፋ ሰጪ በመሆኑ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ አክለው የክልሉ መንግሥት እየተከናወነ ያለውን የልማት ስራዎች በመደገፍ የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ እንደሚደግፍም ተናግረዋል።

በጉብኝቱ የክልሉ መንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ሌሎችም የባለድርሻ አካላት ተሳተፊ ነበሩ።

በዕድገቱ በዛብህ

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

08 Feb, 14:01


በቦንጋ ከተማ የተገነባው የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና የሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል ምረቃ ሥነ ሥርዓት በፎቶ

Southwest Communications

08 Feb, 11:07


የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ አዲስ አበባ ገቡ

የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡

ዋና ዳይሬክተሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሺዴ፣ የብሄራዊ ባንክ ገዢ አቶ ማሞ ምህረቱ እና የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡

ዋና ዳይሬክተሯ በኢትዮጵያ ቆይታቸው፥ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ከከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ጋር በኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እድገት፣ ቅድሚያ በሚሰጣቸው ፖሊሲዎች እና በኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ዙሪያ ውይይት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።

ክሪስታሊና ከግሉ ዘርፍ ተዋንያን ጋር በኢትዮጵያ ስላሉ የንግድ እና ኢኮኖሚ እድሎች አስመልክቶ ሀሳቦችን እንደሚለዋወጡም ገልጿል።

የዋና ዳይሬክተሯ ጉብኝት አይኤምኤፍ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ልማት ለመደገፍ እና የፖሊሲ ምክክሮችን በማድረግ የማይበገር፣ የጋራ እና ዘላቂነት ያለው ብልጽግና እንደሚመጣ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያመላክት እንደሆነ ተገልጿል።

ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ እ.አ.አ በ2019 በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸውን ሚኒስቴሩ በመረጃው አስታውሷል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

08 Feb, 09:55


ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የብልጽግና ፓርቲ የትኩረት አቅጣጫ ነው - ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር)

ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነትን እውን በማድረግ የኢትዮጵያን ብልጽግና ማረጋገጥ የብልጽግና ፓርቲ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን የፓርቲው ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልና የገንዘብ ሚኒስትር ዴዔታ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ገለጹ።

በ2ኛው የብልጽግና ፓርቲ መደበኛ ጉባዔ ባለፉት ሦስት ዓመታት ፓርቲው ለሕዝብ የገባውን ቃል በብዙ ጥረትና የተቀናጀ ሥራ እያሳካ እንደቆየ ተገምግሟል።

ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር)÷ብልጽግና ከዚህ በፊት የጀመረውን ዘርፈ ብዙ የልማትና የእድገት ሥራዎች በማጠናከር የኢትዮጵያን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ስብራት ለመጠገን አዳዲስ ሀገር በቀል ሃሳብ ይዞ የመጣ ፓርቲ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

ፖርቲው በዜጎች መካከል መለያየትን ይፈጥር የነበረውን የፖለቲካ እሳቤ ከመሰረቱ የቀየረ ነው ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡

በኢኮኖሚው መስክ ሰፋፊ የሪፎርም ሥራዎች ሲከናወኑ እንደቆዩ ማንሳታቸውን ከፓርቲው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የመጀመሪያው የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተጠናቆ በሁለተኛው የኢኮኖሚ ሪፎርም በዋና ዋና ዘርፎች ጠንካራ ተወዳዳሪ የኢኮኖሚ ማዕቀፍ በመገንባት በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በቱሪዝም፣ በማዕድን እና በዲጂታል ኢኮኖሚ ልማት መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግር በማምጣት የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ማረጋገጥ መቻሉን አብራርተዋል፡፡

በ2023 ኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልጽግና የተረጋገጠባት አፍሪካዊት የብልጽግና ተምሳሌት እንድትሆን የሚያግዝ ስራ በቁርጠኝነት፣ በትጋትና በታማኝነት መስራት እንደሚገባም አሳስበዋል ሲል ኤፍኤም ሲ ዘግቧል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

07 Feb, 16:01


ክልሉ ያለው አቅም የሀብት ምንጭ እንዲሆን መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የስራ ኃላፊዎች ገለጹ

በሚቀጥሉት 3 ዓመታት በተለያዩ ዘርፎች ሊተገበሩ በታቀዱ ሥራዎች ዙሪያ በቦንጋ አተማ ውይይት ተደርጓል።

ውይይቱ “ከዕምቅ አቅም ወደሚጨበጥ ሀብት” በሚል መሪ ቃል በክልሉ መንግስት የተዘጋጀ የፖለቲካና የልማት ውይይት ሲሆን ፤ ክልሉ ለቀጣይ ትውልድ የሚተላለፉ በርካታ ሀብቶች ባለቤት መሆኑ ተገልጿል።

በክልሉ ያሉ የመልማት አቅሞችን በተገቢው መለየትና መጠቀም፣ ህብረተሰቡን በማስተባበር ልማታዊ ስራዎችን ማጠናከር፣ የአመራሩን እና የአገልግሎት ሰጪ ተቋማትን አቅም ማሳደግ የሚያስፈልግ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ-መስተዳደር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ገልጸዋል።

በሰላምና ፀጥታ፣ በልማት ፣ በመልካም አስተዳደር እና በፖለቲካ ዘርፎች የህብረተሰበቡን ጥያቄዎች ለመመለስ መስራት ከሁሉም የሚጠበቅ ጉዳይ እንደሆነም አስገንዝበዋል።

የክልሉ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ የሺዋስ ዓለሙ ክልሉ የበርካታ ሀብቶች ባለቤት ነው ብለዋል።

ይህንን ሀብት ለመጠቀም አመራሩና ህዝቡ የተግባር አንድነትን መፍጠር እንደሚጠበቅባቸው አመላክተዋል።

ባለፉት ጊዜያት በሌማት ትሩፋት፣ በኮሪደር ልማትና በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብሮች የተከናወኑ ተግበራትን በጥራትና በፍጥነት ከመከወን አንጻር የታዩ ክፍተቶች እንዳይደገሙ የጋራ ግንዛቤ መያዙን ተናግረዋል።

በተለይ ክልሉ በሚታወቅባቸው ቡና፣ ሻይ፣ ቅመማ-ቅመምና ማር እንዲሁም የተለያዩ ማዕድናትን በአግባቡ በመጠቀም ከተረጂነት ወደ ሀብት ለሚደረገው ጉዞ የአመራሩ ቁርጠኝነት ወሳኝ ነው ብለዋል።

ክልሉ በእንስሳት ሃብት በእንሰትና ሌሎችም በርካታ ዘርፎች ያለዉን እምቅ ሃብት በአግባቡ ያላሳየ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የካፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አጣፉ ሃይሌ ናቸዉ።

ከዚህ ቀደም ወጥ ባልሆነ አሰራር ሲሰሩ የነበሩ ተግበራትን በማስተካከል በቀጣይ 3 ዓመታት በተለያዩ ዘርፎች ለዉጦችን ለማስመዝገብ ወደ ተግባር ገብተናል ያሉት አቶ አጥናፉ በተለይ እንደ ሃገር ትልቅ ሃብት የሚያስገኙ የግብርና ምርቶችን አዉጥቶ ለማሳየት መስራት ይጠበቃል ብለዋል።

የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሃብታሙ ካፍትን ከዚህ ቀደም በመደበኛ ስራ ሲከወኑ በቆዩና ልዩ ትኩረት ባልተሰጣቸው ጉዳዮች ዙርያ በክልሉ ሃሳብ አመንጪነት ይህ ዉይይት መደረጉ ትልቅ ለውጥ ይዞ የሚመጣ ይሆናል ብለዋል።

ከዚህ በተለየ በቀጣይ 3 አመታት የተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ከሌብነት እና ብልሹ አሰራር የጸዳ እንዲሆን ክትትል ማድረግ፣ ህገ-ወጥ ንግድን መቆጣጠር፣ ከህዝቡ የሚነሱ ቅሬታዎች በአፋጣኝ ምላሽ እንዲያገኙ በየደረጃው ቅሬታ የሚፈታበትን አሰራር ማጠናከር የሚያስፈልግ መሆኑ በመድረኩ አጽንኦት ተሰጥቶበታል።

በመድረኩ የክልሉ ርዕሰ-መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ፣ የክልሉ አስፈጻሚ አካላት፣ የዞኖችና የከተማ አስተዳደሮች የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል ሰል የቦንጋ ኤፍ ኤም 97.4 ዘግቧል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

07 Feb, 15:57


ልዩ መለያ ኮድ (QR Cod) የተካተተበት የደረሰኝ ህትመት ጥያቄ የማቅረቢያ ቀነ ገደብ እስከ የካቲት 30 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ እንዲራዘም ተወሰነ

ልዩ መለያ ኮድ (QR Cod) የተካተተበት የደረሰኝ ህትመት ጥያቄ ያለበት ደረጃ ላይ በበይነ መረብ ውይይት ተካሂዷል።

የገቢዎች ቢሮ ምክትል ኃላፊና የደንበኞች አገልግሎት የግብር አወሳሰንና አሰባሰብ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ወንዱ ታደሰ እንዳሉት በክልሉ ከዚህ ቀደም የደረሰኝ ህትመት ጥያቄ ማቅረብ የሚቻለው እስከ ጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም ብቻ መሆኑ በተገለጸው መሰረት ቁጥራቸው 1,568 (22%) የሆኑ ግብር ከፋዮች የህትመት ጥያቄ ማቅረብ መቻላቸውን ገልፀው

በዛሬው ዕለት የደረሰኝ ጥያቄ አፈፃፀም ዙሪያ ከገቢዎች ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሤ በተመራው እና ሁሉም የክልልና ከተማ አስተዳደር ገቢዎች የተሳተፋበት የበይነ መረብ ውይይት መደረጉን ገልፀዋል፡፡

በበይነ መረብ ውይይቱም በተለያዩ ምክንያቶች የህትመት ጥያቄያቸውን ያላቀረቡ ግብር ከፋዮች መኖራቸውና ይህን ታሳቢ በማድረግ የህትመት ጥያቄ ማቅረቢያ ቀነ ገደብ እስከ የካቲት 30 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ እንዲራዘም በውይይቱ መወሰኑን አቶ ወንዱ ታደሠ ገልፀዋል፡፡

ህገ-ወጥነትን እና የታክስ ማጨበርበር ወንጀሎችን ከመከላክል አንፃር የደረሰኝ አጠቃቀም እና አስተዳደር ሥርዓታንን በልዩ መለያ ኮድ (QR Cod) የተደገፈ እንዲሆን ማደረጉ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው የገለፁት አቶ ወንዱ ታደሠ

በተጨመረው ጊዜ ግብር ከፋዩ መለያ ኮድ (QR Cod) የተካተተበትን ደረሠኝ ማሳተም እንዳለበት የገለፁት ምክትል ቢሮ ኃላፊው ከየተካቲት 30/2017 ዓ.ም በኋላ ነባሩን ደረሠኝ መጠቀም አስተዳደራዊና ህጋዊ ተጠያቂነት የሚያስከትል መሆኑን ገልፀዋል ሲል የዘገበው የገቢዎች ቢሮ ኮሙኒኬሽን ነው።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

07 Feb, 13:40


በክልሉ ለጤና ልማት ሥራዎች ትኩረት በመስጠት የሚታዩ መሠረታዊ ችግሮችን በማረም የማህበረሰቡን ጤና ማስጠበቅ ይገባናል ሲሉ ዶ/ር ነጋሽ ዋጌሾ ተናገሩ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ ከኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት የሚዛን አማን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር የ2017 በጀት ዓመት ክልላዊ ማህበረሰብ ዓቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት'' የጤና መድህን አገልግሎት ለጋራ ተጠቃሚነት'' በሚል መሪ ቃል የንቅናቄ መድረክ በቦንጋ ከተማ አካሂደዋል።

በመድረኩ የ2017 በጀት ዓመት የማህበረሰብ ዓቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት የእስካሁን አፈጻጸምና ማቀጣጠያ ንቅናቄ ሰነድ ቀርበው ውይይት ተደርጓል።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ በመድረኩ እንደገለጹት፤በክልሉ ለጤና ልማት ሥራዎች ትኩረት በመስጠት የሚታዩ መሠረታዊ ችግሮችን በማረም የማህበረሰቡን ጤና ማስጠበቅ ይጠበቅብናል።

በተለይም በሆስፒታሎች እና ጤና ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት ማሻሻልና ማዘመን፣ የመድኃኒት አቅርቦት ችግር መቅረፍ፣የውስጥ መገልገያ ቁሳቁሶችን በማሟላት ከህዝብ የሚነሱ ቅሬታዎችን መፍታት ቅድሚያ የሚሰጡ ጉዳዮች እንደሆናቸውም ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ጠቁመዋል።

በክልሉ በጤና መድህን አገልግሎት የታየውን ዝቅተኛ አፈጻጸም ማረም እንዲያስችል ንቅናቄውን ወደታች ማውረድና የጋራ ውይይት መድረኮችን በመፍጠር ረገድ የዞን፣የከተማ አስተዳደር እና የወረዳ አስተዳዳሪዎች ሚናቸውን እንዲወጡ ርዕሰ መስተዳደሩ አሳስበዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው የጤና መድህን አገልግሎት ለማህበረሰብ ጤና እና ለጤና ዘርፍ ስኬት የሚያስገኘው ጠቀሜታ የጎላ በመሆኑ ግንዛቤ ማስጨበጫ ፣የደሃ ደሃ ማህበረሰብ ክፍሎችን ልየታ እንዲሁም ሁሉም ጤና ተቋማት የጤና መድህን ህክምና አገልግሎት እንዲሰጡ ማስቻል ይገባል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ወርቁ በክልሉ የጤና መድህን አገልግሎት አፈጻጸም ከነበረበት ደረጃ ከፍ እንዲል አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።

የጤና አመራሩና ባለሙያው ለጤናው ዘርፍ ልዩ ትኩረት እንዲሰጥ የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ተማም አሳስበዋል ።

በጤና ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ጥራት ማሻሻል፣የመድሃኒት አቅርቦት ችግር ለመፍታት ይሰራል ያሉት የቢሮ ኃላፊው፤ የ2017 አዳዲስ አባላት ማፍራት ፣ነባር ዕድሳት፣ ዕዳዎችን መክፈል መዋጮ አሰባሰብ እንዲሁም ሀብት አሰባሰብ ሥራዎች በተያዘው ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ሁሉም መረባረብ እንደሚገባዉ ኃላፊዉ ተናግረዋል።

የሀብት አሰባሰብና ሌሎች ሥራዎች በትኩረት እንዲመሩ አቅጣጫ ተቀምጦ በቀጣይ 1 ወራት የሚከናወኑ ተግባራት ላይ ርዕሰ መስተዳደሩ ከዞን ዋና አስተዳዳሪዎች ጋር ተፈራርመዉ መድረኩ ተጠናቋል።

በፍቅር ከበደ

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

07 Feb, 13:06


በብልጽግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባዔ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን ገቢራዊ በማድረግ የክልሉን ህዝብ ዘላቂ የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል።አቶ ማስረሻ በላቸው

የብልጽግና ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው ሁለተኛውን የብልጽግና ፓርቲ ጉባኤ ተከትሎ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን ተፈጻሚ ከማድረግና የህዝቡን የልማት ፍላጎት ከግብ ለማድረስ የተያዘውን ቁርጠኝነት አስመልክቶ ከሚዲያዎች ጋር ቆይታ አድርጓል።

በቆይታቸዉ የብዝሃ ዘርፍ ኢኮኖሚ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚተገበሩም አብራርተዋል ።

በብልጽግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባዔ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን ገቢራዊ በማድረግ የክልሉን ህዝብ ዘላቂ የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራልም ብለዋል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው በአንደኛው የብልጽግና ጉባዔ የተቀመጡ አቅጣጫዎች ሀገርን ያሻገሩና ከመበታተን ወደ አንድነት የሰበሰቡ በርካታ ለውጦች የተገኙባቸው መሆናቸውን አንስተዋል።

በዚህም ሀገራችን ኢትዮጵያ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ትክክለኛ መንገድ ላይ ስለመሆኗም አመላካች መሆኑንም አቶ ማስረሻ ተናግረዋል ።

በአንደኛው የብልጽግና ጉባኤ የተወሰኑ ውሳኔዎች በድል መሳካት መቻላቸው በሁለተኛው ጉባኤ ቀርቦ ስለመገምገሙም አቶ ማስረሻ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ተናግረዋል ።

በሁለተኛው የብልጽግና ጉባኤ ስምንት አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል ያሉት አቶ ማስረሻ ከእነዚህም አቅጣጫዎች ሀገራችንን በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ተሻለ ከፍታ ለማድረስ የሚያስችል ነው ብለዋል።

እነዚህን አቅጣጫዎች ከግብ ለማድረስም ቁርጠኝነት የታከለበት ከአመራር እስከ ህብረተሰቡ በሕብረ ብሔራዊነት ትርክት ማከናወን ይጠበቃል ብለዋል።

ኢኮኖሚውን ለማስፈንጠር በግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ የጉባኤውን ውሳኔ ተግባራዊ በማድረግ ውጤታማ ስኬቶች ተገኝተዋል ሲሉም በመግለጫው አክለዋል።

በሁለተኛው የብልጽግና ጉባኤ የተቀመጡ አንኳር አቅጣጫዎችን ተከትሎም ፈጠራና ፍጥነት የታከለበት ተግባር በመከወን ኢኮኖሚውን ለማስፈንጠር ብዝሃ _ኢኮኖሚ ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባልም ብለዋል።

በዚህም ረገድ በኢንዱስትሪው ፣በግብርና፣በማዕድን ፣በቱሪዝም ፣ በድጂታል ኢኮኖሚውና በሌሎች መስኮች የተጀመሩ ዕድገቶችን የማስቀጠል ስራ ትኩረት ተሰጥቶት ይሰራልም ብለዋል።

በእዚህ ዘርፎች ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እንደሚሰራም አቶ ማስረሻ ተናግረዋል ።

የየዘርፉ ምርትና ምርታማነት ሲያድግ የሀገሪቱ የማክሮ ኢኮኖሚ ግብ እንዲሳካ ማድረግ ይጠበቅብናል ብለዋል።

የማክሮ ኢኮኖሚ ግቦችን ለማሳካት የተረጋጋ ማክሮ ኢኮኖሚ እንዲኖር ማድረግ ያስፈልጋል፣ዘላቂ የልማት ፋይናንስ በሀገሪቱ ትኩረት ተደርጎ ቀጣይነት ባለው መልኩ ይተገበራል ሲሉም ተናግረዋል ።

የመጀመሪያው ጉባኤ ውሳኔዎችን ተከትሎ ባሳለፍነው 3 ዓመታት ቀጣይነት ያለው 7.2 ከመቶ ዕድገት መመዝገቡንና በቀጣይም እስከ ጉባኤ ድረስ በአማካይ 8.4 ከመቶ ዕድገት ለማስመዝገብ በትኩረት ይሰራልም ብለዋል።

ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርምን የማስቀጠል ስራ ተጠናክሮ ይሰራልም ብለዋል።

እንደሀገር የተጀማመሩ ሜጋ ፕሮጀክቶችን እና በየአካባቢው የተጀመሩየልማት ውጥኖች ውጤታማ እንዲሆኑ ይሰራል ።

ከዚህም ባሻገር የመንግስት ወጪን በመቀነስም ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ሀብት አሟጦ የመጠቀም ስራም ይሰራል ብለዋል።

ኢኮኖሚውን ለማሳደግም ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት የመተካት ስራ በስፋት እንደሚሰራም አቶ ማስረሻ ተናግረዋል ።

ለውጭ ንግድ የሚቀርቡ ምርቶችን በጥራት፣በስፋት የማምረት ስራው ተጠናክሮ እንደሚሰራበትም አቶ ማስረሻ ተናግረዋል ።

ቀጠናዊ ትብብርን በማስፋት ጠንካራ የፊሲካል ፖሊሲን በመተግበር የኑሮ ውድነትንና የዋጋ ግሽበትን ለማርገብ ምርትና ምርታማነትን የማሳደግ፣የሀገር ውስጥና የውጭ ጫናዎችን የመቀነስ፣የበጀት ጉድለት ከ3ከመቶ በላይ እንዳይሆን ትኩረት ተሰጥቶት ይሰራልም ብለዋል በመግለጫቸው ።

ባለፉት ጊዜያት ገቢን የማሳደግ ስራዎች ትኩረት ተሰጥቷቸው መሰራታቸውን የገለጹት አቶ ማስረሻ በታክስ ገቢ 24 ከመቶ፣ታክስ ባልሆኑ ገቢዎች 28 በመቶ ማደጉንና ምርትና ምርታማነት ተጣጥሞ እንዲያድ የማድረጉ ስራ ትኩረት እንደሚሰጠውም ተናግረዋል ።

ባለፉት 3 ዓመታት ከ9.1 ሚሊዮን በላይ የዜጎች የስራ ዕድል ተጠቃሚነት የተረጋገጠበት መሆኑንና ይህንንም የማስቀጠሉ ስራ እንደሚጠናከር ገልጸዋል ።

እንደ ሀገር በግብርናው ዘርፍ ባለፉት 3 ዓመታት 6.5 በመቶ ዕድገት መመዝገቡንና ከ1.2 ቢሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱንም እንዲሁ ገልጸዋል ።

እንደሀገር በስንዴ ምርት ከአንደኛው ጉባኤ በፊት 1.3 ሚሊየን ኩንታል ምርት የነበረው አሁን ላይ ከጉባኤው በፊት 107 ሚሊዮን ኩንታል ማድረስ ተችሏል ያሉት አቶ ማስረሻ በቀጣይም 2017 መጨረሻ ላይ 207 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማግኘት በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
ከዚህም ረገድ አሲዳማ መሬቶችን በኖራ የማከም፣የመካናይዜሽን እርሻን የማጠናከር ፣የግብርና ስራዎችን ባህል የማድረግ ተግባር ትኩረት ይሰጠዋል ብለዋል።

ኢንዱስትሪውን ዘርፍ ከማነቃቃት አንጻር በምግብ ራስን ከመቻል አልፎ ለኢንዱስትሪ ደጋፊ ምርት ማምረት፣ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ስራዎች ፣ለአካባቢ ተስማሚ የሆኑ የኢንዱስትሪ መሠረተ ልማት ዝርጋታ፣በቂ የፋይናንስ አቅርቦት ማመቻቸት፣የእርስ በርስ ትስስርን የማጠናከር ስራዎች ትኩረት ይሰጣቸዋል ብለዋል።

በኢኮኖሚው ዘርፍ መዋቅራዊ ለውጥ በሚያመጡ እንደ ቱሪዝምና የቱሪዝም አገልግሎት አሰጣጡን የማዘመን፣ድጂታል ኢኮኖሚውን የማሳደግ የመሠሰተ ልማት አውታሮችን በጥራት፣በቅልጥፍናና በፍትሐዊነት የማከናወን ተግባር ይጠናከራል ሲሉም ገልጸዋል።

የከተማና የገጠር ኮሪደር ስራዎች ለብልጽግና ምሳሌ በሚሆን መልኩ ተጠናክረው ተግባራዊ ይደረጋል ብለዋል።

እንደክልል ከሀገራዊ ኢኒሼቮች በተጨማሪ በክልሉ አዳዲስ ኢኒሼቲቮች ተግባራዊ እንደሚደረጉም አቶ ማስረሻ ተናግረዋል ።

የሌማት ትሩፋት፣የበጋ መስኖ ልማት ስራዎች የኮሪደር ልማት ስራዎችን ተከትሎም በቡና ልማት፣በሻይ ልማት፣ በሩዝ ምርት፣በማር ምርታማነት፣በፍራፍሬ ልማት በተለይም በአቮካዶ ምርታማነት፣በቅመማ ቅመም በተለይም ኮረሪማ ምርታማነት ላይ ትኩረት ተደርጎ እንደሚሰራ አክለዋል ።

በታጠቅ አበበ

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

07 Feb, 12:00


በተቀናጀና በተሟላ የግብርና ፓኬጅ ምርታማነትን ለማሳደግ እየሰራሁ ነው፦ ኮርፖሬሽኑ

ግብርናውን በተቀናጀና በተሟላ ፓኬጅ ተግባራዊ በማድረግ ምርታማነትን በማሳደግ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ እየሰራ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ገለፃ።

የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ክፍሌ ወ/ማርያም በቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና የሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል ተገኝተው ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ከአስር ዓመቱ መሪ የግብርና እቅድ መነሻ የግብርና ግብዓት አግልግሎት አቅርቦት ተደራሽነት ለማስፋፋት በመላው ሀገሪቱ ዘርፍ ብዙ እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን የጠቆሙት የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ-አፈጻሚ አቶ ክፍሌ የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና የሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከልም በደቡብ ምዕራብ ቀጠና ለሚገኙ አከባቢዎች ትልቅ ዕድል ይዞ የመጣ መሆኑን ተናግረዋል።

ኮርፖሬሽኑ በቦንጋ ከተማ በ743 ሚሊዮን ብር፣ በ2.5 ሄኪታር መሬት ላይ ያስገነባው የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና የሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል በውስጡ ባለ አራት ወለል የአስተዳደር ህንጻ፣ በአመት ከ150ሺህ ኩንታል በላይ ዘር ማዘጋጀት የሚያስችል ዘመናዊ የዘር ማበጠሪያ ማሽን፣ የግብርና ግብዓት ማከማቻ መጋዘኖች፣ የእርሻ መሳሪያዎችና ቴክኖሎጂ ማሳያ እንዲሁም ዘመናዊ የዘር ቁጥጥር ላብራቶሪን ያካተተ መሆኑን ነው አቶ ክፍሌ ያስረዱት።

ኮርፖሬሽኑ አለምአቀፍ የጥራት መመዘኛዎችን ያሟሉ ምርጥ ዘሮችን በማምራት ለሀገር ውስጥና ለአለም ገበያ ለማቅረብ ከማሳ ዝግጅት እስከ ጎተራ የተሟላ የጥራት ቁጥጥርና ክትትል ስርዓት እንዳለው የገለጹት ኃላፊው ማዕከሉ በቀጠናው ምርታማነቱ የተረጋገጠ ዘር ለአርሶና ከፍል አርብቶአደሮች በተመጣጣኝ እንደሚያቀርብ ተናግረዋል።

የኮርፖሬሽኑ ማዕከል በዋናነት ለደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፣ ከፍል ኦሮሚያና ጋምቤላ ክልሎች ተደራሽ በመሆን የተሟላ የዘርና ግብርና ግብዓት አቅርቦት፤ የአፈር ማዳበሪያና ፀረ ተባይ ኬሚካል አቅርቦት፤ የእንሳሳት መድኃኒት አቅርቦት፣ የተፈጥሮና ኬሚካል ማዳበሪያ እንዲሁም የእርሻ የሜካናይዜሽን አግልግሎት የሚሰጥ መሆኑን ነው የገለጹት።

የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የመሬት ዝግጅት እና የምርጥ ዘር አጠቃቀም እንዲሁም የተሟላ የግብርና ግብዓት አቅርቦት ከማሳለጥ ባሻገር አጠቃላይ የስነ እርሻ ዘዴ ለማሻሻል ማዕከሉ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ነው አቶ ክፈሌ የገለጹት።

ማዕከሉ በቀጠናው በስፋት የሚመረተውን የበቆሎ ምርት በአጭር ጊዜ ከማሳ እስከ ጎተራ የሚሰበሰብ የእርሻ ቴክኖሎጂ በክራይ ለተጠቃሚዎች እንደሚያቀርብ የገለጹት አቶ ክፍሌ ይህም የአርሶአደሩን ጊዜና ጉልበት ከቀነሰ ባሻገር የምርት ብክነት በእጅጉ የሚቀንስ አዲስ ቴክኖሎጂ መሆኑን ተናግረዋል።

ግብርናን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በማዕከሉ በሽያጭ ለሚቀርቡ ከቀላል እስከ ውስብስብ የእርሻ ቴክኖሎጂዎች የባለሙያ ስልጠና፣ የመለዋወጫ አቅርቦት እንዲሁም አጠቃላይ የድህረ ሽያጭ የተሟላ አግልግሎት የሚሰጥበት መሆኑን ጨምረው ተናግረዋል።

ማዕከሉ ከማሳ ዝግጅት እስከ ምርት ብዝዬት በሚያደርገው ረዥም የእሴት ሰንሰለት ሂዴት ለበርካታ የአከባቢው ወጣቶች በቋሚነትና በጊዚያዊነት የሥራ ዕድል የሚፈጠርም መሆኑ ነው የገለጹት።

የመንግሥት የልማት ድርጅት የኾነው ኮርፖሬሽኑ የአፈር ማዳበሪያን በብቸኝነት በሀገሪቱ እያቀረበ እንደሚገኝ የገለጹት ስራ አስፈፃሚው መንግሥት እንደሀገር ግብርናን ለማዘመን ያቀደውን ተልዕኮ በማሳካት ረገድ ኮርፖሬሽኑ ከፍተኛ ሚና ያለው መሆኑን አስረድተዋል።

የቦንጋ ማዕከል ግንባታው የተጠናቀቀ በመሆኑ በቅርቡ ተመርቆ የተሟላ አግልግሎት መስጠት እንደሚጀመርም ስራ አስፈፃሚው ጨምረው ገልጸዋል።

በዕድገቱ በዛብህ

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

07 Feb, 10:00


በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ ቤንዚን ለቁጠባ በሚል ከሞተር ሲቀንስ በተነሳ የእሳት አደጋ በሁለት ሰዎች ላይ ጉዳት አደረሰ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በዳውሮ ዞን የታርጫ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኢንስፔክተር ሙሉጌታ መንግስቱ ለክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮምንኬሽን ዳይሬክቶሬት እንደገለፁት በከተማ አስተዳደሩ ቦዲ ቀበሌ ጥር 28 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 2፡00 ሰዓት በቤንዝል አማካኝነት በተነሳ እሳት በሰውና በንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱን የገለፁት፡፡

የእሳት ቃጠሎ መንስኤ ፖሊስ ባደረገው ማጣራት ተጎጂው አስናቀ አበራ በቦክሰር ሞተር ከማደያ የቀዳውን 14 ሊትር ቤንዝል ወደ መኖሪያ ቤት ከወሰደ በኃላ ለቁጠባ በሚል ምሽቱን ከሞተሩ ታንከር እየቀነሰ ባለበት ለብርሃን ተብሎ ከተለኮሰው ሻማ ቤንዝሉን በመሳቡ ምክንያት በአንድ ወንድ እና በአንዲት ሴት ላይ ከፍተኛ የቃጠሎ ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን በቆርቆሮ መኖሪያ ቤት ከነሙሉ ቁሳቁሱ እና ሞተሩ ጋር መውደሙን ገልፀዋል፡፡

በእሳቱ ቃጠሎ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸውን ሁለቱ ግለሰቦች ለህክምና ወደ ታርጫ ሆስፒታል ተወስደዉ ህክምና እየተደረገላቸው መሆኑን አዛዡ አስረድተው በንብረት ላይ የደረሰው የጉዳት መጠንና የቃጠሎው ምክንያት እየተጣራ መሆኑን ጠቁመዋል።

አንዳንድ ግለሰቦች ቤንዝልን ለቁጠባ በሚል እየቀነሱ ማስቀመጥ እና በህገወጥ መንገድ ለሽያጭ የሚያስቀምጡ በመኖራቸው በራሳቸውና በጎሪቤቶቻቻው ለዘመናት ያፈሩትን ሀብት ንብረታቸውን የሚያወድም በመሆኑ ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ነዳጅ በህገወጥ መንገድ መኖሪያ ቤት ማስቀመጥ እንደሌለባቸው ነንግድ ስራ ላይ ተሰማርተው የሚገኙ አካላትን ጥቆማ መስጠት እንደሚገባቸው አዛዡ ጥሪያቸውን አቅርቧል ሲል የክልሉ ፖሊስ ኮምሽን ህዝብ ግንኙነትና ኮምንከሽን በዘገባው አመላክቷል፡፡

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

07 Feb, 09:59


ከጥንቃቄ ጉድለት ከመኖሪያ ቤት የተነሳ እሳት በንብረትና ላይ ጉዳት ማድረሱን በካፋ ዞን የአዲዮ ወረዳ ፖሊስ ገለፀ፡፡

በካፋ ዞን አዲዮ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ዋና ሳጅን ሀብታሙ አለማየሁ ለክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት እንደገለፁት በወረዳው ከሊሰ ቀበሌ ልዩ ስፍራው ማርና ተብሎ በሚጠራበት ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 3፡00 ሰዓት ከመኖሪያ ቤት በተነሳ እሳት በንብረት ላይ ቃጠሎ መድረሱ ተናግረዋል፡፡

የእሳት ቃጠሎ ግለሰቦቹ ምሽቱን በእሳት ምግብ እያበሰሉ ጎረቤት ቡና ለመጠጣት በሄዱበት እሳቱ መነሳቱን ፖሊስ ማረጋገጡን የገለፁት አዛዡ በቃጠሎውም አንድ የሳር ኪዳን መኖሪያ ቤት፤ 5 የቀንድ ከብቶች፤ዶሮዎች፤2 ኩንታል በቆሎ እና የቤት ቁሳቁሶች ሙሉ በመሉ መውደማቸውን አስረድተዋል፡፡

በእሳቱ በሰው ላይ ጉዳት አለማድረሱን እና እሳቱ ወደ ሌሎች አከባቢዎች ሳይዛመት የመንደሩ ነዋሪዎች ማጥፋታቸውን የገለፁት ዋና ሳጅን ሀብታሙ ወቅቱ በጋና ነፋሻማ በመሆኑ የእሳት ቃጠሎ በቀላሉ ሊከሰት ስለሚችል ህብረተሰቡ ተቀጣጣይ ነገሮችን ከእሳት አከባቢ በማራቅና እሳትን ለተለያዩ አገልግሎቶች ከተጠቀመ በኃላ በውሃ ማጥፋት እንደሚገባቸው አሳስበዋል፡፡

በተመሳሳይ የእሳት ቃጠሎ በኮንታ ዞን አመያ ከተማ አስተዳደር ጨታ ቀጭቀጫ ቀበሌ ዲዛ በሚጠራበት መንደር ጥር 28 ቀን 2017 ዓ.ም ከሌሊቱ 10፡00 ሰዓት ከአንድ ግለሰብ መኖሪያ የሳር ኪዳን መኖሪያ ቤት በተነሳ እሳት 40 ኩንታል ጤፍ፤በቤቱ ዙሪያ የነበሩ የተለያዩ የጓሮ አትክልቶች በቃጠሎው መውደማቸውን ታውቋል፡፡

በሸካ ዞን የኪ ወረዳ ፊዴ ቀበሌ ጥር 27 ቀን 20917 ዓ.ም ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት ከየአንድ ግለሰብ የሳር ኪዳን ማዕድ ቤት በተነሳ እሳት የተለያዩ ቅሳቁሶች መውደማቸውን በሰዉ የደረሰ ጉዳት አለመኖሩን ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል መረጃ ኢንተለጀንስ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

ህብረተሰቡ መሰል የእሳት ቃጠሎዎች እንዳይከሰት አስፈለጊውን ጥንቀቄ እንድናደርግ ፖሊስ ጥሪውን ያቀርባል ሲል የክልሉ ፖሊስ ኮምሽን ዘግቧል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

18 Jan, 16:11


በጀሙ ከተማ የከተራ በዓል በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።

በምዕራብ ኦሞ ዞን በጀሙ ከተማ የከተራ በዓል በድምቀት እየተከበረ ይገኛል ሲል የዞኑ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ዘግቧል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab           
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

18 Jan, 15:55


የጥምቀት ከተራ በዓል በኮንታ ዞን አመያ ከተማ አስተዳደር በልዩ ልዩ ሀይማኖታዊ ሥርዓቶች እየተከበረ ይገኛል ሲል የኮንታ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ዘግቧል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

18 Jan, 15:55


በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ የከተራ በዓል በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።

ታቦታትም ከመንበረ-ክብራቸው በካህናት፣ በሊቃውንት እና በምዕመናን በዝማሬ ታጅበው ወደ ባህረ ጥምቀቱ ስፍራ በመጓዝ ላይ ይገኛሉ ያለው የዞኑ መንግስት ኮሙኒኬሽን ነው።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

18 Jan, 15:54


በሸካ ዞን የጥምቀት ከተራ በዓል በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት የሚከበረው የጥምቀት ከተራ በዓል በዞኑ ሁሉም አካባቢዎች በድምቀት መከበር ጀምሯል።

የእምነቱ ተከታይ በሆኑ ምዕመናን እና ሌሎች አካላት በመታጀብ ታቦታቱ ከማደሪያ ስፍራቸው በመውጣት ወደ ጥምቀተ ባህር እያመሩ ይገኛሉ።

የሸካ ዞን ዋና ከተማና የክልሉ ብዝሃ ማዕከል በሆነችው ቴፒ ከተማ ታቦታቱ ከየአቅጣጫው ታጅበው በድምቀት ወደ ጥምቀተ ባህር እያመሩ ሲሆን በአንድራቻ ወረዳ ጌጫ ከተማና ማሻ ከተማ ላይም በተመሳሳይ ወደ ጥምቀተ ባህሩ እያመሩ ናቸው።

በሌሎችም የዞኑ ወረዳዎችም ታቦታቱ ወደ ጥምቀተ ባህሩ የሚገኙ ሲሆን በነገው ዕለትም የጥምቀት በዓል በድምቀት ይከበራል ተብሎ ይጠበቃል ሲል የዘገበው የዞኑ መንግስት ኮሙኒኬሽን ነው።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

18 Jan, 15:53


ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

ጥምቀት ኢትዮጵያ ለዓለም ያበረከተችው የአደባባይ የወል በዓል ነው። በዓሉ ከሃይማኖታዊ በዓልነት ባሻገር የሚታይ ለዓለም በማይዳሰስ ቅርስነት የተበረከተ ሀብታችን ነው፡፡ የበዓሉ መሠረት ሃይማኖታዊ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን ደግሞ ሃይማኖታዊ መሠረቱን እንደያዘ ባህላዊ እሴት እንዲኖረዉ ጭምር አድርገውታል፡፡ በዓሉ በየዓመቱ ሲከበር ከክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች ባሻገር መላው ሕዝብ የሚታደምበት የዐደባባይ የወል በዓል ተደርጓል፡፡ ኢትዮጵያ ለዓለም ሕዝብ ያበረከተችው የማይዳሰስ ቅርስ ኾኖ መመዝገቡም ለዚህ ማሳያ ነው፡፡

የጥምቀት በዓል ከሌሎች የሃይማኖታዊ በዓላት ለየት የሚያደርገዉ በሃይማኖት ተቋማት ቅጥረ ግቢ ወይም በቤት ውስጥ ብቻ የሚከወን አለመኾኑና ደስታን ለአጠቃላይ ማኅበረሰቡ ማጋራቱ ነው፡፡ በሃይማኖታዊ እና ባህላዊ አልባሳት ያጌጡ ምዕመናንና ታዳሚዎች በጋራ የሚያከብሩት ድንቅ በዓል ነው፡፡
በዓሉ ከሃይማኖታዊ ሥነ ሥርዐት፣ መዝሙሮች እና ባህላዊ ጭፈራዎች ባሻገር የገና ጨዋታ እና የፈረስ ግልቢያ መሰል ኹነቶች የሚያደምቁት ነው፡፡ ይህንን ትውፊቱን የጠበቀ በዓል ጎብኝዎች ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች ለመታደም ዐቅደዉ ይመጣሉ፤ የኢትዮጵያን መልካም ገጽታ፣ የሕዝቧን አብሮነት እና እንግዳ ተቀባይነት ተመልክተዉበትም ይመለሳሉ፡፡

በዚህ በዓል ላይ የወጣቶች ተሳትፎ እና ሚና በእጅጉ ልቆ ይታያል፡፡ ታቦታቱን ከከተራ እስከ ቃና ዘገሊላ ድረስ በዝማሬ እና ጭፈራ ያጅባሉ፤ የታቦታቱን መንገድ ይጠርጋሉ፤ ምንጣፎችን ያነጥፋሉ፤ ይሸከማሉ፤ በገና ጨዋታና ፈረስ ጉግስ ይሳፋሉ፡፡ ይህ ጠንካራ ማኅበራዊ እሴት እየዳበረ መጥቷል፡፡

የጥምቀትንም በዓል ስናከብር ጥንታዊ ሃይማኖታዊ፣ ባህላዊና ታሪካዊ ትውፊቱን ጠብቀን፤ የሃይማኖት አባቶች፣ ምዕመናን፣ ወጣቶች እና መላዉ ሕዝባችን የነበረ ሚናችንን እየተወጣን ሊኾን ይገባል፡፡ በዓሉ ደስታን የምንጋራበት የዐደባባይ በዓል ነውና ደስታችንን እየተጋራን ልናከብረው ይገባል፡፡

ለመላዉ የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች እና ለበዓሉ ታዳሚዎች በሙሉ እንኳን ለከተራ፣ ለጥምቀት እና ቃና ዘገሊላ በዓላት በሰላም አደረሳችሁ!

የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

18 Jan, 15:52


በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ የከተራ በዓል

#ደሬቴድ
ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

18 Jan, 15:46


የጥምቀት ከተራ በዓል በቦንጋ ከተማ በልዩ ልዩ ሀይማኖታዊ ሥርዓቶች እየተከበረ ነው።

የጥምቀት ከተራ በዓል በየዓመቱ በተለያዩ ሀይማታዊ እና ባህላዊ ሥርዓቶች በደምቀት እንደሚከበር ይታወቃል ፡፡

የጥምቀት ከተራ በዓል ታሪካዊና ሀይማኖታዊ ሥርዓቱን ተከትሎ ቦንጋን ጨምሮ በመላው ሀገሪቱ እየተከበረ ይገኛል።

የጥምቀት በዓል በየዓመቱ ከጥር 11 ጀምሮ የሚከበረው ኢየሱስ ክርስቶስ በአጥማቂው ቅዱስ ዮሐንስ እጅ በዮርዳኖስ ባህር የተጠመቀበትን ዕለት ለማስታወስ ተፈልጎ እንደሆነ ይነገራል ፡፡

የጥምቀት በዓል በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና አግኝተው በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትምህርት የሳይንስና የባህል ተቋም ዩኔስኮ የተመዘገበ የኢትዮጵያ ትልቁ ቅርስ ነው ፡፡
የጥምቀት በዓል በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ዘንድ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው በዓል ሲሆን በዓሉ የህዝቦችን አንድነትና አብሮነት የሚያጠናክር ከመሆኑም ባለፈ በዓለም ቅርስነት መመዝገቡ በቱሪዝም ዘርፍ የሀገሪቱን ኢኮኖሚሚ ከማሳደግ አንጻር ሚናው የጎላ ነው ፡፡

ይሄው የጥምቀት ከተራ በዓል በቦንጋና በዞኑ በሁሉም አካባቢዎች በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።

ዘገባው የካፋ ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው ።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

18 Jan, 12:52


ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ ለከተራና ጥምቀት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በደማቅ ሁኔታ ለሚከበረው የከተራና ጥምቀት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ሙሉ መልዕክታቸው እንደሚከተለው ቀርቧል፦

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ!

ጥምቀት፣ ከሰማየ ሰማያት ወረደ፣ በባሕር መካከልም ቆመ ብለን የምናከብረው በዓል ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ የሕዝቡን ችግር ለመፍታት ማድረግ ያለብንን አራት ነገሮች አስተምሮናል።

እነዚህም ወደ ሕዝቡ መውረድ፣ ራስን አሳልፎ መስጠት፣ ሕዝቡ የሚፈልገውን ብቻ ሳይሆን ለሕዝቡ የሚያስፈልገውን ማድረግ እና ዓላማን ብቻ መመልከት ናቸዉ።

አንደኛ የሕዝብን ችግር ለመፍታት ወደ ሕዝብ መውረድ ያስፈልጋል። የሕዝብን ፈተና በሪፖርት መስማት ሳይሆን ወርዶ ማየትና መቅመስ ያስፈልጋል። በየአካባቢው፣ በየፕሮጀክቱ፣ በየማኅበረሰቡ እየሄድን ለማየት የምንሞክረውም ለዚህ ነው።

ሁለተኛዉ የሕዝብን ችግር ለመፍታት ራስን አሳልፎ መስጠት ነዉ። በጎችን ለማዳን መፍትሔዉ በጎችን መሠዋት አይደለም። በጎችን ለመታደግ ራስን መሠዋት እንጂ። የሕዝብን ችግር ለመፍታት ጊዜን፣ ጉልበትን፣ ዕውቀትን፣ መሠዋት ያስፈልጋል። የዕረፍት ሰዓትን፣ የድካም ውጤትን መሠዋት። በመደመር መጽሐፍ ሽያጭ የሚሠሩ ፕሮጀክቶችም የዚህ ምሳሌዎች ናቸው።

ሶስተኛዉ በምንፈልገውና በሚያስፈልገን መካከል ብዙ ጊዜ ልዩነት አለ። የመንግሥት ዋና ተግባር በጥናት ተመሥርቶ፣ ዐቅሙን አደራጅቶ ለሕዝብ የሚያስፈልገውን መሥራት ነው።

እሥራኤል ክርስቶስ እንዲነግሥ ይፈልጉ ነበር። እርሱ ግን በከብቶች በረት ተወለደ። እንዲዋጋ ይፈልጉ ነበር። እርሱ ግን ሰላማዊ ሆኖ መጣ። የሚፈልጉትን ሳይሆን የሚያስፈልጋቸውን አደረገ።

ከልደት እስከ ጥምቀት፣ ከጥምቀት እስከ ስቅለት ብዙ ፈተናዎች አሉ። በኃይል፣ በማባበል፣ በማታለል፣ እንደ ወዳጅ በመቅረብ፣ በከንቱ ውዳሴ፣ ብዙ ፈተናዎች ቀርበዋል። ክርስቶስ ግን የሰውን ልጅ ማዳን ነበር ዓላማው። ከጽንሰት እስከ ዕርገት የፈጸማቸው ሥራዎች ሁሉ ዓላማቸው ድኅነት ነው።

አራተኛዉ ከግራ ከቀኝ፣ ከፊት ከኋላ ብዙ መጎተቻዎች አሉ። ብዙ ማሳሳቻዎች አሉ። ብዙ ማሰናከያዎች አሉ። ብዙ ማስፈራሪያዎች አሉ። ግን ከዓላማችን ዝንፍ አንልም። ዓላማችን ሕዝቡን ከድህነት ማውጣት ነው። ኢትዮጵያን ወደ ልዕልና ማድረስ ነው። ኢትዮጵያን ማበልጸግ ነው።

የዘንድሮውን የጥምቀት በዓል የምናከብረው እነዚህን ትምህርቶች እየወሰድን ነው።

መልካም በዓል ይሁንልን።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

18 Jan, 11:58


ኢትዮጵያ እና ኬኒያ ሽብርተኝነትን በጋራ መከላከል በሚችሉበት ሁኔታ ላይ መከሩ

የብሔራዊ መረጃ ደኅንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከኬኒያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ጋር በናይሮቢ ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም እንደ ሽብርተኝነትና የተደራጁ ወንጀሎች ያሉ የደኅንነት ችግሮች በአፍሪካ ቀንድ ውስጥ ባሉ ሀገራት መካከል መተባበርን እንደሚጠይቅ ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል፡፡

ለዚህም ኬንያ መረጋጋትን ለማምጣት ከአጋሮቿና ከሀገራት ጋር እንደምትሰራ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ አረጋግጠዋል ሲል ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል፡፡

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

18 Jan, 11:43


ከተራና ጥምቀትን ስናከብር ትስስራችንን በሚያጠናክር ተግባር መሆን አለበት- ምክር ቤቱ

የከተራና እና ጥምቀት በዓላትን ስናከብር ማህበራዊ ትስስራችንንና አብሮነታችንን በሚያጠናክሩ ተግባራትን ሊሆን ይገባል ሲል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስገነዘበ፡፡

ምክር ቤቱ ለከተራ እና ጥምቀት በዓላት የእንኳን አደረሳችሁ የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት አስተላልፏል፡፡

በመልዕክቱም የጥምቀት በዓልን ስናከብር ከሐይማኖታዊ በዓልነቱ ባለፋ ለማህበራዊ ኢኮኖሚ ልማት የሚያስገኘውን አበርክቶ በመገንዘብና ይህንኑ በማጠናከር ሊሆን ይገባል ብሏል፡፡

የመልዕክቱ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፡-

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሣችሁ! አደረሰን!

የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለከተራና ጥምቀት በዓል አደረሳችሁ ሲል የመልካም ምኞት መልዕክት አስተላልፏል።

የጥምቀት በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ትልቅ ሥፍራ የሚሰጠው በየዓመቱ በደማቅ አከባበር የሚከበር የአደባባይ በዓል ነው።

ሀገራችን በዩኔስኮ በቅርስነት ካስመዘገበቻቸው ከማይዳሰሱ ብሔራዊ ቅርሶች መካከል አንዱ የሆነው የጥምቀት በዓል ሐይማኖታዊ ሥርዓቱንና ትውፊቱን ጠብቆ መከበር ከጀመረ ረጅም ዘመናትን አስቆጥሯል።

ሕዝበ ክርስቲያን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በተለያዩ አልባሳትና ጌጣጌጦች አጊጠው ፣ አሸብርቀውና ደምቀው የተለያዩ ሐይማኖታዊ ሥርዓቶችን በመፈፀም ታቦታቱን በዕልልታና ጭብጨባ እያጀቡ የከተራና የጥምቀት በዓልን በደስታና በፍቅር ያሳልፉታል።

በዓሉ ከሐይማኖታዊ አምልኮተ ሥርዓቱ ባለፈ ለማህበራዊ ትስስርና ለአብሮነታችን መጠናከር ፣ ለገፅታ ግንባታና ለቱሪዝም ኢንዱስትሪው ዕድገት ያለው አበርክቶ እጅግ ከፍተኛ ነው።

ስለሆነም የጥምቀት በዓልን ስናከብር ከሐይማኖታዊ በዓልነቱ ባለፋ ለማህበራዊ ኢኮኖሚ ልማት የሚያስገኘውን አበርክቶ በመገንዘብና ይህንኑ በማጠናከር ሊሆን ይገባል።

የጥምቀት በዓል ፍቅር ሠላምና ትህትና የተገለጠበት እንደ መሆኑ የከተራና የጥምቀት በዓልን ስናከበር ኃይማኖታዊ አስተምህሮውን በጠበቀ፣ ማህበራዊ ትስስራችንንና አብሮነታችንን በሚያጠናክሩ ተግባራትን በማከናወን ፣ በፍቅር ፣ በሠላም፣ ለተቸገሩ ወገኖች ካለን በማካፈል፣ በመተሳሰብ ስሜትና ተግባራት ሊሆን ይገባል።

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሣችሁ ! አደረሰን!

መረጃው የኤፍ ኤም ሲ ነው።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

11 Jan, 18:34


#ቲከሻ_ቤንጊ

"ቲከሻ ቤንጊ" የሸኮ ህዝብ ዘመን መለወጫ በነገው እለት ማለትም ጥር 4 በአዲስ አበባ በሀገር ፍቅር ቲያትር አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ ይከበራል።

ቲከሻ ቤንጊ የአካባቢውን ምቹ የኢንቨስትመንት ሁኔታዎች ፣ስለማህበረሰቡ ቱባ ባህሎችና እሴቶች በዕሉ ክረምቱን አልፎ ወደ በጋ የመጣበትና ምርት ከተሰበሰበ በኃላ በጋራ የሚደረግ የምስጋናና የአዲስ አመት ማብሰሪያ በዓል መሆኑ የሸኮ ህዝብ ሰላም ወዳድ ፣ ከህዝቦች ጋር በጋራና በአብሮነት የመኖር እሴት ያለውና ከተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦች ጋር ተጋብቶና ተዋልዶ እየኖረ የሚገኝ ህዝብ መሆኑን ለዓለም ህዝቦች ለማሳየት በነገው እለት በአዲስ አበባ በሀገር ፍቅር ቲያትር አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ ይከበራል።

መረጃዉ የቤንች ሸኮ ዞን ኮሙኒኬሽን ነዉ።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

11 Jan, 18:33


የኢትዮጵያ መንግስት እና የሶማሊያ መንግስት ያወጡት የጋራ የአቋም መግለጫ
#PMOEthiopia

Southwest Communications

11 Jan, 16:41


የክልሉ የባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ሃላፊ አቶ ፋንታሁን ብላቴ የቤንች ብሄር ዘመን መለወጫና የምስጋና "ቢስት ባር" በዓል እንኳን ደረሳችሁ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ኃላፊው ዞኑ በተፈጥሮዊ ባህላዊ ታሪካዊና ሰው ሰራሽ ጸጋዎች የታደለ ውብ ምድር መሆኑን ጠቅሰው ለቱሪዝም ዘርፉ የላቀ አስተዋጽኦ የሚኖራቸው ዋሻዎች፣ ፏፏቴዎች፣ ትላልቅ ወንዞች ሀይቆች እንድሁም የአሬንጎዴ ሽፋኑ ምድርን እያረሰረሰ ዓመቱን ሙሉ የሚኖሩበት አካባቢ ነው ሲልም ገልጸዋል።

የቤንች ብሔር የዘመን መለወጫ "ቢስት ባር" ስከበር የብሔረሰቡን ቱባ ባህል መሰረት ያደረገ ሆነው ህብረ- ብሔራዊ አንድነትን ማዕከል በማድረግ ለወንድማማችነት እና እህትማማችነት ዕሴት ግንባታ ልዩ ቦታ በመስጠት ነው ሲሉም የበዓሉን ትልቅነት ገልፀዋል።

የብሔረሰቡ የዘመን መለወጫ ለምተው የቱሪስት መዳረሻ እንዲሆን ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንደምሰራም የቢሮ ኃላፊው ተናግረዋል።

በድጋሚ እንኳን ለቤንች ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ "ቢስት ባር" በሠላም አደረሳችሁ ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

መረጃው የባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ነው።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

11 Jan, 16:39


የሶማሊያ ፌደራል ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ ይፋዊ ጉብኝት ለማድረግ እንኳን ወደ ኢትዮዽያ መጡ እላለሁ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር)

Southwest Communications

11 Jan, 14:37


የጅማ - ጭዳ መንገድ ፕሮጀክት ወደ አስፋልት የማንጠፍ ምዕራፍ ተሸጋገረ

የኦሮሚያ እና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎችን የሚያገናኘው የጅማ - ጭዳ 80 ኪሎሜትር መንገድ ፕሮጀክት ወደ አስፋልት የማንጠፍ ምዕራፍ ተሸጋግሯል።

የመንገድ ፕሮጀክቱ በሁለቱ ክልሎች የሚገኙ ሦስት ወረዳዎችን የሚያስተሳስር ሲኾን፣ አሁን ላይ የ10 ኪሎሜትር የአስፋልት ንጣፍ ተከናውኖለታል።

በተጨማሪም የ14 ኪ.ሜ ሰብቤዝ፣ 11 ኪ.ሜ ቤዝኮርስ እና የ52 በመቶ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ሥራዎች ተሠርተዋል። እንዲሁም የአንድ ድልድይ ግንባታ በሂደት ላይ ይገኛል። አጠቃላይ አፈጻጸሙ 31 በመቶ ደርሷል።

የፕሮጀክቱን የተሻለ አፈጻጸም በተጠናከረ መልኩ ለማስቀጠል የሚያስችሉ በማሽነሪ፣ የሥልጡን ባለሞያ ቅጥር እና በግብአት በኩል በቂ ዝግጅት መደረጉን ቦታው ድረስ በተደረገ ቅኝት መመልከት ተችሏል።

ከዚህም ባሻገር ግንባታው የአካባቢውን ሥነ-ምኅዳር ባገናዘበ መልኩ የአካባቢ እና የማኅበራዊ ደኅንነት መርሆዎችን ተከትሎ በጥንቃቄ እየተከናወነ ይገኛል።

ቻይና ቲሲጁ ኢንጅነሪንግ ግንባታውን የሚያከናውን ሲኾን፣ ኪዮንግዶንግ ኢንጅነሪንግ፣ ኦሪየንታል ኮንሰልቲንግ እና ኮር ኮንሰልቲንግ የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን በጥምረት ይሠራሉ። ለግንባታው የተመደበው 2 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ወጪ በአፍሪካ የልማት ፈንድ እና በጃፓን ዓለም-አቀፍ የልማት ተራድዖ ድርጅት የፋይናንስ ድጋፍ ይሸፈናል።

መንገዱ ሲጠናቀቅ ቀድሞ ከጅማ ከተማ አንስቶ እስከ ጭዳ ከተማ ለመድረስ የሚወስደውን 4 ሰዓት የጉዞ ጊዜ ከአንድ ሰዓት ተኩል ባነሰ ጊዜ ለመግባት ያስችላል። የጅማ፣ ዴዶ፣ ሚቴሶ እና መሰል ከተሞች ትስስርን በማጠናከር ምርት በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማድረስ ያስችላል።

የጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ እና የሃላል ኬላ መዳረሻ እንደመኾኑም መንገዱን ለቱሪስቶች ምቹ በማድረግ ረገድ ጉልህ አስተዋጽዖ ያበረክታል ስል ኢመአ ዘግቧል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

11 Jan, 14:35


የሚዛን አማን ከተማ ከፊል ገጽታ!
የድሮን ምስል

Southwest Communications

11 Jan, 11:08


ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ የካድፕ አስቸኳይ ስብሰባ ላይ እየተሳተፉ ነው

ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በመሪዎች ደረጃ እየተካሄደ በሚገኘው የአፍሪካ ሁሉን አቀፍ የግብርና ልማት ፕሮግራም (ካድፕ) አስቸኳይ ስብሰባ ላይ እየተሳተፉ ይገኛሉ።

በስብሰባው ላይ የኡጋንዳ ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ፤ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋቂ ማህማት ጨምሮ የህብረቱ አመራሮች፣ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች፣ የግብርና ሚኒስትሮች፣ የልማት አጋሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፥ በአፍሪካ ህብረት እና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ሂሩት ዘመነ እና የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ኢትዮጵያን ወክለው በስብሰባው ላይ እየሳተፉ ይገኛል።

በስብሰባው የካድፕ ያለፉት 10 ዓመታት አፈጻጸም የሚገመገም ሲሆን፤ በፈረንጆቹ ከ2026 እስከ 2035 የሚተገበረው የካድፕ ስትራቴጂ እና የድርጊት መርሃ ግብር እንደሚጸድቅ ይጠበቃል።

ዘላቂ የምግብ ምርታማነት፣ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ የግብርናና ኢንዱስትሪ ልማት፣ ሁሉን አቀፍ የዜጎች ተጠቃሚነት፣ የማይበገር የምግብ ስርዓትን ግንባታ እና የመንግስትና የግሉ ዘርፍ አጋርነት ውይይት ከሚደረግባቸው ርዕሰ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ።

የመሪዎቹ ስብስባ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ዛሬ ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅም ኢዜአ ዘግቧል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

08 Jan, 08:31


የኢትዮጵያን ብልጽግና እውን ለማድረግ በለውጥ ሂደት ውስጥ አብሮ የሚዘምን የማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ባህል ይዘን መጓዝ ያስፈልጋል ፦ አቶ አልማው ዘውዴ

"ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ቃል ለዞን ፣ ወረዳና ከተማ አስተዳደር አጠቃላይ አመራር የምክክር መድረክ በሚዛን አማን እየተካሄደ ይገኛል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አልማው ዘውዴ በምክክር መድረኩ እንደተናገሩት ለውጥ ተፈጥሯዊና የማይቀር ሂደት መሆኑን ገልጸው ከለውጡ ባህል ጋር አብሮ መዘመን እና ራስን ማዘጋጀት ያስፈልጋል።

መደመር ትላንት ፣ ዛሬና ነገን አስታርቆ የሚጓዝ አስተሳሰብ መሆኑን ገልጸው መደመር የኢትዮጵያን ህልም በእውን እያረጋገጠ ነው ብለዋል። እንደ ሀገር የማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ባህልን ማዘመንና ስብራቶችን በመጠገን ወደ አዲስ ባህልና ሁለንተናዊ ብልጽግና ማሻገር ነው ብለዋል።

ብልጽግና ሰብአዊ ልዕልናን ማረጋጥ ፣ ኢኮኖሚያዊ ሉአላዊነትና አፍሪካዊት ሀያል ሀገር መገንባትን ቁልፍ ተግባር አድርጎ እየሰራበት ይገኛል ብለዋል። አለም ቀጣይነት ባለው የለውጥ ሂደት ናት ያሉት ኃላፊው ሀገራችንም አዲስ የፖለቲካ ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ልምምድና ትግበራ ውስጥ ትገኛለች ብለዋል።

ለውጡ ስኬታማ መሆን የሚችለውም ሀሳብን ወደ ተግባር መቀየር የሚችል የአስተሳሰብና የአመለካከት ለውጥ ሲኖር ነው ብለዋል። ገዥ ትርክትን ለማፅናት ሀገራዊ መግባባት ላይ ለመድረስ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን የገለጹት አቶ አልማው ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር ሀገር አቀፍ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል ብለዋል።

መድረኩ ቀጥሎ እየተካሄደ ሲሆን አቶ አልማው ዘውዴ ለምክክር መድረኩ ተሳታፊዎች ለውይይት መነሻ ሰነድ እያቀረቡ ይገኛሉ።

መረጃው የቤንች ሸኮ ዞን የመንግሰት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ነው።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

08 Jan, 07:07


የካፋ ገፀ በረከቶች

ምንጭ:-ካፋ ቴቪ

Southwest Communications

07 Jan, 18:55


የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማስተካከያ ተደረገ

በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማስተካከያ መደረጉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ሚኒስቴሩ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን በላከው መረጃ መሰረት÷ ከዛሬ ታኅሣሥ 29 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ተግባራዊ የሚሆነው የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ተወስኗል።

በዚሁ መሰረት አንድ ሊትር ቤንዚን 101.47 ብር፣ አንድ ሊትር ናፍጣ 98.98 ብር፣ አንድ ሊትር ኬሮሲን 98.98 ብር፣ አንድ ሊትር የአውሮፕላን ነዳጅ 109.56 ብር፣ አንድ ሊትር ከባድ ጥቁር ናፍጣ 105.97 ብር እንዲሁም አንድ ሊትር ቀላል ጥቁር ናፍጣ 108.30 ብር ሆኖ እንዲሸጥ መወሰኑን ሚኒስቴሩ አስታውቋል ሲል ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል።
ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

07 Jan, 15:27


"እንኳን ለ2017 ዓ.ም የቤንች ብሔር የዘመን መለወጫ "ቢስት ባር" በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን።

የቤንች ብሔር የዘምን መለወጫ “ቢስት ባር” ለረዥም አመታት ተቋርጦ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በእኛ ዘመን ትውልድ በተደረገው ፈጣን እርምጃ ታሪክ በሚያመሰግነው ልክ እጅግ በጣም በደመቀ ሁኔታ ማክበራችን የሚታወስ ነው።

የመጀመሪያው የቢስት ባር አከባበር የተገኘው ስኬት በቀጣይ የቤንች ብሔር በታቀደው ልክ ባህሉ ወጉና አኗኗሩ በአለም ደረጃ ጎልቶ እንዲታይ ትልቅ በርን ከፍቷል።

እንደሚታወቀው የቤንች ህዝብ በቀደምት አባቶቻችን የራሱን በዓል በተለያዩ ኩነቶች ሲያከብር የነበረ መሆኑን በተለያዩ ጊዚያት ስንገልፅና በጥናትም የተረጋገጠ መሆኑ ግልፅ ነው። በመሆኑም በታሪክ አጋጣሚ በእኛ ዘመን ትውልድ በመከበሩ ደግሞ የታሪኩ ባለቤትና አንድ እርምጃ የብሔሩን ባህል፤ ወግ፤ አኗኗር ከፍ ማድረግ የቻልንበት በዓል ነው ለዚህም የተሰማኝ ደሰታ ልገልፅ እወዳለሁ ነው።

በተለያዩ ጊዚያት እንደገለፅኩኝ የቤንች ህዝብ ሰላምን የሚወድ በመተባበርና ለውጥ መምጣት እንደሚችል የሚያምንና ከሀገሪቱ መላው ወንድም እህቱ ጋር በፍቅር በጋራ እየኖረና ቀጣይም የሚኖር ህዝብ መሆኑ የማይካድ ሀቅ ነው።

የቤንች ህዝብ ለልማት የሚተባበር የአባቶችን ምክር የሚሰማና የሚቀበል ባህሉን የሚያከብርና የሚጠብቅ ህዝብ መሆኑም ባለፉት ግዚያት ሲነገር መጥቷል።ሀገራችን ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ አመታት በሁሉም ዘርፍ በፈጣን እድገት ላይ መሆኗ
ይታወቃል በመሆኑም ለቤንች ህዝብ ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ እድሉም ጊዜውም አሁን መሆኑን በዚሁ አጋጣሚ ለመግለጽ እወዳለሁ።

ቢስት ባር ብዙ ወደፊት መውጣት የምንችልበት አጋጣሚ ተፈጥሯል በተለይ የቤንች ህዝብ የተረሳውን ታሪክና ማንነታችንን እንደገና ከፍ ለማድረግ ትልቅ አጋጣሚ ያገኘነብትና ታላላቅ የባህል እሴቶቻችንን ለሀገርና ለዓለም የምናስተዋውቅበት ጊዜ ነው።

ቢስት ባር ሰዎች ብቻ በአብሮነት የሚያከብሩት ሳይሆኑ ለቤት እንስሳትም ጭምር የሚተርፍ ቀልብን የሚስብ፤ ዓይን የሚማርክ በአስገራሚ ኩነት የታጀበ ልዪ በዓል። ይህ በዓል ለጋራ ደስታና ስኬት ሕፃናትን ጨምሮ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል የራሱን የሥራ ኃላፊነት የሚወጣበት የመደመር፤ የመረዳዳት፤ የመደጋገፍና የመቻቻል በዓል ነው።

በቀጣይም በ“ቢስት ባር” ቱሩፋቶች በአብሮነት፤ በመቻቻልና በፍቅር የበለጸገውን የቤንች ህዝብ የሰላም እና የአብሮት ተምሰሌትነት ለሀገሪቱ በጋራ በመጠቀም ከትላንት በተሻለ ቤተሰባዊ አንድነት እጅ ለእጅ ተያይዘን፤ ሁላችንም በጋራ የምንቋደሰውን ፈጣን ልማት ለማረጋገጥ እንረባረብ ስል ጥሪዬን አስተላልፋለሁ።

ዲጋም ቢስት ባርሸን ኑአስሽ የሪ ጋላታስማኬ"

አቶ ፀጋዬ ማሞ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

07 Jan, 11:11


ነባርና አዳዲስ የቱሪስት መዳረሻዎችን በማልማት ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ማሳደግ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ ነው- ሰላማዊት ካሳ

አዳዲስ የቱሪስት መዳረሻዎችን በማልማት እና ነባሮቹን ዓለም አቀፍ ደረጃ በማሳደግ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስትሯ ሰላማዊት ካሳ ገለጹ።

የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል የቱሪዝም ሚኒስትሯ ሰላማዊት ካሳ፤ የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ ብጹዓን ሊቃነ ጻጻሳትና የፌዴራልና የክልል የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና እንግዶች በተገኙበት በታሪካዊቷ የላሊበላ ከተማ ተከብሯል።

ሚኒስትሯ ሰላማዊት ካሳ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ላሊበላን መሰል ዓለምን ያስደመሙ የተፈጥሮና ታሪካዊ መስህቦች ባለቤት ናት።

በርካታ የቱሪስት መስህቦቿ በተባበሩት መንግስታት የሳይንስ፣ የትምህርትና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) መመዝገባቸውን ገልጸዋል።

መንግስት የቱሪስት መስህቦችን የማልማትና አዳዲሶችን የመገንባት ስራ እንዲሁም በዓላትና ባህላዊ ክዋኔዎች እሴታቸው ተጠብቆ እንዲከበሩና በስፋት እንዲተዋወቁ የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ስራዎች እያከናወነ ነው።

የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶችን የማብዛት፣ የቱሪዝም ኢንቨስትመንት ማስፋፋትና የውጪ ምንዛሪ ግኝትን ማሳደግ የሚያስችሉ በርካታ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም እንዲሁ።

ኢትዮጵያን የአፍሪካ ተመራጭ የሚያደርጉ ነባርና አዳዲስ የቱሪስት መዳረሻዎች ዓለም አቀፍ ደረጃ በጠበቀ መልኩ እየለሙ ነው ብለዋል።

አዳዲስ መደራሻዎችን በማስፋትና በማስተዋወቅ የማህበረቡ የዘርፉ ተጠቃሚነት ለማድረግ በስፋት እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።

አማራ ክልል የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት፣ የጎንደር አብያተ መንግስታት፣ የሰሜን ተራሮች፣ ጎርጎራ፣ የጣና ሃይቅ ደሴቶችና ገዳማትና ጢስ አባይ ፏፏቴና መሰል ድንቅ የቱሪስት መዳረሻዎች ባለቤት መሆኑን ጠቅሰዋል።

የቱሪስት መዳረሻዎቹ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳቸው የላቀ መሆኑን ጠቅሰው በተለይም የላሊበላ ኪነ ሕንፃዎች ያኔ ቀርቶ በዚህ ዘመን ለመገንባት የሚከብዱ እንደሆኑ ነው ያነሱት።

የላሊበላ መካነ ቅርስ መደረሻ ልማትና ቅርሱን ከነሙሉ ውበቱ ለቀጣይ ትውልድ ለማሻገር መንግስት ለቅርስ ጥበቃ ልማት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን አንስተዋል።

እስካሁንም በመካነ ቅርሱ የውስጥ ለውስጥ መንገዶችና ድልድዮች፣ የመታጠቢያ ቤት ግንባታዎች እንዲሁም አስጎብኚ ማህበራትን የሚደግፉ ስራዎች ተከናውነዋል ነው ያሉት ሲል ኢዜአ ዘግቧል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

07 Jan, 08:28


እንኳን ለቤንች ብሔር የዘመን መለወጫ "ቢስት ባር" በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን

Southwest Communications

07 Jan, 08:25


ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ ማዕድ አጋሩ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ ማዕድ አጋርተዋል፡፡

የማዕድ ማጋራት መርሐ-ግብሩ በብሔራዊ ቤተመንግሥት የተከናወነ ሲሆን÷ ከአዲስ አበባ ከተለያዩ ከፍለ ከተሞች የተውጣጡ አረጋውያንና አካል ጉዳተኞች ተሳትፈዋል፡፡

ከመርሐ-ግብሩ በኋላም የብሔራዊ ቤተ-መንግሥት ሙዚየምን መጎብኘታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያከናወኑት በጎ ተግባር ልዩ ደስታ እንደፈጠረላቸው በዚሁ ወቅትም የማዕድ ማጋራቱ ተሳታፊዎች ተናግረዋል፡፡

እርስ በርስ መደጋገፍ የኢትዮጵያውያን መገለጫና እሴት መሆኑን ጠቅሰው÷ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዓሉን ከአረጋውያን እና አቅመ ደካሞች ጋር ማሳለፋቸው ሁሉም በየአካባቢው ሊተገብረው ይገባል ብለዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለአቅመ ደካሞችና አረጋውያን በየጊዜው ማዕድ ከማጋራት በተጓዳኝ በልማት ስራዎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለሚያከናውኑት ስራም ምስጋና አቅርበዋል፡፡

በተለይ የልማት ስራዎች ለአካል ጉዳተኞች ምቹ እንዲሆኑ በማድረግ ረገድ መንግስት እያከናወነ ያለውን ስራም አድንቀዋል፡፡

የብሔራዊ ቤተመንግሥት ሙዚየምንም በመጎብኘታቸው መደሰታቸውን ገልጸው÷ ሙዚየሙ የያዛቸው ታሪካዊ ቅርሶች አጠቃላይ ገጽታ እጅግ ማራኪ መሆኑን አንስተዋል ሲል ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል፡፡

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

06 Jan, 14:03


መላዉ የክርስትና እምነት ተከታዮች፣
እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሠላም አደረሳችሁ! አደረሰን!

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች አንኳን ለዘንድሮው የገና በዓል በሠላም አደረሳችሁ ! አደረሰን! እያልኩ መልካም ምኞቴን ለመግለጽ እወዳለሁ።

የዘንድሮዉን የገና በዓል ስናከብር ከወትሮዉ በተለየ የአብሮነትንና የመቻቻልን መንፈስ ከፍ በማድረግ ሊሆን ይገባል፡፡

የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት የይቅርታ፣ የፍቅር እና የአንድነት ማዕድ እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ ይመሰክራል፤

በክርስትና አስተምህሮት ከኢየሱሰ ክርሰቶስ ልደት በፊት የነበረው ዘመን ለሰው ልጆች የጨለማ ዘመን ተደርጎ የሚወሰድ ሲሆን በክርስቶስ መወለድ የጨለማው ግርማ ተገፎ አዲስ የተስፋ ብርሃንን የተጎናፀፍንበት በመሆኑ በአዲስ ጉልበት ለበጎ ተግባርና ለተግባራችን ስኬታማነት የምንተጋበት በዓል ሊሆን ይገባል።

ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምድር ላይ ሰላምን፣ ፍቅርን እና ይቅርታን ለመዝራት እንዲሁም ትህትናን ለማስተማር አምላክ ሆኖ ሳለ ራሱን ዝቅ በማድረግ በከብቶች በረት ተወልዶ ያሳየንን ትህትና ልንማርና ልንተገብረው ይገባል።

የክርስቶስ መወለድ እውነት ገዢ ኃይል መሆኗን አስተምሮናል፤በምንኖርበት በዚህ ዓለም እውነትን በማስቀደም በእውነት መስራት፣በእውነት መደገፍ፤ በእውነት መቃወም እና ባጠቃላይ እውነትን መርሃችን ልናደርግ ይገባል።

በዓሉን ስናከብር የወንድማማችነትንና የእህትማማችነትን እሴቶች በማጠናከር ለህብረ-ብሔራዊ ሀገራዊ አንድነት ማበብ የበኩላችንን ለመወጣት ዝግጁነታችንን እያሳደግን መሆን አለበት፡፡

ከሚያለያዩን ጉዳዮች ይልቅ የሚያስተሳስሩን የጋራ እሴቶቻችን ጠንካራ መሆናቸውን በማስተዋል ለጋራ ራዕይ እና ዓላማ በጋራ ለመቆም ቃላችንን ማደስ ይኖርብናል።

በዞናችን በሁሉም አካባቢዎች የተጀማመሩ የልማት ስራዎቻችን ከግብ እንዲደርሱ በጋራ በመሳተፍ የራሳችንን አሻር የማኖር ኃላፊነት ልንወጣ ይገባል።

የህዝባችንን አንድነት እና ስኬታማ ጉዟችንን ለማደናቀፍ እኩይ ተግባራትን አንግበው የሚንቀሳቀሱ አካላትን ነቅተን በመመከት ለዘላቂ ሰላም፣ ለልማትና ለዲሞክራሲ ግንባታ መጠናከር የበኩላችንን ድርሻ እናበርክት።

በዓሉን ካለን ላይ ለተቸገሩ ወገኖቻችን በማካፈል ተደጋግፎ የመኖር እሴትን ከፍ የምናደርግበት እንዲሆን እየተመኘሁ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በዓሉ የሰላም፣የጤና፣የመተሳሰብ እና የብልፅግና እንዲሆን እመኛለሁ።

አቶ ታከለ ተስፉ የኮንታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ

መረጃው የኮንታ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

06 Jan, 11:36


የብሔረሰቦች ምክርቤት ዋና አፈጉባኤ የተከበሩ አቶ መኩ አኩ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

ዋና አፈጉባኤ መቱ አኩ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል ።

የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ለዓሉ ብርሃንን ያበሰረ ለሰው ልጆች ጨለማን የገፈፈ በልዩ ድምቀት የሚከበር መንፈሳዊ በዓል ነው ብለዋል።

በዓሉን ስናከብር ለሀገር ሰላም ፈጣሪን በመማጸን ፣የተቸገሩትን በኢትዮጵያዊነት የእንግዳ አቀባበል ካለን ላይ በማካፈል ሊሆን ይገባል ሲሉም ገልጸዋል።

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በዓሉ የሰላም፣የአብሮነትና የመተሳሰብ እንዲሆንም አፈጉባኤ መቱ አኩ ተመኝተዋል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

04 Jan, 11:17


በቤንች ሸኮ ዞን ሰሜን ቤንች ወረዳ በ17.8 ሚሊየን ብር በጀት የተሰሩ የመስኖና የአትክልትና ፍራፍሬ ግብይት ማዕከል ግንባታዎች ተመረቁ።

የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን ግንባታዎቹን መርቀው ከፍተዋል።

በቤንች ሸኮ ዞን ሰሜን ቤንች ወረዳ በስርዓተ ምግብ ማጠናከሪያ ፕሮግራም (FSRP) ፕሮግራም ከ17.8 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የቲሹ - ጎሪትና ማግ አነስተኛ መስኖና የቢርቃን የአትክልትና ፍራፍሬ ግብይት ማዕከል ተመርቀው ተከፍተዋል።

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን ፕሮጀክቶቹን መርቀው ሲከፍቱ እንደተናገሩት አጋር ድርጅቶችና ፕሮጀክቶች የመንገስት የልማት ክፍተትና የህዝቡን ጥያቄዎች ቀርቦ በመፍታት ረገድ ሚናቸውን እየተወጡ ነው ብለዋል። በተለይም የስርዓተ ምግብ ማጠናከሪያ ፕሮጀክት (FSRP) የአርሶ አደሩን በመቀየር ረገድ ተግቶ እየሰራ የሚገኝ ባለውለታ ፕሮጀክት ነው ብለዋል።

እንደ ዞን ያለንን የገጸ ምድር ውሀ ሀብት አሟጦ በመጠቀምና በማልማት ረገድ ባለፉት አመታት በርካታ የመስኖ አውታሮችን በማልማት ወደ ስራ እየተገባ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም እንደ ሰሜን ቤንች አይነት ወረዳዎችን የአትክልትና ፍራፍሬ ማዕከል ለማድረግ ዞኑ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ፕሮጀክቶቹ ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ ባሻገር ለበርካታ ወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራ ማዕከል ይሆናሉ ብለዋል።

የሰሜን ቤንች ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ስንታየሁ በፍቃዱ እንደተናገሩት በዛሬው ዕለት የተመረቁ ፕሮጀክቶች አርሶ አደሩን ከዝናብ ጥገኝነት በማላቀቅ በአመት ሁለቴና ከዚያ በላይ ማምረት የሚያስችል ነው ብለዋል። የገበያ ማዕከሉም አትክልትና ፍራፍሬን ዘመናዊ በሆነ መልኩ ግብይት ለመፈጸም የሚረዳ ነው ብለዋል።

የዞኑ ግብርና ፣ አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን ጉብላ እንደተናገሩት ዞኑ ክረምት ከበጋ በሚፈሱ ውሃዎች የታደለ ነው ብለዋል። ይህን ሀብት ወደ ልማት በማዋል ረገድ ባለፉት አመታት በመንግስትና በፕሮጀክቶች ድጋፍ 14 የመስኖ አውታሮች በስራ ላይ ይገኛሉ ብለዋል።

እንደዞን በተያዘው የምርት ዘመን በአንደኛና በሁለተኛ መስኖ ከ13ሺ ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው እስካሁን ከ7ሺ ሄክታር መሬት በመስኖ እየለማ መሆኑን ገልጸዋል።

የሰሜን ቤንች ወረዳ የስርዓተ ምግብ ማጠናከሪያ ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ብዙአብ ደመላሽ እንደገለጹት የቲሹ- ጎሪትና ማግ አነስተኛ መስኖ በፕሮጀክቱ ከ5.6 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ተደርጎ የተገነባ መሆኑን ገልጸዋል። መስኖው ከ20 ሄክታር በላይ መሬት ማልማት የሚችል ፣ 78 አባወራና ከ368 በላይ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል። ግንባታውም በሲሳይ ጥላሁን ጠቅላላ የውሀ ተቋራጭ የተገነባ መሆኑን ጠቁመዋል።

አቶ ብዙአብ አክለውም በፕሮጀክቱ በ12.3 ሚሊየን ብር የተገነባውና ዛሬ የተመረቀው የቢርቃን የአትክልትና ፍራፍሬ ግብይት ማዕከል እንደ ወረዳ የተያዘውን የግብርና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የሚያሳካና ለበርካታ ስራ አጥ ወጣቶች የስራ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።

መረጃዉ የቤንች ሸኮ ኮሙኒኬሽን ጉዳዪች ጽ/ቤት ነዉ

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

04 Jan, 10:50


መንግሥት የርዕደ መሬቱ ማዕከል ከሆኑ አካባቢዎች ነዋሪዎችን የማራቅ ሥራ እያከናወነ ነው - የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

መንግሥት የርዕደ መሬቱ ማዕከል ከሆኑ አካባቢዎች ነዋሪዎችን የማራቅ ሥራ እያከናወነ መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታውቋል፡፡

አገልግሎቱ መንግሥት የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቶቹን በዘርፉ ባለሙያዎች በቅርበት በመከታተል ላይ መሆኑንም አስታውቋል፡፡

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ጉዳዩን አስመልክቶ ያወጣው ወቅታዊ መረጃ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይቀርባል፡፡

በአፋር፣ ኦሮሚያ እና አማራ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች ማዕከላቸውን አድርገው የተለያየ መጠን ያላቸው የርዕደ መሬት ክስተቶች በተደጋጋሚ መከሰታቸው ይታወቃል።

ክስተቶቹ ከጊዜ ወደ ጊዜ በመጠን እና በድግግሞሽ እያደጉ ይገኛሉ። በተለይም በዚህ ሳምንት በርዕደ መሬት መለኪያ እስከ 5.8 ሬክተር ስኬል የተመዘገበ መንቀጥቀጥ መከሰቱን መረጃዎች ያሳያሉ።

መንግሥት ክስተቶቹን በዘርፉ ባለሙያዎች በቅርብ እየተከታተለ ደገኛል። በተጨማሪም በተለይ የርዕደ መሬቱ ማዕከል (epicenter) የሆኑት አካባቢዎችን በመለየት በ12 ቀበሌዎች ላይ መንግሥት ከተለያዩ የሙያ ዘርፎች የተውጣጡ የአደጋ ጊዜ ሠራተኞችን በቦታው በማሰማራት የጉዳቱን መጠን አሰሳ እያደረገ ይገኛል።

በእነዚህ ቀበሌዎች ከሚኖሩ 80 ሺህ ዜጎች ቅድሚያ የሚሰጣቸውን በመለየት ነዋሪዎችን ከአካባቢው በማራቅ ለማስፈር ከፍተኛ ርብርብ እያደረገ ነው፡፡

በተጨማሪም ርዕደቱ በማኅበራዊ አግልግሎት ሰጭ ተቋማት፣ በኢኮኖሚ ተቋማት እና በመሠረተ ልማት ላይ ሊኖረው የሚችለውን ተጽዕኖ በመከታተል ላይ ነው፡፡

እስካሁን ባለው ሁኔታ በዋና ዋና ከተሞች የጎላ ተጽዕኖ ያላደረሰ ቢሆንም ዜጎች በባለሙያዎች የሚሰጡ የጥንቃቄ መልዕክቶችን እንዲከታተሉ እና በጥብቅ እንዲተገብሩ ለማሳሰብ እንወዳስን።

በቀጣይም ጉዳዩን በቅርበት በመከታተል አስፈላጊ መረጃዎችን በሚመለከታቸው ተቋማት አማካኝነት የሚያደርስ መሆኑን መንግሥት ያስታውቃል።

በኢፌዲሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

ታኀሣሥ 26 ቀን 2017

Southwest Communications

04 Jan, 10:48


ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የጄቱር መኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካን ጎበኙ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጂግጂጋ ከተማ የሚገኘውን የጄቱር መኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካን ጎብኝተዋል።

በቀን አስር መኪናዎች መገጣጠም የሚችለው ፋብሪካ በ22 ሺህ ስኩዌር ሜትር ስፋት ላይ ያረፈ መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ አመልክቷል ሲል ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

03 Jan, 10:23


ከሁለት አመታት ወዲህ በጎዴ እየተካሄደ ያለው ለውጥ አበረታች ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

ከሁለት አመታት ወዲህ በጎዴ እየተካሄደ ያለው ለውጥ አበረታች ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ከሁለት አመታት በፊት ወደ ጎዴ መጥቼ ነበር። ከዚያ ወዲህ እየተካሄደ ያለው ለውጥ አበረታች ነው ብለዋል።

በጽኑ ሃሳብ ማተኮር ያለብን በልማት ላይ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይኽ መንገድ ለእድሎች በር የሚከፍት፣ የሕይወት ደረጃን የሚያሻሽልና ማኅበረሰብን የሚያሻግር ጎዳና ነው ሲሉም ገልጸዋል።

በምዕራብ ጎዴ የመስኖ ፕሮጀክት በተለየ ደስታ ተስምቶኛል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአንድ ወቅት ገላጣ የነበረው በረሃማ መሬት በመስኖ አሁን ታርሶ በተስፋ ሰጪ አቅም የሰሊጥ፣ ስንዴ፣ በቆሎ አዝርዕት ምርት እና በተለያዩ የፍራፍሬ ምርቶች የተሞላ ስፍራ ሆኗል ሲሉም ነው የገለጹት።

ኢዜአ

Southwest Communications

03 Jan, 10:09


የገና በዓል በሰላም እንዲከበር አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጎ ስምሪት መደረጉን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።

በመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በየአመቱ በድምቀት ከሚከበሩት በዓላት መካከል የገና በዓል የፊታችን ማክሰኞ ታህሳስ 29 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚከበር ያመለከቱት የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሚንኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ በአሉ በሁሉም የክልሉ አከባቢዎች በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ፖሊስ በቂ ዝግጅት አድርጎ ወደስራ መገባቱን ለመገናኛ ብዙሃን ባሰራጩት መግለጫ አመልክተዋል፡፡

በቀጣይነት የሚከበሩትን የጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል፤ የከተራ እና የጥምቀት በዓላት በሰላም ተጀምረው በሰላም እንዲጠናቀቁ ፖሊስ በሁሉም ዞኖች፤ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን እና በየደረጃው የሚገኙ የፖሊስ መዋቅሮች ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ስምሪት ተሰጥቷቸዉ ስራ መጀመራቸውን ተናግረዋል፡፡

ህገወጦች የበዓላት ወቅት እንደምቹ አጋጣሚ በመጠቀም የሀሰተኛ የገንዘብ ዝውውርን በስፋት ወደገበያ ስለሚያሰራጩ ህብረተሰቡ በግብይት ወቅት ባለሁለት መቶ ብሮችን ሲሠጥም ሆነ ሲቀበል በጥንቃቄ መገበያያት እንዳለበት ገልፀዋል።

በተመሳሳይ በበዓላት ጊዜ የተሰረቁ የእርድ እንስሳት ለገበያ የሚቀርቡ በመሆናቸው ሸማቾች የእንስሳቱን ትክክለኝነት አጣርተው መግዛት እንደሚገባቸው እና ባዕድ ነገር የተቀላቀለባቸው ቅቤ፤ማር፤ እና በርበሬ ሊኖር ስለሚችል ህብረተሰቡ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ መክረዋል።

በዓላትን ተከትሎ የትራንስፖርት ፍሰት ከፍተኛ በመሆኑ ሰዉ ሰራሽ የትራንስፖር እጥረት እንዳይኖር ከሚመለከታቸዉ የትራንስፖርትና መንገድ መምሪያዎች ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

የትራፊክ አደጋን ለመከላከል የትራፊክ ፖሊስ በተመረጦ ቦታዎች የመንገድ ላይ ቁጥጥር እና ክትትል እንደሚደረግ ያመለከቱት ኢንስፔክተር ደጀኔ አሽከርካሪዎች ፍጥነታቸዉን ቀንሰዉ በጥንቃቄ በማሽከርከር ራሳቸውን እና ሌሎችን ከትራፊክ አደጋ ተጠብቀው ማሽርከር እንደሚገባቸው ጨምረው አሳስበዋል፡፡

በክልሉ በየትኛውም አካባቢ አጠራጣሪ ነገሮች ሲጋጥሙ ህብረተሰቡ በየአቅራቢያው በሚገኙ ፖሊስ ጣቢያዎች በግንባር በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥሮች 👉በክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የመረጃ ስልክ 047-331-25-04
👉ካፋ ዞን ፖሊስ 047_331_00_65
👉 ቤንች ሸኮ ዞን ፖሊስ 047_335_00_95
👉ምዕራብ ኦሞ ዞን ፖሊስ 047 _452_75_73
👉ዳዉሮ ዞን ፖሊስ 046_345_04_31
👉ሸካ ዞን ፖሊስ 047_556_08_36
👉ኮንታ ዞን ፖሊስ 047_227_00_11 ስልክ መስመሮችን መጠቀም የሚችል መሆኑን የክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

በመጨረሻም ህብረተሰቡ ለፀጥታ ስራው ስኬታማነት እያደረገ ላለው ቀና ትብብር የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን በመላው የፀጥታ አካለት ስም ምስጋናውን እያቀረበ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በዓሉ የሰላምና የደስታ እንዲሆንላቸው መልካም ምኞቱን ገልጿል ሲል የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ያደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡

Southwest Communications

03 Jan, 07:40


ኢትዮጵያ የ2025 የብሪክስ ፕሬዚደንትነት ለተረከበችው ብራዚል የእንኳን ደስ አለሽ መልእክት አስተላለፈች

ኢትዮጵያ የ2025 የብሪክስ ፕሬዚደንትነት ለተረከበችው ብራዚል የእንኳን ደስ አለሽ መልእክት አስተላልፋለች፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ብራዚል በብሪክስ ፕሬዚደንትነት ጊዜያዋ ፍትሃዊ፣ አካታች እና ውጤታማ የአለምአቀፍ አስተዳደርን ለማስቀጠል የሰነቀችውን ራዕይ እንደምትደግፍ አስታውቋል፡፡

ጠንካራ ኢኮኖሚያዊ ትስስርን ለመፍጠር እና የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ላይ በትብብር ለመስራት ኢትዮጵያ እንደምትሻም ገልጿል።

ኢትዮጵያ በ2025 የብሪክስ ፕሬዚደንትነትን ከተረከበችው ብራዚል ጋር በጋራ ለመስራት ፍላጎት እንዳላትም ሚኒስቴሩ ጠቅሷል፡፡

ሩሲያ በ2024 የብሪክስ ፕሬዚደንትነት ጊዜዋ ለሰጠችው አርአያነት ያለው አመራር ኢትዮጵያ አድናቆት እንዳላትም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጨምሮ ገልጿል ሲል ኢቢሲ ዘግቧል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

03 Jan, 06:50


የባንክ ስራ አዋጅ ኢትዮጵያ የፈረመችውን የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ለማሳለጥ የጎላ ሚና አለው

የውጭ ባንኮች እንዲሳተፉ የሚፈቅደው የባንክ ስራ አዋጅ ኢትዮጵያ የፈረመችውን የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ለማሳለጥና የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲዋን ለማጎልበት ጉልህ ድርሻ እንደሚኖረው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ባለሙያዎች ማህበር ከፍተኛ የምጣኔ ሀብት ተመራማሪ አቡሌ መሀሪ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡

የፋይናንስ ዘርፉን በእውቀትና በቴክኖሎጂ በመደገፍ ኢኮኖሚው ከዓለም ገበያ ጋር ያለውን ትስስር ለማሳደግ መንግስት ዘርፈ ብዙ ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡

ይህን ተከትሎ የዘርፉን ተወዳዳሪነት በማሳደግ በቂ የፋይናንስ አቅርቦት እንዲኖር ለማስቻል ያለመ የባንክ ስራ አዋጅ ጸድቆ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል።

በዚህም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ታህሳስ 8 ቀን 2017 ዓ.ም ባካሄደው 11ኛ መደበኛ ስብሰባ የውጭ ባንኮች በኢትዮጵያ እንዲሳተፉ የሚፈቅደውን የባንክ ሥራ አዋጅ ቁጥር 1360/2017 አጽድቋል፡፡

አዋጁ የባንክ ዘርፉ ለውጭ ባንኮች ክፍት የሚሆንበትን ስርዓት የዘረጋ ነው።

የውጭ ባንኮች እና አልሚዎች በፋይናንስ ዘርፉ ሲሰማሩ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ቀጣይነት ያለው እድገት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማበርከት ያስችላቸዋል፡፡

በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ባለሙያዎች ማህበር ከፍተኛ ተመራማሪ አቡሌ መሀሪ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ የውጭ ባንኮች ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ መፈቀዱ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ እድገት የሚያቀላጥፍ ነው፡፡

በኢትዮጵያ የውጭ ባንኮች እንዲሳተፉ ፈቃድ ሲያገኙ እውቀት፣ ቴክኖሎጂ እና ካፒታል ይዘው እንደሚመጡ የገለጹት የምጣኔ ሀብት ተመራማሪው፤ የባንክ አገልግሎት የማያገኘውን የህብረተሰብ ክፍል ተደራሽ ለማድረግ ያስችላል ብለዋል፡፡

በተጨማሪም ኢንቨስትመንትን በማስፋፋት ለሥራ እድል ፈጠራ እና ቴክኖሎጂ ሽግግር የጎላ አበርክቶ ይኖረዋል ነው ያሉት፡፡

ኢትዮጵያ የፈረመችውን የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና በማሳለጥ፣ ባንኮች ከመጡባቸው ሀገራት ጋር ያለውን የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ በማጠናከር ጠንካራ ኢኮኖሚ መፍጠር ያስችላል ብለዋል፡፡

የውጭ ባንኮች ፈቃድ ለሀገር ውስጥ ባንኮች ተስፋም ስጋትም መሆኑን የገለጹት ተመራማሪው፤ የበለጠ ትርፋማ ለመሆን የገጠሩን ማህበረሰብ በቴክኖሎጂ ተደራሽ ማድረግ ይገባቸዋል ብለዋል፡፡

የሀገር ውስጥ ባንኮች ቅድመ ዝግጅት በማድረግ የካፒታል ገበያ የፈጠረላቸውን እድል በመጠቀም አቅማቸውን ማጠናከር እንዳለባቸውም ነው የገለጹት ሲል ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

02 Jan, 18:58


ፓኪስታን የኢትዮጵያን የብልጽግና ጉዞ አደነቀች

በፓኪስታን የኢትዮጵያ አምባሳደር ጀማል በከር(ዶ/ር) ከፓኪስታን የፕላን፣ ልማት እና ልዩ ተነሳሽነት ሚኒስትር አህሳን ኢቅባል ጋር ተወያይተዋል፡፡

አምባሳደሩ በኢትዮጵያ ስለተመዘገበው የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ የውጭ ግንኙነትና የማህበራዊ ዘርፎች ዋና ዋና ማሻሻያዎች ለሚኒስትሩ አብራርተዋል።

መንግስት ጎረቤት ተኮር አብሮነት ላይ የተመሠረተ የሠላም ደሴት መፍጠር መቻሉን አምባሳደሩ መናገራቸውን ነው በፓኪስታን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን በላከው መግለጫ የተመላከተው፡፡

በኢትዮጵያ በመተግበር ላይ የሚገኘው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሐ-ግብር በሀገሪቱ ውስጥ የተደረጉ ማሻሻያዎች ውጤት እንደሆነም አንስተዋል፡፡

በሌላ በኩል ሚኒስትሩ አህሳን ኢቅባል ÷ኢትየጵያ በአፍሪካ ውስጥ ታላቅ የስኬት ምሣሌ መሆኗንና ብዝሃነት ባለው የኢኮኖሚ ፖሊሲዎች እንዲሁም በንቁ አመራር አማካኝነት ኢኮኖሚዋን መቀየሯን አንስተዋል፡፡

ኢትዮጵያ በለውጥ አመራሩ ሥር በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚና በማህበራዊ ዘርፎች ያጋጠሟትን ችግሮች በመፍታት ያስመዘገበችውን ከፍተኛ የብልፅግና ጉዞም አድንቀዋል።

በቀጣይም ሀገራቱ በልማትና በልዩ ልዩ ተነሣሽነቶች ላይ በትብብር ለመስራት ተስማምተዋል ሲል ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

01 Jan, 16:41


መከላከያ ሀገራዊ ተልዕኮውን ከመፈፀም ጎን ለጎን በልማቱም መስክ ሠፋፊ ስራዎችን እያከናወነ ነው - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ

የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በመከላከያ ተቋማት የኮሪደር ልማት አካል የሆኑ የመሰረተ ልማት ግንባታ ስራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡

በጉብኝታቸውም በመከላከያ ጠቅላይ መምሪያ ግቢ እና በሎጀስቲክስ ማእከሎች እየተሰሩ ያሉ የግንባታ ስራዎች እና ማዕከሎችን አረንጓዴ፣ ወብና ፅዱ የስራ አካባቢ ለማድረግ እተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎችን ተመልክተዋል፡፡

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ መከላከያ የሀገርን ሉአላዊነት ማስከበር ዜጎች በሰላም ወጥተው በሰላም እንዲገቡ ደህንነታቸው የተረጋገጠና ሰላማቸው የተጠበቀ እንዲሆን የተሰጠውን ሀገራዊ ተልዕኮ እየፈፀመ ከዚሁ ጎን ለጎን በልማቱም ረገድ እንደ ሀገር የተቀመጠውን አቅጣጫ ተከትሎ ዘርፈ ብዙ እና ሰፋፊ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች እና የልማት ስራዎች እያከናወነ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

ይህ ስራ በሀገር አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ርብርብ እየተተገበሩ ካሉት የኮሪደር ልማት ስራዎች አካል ሆኖ በተቀመጠው ዕቅድ መሰረት በጥራትና በፍጥነት እየተከናወነ እንደሆነ አረጋግጠው ቀሪው ስራ በአጭር ጊዜ ተጠናቆ ለተገነባበት አላማ እንዲውልም አሳስበዋል ሲል ኢቢሲ ዘግቧል፡፡

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

28 Dec, 18:02


የህብረተሰቡን የጤና አገልግሎት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በዞኑ እየተሰጠ ያለው አገልገሎት አበረታች መሆኑ ተገለፀ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊና በኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር የሱፐርቪዥን ቡድን የተመራ ልዑክ በኮንታ ዞን የአመያ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል እና የጪዳ ጤና ጣቢያ ስራ እንቅስቃሴ ምልከታ አድርገዋል።

የህብረተሰቡን የጤና አገልግሎት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በዞኑ እየተሰጠ ያለው አገልገሎት አበረታች መሆኑ ተገልጿል።

በምልከታው ላይ የተገኙት የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ተማም እንደተናገሩት በዞኑ በጤና ተቋማት ላይ ያለው የመረጃ አያያዝና አደረጃጀት ጥራት የሚበረታታ መሆኑን በመግለጽ የሚስተዋሉ ጥቃቅን ክፍተቶች በአፋጣኝ ልታረሙ ይገባል ብለዋል።

የዞኑ መንግስት ለጤናው ዘርፍ ከሰጠው ትኩረት መነሻ ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ያነሱት ኃላፊው በአካባቢው የሚስተዋለውን የወባ ወረርሽኝ ጫና ለመቀነስ የህ/ሰብ ተሳትፎ ማሳደግ ይገባል ብለዋል።

አያይዘውም ውሃ ያቆሩ ቦታዎችን ማፋሰስና ማዳፈን፣የአልጋ አጎበር አጠቃቀም፣ የአከባቢ ፅዳትና ሌሎች በወባ መከላከያ መንገዶች ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ልጠናከሩ እንደሚገባ ተናግርዋል።

የሆስፒታሉን ደረጃ ለማሻሻል የህክምና አገልግሎት መስጫ መሳሪያዎችን ከማሟላት በተጨማሪ የተለያዩ ስፔሻልስቶችን በመቅጠር ለህ/ሰቡ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት እየተሰራ እንደሚገኝ ያነሱት ደግሞ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታከለ ተስፉ ናቸው።

ዋና አስተዳዳሪው አያይዘውም የወባ ወረርሽኝ ጫና ባለባቸው መዋቅሮች ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልፀው ጉብኝቱ በዞኑ በጤናው ዘርፍ የሚታዩ ችግሮችን በመለየት አገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻል ላይ ያተኮረ በመሆኑ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባልም ብለዋል።

የሱፐርቪዥን ቡድን አባላት በበኩላቸው ምልከታ በተደረገባቸው ጤና ተቋማት በመረጃ አያያዝና በመድኃኒት ቁጥጥር ስርዓት ላይ ያሉ ጥንካሬዎች ሊበረታቱ እንደሚገባ ገልፀው ሌሎች ጥቃቅን ችግሮች አፋጣኝ መፍትሔ እንደሚያስፈልጋቸው አሳስበዋል።

በተደረገው ምልከታ ከሆስፒታል ጀምሮ እስከ ጤና ኬላ ያሉ ሰራተኞች ለሙያቸው ያለው ክብርና የስራ ተነሳሽነት አበረታች መሆኑን መታዘብ መቻላቸውን የተናገሩት የኢንስፔክሽን ቡድኑ አባላት ተነሳሽነቱን አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባልም ብለዋል።

በአካባቢው የተከሰተውን የወባ ወረርሽኝ ጫና ለመቆጣጠር የቅድመ መከላከል ስራዎች ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የተናገሩት የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ኡቴ አየለ ህመሙ ሲከሰት ፈጣን የህክምና አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑንም ጠቁመዋል።

በቤተሰብ ዕቅድ፣ በወላድ እናቶች እና ህፃናት ጤና አገልግሎትም ውጤታማ ስራ እየተሰራ መሆኑ የተመለከተ ሲሆን በየደረጃው ያሉ የህክምና ተቋማት አክሞ በማዳን ብቻ ሳይሆን ቀድሞ በመከላከሉ ረገድም ልዩ ትኩረት ሰጥተው ልሰሩ ይገባል ተብሏል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

28 Dec, 17:58


በሁሉም መስክ የሴቶችን ተሳታፊና ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ የሴቶች ልማት ህብረትን ብቁና ሞዴል ማድረግ እንደሚገባ ተገለጸ

የክልሉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዲይ ቢሮ አዲስ በተሻሻለው የሴቶች ልማት ህብረትን ሞዴል ለማድረግ ከቤንች ሸኮ ዞን የመዋቅሩ አመራሮች ጋር የንቅናቄ መድረክ በሚዛን አማን አካሂዷል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የሴቶች ዘርፍ ምክትል የቢሮ ኃላፊ ወይዘሪት ለምለም አምሳሉ የንቅናቄ መድረኩን ሰነድ ሲያቀርቡ እንደተናገሩት ቀደም ብሎ ሲሰራበት የቆየውን የሴቶች ልማት ቡድን አደረጃጀትና ስያሜን በመቀየር የሴቶች ልማት ህብረት በሚል ተሻሽሎ መቅረቡን ገልጸዋል።

እንደ ክልል 53ሺ 442 የ1ለ10 ፣ 17ሺ 186 የልማት ህብረቶች እንዲሁም 522ሺ 703 አባላት ትስስር መፍጠር ተችሏል ያሉት ኃላፊዋ አደረጃጀቱን ውጤታማ ፣ ወጥነት ያለውና እስከ ቀበሌ ድረስ ለማውረድ ከታህሳስ 10 እስከ መጋቢት 10 ለ3 ወራት የሚቆይ የንቅናቄ መድረክ በሁሉም ዞኖች ፣ ወረዳዎችና በተመረጡ ቀበሌዎች ንቅናቄው ይካሄዳል ብለዋል።

ከዚህ ቀደም በክልሉ በሚገኙ ሁሉም መዋቅሮች በሴቶች ልማት ህብረት አደረጃጀት ፣ አሰራርና የምዘና ሂደት ላይ ስልጠናዎች መሰጠታቸውን ገልጸው ሁሉም መዋቅሮች ከየወረዳው 3 ወደኀላ የቀሩ ቀበሌዎችን መርጦ ሪፖርት ማድረጉን ገልጸዋል። በቀጣይም ለተመረጡ ቀበሌዎች ድጋፍ ፣ ክትትል በማድረግና በማብቃት ሞዴል ለማድረግ ይሰራል ብለዋል።

ቀድሞ ሲሰራበት በነበረው የሴቶች ልማት ቡድን አደረጃጀት አንድ ወጥ የሆነ አደረጃጀት ፣ አሰራርና ስያሜ ያለመኖር ፣ ከአደረጃጀት ይልቅ በተናጠል ለመስራት መፈለግ በዋናነት የሚታዩ ችግሮች ነበሩ ያሉት ወይዘሪት ለምለም የአዲሱ የሴቶች ልማት ህብረት አላማው የተስተካከለ መዋቅራዊ አደረጃጀት እንዲኖር ፣ በጤና ፣ በትምህርት ፣ በግብርና ፣ በተፈጥሮ ሀብትና በጎልማሶች ትምህርት ውጤታማና ሞዴል አደረጃጀቶችን ለመፍጠር መሆኑን ገልጸዋል።

በመድረክ የተሳተፉ አካላት እንደተናገሩት የሴቶችን ሁሉ አቀፍ ተሳታፊና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ተቋማት የሴት አደረጃጀቶችን ማዕከል አድርገው ሊሰሩ ይገባል ብለዋል። የሴቶች ልማት ህብረትን እንደ አቅም ከመጠቀም ይልቅ በተናጥል የመስራት ሁኔታዎች ይታያሉ ያሉት አስተያየት ሰጪዎች በዚህም በዘርፉ አመርቂ ውጤት እየተመዘገበ አይደለም ብለዋል።

ሴቶች ያልተሳተፉበት የትኛውም ተግባር ግቡን ሊመታ አይችልም የሚሉት የመድረኩ ተሳታፊዎች በቀጣይም የሴቶች የልማት ህብረትን በመጠቀም በቅንጅት መስራት እንደሚገባም ጠቁመዋል።

የክልሉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የሴቶች ዘርፍ ምክትል የቢሮ ኃላፊ ወይዘሪት ለምለም አምሳሉ በመድረኩ ማጠቃለያ እንደተናገሩት ሴቶች በትምህርት ፣ በጤና ፣ በልማት ፣ በዲሞክራሲ ስርዓት ፣ በሰላም እሴት ግንባታ ሂደት ውስጥ ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ በቅንጅት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

በክልሉ በሴቶችና በማህበራዊ ጉዳይ ዘርፍ በርካታ ተግባራት መፈፀማቸውና ውጤቶች እየተገኙ መሆኑን ኃላፊዋ ጠቁመው ተግባራትን በሚዲያ ከማጀብ አንጻር ክፍተቶች እንዳሉ ገልጸዋል። በክልል ፣ በዞንና በወረዳ ደረጃ ስትሪንግ ኮሚቴዎችን ወደ ስራ ማስገባት በየወቅቱ ከዕቅድ ጀምሮ ተግባራት እየገመገሙና አቅጣጫ እየሰጡ መጓዝ ያስፈልጋል ማለታቸዉን የቤንች ሸኮ ዞን ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።

በመድረኩ ከዞኑ ከሁሉም መዋቅር የሴቶችና ህጻናት መዋቅር አመራሮች ፣ የኦሞ ባንክ አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው ተቋማት አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

28 Dec, 15:36


በለውጡ ዓመታት የተተገበሩ አካታች የፖለቲካ አካሄዶች አሰባሳቢ ትርክት ለመፍጠር ትልቅ ሚና አላቸው-የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ ቤልጅጌ (ዶ/ር)

Southwest Communications

28 Dec, 12:57


የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን ማድረግ የሚያስችል ነው

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው መሰረታዊ የኢኮኖሚ ለውጥ በማምጣት የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን ማድረግ የሚያስችል መሆኑን የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ገለጸ፡፡

የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት፣ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ባለሙያዎች ማህበር እና በጆሀንስበርግ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና በይነ አፍሪካ ንግድ ጥናት ማዕከል በጋራ ያዘጋጁት የግብዓት ማሰባሰቢያ መድረክ በአዲስ አበባ ተካሂዷል፡፡

መድረኩ በቀጣይ ጥር ወር በአዲስ አበባ በሚካሄደው ዓለም አቀፍ ኮንፍረንስ ላይ በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የዶላር ዋጋ በገበያው መወሰኑ ያመጣው ጥቅም፣በሂደት ያጋጠሙ ችግር እና መፍትሔ ለማቅረብ የማጠናከሪያ ሃሳብ ማሰባሰቢያ ነው፡፡

የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ተፈሪ ጥያሩ፤ ኢትዮጵያ በሀገራዊ ኢኮኖሚው ላይ መሰረታዊ ለውጥ የሚያመጣ የፖሊሲ ለውጥ ማድረጓ ተገቢና ወቅታዊ መሆኑን አንስተዋል።

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ወሳኝ ሚና የሚጫዎት መሆኑን ጠቅሰው፥በአጭር ጊዜ ችግር ዘላቂ ጥቅምን የሚያረጋግጥ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ላይ የሚደረጉ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ውይይቶችም ክፍተቶችን በመሙላት የማስተካከያ ርምጃዎች እንዲወሰዱ መክረ ሃሳብ ለማቅረብ ያግዛሉ ብለዋል፡፡

በመሆኑም የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው መሰረታዊ የኢኮኖሚ ለውጥ በማምጣት የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን ማድረግ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ባለሚያዎች ማህበር ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሃና፤የዶላር ዋጋ በገበያ እንዲተመን ከፍተኛ ምስቅልቅል ያጋጥማል ተብሎ የሚጠበቅ ቢሆንም በኢትዮጵያ ከታሰበውም በላይ የተረጋጋ ሁኔታ የታየበት ሆኗል ብለዋል፡፡

በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በትይዩ መደበኛ ገበያ መካከል ያለውን ልዩነት በማጥበብ፣የባንኮችን የመሸጫና የመግዣ ዋጋ በማቀራረብ አዎንታዊ ውጤት መመዝገቡን ጠቅሰዋል።

የህዝብን ተጠቃሚነት በዘላቂነት ማረጋገጥ እንዲችል እንደ ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ማህበር ያሉ ተቋማት በጥናት ላይ የተመሰረተ ምክረ ሃሳብ ማቅረብ እንዳለባቸውም አንስተዋል።

በጆሀንስበርግ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደርና በይነ አፍሪካ ንግድ ጥናት ማዕከል ዳይሬክተር ሰይፈ ታደለ (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያውያን አብሮነትና በትብብር የመሥራት ባህል ለቀጣናዊ ትስስር ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል፡፡

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ውጤታማ ለማድረግ የመሰረተ ልማት ዝርጋታና ጠንካራ ተቋም መፍጠር እንደሚገባ ገልጸው፥ ሀብትን፣ ጉልበትና ገንዘብን በማቀናጀት ሥራ መፍጠር ይገባልም ነው ያሉት ሲል ኢዜአ ዘግቧል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

28 Dec, 12:28


በህዳሴ ግድብ ዓሳ የማምረት ስራ በስፋት እየተከናወነ ነው

በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እና በሌሎችም የሀገሪቷ አካባቢዎች ዓሳ የማምረት ስራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) ገለጹ።

ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) እንዳሉት÷መንግስት ሀገሪቷ ጥራትና ብዛት ያላቸውን የዓሳ ምርቶች ማምረት የሚያስችላትን አቅም ለማሳደግ ፖሊሲዎች እና ስትራቴጂዎችን እንዲሁም አቅጣጫዎችን በማውጣት ወደ ተግባር ገብቶ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን በመስራት ላይ ይገኛል።

በመሆኑም በህዳሴ ግድብ እና በሌሎችም የሀገሪቷ አካባቢዎች ዓሳ የማምረት ስራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

የግብርና ሚኒስቴር በበጀት ዓመቱ 9 ነጥብ 2 ሚሊየን የዓሳ ጫጩቶችን በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ለማሰራጨት አቅዶ በስፋት እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።

በእስካሁኑ ሂደትም 4 ነጥብ 5 ሚሊየን የዓሳ ጫጩቶች ማሰራጨቱን ጠቅሰው፥በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

በዓሳ ልማት ዙሪያ በተለይም በታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ላይ በስፋት የማልማት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፥ ከሁለት ሳምንት በፊት 56 ቶን ዓሳ ማምረት ተችሏል ብለዋል።

በዘርፉ ልማት ለሚሰማሩ ሚኒስቴሩ አስፈላጊውን ድጋፍና እገዛ እንደሚያደርግ ገልጸው የዘርፉን ልማት ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ ከመንግስት ጥረት ባለፈ የባለሃብቶች ተሳትፎ እንዲጠናከር ጠይቀዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

28 Dec, 10:46


ለጋራ ዘላቂ ጥቅም ሲባል የባህር በር የማግኘት ጥረቱ የማይቀር ነው

ለኢትዮጵያም ሆነ ለቀጣናው ሀገራት ዘላቂ ጥቅም ሲባል የባህር በር የማግኘት ጥረቱ የማይቀር መሆኑን የታሪክ ምሁራን ገለጹ።

ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ በአንካራ ያደረጉት ስምምነት የቀጣናውን ሰላም ለማወክ የሚንቀሳቀሱ አካላትን ሴራ ያመከነ ሁነኛ መፍትሄ መሆኑንም ተናግረዋል።

የባህልና የታሪክ ተመራማሪው ፕሮፌሰር አህመድ ዘካርያ ለኢዜአ እንዳሉት፥ ሁለቱ ሀገራት ችግሮችን በሰላም ለመፍታት መስማማታቸው የሚደነቅና ለቀጣናው ሰላምና ልማት ወሳኝ ሚና ያለው ነው።

ኢትዮጵያ ለጎረቤቶቿ ቅድሚያ የሚሰጥ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ እንዳላት ጠቅሰው፥ ስምምነቱ ለቀጣናዊ ትብብር መጠናከር ያላትን ጉልህ ሚና የሚያጎለብት ነው ብለዋል።

የታሪክ ተመራማሪው ረዳት ፕሮፌሰር አደም ካሚል በበኩላቸው ኢትዮጵያ የእውነትና የፍትሕ ሀገር መሆኗን አንስተው፥ ብሔራዊ ጥቅሟን የምታስከብረው የሌሎችን ጥቅም በማይጎዳ መልኩ መሆኑን ገልጸዋል።

ከዚህም ባለፈ ለአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ድርጅቶች ምስረታና ለተልዕኮዎች መሳካት ያበረከተችው አስተዋፅኦ በታሪክ ከፍ ብሎ የተቀመጠ መሆኑን አውስተዋል።

በተለይም ለቀጣናዊና አህጉራዊ ሰላምና መረጋጋት የከፈለችው ዋጋ ማንም የማይተካው መሆኑንም ጠቅሰዋል።

ኢትዮጵያ እያደገ ያለውን የወጪና ገቢ ንግድ በአንድ ወደብ ብቻ ማሳለጥ ስለማትችል ብዙ ወደቦች እንደሚያስፈልጓት ፕሮፌሰር አህመድ ዘካርያ ተናግረዋል።

ሀገራዊ አቅሟን ማስተናገድ የሚያስችል የባህር በር ጥያቄ ማቅረቧ ተገቢ ከመሆኑም በላይ የሚሳካበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም ብለዋል።

ረዳት ፕሮፌሰር አደም ካሚል የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ለቀጣናው ሰላምና ልማት ያላትን ታሪካዊ ሚና ያገናዘበ ነው ይላሉ።

በመሆኑም ለኢትዮጵያና ለቀጣናው ዘላቂ ጥቅም ሲባል የባህር በር ማግኘታችን አየቀሬ ነው ብለዋል።

ሌሎች ሀገራትም የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የኢትዮጵያን ጥያቄ በአግባቡ ሊመልሱና በትብብር ሊሰሩ እንደሚገባ ተናግረዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

28 Dec, 10:42


በዞኑ ወባን ለመከላከል በተደረገ ርብርብ የበሽታውን ጫና መቀነስ የተቻለ ቢሆንም በመረጃ አያያዝና በመድሀኒት ቁጥጥር ስርዓት ላይ ያሉ መነቆዎች ልፈቱ እንደሚገባ ተገለፀ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ ሀላፊና በኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር የሱፐርቪዥን ቡድን የተመራ ልዑክ በሁለተኛ ቀን ጉብኝታቸው በዳውሮ ዞን የታርጫ አጠቃላይ ሆስፒታል፣ የታርጫ ጤና ታጣቢያ የስራ እንቅስቃሴና የግንባታ ሂደቱ በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘውን የዋካ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን ተመላክቷል።

የሱፐርቪዥን ቡድኑ በሁሉም የጤና መዋቅር እየተሰጠ ያለው የጤና አገለግሎት የተሻለና የባለሙያዎች እንቅስቃሴ አበረታች ነው ብለዋል።

በዞኑ በጤና መረጃ አያያዝ ጥራትና ታአማንነት ላይ የሚታየው ሰፊ ክፍተት በአፋጣኝ ልታረም እንደሚገባ አቅጣጫ ተቀምጧል።

በመድኃኒት ቁጥጥር ስርዓት ላይ የታዩ ማነቆዎችን ለመፍታት የአመራር አካላት ቁርጠኛነትና ክትትል ተጠናክሮ ልቀጥል እንደሚገባ ተገልጿል።

የክልሉ ጤና ቢሮ ሀላፊ አቶ ኢብራሂም ተማም በክልሉ የወባ ትንኝ መራቢያ ቦታዎችን የማዳፈንና የማፋሰስ፣ የአጎበር ስርጭት፣ የፀረ ወባ ኬሚካል ርጭት፣ የመድኃኒት አቅርቦትና የክትትልና የድጋፍ ስራዎች የተሻለ እንደሆነም አብራርተዋል።

አቶ ኢብራሂም አክለውም በትምህርት ቤቶች፣ በሚዲያዎችና በሌሎች አማራጮች የሚሰሩ የአጎበር አጠቃቀም ፣ የአከባቢ ፅዳትና የሌሎች የወባ መከላከያ መንገዶች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ልጠናከሩ ይገባል ብለዋል።

በዞኑ ተጀምረው ያልተጠናቀቁ የጤና ተቋማት ተጠናቅቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ ከባለድርሻ አካላት በመቀናጀት ሰፋፉ ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝም ተገልጧል።

የዋካ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በመጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ የተብራራ ሲሆን በተለይ በሆስፒታሉ አከባቢዎች የጎርፍ ማፋሰሻ ቦዮችንና ችግኞችን የመትከሉን ስራ የአከባቢው የስራ ሀላፊዎች ማህበረሰቡን በማስተባበር እንዲሰራ አቅጣጫ ተቀምጧል።

የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና እንስቲትዩት ም/ዋና ዳይሬክር ዶ/ር ጌታቸው ቶሌራ በበኩላቸው የወባ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የአመራር ቁርጠኛነት የላቀ ሚና እንደሚኖረው አንስተዋል።

ዶ/ር ጌታቸው አክለውም በአከባቢው በየደረጃው ያሉ የህክምና ተቋማት አክሞ በማዳን ብቻ ሳይሆን ቀድሞ በመከላከሉ ረገድም ልዩ ትኩረት ሰጥተው ልሰሩ ይገባል ብለዋል።

በጤና ሚኒስቴር የመሰረተ ልማት መሪ ስራ አስፈፃሚ የሆኑ ኢንጂነር ታደሰ የማነ በበኩላቸው በተለይ በዞኑ በጤና ኬላዎች ውስጥ ያለው የሰው ሀይል እጥረት ቅድሚያ ተሰጥቶ ልቀረፍ የሚገባ ጉዳይ እንደሆነ አሳስበዋል።

የጤና ሚኒስቴር መስራያ ቤት አቅም በፈቀደ መልኩ ለክልሉ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ያብራሩ ኢንጂነር ታደሰ በጤና ኬላና ጤና ጣቢያ ያሉ ንብረቶች፣ ሶላሮችና ሌሎች ቁሳቁሶች በአግባቡ ልያዙ እንደሚገባም ተናግረዋል።

የዞኑ የመንግስትና የፓርቲ የስራ ሀላፊዎች በሱፐርቪዥን ቡድኑ የተለዩ ደካማ አፈፃፀሞችን በመቀበል ክፍተቶችን ለማረም በትኩረት እንደሚሰራ አንስተዋል።

የዞኑ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ታሪኩ አካሉ በዞኑ የወባ በሽታን ለመከለከልና ለመቆጣጠር የክልሉ ጤና ቢሮ እያደረገ ያለው ያልተቋረጠ ድጋፍ የሚያስመሰግን እንደሆነ ገልፀው የተጀመሩ ድጋፎች ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

28 Dec, 07:30


የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ መካሄድ ተጀመረ

የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ መካሄድ መጀመሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስታውቀዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው÷"ዛሬ ጠዋት እየተከናዋኑ ባሉ ጥረቶች ላይ ለመወያየት የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ጀምረናል" ብለዋል፡፡

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

07 Dec, 13:23


ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአርባምንጭ የተደረገላቸው አቀባበል

19ኛውን የብሄር ብሄረሰቦች ቀን "ሀገራዊ መግባባት ለህብረብሄራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል ነገ ለማክበር የተዘጋጀችው እንግዳ ተቀባይዋ የአርባ ምንጭ ከተማ፣ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው እና ለከፍተኛ የመንግስት ሀላፊዎች ደማቅ አቀባበል አድርጋለች።

ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

07 Dec, 11:12


በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ያለውን የኤሌክትሪክ ኃይል በተሟላ ሁኔታ ለማቅረብ የባለድርሻ ተቋማት ትብብር ማጠናከር ይገባል- ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር)

በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ያለውን የኤሌክትሪክ ኃይል በተሟላ ሁኔታ ለማቅረብ የባለድርሻ ተቋማት ትብብር ማጠናከር እንደሚገባ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር) ገለጹ።

የኮርፖሬሽኑ አመራሮች ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል።

ውይይቱ በልዩ የኢኮኖሚ ዞን ያለውን የኃይል አቅርቦት በተሟላ ሁኔታ ማቅረብ በሚቻልባቸው ሁኔታ እና የሚያጋጥሙ ችግሮችን በፍጥነት ለመፍታት ያለመ ውይይት ተካሄዷል።

የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር) በልዩ ኢኮኖሚ ዞን ውስጥ የሚገቡ ባለሃብቶች ስራቸውን በስኬት ለመከወንና ወደ ዞኖቹ ለመግባትም የኃይል አቅርቦት ጉዳይ የመጀመሪያ ጥያቄያቸው መሆኑን ገልጸዋል።

ለዚህም ከሁለቱ ተቋማት ጋር በቅንጅት መስራት አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው፥ ተግዳሮቶች ሲያጋጥሙም ደግሞ በፍጥነት መልስ መስጠት መቻሉ የሚበረታታና ትብብሩን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በበኩላቸው ከኮርፖሬሽኑ ጋር በመላው ሃገሪቱ በሚገኙት ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖችና በድሬዳዋ ነጻ የንግድ ቀጠና የኃይል አቅርቦቱን በተሟላ ሁኔታ ተደራሽ ለማድረግ ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን አመልክተዋል።

ወደፊትም የሃገርን ልማት ለማረጋገጥ በጋራ እንሰራለን ብለዋል፡፡

በልዩ የኢኮኖሚ ዞን በተሟላ ሁኔታ አቅርቦቱን ለማቅረብና የሚያጋጥሙ ችግሮችን በፍጥነትና በጥራት ለማከናወን የሚያስችል ከሶስቱ ተቋማት የተውጣጣ የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሯል።

ኮሚቴው በቀጣይም ስራዎችን በጋራ በመስራት ችግሮች ሲያጋጥሙ ፈጣን ምላሽ መስጠት እንደሚያስችል ከኮርፖሬሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

07 Dec, 11:10


ደቡብ ኢትዮጵያን መጎብኘት እና እንደ አርባምንጭ ያሉ ከተሞችን እድገት መመልከት ሁልጊዜም አስደሳች ነው።

እንደ ሀገር የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ለከተሞችም ሆነ ለገጠር አካባቢዎች ፈተና ሆኖ የቀጠለ ጉዳይ ነው። ዛሬ በመጎብኘት ላይ እንዳለነው አይነት የሙዝ ልማት ሥራዎችን በገጠር አካባቢዎች በማሳዎች ላይ የኩታ ገጠም እርሻ አሰራረን ጀምረናል። እነዚህን ጥረቶች የሚደግፈው የሌማት ትሩፋት ሥራ በየአርሶአርብቶአደሩ ቤት የእንቁላል ምርትን ከአሳ እና ከብት ርባታ ብሎም ንብ ማነብ ጋር ምርት በማሳደግ ላይ ይገኛል።

እነዚህ መርሃግብሮች በጥምር የገጠሩ እና የከተማው ነዋሪዎች ከትሩፋቱ እንዲካፈሉ አልመው ሰርተዋል። በተለይ የኩታ ገጠም እርሻ በአርባምንጭ ታላቅ ተስፋ የሰነቀ ነው።

Abiy Ahmed Ali

Southwest Communications

07 Dec, 09:00


የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር ዘላቂ ሠላምን በመገንባት ቀጣይነት ያለውን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ለመገንባት ያስችላል። አፈ ጉባዔ አቶ አገኘሁ ተሻገር

የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን መከበር ዘላቂ ሠላምን በመገንባት ቀጣይነት ያለውን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ለመገንባት እንደሚያስችል የኢፌዴሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ የተከበሩ አቶ አገኘሁ ተሻገር ተናገሩ።

19ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን የባህልና ታሪክ ሲምፖዚየም በአርባምንጭ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

"ህብረ ብሄራዊ አንድነት ለሀገራዊ መግባባት" በሚል መርህ ቃል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ አርባምንጭ ከተማ ህዳር 29 የሚከበረውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በማስመልከት በብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ባህልና ታሪክ የሚያተኩር ሲምፖዚየም እየተካሄደ ይገኛል።

በጋሞ ባህልና ምርምር ማዕከል አዳራሽ ክቡራን የእለቱ እንግዶች በተገኙበት እየተካሄደ በሚገኘው ሲምፖዚየም ላይ ንግግር ያደረጉት የኢፌዲሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፌ-ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገረ ባለፉት 18 ዓመታት በሀገር አቀፍ ደረጃ የቀኑ መከበር ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች የጋራ እሴቶቻቸውን በማጎልበት በሀገረ መንግሥት ግንባታ ላይ አዎንታዊ ሚና እንዲወጡ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።

የዘንድሮው በዓል በሀገሪቱ ዘርፈ ብዙ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መዋቅራዊ ሽግግር እየተተገበረ ባለበት ጊዜ መሆኑ ልዩ ያደርገዋል ያሉት አቶ አገኘሁ የበዓሉ መከበር የህዝቦችን የጋራ እሴቶችን በማስተዋወቅ፣ ዘላቂ ሠላምና ልማት ለማፋጠን የሚረዳ መሆኑን ጠቁመዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፌ-ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ፀሀይ ወራሶ በበኩላቸው ቀኑ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች የጋራ ማንነታቸውን፣ ታሪክና ባህላቸውን ለመላው አለም እንዲያስተዋውቁ ዕድል የፈጠረ መሆኑን በመግለጽ 19ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በክልሉ መዘጋጀቱ የክልሉን የልማት አቅሞች ለማስተዋወቅ ምቹ አጋጣሚ የፈጠረ እንደሆነ ተናግረዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በብዝሀነት ላይ የተመሠረተ የህብረብሄራዊነት መገለጫ መሆኑን የገለጹት አፌ-ጉባኤ ወ/ሮ ፀሀይ ይህንን አንድነት በጠንካራ መሠረት ላይ በመገንባት፣ አብሮነትና አንድነት እንዲሁም መቻቻልን አጠናከረው መቀጠል ይገባል ብለዋል።

"በዓሉን ስናከብር በለውጡ መንግሥት የመጡ ድሎችን ማስቀጠል ይገባል" ያሉ አፌ-ጉባኤ ወ/ሮ በህዝቦች መካከል ያለውን ሠላማዊ ግኑኝነት በማጠናከር ለሀገረ መንግሥት ግንባታና ለዘላቂ ሠላም መጎልበት መጠቀም እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

በዕድገቱ በዛብህ

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

07 Dec, 08:10


በፓናል ውይይት እና ሲምፖዚየሙ ላይ የሚሳተፉ የክልል ርዕሳነ መስተዳድራን እና የከተማ አስተዳደር ከንቲባዎቹ ወደ አዳራሽ ገብተዋል

በፓናል ውይይት እና ሲምፖዚየሙ ላይ የሚሳተፉ የክልል ርዕሳነ መስተዳድራን እና የከተማ አስተዳደር ከንቲባዎቹ ወደ አዳራሽ ገብተዋል።

በመርሃ ግብሩ የኢፌዲሪ ፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፣የኢፌዲሪ ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ቴዎድሮስ ምህረት፣የክልሎች ርዕሰ መስተዳደሮች፣የሁለቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች ፣የኬንያ ሪፐብሊክ ልዑካን እና ጥሪ የተደረገላቸው አካላት ተገኝተዋል።

መርሃ ግብሩ የኢትዮጵያ ብሄራዊ መዝሙር በመዘመር ተጀምሯል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

05 Dec, 10:03


በቤንች ሸኮ ዞን የከተማ ቦታና ይዞታ መስፋፋትን በወጣው ደንብ ቁጥር 012/2015 ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር በሚዛን አማን ከተማ ዉይይት እየተካሄደ ነዉ።

የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን መድረኩን በንግግር ሲከፍቱ እንደተናገሩት በአለም ከተሞች የማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊና የፖለቲካ ማዕከላት ናቸው ብለዋል። እንደ ሀገር የፖለቲካ ፣ ኢኮኖሚና ማህበራዊ ጉዳዮች መሰረት በከተሞች ልማትና ዕድገት ጋር የተመሰረተ ነው ብለዋል።

ከተሞች በተገቢው ከተመሩ የገጠሩን ኢኮኖሚ የመምራትና የማሳደግ ሀይል አላቸው ያሉት አቶ ሀብታሙ ከሀገራዊ ለውጡ ማግስት መንግስት ለከተሞች ልማትና ዕድገት ከፍተኛ ትኩረት መስጠቱን ገልጸዋል። የገጠር ከተሞችም በፕላን እንዲመሩና ዕድገታቸው በህግና መመሪያ መሰረት እንዲሆን እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የክልሉ መንግስትም ለከተሞች ዕድገት በልዩ ትኩረት እየሰራ በመሆኑ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን መንገሻ በመድረኩ ባደረጉት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ባለፉት 2 አመታት ሳይፈቀዱ የተያዙ የከተማ መሬቶችን ለመቆጣጠርና ለመከላከል የወጣውን መመሪያና ደንብ ተግባራዊ ለማድረግ ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል።

በዚህም በዞኑ 10ሺ 609 ሳይፈቀዱ የተያዙ የከተማ ቁራሽ መሬቶች የተለዩ ሲሆን 8 ሺ200 ቁራሽ መሬቶችን የመለካት ስራ መሰራቱን ገልጸዋል። ከዚህ ውስጥ 6ሺ 600 ቁራሽ መሬቶች ላይ የፕላን ስምምነት የተሰራ ሲሆን 3ሺ 522 መሬቶች ሰነድ የተሰራላቸው መሆኑን ገልጸዋል።

ከተሰጠው አገልግሎት 22 ሚሊየን ብር ገቢ መገኘቱን አቶ መስፍን ገልጸው የተገኘው ሀብትም መልሶ ለመሰረተ ልማት ስራ መዋሉን ገልጸዋል። በመልሶ ማልማት ስራዎች በዞኑ በሁሉም መዋቅሮች ተግባራዊ እንዲደረግ አቅጣጫ የተቀመጠ ቢሆንም ሚዛን አማንና ሸኮ ወረዳ ፈጥነው ወደ ስራ የገቡ መዋቅሮች እንደሆኑ ገልጸዋል።

የካዳስተር ፣ የአከራይ ተከራይ ስራዎች እንደ ዞን ያልተሻገርንባቸው ስራዎች ናቸው ያሉት አቶ መስፍን ከተሞችን ለዜጎች ስራና ኑሮ ምቹ ማድረግ የተቋሙ ቁልፍ ተግባራት በመሆናቸው ትኩረት ሰጥተን እንሰራለን ማለታቸውን የዞኑ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመልክታል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

05 Dec, 09:07


ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ገዢ ትርክትን በማስረጽ ረገድ በትኩረት ሊሰራ ይገባል - አቶ አደም ፋራህ

ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ገዢ ትርክትን በህብረተሰቡ ዘንድ በማስረጽ ረገድ በትኩረት ሊሰራ ይገባል ሲሉ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ አሳሰቡ።

የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን የማብሰሪያ እና ስራ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በግራንድ ኤሊያና ሆቴል እየተካሄደ ነው።

በመርሐ-ግብሩ ላይ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር)፣ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ተገኝተዋል።

በተጨማሪም የሚዲያው አመራሮች የድርጅቱ ሰራተኞች፣ ተባባሪ አዘጋጆች፣ የሚዲያው አጋሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

በመርሐ-ግብሩ ላይ አቶ አደም ፋራህ ባስተላለፉት መልዕክት ፥ አዲስ ታላቅ ኢትዮጵያዊ ተቋም በመፈጠሩ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን የሚዲያ የነጻነት መርህን መሰረት በማድረግ እንዲዋቀር መሰራቱን መዋቀሩን ገልጸዋል።

የሚዲያ ተቋማት ብዛት እና ተደራሽነት ላይ በትኩረት መሰራቱን የገለጹት አቶ አደም ፋራህ ፥ ፋና እና ዋልታ የመንግስት ግልጸኝነት እና ተጠያቂነት ላይ በስፋት መስራታቸውን አስታውሰዋል።

ውህደቱ ጠንካራ፣ ተወዳዳሪ፣ ሚዛናዊና የዘመኑን ቴክኖሎጂ የታጠቀ ሚዲያ ፈጥሯል ብለዋል።

ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ገዢ ትርክትን በህብረተሰቡ ዘንድ በማስረጽ ረገድ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ አስገንዝበው ፥ ብሔራዊና ገዢ ትርክትን በማስረጽ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚያጎላና የሚያስተዋውቅ ተጽዕኖም እንዲፈጥር ይጠበቃል ሲሉ ገልጸዋል።

ሚዲያን በተገባ መንገድ ከተጠቀምን ሀገርን የምንገነባበት ባልተገባ መንገድ ከተጠቀምነው ደግሞ ሀገር እስከማፍረስ አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚፈጥር ገልጸዋል ሲል ኤፍቢሲ ዘግቧል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

05 Dec, 09:05


የኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን የአርሶና አርብቶ አደሩን ኋላ ቀር የግብርና ዘይቤ በመቀየር የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ ለማድረግ ይሰራል። አቶ ክፍሌ ወልደማርያም

የኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን የኮካ እርሻ ማቋቋሚያ የመሬት ልማት ማስጀመሪያ የአጋሮች የውይይት መድረክ በቱም ከተማ እያካሄደ ነው።

የኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን ለኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ተጠሪ ከሆኑ ተቋማት አንዱ መሆኑንና ግብርናን ለማዘመን ተልዕኮ የተሰጠውና በአምስት አንጋፋ የልማት ድርጅቶች ውህድ የተቋቋመ የመንግስት የልማት ድርጅት ነው ።

ኮርፖሬሽኑ የህዝብ ተቋም እንደመሆኑ መጠን ግብርናን በማዘመን በሀገር ደረጃ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የድርሻውን ለማበርከት በስፋት እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ክፍሌ ወልደማርያም ተናግረዋል ።

ኮርፖሬሽኑ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከ2013 ዓ/ም ጀምሮ ወደ ስራ ለመግባት በክልሉ ያለውን እምቅ የተፈጥሮ ሀብትና ለስራ ታታሪ የሆነ የልማት ጥያቄን ያነገበ እና ለሰላም ዋጋ የሚሰጥ ህዝብና የፖለቲካ አመራር የሚገኝበት በመሆኑ ክልሉን መምረጡን ተናግረዋል።

ኮርፖሬሽኑ በክልሉ የታማሻሎ የምርጥ ዘር ማባዣ እርሻ ልማት ፣ በቅርቡ የሚመረቀው የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብኣትና የሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል ቀጥሎ የኮካ አካባቢ የእርሻ ማቋቋሚያ የመሬት ልማት የሰብል ዘሮችን ለማባዛት እና ለውጭ ገበያ የሚላኩ ምርቶችን በስፋት ለማምረት በክልሉ ሶስተኛው መዳረሻ መሆኑን አቶ ክፍሌ ተናግረዋል ።

የኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን የአርሶና አርብቶ አደሩን ከእጅ ወደ አፍ የሆነውን ኋለቀር የግብርና ዘይቤ በመቀየርና ቴክኖሎጂን በማስረጽ ለአካባቢው ነዋሪዎች በቅርበት ሆኖ ያገለግላል ሲሉም አቶ ክፍሌ ተናግረዋል ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብሔረሰቦች ምክርቤት ዋና አፈጉባኤ የተከበሩ አቶ መቱ አኩ በበኩላቸው ልማቱ የአርብቶና አርሶ አደሩን ህይወት የሚቀይርና ግብርናን የሚያዘምን ነው ሲሉ ተናግረዋል ።

የኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን ውጤታማ እንዲሆንም የአካባቢው ነዋሪዎች በቅንጅትና በትብብር መስራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።

በክልሉ በምዕራብ ኦሞ ዞን በኮካ አካባቢ የመጣውን የልማት ዕድል ሳንጠቀም አልፎን ትውልድ እንዳይወቅሰን በመተባበርና በመደማመጥ ወደ ስራ መግባት ይኖርብናል ሲሉም አቶ መቱ ተናግረዋል ።

የኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን ገጽታና እያከናወነ ያለውን ስራዎች የተመለከተ ሰነድ ቀርቦ በተሳታፊዎች ውይይት እየተደረገበት ነው።

በታጠቅ አበበ

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

05 Dec, 08:54


የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን የማብሰሪያና ሥራ ማስጀመሪያ መርኃ ግብር እየተካሄደ ነው

የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን የማብሰሪያ እና ሥራ ማስጀመሪያ መርኃግብር በግራንድ ኤሊያና ሆቴል እየተካሄደ ይገኛል።

በመርኃ ግብሩ ላይ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ፣ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ፣ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማኅበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር እና የፋና ሚድያ ኮርፖሬሽን ቦርድ ሰብሳቢ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ተገኝተዋል።

በተጨማሪም የሚዲያው አመራሮች የድርጅቱ ሰራተኞች፣ ተባባሪ አዘጋጆች፣ የሚዲያው አጋሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል።

የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን የቀድሞ ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እና ዋልታ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኮርፖሬት ተዋህደው የመሰረቱት ግዙፍ የሚዲያ ተቋም ነው።

ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን

Southwest Communications

05 Dec, 08:52


ፋና እና ዋልታ በይፋ ተዋሃዱ

ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት አ.ማ እና ዋልታ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኮርፖሬት አ.ማ ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን አ.ማ በሚል መጠሪያ በይፋ ተዋሃዱ።

የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን የማብሰሪያ እና ስራ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በግራንድ ኤሊያና ሆቴል እየተካሄደ ነው ሲል ኤፍቢሲ ዘግቧል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

04 Dec, 14:55


በክልላችን የተማሪዎችን ዉጤትና ስነ ምግባር ለማሻሻል የትምህርት ቤት አምባሳደር እንዲሰየም መደረጉ አበረታች ዉጤት እያመጣ መሆኑን አቶ አልማዉ ዘዉዴ ገለጹ

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አልማዉ ዘዉዴ በማህበራዊ ተስስር ገጻቸዉ ባስተላለፉት መልዕክት የትምህርት ጥራትና የተማሪ ዉጤት ለማሻሻል በየደረጃዉ የሚገኙ አመራሮችና ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችን በየትምህርት ቤት አምባሳደር አድርጎ በመሰየም ኃላፊነታቸዉን ከትምህርት ቤቶች ጋር ተቀራርበዉ እንዲሰሩ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም ከተማሪዎች፣ ከመምህራን፣ ትምህርት ቤት አመራሮችና ወላጆች ጋር በመወያየት የተማሪዎች ዉጤት ለማሻሻል በተግባባነዉ መሰረት ወደ ስራ ተገብቷልም ብለዋል።

በኮንታ ዞን፣ በካፋ ዞንና ቤንች ሸኮ ዞኖች ይህ ተግባራዊ በማድረግ እያከናወኑ ያለዉ ተግባር የሚደነቅ መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊዉ ሌሎች ዞኖችም በተመሳሳይ በፍጥነት ወደ ተግባር መግባት ይጠበቅባቸል ስሉ አሳስበዋል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

04 Dec, 12:54


የደቡብ ምዕራብ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን የደንበኞችን ፍላጎት ለማርካትና ኮርፖሬሽኑ ውጤታማና ትርፋማ እንዲሆን እየሰራ እንደሚገኝ ገለጸ

የደቡብ ምዕራብ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን በንጹሕ መጠጥ ውሃ፣በመስኖ ልማት፣ በህንጻ ግንባታና ሌሎችም ግንባታ ስራዎችን በማካሄድ የደንበኞችን ፍላጎት ለማርካትና ኮርፖሬሽኑ ውጤታማና ትርፋማ እንዲሆን እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ኮርፖሬሽኑ የ2017 በጀት ዓመት የ4 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ፣የኮርፖረሽኑ ስራ አመራር ቦርድ አባላት የስብሰባ ስነስርዓት መመሪያ እና የኮርፖሬሽኑ መዋቅር ሠራተኞችን ለመደልደል በተዘጋጀው መመሪያ ላይ ከቦርድ አባላት ጋር በቦንጋ ከተማ ተወያይተዋል።

የኮርፖሬሽኑ ቦርድ ሰብሳቢና የክልሉ ውሃ፣ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር በየነ በላቸው ኮርፖሬሽኑ ለትርፍ የሚሰራ የቢዝነስ ተቋም እንደመሆኑ መጠን የወጪ ቁጠባ ስትራቴጂ በመንደፍ የሚያገኘው ገቢ እና ወጪ በተገቢው ኦዲት እያደረገ ውጤታማነቱን እያረጋገጠ መጓዝ ያስፈልጋል ብለዋል።

ኢንጂነር በየነ በላቸው በማከልም ፕሮጀክቶች የራሳቸውን በጀት ወጪን ከውሉ አንጻር እያመሳከሩ መሄድ እንዳለባቸው፣ ፕሮጀክቶች ውል እንደተገባና ቅድመ ክፍያ እንደተወሰደ የግንባታ ግብዓቶችን ቀድመው ገዝተው ማስቀመጥ እንዳለባቸውና ኮርፖሬሽኑ የራሱ መስሪያ ቤት ግንባታ ቦታውን ከሚለመለከታቸው አካላት በመነጋገር ወደ ስራ በመግባት የኪራይ ወጪውን መቀነስ ይጠበቃልም ብለዋል።

የክልሉ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ፍቅሬ ኃይሌ ኮርፖሬሽኑ የንጹህ መጠጥ ውሃ ግንባታ ፕሮጀክትና ሌሎች የህንጻ ግንባታ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን አንስተዋል።

ለአብነትም የሜራ ንጹሕ መጠጥ ውሃ ግንባታ፣የቦንጋ መምህራን ኮሌጅ የቧንቧ መስመር ጥገና ስራ እንዲሁም የቦንጋ ከተማ የመጠጥ ውሃ የመስመር ጥገና ስራ ተጠናቆ አገልግሎት ላይ መዋሉን ጠቅሰዋል።

ኮርፖረሽኑ በቦንጋ ከተማ እየገነባ ያለው የመደመር ትውልድ ቤተመጻሕፍት ግንባታ ፕሮጀክት በመጠናቀቅ እንዳለና የአመያ ከተማ ማምረቻ ሼድ ግንባታ ስራ በተሻለ አፈጻጸም እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ኮርፖሬሽኑ የደንበኞችን ፍላጎት ለማርካትና ውጤታማና ትርፋማ እንዲሆን እየሰራ ነው ያሉት ዋና ስራ አስፈጻሚው በዚህም ባለፉት አራት ወራት ውስጥ ለ410 ሰዎች ጊዜያዊ የስራ ዕድል መፍጠር መቻሉንም ገልጸዋል።

የኮርፖሬሽኑ የአስካሁኑ የስራ እንቅስቃሴ የተሻለና መጠናከር የሚገባ እንደሆነም ያነሱት የቦርድ አባላት ኮርፖረሽኑ በቀጣይ ራሱን ለመቻልና በሚያከናውናቸው ፕሮጀክቶች ውጤታማ ለመሆን በትኩረት መስራት ይጠበቃልም ብለዋል።

የተጀመረው የተሻለ አፈጻጸም እንዲጠናከር ከአሰሪ መስሪያ ቤቶች ጋር በቅንጅት መስራት እንደሚጠበቅም ተመላክቷል።

የቦርዱ አባላት የኮርፖሬሽኑ መዋቅር የሠራተኞች የድልድል መመሪያ ላይ መሻሻልና መስተካከል በሚያስችል ጉዳዮች ላይ በመወያየት መመሪያውን አጽድቋል።

በፍቅር ከበደ

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

30 Nov, 14:45


በቤንች ሸኮና ሸካ ዞን ግምታዊ ዋጋቸው ከ1 ሚሊየን ብር በላይ የሆኑ ህገ ወጥ መድሀኒቶች እና የህክምና መገልገያ ቁሳቁሶች መያዛቸው ተገለፀ

አብዛኛዎቹ መድሀኒቶች በሀገር ውስጥ ያልተመዘገቡና ፍቃድ ያልተሰጣቸው ሲሆኑ ቀሪዎቹ ከመንግስት የጤና ተቋማት ወጥተው በግለሰብ መድሀኒት መደብር ውስጥ መገኘታቸው ተገልጿል።

በቤንች ሸኮ ዞን ጤና መምሪያ የጤናና ጤና ነክ አገልግሎት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪ አቶ ለገሰ ግርማዬ እንደተናገሩት የወባ ወረርሽኝን ተከትሎ በዞኑ በተለያዩ አካባቢዎች የህገ ወጥ መድሀኒት በግል ተቋማት መበራከቱን ገልጸዋል።

ከክልል የህገ ወጥ መድሀኒት ቁጥጥር ግብረ ሀይል አባላት ጋር በመሆን በጉራፈርዳ ፣ ሰሜን ቤንችና ደቡብ ቤንች ወረዳዎች ላይ የቁጥጥርና ኢንስፔክሽን ስራ መሰራቱን ገልጸው በዚህም ግምታዊ ዋጋቸው ከግማሽ ሚሊየን ብር በላይ የሆኑ ህገ ወጥ መድሀኒቶችና የህክምና መገልገያ ቁሳቁሶች መገኘታቸው ተገልጿል ብለዋል።

ከዚህ ባሻገርም ከተፈቀደላቸው ደረጃ በላይ አገልግሎት መስጠት በኢንስፔክሽኑ ከታዩ ጉዳዮች አንዱ መሆኑን አቶ ለገሰ ገልጸው ህብረተሰቡ በሀኪም ከተፈቀደና ፈዋሽነታቸው የተረጋገጡ መድሀኒቶችን ብቻ በመጠቀም የራሱንም ሆነ የቤተሰቡን ጤንነት ሊጠብቅ ይገባል ብለዋል።

በደቡብ ምዕራብ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ የጤናና ጤና ነክ ተቋማት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አብዱልአዚዝ ፈረጃ እንደተናገሩት ሀገራዊ የወባ በሽታ ወረርሽኝ ስርጭትን ተከትሎ በኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ቁጥጥር ባለስልጣን ያልተመዘገቡ እና ፍቃድ ያልተሰጣቸው እንዲሁም ፈዋሽነታቸው ያልተረጋገጡ መድሀኒቶች በገበያ ውስጥ ይገኛሉ ብለዋል።

በተለይም የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ከጎረቤት ሀገራትና ክልሎች ጋር የሚዋሰን ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ለህገ ወጥ መድሀኒቶች ዝውውር ተጋላጭ ነው ብለዋል። በቅርቡ በሸካና ቤንች ሸኮ ዞን በተደረገው ድንገተኛ አሰሳ ግምታቸው 1 ሚሊየን ብር የሚጠጋ ህገ ወጥ መድሀኒቶችና የህክምና ግብዓቶች መያዛቸውን ገልጸዋል።

አቶ አብዱልአዚዝ አክለውም በመንግስት የጤና ተቋማት ብቻ መገኘት የነበረባቸው ኳርተምን ጨምሮ ሌሎች መድሀኒቶች በግል የመድሀኒት መደብር ውስጥ መገኘታቸውን ገልጸው እንደዚህ አይነት ወንጀሎች ከማሸግና ከአስተዳደራዊ እርምጃ ባሻገር በህግ የሚያስጠይቅ በመሆኑ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

በተለይም በሁለቱ ዞኖች በተደረገ ድንገተኛ አሰሳ የህብረተሰቡ ድጋፍና ጥቆማ ከፍተኛ እንደነበር ገልጸው በቀጣይም በክልሉ ዞኖችና ወረዳዎች ላይ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል ሲል የዞኑ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ዘግቧል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

30 Nov, 13:45


ብልጽግና ፓርቲ በጥቂት ዓመታት ለትውልድ የሚሸጋገሩ ድሎችን አስመዝግቧል- የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዳንት እና የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

ብልጽግና ፓርቲ በጥቂት ዓመታት የኢትዮጵያን ስብራቶች ከመጠገን ባሻገር ለትውልድ የሚሸጋገሩ ድሎችን አስመዝግቧል ሲሉ የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዳንት እና የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

“የሃሳብ ልዕልና ለሁለንተናዊ ብልጽግና" በሚል መሪ ሃሳብ የብልጽግና ፓርቲ 5ኛ ዓመት ምሥረታ በዓል የማጠቃለያ መርሐ ግብር በአድዋ ድል መታሰቢያ ተካሂዷል፡፡

በመርሃ ግብሩም የፓርቲው ፕሬዝዳንት እና የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንዲሁም የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንቶች፣ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት፣ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት፣ የፓርቲው አባላት፣ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተዋል፡፡

የፓርቲው ፕሬዝዳንትና የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ፤ ኢትዮጵያ ከድህነት ለመውጣት ካላት ቁርጠኝነት አንጻር ብልጽግናን ማረጋገጥ የሁሉም ዜጎች የወል እውነት ነው ብለዋል፡፡

ፓርቲው ባለፉት ዓመታት ብሔራዊ ወንድማማችነት እንዲሁም እውነት፣ እውቀትና ጥበብን መለያው አድርጎ ፈተናዎችን ወደ ድል በመቀየር በርካታ ስኬቶችን አስመዝግቧል ነው ያሉት፡፡

ብልጽግናን ማረጋገጥ ለኢትዮጵያዊያን የያዝነው ራዕይ ነው ሲሉም ተናግረዋል፡፡

በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ፓርቲዎች እንዳይሳካላቸው ያደረጉ አምስት ዋና ዋና ስብራቶች መኖራቸውንም አንስተዋል፡፡

እነዚህም ሙሉ ለሙሉ ከውጭ የተቀዳ ርዕዮት ዓለም፣ ኃይልና ሃሳብን መቀላቀል፣ የወዳጅና ጠላት ፖለቲካ፣ አካታች አለመሆን እንዲሁም የዴሞክራሲ እጥረት መሆናቸውን አውስተዋል፡፡

ብልጽግና ፓርቲ ከእነዚህ ስብራቶች ትምህርት በመውሰድ ሀገር የሚያሻግር ተራማጅ ፓርቲ መሆን መቻሉንም ጠቁመዋል፡፡

"የሃሳብ ልዕልና" የሚለው እሳቤም የብልጽግና መገለጫ መሆኑን ጠቅሰው፤ ፖለቲካ የኃይል ሳይሆን የሃሳብ ሜዳ ብቻ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል፡፡

በመሆኑም ሃሳብን በሃሳብ እንጂ በኃይል ማሸነፍ እንደማይቻል አጽኖት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡

ብልጽግና ፓርቲ ባለፉት ዓመታት ያጋጠሙ ፈተናዎችን አዲስ በሆነ አካሄድ ለመፍታት የሄደባቸው ርቀቶች ስኬታማ እንደነበሩም ነው የተናገሩት፡፡

በቀጣይም የሚያጋጥሙ ፈተናዎችን በሪፎርም፣ በንግግር፡ በሽግግር ፍትህ፣ ሰጥቶ በመቀበል እና በሀገራዊ ምክክር ለመፍታት የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አውስተዋል፡፡

በአንዳንድ አካባቢዎች ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ ኃይሎችም በኃይል የሚያሳኩት ምንም አይነት ነገር አለመኖሩን ገልጸው፤ መንግስት ችግሮችን በሰላም ለመፍታት ቁርጠኛ በመሆኑ ወደ ሰላም እንዲመጡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ገዥው ፓርቲ ባለፉት አምስት ዓመታት በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዘርፎች በርካታ ድሎችን ማስመዝገቡን አንስተው፤ ለአብነትም የኢትዮጵያን ጥቅል ዓመታዊ እድገት በአጠረ ጊዜ ውስጥ በእጥፍ ማሳደግ መቻሉን ተናግረዋል፡፡

በቀጣይ ዓምስት ዓመታት ደግሞ አሁን ያለውን ጥቅል ዓመታዊ አድገት በእጥፍ ለማሳደግ እንደሚሰራ አብራርተዋል፡፡

በቀጣይ 5 ዓመታት በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም ሰፍኖ ዜጎች በተደመረ አቅም ሀገራቸውን የሚያሳድጉበት እንደሚሆንም ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡

ኢትዮጵያዊያን ከፓርቲው ጎን ተሰልፈው የተሻለ ስኬት እንዲመዘገብ ላበረከቱት አስተዋጽኦም ምስጋና አቅርበዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል፡፡

Southwest Communications

30 Nov, 13:20


በፓርቲዉ መሪነት የተጀመሩ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክሮ ይቀጥላሉ- ወ/ሮ ህይወት አሰግድ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ገቢዎች ቢሮ ለአንድ አቅመ ደካማ ቤተሰብ ያስገነባውን የመኖሪያ ቤት ርክብክብ አድርገዋል።

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ በሸካ ዞን በቴፒ ከተማ አስተዳደር ህብረት ቀበሌ በልዩ ስሙ ዶሮ እርባታ መንደር ለሚገኙት ወ/ሮ ተዋበች ዱባለ ያስገነባውን ቤት ዛሬ ርክክብ አድርጓል።

በክልሉ በሚገኙ ተቋማት አማካኝነት ለአቅመ ደካሞችና ለአረጋዊያን ቤት ገንብቶ መስጠትን ጨምሮ የተለያዩ ድጋፎች እየተደረጉ እንደሚገኝም ተገልጿል።

በርክብክቡ ወቅት የተገኙት የቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ህይወት አሰግድ እንደ የብልፅግና ፓርቲ ሰው ተኮር በሆኑት ፕሮግራሞቹ አቅመ ደካሞችንና አረጋውያንን እንዲሁም በዝቅተኛ ኑሮ ደረጃ የሚገኙ ወገኖችን የመደገፍ ተግባር በትኩረት እየተሰራበት እንደሚገኝ ገልፀዋል።

ወ/ሮ ህይወት አክለውም በግንባታው ሂደት ተሳታፊ የነበሩ የቴፒ ከተማ ሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ባልደረቦችን የህብረት ቀበሌ አመራርና ማህበረሰብን እንዲሁም ግንባታውን የፈፀመው ቅዱስ ግንባታ ማህበር ላሳዩት የመደጋገፍና የመተባበር ተግባር ምስጋና አቅርበዋል።

በሀገራችን ብልፅግና እውን ሆኖ ዜጎቻችን የተሻለና ኑሮ እንዲኖሩ ገቢን አሟጦ በመሰብሰብ ለልማት ማዋል እንደሚያስፈልግ የገለፁት ኃላፊዋ ሁሉም ዜጋ የግብር ጉዳይ የኔም ጉዳይ ነው ብሎ እንዲሠራና በግብይት ወቅት ደረሠኝ ጠይቆ በመቀበልም የዜግነት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ መልክት አስተላልፈዋል።

ቤት ተገንብቶ የተሰጣቸው አረጋዊ ወ/ሮ ተዋበች ዱባለ በሚያፈስ ደሳሳ ጎጆ በደጋፊ እጦት ችግር ውስጥ እንደነበሩ በመግለፅ አሁን ቢሮው መኖሪያ ቤት ገንብቶ በመስጠቱ ምስጋና አቅርበዋል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

30 Nov, 13:15


ቃልን በተግባር መፈጸም የብልጽግና ተጨባጭ መለያዎቹ ናቸው - አቶ አደም ፋራህ

ቃልን በተግባር መፈጸም የብልጽግና ተጨባጭ መለያዎቹ ናቸው ሲሉ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ተናገሩ።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝደንት ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት የብልጽግና ፓርቲ አምስተኛ አመት የምስረታ በዓል የማጠቃለያ መርሀ-ግብር በአድዋ መታሰቢያ ተካሂዷል።

በመርሀግብሩ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝደንት ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እንዲሁም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት ተመስገን ጥሩነህ፣ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፣ እንዲሁም የፓርቲውና የመንግሥት ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ተከብሯል።

በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልእክት የበአሉ አላማ ፓርቲው ከምስረታው ጀምሮ እስካሁን ያደረገውን ጉዞ ለመዘከር እና ቃላችንን ለማደስ ነው ብለዋል።

ፓርቲው በርካታ ፈተናዎች ቢያጋጥሙትም እነዚህን ፈተናዎች ወደ ድል በመቀየር አንጸባራቂ ድል ማስመዝገቡን ተናግረዋል።

የትግላችን መዳረሻ ጠንካራ ሀገረ መንግስት መገንባት ነው ያሉት ምክትል ፕሬዝዳንቱ ቃልን በተግባር መፈጸም የብልጽግና ተጨባጭ መለያዎቹ ናቸው ብለዋል።

ባለፉት አምስት አመታት በሁሉም ዘርፍ የታሪክ እጥፋት የተመዘገበበት መሆኑን ማመላከታቸውን ከፓርቲው ማህብራዊ ትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

በሁሉም ዘርፎች ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን ገልጸው በተገኙ ውጤቶች ሳንዘናጋ ውጤቶቻችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉም ተናግረዋል።

የብልጽግና ፓርቲ አምስተኛ አመት የምስረታ በዓል "የሀሳብ ልእልና ለሁለንተናዊ ብልጽግና" በሚል መሪ ሀሳብ በተለያዩ ሁነቶች ሲከበር መቆየቱ ይታወሳል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

30 Nov, 11:37


ኢትዮጵያ ከድህነት ለመውጣት ካላት ቁርጠኝነት አንጻር ብልጽግናን ማረጋገጥ የሁሉም ዜጎች የወል እውነት ነው - ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር)

ኢትዮጵያ ከድህነት ለመውጣት ካላት ቁርጠኝነት አንጻር ብልጽግናን ማረጋገጥ የሁሉም ዜጎች የወል እውነት ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ብልጽግና ፓርቲ ህብረ ብሔራዊ ወንድማማችነት እንዲሁም እውነት፣ እውቀትና ጥበብን መለያው አድርጎ ባለፉት አምስት ዓመታት ፈተናዎችን ወደ ድል በመቀየር በርካታ ስኬቶችን አስመዝግቧል ብለዋል።

በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና ማህበራዊ ዘርፎች የተመዘገቡ ድሎችም የዜጎችን ተጠቃሚነት በተግባር ያረጋገጡ መሆናቸውንም አንስተዋል፡፡

በቀጣይ አምስት ዓመታት ደግሞ አዳዲስ ድሎችን በማስመዝገብ ከራሷ አልፋ ለሌሎች የምትተርፍ ሀገር ለመገንባት እንሰራለን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡፡

Southwest Communications

14 Nov, 10:09


የኢኮኖሚ ማሻሻያው ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች ላይ ጫና እንዳያሳድር የበጀት ድጎማ ሥርዓት ተግባራዊ እየተደረገ ነው - ኢዮብ ተካልኝ(ዶ/ር)

መንግስት የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲው ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ላይ ጫና እንዳያሳድር የበጀት ድጎማ ሥርዓት ተግባራዊ ማድረግ መጀመሩን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ኢዮብ ተካልኝ(ዶ/ር) ፥ እንደ ሀገር የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ማሻሻያ ተግባራዊ መደረጉ ለኢኮኖሚ እድገት ማነቆ የነበሩ በርካታ ችግሮችን መፍታት አስችሏል ብለዋል።

በዚህም የበጀት ዓመቱ ቀሪ ጊዜያት የተጀመሩ ስራዎች መሬት የሚይዙበት ወሳኝ ወቅቶች መሆናቸውን ጠቁመው አሁን ላይ የኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሪና አጠቃላይ ገበያ እንዳይረጋጋ የሚያደርግ አንድም ምክንያት የለም ብለዋል።

በሩብ ዓመቱ በወጪ ንግድ፣ በገቢና በሐዋላ ፍሰት የታዩ ውጤቶች ጥሩ ማሳያ መሆናቸውን ፤ከወጪ ንግድ አኳያ በወርቅ የታየው አፈጻጸም ከፍተኛ መሆኑንና በታንታለም የታየው ለውጥም የሚበረታታ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

መንግስት የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከግብ ለማድረስ አስፈላጊውን ሁሉ እርምጃ ለመውሰድ ዝግጁ ነው ያሉት ኢዮብ (ዶ/ር) በግብርና፣ በቱሪዝም፣ በማዕድንና በዲጂታል ዘርፎች የታዩ ውጤቶችም ለውጡ ፍሬ ማፍራት መጀመሩ ለዚህ ማሳያ ናቸው ብለዋል፡፡

መንግስት የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲው ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው የማህበረሰብ ክፍሎች ላይ ጫና እንዳያሳድር የበጀት ድጎማ ሥርዓት ዘርግቶ ተግባራዊ ማድረግ መጀመሩንም አመላክተዋል፡፡

በሌላ በኩል ባለፉት ወራት የሸቀጦች የዋጋ ሁኔታ እየተረጋጋ መምጣቱንም መግለፃቸውን የዘገበው ኢዜአ ነው፡፡

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

14 Nov, 10:08


በካፋ ዞን፣ጨታ ወረዳ የሩዝ እርሻ በከፊል

Southwest Communications

14 Nov, 10:08


አዲስ በተሻሻለው የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክ መቆጣጠሪያ አፈጻጸም ላይ በመናኸሪያ እና መንገድ ላይ በቤንች ሸኮ ዞን ምልከታ ተደረገ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የትራንስፖርትና መንገድ ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋጅዋ ሳፒ የመንገድ ትራፊክ ህጎች አተገባበር ላይ በቤንች ሸኮ ዞን በሚዛን በመናኸሪያ አገልግሎት አሰጣጥና በመንገድ መኪና ፍሰት ላይ ምልከታ አድርገዋል።

አዲስ በተሻሻለው የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክ መቆጣጠሪያ ደንብን ከባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መሰጠቱን አቶ ፋጂዮ ተናግረዋል።

በደንቡ ውስጥ በርካታ ጉዳዮች መካተታቸውን ጠቁመው ወደ ትግበራ መግባታቸውን ለማረጋገጥ በሚዛን መናኸሪያ እና በመንገድ ላይ ምልከታ ማድረጉ ለትግበራው አስተዋጽኦው ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል ።

በመናኸሪያ አገልግሎት እና በጉዞ ላይ ላሉ ለተሳፋሪዎች እና ለአሽከርካሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ምክር አቶ ፋጂዮ ሰጥተዋል።

አቶ ፋጂዮ በምልከታው ጥሩ ዕንቅስቃሴ ዉስጥ መግባቱን ማስተዋላቸዉን ገልጸዉ በሌሎችም ዞኖች ቀጣይ መሰል ምልከታና ቁጥጥሮች እንደሚኖሩ ተናግረዋል።

የቤንች ሸኮ ዞን የትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ አበበ ኑራ በበኩላቸው የአዲሱ ደንብ የግንዛቤ ማስጨበጫ ከተሰጠ እና ወደ ትግበራ ሂደት ያለውን ክትትል ማድረግ ለደንቡ ተፈፃሚነት ድርሻው ከፍ ያለ መሆኑን ተናግረዋል።

በተሻሻለው የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክ መቆጣጠሪያ ደንብ 557/2016ን መሠረት በማድረግ እንደ ክልል ከ16 ሺህ በላይ የአሽከርካሪዎች ዓመታዊ የተሃድሶ ስልጠና መዉሰዳቸዉን ገልጸዋል።

በመናኸሪያ እና በመንገድ ላይ በነበረው ምልከታ የክልሉ ትራንስፖርት ና መንገድ ልማት ቢሮ የመንገድ ደህንነትና ከህዝብ ትራንስፖርት ከፍተኛ ባለሙያዎች ፣ የዞንና የከተማ አስተዳደር የመንገድና ትራንስፖርት ኃላፊዎችን ጨምሮ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

14 Nov, 10:07


የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በዓልን ለማስተናገድ ዝግጅቱን እያጠናቀቀ ነው

19ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በዓልን በድምቀት ለማክበር ዝግጅት ማድረጉን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አስታወቀ።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ለበዓሉ እየተደረገ ያለውን ዝግጅት አስመልክቶ በአርባምንጭ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።

በዓሉን ኅብረ-ብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናከር መንገድ በድምቀት ለማክበር ዝግጅት መደረጉን ርዕሰ መሰተዳድሩ ተናግረዋል።

የማክበሪያ ቦታ እና የአገልግሎት ሰጪ ተቋሟትን ጨምሮ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በመገባደድ ላይ እንደሚገኙ በመግለጫው ተመልክቷል።

ላለፉት ዓመታት በዓሉ ሲከበር ለእርስ በርስ ግንኙነት ምቹ አውድ በመፍጠር ኢኮኖሚያዊ፤ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ትስስር ለማጠናከር አዎንታዊ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።

የዘንድሮው 19ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን "ሀገራዊ መግባባት ለኅብረ-ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሃሳብ እንደሚከበር የኢቢሲ መረጃ ያመለክታል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

14 Nov, 09:01


የቱሪዝም ዘርፉ ትልቅ የስራ ዕድል የሚፈጥርና ኢኮኖሚ የሚያመነጭ በመሆኑ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ያስፈልጋል ፦ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ

የዓለም የቱሪዝም ቀን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ለ3ኛ ጊዜ "ቱሪዝም ለሠላም በሚል መሪ ቃልበተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል፡፡

በመድረኩ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ባስተላለፉት መልዕክት ቱሪዝም መድረኩ የቱሪዝም አቅሞችና ሀብቶችን የሚንዳስስበት፣ የሚንመካከርበትና እንደ ክልል የተጀመሩት ስራዎች የሚናጠናክረበት ብለዋል።

ሀገራችን እምቅ የቱሪዝም ሀብት ያሉ ቢሆንም ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ አጥጋቢ ባለመሆኑ በለውጡ ዓመታት በመንግስትና በፓርቲ ትኩረት ከተሰጡት ከኢንዱስትሪ ዘርፎች ውስጥ ተጠቃሽ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም የቱሪዝም መስህቦችንና መደረሻዎችን ለማስፋት የተደረጉት ሙከራዎች በኢንዱስትሪ የተሻለ መነቃቃት እየተፈጠረ እንደሆነ ርዕሰ መስሀዳድሩ ገልጸዋል።

በቱሪዝም ኢንዱስትሪው የሚያጋጥሙት ተግዳሮች ሁሉም ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ አሰራርን በማሳለጥ ከኢኮኖሚ የሚገኘውን ጥቅም አሟጦ ለመጠቀም በትኩረት መስራት ያሻል ሲሉ አስገንዝበዋል ።

ዘርፉ ትልቅ የስራ ዕድል የሚፈጥርና ኢኮኖሚ የሚያመነጭ በመሆኑ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

በቱሪዝም ዘርፍ የጎብኚዎችን የቆይታ ጊዜ ምቹ ሁኔታ በመፍጠር የመስተንግዶ ስፍራዎችን የመዝናኛ ቦታዎችንና መሠል ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጎ በመስራት የተፈጥሮ ሀብት ፣የታሪክ እና የባህል ትውፊቶችን በማስተዋወቅ ኢኮኖሚ ማሳደግ ያስፈልጋል ብለዋል።

የዓለም የቱሪዝም ቀንን በሚመለከት መልዕክት ያስተላለፉት የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዮት ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ነጋሽ
የዓለም የቱሪዝም ቀን በየዓመቱ የሚከበረው የቱሪዝም አስፈላጊነትና ጠቀሜታ እንዲሁም ቱሪዝም በሀገር አቀፍ ደረጀ በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና በፖለቲካዊና ባህላዊ እሴቶች ላይ የሚኖረው አዎንታዊ ተጽዕኖ ለመላው የዓለም ማህበረሰብ ለማሳወቅ ታስቦ ነው ብለዋል።

ቱሪዝም ስራና የስራ ዕድሎችን የመፍጠር አቅም ከመፍጠር አኳያ ሁለገብ ድርሻ ያለው ዘርፍ ከመሆኑም ባሸገር ቱሪዝም ዘርፉን ተፈጥሯዊ ታርካዊና ባህላዊ ይዘቶችን በመጠበቅ ፣ በመንከባከብ ና በማስተዋወቅ እንዲሁም የከተማ ፍልሰት በመቀነስ በኩል ከፍተኛ ድርሻ ያለው መሆኑን ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው አስገንዝበዋል ።

የክልሉ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋንታሁን ብላቴ ለእንግዶች የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግራቸው ክልሉ ብዙ የቱሪዝም አለኝታ እና በርካታ የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎች ባለቤት መሆኑን ገልፀዋል።

በተለይም ክልሉን በአረንጓዴ ቱሪዝም ልዩ ፀጋ ያለዉ መሆኑን በመግለጽ ይህ መድረኩ እምቅ የቱሪዝም ሀብት በአግባቡ በማስተዋወቅ እና በማልማት ከዘርፉ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለማሳደግ በር ከፋች መሆኑን አቶ ፋንታሁን ተናግረዋል።

ከቱሪዝም ዘርፍ ተገቢው ጥቅም እንዲገኝ ለማስቻል የባለድርሻ አካላት ያላሰለሰ ጥረትን የሚጠይቅ መሆኑን ተናግረዋል።

በተከተል ወ/ሚካኤል

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

05 Nov, 14:18


የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ሂደቱ ግለፀኝነትና አሳታፊ መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮች ገለፁ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል እየተከናወነ ያለውን 3ኛ ቀኑን የያዘውን የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር መድረክ አስመልክቶ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በቦንጋ ከተማ መግለጫ ሰጥቷል።

በመግለጫው ላይ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ሙሉጌታ አጎ የእስካሁን ያለውን የምክክሩን ሂደት ከሁሉም ወረዳዎች የተመረጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ወኪሎች ግልጽና አሳታፊ በሆነ መልኩ አጀንዳቸውን አደራጅተው ያጠናቀቁበት የምክክር መድረክ መሆኑን ገልፀዋል።

በክልሉ የህብረተሰብ ወኪሎች ጋር የተደረገው ያለፉት የሶስት ቀናት የምክክር መድረክ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ተሳታፊዎች አጀንዳቸውን በማቅረብና በመፈራረም፣ በቀጣዮቹ ቀናት ለሚደረጉት የምክክር ሂደቶች ተወካዮቻቸውን በመምረጥ ሂደቱም በታቀደው መልኩ በስኬት መጠናቀቁንም አክለዋል።

ከነገ ጀምሮ በሚኖሩ ቀጣዮቹ ቀናት ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችና የባለድርሻ አካላት ምክክር መድረክ እንደሚቀጥልም ገልፀዋል።

በክልሉ እየተካሄደ ያለው የምክክር መድረክ እንዲሳካ አስተዋፅኦ እያደረጉ ላደረጉ አካላትም ኮሚሽነር ሙሉጌታ አጎ አመስግነዋል።

ኮሚሽነር ዘገየ አስፋው በበኩላቸው፤ ኮሚሽኑ ከህዝብ የተሰጠውን ኃላፊነት ለመወጣት የተቻለውን ሁሉ እየተወጣ መሆኑን ገልፀዋል ፡፡

በዚህም ሂደት ኮሚሽኑ ከህብረተሰቡ የሚነሱ አጀንዳዎች ውሳኔ እንዲሰጥበት አበክሮ እንደሚሰራ አስረድተዋል።

የምክክር ሂደቱ ውጤታማ ለማድረግና ችግሮቹን ለመፍታት ውይይት፣ በመመካከር እና የመደማመጥ ባህልን መሠረት በማድረግ በአስፈላጊውን ጥረት ሁሉ የሚያደርግ መሆኑን ኮሚሽነር ዘገየ አስፋው አብራርተዋል።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በቀጣይ ቀናት በሚኖራው አጀንዳ የማሰባሰብ ሂደት ላይ ሁሉም የባለድርሻ አካላት ወኪሎች የአጀንዳዎቹ አስፈላጊነት በመገንዘብ በንቃት እንዲሳተፉም ጥሪ አቅርበዋል።

በተከተል ወ/ሚካኤል

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

05 Nov, 14:16


ማስታወቂያ

#የደቡብ_ምዕራብ_ዲዛይንና_ቁጥጥር_ኮርፖሬሽን ከዚህ በታች የተዘረዘሩ ክፍት የስራ መደቦች አመልካቾችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል።

የተዘረዘሩ መስፈርቶችን የሚታሟሉ አመልካቾችን እንዲትወዳደሩ ኮርፖሬሽኑ ጥሪዉን ያቀርባል።

Southwest Communications

05 Nov, 14:15


በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኤርባስ A350-1000 አውሮፕላን አዲስ አበባ ገባ!

የኢትዮያ አየር መንገድ ከኤር ባስ ኩባንያ የገዛውና በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነው ኤርባስ A350-1000 አውሮፕላን ከፈረንሳይ፣ ቱሉዝ ተነስቶ አዲስ አበባ ገብቷል።

አውሮፕላኑ "ኢትዮጵያ፣ ምድረ ቀደምት" የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

05 Nov, 14:14


የቦንጋ ማዕከል መሠረታዊ ድርጅት አመራሮችና አባላት የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፥ የቦንጋ ማዕከል የክልል ቢሮዎች የብልጽግና ፓርቲ የኢኮኖሚ ዘርፍ መሠረታዊ ድርጅት አመራሮችና አባላት የአቅም ግንባታ ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል።

የአቅም ግንባታ ስልጠናው "የህልም ጉልበት ለእምርታዊ እድገት" በሚል መሪ ቃል በቦንጋ ማዕከል ለሚገኙ የብልፅግና ፓርቲ የኢኮኖሚ ዘርፍ የመሠረታዊ ድርጅት አመራሮችና አጠቃላይ አባላት በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ እየተሰጠ ይገኛል።

በቦንጋ ማዕከል የኢኮኖሚ ዘርፍ መሠረታዊ ድርጅት አመራር ወ/ሮ ቤተልሔም ተሾመ ስልጠናውን አስመልክተው እንደገለጹት የአቅም ግንባታ ስልጠናው በፓርቲው አመራርና አባላት መካከል የሀሳብና ተግባር አንድነት የሚፈጥር እንደሆነ በመግልጽ በፓርቲው መሪነት እንደሀገር የተመዘገቡ ሁለንተናዊ ለውጦችን ለማስቀጠል አመራርና አባሉ በጋራ አቅም የሚገነባበት እንደሆነም ነው ያስረዱት።

የአቅም ግንባታ ስልጠናው የአባላትን አቅም በመገንባት በፓርቲው የተቀመጠውን ሀገራዊ ትልም ለማሳካትና ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ሁለንተናዊ ዕድገት ለማሸጋገር ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።

ለቀጣይ ሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና፥ የስልጠናው መወያያ ሰነድ እየቀረበ የሚገኝ ሲሆን፥ በሚቀርበው ሰነድ መነሻ ሰፊ ውይይት እንደሚደረግ ተመላክቷል።

በስልጠናው የቦንጋ ማዕከል የኢኮኖሚ ዘርፍ የመሠረታዊ ፓርቲ አባላትና አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛል።

በዕድገቱ በዛብህ

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

05 Nov, 14:10


#ደቡብ_ምዕራብ_ኢትዮጵያ_ህዝቦች_ክልል

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ሲካሄድ የቆየው የማህበረሰብ ወኪሎች የአጀንዳ ልየታ የምክክር መድረክ ተጠናቀቀ፡፡

የማህበረሰብ ወኪሎቹ ካለፈው እሁድ ጥቅምት 24/2017 እስከ ዛሬ ጥቅምት 26/2017 ዓ.ም ድረስ ከወከሉት ማህበረሰብ ይዘዋቸው የመጡትን አጀንዳዎች በውይይት ሲያደራጁ ቆይተዋል፡፡

የማህበረሰብ ክፍል ወኪሎቹ በውይይት ያደራጁትን አጀንዳ በአደራ ተረክበው ከባለ ድርሻ አካላት ጋር የሚመካከሩ ወኪሎችንም መርጠዋል፡፡

የክልሉ የባለድርሻ አካላት ምክክር ቀጥሎ ባሉ ቀናት የሚካሄድ ይሆናል፡፡ በዚህ መድረክ ከማህበረሰብ ወኪሎች የተመረጡ ተሳታፊዎችን ጨምሮ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የመንግስት አስፈፃሚ አካላት፣ የተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ወኪሎች እንዲሁም የሃይማኖት ተቋማትን ጨምሮ የልዩ ልዩ ማህበራትና ተቋማት ወኪሎች የሚሳተፉ ይሆናል፡፡

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

05 Nov, 14:08


ስምምነቱ ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላትን ትስስር የሚያጠናክር መሆኑ ተገለጸ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 4ኛ መደበኛ ስብሰባው በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክና በደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ መካከል የተደረገውን የብድር ስምምነትን አፅድቋል፡፡

ስምምነቱ ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላትን የባለብዙ ወገን ትስስርን የሚያጠናክር መሆኑም ተገልጿል፡፡

የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) በሰጡት ማብራሪያ ረቂቅ አዋጁ ሀገሪቱን ጥቅም ባስከበረ መልኩ በህዝቦች መካካል ያለውን ትስስር ወደ ከፍተኛ ደረጃ ለማድረስ የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡

በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ፍላጎት መሰረት ያደረገ የመንገድ መሰረተ ልማት ስምምነት ኢትዮጵያን ከደቡብ ሱዳን ጋር የሚያስተሳስር ከ738 ሚሊየን 264 ሺ የአሜሪካ ዶላር ባልበለጠ ብድር የሚከናወን መሆኑን ገልጸዋል።

የመንገድ ፕሮጀክቱ በደቡብ ሱዳን በኩል በደቡብ ሱዳን መንገዶች ባለስልጣን፣ በኢትጵያ በኩል በኢትጵያ መንገዶች አስተዳደር እንደሚመራም ተናግረዋል።

የምክር ቤት አባላት በበኩላቸው ስምምነቱ ሀገሪቱ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላትን ትስስር የሚያጠናክር፣ በጋራ መልማትን የሚያረጋግጥና ቃሏን በተግባር መፈጸም የምትችል ሀገር መሆኗን አመላካች ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክና በደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ መካከል የተደረገውን የብድር ስምምነት ለማፅደቅ የቀረበ ረቂቅ አዋጅን፤ አዋጅ ቁጥር 1347/2017 አድርጎ በሙሉ ድምጽ አፅድቋል ሲል ኢፕድ ዘግቧል።

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

05 Nov, 14:03


በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኤርባስ ኤ350-1000 አውሮፕላን አዲስ አበባ ገባ

የኢትዮያ አየር መንገድ ከኤር ባስ ኩባንያ የገዛው ኤ350-1000 አውሮፕላን ከፈረንሳይ ቱሊስ ተነስቶ አዲስ አበባ ገብቷል።

አውሮፕላኑ "ምድረ ቀደምት ኢትዮጵያ" የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል።

በዓለምሰገድ አሳዬ
ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

05 Nov, 13:58


የክልል ተቋማት የቦንጋ ማዕከል የኢኮኖሚ ዘርፍ መሠረታዊ ድርጅት አመራሮችና አባላት የአቅም ግንባታ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የቦንጋ ማዕከል ለኢኮኖሚ ዘርፍ መሠረታዊ ድርጅት አመራሮችና አባላት የአቅም ግንባታ ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል።

"የህልም ጉልበት ለእምርታዊ እድገት" በሚል መሪ ሀሳብ በቦንጋ ማዕከል ለሚገኙ የኢኮኖሚ ዘርፍ የመሠረታዊ ድርጅት አመራሮችና አባላት በተለያዩ ርዕሶች ላይ ስልጠና እየተሰጠ ነው ።

በመድረኩ በቦንጋ ማዕከል የኢኮኖሚ ዘርፍ መሠረታዊ ድርጅት አመራር የሆኑት አቶ በላይ ኮጁዋብ ስልጠናው የአመራሮችና አባላትን ፖለቲካዊና የስራ ላይ ተነሳሽነትን እንደሚያጠናክር ገልጸዋል።

ለ4ኛ ዙር የሚሰጠው የአባላት የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ላይ የቡናና ኩታ ገጠም ህዋስ አባላት እየተሳተፉ ሲሆን በመደበኛ ስልጠናው ስራዎቻችን ላይ አቅም ይሆነናል በማለትም አቶ በላይ ተናግረዋል።

በኢኮኖሚው ዕድገት ውስጥ ግብርናው ድርሻው የጎላ መሆኑን ያመላከቱት አቶ በላይ ኮጁዋብ ከስልጠናው የሚገኘውን አቅም በስራዎቻችን ላይ በመተግበር ውጤታማ ለመሆን ስልጠናውን በነቃ መከታተል ይገባል ብለዋል።

"የህልም ጉልበት ለእምርታዊ እድገት" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጁ የመወያያ ርዕሶች በአቶ ታመነ በቀለ ቀርቦ ውይይት ይደረጋል።

በአቶ ታመነ በቀለ እየቀረበ በሚገኘው ሰነድም ብልጽግና ፓርቲ ባለፉት 5 ዓመታትየሪፎርም ስራዎች ተጠናክረው በመቀጠላቸው ለውጦች እየተመዘገቡ መሆኑን ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ ታሪክ አካታች፣አሳታፊና ሁሉንም አይነት ኢትዮጵያዊ ብዝሃነቶችን ይዞ የተፈጠረ ፓርቲ መሆኑንም አቶ ታመነ ገለጻ አድርገዋል።

የብልጽግና ፓርቲ 15 ሚሊዮን አባላት ያሉት ሲሆን ይህም በአፍሪካ ግዙፍ ፓርቲ እንዲሆን አድርጎታል ብለዋል።

ስልጠናው ከዛሬ ጀምሮ ለሚቀጥሉት ሁለት ተከታታይ ቀናት በገለፃና በውይይት እንደሚሰጥም ታውቋል።

በታጠቅ አበበ

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

05 Nov, 10:27


ሀገራዊ ሪፎርም ከተጀመረ በኋላ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ የመጠባበቂያ ክምችት በእጥፍ አድጓል

ሀገራዊ ሪፎርም ከተጀመረ በኋላ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ የመጠባበቂያ ክምችት በእጥፍ ማደጉን የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምሕረቱ አስታወቁ፡፡

አዲሱ የብሔራዊ ባንክ ማሻሻያ አዋጅ ከዚህ ቀደም ለረዥም ዓመታት ሲሠራበት የቆየውንና ለዋጋ ንረት ዋና መነሻ ነበር ሲባል በቆየው አሠራር ላይ ጠበቅ ያለ የማሻሻያ ድንጋጌ ይዞ መቅረቡን የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምሕረቱ ከሴንትራል ባንኪንግ መጽሔት ጋር ባደረጉት ቆይታ አስታውቀዋል፡፡

የብሔራዊ ባንክ ግብ የፋይናንስና የዋጋ ንረትን ማረጋጋት እንደሆነ በመጥቀስ አዲሱ ረቂቅ አዋጅና፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክን ሥልጣንና ተግባር ለመወሰን የወጡ አዋጆችም ይህንኑ ግብ ለማሳካት በሚያስችል መንገድ ማሻሻያ እንደሚደረግባቸው ጠቅሰዋል፡፡

ይህን ተከትሎ ሀገራዊ ሪፎርሙ ከተጀመረ በኋላ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ የመጠባበቂያ ክምችት በእጥፍ ማደጉን ከመጽሔቱ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል፡፡

ለክምችቱ ማደግ ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋምና የዓለም ባንክ ያደረጉት ድጋፍ፣ አበዳሪዎች እንደሚሰጡት የሚጠበቀው የብድር ክፍያ መራዘምና የወርቅ የወጪ ንግድ ግብይት በማዕከላዊ ባንክ በኩል እንዲያልፍ የተደረገው አሠራር ምክንያት መሆኑን በአብነት አንስተዋል፡፡

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ለኢትዮጵያ የሚያደርገው የፋይናንስ ድጋፍ ኢትዮጵያ የጀመረችውን ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያን ለማሳለጥ ከፍተኛ እገዛ አለው ብለዋል፡፡

በዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም የሚተገበሩ የማሻሻያ ፕሮግራሞችን ኢትዮጵያ ቀደም ብላ መጀመሯን በማስታወስ፤ ለአብነትም የሞኒተሪ ፖሊሲ ማሻሻያና የዋጋ ንረትን ለመቀነስ የተወሰዱ እርምጃዎችን ጠቅሰዋል፡፡

ኢትዮጵያ የዋጋ ንረትን ለመቀነስ የጀመረችው ጥረት የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ኢኒሼቲቭ ከመጀመሩ ከዓመት በፊት መሆኑን በመጠቆም፤ በዚህም አመርቂ ውጤት ተገኝቷል ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ የወለድ ምጣኔን መሠረት ያደረገ የሞኒተሪ ፖሊሲ እ.አ.አ. በነሐሴ 2023 መጀመሯን በመጥቀስ፤ በዚህም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክን ብድር የመስጠት አቅም ማሳደግ መቻሉን አስታውቀዋል፡፡

በሀገሪቱ ያለው የዋጋ ግሽበት እ.አ.አ. በነሐሴ 2024 ላይ 17 በመቶ እንደነበርና ምግብ ነክ ያልሆኑ የፍጆታ ዕቃዎች የዋጋ ግሽበት 14 በመቶ እንደነበር ጠቁመዋል፡፡

መንግሥት እየወሰዳቸው ባሉ የተለያዩ እርምጃዎች በቀጣይ ወራት የዋጋ ግሽበቱ እንደሚቀንስ ያላቸውን እምነትም ገልፀዋል፡፡

መንግሥት ክፍት ያደረገው የንግድ እንቅስቃሴ የዋጋ ግሽበትን ለመቀነስ ካለው አስተዋጽዖ በተጨማሪ የውጭ ምንዛሬ ማሻሻያውን ለማሳለጥ ሚናው የላቀ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

የውጭ ምንዛሬ ግብይትን በተመለከተ ከናይጄሪያ፣ ግብፅና ፓኪስታን ልምድ በመውሰድ ተግባራዊ እንደተደረገና የኢትዮጵያ አካሄድ በቀጣይ ገበያው የውጭ ምንዛሬ ሂደቱን እንዲመራው ማድረግ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

ኢትዮጵያ የጀመረችው ማሻሻያ በቀጣይ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት አርዓያ እንደሚሆን ያላቸውን እምነትም ገልፀዋል፡፡

በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ የመጀመሪያዎቹ ሁለት ወራት ለውጭ ገበያ የቀረበው የቡና፣ ወርቅና የቅባት እህል ግብይት በእጥፍ ማደጉን በመጠቆም፤ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ ምርቶች በአንፃሩ መቀነስ ማሳየታቸውን ገልፀዋል፡፡

እንዲሁም የባንኮች ተቀማጭ ገንዘብና ከውጭ ወደ ሀገር ውስጥ በሐዋላ የሚላከው ገንዘብ በእጅጉ እድገት ማሳየቱን ጠቅሰዋል፡፡

መንግሥት አሁንም የዋጋ ግሽበትን ለመከላከል በነዳጅ፣ በማዳበሪያ፣ በመድኃኒትና በምግብ ዘይት ላይ ድጎማ ማድረግ መቀጠሉን ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክን ሥልጣን የሚወስነው ሕግ ከሁለት ወራት በኋላ ይጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ በመጠቆም፤ ይህም የባንኩን ተወዳዳሪነት በእጅጉ እንደሚያሳድገው አስታውቀዋል፡፡

ሕጉ ባንኩ የዋጋ ምጣኔን ለማረጋጋት፣ የፋይናንስ ተቋማትን ህልውና ለማስጠበቅና ለኢኮኖሚ ዕድገቱ የራሱን አስተዋጽዖ እንዲያበረክት ሰፊ ዕድል እንደሚፈጥርለት ነው ያስረዱት፡፡

በኢትዮጵያ ያለው የባንክ ዘርፍ ላለፉት 40 ዓመታት ለውጭ ባንኮች ዝግ ሆኖ መቆየቱን በማስታወስ፤ የውጭ ባንኮች ተሳትፎ ተወዳዳሪነትን ለማስፋት፣ ቴክኖሎጂን ለማስረፅና የአገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመን አጋዥ መሆኑን አንስተዋል፡፡

ኢትዮጵያ ብሔራዊ የፋይናንስ ክፍያና ተደራሽነት ስትራቴጂ መቅረጿን ተከትሎ የተጀመረው ዲጂታል ፋይናንሲንግ ለመጀመሪያ ጊዜ በእጅ የሚፈጸመውን የገንዘብ ዝውውር መብለጡን ለስኬቱ ማሳያ በማድረግ አቅርበዋል፡፡

በቀጣይም በዲጂታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ የብድር አገልግሎት፣ ዲጂታል ኢንቨስትመንትና ኢንሹራንስን ተደራሽ ለማድረግ ይሰራል ብለዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

26 Oct, 09:40


የመኸር እርሻ የስንዴ ክላስቴር በካፋ ዞን ጨና ወረዳ አጃ ባምባ ቀበሌ።

በ30 ሄ/ር ማሳ ላይ እየለማ ያለው የስንዴ ሰብል የአሁናዊ ገፅታ በፎቶ።

Southwest Communications

26 Oct, 09:37


የወከሉትን የማህበረሰብ ክፍል አጀንዳ ለመስጠት ይዘጋጁ፡፡

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍን ለመጀመር ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡

ኮሚሽኑ በዚህ የምክክር ምዕራፍ ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤው የሚሆኑ የአጀንዳ ሀሳቦችን ከክልሉ ባለድርሻ አካላት ይሰበስባል፡፡

በሂደቱም የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን የሚወክሉ ተወካዮች ፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትና ማህበራትን የሚወክሉ ግለሰቦች ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የመንግስት አካላት ዋነኛ ተሳታፊዎች ይሆናሉ፡፡

ስለሆነም በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን በመወከል ተመራጭ የሆናችሁ ተወካዮች የወከላችሁትን የሕብረተሰብ ክፍል በማወያየት የአጀንዳ ሀሳቦችን እየሰበሰባችሁና እያጠናከራችሁ ዝግጅት እንዲታደርጉ ኮሚሽኑ ያሳስባል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም የፖለቲካ ፖርቲዎች ፣ መንግስታዊ ተቋማት እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት እና ማህበራትን እንዲሁም ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችን በመወከል የምትሳተፉ ተወካዮች የምትወክሉትን አካል የአጀንዳ ሀሳብ በአግባቡ ይዛቸሁ እንድትቀርቡ ኮሚሽኑ ጥሪውን ያቀርባል፡፡

ሀገራዊ ምክክር ለሀገራዊ መግባባት!
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን

Southwest Communications

25 Oct, 16:45


#የቦንጋ ከተማ ዉብ የምሽት ገጽታ

ፎቶ፣ቡና ሚዲያና ኮሙኒኬሽን

Southwest Communications

25 Oct, 16:25


የክልሉ ቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን በታጠበ ቡና ምርት ዝግጅትና ጥራት አጠባበቅ ላይ የተግባር ተኮር ስልጠና ሰጠ።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቡና ሻይና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ከክልሉ የምግብ ሥርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም (FSRP) ጋር በመተባበር በታጠበ ቡና ምርት ዝግጅትና ጥራት አጠባበቅ ላይ ለዞንና ወረዳ ባለሙያዎች በቦንጋ ከተማ የተዘጋጀ ስልጠና ተጠናቋል።

በስልጠና መዝግያ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት አቶ በላይ ኮጁአብ የባለስልጣኑ ም/ዳይሬክተር በዘርፉ የተሰማሩ ባለሙያዎች ፈጠራና ፍጥነትን በመጨመር፣ ሙያውንም በማክበር ክልላችንን የቡና ልማትና የግብይት ማዕከል ለማድረግ መስራት ይገባል ብለዋል።

ለውጤታማነቱም በየአካባቢው ያለውን አርሶ አደርን በማደራጀት ግንዛቤ ማስጨበጥ፣ ብድርን ማመቻቸት፣ ጥራት ያለውን ቡና በማምረት ከገበያ ጋር ማስተሳሰር እንደሚገባ አንስተዋል።

ሰልጣኞቹ በካፋ ዞን ማታፋ ምችት የቡና ተክል ኃ/የተወሰነ የግል ማህበር ቡና ማጠቢያ ኢንዱስትሪ የተግባር ስልጠና ወስደዋል ።

የስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው በሰጡት አስተያየት ስልጠናው በዘርፉ የነበረውን የክህሎት ጉድለትን የሚፈታ መሆኑን ገልጸዋል ።

በማጠቢያ ኢንዱስትሪ ዙሪያ ያሉ አርሶ አደሮችን በማስተሳሰር የስራ ዕድል ከመፍጠርም በላይ የግብይት ችግሩን በቅርበት መፍታቱ እንደተሞክሮ እንደሚወሰድ ሰልጣኞቹ አንስተዋል ።

አክለውም በቡና ማጠቢያ ኢንዱስትሪ እየተሰራ ያለዉ ተግባር ከቡና ለቀማ እስከ ግብይት ድረስ ያለውን የጥራት ማነቆን ከመፍታትም ባሻገር ለቴክኖሎጂ ሽግግርና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ለማጠናከር ከፍተኛ ሚና እንደሚኖር አጽንኦት በመስጠት ገልጿል ።

በመድረኩ ላይ ከክልል የባለስልጣኑ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ከዞንና ወረዳ የመጡ የዘርፉ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል ።

በጌታሁን ግርማ

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Southwest Communications

25 Oct, 16:24


ኢትዮጵያ እና አሜሪካ ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር ተስማሙ

ኢትዮጵያ እና አሜሪካ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር ተስማምተዋል፡፡

በገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ የሚመራው ልዑክ ከዓለም ባንክ እና ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት የጋራ ጉባኤ ጎን ለጎን ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ሞሊ ፊ እና የዩኤስ የዓለም አቀፍ ጉዳዮች ግምጃ ቤት ረዳት ጸሐፊ ብሬንት ኒማን ጋር ተወያይቷል፡፡

የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ በኢትዮጵያ ወቅታዊ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በተጨማሪም የማክሮ ኢኮኖሚ ትግበራውን አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል፡፡

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ሞሊ ፊ እና የዩኤስ የዓለም አቀፍ ጉዳዮች ግምጃ ቤት ረዳት ጸሐፊ ብሬንት ኒማን በበኩላቸው የማክሮ ኢኮኖሚ ትግበራው ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው ዜጎች ላይ ጫና እንዳይፈጥር መንግሥት እየወሰዳቸው ያሉ እርምጃዎችን አድንቀዋል፡፡

ሀገራቱ በሁለትዮሽ እና በባለ ብዙ ወገን መድረኮች ያላቸው ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ተስማምተዋል ሲል ኢቢሲ መረጃ ያመለክታል፡፡

ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን 👇
📌በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
📌ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
📌በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
📌በትዊተር twitter.com/sweprs
📌በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
📌በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab 📌በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication