DEBO MEDIA ደቦ ሚዲያ @debo_media Channel on Telegram

DEBO MEDIA ደቦ ሚዲያ

@debo_media


DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹 (Amharic)

ደቦ ሚዲያ (DEBO MEDIA) የመዝናኛና የቁምነገር ፕሮግራሞችና መረጃዎች የሚያገኙበትና የሚቀርቡበት ቻናል ነው። የሚመረጡበት መረጃዎችን ለተቀናጀ ቦታዎች እና ለተይዘው ቦታዎች የመረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን እንሰራለን። በDEBO MEDIA በተጠቃሚ ቻናሉውን ምንም ማደስ አይችልም።nnየDEBO MEDIA ፕሮግራም እና መረጃዎችን ለተቀናጀ በሚወዳደረ እና በአገልግሎት በአሰፋል እንዲሂዋላ ያልፈለገ ነው። ስለዚህ ለመረጃዎችን እና ፕሮግራምን ለመቀነስ ለማንበብ መርህምነት ያሳለፈ አለምንም ማስከበር እንችላለን።nnድረገላዎ መነሻም በቀላሉ በአፕ ሲለዎት ይቃና አገልግሎት ያልተከፈተ እንዲሆኑም ነው። ይኾናቸዋል!
የወገኖቻችንን ፕሮፓጅን ለብቻ ተቀናጀ። ስለዚህ እናመሰግናለን በአሁኑን ጊዜ የለም።nnለተጨማሪ መረጃዎችና ፕሮግራሞች ተጨማሪ የመረጃዎችን በማገኘት በስርጭ እና በማውጣት ከእንጠቀማለን።nnያጋጣል ለማለፍና ተጨማሪ መረጃዎችም ሰርቷል በድምፅ እና በገራገር ጊዜ ዝናኑን ይኖራል ።nnበስለትናቱ ሁሉንም ትግል የሚፈልጉት አስፈነጠላ ድረገላና ቅርምቶችን የሚያይ የስራ አስተሳሰብ በእንቅስቃሴዎ እና በወር አበባዎችዎ በጊዜ ለማድረግ እና ለመመዝገብ የምርት ብሔር ነው። ለመከታወል እና ለመረጃዎችን እና ፕሮግራማውን እንዲሰራጩ ከታክሲ እባክዎ ተጠቀሙ። የሚከታተሉበት ቦታም ዘርፉበታም ።

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

02 Dec, 04:46


ትኩረት

📌ከጥር 2017 አጋማሽ ጀምሮ በአዲስ አበባ አዲስ የባንክ አገልግሎት ለማግኘት ግዴታ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ያስፈልጋል።

📌ከሰኔ ወር 2017 መጨረሻ ጀምሮ ደግሞ በሀገሪቱ ባሉ ሁሉም ትልልቅ ከተሞች ባሉ ባንኮች አካውንት ለመክፈት ፋይዳ ግዴታ ነው

📌በመላው ሀገሪቱ ያሉ ሁሉም ባንኮች ከጥር 2018 ዓ.ም ጀምሮ ፋይዳ መታወቂያን ግዴታ ያደርጋሉ

📌በታሕሳስ 2019 ዓ.ም ነባር የባንክ ደንበኞችም ቢሆኑ ፋይዳ ካልያዙ አገልግሎት አያገኙም መባሉን ሰምተናል።

#ደቦ_ሚዲያ

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

23 Nov, 09:14


ለቴሌቲቪ ቲክቶክ ቻሌንጅ አሸናፊዎች ሽልማት እና ዕውቅና ተሰጠ

የቴሌቲቪ መተግበሪያን ለማስተዋወቅ ባለመው የቲክቶክ ቻሌንጅ ላይ ተሳትፈው ላሸነፉ ቲክቶከሮች ሽልማት ተበርክቷል።

ከሐምሌ 26 ጀምሮ በተደረገው ቻሌንጅ ላይ በርካቶች ተሳታፊ ሲሆኑ ከፍተኛ ዕይታ እና ከፍተኛ  ተወዳጅነትን ያገኙ ተሳታፊዎች ሽልማቱ ተበርክቶላቸዋል።

በ3.4 ሚሊዮን ዕይታ እና 145.7 ተወዳጅነት አንደኛ በመውጣት ነፃነት ታምራት የአይፎን ፕሮማክስ 15 ተሸላሚ ሆናለች።

ያቤፅ በላይ እና ዳዊት ፀጋዬ በተመሳሳይ የ2.1 ሚሊዮን ዕይታ እና በተወዳጅነት ቁጥር ተበላልጠው የ2ኛ እና 3ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል።

በቀጣይም የቴሌቲቪ መተግበሪያ የተለያዩ መሰል ቻሌንጆችን በሚዘጋጀት ይፋ እንደሚያደርግ የቴሌቲቪ መስራች እና ባለቤት አቶ በሱፍቃድ ጌታቸው ተናግረዋል።

ኢግልላየን ሲስተም ቴክኖሎጂ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በአጋርነት ባቀረበው የቴሌቲቪ መተግበሪያ እስከአሁን ድረስ ስምንት ፊልሞችን ተደራሽ በማድረግ ተወዳጅነትን አትርፏል።

#ደቦ_ሚዲያ

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

23 Nov, 06:36


#የተኖረ_ህይወት

የኖራችሁት ወይም ያለፋችሁት የህይወት መንገድና ውጣ ውረድ ለሌሎች ምስክርነት ይሆናል ከኔ ብዙዎች ይማራሉ እንዲሁም ከታሪኬ ብዙ ያተርፋሉ የምትሉ ሁሉ የተኖረ ህይወት በተሰኘው አዲሱ ፕሮግራማችን ላይ እንግዳ እንድትሆኑ የአክብሮት ግብዣችን ነው፡፡

#ደቦ_ሚዲያ
0913302637 በዚህ ስልክ ይደውሉልን ወይም ቴሌግራም ላይ ይፃፉልን፡፡

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

22 Nov, 09:03


የደህንነት መስፈርቶችን ባላሟሉ ተቋማት ላይ ከ10 ሺሕ ብር ጀምሮ ሊያስቀጣ የሚችል መመሪያ ጸደቀ

የተለያዩ የደህንነት መስፈርቶችን ባላሟሉ ተቋማት ከ10 ሺሕ ብር የገንዘብ መቀጮ ጀምሮ እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችለውና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የተዘጋጀው መመሪያ መጽደቁ ተሰምቷል፡፡

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የአደጋ መከላከል ቁጥጥር ፍተሻና ብቃት ማረጋገጥ ስርዓት መመርያ ቁጥር 163/2017ን ያጸደቀ ሲሆን፤ መመርያውን ተግባራዊ በማያደርጉ ተቋማት ላይም ከገንዘብ ቅጣት ጀምሮ ንግድ ፍቃድን እንዲታገድ ፈቃዱን ለሰጠው አካል እስከማሳወቅ የሚደርስ እርምጃን ማካተቱ ተገልጿል፡፡

በቂና ተገቢ የእሳት ማጥፊያ መሳሪያዎችን ያላሟላ፣ በቂ መተላለፊያዎችን ከነሆሱ ያላዘጋጀ፣ አውቶማቲክ የውሃ መርጫ ስርዓትና መለያዎችን (ዲቴክተሮችን) ያላሟላ፣ የኮሚሽኑን የአደጋ ደህንነት ብቃት ማረጋገጫ የሌለው እና ሌሎች ለደህንነት አስፈላጊ የሆኑ ቁሶችን ያላዘጋጀ ተቋም ቅጣቱ እንደሚተላለፍበት ተጠቁሟል፡፡

መመሪያው የከተማዋ ነዋሪዎች ሕይወትና ንብረት እንዲሁም መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማትን ደህንነት ከማንኛውም አደጋዎች እንዲጠበቁ ለማድረግ የወጣ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በተጨማሪም የተቋማትን የአፈጻጸም ለመከታተል የሚያስችል አመቺ ሁኔታዎችን በመፍጠር የሃላፊነትና የተጠያቂነት ስርዓት ለመዘርጋት አስፈላጊ በመሆኑ ኮሚሽኑ መመርያውን እንዳወጣ ተነግሯል፡፡

#ደቦ_ሚዲያ

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

22 Nov, 07:44


በኒውዮርክ ጨረታ ላይ በግድግዳ ላይ የተለጠፈ ሙዝ 6.2 ሚሊዮን ዶላር ተሽጧል!

ይህን አስገራሚ ጨረታ 6.2 ሚሊዮን በማውጣት ያሸነፈው ታዋቂው የክሪፕቶ ነጋዴ ጀስቲን ሰን ሲሆን ድርጊቱም ዓለምን እያነጋገረ ይገኛል።

#ደቦ_ሚዲያ

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

22 Nov, 04:55


መክሊት እስፔሻል ቆሎ በተሻለ ጥራትና በአዲስ አስተሻሸግ በቅርብ ቀን ይጠብቁን
ለበለጠ መረጃ
+251913587837
+251919413787
ይደውሉ

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

21 Nov, 17:25


አስገራሚ መረጃ

ከቀናት በፊት በስፔን ቫሌንሲያ ግዛት ባጋጠመ ድንገተኛ የጎርፍ አደጋ ከ214 በላይ ዜጎች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን በርካቶች ደግሞ በአደጋው ቀያቸውን እንዲለቁ ተገደዋል።

ከማዝናናት ባለፈ ለተለያዩ ማኅበራዊ ጉዳዮች አለሁ የሚለው እግርኳስም በዚህ ሳምንት ከአደጋው ጋር በተያያዘ ያስመለከተን ነገር ልብን የሚያሞቅ ነው።

በስፔን ሴጉንዳ ዲቪዚዮን ሌቫንቴ ኤልቼን ባስተናገደበት መርሐ-ግብር "እንቁራሪቶቹ" የሚል ቅፅል ስም ያላቸው ሌቫንቴዎች በጨዋታው ለብሰውት ወደ ሜዳ የገቡት መለያ ሙገሳ እንዲቸራቸው አድርጓል። በዚህም ሁሉም ተጫዋቾች በከተማው የደረሰውን የጎርፍ አደጋ በማሰብ ጭቃ የተለወሰ እንዲሁም ከወገኖቻቸው ጎን መሆናቸውን የሚያሳይ ማሊያ ለብሰው ወደ ሜዳ ገብተዋል። ማሊያዎቹም በጨረታ ተሸጠው ድጋፍ ለሚሹ የአደጋው ተጠቂዎች እንዲውሉ ተደርጓል።

#ደቦ_ሚዲያ

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

07 Nov, 09:41


ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር ተያይዞ በወንጀል የተከሰሱት እነ ዮሃንስ ዳንኤል የእምነት ክህደት ቃላቸውን ሰጡ

ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር ተያይዞ በወንጀል የተከሰሱት እነ ዮሃንስ ዳንኤል (ጆን ዳንኤል) የእምነት ክህደት ቃላቸውን ሰጡ።

ዮሃንስ ዳንኤል (ጆን ዳንኤል)፣ አማኑኤል መውጫ፣ ናትናኤል ወንድወሰን፣ ኤልያስ ድሪባ፣ ይዲድያ ነጻነት እና እሌኒ ክንፈ የተባሉ ስድስት ተከሳሾች የኢትዮጵያ አየር መንገድ ደህንነትን አደጋ ላይ ለመጣል ተንቀሳቅሰዋል በሚል የቀረበባቸው ክስ ላይ የወንጀል ድርጊት እንዳልፈጸሙ ጠቅሰው በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ ልዩ ልዩ ከባድ ወንጀል ችሎት ዛሬ ቀርበው የእምነት ክህደት ቃላቸውን ሰጥተዋል።

የፍትህ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ በተከሳሾቹ ላይ ከአንድ ወር በፊት አውሮፕላንን ያለአግባብ መያዝ ወንጀል፣ የመንግስት ሰራተኛ የስራ ግዴታውን እንዳይፈጽም መቃወምና አለመታዘዝ ወንጀል ክስ እንዲሁም በ1ኛ ተከሳሽ ብቻ ደግሞ የአየር መንገዱን መልካም ስም ለሚያጎድፍ በተንቀሳቃሽ ምስል በኮምፒውተር ስርዓት አማካኝነት ማሰራጨት ወንጀል የሚል ክስ ማቅረቡ ይታወሳል።

ተከሳሾቹ የክስ ዝርዝር ከደረሳቸው በኋላ ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄያቸው ውድቅ ተደርጎ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ በተሰጠ ትዕዛዝ መሰረት ከማረሚያ ቤት ቀርበው ጉዳያቸውን ተከታትለዋል።

የተከሳሾች ጠበቆች የክስ ዝርዝሩ እንዲሻሻል የመጀመሪያ ደረጃ የክስ መቃወሚያ ሲያቀርቡ፤ ከሳሽ ዐቃቤ ሕግ ደግሞ የክስ ዝርዝሩ ሊሻሻል አይገባም የሚል መልስ በጽሁፍ ሰጥቷል፡፡

ፍርድ ቤቱ የቀረበውን የክስ መቃወሚያ እና የዐቃቤ ሕግ መልስን መርምሮ በዛሬ ቀጠሮ ተከሳሾቹ ያቀረቡት የክስ መቃወሚያ ፍሬ ነገር ወደ ፊት በማስረጃ የሚጣራ መሆኑን ጠቅሶ ውድቅ አድርጎታል።

ከዚህም በኋላ ተከሳሾቹ በክሱ ዝርዝር የተገለጸውን የወንጀል ድርጊት ሰለመፈጸም አለመፈጸማቸው በፍርድ ቤቱ በቀረበላቸው ጥያቄ መሰረት "የወንጀል ድርጊቱን አልፈጸምንም " በማለት የእምነት ክህደት ቃላቸውን ሰጥተዋል።

ከሳሽ ዐቃቤ ሕግ ለወንጀሉ መፈጸም ያስረዱልኛል ያላቸው ምስክሮች ቃል እንዲሰማለት በጠየቀው ተለዋጭ ቀጠሮ መሰረት የምስክር ቃል ለመስማት ለሁለት ቀን ማለትም ለሕዳር 18 እና ለሕዳር 19 ቀን 2017 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

Via በታሪክ አዱኛ

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

07 Nov, 09:03


ፊናፍ ፊልም በቴሌቲቪ መተግበሪያ ዛሬ መታየት ይጀምራል

ፊናፍ ፊልም በቴሌቲቪ መተግበሪያ ከዛሬ ጥቅምት 26 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለህዝብ መታየት ይጀምራል።

በቢቂላ አስፋው ተጽፎ የተዘጋጀው ፊናፍ ፊልም አንጋፋ እና አዳዲስ ተዋንያኖች ተሳትፈውበታል።

በኦሮምኛ ቋንቋ የተሰራው ፊናፍ ፊልም ከዛሬ ሁለት ዓመት በፊት በግል እና በመንግስት ሲኒማ ቤቶች ለተመልካች እይታ ቀርቦ ነበር።

በወቅቱም ከተመልካች አዎንታዊ ምላሽ ማግኘት የቻለ ተወዳጅ ፊልም ነው ።ፊናፍ የድራማ ዘውግ ያለው 1 ሰዓት ከ 45 ደቂቃ የሚረዝም ፊልም ሲሆን ''English Subtitle '’ እንዳለው አቶ ቢቂላ አስፋው ገልጸዋል።

በጉማ ፣ ኦዳ እና ለዛ አዋርዶች እጩ መሆን የቻለው ይህ ፊልም በ9ኛው የጉማ አዋርድ ላይም ተስፋ የተጣለበት ተዋናይ የውድድር ዘርፍ ብሩክ ግርማ ከፊናፍ ፊልም አሸናፊ መሆን ችልዋል።

ቴሌቲቪን ፊልማቸውን ለማሳየት ተስማሚ ምርጫ ሆኖ እንዳገኙት የተናገሩት አቶ ቢቂላ ፤ ብዙሃኑ ህብረተሰብ ጋር ለመድረስ ድንቅ አማራጭ መሆኑን ተናግረዋል።

ቴሌቲቪ በቅርቡ የራስ መንገድ የተሰኘ ፊልምን ወደ መተግበሪያው ማስገባቱ የሚታወቅ ሲሆን ፣ከርቤ የተሰኘ አዲስ ፊልምም አሁን ላይ በመተግበሪያው ላይ ይገኛል።

ከነዚህ ፊልሞች በተጨማሪም ዘጋቢ ፊልሞችንም በቴሌቲቪ መተግበሪያ ላይ ተመልካቾች በነጻ ማግኘት እንደሚችሉ የኢግል-ላይን መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ በእርሱፊቃድ ጌታቸው ገልጸዋል።

ቴሌቲቪ በኢግልላይን ሲስተም ቴክኖሎጂ ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያዉያን እዚሁ ሃገራችን ዉስጥ የበለጸገ ፕላትፎርም ነው።

አሁን ላይ በቴሌቲቪ መተግበሪያ ፊናፍ ፊልምን ጨምሮ 8 የተመረጡ ሃገርኛ ፊልሞች ይገኙበታል።

#ደቦ_ሚዲያ

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

06 Nov, 10:18


የቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን : “ጓደኛዬ ትራምፕ እንኳን ደስ አለህ ማለት እፈልጋለሁ።”

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

06 Nov, 08:32


ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር አብይ አሕመድ ለዶናልድ ትራምፕ የእንኳን ደስ አሎት መልዕክት አስተላልፈዋል።

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

06 Nov, 08:28


የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ለዶርናድ ትራምፕ የእንኳን ደስ አሎት መልዕክት አስተላልፈዋል።

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

06 Nov, 07:39


የኤልሳልቫዶር ፕሬዜዳንት ማንም ሳይቀድማቸው ከወዲሁ ለዶናልድ ትራምፕ የ ' እንኳን ደስ አልዎት ! ' የደስታ መልዕክት መልዕክት ያስተላለፉ የመጀመሪያው የሀገር መሪ ሆነዋል።

ፕሬዝዳንት ናይብ ቡክሌ ፤ ትራምፕን ተመራጩ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ሲሉ ጠርተዋቸው " እንኳን ደስ አለህ ! አምላክ ይባርክህ ፤ ይምራህ  " ብለዋቸዋል።

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

06 Nov, 07:32


“በአጠቃላይ 315 የሚጠጉ ድምፆችን አግኝቻለሁ።” - ትራምፕ

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

06 Nov, 07:00


ሰበር ዜና

ዶናልድ ትራምፕ 47ኛው የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ሆነው መመረጣቸውን Fox news ዘግቧል።

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

06 Nov, 04:57


ትራምፕ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫውን እየመሩ ነው

የአለም ፖለቲካ ዘዋሪዋ  ሀገር አሜሪካ 47ተኛውን ፕሬዝዳንቷን በመምረጥ ላይ ትገኛለች።

ፉክክሩ የጋለው እና እጩዎቹ  አንገት ለአንገት የተያያዙበት ምርጫ ውጤት በዚህ ሰዐት የሪፐብሊካኑ ዶናልድ ትራምፕ እየመሩ ይገኛሉ።

የዲሞክራቷ እጩ ካማላ ሀሪስም ሆኑ ሪፐብሊካኑ ዶናልድ ትራምፕ ለሀገራቸው ይበጃል ብለው የያዟቸው ፖሊሲዎች አሜሪካውያንና የቀረውን አለም ቀልብ ስቦ የምርጫውን ውጤት አለም በጉጉት እንዲከታተል አድርጎታል።

እስከመጨረሻ ውጤቱን ለመገመት አስቸጋረ የሚሆነው 47ተኛው የአሜሪካ ምርጫ ፉክክር ማንን ፕሬዝዳንት ያደርግ ይሆን?

አሁንም የሁለቱን ፉክክር እና ውጤት ለማወቅ "ስዊንግ ስቴት" የሚባሉትን 7 ግዛቶች የምርጫ ውጤት መጠበቅ አስገዳጅ ነው።

ካማላ ሀሪስ እስካሁን በብዙ ሴቶች በመመረጥ  ቅድሚያውን ቢይዙም በአጠቃላይ የምርጫ ሂደቱ በሪፐብሊካኑ እጩ ዶናልድ ትራምፕ እየተመሩ ይገኛሉ።

አሁን ላይ ባለው መረጃ ትራምፕ ምርጫውን የማሸነፍ ዕድላቸው ወደ 89% ከፋ ማለቱ እየተዘገበ ነው::

#ደቦ_ሚዲያ

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

05 Nov, 11:50


ኢትዮጵያ ፤ ለደቡብ ሱዳን ከ738 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ብድር ሰጠች ተባለ

በአለም አዲስ አገር ለሆነችው ደቡብ ሱዳን የተሰጠው ብድር በሁለቱ አገራት መካከል አገናኝ ለሚሆን መንገድ ግንባታ የሚውል ነው።

የአራት አመት እፎይታ ኖሮት በ10 አመታት ተከፍሎ የሚጠናቀቀው ብድር ከ738 ሚሊየን ዶላር በላይ ነው።

በደቡብ ሱዳን ድንበር ውስጥ የሚገነባው 220 ኪሜ መንገድ በኢትዮጵያ ተቋራጮች እና አማካሪዎች እንዲከናወን በሁለቱ አገራት ከስምምነት መደረሱ ተገልጿል።

የብድር አመላለሱም በካሽ እና በድፍድፍ ነዳጅ እንደሚሆን ነው የተጠቀሰው።

Via ካፒታል
#ደቦ_ሚዲያ

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

05 Nov, 11:40


የኢትዮጵያ አየር መንገድ የገዛው ኤ350-1000 አውሮፕላን አዲስ አበባ ገባ

በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን ኤ350-1000 "Ethiopia land of origins" የሚል ስያሜ የተሰጠው የመንገደኞች አውሮፕላን በዛሬው ዕለት  አዲስ አበባ ገብቷል።

#ደቦ_ሚዲያ

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

31 Oct, 19:18


በእንቅልፍ ወቅት የምናያቸውን ሕልሞች እንደፊልም ደግመን ለማየት የሚያስችለን ቴክኖሎጂ ይፋ ሆነ

የጃፓን ተመራማሪዎች በእንቅልፍ ወቅት የሚከሰቱ ሕልሞችን በመቅረፅ በፊልም መልክ የሚያጫውት መሣሪያ ይፋ አድርገዋል፡፡

ተመራማሪዎቹ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ እና የአዕምሮ ምስልን መውሰድ የሚችሉ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም፤ ሕልምን የሚመዘግብና በፊልም መልክ የሚያሳይ መሣሪያ መፍጠር ችለዋል፡፡

ቴክኖሎጂው ከሕልም ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የነርቭ እንቅስቃሴዎችን ለመመዝገብ ኤም.አር አይ (magnetic resonance imaging) እንደሚጠቀም ተገልጿል፡፡

ይህ ፈጠራ የአንጎል እንቅስቃሴን በመጠቀም አንዳንድ የሕልም ገጽታዎችን የመግለጽ  አቅም እንዳለውም ነው የተነገረው።

በቴክኖሎጂው ላይ በተደረገ ሙከራ ያለሙትን ሕልም ይዘት ሳይቀይር የመተንተን አቅሙ ከ70 በመቶ በላይ ትክክል ሆኖ መገኘቱን ኒውስ18 የተባለው ድረ ገጽ ዘግቧል፡፡

ቴክኖሎጂው የአዕምሮ ጤናን ለማሻሻል፣ የግለሰቦችን ስብዕና ለመተንተን እና ከሥነ-ልቦና ጋር ተያያዥ በሽታዎችን ለመመርመር ጥቅም ላይ እንደሚውል ተመላክቷል፡፡

መሣሪያው ዕውን መሆን የቻለው በኪዮቶ በሚገኘው የኤ.ቲ.አር (ATR) ኮምፒውቲሽናል ኒውሮሳይንስ ላቦራቶሪዎች ውስጥ በተደረገ ጥናት መሆኑን ከኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

30 Oct, 18:22


ከመገናኛ ዐደባባይ ወደ ቦሌ የሚወስደው መንገድ በሁለቱም አቅጣጫ ለተሽከርካሪ ዝግ ሆኗል

ከመገናኛ ዐደባባይ ወደ ቦሌ እና ከቦሌ ወደ መገናኛ ዐደባባይ ያለው መንገድ በሁለቱም አቅጣጫ ላልተወሰነ ጊዜ ለተሽከርካሪ ዝግ መሆኑን የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን አስታውቋል፡፡

በመገናኛ አካባቢ ያለውን ከፍተኛ የትራንስፖርት መጨናነቅ ለመፍታት የሚያግዝ የመሬት ውስጥ የእግረኛ መተላላፊያ መስመር ግንባታ መጀመሩንም ነው ባለስልጣኑ ያስታወቀው፡፡

ለዚሁ ሥራ ሲባልም ከመገናኛ ዐደባባይ ወደ ቦሌ እና ከቦሌ ወደ መገናኛ ዐደባባይ ያለው መንገድ በሁለቱም አቅጣጫ ለተሽከርካሪ ዝግ ሆኗል ብሏል::

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

30 Oct, 17:12


የኢትዮጵያ አየር መንገድ ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ ሽልማትን አሸነፈ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓመታዊው APEX Passenger Choice Awards 2025፣ ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ “Best Overall in Africa award” ሽልማት አሸንፏል፡፡

አየር መንገዱ በዚህ የሽልማት አሰጣጥ መርሓ ግብር ላይ በምርጥ የበረራ ላይ መስተንግዶ፣ በምርጥ የበረራ ላይ መዝናኛ አገልግሎት፣ በምርጥ የበረራ ላይ  የምግብ እና መጠጥ አገልግሎት፣ በምርጥ የአውሮፕላን ውስጥ መቀመጫ ምቾት እንዲሁም በምርጥ የበረራ ላይ ገመድ አልባ ኢንተርኔት አገልግሎት ዘርፎች ከአፍሪካ ምርጡ አየር መንገድ በመሆን ተሸልሟል።

ይህ በ “Airline Passenger Experience Association” (APEX) የመንገደኞችን ድምፅ መሰረት በማድረግ ለአየር መንገዶች ዕውቅና የሚሰጥበት መድረክ በአቪዬሽን ኢንደስትሪው ትልቅ ስፍራ ከሚሰጣቸው ሽልማቶች አንዱ ሲሆን በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚገኙ አየር መንገዶች ለሚያቀርቡት የላቀ የደንበኞች አገልግሎት ዕውቅና የሚሰጥበት ነው።

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

27 Oct, 12:03


#የተኖረ_ህይወት

የኖራችሁት ወይም ያለፋችሁት የህይወት መንገድና ውጣ ውረድ ለሌሎች ምስክርነት ይሆናል ከኔ ብዙዎች ይማራሉ እንዲሁም ከታሪኬ ብዙ ያተርፋሉ የምትሉ ሁሉ የተኖረ ህይወት በተሰኘው አዲሱ ፕሮግራማችን ላይ እንግዳ እንድትሆኑ የአክብሮት ግብዣችን ነው፡፡

ደቦ ሚዲያ
0933331533 በዚህ ስልክ ይደውሉልን፡፡

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

26 Oct, 14:47


የታላቁ የእግር ኳስ ሰው አሥራት ኃይሌ የሽኝት መርሐ ግብር ነገ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይካሄዳል

በትናንትናው ዕለት ህልፈተ ህይወታቸው የተሰማው የቀድሞ ተጫዋች እና አሰልጣኝ አሥራት ኃይሌ ሥርዓተ ቀብር ነገ ይካሄዳል። ከዛ አስቀድሞ ቦሌ ከሚገኘው መኖርያ ቤት 5:00 ላይ በመነሳት ከ6:00-7:00 ታሪክ በሰሩበት አዲስ አበባ ስታዲየም የሽኝት መርሐ ግብር የሚከናወን ሲሆን በመቀጠል 7:00 ላይ ለገሀር በሚገኘው መድሀኔዓለም የካቶሊክ ቤተ-ክርስቲያን የፀሎት መርሐ ግብር ተከናውኖ ሥርዓተ ቀብራቸው ከቀኑ 9:00 በጴጥሮስ ጳውሎስ መካነ መቃብር ይካሄዳል።

መላው የስፖርት አፍቃሪም የሀገር ባለውለታው አሥራት ኃይሌ የሽኝት መርሐ ግብር እና ሥርዓተ ቀብር ላይ እንዲገኝ ጥሪ ቀርቧል።

በስታዲየም በሚካሄደው መርሐ ግብር ላይ የመታሰብያ አበባ ማስቀመጥ የምትፈልጉ ክለቦች እና ተቋሟት በስልክ ቁጥር +251 91 162 0384 ያናግሩን

አስተባባሪ ኮሚቴው

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

25 Oct, 17:49


አስራት ኃይሌ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

በኢትዮጵያ እግርኳስ ታሪክ በተጫዋችነት እና በአሰልጣኝነት ስሙን በደማቅ ያሰፈረው አስራት ኃይሌ ማረፉ ተሰምቷል።

አስራት ኃይሌ ባጋጠመው ከባድ ህመም ምክንያት ለአንድ አመት ከሶስት ወራት ያህል ጊዜ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር ህክምናውን ሲከታተል ቆይቶ ነበር።

ከውጪ ከተመለሰ በኋላ በቤቱ ሆኖ ህክምናውን ሲከታተተል የቆየው አስራት ዛሬ አመሻሹን ይህችን አለም ተሰናብቷል።

ጎራዴው በሚል ቅፅል ስም የሚታወቀው አስራት ከ60 ዓመታት በላይ በዘለቀው የተጫዋችነት እና የአሰልጣኝነት ዘመኑ በርካታ ስኬቶችን አስመዝግቧል።

በተለይም እ.አ.አ በ2005 በሩዋንዳ በተደረገው የሴካፋ ውድድር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን በዋና አሰልጣኝነት እየመራ ሻምፒዮን ማድረጉ የሚታወስ ነው።

ደቦ ሚዲያ ለአስራት ኃይሌ ቤተሰቦች ፣ ጓደኞች ፣ ወዳጆች እና ለመላው የእግርኳስ ቤተሰብ በሙሉ መፅናናትን ይመኛል።

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

23 Oct, 19:11


በሌብነት ዘርፍ ለተሰማሩ መርዶ ለተሰራቂዎች ብስራት የሆነው ዜና !!

ዓለም አቀፍ የጎግል ኩባንያ የተሰረቁ ሞባይል ቀፎዎች ዳግም እንዳይሰሩ የሚያደርግ ፈጠራ መተግበሩን አስታውቋል ። ኩባንያው ኤአይን በመጠቀም ስልካቸውን የተሰረቁ ሰዎች ወደ ስልኩ አምራች ተቋም ሪፖርት የሚያደርጉበት አሰራርን ዘርግቻለሁ ብሏል።

አዲሱ የጎግል አሰራር የስልክ ንጥቂያ ወንጀሎችን ሊቀንስ እንደሚችል ተገልጿል። ሌቦች የስልክ ቀፎን ከወሰዱ በኋላ ለመደበቅ ቢሞክሩ እና ዳግም ጥቅም ላይ ለማዋል ሲሞክሩ ኤአይን በመጠቀም ለዘለቄታው ከአገልግሎት ውጪ እንዲሆን የሚያደርግም ነው ።

ለአንድሮይድ ስልክ የተገጠመለት ኤአይ ቴክኖሎጂ ቀፎው ላይ በተገጠመለት ሴንሰር አማካኝነት እንዳይከፈት አድርጎ መዝጋት ይችላልም ተብሏል፡፡

#ደቦ_ሚዲያ

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

22 Oct, 15:06


ምርጫ ቦርድ 11 ፓርቲዎችን ለጊዜው አገደ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 12፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በጠቅላላ ጉባዔ፣ በኦዲት እና በሴት አባላት አማካኝነት ከሚገኝ የገንዘብ ድጋፍ ጋር በተያያዘ 11 የፖለቲካ ፓርቲዎችን ማገዱን ለኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አሳወቀ፡፡

ፓርቲዎቹም÷የኦሮሞ ነጻነት ንቅናቄ፣ አንድ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ የጌዲኦ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት፣ የሐረሪ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት፣ የገዳ ሥርዓት ለኦሮሞ ነጻነት ፓርቲ፣ የዎላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ፣ አዲስ ትውልድ ፓርቲ፣ የጋምቤላ ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ፣ የጋምቤላ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ፣ የኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ኅብረት እና አገው ለፍትሕና ለዴሞክራሲ ፓርቲ ናቸው፡፡

በፓርቲዎቹ ላይ የተሰጠው የዕግድ ውሳኔም ቦርዱ የተለየ ውሳኔ እስከሚሰጥ ድረስ ለጊዜው ከማንኛውም ሕጋዊ እንቅስቃሴ ታቅበው እንዲቆዩ የሚያደርግ ነው፡፡

የዕግድ ውሳኔውን ቦርዱ እስከሚያነሳ ድረስም ከላይ የተገለጹት ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤቱ በሚያዘጋጃቸው ጉባዔዎች ላይ ሊገኙ፣ ሊመርጡም ሆነ ሊመረጡ እንዲሁም በኮሚቴ አባልነት ሊያገለግሉ አይችሉም ተብሏል፡፡

የጋራ ምክር ቤቱ የዕግድ ውሳኔ የተላለፈባቸውን ፓርቲዎች ከማንኛውም የምክር ቤቱ ሥራዎች እና እንቅስቃሴዎች እንዳይካፈሉ እንዲያደረግ ቦርዱ አሳስቧል፡፡

#ደቦ ሚዲያ

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

13 Oct, 12:22


https://youtu.be/4tUCBee7rpQ?si=FERi92WkN6YBeQJB

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

04 Oct, 21:47


Baga Geechan/ እንኳን አደረሳችሁ !

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

24 Sep, 20:56


አዲስ  በ notcoin የተዘጋጀ ትልቅ Project መጥቷል እሱም Not Pixel  ይባላል

Not Pixel  ልክ እንደ Lost Dog  በ NOTCOIN የተዘጋጀ ትልቅ project  ስለሆነ እንዳያመልጣችሁ  ቀድማችሁ ብትሰሩት መልካም ነው 

Not Pixel ሰርተን ስንጨርስ $NOTPX የሚባለውን  የራሳቸውን Token ነው የምናገኘው 🤝
ማወቅ ያለባችሁት ነገር Not Pixel በ Notcoin   Launch የተደረገ  Project ነው
Notcoin official ቴሌግራም ቻናላቸው ላይ  ስለ Not Pixel ደጋግመው አስተዋውቀዋል " 
Notcoin  "Dogs ' Lostdog " Notpixel
ብዙ Pixel  ለማግኘት    

Notpixel Board ላያ በደንብ paint አድርጉ በጭራሽ ችላ እንዳትሉ ' እያንዳንዷ ዋጋ አላት 🙏
- task ስሩ
-ጓደኞቻችሁን ጋብዙ

👌በደንብ  አትኩራችሁ ብትሰሩት መልካም ነው ቤተሰብ  "

አሰራሩን screen record አድርጌ እለቅላችኋለው🙏

ለመጀመር 👇https://t.me/notpixel/app?startapp=f414459533

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

22 Sep, 11:01


https://youtu.be/0PMsR1L68no?si=0VihvyW180Glilyp

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

15 Sep, 17:09


https://youtu.be/gqG0p_wwQ4w?si=RnH8eJYhKQ3mqzbG

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

10 Sep, 20:06


ለመላው ኢትዮጵያውያን እንዲሁም ለደቦ ሚዲያ ቤተሰቦች መልካም አዲስ ዓመት እያልን አመቱም የሰላም የጤና የስኬት እንዲሆንላችሁ መልካም ምኞታችን ነው።

#ደቦ_ሚዲያ

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

05 Sep, 12:49


Channel photo updated

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

05 Sep, 12:31


Channel name was changed to «DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹»

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

25 Aug, 11:03


https://youtu.be/39cXljxi43w?si=Tp1IyFoDYWinTNzW

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

17 Aug, 18:37


ኢትዮዽ እስክስታ ፊትነስ #3ኛ_አመት_ኮንሰርት ተዘጋጅቷል

#ቅዳሜ በ18/12/2016 ዓ.ም ከቀኑ 11 ጀምሮ
#በአያት 5 ኮንዶሚኒየ ሀይሌ ጉዲና ህንፃ oxygen gym አዲስ ባስገነባው ቦታ ይሆናል!


ሁላችሁም ተጋብዛችኃል ኑና አብረን ቆንጆ ጊዜ እናሳልፍ!

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

14 Aug, 18:06


https://youtu.be/dXhwwWY7qYg?si=ANNB4U4Z_8NL7unn

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

11 Aug, 11:04


https://youtu.be/tj_bNGB66v8?si=N0zbmFDfabe2Pyid

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

10 Aug, 17:58


👉youtube:-https://www.youtube.com/channel/UCX2W3W-y6fSJbxXCIc7WTEQ

👉TikTok:-http://tiktok.com/@debo.podcast

👉Facebook:-https://www.facebook.com/profile.php?id=61559123975938

👉Telegram:-https://t.me/debopodcast

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

07 Aug, 18:04


https://youtu.be/V02Cq5ovsEE?si=9WZM16e1UDqtIt8a

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

04 Aug, 11:02


https://youtu.be/CW6J-GLxrJ0?si=3b97s308gou6UppW

DEBO MEDIA /ደቦ ሚዲያ🇪🇹

04 Aug, 11:01


#ተከፈተ 📸🎥

THON MULTIMEDIA PRODUCTION 📸🎥

ዘመኑን በዋጁ የፕሮዳክሽን ዕቃዎችና ልዮ ተደርጎ በተሰራው ዘመናዊና ውብ ስቱዲዮ ስራችንን ጀምረናል

የምንሰጣቸው አገልግሎቶች
👉 ለተለያዩ ኢቨንቶች
👉 ለሰርግ
👉 ለፋሽን ሾው
👉 ለፊልም እንዲሁም ለዶክመንተሪ
👉 ለማስታወቂያ ስራዎች
👉 ለቤቢ ሻወር
👉 ለብራይዳል
👉 ለልደት

#በተጨማሪም ለተለያዮ የTV እና YOUTUBE ሾው የእስቱዲዮና ሙሉ የፕሮዳክሽን ዕቃዎች የኪራይ አገልግሎት እንሰጣለን

#ይምጡ በስራችን ረክተውና ተደስተው ይመለሳሉ።

አድራሻችን:-አዲስ አበባ/ቤተል መስጂድ አጠገብ/ኤጄ ሞል ላይ መገኛችን ነው

ስልክ ቁጥራችን:-+251921327339