Gurage Zone Government Communication Affairs @comminuca Channel on Telegram

Gurage Zone Government Communication Affairs

@comminuca


Gurage Zone Government Communication Affairs

Gurage Zone Government Communication Affairs (English)

Welcome to the Gurage Zone Government Communication Affairs Telegram channel, where you can stay informed about all the latest news and updates from the Gurage Zone government. This channel is dedicated to providing transparent and reliable information to the residents and stakeholders of the Gurage Zone. Whether you are a local resident, a business owner, or simply interested in the development of the region, this channel is the go-to source for all official communications. The Government Communication Affairs channel covers a wide range of topics, including updates on infrastructure projects, community events, public services, and government policies. By joining this channel, you will have direct access to official announcements, press releases, and statements from the Gurage Zone government. Stay connected and informed by subscribing to the Gurage Zone Government Communication Affairs channel today! Follow us at @comminuca for all the latest updates and news.

Gurage Zone Government Communication Affairs

14 Feb, 15:46


የካቲት 7/2017 ዓ.ም
የተማሪዎች ምገባ ፕሮግራም ማስጀመር ለትምህርት ጥራትና ንቁ ትልድ ለመፍጠር ከፍተኛ ሚና እንዳለው የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ ገለጸ።

በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ ለቅድመ መደበኛ ተማሪዎች የምገባ ፕሮግራም በሰላም በር 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በዛሬው እለት በይፋ ተጀምሯል።

የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ መብራቴ ወልደ ማርያም ምገባው ባስጀመሩበት ወቅት እንዳሉት በዞኑ በ42 ቅድመ አንደኛ ጣቢያዎች በማህበረሰብና በአጋር ድርጅቶች ድጋፍ ምገባ በሙከራ ደረጃ ለማስጀመር ቅድመ ዝግጅት ተደርጎ ወደ ተግባር መገባቱ አስታውቀዋል።
በዛሬው እለትም እንደ ዞን ወልቂጤ ከተማ ጨምሮ በምሁር አክሊል እና በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ምገባ ተጀምሯል።

አቶ መብራቴ እንደገለጹት አንድ አንድ ህጻናት ምግብ ሳይበሉ ወደ ትምህርት ቤት የሚገቡና ሲመልሱም ምግብ የማያገኙ እንዳሉ አመላክተው በዚህ ችግራቸው ትምህርት መማር አስቸጋሪ ነበር።

ስለሆነም ምገባው መጀመሩ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው እንዳይቀሩ፣ የትምህርት ጉጉት እንዲኖራቸው ከማድረጉም ባለፈ በትምህርት ውጤታቸው ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት አንስተዋል አቶ መብራቴ።

ምገባው መጀመሩ ተማሪዎች ረጅም ሰዓት ሳይራቡ በትምህርት ቤት እንዲቆዩ ከማድረገም ባሻገር የትምህርት ፍላጎታቸው እንዲጨምር እና ቀጣይ ንቁ ትውልድ ለማፍራት ሚናው የላቀ ነው ብለዋል።

በመሆኑም በዛሬው እለት በወልቂጤ ከተማ የተጀመረው የምገባ ፕሮግራም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ተግባሩ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አቶ መብራቴ አሳስበዋል።

የወልቂጤ ከተማ ምክትል ከንቲባና የጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙባረክ ዘይኑ በበኩላቸው ለተማሪዎች ምገባ መጀመሩ የትምህርት ፍላጎታቸው እንዲጨምር፣ መጠነ መቅረት ከመቀነሱም ባለፈ መቀንጨርን በመቀነስ ጤናማ ትውልድ እንዲፈጠር ያደርጋል ነው ያሉት።

አክለውም በህጻናት ላይ የሚከሰቱ ተያያዥ በሽታዎች የመከላከል አቅም ይፈጥርላቸዋል ያሉት አቶ ሙባረክ ትምህርት ቤቱ ወቅቱን ታሪኩን የሚመጥን ተቋም ለማድረግ በጋራ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

የወልቂጤ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ስሜነሽ ግርማ የትምህርት መሰረት የሚጣለው ከቅድመ አንደኛ ጀምሮ ነው።ስለሆነም ለቅድመ አንደኛ ተማሪዎች ትኩረት መስጠት የትምህርት ውጤት እንዲሻሻል የማይተካ ሚና እንዳለው ተናግረዋል።

የተማሪዎች የምገባ ፕሮግራም፦ለህጻናት ብሩህ አእምሮ ፣ለተሻለ የትምህርት አቀባበል እና ያለ እረሀብ ሰፊ ጊዜ እንዲማሩ ያደርጋል ሲሉ ገልጸዋል።

በከተማው በ3 ቱም ክፍለ ከተሞች ከ9 መቶ በላይ የቅድመ አንደኛ ተማሪዎች በዛሬው እለት ምገባ መጀመሩ አስገንዝበዋል።

ኃላፊዋ አክለውም ይህ የምገባ ፕሮግራም ደግሞ የተማሪ የምግብ እጥረት ችግሮችን በመቅረፍ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ጥቅም የሚያስገኝ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የተጀመረው የተማሪዎች ምገባ ፕሮግራም ቀጣይነት እንዲኖረው ከአጋር ድርጅቶች እና ከወላጆች ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ ገለጸው እገዛቸው እንዲያጠናከሩም ወ/ሮ ስሜነሽ አሳስበዋል።

Gurage Zone Government Communication Affairs

12 Feb, 13:44


የካቲት 5/2017 ዓ.ም
የህብረተሰቡ ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማረጋገጥ በፓርቲው የተገኙ ውጤቶች በማጠናከርና ችግሮችን በመለየት ብልጽግናን እውን ማድረግ እንደሚገባ ተገለጸ።

"መፍጠን እና መፍጠር ፣ለጉባኤያችን ውሳኔዎች ስኬት " በሚል መሪ ሀሳብ በጉራጌ ዞን በ2ኛው የብልጽግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ውሳኔዎች እና አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ የአመራር የውይይት መድረክ በወልቂጤ ከተማ ተካሂዷል።

የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ገብሬ ጋጌ ብልጽግና ፓርቲ በብዙ ፈተናዎችን እየተወጣ አመርቂ ለውጦች እያመጣ ያለ ፓርቲ ነው።

በክልሉ እንዲሁም በዞኑ ከፌደራል ጀምሮ በተደረጉ የሱፐርቪዥን ስራዎች የታዩ ተግባራት ሞዴል መሆናቸው እና ክልልሉም በትክክለኛ መስመር ያለ ክልል እንደሆነ መታወቁ አስገንዝበዋል።

እነዚህ የተመዘገቡ አመርቂ ውጤቶች ዘላቂነታቸው ለማረጋገጥ የበለጠ መትጋት እንደሚያስፈልግና የአገልግሎት አሰጣጣችንን በማሳደግ በመመሪያና ደንቦችን ተከትሎ መስራት ይጠበቃል ብለዋል።

በየ ቦታው የሚነሱ የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመፍታት የበለጠ ተግቶ መስራት ይገባል ያሉት አቶ ገብሬ ግጭት የሚያስነሱ አካላት መታገልና ለህግ ማቅረብ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።

የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ የህብረተሰቡ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሁሉም ዘርፎች ምርትና ምርታማነትን ማረጋገጥ ላይ በትኩረት መስራት ያስፈልጋል።

በዞኑም በተለይ በግብርና ፣በትምህር፣በጤና ፣በመንገድ በስራ እድል ፈጠራ ፣በገቢ ፣በውሃ ፣በሰላምና ጸጥታ ዘርፎች በአጽንኦት እየተሰራ ሲሆን በዚህም አመርቂ ለውጦች መጥተዋል ብለዋል አቶ ላጫ

ህገ ወጥነትን መከላከል ፣ፍትህን ማስፈን ፣ብልሹ አሰራሮችን መታገል የሁሉም ተግባር ሊሆን እንደሚገባና አገልግሎት አሰጣጣችንን በማስተካከል ዘመን ተሻጋሪ ስራዎች መስራት ይጠበቃል ሲሉ ተናግሯል።

የተለያዩ አደረጃጀቶችን ማጠናከር ለብልጽግና መሳካት ወሳኝ በመሆኑ አደረጃጀቶችን ማጠናከር ይገባል ያሉት አቶ ላጫ ለሁሉም ተግባራት አመራሩ ግንባር ቀደም ሆኖ መገኘት እንዳለበት መክረዋል።

የህብረተሰቡ ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማረጋገጥ በፓርቲው የተገኙ ውጤቶች በማጠናከርና ችግሮችን በመለየት ብልጽግናን እውን ማድረግ እንደሚገባ አቶ ላጫ ጋሩማ ገልጸዋል።

የጉራጌ ዞን ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አለማየሁ ገ/መስቀል እንደ ሀገር የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ እውን በማድረግ ረገድ አመራሩ ግንባር ቀደም ሆኖ መገኘት አለበት ብለዋል።

በቀጣይ መንግስትና ህዝብ የጋራ አንድነት በመያዝ ፓርቲው ሊያከናውናቸው ያሳባቸው ተግባራት እውን እንዲሆኑ እና ከቃል ወደ ባህል ለመሸጋገር ታሳቢ ያደረገ መድረክ እንደሆነ አብራርተዋል።

ፓርቲው እያከናወናቸው ያሉ ስራዎች ከቃል ባለፈ ባህል እንዲሆኑ መስራት አንዱ አላማው ነው ብለዋል አቶ አለማየሁ።

ለዚህም ጠንካራ ተቋም መገንባት ፣ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር ተጠያቂነት ማስፈን እንደሚያስፈልግ አቶ አለማየሁ ለአብነት አንስተዋል።

ውጤታማና የውሳኔ ጥራት ያለው ፍትህን የማስፈን ስራ ማከናወን ወሳኝ ነው ያሉት አቶ አለማየሁ በዞኑ በሁሉም ዘርፎች እየመጡ ያሉ አመርቂ ለውጦች አጠናክሮ በማስቀጠል ሀገራዊ ለውጡን እውን ማድረግ ይገባል ብለዋል።

በመድረኩ የተገኙት አካላት የአመራሩና የአባሉ ጥራት በማረጋገጥና ወጥ አመለካከት በመያዝ ፓርታው የያዛቸው እሳቤዎች ተግባራዊ ማድረግ ይገባል።

የኢኮኖሚ ብልጽግና ለማረጋገጥ ፍትሀዊ የሀብት ክፍፍል ማድረግ ፣ግብርናችንን ማጠናከር እና የገቢ አሰባሰብ ስራዎቻችን በትኩረት መስራት እንደሚገባ አንስተዋል።

የሚገጥሙን ፈተናዎች በመቋቋም ፓርቲው ያቀዳቸው እቅዶች በድል ለማጠናቀቅ አመራሩ በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል ሲሉ አስታውቋል።

ሰላም የሁሉም ነገር መሰረት በመሆኑ በዞኑ የተገኙ አንጻራዊ ሰላም አጠናክሮ ማስቀጠል እና ያሉን ጸጋዎቻችንን በአግባቡ መለየት አለብን ሲሉ ሀሳብ ሰጪዎቹ ተናግረዋል።

Gurage Zone Government Communication Affairs

05 Feb, 17:35


ጥር 28/2017 ዓ.ም
በዞኑ ለተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር የተጋለጡ የህብረተሰብ ክፍሎችን በመደገፍ ተጠቃሚ ለማድረግ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው የጉራጌ ዞን ሰራተኛና ማህበራዊ መምሪያ ገለጸ።

መምሪያው የመጀመሪያ ግማሽ አመት እቅድ አፈጻጸም ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በወልቂጤ ከተማ አካሂዷል።

የጉራጌ ዞን ሰራተኛና ማህበራዊ መምሪያ ኃላፊ አቶ መኩሪያ ተመስገን በግማሽ ዓመቱ ከብሄራዊ ማህበራዊ ጥበቃ ፖሊሲ ተግባራዊ በማድረግ የአካል ጉዳተኞች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሚነታቸውን ለማረጋገጥ ስራዎች ተሰርቷል።

በዚህም በሲሲ አማካኝነት 9 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በማሰባሰብ የማህበረሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉንም አንስተዋል።

አክለውም ለተለያዩ አቅመ ደካማ የህብረተሰብ ክፍሎችን አዲስ ቤት የመገንባትና ጥገና የማድረግ ስራ መሰራቱን ጠቅሰዋል።

ከዚህም ባለፈ ከአጋፔ ሞብሊቲይ ኢትዮጵያ ድርጅት ፕሮጀክት ፕሮፖዛል በማቅረብ ችግር ውስጥ ያሉና ከቤት መውጣት ያልቻሉ አካል ጉዳተኞች 1መቶ 16 የዊልቸር ድጋፍ በማድረግ ተጠቃሚ ማድረግ እንደተቻለም ገልጸዋል።

ከስራ ስምሪት አንጻር ህገወጥ የሰዎች ዝውውር በዞኑ እየተበራከተ መምጣቱን ገልጸው ይህንንም ግንዛቤ የመፍጠር ስራ ከመስራት ባለፈ በዘርፉ የተሰማሩ ህገወጦችን ተጠያቂ የማድረግ ስራ መሰራቱንም አስረድተዋል።

አካል ጉዳተኞችና አረጋውያን ማህበር እንዲኖራቸውና እንዲጠናከር ከማድረግ ባሻገር በበጀት እንዲደገፉ መደረጉንም ገልጸዋል።

በተለይም አቅም የሌላቸውና ከፍለው ጥብቅና ማቆም የማይችሉ አቅመ ደካማ ወገኖች ነጻ የጥብቃና አገልግሎት እንዲያገኙ እንዲሁም ከህንጻ ግንባታ አንጻር ለአካል ጉዳተኞች ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን በቀጣይ በማጠናከር በትኩረት ይሰራል ነው ያሉት።

መምሪያው ተጋላጮች የመለየትና ከችግራቸው እንዲወጡ የሀብት አሰባሰብና እህል የመሰብሰብ ስራ በመስራት ድጋፍ በማድረግ የተሻለ የኑሮ ደረጃ እንዲደርሱ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

በዘርፉ የሚፈለገውን ውጤት በማምጣት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ከባለድርሻ አካላት ጋር ቅንጅታዊ አሰራር በማጠናከር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በመጀመሪያ ግማሽ አመት የተከናወኑ ጠንካራ ተግባራት በማጠናከርና ጉድለቶችን በማረም የተጠናከረ ስራ መስራት እንደሚገባም አመላክተዋል።

አንደ ኃላፊው ገለጻ ብሔራዊ የማህበራዊ ጥበቃ ፖሊሲ በተለያየ ምክንያት ለማህበራዊ ችግር የተጋለጡ አረጋውያን፣ አካል ጉዳተኞች፣ አቅመ ደካሞች የመደገፍ፣ የማገዝ ስራ እንደሚሰራ ያነሱት ኃላፊው እነዚህ ወገኖች ለማገዝ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን እንዲወጡም አስገንዝበዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች እንዳሉት መምሪያው አካል ጉዳተኞች በሁሉም ዘርፍ ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ የተሰሩ ስራዎች አበረታች ናቸው።

በተለይም ለአካል ጉዳተኞች የዊልቸር ድጋፍ ከማድረግ ባለፈ ለአቅመ ደካማ የህብረተሰብ ክፍሎችን የተለያዩ ድጋፍ የማድረግ ስራ መሰራቱን ተናግረዋል።

በተቋሙ በመጀመሪያ ግማሽ አመት የተከናወኑ ጠንካራ ተግባራት በማጠናከርና ጉድለቶችን በማረም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ እንደሚሰሩም አመላክተዋል።

Gurage Zone Government Communication Affairs

05 Feb, 12:26


ጥር 28/2017 ዓ.ም
ኪነ_ጥበብ እና ስነ_ጥበብ የአንድ ማህበረሰብ ባህል፣ታሪክና ቋንቋ ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያለው በመሆኑ ዘርፉን ማነቃቃት እንደሚገባ የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ገለጸ።

የጉራጌ ዞን ባህል ቱሪዝም መምሪያ ይህንን ትኩረት ያደረገ ዞናዊ የኪነ_ ጥበብ እና የስነ_ጥበብ የውድድር መድረክ በወቂጤ ከተማ አካሂዷል።

ኪነ-ጥበብ የሰው ልጅ የሚኖርበትን ዘመንና ጊዜ መሠረት አድርጎ፣ አኗኗሩን ልዩ በሆነ መንገድና ሁኔታ፣ ሥነ-ጽሑፍን፣ ሙዚቃን፣ ሥነ-ጥበብን፣ ትያትርን፣ ሲኒማ እና ሌሎችም በመጠቀም የሚገልፅበት ዘርፍ ነው፡፡

የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ሀላፊ ወ/ሮ መሠረት አመርጋ ኪነ-ጥበብ የአንድ ማህበረሰብ ባህሉን፣ ታሪኩን ፣ወጉንና ቋንቋውን ለትውልድ ለማስተላለፍ የሚጠቅም በመሆኑን ዘርፉን ማነቃቃት እንደሚገባ ገልጸዋል።

ቋንቋን ለማሳደግና ለትውልድ ለማሸጋገር ኪነ ጥበብ እና ስነ ጥበብ ከፍተኛ ድርሻ አለው ያሉት ወ/ሮ መሰረት መሰል አይነት መድረኮች አጠናክሮ መስራት ለባህል እና ቋንቋ እድገት ወሳኝነት አለው ነው ያሉት።

አለማውም የኪነ ጥበቡ ዘርፍ ለማነቃቃት ፣ወጣት ባለተስጦኦችን መድረክ በማመቻቸት ጎልተው ወጥተው በሀገር አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለማድረግ ላይ ያተኮረ መሆኑን አስገንዝበዋል።

ወ/ሮ መሰረት አክለውም የጉራጌ ማህበረሰብ በርካታ የስነ ጥበብና ኪነ ጥበብ ባለሙያተኞችን ለሀገር ያበረከተ ሲሆን አብዛኞቹ መነሻቸው መሰል አይነት መድረኮችን ተጠቅመው እንደሆነ አመላክተዋል።

ስለሆነም ወጣቶች ያላቸው ተስጦ ሳይሰላቹ ይበልጥ በማንበብ ፣በመለማመድ ፣ በመጻፍ እና እውቀታቸው በማዳበር ማህበረሰቡ እንዲሁም እራሳቸው እንዲቀይሩ መክረዋል ።

በእለቱም በባህልና ሙዚቃ ፣በውዝዋዜ፣ በባህል አልባሳት ትርኢት (ፋሽን) በስእልና ቅርጻ ቅርጽ፣በትያትር፣ በአጫጭር ፊልም፣በፎቶ ግራፍ ውድድሩ እንደ ተካሄደ ወ/ሮ መሰረት አስገንዝበዋል።

በዛሬው እለት ያሸነፉ ባለተስጦ ወጣቶች በቀጣይ በክልል በሚዘጋጁ የኪነ _ጥበብና የስነ_ ጥበብ ስራዎች ላይ ዞኑን በመወከል ተወዳዳሪ እንደሚሆኑ አስታውቀዋል።

በፕሮግራሙ የተገኙ አካላት በበኩላቸው መሰል የኪነ- ጥበብ እና የስነ- ጥበብ ስራዎች በማጎልበት ባለ ተስእጥኦዎችን እንዲፈሩ የሚያደርግ በመሆኑ ተጠናከሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።

አክለውም ከዚህ በፊት በግላቸው የጉራጌን ባህል የሚያስተዋውቁ ኪነ ጥባዊ ስራዎች ይሰሩ እንደነበር ጠቅሰው መሰል አይነት መድረኮች መዘጋጀታቸውን የጉራጌን ባህል ፣ታሪክ እና ቋንቋ የበለጠ ለማስተዋወቅ እድል ይፈጥርልናል ሲሉ ገልጸዋል።

ባህላችን በመጤ ባህሎች እንዳይበረዝ በማድረግ፣የወጣቱን ተሰጥኦውን በማሳደግ የጉራጌ ማህበረሰብ ያሉት አኩሪ እሴቶች በሁሉም ቦታ ለማስተዋወቅ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

በእለቱም በተለያዩ የኪነ -ጥበብ እና የስነ -ጥበብ ስራዎቻቸው ያቀረቡ ወጣት ባለሙያዎች ጨምሮ ዳኞች የእውቅና ሰርተፍኬት ተሰጥቶዋቸዋል።

Gurage Zone Government Communication Affairs

27 Jan, 18:37


ጥር 19/2017 ዓ.ም
የተቀናጀ የግብርና ልማት ስራ በማጠናከር የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እንደሚሰራ የጉራጌ ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

በጉራጌ ዞን እየተሰሩ ያሉ ሞዴል የግብርና ስራዎች አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ የማእከላዊ ኢትዩጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ገለጿል።

የጉራጌ ዞን ግብርና መምሪያ የ2017 ዓ.ም የበልግና የተቀናጀ የግብርና ልማት ስራዎች ዞናዊ የንቅናቄ መድረክ በእዣ ወረዳ አገና ከተማ አካሂዷል።

የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ እና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ በዞኑ በግብርና ዘርፉ ጠንክሮ በመስራት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በአጽንኦት ይሰራል ብለዋል።

በዞኑ ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የተቀናጀ የግብርና ልማት ስራ ማከናወን ያስፈልጋል ያሉ ሲሆን ከምርምር ማእከላት፣ከወልቂጤ ዩኒቨርስቲ እና አጋር ድርጅቶች ጋር በቅንጅት መስራ ይገባል ነው ያሉት።

በዘንድሮ የተፋሰስ ልማት ከ3 መቶ 85 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚሳተፉ ሲሆን የተፋሰስ ልማት ስራችን በጠረጴዛማ የእርከን ስራ በማትኮር በውበት፣በጥራት ፣በምርታማነት እና በቴክኖሎጂ በማዘመን ባህል ተደርጎ የመጣው የተፋሰስ ስራ ዘንድሮም ለሌሎችም አስተማሪ ሆነን መገኘት አለብን።

በቀጣይም ባህር ዛፍ በመንቀል መሬት በሰብልና በፍራፍሬ እንዲለማ ማድረግ እንዲሁም በግብርና ዘርፉ የወጣቶች የስራ እድል መፍጠር ያስፈልጋል ነው ያሉት።

አቶ አበራ አክለውም የእንሰት ምርት እንዳይጠፋ ከ32 ሚሊየን በላይ የእንሰት ብዜት ስራ እንደሚሰራም አስታውቋል።

የቡናና ቅመማ ቅመም እንዲሁም በእንስሳትና አሳ ሀብት ያሉን ጸጋዎችን በአግባቡ በመለየት በዘርፉ የሚገኘው ውጤት ይበልጥ አስፍቶ መስራት እንደሚገባ አንስተው በዞኑ ቡና ኤክስፖርት የማድረጉ ተግባር በትኩረት ይሰራበታል።

አዳዲስ የግብር ስራዎች በዞኑ በማስጀመር ነባር ሞዴል ስራዎች በማጠናከር የአርሶ አደሩን ኑሮ እንዲሻሻል የበለጠ ይሰራል ሲሉ አቶ አበራ ተናግረዋል።

የጉራጌ ዞን ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ ፈይሰል ሀሰን እንደገለፁት በዘርፉ የሚገጥሙ በተለይ የቤንዚል እና የግብአት ችግር ለመቅረፍ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ እየተሰራበት እንደሚገኝ አንስተዋል።

አደረጃጀቶች በማጠናከርና በማሳተፍ የተፋሰስ ልማት ተግባራችን በጥራት እና በፍጥነት መስራት ይገባል ያሉት አቶ ፈይሰል የተጎዱ የጀፎረ መንገዶች መጠገን ፣አዳዲስ የተፋሰስ ስራዎችን መስራት ያስፈልጋል ነው ያሉት አቶ ፈይሰል ሀሰን።

የማእከላዊ ኢትዩጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል እና የእንስሳትና አሳ ሀብት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኢያሱ ተረፈ በጉራጌ ዞን እየተሰሩ ያሉ ሞዴል የግብርና ስራዎች አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ብለዋል።

በዞኑ እየተሰሩ ያሉ የግብርና ስራዎች ለክልሉም ግንባር ቀደም ናቸው ያሉ ሲሆን በጥራት፣በፍጥነት፣በተደራሽነትና ወቅትን ጠብቆ ከመስራት አንጻር ይበልጥ ማዳበር እንደሚያስፈልግ ተናግሯል።

ያሉን ጸጋዎች በአግባቡ በመለየት ፣በሌማት ትሩፉት ፣በተፈጥሮ ሀብት ፣በእርሻ ፣በእንስሳትና አሳ ፣በተፈጥሮ ሀብት በቡናና ቅመማ ቅመም እና በሌሎችም ያሉ በርካታ ጸጋዎች ወደ ተግባር በቀየር ምርታማነትን ማሳደግ ይገባል።

አቶ ብስራት ገብሩ የምሁር አክሊል ወረዳ፣አቶ ዘውዱ ዱላ የእዣ ወረዳ ፣አቶ ካሱ ጁኋር የአበሽጌ ወረዳ አስተዳዳሪዎች ሲሆኑ በተቀናጀ የግብርና ልማት ስራ በተሰሩ ስራዎች የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚ መቀየር እየተቻለ ነው።

ባህርዛፍን በማንሳት የፍራፍሬና ሌሎች ሰብሎች ማልማት የተቻለ ሲሆን እንሰትን ከመጥፋት ወደ ማብዛት እንዲሁም በሽታ የመከላከል ስራ ላይ የተጀመሩ ስራዎች እንደሚያስቀጥሉ ጠቅሰዋል።

በቡናና ፍራፍሬ ፣በሌማት ትሩፋት፣በንብ ማነብ በሌሎች በሌማት ትሩፉት ስራዎች የተገኙ ውጤቶች አበረታች ሲሆኑ ዝርያ በማሻሻል ፣ግበአት በማሟላት ተግባር ላይም ውስንነቶች ማረም ያስፈልጋል ብለዋል።

ከዚህ በፊት በዞኑ የነበሩ ሞዴል የተፋሰስ ልማት ስራዎች ይበልጥ በማጠናከር እረገድ በትኩረት እንደሚሰሩ ተናግረው ከምርምር እና ከግብር ደጋፊ ድርጅቶች ጋር በቅንጅት እንደሚሰሩ አስገንዝበዋል።

Gurage Zone Government Communication Affairs

26 Jan, 17:26


የጉራጌ ማህበረሰብ የሴቶችን መብት አስቀድሞ የተረዳና ለሴቶች የእኩልነት ትግል ያረጋገጠ መሆኑ አንትሮሽት አንዱ ማሳያ መሆኑ የጉራጌ ዞን አስተዳደር አስታወቀ።

በጉራጌ ዞን የእናቶች ቀን (አንትሮሽት) በእዣ ወረዳ ያስሁራና የዋርበያ ቀበሌ በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት ተከበረ።

የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ እንዳሉት የጉራጌ ማህበረሰብ ከኢትዮጵያ ህገ መንግስት ድንጋጌ አስቀድሞ የጾታ እኩልነት ያረጋገጠ ህዝብ ነው።

ከእነዚህም አንዱ አንትሮሽት አንዱ ሲሆን ለወጣት ሴቶች ልጃገረዶች ነቐ ፣የገንየ ፣ ለወጣት ወንዶች ለበሞ ፣ላገቡ ሴቶች ይፍትዝፓር እንዲደረግልላቸው አስቦና ተረድቶ የተገበረ ማህበረሰብ መሆኑን አስታውቀዋል።

ይህ የመሰለ በዓል ተቀዛቅዞ የነበረ ቢሆንም የዞኑ መንግስት በሰጠው ልዩ ትኩረት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን በየአመቱ በፌስቲቫል ደረጃ እንዲከበር ተደርጓል ነው ያሉት።

ዋና አላማውም ባህላችን በመጤ ባህሎች በመከላከል በሀገር አቀፍ ደረጃ በሞዴልን ተወስዶ የኢትዮጵያ የእናቶች ቀን ሆኖ እንዲከበር እና ወደፊትም በአለም አቀፍ ቅርስነት ተመዝግቦ የቱሪዝም ሀብት እንዲሆን ለማስቻል ነው ሲሉ አቶ ላጫ አስገንዝበዋል።

አክለውም በዓሉ በብሄረሰቡ ዘንድ ያሉትን የመከባበርና የሰላም እሴቶቻችንን ይበልጥ እንዲለሙ የሚደረጉበት፣ ሴቶች መብታቸው እንዲያስከብሩና ተጠቃሚነታቸውን እንዲያረጋግጡ ትልቅ ፋይዳ አለው ብለዋል።

የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህጻናት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ዘቢባ መሀመድ እንዳሉት የጉራጌ ማህበረሰብ የሴቶችን መብት በማክበር ዘመኑን የቀደመ ለሴቶች የእኩልነት ትግል ያረጋገጠ መሆኑ አንትሮሽት ማሳያ እንደሆነ ገልፀዋል።

አያይዘውም የቃቄ ወርድወትም ስለ ሴቶች መብት በማይነገርበት ወቅት ስለሴቶች እኩልነት የታገለች ናት ያሉት ወ/ሮ ዘቢባ ይህ ደግሞ ለሴቶች ክብርና ነጻነት ከጥንት ጀምሮ የታገለ ማህበረሰብ መሆኑን ተጨማሪ ማስረጃ መሆኑ ተናግሯል።

የጉራጌ ዞን ሴቶችና ህጻናት መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ነጅሚያ መሀመድ በበኩላቸው አንትሮሸት የጉራጌ ብሔረሰብ ከጥንት ዘመን ጀምሮ የሴቶችን ክብር የሚዘክርበት ድንቅ ባህሉ ነው።

በሌላ አጠራር አሁን በዘመናዊ መልኩ በየ ዓመቱ በፈረንጆቹ ማርች 8 የሴቶች ቀን ብለን የምናከብረውን በዓል ማለት እንደሆነ አብራርተዋል።

የእናቶች ኃላፊነት የተረዳው የጉራጌ ማህበረሰብ የእናቶች ክብር ለመግለጽ ሲል የአንትሮሽት በዓል መፍጠር የቻለና የአርቆ አሳቢነት ምልክት ነው ሲሉ ኃላፊዋ ገልጸዋል።

አንትሮሽት ልጆች ለእናታቸው፤ እንዲሁም ባል ለሚስቱ ያላቸውን ፍቅርና አክብሮት የሚገልፁበት፤ ምስጋናቸውን የሚያቀርቡበት፣ስለራሳቸው የሚወያዩበትና በዓል ነው ያሉት ወ/ሮ ነጅሚያ በዓሉ በሀገር እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የበለጠ እንዲተዋወቅ የሚመለከተው ሁሉ አስተዋጾኦ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

የእዣ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘዉዱ ዱላ አንትሮሽት ለሴቶች ማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነትታቸው ያረጋገጠ በዓል እንደሆነ ተናግረዋል።

በእለቱ ያገኘናቸው እናቶች እንዳሉት አንትሮሸት፣የደስታ ፣የሰላም ፣የእኩልነት ፣የነጻነት ቀናችን በመሆኑ በልዩ ልዩ ድምቀቶች እያከበርነው እንገኛለን።

በእለቱም ዝማሙጃት ፣የጎመን ክትፎ ፣ቆጮ ፣ ጥሬ ስጋ፣ክትፎ ፣አይብ ፣ጠላ እና ሌሎች በርካታ የምግብ አይነቶች ተዘጋጅተው ቤተሰብ ሁሉ በጥጋብ እንዲያሳልፍ ይሆናል።

በእለቱም በምግብና በመጠጥ፣በጭፈራ እና በመከባበር እንዲሁም በእረፍት እንደሚያከብሩት ተናግረው ይህ በዓል ተቀዛቅዞ ከነበረበት አሁን ደምቆ እየተከበረ በመሆኑ ለሴቶች ደግሞ የሚያሰገኘው ጠቅም ከፍተኛ እንደሆነ አስገንዝበዋል።

በእለቱም በዓሉን የሚገልጹ ኪነ ጥበባዊ ስራዎች ለታዳሚው የቀረቡ ሲሆን በዞኑ ላሉ ሞዴል የልማት ህብረት መሪ ሴቶች ፣አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት እውቅናና ሽልማትም ተደርጎላቸዋል።

Gurage Zone Government Communication Affairs

23 Jan, 15:32


ጥር 15/2017 ዓ.ም
በዞኑ የህግ የበላይነት በማረጋገጥ ህብረተሰቡ በፍትህ ተቋማት ላይ እምነት እንዲኖራቸው ሁሉም ባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራር በማጠናከር መስራት እንዳለባቸው የጉራጌ ዞን ፍትህ መምሪያ ገለጸ።

መምሪያው የ2017 በጀት አመት የመጀመሪያ ግማሽ አመት እቅድ አፈጻጸም ከህዝብ ክንፍና ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት በወልቂጤ ከተማ አካሂዷል።

የጉራጌ ዞን ፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ ኤሊያስ ሰብለጋ እንዳሉት በግማሽ አመቱ የምርመራ ስራ ከፖሊስ በጋራ ከማጣራት ባለፈ ጠንካራ የችሎት ክርክር በማድረግ ወንጀለኞችን ለህግ በማቅረብ የህግ የበላይነት ለማረጋገጥና ስርአት አልበኝነት ለማስቆም በርካታ ስራዎች ሲሰሩ ቆይቷል።

እንደ አቶ ኤሊያስ ገለጻ በግማሽ ዓመቱ ከፖሊስ የቀረቡ 823 የወንጀል መዝገቦችን በማየት ውሳኔ መሰጠቱን ተናግረዋል።

የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመፍታት ውጤታማ የፍትህ ስርአት እንዲኖር ከማድረግ ባለፈ ዜጎች በፍትህ ተቋማት ላይ እምነት እንዲኖራቸው መስራት ይገባል ብለዋል።

ህገወጥ የመሬት ወረራ በገጠርና በከተማ መኖሩን አንስተው ለዚህም ህግና አሰራሩን መሰረት በማድረግ ማስመለስ ላይ በትኩረት መሰራት እንዳለበት ተናግረዋል።

በዞኑ ጠበቃ ቀጥረው መከራከር አቅም ለሌላቸው ሴቶች፣ ህጻናት፣ አረጋውያንና አካል ጉዳተኞች በመንግስት በልዩ ሁኔታ እንዲደገፉ የህግ ማዕቀፍ መዘጋጀቱን ተከትሎ በግማሽ ዓመቱ 38 መዝገብ መሰራቱን ጠቁመው በቀጣይ በዘርፉ የተጠናከረ ስራ መስራት ይገባል ብለዋል።

ጠንካራ የፍትህ ተቋማት በመፍጠር ለህብረተሰቡ ተገቢውን አገልግሎት መስጠት ይገባል ያሉት አቶ ኤሊያስ ለዚህም ፖሊስ፣ አቃቢ ህግና ፍርድ ቤት ቅንጅታዊ አሰራር በማጠናከር መስራት ይኖርባቸዋል ነው ያሉት።

ወንጀልን አስቀድሞ ለመከላከል የግንዛቤ ስራ ላይ የተጠናከረ ስራ መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።

በመምሪያው የልማት እቅድ አስተባባሪ ወይዘሮ ህይወት ታከለ የ6 ወር አፈፃፀም ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት የፍትህ ትራንስፎርሜሽን እቅድ ትግበራ ለማጠናከር የጉራጌ ባህላዊ የዳኝነት ስርአት እንዲጠናከር የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ መዘጋጀቱን አመላክተዋል።

የፍትህ ተደራሽነት እንዲኖር በዞን ደረጃ ተቋርጦ የነበረው የተዘዋዋሪ ችሎት ስራ በሶስት ማዕከሎች መጀመሩን ገልጸዋል።

ከሙስና ወንጀል ጋር በተያያዘ በኦዲት ጉድለት ለመንግሥት ገቢ የተደረገ በክስ ሒደትና በውሳኔ ያለ በአጠቃላይ 2 ሚሊየን 1 መቶ 57 ሺ 96 ብር ለመንግሥት ገቢ እንዲሆን ተደርጓል ብለዋል።

በታክስና ኢኮኖሚ ነክ ወንጀሎች የተመዘበረ የመንግስትና የህዝብ ሃብት 2 ሚሊየን 5 መቶ 17 ሺ 768 ብር ማስመለስ መቻሉን ጠቅሰዋል።

በህገወጥ መንገድ የተወረረ የወልና የከተማ መሬት በክስ በምርመር ለማስመለስ በመሰራቱ የወል መሬት 76 ነጥብ 37 ሔክታር እና የከተማ መሬት 39 ሺህ 220 ካሬ ሜትር ተመላሽ መደረጉን አንስተዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት በዞኑ የህግ የበላይነት በማረጋገጥ ህብረተሰቡ ተገቢውን የፍትህ አገልግሎት ማግኘት እንዲችል ቅንጅታዊ አሰራር በማጠናከር መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል።

በዘርፉ የሚፈለገውን ውጤት ማምጣት እንዲቻል ባህላዊ ቂጫ በማጠናከር መስራት ይገባል።

የምርመራ ፖሊስ እጥረት፣ የዜጎች የሰብአዊ መብት አያያዝና የማረሚያ ቤት እጥረት መኖሩ ተከትሎ በዘርፉ በትኩረት እንዲሰራም አመላክተዋል።

Gurage Zone Government Communication Affairs

17 Jan, 12:28


የጥምቀት በዓል ስናከብር ፍቅር ፣ አብሮነትና መቻቻልን በማጎልበት ሊሆን እንደሚገባ የጉራጌ ሀገረስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹኡ አቡነ መልከጼዴቅ ገለጹ።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ጠባቂ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ከፊታችን የሚከበሩ የከተራና የጥምቀት በዓልን ምክንያት በማድረግ የሰጡት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት።

በዓሉን ስናከብር እግዚአብሔር በመፍራትና መልካም እሴቶቻችን በማጎልበት መሆን አለበት ብለዋል።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ጠባቂ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ እንደገለጹት የጥምቀት በዓል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአደባባይ በድምቀት  ከምታከብራቸው በዓላት ውስጥ በየዓመቱ ጥር 11 ቀን የሚከበረው የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት አንዱ ነው።

መላው የሰው ልጅ በሙሉ የእዳ ደብዳቤው  ተቀዶለት ነጻ የወጣበትና ሚስጢር የተገለጸበት እለት መሆኑን ተናግረዋል።

የጥምቀት በዓል አምላካችን ለሰው ልጆች ያለውን ጥልቅ ፍቅር ያሳየበት ሲሆን እኛም ከክርስቶስ በተማርነው መሰረት በፍቅር በሰላም እና በአብሮነት ልንኖር ይገባል።

ብጹእ አቡነ መልከ ጼዲቅ አክለውም ምእመናኑም ተንኮል፣ቂም በቀል፣ዘረኝነት ጸብንና ክፉ ስራዎችን በመተው ለጽድቅ ስራ የበለጠ መትጋት እንዳለባቸው መክረዋል።

በዓሉን ስናከብር የተጣላውን በማስታረቅ የተለያየው አንድ በማድረግ፣አብሮ በመጸለይ፣ በመዘመር ፣አብሮ በመብላትና በመጠጣት ፣ድሆችን በመመገብ ሌሎች ወደ ጽድቅ መንገድ ሊወስዱ የሚችሉ ስራዎች በመስራት ፈጣሪያችንን ልናስደስት ያስፈልጋል።

ይህ በዓል ያለ እምነት ልዩነት ክርስቲያኑና ሙስሊሙ ተባብረው በዓሉ በድምቀት እንዲከበር በማድረግ አብሮነታቸው የሚያሳዩበት እንዲሁም ኢትዮጵያዊ አንድነታቸውን የሚያስመሰክሩበት እንደሆነ አስገንዝበዋል።

ለአብነትም ለበዓሉ ድምቀት በሰላምና ጸጥታ፣በጽዳት እና ሌሎች በርካታ ስራዎች በጋራ እንደሚያከናውኑ አስታውሰው ይህንን የሚበረታታ ተግባር ነው ብለዋል።

በዓሉን ምክንያት በማድረግ ሀይማኖቱ የማይፈቀድው እና ስርዓቱን ከሚያበላሹ  አላስፈላጊ ድርጊቶች መቆጠብ እንደሚገባ ብጹእ አቡነ መልከ ጼዲቅ ገልጸዋል።

በዓሉ ሀይማኖታዊም ብሄራዊ ከመሆኑ በተጨማሪ  አለም አቀፋዊ ቅርስ በመሆኑ ይህንን ጠብቀን ለትውልድ ማስተላለፍ እንደሚገባ አባታዊ መልእክታቸው አስተላልፏል።

በዓሉ የሰላም ፣የፍቅር፣ የአብሮነት፣ የደስታ ፣የመቻቻል እንዲሆንም ተመኝተዋል።

Gurage Zone Government Communication Affairs

14 Jan, 14:39


ጥር 6/2017 ዓ.ም
የግብርና ዘርፉን በማዘመን የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የምርምር ስራዎች ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለጸ።

የግብርና የምርምር ማእከላት በዞኑ በሚሰሩዋቸው የምርምር ስራዎች አመርቂ ለውጥ እያመጡ እንደሆነ የግብርና መምሪያ አስታውቋል።

የጉራጌ ዞን የግብርና ልማት አካላት የግንኙነት አማካሪ ካውንስል 12ኛ መደበኛ ጉባኤ በወልቂጤ ከተማ አካሂዷል።

የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ እንደገለፁት በግብርናው ለውጥ ማምጣት ካልተቻለ የሀገራችን ብልጽግና ማረጋገጥ አይቻልም።

ስለሆነም ግብርናውን ለማዘመን፣ችግሮችን ለመፍታት እና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የምርምር ማእከላት ከዚህ የበለጠ መስራት እንደሚጠበቅባቸው መክረዋል።

የአርሶ አደሩን ጊዜንና ጉልበት ሊቆጥቡ የሚችሉ የሜካናይዜሽን ስራዎች ማቅረብ ይጠበቃል ነው ያሉት አቶ ላጫ ጋሩማ።

ከተለያዩ አካባቢዎች መጥተው በዞኑ የምርምር ስራ የሚሰሩ የምርምር ተቋሟት አመስግነው በቀጣይም በተለይ በእንሰት በሽታ ፣በጉራጌ ቡና ፣በድንች ፣በአፈር አሲዳማነት፣በፍራፍሬ ምርቶች እና በሌሎች በሽታዎች ላይ ትኩረት አድርገው እንዲሰሩ ጠይቀዋል።

የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ እና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ የግብርና ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ ቅድሚያ መሬቱን ማከምና ጤነኛ ማድረግ ይገባል ነው ያሉት።

በመሆኑም የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሁሉም አካባቢ ካሉ የምርምር ተቋማት ጋር በጋራ የሚሰራ መሆኑን የገለፁት አቶ አበራ በወልቂጤ ዩኒቨርስቲ እና በወልቂጤ ግብርና ምርምር ማዕከል የተሰሩ ስራዎች አበረታች እንደነበሩ አስታውቀዋል።

አቶ አበራ አክለውም በዞኑ በግብርና ያሉ ተግዳሮቶች ለመፍታት ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የግብርና ዘርፉ ከሚደግፉ ድርጅቶች እና አካላት በቅንጅት መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።

በተለይም አሲዳማ መሬቶችን በኖራ የማከም እና የተሻሻሉ ዝርያዎችን በማባዛት ውጤታማ የሆኑ ስራዎች መሰራታቸው አስታውሰዋል ኃላፊው።

የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምርምር ማእከል ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ጸጋዬ ተረፈ በበኩላቸው በዞኑ በምርምር ማእከላት የሚወርዱ ስራዎች ተግባራዊ ከማድረግ አንጻር አበረታች ናቸው።

በቀጣይም በዞኑ በከፍተኛ ሁኔታ ችግር የሆኑ በእንሰት በሽታ፣በድንች ፣በደጋ ቦቆሎ፣በአፈር አሲዳማነት፣ በቡናና ቅመማ ቅመም ዝርያ ማሻሻል ላይ ትኩረት ተደርጎ እንደሚሰራ አስገንዝበዋል።

የወልቂጤ ግብርና ማእከል ተመራማሪና ዳይሬክተር አቶ ቤተል ነክር ምርምር ማእከሉ ከተቋቋመ ቅርብ አመታት ያስቆጠረ ቢሆንም በአሲዳማነት የተጠቁ መሬቶች የማእከምና 1መቶ 21 የምርምር ስራዎች ማከናወናቸው ለአብነት አንስተዋል።

በውይይቱ የተሳተፉ አካላት እንዳሉት በምርምር ማእከላት በተሰሩ የምርምር ስራዎች እና ድጋፎች በግብርና ዘርፉ እምርታዊ ለውጥ እየመጣ እንደሆነ ገልጸዋል።

ይሁን እንጂ ዞኑ ካለው የግብርና እምቅ አቅም አንጻር ገና ብዙ መስራት ስለሚጠይቅ ከግብርና ምርምር ማእከላት ጋር ተቀናጅቶ መስራት ይገባል ብለዋል።

በወልቂጤ ዪኒቨርስቲ ፣በወልቂጤ ምርምር ማእከልና በዞኑ ግብርና መምሪያ በምርምር የተሰሩና የተገኙ ውጤቶች ላይ ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎባቸዋል።

በመድረኩ ከወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፣ከአቦ ፣ከወልቂጤ፣ከጅማ ፣ከደብረ ዘይት ፣ከሆለታ፣ከመልካሳ እና ከክልሉ ግብርና ምርምር ማእከል የመጡ ተመራማሪዎች ፣ ኃላፊዎች እንዲሁም ሌሎችም ጥሪ የተደረገላቸው አካላት ተገኝተዋል።

Gurage Zone Government Communication Affairs

14 Jan, 07:13


ጥር 6/2017 ዓ.ም
የጉራጌ ዞን የግብርና ልማት አካላት የግንኙነት አማካሪ ካውንስል 12ኛ መደበኛ ጉባኤ በወልቂጤ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።
በዞኑ በግብርና ዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮች ለማረም እና በግብርና ዘርፉ የሚታዩ ለውጦች ይበልጥ በማሳደግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑ የዞኑ የግብርና መምሪያ ኃላፊው አቶ አበራ ወንድሙ ገልጿል።
ግብርና ያለ ምርምር ውጤታማ መሆን አይችልም ያሉት አቶ አበራ በዞኑ በግብርና ያሉ ተግዳሮቶች በመፍታት ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ሁሉም የድርሻው ሊወጣ ይገባል ብለዋል።

በጉራጌ ዞን በአለፉት ጊዜያት የተለያዩ የምርምር ስራዎች በመስራት በግብርና ዘርፉ ያሉ ችግሮች መቅረፍ መቻሉ ጠቁመዋል።

በተለይም አሲዳማ መሬቶችን በኖራ የማከም እና የተሻሻሉ ዝርያዎችን በማባዛት ውጤታማ የሆኑ ስራዎች መሰራታቸው አስታውሰዋል።

በመድረኩም የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ፣የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪ እና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ፣የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ የጽ/ቤት ኃላፊ እና የቢሮው ኃላፊ ተወካይ አቶ አህመድ ሀቢብ ፣የከተማ እና የወረዳ አስተዳዳሪዎች ፣የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊዎች ፣በዞኑ እና በተለያዩ አካባቢዎች ያሉ የምርምር ማእከላት ሌሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

Gurage Zone Government Communication Affairs

04 Jan, 13:04


በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የወልቂጤ ክላስተር የአመራር ምዘና እየተካሄደ ይገኛል።

ታህሳስ፣26/2017
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የወልቂጤ ክላስተር አመራሮች የግምገማ መድረክ "ከቃል ወደ ባህል" በሚል መሪ ቃል በወልቂጤ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።

የክላስተሩን የምዘና መድረክ በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የመሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር መሐመድ ኑሪዬ እየመሩ ሲሆን የክላስተሩ መሰረታዊ ድርጅት ሰብሳቢ እና የክልሉ ስራ አድል ፈጠራና ኢንተር ፕራይዝ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙስጠፋ ኢሳን ጨምሮ በወልቂጤ ክላስተር የሚገኙ ሁሉም የክልል አመራሮች ተገኝተዋል

Gurage Zone Government Communication Affairs

04 Jan, 11:08


ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የጄቱር መኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካን ጎበኙ

ታሕሣሥ 26፣ 2017
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጂግጂጋ ከተማ የሚገኘውን የጄቱር መኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካን ጎብኝተዋል።

በቀን አስር መኪናዎች መገጣጠም የሚችለው ፋብሪካ በ22 ሺህ ስኩዌር ሜትር ስፋት ላይ ያረፈ መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ አመልክቷል።
#(ኤፍ ኤም ሲ)

Gurage Zone Government Communication Affairs

01 Dec, 18:49


https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid02WJESET5hhQHy6atJKeDBNT6akcZymJnizDgk8j2YybdPVzeHmRGjNLVf1z3SzbVTl&id=100064792596360&mibextid=NnVzG8

Gurage Zone Government Communication Affairs

30 Nov, 18:12


ህዳር 21/2017 ዓ.ም
የእናቶች ማቆያ በሁሉም አካባቢዎች በመገንባትና በማጠናከር የእናቶችና የጨቅላ ህጻናት ሞት መቀነስ እንደሚገባ የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው የእናቶች ማቆያ ቤት ግንባታ ፣እድሳትና ማደራጀት የአፈጻጸም ግምገማና የልምድ ልውውጥ መድረክ በጉራጌ ዞን አገና ከተማ አስተዳደር አካሂዷል።

የእናቶችና የጨቅላ ህጻናት ሞት ለመቀነስ በእናቶች ማቀያ ላይ በትኩረት እንደሚሰራ የጉራጌ ዞን ጤና መምሪያ ገልጿል።

የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ በጤና ተቋማት የሚወልዱ እናቶችን ቁጥር ለመጨመር እና የጨቅላ ህጻናት ሞት ለመቀነስ የእናቶች ማቆያ ቤት መገንባት እና ማጠናከር እንደሚገባ አስታውቋል።

የእናቶች እና የጨቅላ ህጻናት ሞት ለማስቀረት የሚደረገውን ጥረት የጉራጌ ዞን የእናቶች ማቆያ በመጀመር ግንባር ቀደም መሆኑን ተናግረዋል።

አቶ ሳሙኤል አያይዘውም በርካታ የአፍሪካ ሀገሮችን ጨምሮ የተሞክሮ ማዕከል የሆነ ዞን ስለመሆኑም አመላክተው በአገና ከተማ የታየው ምርጥ ተሞክሮ በሁሉም አካባቢዎች ማስፋት እንደሚገባ መክረዋል።

ከጤና አገልግሎት ሰጪዎች መዘግየት፣ የባለሙያና የህክምና ግብአት እጥረት፣ የግንዛቤ ችግር ለእናቶች እና ለጨቅላ ህጻናት ሞት በመንስኤነት ተጠቃሽ ስለመሆናቸው አንስተው ችግሩን ለማረም በቁርጠኝነት መስራት ይገባል ብለዋል።

እነዚህ ችግሮች ለማረም ማህበረሰቡ አሳታፊ ማድረግ ያስፈልጋል ሲሉ አቶ ሳሙኤል አሳስበዋል።

የቢሮው ምክትል ቢሮ ኃላፊ እና የጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ተጠሪ አቶ አሸናፊ ጴጥሮስ የዘለቄታዊ የልማት ግቦችን ለማሳካት የእናቶችን እና ህጻናትን ሞት ማስቀረት ተገቢ ስለመሆኑ ተናግረዋል።

ለዚህም ከወሊድ በፊት እናቶች በሰለጠኑ ባለሙያዎች አገልግሎት ማግኘት እንዲችሉ የማቆያ ማዕከላት ሚና የላቀ በመሆኑ ልዩ ትኩረት መስጠት ይገባል ብለዋል።

የጉራጌ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ አየለ ፈቀደ በዞኑ የእናቶችና የጨቅላ ህጻናት ሞት ለመቀነስ በእናቶች ማቀያ ላይ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግሯል።

በዚህ ተግባር ጉራጌ ዞን የተሻለ ቢሆንም በሁሉም መዋቅሮች ተግባራዊ ማድረግ ሰፊ ስራ ይጠይቃል ያሉት አቶ አየለ ለዘርፉ ትኩረት መስጠት በነገው ሀገር ተረካቢ ትውልድ ላይ መስራት ማለት እንደሆነ አስገንዝበዋል።

በማቆያ ውስጥ ያሉ እናቶች የህክምና ክትትል ፣የምግብ ድጋፍ ፣ከንጽህና እና ሌሎችም ምቹ ሁኔታዎች የሚመቻችላቸው ሲሆን ነፍሰጡር እናቶች ይደርስባቸው የነበረው ችግር የሚቀርፍ እንደሆነ አመላክቷል።

አቶ ዳዊት ጡምደሎ የሆሳና ከተማ ከንቲባ ፣አቶ ታሪኩ ተስፋዬ የሺሺቾ ከተማ ከንቲባ ሲሆኑ በአገና ከተማ የታየው የእናቶች ማቆያ ወደ አካባቢያቸው ወስደው ተግባራዊ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል።

በእለቱ በአገና ከተማ አስተዳደር በአገና ጤና ጣበያ የእናቶች ማቆያ ውስጥ አግኝተን ያነጋገርናቸው እናቶች እንዳሉት በጤና ተቋሙ የጤና ክትትል ፣የምግብና ሌሎች ድጋፎች እየተደረገላቸው እንደሆነ አስታዉቀዋል።

በግል ቤት ውስጥ ስንሆን በተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮች እራስን ለመንከባከብ ብዙም ምቹ ሁኔታዎች ስለማይኖሩ ጤና ተቋም ላይ ቁጭ ብሎ መከታተል ግን ወሳኝነት አለው ብለዋል።

Gurage Zone Government Communication Affairs

16 Nov, 18:38


ህዳር 7/2017 ዓ.ም
የጉራጌ ዞን ግብርና መምሪያና የእዣ ወረዳ የግብርና ጽ/ቤት የስራ ኃላፊዎች በእዣ ወረዳ እየተሰሩ ያሉ የግብርና ልማት ስራዎች ጎበኙ።

እየተከናወኑ ያሉ የግብርና ስራዎች የምግብ ዋስትና ከማረጋገጥ በተጨማሪ የአርሶ አደሩ እና የወጣቱ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጡ መሆኑ የጉራጌ ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

በእለቱም በተለያዩ ቀበሌዎች በሰብል ፣በችግኝ ማፍላት ፣በሮዝመሪ ፣ በነጭ ሽንኩርት ፣ በድንች ፣በዶሮ እና በሌሎችም የግብርና ዘርፎች ላይ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ነው የታዩት።

የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ እና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ በ2016/17 የምርት ዘመን ያላግባብ የተተከሉ ባህር ዛፎች ማንሳትና ለዘመናት ያልታረሱ መሬቶች እንዲታረሱ በትኩረት ሲሰራበት ነበር ብለዋል።

በዚህም 5ሺ 9መቶ ሄክታር መሬት ለዘመናት ያልታረሱ መሬቶች መታረሳቸው እና ዞኑ እምቅ የግብርና አቅም እንዳለው በሀገር አቀፍም ማሳየት ተችሏል።

አቶ አበራ አክለውም በእንስሳት እርባታ ፣በፍራፍሬ ልማት ፣በቡና ፣በሰብል ልማት፣በዶሮ ፣በንብ ማነብ፣በጤፍ እና በሌሎችም የግብርና ዘርፎች ተሰማርተው አርሶ አደሩ እንዲሁም ሴቶችና ወጣቶች የምግብ ዋስትና ከማረጋገጥ በተጨማሪ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያረጋገጡ መሆኑ አስታውቋል።

ለአብነትም በዘርፉ ከ20 ሺ በላይ ወጣቶች የስራ እድል የተፈጠረላቸው ሲሆን 1ሺ 2መቶ ሄክታር መሬት በወጣቶች ለምቷል ነው ያሉት።

በእነዚህ ምርቶች ሻጩና ሸማቹ በቀጥታ በማገናኘት ምርቱ በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲቀርብ በመደረጉ የኑሮ ግሽበቱ እንዲረጋጋ አስችሏል ብለዋል።

በዚህም የእዣ ወረዳ ለግብርና ዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት የተከናወኑ የግብር ስራዎች እጅግ አመርቂ መሆናቸው የገለጹት አቶ አበራ በዛሬው እለት በተለያዩ ቀበሌዎች በሰብል ፣በችግኝ ማፍላት ፣በሮዝመሪ ፣ በነጭ ሽንኩርት ፣ በድንች ፣በዶሮ እርባታ እና በሌሎችም የግብርና ዘርፎች ላይ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች መመልከት ተችሏል።

የእዣ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መቻል ተሰማ እንደገለጹት በወረዳው የአርሶ አደሩ የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል እና ወጣቱ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚ ለማድረግ በልዩ ትኩረት ይሰራል።

በእንስሳት እርባታ ፣በጤፍ ፣በፍራፍሬ ልማት ፣በቡና ፣በጥራጥሬ ሰብሎች፣በችግኝ ማፍላት ፣ በዶሮ እና በሌሎችም የግብርና ዘርፎች ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ አብራርተዋል።

በምርት ዘመኑ ከ6 ሺ 4መቶ 35 ሄክታር መሬት በላይ በተለያዩ ሰብሎች የተሸፈነ ሲሆን 8 መቶ 90 ሺ ኩንታል ምርት ይገኛል ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል አቶ መቻል።

በዘንድሮ አመት በወረዳው ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር ከ9 መቶ ሄክታር መሬት በላይ ያልታረሱ መሬቶች እንዲሁም 1 ሺ 7 መቶ ሄክታር መሬት በኩታ ገጠም መታረሱ አመላክቷል ኃላፊው።

ምርትና ምርታማነት ለመጨመር ከቅድመ ዝግጅት ስራ ጀምሮ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን የቴክኖሎጂና የግብአት አቅርቦት የማመቻቸት ፣አፈርን በኖራ የማከም ፣ጸረ ተባይ ኬሚካል የመርጨት ፣የባለሙያ ድጋፍ ክትትል የማድረግ፣የገበያ ትስስር የመፍጠር ስራ መሰራቱ አስታውሰዋል።

አቶ መቻል እንደተናገሩት በወረዳው በግልና በማህበር በግብርና ዘርፍ ከተደራጁት ከ1 ነጥብ 9 ሚሊየን ብር በላይ ካፒታል የሚያስመዘግቡ እንዳሉ ጠቁመዋል።

ወጣት አዳነ ብሩ በወረዳዉ በዶሮ እረባታ ያገኘነው ሲሆን በኢንጂነሪንግ የተመረቀ ቢሆንም ዛሬ ላይ 5 መቶ ዶሮዎች እያረባ በቀን ከ4መቶ 50 እስከ 5መቶ እንቁላል ለገበያ አቅርቦ ውጤታማ መሆኑ ተናግሯል።

ልሎች በወረዳው ያነጋገርናቸው አርሶ አደሮች በበኩላቸው በየጊዜው በራሳቸው ጥረት እና በመንግስት ድጋፍ በሰሩዋቸው የግብርና ስራዎች በኑሮዋቸው ላይ ለውጥ በማምጣት ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚ መሆናቸው ገልጸዋል።

Gurage Zone Government Communication Affairs

12 Nov, 13:59


ህዳር 3/2017 ዓ.ም
የጉራጌ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት የዞን የወረዳና የከተማ አስተዳደር የስነ-ምግባርና ፀረ_ ሙስና ቡድኖች ፎረም የአሰልጣኞች ስልጠና በወልቂጤ ከተማ እየሰጠ ይገኛል።

ከመንግስት የሚመደበው ውስን ሀብት ለተፈለገው አላማ በማዋል የህብረተሰቡ የልማትና መልካም አስተዳደር ስራዎችን ለማረጋገጥ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አስተዳደር ጽ/ቤቱ አስታውቋል።

የሙስና ወንጀል በአመዛኙ ስልጣን ያለአግባብ በመገልገል እራስን ለመጥቀም ሌላውንም ለመጠቀምና ወይም ለመጉዳት ታስቦበት የሚሰራ የወንጀል አይነት ነው።

ቅድመያ ሙስናን መከላከል እና ከተገኘም ማስመለስ እንዲሁም ተጠያቂነትን ማስፈን ያስፈልጋል።

ሰልጣኞች በወንጀል ህግ መሰረታዊ ጽንሰ ሀሳብ ፣በሙስና ወንጀሎች አዋጅ መሰረታዊ ጉዳዮች ፤ ዝርዝር የሙስና ድርጊቶች ግንዛቤ አግኝተውና ለሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ግንዛቤ በመፍጠር ሙስናን የማይሸከም ህብረተሰብ የመፍጠር አላማ ታሳቢ ያደረገ ስልጠና ነው።

ከመንግስት የሚመደበው ውስን ሀብት ለተፈለገው አላማ በማዋል የህብረተሰቡ የልማትና መልካም አስተዳደር ስራዎችን ለማረጋገጥ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተመላክቷል።

ስልጠናው የጉራጌ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት ከማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስነ ምግባር እና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ጋር በመተባበር ሲሆን ለሁለት ቀናት የሚቆይ ይሆናል ።

Gurage Zone Government Communication Affairs

12 Nov, 13:20


https://www.facebook.com/share/p/17d6BmBntx/?mibextid=oFDknk

Gurage Zone Government Communication Affairs

11 Nov, 07:55


ህዳር 2/2017 ዓ.ም
አርሶ አደሮች አኩሪ አተርን በተለያየ የአዘገጃጀት ዘዴ ለምግብነት በማዋል የአመጋገብ ስርዓት እንዲያሻሽሉ እየሰራ እንደሚገኝ የወልቂጤ ግብርና ምርምር ማዕከል አስታወቀ፡፡

የምርምር ማዕከሉ በአበሽጌ ወረዳ አቡኮ ቀበሌ ውስጥ ለሚገኙ ሴት አርሶ አደሮች አኩሪ አተርን በተለያየ ዘዴ ለምግብነት ማዋል እንዲችሉ ስልጠና መስጠቱን ተመልክቷል፡፡

አኩሪ አተር ከፍተኛ የፕሮቲን፣ የካርቦሀይድሬት፣ የቅባትና የኦሜጋ 3 እና 6 ንጥረ ነገሮች በውስጡ ይዟል፡፡ እነዚህ ንጥረ ነገሮች ለሰውነታችን እጅግ በጣም አስፈላጊ በመሆናቸው አርሶ አደሩ በእለት ተእለት አመጋገቡ አኩሪ አተር በተለያየ መንገድ እንዲጠቀም የወልቂጤ የግብርና የምርምር ማዕከል ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ የማዕከሉ ዳይሬክተርና ተመራማሪ አቶ ቤቴል ነክር ገልፀዋል፡፡


እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ ማዕከሉ ለአካባቢው ስነ ምህዳር ተስማሚ የሆኑ አዳዲስ የግብርና ውጤቶች በመለየት ወደ አርሶ አደሮች ለማስፋት እየሰራ ይገኛል፡፡

ከእነዚህም አንዱ በአበሽጌ ወረዳ አቡኮ ቀበሌ የአኩሪ አተር ሰብል ልማት በማልማት እና በተለያየ የአዘገጃጀት ዘዴ ለምግብነት እንዲያውሉ ለቀበሌው አርሶ አደሮች ማስተዋወቁን አስረድተዋል፡፡

አርሶ አደሮች አኩሪ አተር ከማምረት ባለፈ ከሌሎች የሰብል ውጤቶች ጋር በማደባለቅ ለምግብነት እንዲያውሉ ግንዛቤ ተፈጥሮላቸዋል ብለዋል፡፡

ማዕከሉ በምርምር ውጠለታማነታቸው የተረጋገጠ የሰብል ዝርያዎች በመለየት ለአርሶአደደሮች በማስተዋወቅ በስፋት እንዲመረት እየሰራ እንደሚገኝ አቶ ቤቴል አስገንዝበዋል፡፡

በጉራጌ ዞን ግብርና መምሪያ የኤክስቴንሽን ኮሚዩኒኬሽን ስራሂደት አስተባባሪ ወ/ሮ ሲሳይ ኮራ እንዳሉት የወልቂጤ ግብርና ምርምር ማዕከል ምርትና ምርታማነትን የሚያሻሽሉ ቴክኖሎዎች ከአርሶ አደሮች እያቀረበ ይገኛል።

የምርምር ማዕከሉ ውጤታማ የሆኑ የግብርና ውጤቶች ወደ አርሲ አደሮች ከማስፋት በተጨማሪ በማሳ አዘገጃጀት፣ በሰብል አዘራርና እንክብካቤ፣ በግብዓት አጠቃቀም፣ በምርት አሰባሰብና አጠቃቀም ላይ ግንዛቤ ይፈጥራል ብለዋል።

በመሆኑም አርሶአደሮች ያገኙትን ግንዛቤ ተጠቅመው በሚያዘጋጇቸው የምግብ አይነቶች በፕሮቲን የበለፀገውን አኩሪ አተርን መጠቀም እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡

የአበሽጌ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ሙላቱ ደሳለኝ የአኩሪ አተር ምርት በሁሉም ቀበሌዎች ለማስፋት እንደሚሰራ ገልፀዋል፡፡

አርሶ አደሩ በስፋት በማምረት ከምግብ ፍጆታ ባለፈ ለገበያ እንዲያቀርቡ በትኩረት እንደሚሰራ አብራርተዋል፡፡

በወልቂጤ ግብርና ምርምር ማዕከል የግብርና ኤክስቴንሽን ተመራማሪ የሆኑት አቶ ተስፋሁን ፍቅሬ በበኩላቸው አኩሪ አተር ከፍተኛ የፕሮቲን ንጥረነገር እና የተለያዩ ሚነራሎች የያዘ በመሆኑ ለአእምሮ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል፡፡

የዞኑ አርሶ አደሮች ዝቅተኛ የፕሮቲን ይዘት ያላቸው ሰብሎች ከማምረት ይልቅ አኩሪ አተር ምርጫቸው ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው የተናገሩት ተመራማሪው ከፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ የገቢ አቅማቸው እንዲያሳድጉ መስራት እንዳለባቸው አስረድተዋል፡፡

ማዕከሉ በዚህ አመት በጉራጌ ዞን፣ በቀቤናና ማረቆ ልዩ ወረዳዎች በአነስተኛ ማሳዎች የአኩሪ አተር የሙከራ ትግበራዎች ማከናወናቸው የተናገሩት ተመራማሪው ከአካባቢው ስነ ምህዳር ጋር ተስማሚ የሆኑ የአኩሪ አተር ዝርያዎች እያስተዋወቀ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

አክለውም አኩሪ አተር አሰባጥረው መጠቀም እንዲችሉ ከጅማ ግብርና ምርምር ማዕከል ጋር በመተባበር ለ25 ሴት አርሶ አደሮች አኩሪ አተር በመጠቀም የተለያዩ የምግብ አይነቶች ማዘጋጀት እንዲችሉ ስልጠና መስጠት መቻሉ ተናግረዋል፡፡

ያነጋርናቸው አርሶ አደሮች አኩሪ አተር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው የሰብል አይነት ሲሆን ማዕከሉ በፈጠረላቸው ግንዛቤ ዳቦ፣ አይብ፣ ወተት፣ ኩኪስ፣ ቆጮ፣ ወጥና ሌሎች የምግብ አይነቶች ማዘጋጀት መቻላቸው ገልፀዋል፡፡

በመሆኑም በቀጣይ የአመጋገብ ስርዓታቸውን ለማሻሻል አኩሪ አተርን በስፋት በማምረት ከፍጆታ ባለፈ ለገበያ ለማቅረብ እንደሚሰሩ አስረድተዋል፡፡

Gurage Zone Government Communication Affairs

11 Nov, 07:45


ህዳር01/2017ዓ.ም

ከቤልጅየም የመጡ ቱሪስቶች በጉራጌ ዞን እዣ ወረዳ ላይ እጅግ አስደሳች ጉብኝት አድርገዋል።

የጉራጌ ዞን የቱሪስት ፍሰት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱ ፋይዳው የጎላ ነው።

አለም አቀፍ አስጎብኚ ድርጅት Simon eco tours አማካኝነት ከጥቅምት 28/17 ጀምሮ ከቤልጂየም የመጡ የውጭ ሀገር ቱሪስቶች ለሣይክልና ለእግር ጉዞ ተመራጭ ከሆኑ ወረዳዎቻችን መካከል በእዣ ወረዳና አካባቢው የተሣካ ጉብኝት አድርገው በማህበረሰቡ እንግዳ ተቀባይነት ተደስተው ተመልሠዋል።

እዣ ወረዳ በርካታ ጥንታዊና ታሪካዊ የሆኑ የተፈጥሮና ሰውሰራሽ የቱሪስት መዳራሻ ስፍራዎች ባለቤት ናት ።

መረጃው የእዣ ወረዳ ኮሚዩኒኬሽን ነው

Gurage Zone Government Communication Affairs

01 Nov, 19:26


ጥቅምት 22/2017 ዓ.ም

የጉራጌ ዞን አስተዳደር ጽህፈት ቤት የ2017 ዓ.ም የ1ኛዉ ሩብ አመት እቅድ አፈጻጸም ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በወልቂጤ ከተማ ገምግሟል።

በግምገማ መድረኩ ተገኝተዉ ንግግር ያደረጉት የጉራጌ ዞን አስተዳደር ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ደሳለኝ ፈቀደ እንዳሉት በተቋሙ ቀልጣፋና ዉጤታማ አገልግሎት ለማህበረሰቡ እየተሰጠ ይገኛል።

በዞኑ ዉስጥ የታቀዱ የመልካም አስተዳደር ሰራዎች በተቀናጀ መንገድ እንዲመሩ ለማድረግ ሁሉም የዞን ተቋማት እቅድ አዘጋጅተዉ እንዲያቀርቡና ክትትል በማድረግና የተቋማት የመልካም አስተዳደር መረጃዎች እንዲደራጅ የማድረጉ ስራ በትኩረት ተሰርቷል።

ሪፖርቱን ያቀረቡት የጉራጌ ዞን አስተዳደር ጽህፈት ቤት እቅድ በጀት ክትትልና ግምገማ ቡድን መሪ አቶ እንዳለ አህመድ እንዳሉት በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተመዘገበ ያለዉን ኢኮኖሚያያዊ እድገት በሚቀጥሉት አመታት በማስቀጠል ሀገራችን ኢትዮጵያ መካከለኛ ገቢ ካላቸዉ ሀገሮች ተርታ እንድትሰለፍ ከመቸዉም ጊዜ በላይ በትኩረት መሰራት እንዳለበትም አመላክተዋል።

የዞኑ አስተዳደር እንደዞን በሚከናወኑ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ አስተዳደራዊ የልማት ስራዎች ዉጤታማ እንዲሆኑ የበኩሉን እየተወጣ እንደሆነም ተናግረዋል።

የተቋሙ ሰብአዊና ቁሳዊ ሀብት አቀናጅቶ ለመምራት ዉጤታማ የዕቅድ አፈጻጸም ለማስመዝገብ ህብረተሰቡ የበለጠ ተጠቃሚ ለማድረግ የ2016 በጀት አመት እቅድ አፈጻጸም ከጽህፈት ቤቱ አጠቃላይ የመኔጅመንት አባላት በስፋት በመገምገም ጠንካራ ጎኖች በማስቀጠልና መሻሻል ያለባቸዉ ለማሻሻል እየተሰራ እንደሆነም ተናግረዋል።

የለዉጥ ስራዎችና የሪፎርም ፕሮግራሞች አተገባበር ዉጤታማነት ማሳደግ ይገባል ብለዉ ለተግባራዊነቱ ቅንጅታዊ ስራዎች አጠናክረዉ ማስቀጠል እንደሚገባም አብራርተዋል።

የተገልጋይ እርካታና አመኔታ ለማሳደግ እንዲሁም የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚደረገዉ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ስራዎች በሩ አመቱ አንድ ጊዜ ክትትል ለማድረግ ታቅዶ ተከናዉኗል ብለዋል።

ለሚቀርቡ የጸጥታ ጉዳዮች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ታቅዶ ከሚመለከታቸዉ አካላት ጋር በመቀናጀት የጸጥታ ጉዳዬች ምላሽ ተሰጥቷል ብለዋል።

የቅሬታና አቤቱታ ዉሳኔ አሰጣጥ የተገልጋይን እርካታ ለማሳደግ 698 ቅሬታና አቤቱታ በመቀበል በመመርመርና በማጣራት ዉሳኔ ማግኘት እንደተቻለም አብራርተዋል።

ከመንገድ ፣ከንጹህ መጠጥ ዉሃ ጋር ተያይዞ 257 አቤቱታዎች በማጣራት ከሚመለከታቸዉ የመንግስት ተቋማት ጋር ጋር ተቋማት በጋራ ግብረሃይ በማዋቀር በተቀመጠዉ አቅጣጫ መሰረት ምላሽና ዉሳኔ እንዲያገኙ የተደረገበት ሁኔታ መኖሩም አስረድተዉ በአስተዳደራዊ ዉሳኔ መፈታት ሳይችሉ የቀሩ ወደ ፍርድ ቤት ሄደዉ መፍትሄ እንዲሰጥ የተደረጉ አቤቱታዎች ይገኙበታል ብለዋል።

Gurage Zone Government Communication Affairs

01 Nov, 17:26


ጥቅምት 22/2017
በጉራጌ ዞን ብልጽግና ፓርቲ በወልቂጤ ማእከል ለሶስተኛ ዙር ሲሰጥ የነበረው የአመራሮች አቅም ግንባታ ስልጠና መጠናቀቁ የጉራጌ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት አስታወቀ።

የጉራጌ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ ገ/መስቀል በሰጡት ማጠቃለያ ሀሳብ በዞኑ "የህልም ጉልበት ለእምርታዊ እድገት" በሚል ርእስ ለ10 ተከታታይ ቀናት በተለያዩ እርሰ ጉዳዮች ላይ ስልጠና ሲሰጥ ቆይቷል።

የስልጠናው ዋና ዓላማ አመራሩ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የማህበራዊ እና የውጭ ግንኙነት ሥራዎችንና የተቋማት ግንባታ ውጥኖችን ከሀገራዊ ህልም እና ከብሔራዊነት ትርክት ጋር አስተሳስሮ የአገልጋይነት ስነ-ምግባራዊ አመራርን መሰረት ባደረገ መልኩ በውጤታማነት ተግባራዊ እንዲያደርግ ለማስቻል ነው።

ስልጠናው ብቻው ግብ ስለማይሆን ሁሉም ነገን ለመስራት ዛሬ መዘጋጀት ይጠበቅብናል ሲሉ መክረዋል።

በተጨማሪ ፓርቲውንና እና መንግስትን የሚያጠናክሩ፣ ችግር ፈቺ እና ለቀጣይ የብልፅግና ጉዞ አጋዥ የሆኑ ገንቢ ሀሳቦችን በግብዓትነት የተገኘበት መሆኑንም አቶ አለማየሁ ገልጸዋል።

በቀጣይም አመራሩ በስልጠናው ላይ በተነሱ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በራስ ጥረት የበለጠ አቅሙን አዳብሮ በልማት፣ በመልካም አስተዳደር፣ በሰላም፣ በዲፕሎማሲ፣ በተቋምና በዴሞክራሲ ባህል ግንባታ በአጠቃላይ ሁለንተናዊ ብልፅግናን እውን ለማድረግ የሚደረገውን ትግል ይበልጥ ለማቀጣጠል አስተዋፆ ለማበርከት እንደሚጠበቅም አመልክተዋል።

በሰላምና ጸጥታ እንዲሁም የህዝቡን የደህንነት ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ አመራሩ በቁርጠኝነት መስራት የሚያስችለውን አቅም መገንባት የሚያስችል ስልጠና እንደነበርም ጠቁመዋል።

የጋራ ትርክቶቻችን የሚጠናከሩበትን አብይ ጉዳዮች በስልጠናው መዳሰስ ተችሏል ያሉት ኃላፊው የፖለቲካ የዴሞክራሲ እምርታ ላይ ያለውን የላቀ ድርሻ ማስገንዘብ ተችሏል ብለዋል።

የአመራር ስርዓቱን በማዘመን በህዝቡ ሁለንተናዊ ህይወት ላይ መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት የአመራሩን አቅም መገንባት አብይ ጉዳይ በማድረግ እየተሰራ መሆኑንም ኃላፊው ጠቅሰዋል።

ብልጽግና ፓርቲ ሰው ተኮር ነው ያሉት ኃላፊው በዚህም በበጎ ፍቃድ አገልግሎት ስራ በማከናወን 1መቶ 63 ዩኒት ደም የማሰባሰብ እና 1መቶ 80 ሺ ብር በማሰባሰብ በህክምና ላይ ያሉ ወገኖች ማሳከሚያ ተበርክቷል ብለዋል።

በቀጣይ በሁሉም መስኮች እምርታዊ ለውጥ በማሳየት የዞናችን ህዝብ ተጠቃሚ ማድረግ ይጠበቅብናል ነው ያሉት።
ለዚህ ስልጠና አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት እና ተቋማት በሙሉ ምስጋናቸው አቅርበዋል።

በውይይቱ የተሳተፉ አካላት እንዳሉት ስልጠናው አመራሩ የሀሳብ እና የተግባር አንድነት እንድይዝ እና ዞናዊ፣ ክልላዊ ሀገራዊና አለም አቀፋዊ ጉዳዮች በቂ ግንዛቤ በመያዝ እንዲሁም የአመራሩ ክህሎት በማሳደግ ለስራ ውጤታማነቱ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።

በቀጣይም ያገኙት ስልጠና ወደ ተግባር በመቀየር የብልጽግና ጉዞ ለማረጋገጥ እና ህብረተሰቡን በሁሉም ዘርፍ ተጠቃሚ ለማድረግ እንሰራለን ብለዋል።
በመጨረሻም የቀጣይ አቅጣጫዎች እና የአቋም መግለጫዎች በማውጣት መድረኩ ተጠናቋል።

Gurage Zone Government Communication Affairs

29 Oct, 08:30


ጥቅምት 19/2017 ዓ.ም
የወልቂጤ ከተማ ምክር ቤት ባደረገው አስቸኳይ ጉባኤ አቶ ሙራድ ከድር የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ተጠባባቂ ከንቲባ አድርጎ ሾመ።

በጉራጌ ዞን የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 2ኛ ዙር 12ኛ አመት 8ኛ አስቸኳይ ጉባኤ አቶ ሙራድ ከድር የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ተጠባባቂ ከንቲባ አድርጎ ሾሟል።

በጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳደር እና የግብርና መምሪያ ሀላፊ  አቶ አበራ ወንድሙ አቅራቢነት አቶ  ሙራድ ከድር በእጩነት ቀርበው የምክር ቤት አባሉ በሙሉ ድምፅ የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ተጠባባቂ ከንቲባ አድርጎ ሾሟል።

አቶ ሙራድ ከድር  በጉራጌ በዞንና በወረዳ በተለያዩ የመንግስት ተቋማት በከፍተኛና በመካከለኛ የስራ ሀላፊነት ህዝብ ሲያገለግሉ  የቆዩና በነበራቸው የስራ ቆይታ  መልካም አፈፃፀም የነበራቸው ሲሆን በዛሬው እለት  አቶ ሙራድ ከድር የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ተጠባባቂ ከንቲባ አድርጎ የምክር ቤት አባሉ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።

አቶ ሙራድ  ከድር ባደረጉት ንግግር ወልቂጤ ከተማ የብዙ ታሪኮችና የልማት እድሎች ባለቤት ፣ የታታሪዎችና የስራ ወዳዶች መፍለቂያ እንዲሁም የብዙ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች መኖርያና የንግድ ኮሪደርና ከሀገራችን ከተለያዩ ክፍሎች የሚቀሳቀሱ እንግዶች ማረፊያ የሆነችው ከተማችን ካሏት ምቹ እድሎች አኳያ አቻ ከተሞች ከደረሱበት የእድገት ደረጃና ተወዳዳሪ እንድትሆን ሁሉም በቅንጅት ሊሰራና ሊያግዝ ይገባል ብለዋል።
በዛሬው አስቸኳይ ጉባኤ በተመሳሳይ አቶ ታደለ በቀለ  የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ዋና የመንግስት ተጠሪ አድርጎ የሾመ ሲሆን ሹመቱም ለምክር ቤት አባላት ቀርቦ በሙሉ ድምፅ ፀድቋል።

1,484

subscribers

22,171

photos

17

videos