Abu hatim Abduselam Assalefiy @abuhatimaselefiy Channel on Telegram

Abu hatim Abduselam Assalefiy

@abuhatimaselefiy


ትክክለኛው እስላማዊ አስተምህሮ ከቁርአንና ከሐዲስ ከደጋግ ቀደምቶች አረዳድ ከታማኝ ዑለሞች ንግግር የሚሰራጭበት ቻናል ነው።

Abu hatim Abduselam Assalefiy (English)

Abu hatim Abduselam Assalefiy is a Telegram channel that provides valuable insights and teachings on Islamic faith and practices. Led by the knowledgeable and respected individual, Abu hatim Abduselam Assalefiy, this channel is a great resource for those looking to deepen their understanding of Islam. With a focus on promoting peace, love, and unity through the teachings of the Quran and the Prophet Muhammad, this channel offers daily reminders, lectures, and discussions on various topics related to Islam. Whether you are a seasoned Muslim seeking further knowledge or someone new to the faith wanting to learn more, Abu hatim Abduselam Assalefiy is the perfect channel for you. Join the community today and embark on a journey of spiritual growth and enlightenment.

Abu hatim Abduselam Assalefiy

17 Feb, 09:02


🟢 የአዛውንቱ ምስክርነት ከሌራው ዝግጅት መልስ

ድምፃቸውን የምትሰሙት አባት ከነበሩበት የሺርክና የቢድዐህ መንገድ ኮተት ወደ ተውሂድና ሱነህ ብርሃን በቅርቡ የገቡ የእድሜ ባለፀጋ አዛውንት ናቸው። አላህ ይጠብቃቸው።

ከሌራው ሀገር አቀፍ የዲን ድግስ ስንመለስ መጓጓዣ ላይ ተገናኝተን ከተናገሯቸው ጣፋጭ ቁምነገሮች ውስጥ፦

↪️ አህሉሱነህ ሰለፊዩች ማህበረሰቡን በአላህ ፈቃድ ከጥመት እያወጡ ነው።

↪️ ሀቅ ያልደረሰው ሀቅ ናፋቂ ማህበረሰብ እጅግ ብዙ ነው።

↪️ ኢኽዋኖች እና ሙመይዓዎች እንሚሞግቱት ሺርክን በስሙ በዝርዝር ማስጠንቀቅ ማህበረሰቡን የሚያስበረግግ ሳይሆን የሚያስደስት ኑር ነው።

↪️ የመጅሊሱ ባለስልጣናት በተውሂድ ዳዕዋ ላይ እያደረሱት ያለውን ጫና የገጠሩ ማህበረሰብ እንኳን አውቆታል።

↪️ አህሉሱናን የሚቃረናቸው ፣ የሚያንቆሽሻቸው ፣ የሚያሴርባቸው ሸረኛ ሁሉ አይጎዳቸውም ምክንያቱም አላህን ይዘዋልና።

↪️ ሁሌም ሀቅ ወደ ፊት ሁሌም ሀቅ ወደ ኸይር ነው !!

🤲"ከዚያ ጥመት አውጥቶ በዚህ ኒዕማ (ፀጋ) ላይ ያደረገኛ አላህ ሞቴንም በዚሁ ላይ ያድርገው!! " ይላሉ

አላህ ለሀቅ ይምራን እስከመጨረሻውም ያፅናን!

✏️ ሰውየው "ሀጂ ሀሚድ" ሲሉ አሸይኽ ዐብዱልሀሚድ አለተሚይ ነው።

http://t.me/Abuhemewiya

Abu hatim Abduselam Assalefiy

17 Feb, 07:48


👉 የሌራን ኮንፈረንስ ልዩ የሚያደርገው ምንድነው ?

የሌራ ሀገር አቀፍ ኮንፈረንስ ከሌሎች ለየት የሚያደርገው ብዙ ነገር ቢኖርም በዋነኝነት 3 ነገሮችን ልጥቀስ : –
1 – አስገራሚ ማኔጅመንት
ፕሮግራሙ በጣም አስገራሚ በሆነ ሁኔታ ማኔጅ ተደርጎ ነበር ። ለዚህ ትልቁን ድርሻ የወሰደው ወንድማች ዐ/ሀዲ ሲሆን አላህ ይጨምርለትና በሚገርም ሁኔታ ፕሮግራሙን ከመጀመሪያ እስከመጨረሻ ማኔጅ አድርጎታል ። እንግዶቹን የተቀበሉበትና ያስተናገዱበት ሁኔታ አስደማሚ ነበር አላህ ይቀበላቸው ።

2 – የአካባቢው ሴቶች ተሳትፎ
በጣም በሚገርም መልኩ የአካባቢው ሴቶች ኮሚቴው ካዘጋጀው መስተንግዶ ውጪ ለእንግዶች መቀበያ እንዲሆን አዋጥተው አንድ ሰንጋ ገዝተው በመስጠት ኮሚቴውን ካስደነገጡ በኋላ ላጠቃላይ በሺዎች ለሚቆጠረው እንግዳ ቁርስ አዘጋጅተው አብልተዋል ። ይህ በጣም የሚገርም የሴቶቹ ተግባር አላህ በመልካም ስራ መዝገባቸው ላይ አስፍሮ ለጭንቁ ቀን ስንቅ ያድርግላቸው የሚል ዱዓእ እንዲደረግላቸው አድርጓል ።

3 – የኻዲሞቹ ቅንጅት
በርግጥ በዚህ ነጥብ ላይ የጉንችሬና የሓራ ኻዲሞች የሚጋሩዋቸው ቢሆንም የእነርሱን ለየት የሚያደርገው አንድ ነገር አለ ። እሱም ሌሎቹን ሳይጨምር የወጥ ቤት ኻዲሞች ብቻ አዋጥተው ለወላኢታ ዩንቨርሲቲ ተማሪዮች ለመድረሳ ኪራይ ድጎማ 11 ሺህ ብር ለግሰዋል ። እነርሱንም አላህ ይቀበላቸው እንላለን ።
ባጠቃላይ ፕሮግራሙ ልዩ ትዝታ በሰለፍዮች አእምሮ ላይ ጥሎ አልፏል ምስጋና ለዓለማቱ ጌታ የተገባ ይሁን ።

http://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

17 Feb, 07:48


👉 ለእነሞር ወረዳ ቀበሌ መስጂድ ኮሚቴዎች

🏝 ውድ የእነሞር ወረዳ ቀበሌ መስጂድ ኮሚቴዎች አላህ ካለ የ1446ኛው አመተ ሂጅሪያ ረመዳን ወር ፆም ቀናቶች ቀርተውታል። በመሆኑም ተራዊሕን በሒፍዝ በየደረጃው መስገድ የምትፈልጉ የየመስጂዶች ከሚቴዎች በአስቸኳይ ወደ ጉንችሬ ዳሩል ሂጅራ የሒፍዝና የሸሪዓ እውቀት ማእከል በመቅረብ መመዝገብና አሰጋጅ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን ለመግለፅ እንወዳለን።
   
   የዳሩል ሂጅራ አስተዳደር

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

16 Feb, 15:36


🔊ፈትዋ   በሸኽ  አብዱሀሚድ(ሀፊዘሁላህ)


በስልጤ  ዞን  በሌራ ከተማ  ሀገር አቀፍ ኮንፈረንስ
የተደረገ    ገራሚ ፈትዋ
በዙ   ፈዋዒዶች  ያቀፈ  የሆነ  ፈትዋ ነው


  




https://t.me/hayider_tajudein

Abu hatim Abduselam Assalefiy

16 Feb, 15:36


በአላህ ስም እና ባህሪያት ዙሪያ
^^^^^^^^^^^^^^^^^^

🏝 بَيَانٌ عَنِ التَّوْحِيْدِ وَالْأَسْمَاءِ وَالصِّفَاتِ
🏝 ስለ አላህ አንድነት ስለ ስሞቹ እና ባህሪያቶቹ ዙሪያ ማብራሪያ


🎙 لفَضِيلَةِ الشَّيخِ عبد الحميد بن ياسين السني السلفي السلطي اللتمي «حفظه الله ورعاه»

🎙 ሸይኽ ዐብዱልሐሚድ ብን  ያሲን አል'ለተሚይ! አላህ ይጠብቃቸው!

🛖 በስልጤ ዞን ምዕራብ አዘርነት ወረዳ ሌራ ከተማ በኢማሙ አህመድ መስጂድ ላይ የተደረገ ሙሐደራ

🗓  የካቲት 8/2017

🌐 t.me/abuzekeryamuhamed

🏝 ••⇣⇣.  🏖   ••⇣⇣ 
╰𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞.   ╰𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞

---------------⫷⫸-----------------
🖥️ በ 𝐓𝐞𝐥𝐞𝐠𝐫𝐚𝐦~𝐂𝐡𝐚𝐧𝐧𝐞𝐥
🏝 ⇣⇣⇣🍭⇣⇣⇣📲 ⇣⇣⇣↙️
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy
⫷⫸⫷~⫸⫷⫸⫷~⫸⫷⫸⫷~⫸

Abu hatim Abduselam Assalefiy

16 Feb, 15:15


ሙመዪዖች ከዚህ በፊት የነበሩበትን ሀቅና አሁን ላይ ያሉበትን ጥመት የሚያብራራና ግልፅ የሚያደርግ ተከታታይ ሙሃዷራ !!

        ክፍል (1⃣5⃣)
🎙الشيخ الفاضل أبو طلحة أبوذر بن حسن الولوي حَفِظَهُ اللَّهُ

https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha

     https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha

Abu hatim Abduselam Assalefiy

16 Feb, 08:15


የባሕሩ አባት ሰልሟል ወይ ላላች ወንድምና እህቶች

በአልከሶና አካባቢዋ ሰለፍዮች ግሩፕ ላይ አንድ ወንድም ባሕሩ ተካ ( አሕመድ ) ብሎ ፅፎ አሕመድ ማን ነው ? የአባቱ ስም ነው ወይ ? ወይስ ሌላ ባሕሩ ነው ? ባሕሩ ተካ ከሆነ አባቱ ሰልሟል ወይ የሚሉ ጥያቄዎች ተደጋግሞ አይቻለሁ ። ይህ ጥያቄ በብዙዎች አእምሮ ሊኖር ስለሚችል ለወንድምና እህቶች ቤተሰቦቼ በሙሉ የሰለሙ መሆኑን ላሳውቃቸው ወደድኩ ። መስለማቸው ብቻ ሳይሆን ሁሉም ቤተሰቦቼ ሰለፍዮች መሆናቸውንም አውቃችሁ ዱዓእ እንድታደርጉላቸው ላስታውሳችሁ እወዳለሁ ።
ምስጋና ለአለማቱ ጌታ የተገባ ይሁንና ከአጎቴቼ ውስጥ አብዛኞቹ ከነቤተሰቦቻቸው ሰልሟል ። የተወሰኑት ደግሞ ልጆቻቸው ሰልሟል ። አላህ ሁላችንንም ፅናቱን ይስጠን ።

http://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

16 Feb, 03:23


ኮርስ ተጀምሯል።

📚 شُروطُ الصَّلاةِ وَواجِباتُها وَأركانُها
📚 የሶላት መስፈርቶች ማዕዘናቶቿ እና ግደታዎቿ
📝
للشـيخ محمد بن عبد الوهاب النجدي
🎙 በሸይኽ አብዱልሐሚድ ብን ያሲን አል`ለተሚይ

🏝           ➘➘➘➘➘➘

👇
https://t.me/AbuImranAselefy?livestream=5ac234d0514db83d97

Abu hatim Abduselam Assalefiy

15 Feb, 16:16


👉 ሌራ ተረኛዋ የተውሒድ ጮራ አሰራጭ

በምእራብ ስልጤ ዞን የምትገኘው ሌራ ከተማ ተረኛዋ የታደለች የተውሒድ ጮራ አሰራጭ ሆናለች ። የሌራ አል – ኢማሙ አሕመድ መስጂድ የተውሒድና ሱና መሻኢኽና ኡስታዞችን እንዲሁም ዱዓቶችና እንግዶችን ለመቀበል አንፀባራቂ በለበሱ የሱና ኻዲሞች ተውቦና አምሯል ። መስጂዱ ከተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች በተመሙ መሻኢኾችና ኡስታዞች እንዲሁም ዱዓቶች የተውሒድ ዘር እየተዘራበትና የብርሃኑ ጮራ እየፈነጠቀ ይገኛል ።
ሰው ምን ይለኛልን በማይፈሩ የቁርጥ ቀን ዑለሞችና መሻኢኾች ነጭ ነጩ እንቅጭ እንቅጩ እየተነገረ ነው ። የተውሒድ ሚስጢር እየተገለፀ የሽርክ ቫይረስ ላይ አጥፊ መድሃኒት እየተረጨ ነው ። ሐቅን ደብቆ አንድነት የለም, ሐቅን ደብቆ ስምምነት የለም ሐቁ ይነገራየጠላ ይጠላል የወደደ ይወዳል ። ስለተውሒድ ለተበሩክ ሳይሆን ሽርክን ለማጥፋት ማስተማር ነብያዊ ተልእኮ ነው ። በመሆኑም ሽርክን በጥቅሉ ሳይሆን በዝርዝር እየአንዳንዱ በስሙ ሌራ ላይ እየተነገረ ይገኛል ።
የሌራ ከተማ በተውሒድና ሱና መአዛ ታውዳለች ። መንገዶቿ ፣ መንደሮቿ ፣ ጋራ ሸንተረርዋ ተውሒድ ተውሒድ ይሸታሉ ። ጎዳናዎቿ የሱና አበባ ተነስንሶ ላየ ጤነኛ ልቦና ባልተቤት የደስታ ሲቃ ያሲዛል ።
ለዚህ ታላቅ ፕሮግራም መሳካት የከተማዋ የፖሊስ የፀጥታና የድርጅት ሀላፊዮች የተጣለባቸውን ህዝብን የማገልገል ሀላፊነት በቅንነት መወጣት አላህን ከማመስገን በኃላ ሊመሰገኑ ይገባል ። በቅርቡ አሊቾ ወረዳ ላይ ያየነውና አሁን ምእራብ አዘርነት በርበሬ ሌራ ወረዳ ላይ ያለው ሁኔታ የእነዚህ የሴክተር መ/ቤቶች ያሳዩት ሀላፊነትን በአግባቡ መወጣት የስልጤ ዞንን ገፅታ የሚቀይርና እሰይ የሚያሰኝ ሌሎችም ሊከተሉት የሚገባ የሚደነቅ ተግባር ነው ።

http://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

15 Feb, 10:12


👉 የአላህን ባህርይ መለመን

የአላህን ባህርይ ነጥሎ መለመን ሽርክ ነው ይላሉ ዑለሞች ። አላህ የተከበሩና የተላቁ ስምና ባህሪያቶች አሉት ። የአላህ ባህርይ ደግሞ ከባህሪው ባለቤት ተነጥሎ አይታይም ። በመሆኑም አንድ ስው " ያ ዐሊሙ ዐሊምኒ ፣ ያ ጘፉሩ ኢጝፊር ሊ …… " ቢል አላህን ነው እየለመነ ያለው ይባላል ። ነገር ግን አንድ ሰው ባህሪውን ብቻ ነጥሎ ቢለምን ለምሳሌ ያ ረሕመተላሂ ኢርኸምኒ ፣ ያ መጝፊረተላሂ ኢጝፊር ሊ ፣ ያ ዒልመላሂ ዐሊምኒ ቢል በአላህ ላይ አጋራ ይባላል ። ይህ የሚሆነው ይላሉ ዑለሞች ባህሪውን ከባህሪው ባለቤት ለይቶ ሲለምን ከአላህ ሌላ የጠራ ስለሚሆንበት ነው ።
ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያ " የአላህን ባሪዮችና ንግግሮቹን ነጥሎ መለመን በሙስሊሞች ስምምነት ኩፍር ነው " ይላል ። ምክንያቱም የሚለመነው የባሕሪው ባለቤት እንጂ ባሕሪው አይደለምና ። የአላህን ባሕሪ ከሱ መነጠል አይፈቀድም ምክንያቱም በራሱ የቆመ ሳይሆን በአላህ የቆመ ስለሆነ ። በራሱ የሚቆም ባህሪይ ፉጡር ነው ። ልክ በይቱላሂ እንደሚባለው ። በአላህ ላይ እንጂ የማይቆምን ባሕር ነጥሎ መጥራት ወይም መለመን ባሕሪውን ፉጡር ማድረግና ፉጡርን መለመን ስለሚያስመስል ከባድ ወንጀል ነው ። ለዚህ ነው ሽርክ ነው የሚባለው ። ሸይኽ ሙሐመድ ሳሊኸል ዑሰይሚንም በዚህ መልኩ ይገልፁታል ። የተወሰነ ተጨምሮበት ሸይኻችን ሸይኽ ዐ/ሐሚድ ሌራ በኮንፈረሱ ላይ ካደረጉት ሙሓደራ የተወሰደ ።

http://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

15 Feb, 07:03


🚫 የጉሩፖች ልመና

♻️ መልካም ስራ ላይ መተባበርና ሁሉም በየአቅሙ አሻራ ማኖሩ ጠቀሜታው የበዛ ነው። በተለያዩ ግሩፖች በጣም አመርቂ ሥራዎች ተሠርተዋል እየተሰሩም ነው። በተለይ በሱናው ዳዕዋ መንገድ ላይ የተጋረጡ የመስጂድ እጦትና የመድረሳ ችግሮችን ለመፍታት እንዲሁም ቦታ ጭምር ገዝቶ እነዚህን የተቀደሱ ሥራዎችን ለመስራት

ይህ እንቅስቃሴ ያበረከተው አስተዋፆ ቀላል አይደለም። በተቃራኒው ግሩፕ እየከፈቱ ደርስ ብለው ጀምረው ብዙም ሳይቆዩ ግሩፑን ለልመና የሚያውሉ ይህን ተግባር በተቀነባበረ መልኩ የሚፈፅሙ እየበዙ ነው። የሱናውን ማህበረ ሰብ ለመያዝ ለተወሰነ ጊዜ በሱና የሚታወቁ ወንድሞችን ኦዲዮና ፁፎችን ሼር በማድረግ አባል ከሰበሰቡ በኃላ ወደ ዋናው አላማቸው በመሸጋገር እንዲህ የሚባል አካባቢ ሙስሊሞች በመድሰሳና በመስጂድ እጦት እየተሰቃዩ ነው በሚል አካውንት በመክፈት ብር መሰብሰብ ይጀምራሉ ኸይር ፈላጊው የሱና ማህበረ ሰብ ማን ነው የት ነው ብሎ ከመጠየቅ ይልቅ የምችለውን ላበርክት በማለት የበኩልን ድርሻ ከተወጣ በኀላ ዞር ብሎ አያይም። ምናልባትም የሚፈልጉትን ካገኙ በኀላ ግሩፑን ዘግተው ቢሄዱ የት እንደሄዱም አይታወቅም።

በአብዛኛው የዚህ አይነት ስራ የሚሰሩ ሰዎች አካውንት የሚከፍቱት በአንድ ሰው ስም ወይም በሚስማሙና አንድ ላይ ተነጋግረው በጀመሩ ሰዎች ስም ነው። እንደነዚህ አይነት ሰዎች አላህን ሊፈሩ ይገባል። ይህ ከሌብነት የተናነሰ አይደለም። ከተለያየ ሰው አጅር አገኛለሁ ብሎ በፈቃዱ የተሰበሰበ መሆኑ ከተባለለት አላማ ውጪ ከዋለ ከሌብነት አያወጣውም። ምክንያቱም የሰጠው ሰው ለተባለው ነገር ባይሆን አይሰጥም ነበርና።

↪️ ትክክለኛ አላማ ይዘው ለሱና የሚለፉ ወንድምና እህቶች በተቻለ መጠን ለዚህ አይነት ተግባር የሚከፈት አካውንት በፍፁም በግለሰብ ስም መሆን የለበትም። ምክንያቱም ሰው ነውና ወደ አኼራ ቢሄድ የወራሽ ንብረት ነው የሚሆነው። ሌላው ኡስታዞች ወይም ዱዓቶች በፍፁም ከገንዘብ ጋር ሊገናኙ አይገባም እነርሱ መቆጣጠር አቅጣጫ መስጠት ነው ያለባቸው። ከተቻለ አቅም ባላቸው ምንም በማይፈልጉ በተለያዩ አላህን ይፈራሉ ብሎ በሚታመንባቸው ሶስት ሰዎች ስም ቢሆን በጣም ጥሩ ነው። ይህም መሆን ያለበት አካባቢው ላይ ባሉ ወንድሞች መነጋገርና መተማመን ላይ ከተደረሰ በኋላ ቢሆን ጥሩ ነው።

አንድ ሰው ተነስቶ አካውንት ከፍቶ እንዲህ አይነት ተቋም ልመሰርት ነው ብሎ ወደዚህ አካውንት አስገቡ ማለት በጣም ትልቅ ስህተት ነው። ሌላው በተቻለ መጠን የሚያስፈልገው ነገር ታውቆ ተነግሮ ጉዳዩ ሲያበቃ ግሩፑን መዝጋቱ ለታአማኒነቱ የቀረበ ነው። ይህ በአንዳንድ ወንድሞች አይተንዋል አላህ ይጨምርላቸው። የዚህ አይነቱ ጉዳይ በጣም ሊፈሩት የሚገባ ከገቡበትም በጣም ጥንቃቄ የሚፈልግ ነው። ካልሆነ ምንም የማያውቁ ህፃናቶቻችንን ሐራም እያበላን እንዳናሳድጋቸው

በአሁኑ ጊዜ ደግሞ እገሌ የሚባል ወንድማችን ወይም እህታችን የሰው እዳ አለበት/ባት በሚል በዚሁ መልኩ ግሩፕ ተከፍቶ መለመን እየተስፋፋ ነው። የዚህኛው ከሌሎች በጣም የከፋ ነው የሚሆነው። ምክንያቱም እዳ የሌለበት የማግኘቱ እድል ጠባባ ስለሆነ ይህም አለ እንዴ ብሎ ሁሉም መክፈቱ ስለማይቀር። በዚህ መልኩ የምትለምኑ ወንድምና እህቶች የምትለምኑለት ሰው አላህ ከእዳ እንዲያወጣው ዱዓእ አድርጉለት። ከዛ በኋላ እዳ ያለበት ሰው የሚያደርገውን ዱዓእ አስተምሩት። በህይወት የሌለ ከሆነ ወልዮቹ የመጀመሪያውን ድርሻ ይወስዳሉ። እነርሱ ካልቻሉ ዘመድ አዝማድ የሚችለውን ማድረግ ይጠበቅበታል። ከዚህ ባለፈ ግሩፕ ከፎቶ ለምኖ ማሳየት በጣም አስቸጋሪ ነውና መተዉ ይሻላል። ከዚህ ጋር በተገናኘ ለማጣራት ሞክረን የደረስንበት ውጤት አሳፋሪ የሆነ መኖሩን ለመጠቆም እወዳለሁ።

ኢስላም ልመናን በፅኑ ያወግዛል። ይህን ማህበራዊ ችግር ለመፍታት ነው ዘካ ግዴታ የተደረገው። በተለይ ይህን ተግባር ክፍት የስራ ቦታ አድርገው የሚንቀሳቀሱ ሰዎች እየበዙ ስለሆነ ነው ለማስታወስ የፈለግሁት

ከተወሰነ ጭማሪ ጋር በድጋሚ የተለቀቀ

http://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

15 Feb, 06:59


🔸 አዲስ ኹጥባ

🔊 “የረመዳን ትሩፋቶች!!”

🎙በሸይኽ አቡ ዐብዲል ሀሊም ዐብዱል ሀሚድ ያሲን አል-ለተሚይ (ሐፊዘሁላህ)

ሌራ ኢማሙ አህመድ መስጂድ የተደረገ

🗓
ሸዕባን 15/1446
https://t.me/abdulham
https://t.me/abdulham
https://t.me/abdulham

Abu hatim Abduselam Assalefiy

15 Feb, 06:55


Live stream finished (3 hours)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

15 Feb, 03:44


የኮርሱ ኪታብ pdf

📚 شُروطُ الصَّلاةِ وَواجِباتُها وَأركانُها
📚 የሶላት መስፈርቶች ማዕዘናቶቿ እና ግደታዎቿ

📝 للشـيخ محمد بن عبد الوهاب النجدي

🎙 በሸይኽ አብዱልሐሚድ ብን ያሲን አል`ለተሚይ

🏝           ➘➘➘➘➘➘
https://t.me/AbuImranAselefy/9844

Abu hatim Abduselam Assalefiy

15 Feb, 03:28


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

14 Feb, 19:38


📙 ከሙብተዲዖች ጋር መቀማመጥ ያለው አደጋ!

ታላቁ የየመኑ ሊቅ ሙሀመድ አሽ’ሸውካኒይ ረሂመሁላህ እንዲህ ይላሉ፦

«قال الله تعالى "وَإِذَا رَأَيْتَ الَّذِيْنَ يَخُوْضُوْنَ فِيْ آيَاتِنَا فَأَعْرِضْ عَنْهُمْ حَتَّىٰ يَخُوْضُوْا فِيْ حَدِيْثٍ غَيْرِهِ" الأنعام: ٦٩

አላህ ጀለ ወዓዘ እንዲህ አለ "እነዚያንም በአንቀጾቻችን የሚገቡትን ባየህ ጊዜ ከእርሱ ሌላ በኾነ ወሬ እስከሚገቡ ድረስ ተዋቸው፡፡" አንዓም 68

وفي هذه الآية موعظة عظيمة لمن يتسمح بمجالسة المبتدعة، الذين يحرفون كلام الله، ويتلاعبون بكتابه وسنة رسوله صلى الله عليه وسلم ويردون ذلك إلى أهوائهم المضلة وبدعهم الفاسدة، فإنه إذا لم ينكر عليهم ويغير ما هم فيه فأقل الأحوال أن يترك مجالستهم، وذلك يسير عليه غير عسير.

በዚች አንቀፅ ውስጥ እነዚያ የአላህን ንግግር የሚያንሻፍፉ፣ በመፅሀፉ እና በመልእክተኛው መንገድ የሚጫወቱ፣ ያንን ሁሉ ወደ አጥማሚ ስሜታቸው እና ወደ ተበላሸ ፈጠራቸው የሚመልሱ የሆኑትን ሙብተዲዖችን በመቀማመጥ ለሚተሻሽ ሰው ሁሉ ትልቅ ምክር አለ። እሱ ካልተቃወማቸው እና እነሱ ያሉበትን ሁኔታ የማይቀይር ከሆነ፤ ያለበት ትንሹ ሀላፍትና እነሱን መቀማመጥ መተው ነው። ይህም ደግሞ በሱ ላይ ቀላል ነው ከባድ አይደለም።"

وقد يجعلون حضوره معهم مع تنزهه عما يتلبسون به شبهةً يشبهون بها على العامة ،فيكون في حضوره مفسدة زائدة على مجرد سماع المنكر.

ሰውዬው ከነሱ ቢድዓ የጠራ ከመሆኑም ጋር ከነሱ ጋር መቀማመጡን በተራው ማህበረሰብ ላይ የሚያወዛግቡበት ብዥታ ሊያደርጉት ይችላል። ስለዚህ እነሱ ጋር በመቀማመጡ መጥፎን ነገር ከመስማት በሻገር ተጨማሪ ውድመት ይከሰታል።

وقد شاهدنا من هذه المجالس الملعونة ما لا يأتي عليه الحصر، وقمنا في نصرة الحق ودفع الباطل بما قدرنا عليه، وبلغت إليه طاقتنا.

በርግጥ ከነዚህ የተረገሙ መቀማመጦች የማይገደቡ በርካታ ነገራቶችን አይተናል። ሀቅን በመርዳት እና ባጢልን በመገፍተር የቻልነውን ልክ እና አቅማችን በደረሰችው ቆመናል።

ومن عرف هذه الشريعة المطهرة حق معرفتها، علم أن مجالسة أهل البدع المضلة فيها من المفسدة أضعاف أضعاف ما في مجالسة من يعصي الله بفعل شيئ من المحرمات

ይቺን ንፁህ የሆነችዋን ሸሪዓን ተገቢ የሆነን መገንዘብ የተገነዘበ ሰው የአጥማሚ ፈጠራ ባለቤቶችን መቀማመጥ ከአደጋ ሆኖ በውስጡ ከክልክሎች አንዱን በመስራት አላህን የማመፅ ባልተቤቶችን መቀማመጥ ውስጥ ካለው አደጋ የእጥፍ እጥፍ እንደሆነ ያውቃል።

ولاسيما لمن كان غير راسخ القدم في علم الكتاب والسنة فإنه ربما ينفق عليه من كذباتهم وهذيانهم ما هو من البطلان بأوضح مكان، فينقدح في قلبه ما يصعب علاجه ويعسر دفعه فيعمل بذلك مدة عمره ويلقى الله به معتقدا أنه من الحق ،وهو من ابطل الباطل وأنكر المنكر.


በተለይ ደግሞ በቁርአን እና ሀዲስ እውቀት እግሩ ያልጠለቀ ለሆነ አካል! ምናልባትም ከመዘባረቃቸው እና ከመዋሸታቸው የሆነ በጣም ግልፅ በሆነ ደረጃ ያለ ባጢል ሊደበቅበት ይችላል። ከዚያም መታከሙ የሚያስቸግር እና መገፍተሩ የሚከብድ የሆነ ነገር በልቡ ላይ ይጫራል። እድሜ ልኩ በዚያ ባጢል ይሰራ። በጣም ግልፅ ከሆኑ ውሸቶች እና በጣም ግልፅ ከሆኑ መጥፎዎች የሚቆጠር ሆኖ ሳለ ሀቅ ነው ብሎ ያሰበ ሲሆን አላህን በዛ ባጢል ይገናኛል።»

اهـ فتح القدير سورة الأنعام: الآية ٦٩.

ዛሬ ዛሬ ግን በርካታ ከመንሀጅ የተፍረከረኩ የሆኑ አካላት ከቢድዓ ባልተቤቶች ጋር በመስለሀ ስም አድርገው የሚቀማመጡ፣ የሚጓዙ፣ የሚሳሳቁ፣ የሚወዳደሱ፣ የሚሿሿሙ፣ የሚተጋገዙ፣ እና የሚተሻሹ በርካታ ናቸው። በጣም የሚያሳዝነው እነሱን አይቶ የሚፍረከረከው በበርካታ የሚቆጠር ወጣት ክፍል ነው። አላህን የሚፈሩ ቢሆኑ እዛ የሚገኝ የሆነን ያልተረጋገጠ ጥቅም አይኖች ከሚያዩት ግዙፍ ግዙፍ መፍሰዳዎች ጋር ባላወዳደሩ ነበር። በርግጥ ለኡማው መስለሀ በሚል ይቀባቡት እንጂ የሚፈልጉት የግል ጥቅምን ነው። ስልጣን፣ ገንዘብ፣ እውቅና እና ክብር ፈልገው እንደሆነ እያየን ነው። አላህ ሁሉንም ቀናውን መንገድ ይምራው።


በወንድም፡ ሙሀመድ አል-ወልቂጢይ

t.me/abuzekeryamuhamed
t.me/abuzekeryamuhamed

Abu hatim Abduselam Assalefiy

14 Feb, 19:38


አዲስ ሙሃዶራ

ርእስ:- ከቢድዓ ባለቤቶች ጋር ከመቀማመጥ ማስጠንቀቅ ከአህሉ ሱና መሰረቶች መካከል አንዱ ነው!!

🎙በሸይኽ መህቡብ አስ’ሳንኩሪይ (ሐፊዘሁላህ)

በሌራ ሀገር አቀፍ ፕሮግራም የተደረገ

#join ⤵️ ቴሌግራም ቻናል
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa

Abu hatim Abduselam Assalefiy

13 Feb, 18:37


🏝 ልዩ ሀገር አቀፍ የዳዕዋና ኮርስ ፕሮግራም

👉 በአላህ ፈቃድ የዲን ትምህርት ድግስ ከቀን 07/06/2017 የጁመዓ ኹጥባ እና ሶላት ጀምሮ  ለተከታታይ 3 ቀናቶች ተዘጋጅቷል።

 🏞 ቦታ፦ ሌራ ከተማ በኢማሙ አህመድ መስጂድ እና መድረሳ ተሰናድቶ ይጠብቃችኋል።

🪑 በዝግጅቱ ላይ ከሚገኙ ውድና ብርቅዬ መሻይኾች መካከል፦
🎙 አሸይኽ ዐብዱልሐሚድ ያሲን (ከለተሞ)
🎙 አሸይኽ ሙሐመድ ሀያት (ከወሎ ሐራ)
🎙 አሸይኽ ሙሐመድ ጀማል (ከኮምቦልቻ)
🎙 አሸይኽ ሙባረክ አልወልቂጢይ (ከቀቤና)
🎙 አሸይኽ አብድል ከሪም (ከኦሮሚያ ጅማ)
🎙 አሸይኽ መህቡብ (ከሳንኩራ)     
🎙 አሸይኽ አህመድ ወሮታ (ከጎንደር)
🎙 አሸይኽ አወል (ከዳሎቻ)

በተጨማሪም በቀጥታ ስርጭት
🎙 አሸይኽ ሁሴይን መሀመድ (ከሳዑዲ አረቢያ)
🎙 አሸይኽ አቡ ዘር ሀሰን (ከሳዑዲ አረቢያ)
🎙 አሸይኽ ሀሰን ገላው (ከባህር ዳር)
🎙 አሸይኽ ዩሱፍ አህመድ (ከባህር ዳር)

👉 እንዲሁም እንደ ኡስታዝ ባህሩ ተካ አቡ ዑበይዳህ የመሳሰሉ በርካታ ኡስታዞች የሚታደሙበት ደማቅ ፕሮግራም ነው።

👉 ከሚሰጡ ኮርሶች መካከል፦
📚 شُروطُ الصَّلاةِ وَواجِباتُها وَأركانُها
📚 የሶላት መስፈርቶች ማዕዘናቶቿ እና ግደታዎቿ

📝 للشـيخ محمد بن عبد الوهاب النجدي
🎙 በሸይኽ አብዱልሐሚድ ብን ያሲን አል`ለተሚይ
       
👌 የሀቅ ወዳጆች ሁሉ በአክብሮት ተጋብዛችኋል እንዳትቀሩብን!

♨️ ማሳሰቢያ፦ ሁላችሁም ማንነታችሁን የሚገልፅ መታወቂያ እና የማታ ልብስ እንዳትዘንጉ።

👌 አላህ ካለ ሩቅ ላላችሁ 𝙡𝙞𝙫𝙚 ላይ እናካፍላችኋለን
🏝           ➘➘➘➘ 
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/Ibnushaffi
🔎 ሸር በማድረግ ለሰለፍዮች በሙሉ የማድረስ ሀላፊነታችንን እንወጣ!

Abu hatim Abduselam Assalefiy

12 Feb, 15:17


የጁሙዓ ቀን ሕግጋት


🎙በሸይኽ ዐብዱልሀሚድ አል-ለተሚይ (ሀፊዘሁላህ)

https://t.me/abdulham
https://t.me/abdulham

Abu hatim Abduselam Assalefiy

09 Feb, 21:01


ሸይኽ አብዱልሐሚድ እና የገጠር ዳዕዋ
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯

🏝 የሀገራችን ህዝብ አብዛኛው መካሪ ካገኘ ያለበትን ክፍተት ለማሻሻል የሚጥር ነው። በተለይ በገጠራማ አካባቢ ሰፍሮ የሚገኘው ሙስሊም ልክ እንደህፃን በሚሰጠው መመሪያ የሚቀየር ነው።

ኢትዮጵያ ላይ አብዛኛዎቹ መሻይኾች ኡስታዞች እና ዱዓቶች ትንሽ ተሰሚነት ካገኙ ፈጥነው ወደ አዲስ አበባ ወይም ወደ ክልል ትልልቅ ከተሞች ይዘምታሉ። ከዛም ለገጠሩ ህዝብ ደንታ የላቸውም።

👌 ሸይኽ አብዱልሐሚድ ያሲን ግን ምቾትን ሳይፈልጉ ድካም ሳይበግራቸው በተለያየ መልኩ የሀገራችንን ገጠራማ ክፍል ህዝብ በማንቃት የማይተካ ሚና ተጫውተዋል።

➪ ሸይኽ በዒልማቸው የላቁ ከመሆናቸው ጋር ዝቅ ብለው (በመሰረቱ ከፍታ ነው) በመንቀሳቀስ ህዝቡን ለመጥቀም ደፋ ቀና ብለዋል።

👉 ሸይኹ እስከ "ገነቴ" ድረስ በመሄድ ጥግ ካሉ የአማራ ክልል አካባቢዎች መካከል ዳዕዋ አድርገዋል። በሰሜን ወሎ በመሄድም ከሰሜን ወሎዎቹ ከካክብት ጋር ዳዕዋ አድርገዋል።

🔎 በዚሁ በስልጤ ዞን እና ጉራጌ ዞን እንዲሁም አጎራባች ያሉ አካባቢዎችን ገጠራቸውን በማዳረስ ሊመከር የሚገባውን የገጠር ማህበረሰብ በዳዕዋ እና ኮርሶች ለመቀየር ሞክረዋል። አላህ ይቀበላቸው!

👌 የሚገርመው ይህንን ጥረት ለማደናቀፍ ደፋ ቀና የሚሉ ሚስኪኖች አላህን ሊፈሩ ይገባል።

https://t.me/AbuImranAselefy/9770

Abu hatim Abduselam Assalefiy

08 Feb, 17:24


Live stream finished (1 hour)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

08 Feb, 17:23


#የአህባሽ_ጥመትና_አቂዳ_በተሰኘ_
#ርዕስ_አድስ_ተከታታይ_ሙሐደሯ
           
            ◈◈◈ክፍል1️⃣◈◈◈

በዚህ ድምፅ ከተወሱ አንኳር ነጥቦች በትንሹ➷➷➷

➻◈➻አህባሽን ለማስወገድና ለመገልሰስ መጀመሪያ ግንዱን ማስወገድ ያለብን ስለመሆኑ!! ግንዱ ምንድን ነው ያድምጡ!!

➻◈➻የአህባሽ መሪ  በወልዮች በነብያቶች...ከሞቱ በኋላ ድረሱልኝ ማለት ከኢባዳ አይቆጠርም(ኢባዳ አይደለም) ይህንን የሚያደርግን ላትቃወመው ዋጅብ ነው ያለ ስለመሆኑ

➻◈➻ከአሏህ ውጭ ያለን መለመን መማፀን ትልቁ ኩፍር፣ትልቁ ሽርክ፣ ትልቁ  የጥመት ጥግ ስለመሆኑ

➻◈➻እንድሁም የስቲغاሳ አቅሳሞች(ክፍሎች)እና መሠል ተያያዥ ነጥቦች ተዳሰዋል በማዳመጥ ተጠቃሚ ይሁኑ!!

🎙للشيخ أبي طلحة أبي ذر بن حسن الولوي حَفِظَهُ اللَّهُ


🎙በሸይኽ አቡ ጦለሃ አቡ ዘር ቢን ሀሠን (አሏህ ይጠብቃቸው)

➻◈➻ተጨማሪ ሸሪዓዊይ እውቀት ለመሸመት ይቀላቀሉ➷➷➷

https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha

Abu hatim Abduselam Assalefiy

03 Feb, 19:18


🚫 የነሲሓ ሙሪዶች ጉድ

የነሲሓ ሙሪዶች አይነት ሙሪድነት ከዚህ በፊትም አላየሁም ከዚህ በኋላም የማይ አይመስለኝም ። ከሙሪድነት መስፈርቶች አንዱና ዋነኛው ሸይኽ የሚሰራውን ነገር ለምን አለማለት ነው ። የሱፍይ ሙሪዶች ሸይኾቻቸው ሱፍዮች መሆናቸውን ተቀብለው ነውትክክል ናቸው ነው የሚሉት ። ሸይኾቻቸው ደግሞ ሙሪዶቻቸው እነርሱን እንዲያመልኩ ከሚያደርጉበት ቀመር አንዱ ሙሪድ በሸይኹ ፊት እንደ ጀናዛ መሆን አለበት የሚል ነው ። ጀናዛ አጣቢው እንደፈለገ ሲያደርገው ለምን አይልም ። ሙሪድም በዚህ ልክ ካልነ ሙሪድነቱ አይረጋገጥም ።
የነሲሓ ሙሪዶች ግን ሸይኾቻቸው ኢኽዋኖች መሆናቸው ልቦናቸው እያወቀ አይ ሰለፍዮች ናቸው ይላሉ ። ተውራትና ኢንጂልም እንኳን ቢነበብባቸውም አይሰሙም ። ይልቁንም ከሚሰሙትና ከሚያዩት በተቃራኒ ይሞግታሉ ። በዚህም ዐቅላቸውንና ህሊናቸውን ተለይተው በደናቸውን ለሸይኾቻቸው ጀባ ብለዋል ። ፀሀይን እያዩ አላየንም ሸይኾቻችን ፀሀይ አይደለም ብለውናል ነው የሚሉት ።
በዚህ አካሄዳቸው መሪዮቻቸውን ከሚያመልኩ አሁድና ነሷራዎች ተግባር ድርሻ ወስደዋል ። አዩዶችን ዑለሞቻቸውን ያመለካሉ እንዲባሉ ያደረጋቸው ሐላሉን ሐራም ሐራሙን ሐላል ሲሏቸው ለምን ሳይሉ በመቀበላቸው እንጂ ለእነርሱ በመስገዳቸው አልነበረም ። የዛሬዎቹ የነሲሓ ሙሪዶች ሸይኾቻቸውን ከማምለክ ድርሻ ወስደዋል ማለት ይቻላል ። ምክንያቱም ኢኽዋኖች መሆናቸው ራሳቸው ሸይኾቻቸው በአደባባይ እያሳዩዋቸው አይ እኛ ለማናውቀው መስላሓ ነው ይላሉ ።
ይህ ማለት የሱፍይ ሙሪዶች ሸይኾቻቸው ኸምር ሲጠጡ እያዩ ወተት ነው እንደሚሉት ማለት ነው ። የነሲሓው ዋና መሪ ሸይኻቸው ኢልያስ አሕመድ ኢኽዋንይነቱ በአደባባይ ሲያሳያቸው አይ ለመስላሓ ነው እንጂ በፍፁም ኢኽዋንይ አይደለም ብለው ነበር ። የኢልያስ አሕመድ የአደባባይ ሚስጢር በሚከተለው ሊንክ ይመልከቱ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

https://drive.google.com/file/d/1v6JbCgHa-C4tZAgiG7i-rCWs4GOoMR1c/view?usp=drivesdk

አሁን ደግሞ ሌላኛው ኡስታዛቸው ሙሐመድ ሐሰን ማሜን ከሙሐመድ ዘይን ዘህረዲንና አቡበከር አሕመድ ጋር በአደባባይ ኢኽዋንይ መሆናቸውንና አንድነታቸውን ያረጋገጠበትን ፖስተር በሚከተለው ሊንክ ተመልከቱና ሙሪዶቹን ምንድነው በሉዋቸው
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

https://drive.google.com/file/d/15Z7lgUwh2-8notUwCGpu2XyFJx-tFhyY/view?usp=drivesdk

እግረመንገዳችሁን ኢብኑ ሙነወርን አሁንም ለመስላሓ እንጂ አምነውበት አይደለም ወይ በሉት ።

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

03 Feb, 08:12


⚠️ትናንትና ባስጠነቀቁት ነገር
ላይ ዛሬ የወደቁ ጉዶች

        ክፍል አምስት

⤵️ የከድር ከሚሴ የበፊቱ አቋሙ ይሄ ነበር  አሁን ላይ ቢሟሟም

⚠️ አልሙመዪዓህ የተሰኙት አካላቶች ወይም ጉሩፖች ተምዪዕ እና ነገራቶችን ያለ አግባብ በመለጠጥ እና በማግራረት የሚታወቁ አካላቶች አሉ ግልፅ የሆነ ነገር ነው።

⚠️ የሙመዪዓ መንገድ አዲስ መንገድ ነው ዑለማዎች የኮነኑት መንገድ ነው ብዙ አኢማዎች ኮንኖታል  ይህንን መንገድ እኛ አንቀበልም።

👉 ከቢዳዓ ባልተቤቶች ጋር መተጋገዝ ይቻላል የሚል ቃዒዳ ይዘው የተነሱ አካሎች ሆነው ተስተውለዋል።

ድሮ ሱናን ያንፀባርቁ ነበር  በኋላ በኋላ ላይ ግን ከቢደዓ ባልተቤቶች ጋር አብሮ መስራት ችግር የለውም የሚል ቃዒዳ ይዘው መጥተዋል በመልካም ነገር እስከሆነ ድረስ ይላሉ !  ይህ ባጢል ነው።

⚠️ ተምዪዕ ውስጥ የገቡ አካላቶችን ሌሎች ሙብተዲዓዎች መጠቀሚያ ድልድይ እንደደረጓቸው ተመልክተናል።

<><><><><><><><><><>
👉 እኛ እነዚህን አካላት አቋም ቀይረዋል ስንል በመረጃ ነው።
👌 አሁንም ቢሆን ሰከን ብላችሁ ወደ ጤናችሁ ብትመለሱ ይበጃል።

  አቡ ያሲር ኢብን ሙዘይን!

https://t.me/YusufAsselafy
https://t.me/YusufAsselafy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

03 Feb, 08:11


↪️ ሙመይዖቹ ኢጅቲሀድ በሚያስተናግድ ጉዳይ አታጥብቁ ይላሉ!

አንዱ ሙመይዕ እንዲህ ብሎ ፅፎ አየሁት «ኢጅቲሐድ በሚያስተናግድ ጉዳይ ላይ በፎቶም ይሁን በጀርህ ወት'ተዕዲል መጥበቅ በሌለበት ቦታ አታጥብቁ እንላለን! አስተውሉ በኢጅቲሓድ ርዕስ ነው ያልኩትኝ።»

በጣም የሚገርመኝ ፀሀፊው እንደማውቀው ስለ ጀርህ ወታዕዲል ሊያወራ ይቅርና ቁርአን አስተካክሎ ማንበብ የማይችል ኮልታፋ ነው። እንደዚህ አይነት ሰዎች ናቸው እንግዲህ ዲንን ያለ እውቀት የሚያጨቀዩት። እነዚህ ሩወይቢዳዎች ሲናገሩ ቂያማ መቃረቧን ነው የምንጠብቀው።

ኢጅቲሀድ በሚያስተናግድ ጉዳይ መጥበቅ በሌለበት ቦታ አታጥብቁ አለ። እስኪ በፎቶ ርእስ ኢጅቲሀድ በሚያስተናግድ በኩሉ ያጠበቀው ማነው ለምን አትጠቅሰውም?! የጠበቀበት የሚያስተናግደ የሆነውስ ረቂቅስ ምንድነው?! ወይስ ስለ ፎቶ የመጡ ከባባድ ዛቻዎች እና ማስጠንቀቂያዎችን ማንበብ እና ማስተማርም ማጥበቅ ነው?!

ጀርህ እና ታዕዲልስ ላይ ኢጅቲሀድ በሚያስተናግድ በኩሉ ያጠበቀው ማነው ለምን አትጠቅሰውክ?! የጠበቀበት የሚያስተናግደ የሆነውስ ረቂቅ ምንድነው?! ወይስ ጀርህ እና ታዕዲል ማድረጉ እራሱ ማጥበቅ ነው?! እነዚህን ጥያቄዎች መመለስ አለብህ። ዝም ብሎ ሰውን መኮነን ልማድህ ሆኖ አትንዛዛ።

ከዚህ ባሻገር ደግሞ እጅቲሀድ በሚያስተናግድ ረቂቅ ላይ መረጂያው ግልፅ ከሆነ ለመረጂያው ሲባል ማጥበቅን እንዳንተ አይነት ሙመይዖች እንጂ ማነው ያወገዘው?!

ሙሀዲሱል ዐስር አል-አልባኒይ እንዲህ ይላሉ፦

"الذي يلزم هو العلم، هو العالم الذي يقيم الحجة أي هو وارث رسول الله صلى الله عليه وسلم وليس كل فرد من الأفراد"اهـ

سلسلة الهدى والنور


t.me/aredualelmumeyia
t.me/aredualelmumeyia

Abu hatim Abduselam Assalefiy

01 Feb, 17:43


በኢልያስ አሕመድ "30 ምክሮች ለወሰን አላፊዎች" በሚል ሙሐደራ ላይ በሸይኽ ዶክተር ሑሰይን ቢን ሙሐመድ አስሲልጢ ከዓመታት በፊት የተሰጠ ምላሽ

ክፍል 1

👉
በአህሉል ቢደዕ ላይ ጠንካራነትን (ሺድዳን) መጠቀምን በተመለከተ የሰለፎች ሚንሃጅ

👉እውን ሰለፎች በዚያን ዘመን የተጠቀሙት ዒብራና ተሰሚነት ያላቸው ብቻ ስለሆኑ ናቸውን?

👉እውን አህሉ ሱንና የበላይነትና አቅም ባላቸው ጊዜ ነውን?

👉አውን ሰለፎች ሺድዳን የተጠቀሙት እንደ ጀህሚያ መህዷ ያሉ ሙኻሊፎች ላይ ብቻ ነውን?

https://t.me/aredualelmumeyia
https://t.me/aredualelmumeyia

Abu hatim Abduselam Assalefiy

01 Feb, 17:40


Live stream finished (1 hour)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

01 Feb, 16:20


በአረቅጥ ሰለፊያ መስጂድ ላይ የተደረገ ሙሀዶራ

በሸይኽ ዐብዱል ሀሚድ አል-ለተሚይ ሃፊዘሁሏሁ

ርዕስ↪️ በዒልም ዙሪያ

ቀን፦ 23//05//2017



https://t.me/arekitselefiya_jemea
https://t.me/arekitselefiya_jemea

Abu hatim Abduselam Assalefiy

01 Feb, 16:06


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

01 Feb, 16:06


ሳምንተዊ የቁሪኣን ተፍስር ልጀምር ነዉ
ገባ
       ገባ
                በሉ
https://t.me/abuhatimaselefiy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

01 Feb, 07:16


የጁሙዓ ኹጥባ (ምክር)

ርዕስ በሸዕባን ወር ሊደረጉ የሚገቡ ተግባራት

በሸይኽ ሀሰን ገላው

በቡኻሪ መስጅድ

መጠን 11.72 Mb

የባህር ዳር አህለሱና መሻይኾች ገፅ

https://t.me/alateriqilhaq

كن على بصيرة

Abu hatim Abduselam Assalefiy

31 Jan, 17:31


Live stream finished (1 hour)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

31 Jan, 16:13


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

31 Jan, 16:08


Live stream finished (14 seconds)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

31 Jan, 16:08


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

31 Jan, 16:08


ሳምንተዊ የቁሪኣን ተፍስር ልጀምር ነዉ
ገባ
       ገባ
                በሉ
https://t.me/abuhatimaselefiy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

31 Jan, 14:21


አጭር የኮርስ ፕሮግራም

የፊታችን ቅዳሜ ጥር 24/2017 በጉራጌ ዞን ጉመር ወረዳ አረቅጥ ከተማ ሰለጭያ መስጂድ ላይ ልዩ አጠር ያለ ኮርስ ተዘጋጅቶ ይጠብቃችኋል ።
ኮርሱ የሚሰጠው በሸይኻችን ሸይኽ ዐ/ሐሚድ ለተምይ ነው ።
የኮርሱ ኪታብ ጂናየቱ ተመዩዕ ዓላ ሚንጂ ሰለፍ የሚለው የሸይኽ ዑበይደል ጃቢርይ ነው ።
ሳአት : – ከጠዋቱ 3 : 00 – 6 : 00

Abu hatim Abduselam Assalefiy

29 Jan, 11:32


🚫 ነፍሰ ጡር ለሆነች ሴት ኒካሕ ማሰር

እንከን የለሹ ሸሪዓችን ለትልቁም ለትንሹም የህይወታችን ገጠመኝ መፍትሄና ሸሪዓዊ ብይን አስቀምጧል ። ከእነዚህ ገጠመኞች ውስጥ አንዱ በተለይ አላህ ይጠብቀንና በዝሙት ያረገዘችን ሴት ቶሎ ብሎ ኒካሕ ማሰር ይገኝበታል ።
የኢስላም ሸሪዓ እንዳጠቃላይ ነፍሰ ጡር ለሆነችን ሴት ኒካሕ ማሰርን ይከለክላል ። ያረገዘችው ባልዋ የሞተባትም ትሁን ወይም የተፈታች አሊያም በዝሙት እስክትወልድ ድረስ ኒካሕ ማሰር አይፈቀድም ። ቢታሰርም ባጢል ነው ። ምክንያቱም ቁርኣንና ሐዲስን የኻለፈ ስለሆነ ።
በዝሙት ያረገዘች ሴት ላስረገዘውም ይሁን ለሌላ ኒካሕ ማሰር አትችልም ። የተወለደው ልጅ በእናቱ ይጠራል በዝሙት ባስረገዘው ሰው አይጠራም አባትም አይደለም ። ይህን አስመልክቶ ከመጡ የቁርኣንና ሐዲስ መረጃዎች አንዳንድ ልጥቀስ ። አላህ በተከበረው ቃሉ እንዲህ ይላል : –

« وَأُولَاتُ الْأَحْمَالِ أَجَلُهُنَّ أَن يَضَعْنَ حَمْلَهن »
الطلاق ( 4)

" የእርግዝና ባለቤቶችም ጊዜያቸው እርጉዛቸውን መውለድ ነው " ፡፡

የአላህ መልእክተኛ – ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም – እንዲህ ይላሉ : –

  " من كان يؤمن بالله واليوم الآخر، فلا يسقي ماءه زرع غيره يعني: منيه زرع غيره "
رواه أبو داود
" በአላህና በመጨረሻው ቀን የሚያምን ውሃውን ( የዘር ፈሳሹን ) የሌላውን ማሳ አያጠጣ " ።
የሌላው ማሳ ሲባል ያለ ኒካሕ በተደረገ ግንኙነት የተረገዘም ይመለከታል ። ያለ ኒካሕ የሆነን ወደርሱ ማስጠጋት ስለማይቻል ።

ማስገንዘቢያ : –

ሻፍዕያዎችና ሐነፍያዎች በዝሙት ያረገዘች ሴት ዝሙት በሰራው አካል ከሆነ ኒካሕ ማሰር ይቻላል ይላሉ ። ነገር ግን ከመረጃ አንፃር ቀውላቸው መርጁሕ ስለሆነ መጠንቀቅ ያስፈልጋል ። እነዚህ ዑለሞች ሙጅተሂዶች ስለሆኑ ዑዝር ይሰጣቸዋል ። ነገር ግን ሙጅተሂድን ስህተቱ ከታወቀ በስህተቱ ላይ ሊከተሉት አይበቃምና ልብ እንበል ።

ሌላው :– በዝሙት ላረገዘች ሴት ኒካሕ ማሰር ሐራምን ከሐላል ጋር ማደበላለቅ ስለሆነ በአሁኑ ጊዜ በዚህ ላይ የሚደረገው መሯሯጥ ሰዎችን ሐራም እንዲዳፈሩ የሚያደርግ ስለሆነ አላህን ልንፈራ ይገባል ለማለት እወዳለሁ ።

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

29 Jan, 06:45


የመጅሊስ ሰዎችና ሳዳት
ከትናንት እስከ አሁኗ ሰዓት
➩➩➩➩➩➩➩➩♻️

👉 ሳዳት እና የመጅሊሱ ሰዎች በፍትሃዊ እይታ ድሮና ዘንድሮ

➩ ለሳዳት ከማል ከዚህ ከራሱ ድምፅ በላይ ረድ የለም ማለት ይቻላል። ከመጅሊሱ ሰዎች እና ከሌሎች የሱፍያና አህባሽ ግለሰቦች አባባል ድምፅ ጋር የቀረበ

ትናንት ➘➘➘
👉 አንድ አልሆንም አሞራ ይብላኝ
👉 ከነሱ አንድ ከምሆን አላህ ይውሰደኝ
👉 ግንቡ ይቅርብን አላህን ጫካ እናመልከዋለን።

➶ እያለ ሲናገር ትክክል ነበር።

ዛሬ ደግሞ
👉 ተወደደም ተጠላም... የመጅሊሱ ሰዎች በእድሜ የጠገቡ ናቸው። እንዳንተ ልጅ አይደሉም፤ ጅል አይደሉም፤ ልጅና ጅል ቶሎ አይበስልም።
👉 ስትሸብት መብት እያለህ እንደሌለህ መንግስት ቤት ሄደህ ትለምናለህ! ፈሪነት ግን አይደለም።

➶ እያለ ይቀጥላል። የሚገርመው ትናንት አደንዛዥ እያለ የሚናገራቸውን ሰዎች ፈሪ ያልሆኑ (ጀግኖች)፣ የበሰሉ፣ ጅል ያልሆኑ (ብልሆች) እያለ ሲያሞጋግስ አንድትም ለውጥ የለም። እንደውም ለመውሊድ ከፍተኛ ወጭ ያወጣሉ ወዘተ...

⁉️ አሁንም አቋማቸውን አልቀየሩም የሚልኮ አይጠፋም ሆሆሆ!

https://t.me/AbuImranAselefy/9723

🏝 ••⇣⇣.  🏖   ••⇣⇣ 
╰𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞.   ╰𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞

---------------⫷⫸-----------------
🖥️ በ 𝐓𝐞𝐥𝐞𝐠𝐫𝐚𝐦~𝐂𝐡𝐚𝐧𝐧𝐞𝐥
🏝 ⇣⇣⇣🍭⇣⇣⇣📲 ⇣⇣⇣↙️
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy
⫷⫸⫷~⫸⫷⫸⫷~⫸⫷⫸⫷~⫸

Abu hatim Abduselam Assalefiy

28 Jan, 19:15


ኪታቡ ተ—ለ—ቀ—ቀ
                    
🔍 اسم الكتاب : ➴➴➴
🏝 «الْكَلِمَاتُ النَّافِعَةُ الذَّهَبِيَّة في بَيَانِ أُصُوْلِ وَمَنْهَجِ الدَّعْوَةِ السَّلَفِيَّة»

⬅️ المجلد الأول

🔎 የኪታቡ ስም ፦ ➴➴➴
🏝የሰለፍያ ዳዕዋ አካሄድን እና መሰረቶችን በማብራራት ዙሪያ ጠቃሚ እና ወርቃማ ንግግሮች

የሁለተኛውን ጥራዝ ለማግኘት
➴➴➴➴
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/11953

📝 كَتَبَهُ : أَبُو طَلْحَةَ أَبُو ذَرَ بْنُ حَسَنِ بْنِ إِمَامٍ الْإِثْيُوْبِي الْوَلْوِيَ «حَفِظَهُ الله»


📝 ዝግጅት ፦ በታላቁ በሸይኻችን ሸይኽ አቡ ዘር ሀሰን ኢማም አቡ ጦልሃ አል`ኢትዮጵይ አልወሎውይ አላህ ይጠብቃቸው!

➩ ጥራዝ አንድ
➩ የገፅ ብዛት 487
➩ በወስጡ በአስራ አራት ክፍሎች የተዘጋጁ የተለያዩ ርዕሶች ተካተዋል።
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/11953

Abu hatim Abduselam Assalefiy

28 Jan, 19:05


አልሃምዱሊላህ፣ ዲላ ዩኒቨርስቲ ከ10 ቀናት በላይ ከግቢ ተከልክለው። መስጂድ እያደሩ ለኒቃባቸው የታገሉ እህቶች በመጨረሻም ተፈቅዶላቸው እንዲገቡ ተደርጓል።


በርግጥም የአላህን ዲን ከረዳን አላህ ይረዳናል። እነዚህ እህቶች ብዙ ነገር አስተምረውናል። አሏህ መስዋትነት የከፈሉለት ኒቃባቸው እንዳላቃቸው  ታፍረውና ተከብረው ኖረው የሚሞቱበት ያርግላቸው በጀነትም ልቅናቸውን ይጨምርላቸው።


ምናልባት የነሱ ጉዳይ ለየት የሚያደርገው እነዚህ እህቶች ዱንያዊ ነገር ብለው ከአቋማቸው ተንሸራተው ረሃብ ጥማቱን የበገራቸው ቢሆን ኖሮ ቀጣይም ለሚመጡ እህቶች መንገድ ዘግተው ነበር።

ብቻ አልሃምዱሊላህ ለተጨነቃቹም ሁሉ
እንኳን ደስ አላቹ።

በተረፈው የEuSaCo አጠቃላይ የኢትዮጵያ ሰለፍይ ተማሪዎች ህብረት። ሌሎችም ግቢዎች ያሉ ክልከላዎች በዘላቂነት ለመፍታት ከመሻይኾች ጋር በመሆን እየሰራ ነው። ኢንሻአላህ ለውጥ ያለው አስተዋጽኦ ያረጋል ብለን ተስፋ እናደርጋለን።


በመጨረሻም የሁሉም ግቢ ተማሪዎች አንድነታችንን እናጠንክር እንተዋወስ ኢንሻ አሏህ!!!

https://t.me/EUSaCochannel

Abu hatim Abduselam Assalefiy

27 Jan, 13:15


🟢ደዩስ ጀነት አይገባም!!

👉በቤቱ ላሉ ሴቶችና ህፃናት ደንታ ቢስ የሆነ ወንድ ደዩስ ጀነት አይገባም:

↪️ከአሸይኽ ሳሊህ አልፈውዛን ትምህርት

ደዩስ = በቤተሰቡ ላይ ፀያፍ ነገር አይቶ የሚያልፍ

ከሰበቦቹ
👉ሂጃብ አይለብሱ
👉የለ መህረም ሰፈር ይጓዛሉ
👉ከአጅነቢይ ወንድ ይቀላቀላሉ
👉የሸር በሮችን ይከፍታሉ

በቤተሰቡ ውስጥ እነዚህና ሌሎችም ወንጀሎች እያየ የማይቀና እና የማያስተካክል ደዩስ ነው::
قال شيخ الإسلام ابن تيمية رحمه الله: " والديوث: الذي لا غيرة له " .
"مجموع الفتاوى" (32/ 141).

ነቃ በል ደዩስ አትሁን !

🎤 ሸምሱ ጉልታ (አቡ ሀመዊየህ) :
https://t.me/Abuhemewiya

Abu hatim Abduselam Assalefiy

26 Jan, 19:26


👆👆👆
🔈#«በነሱ {በአህባሾች} እና ውሃቢያህ ብለው በሰየሟቸው ሰዎች መካከል ያለው ልዩነት እምነታዊ ነው» የሚለው የአህባሹ አቡበክር ንግግር እንዲሁም በተምይዕ ተጣሪዎች ላይ ረድ ❴ምላሽ❵


🔶 በአዲስ አበባ አል- ወሰጢየህ መርከዝ እና መድረሳ ከሚሰጥ ደርስ የተወሰደ።


🎙በኡስታዝ ሻኪር ቢን ሱልጣን (ሀፊዘውላህ)

📌 ትምህርቱን ለመከታተል ይህን ቻናል ይቀላቀሉ
👇👇👇
🌐 https://t.me/shakirsultan

Abu hatim Abduselam Assalefiy

26 Jan, 17:24


Live stream finished (1 hour)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

26 Jan, 16:19


ሳምንተዊ የቁሪኣን ተፍስር ልጀምር ነዉ
ገባ
       ገባ
                በሉ
https://t.me/abuhatimaselefiy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

26 Jan, 16:18


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

25 Jan, 19:14


👉  የሙመይዕና የደካማ ሰለፍይ ልዩነት

በአሁኑ ጊዜ በሚያሳዝን መልኩ ድሮ ከኢኽዋን ከተብሊግና ከሱፍይ ሚንሀጅ አራማጆች ጋር ጉሮሮ ለጉሮሮ ሲተናነቁ ለተውሂድና ለሱና ሲሉ ከወንድምና እህታቸው የተለያዩ የነበሩ የወላእና በራእ ድንበር እንዳይደፈር ዘብ በመቆም ውድ ዋጋ በመክፈል ወጣቱ የተውሂድና የሱና ባንዲራ ከፍ እንዲያደርግ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ከቻሉ በአውቶብስ ካልቻሉ በእግራቸው ኑ ወደተባሉበት በመሄድ ከውስጥ እንደ ነበልባል እየነደደ በሚወጣ የቁጭት ስሜት ህዝቡ የተዘፈቀበትን የሽርክ ረመጥ እያወገዙ የተውሂድ ዘር ሲዘሩ የነበሩ ሰዎች ናቸው ።
ዛሬ ያኔ ባላወቅንበትና ባልበሰልንበት ጊዜ ነበር አሁን አውቀናል በስለናል የሰለፍያ ዳዕዋ ማለት እንደሱ አይደለም ። ማጠንከር አያስፈልግም ዳዕዋ በማለስለስ ነው የሚደረገው የሰው ስም መጥራት አያስፈልግም ይለያያል ሰዎችን ያርቃል የሚፈለገው አንድነት ነው የሚሉት ።
በምን ላይ ? ሲባሉ
አይታወቅም ብቻ ሰዎችን አታባሩ በሚል ወደኀላ ተመልሰው ለሌላው ወደኀላ መመለስና ለዘብተኛ መሆን ጥብቅና በመቆም ይህን አልቀበልም ያለና ሌላውም እንዳይቀበል ያደረገን ወሰን አላፊ ሂክማ የሌለው መስለሃ የማያውቅ በማለት ከዚህ አልፎም ሀዳዲ እያሉ ስም በማጥፋት ሰው ትክክለኛው የሰለፍያ ዳዕዋ እንዳይረዳ ውዥንብር ውስጥ እንዲገባ በማድረግ አሳፋሪና አስነዋሪ ድርጊት ሲፈፅሙ የሚታዩት ። ይህ ድርጊት ብዙ ሙሪዶች እንዲያገኙ አድርጓቸዋል ። አብዛኛዎች ዲናቸውን በእውቀት ሳይሆን በሰው ላይ በመንጠልጠል የያዙ ናቸው ። ስለሆነም የያዙት ያ ሰው ወደ ዞረበት ነው የሚያዞሩት ። ከእገሌ የበለጠ አንተ ታውቃለህ ወይ ነው ። የዚህ አይነቱ አካሄድ አብዛኞችን ሰለፍይነታቸው ደካማ እንዲሆን አድርጓል ። እነዚህ አካላት በዛው ከቀጠሉ ሰለፍይነታቸው ሟምቶ ወደ ሙመዪዕነት መሸጋገራቸው አይቀርም ። ነገር ግን በሙመይዕና በደካማ ሰለፍይነት መካከል ያለው ልዩነት ለብዙዎች ግልፅ ባለመሆኑ በወንድሞች መካከል አለመግባባትና ንትርክ እየተፈጠረ ስለሆነ በአላህ ፈቃድ  ልዩነቱን ላስቀምጥ
ወደድኩኝ ።

     🔹 ሙመይዕ ማለት

ከነበረበት አቋም በመንሸራተት ሰለፍያ ሚንሃጅ ሁሉንም የሚያቅፍ ሰፊ ሚንሃጅ ነው በማለት በሰለፎች የማይታወቅ ቀመር ( ቃዒዳ ) በማምጣት ሰዎች ኢኽዋኖችም ሆነ ተብሊጎች ከጠማማ አንጃዎች መሆናቸውን እንዲጠራጠሩ የሚያደርጉ ፣ ማግራራት የሚል አዲስ ሚንሀጅ የሚያመጡ አታጥብቁ ስዎችን አታርቁ የሚሉ ሚንሀጅ ሚንሀጅ አትበሉ ተህዚር ተህዚር አትበሉ በሚል ፍልስፍና ሁሉንም በሰለፍያ ስም ማቀፍ የሚፈልጉ ማለት ነው ።

    🔹 ደካማ ሰለፊ ማለት

እነዚህ አባባሎችን የሚቃወም በአቋም ሁሉንም የሰለፍይ ሚንሀጅ መርሆችን የሚቀበል ተብሊግም ሆነ ኢኽዋኖች ከጥመት አንጃዎች ናቸው እያለ በሙመዪዓና ኢኽዋን ላይ ረድ የሚያደርጉትን  የማይቃወም ሰለፍዮችን የማይተች ነገር ግን ኢኽዋኖችንና ሙመዪዓዎችን ለማኩረፍ አቅም የሌለው የተለያየ ምክንያት እያመጣ ከእነርሱ ጋር የሚቀራረብ ነው ።
በመሆኑም እንደነዚህ አይነት ወንድሞች ብዙ ስለሆኑ እባካችሁን ጠንካራ ሰለፍዮች እንዲሆኑ ልንረዳቸው ይገባል እንጂ ማራቅ አያስፈልግም ። ካልሆ ሸይጣን በመካከላችን ገብቶ ለመበታተን ስለማይተኛ ጥንቃቄ ያስፈልጋል ።
አላህ ሁላችንንም በሀቅ ላይ ያፅናን ።

ከተወሰነ ማስተካከያ ጋር ከንደገና የተለቀቀ ።

http://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

25 Jan, 17:22


Live stream finished (59 minutes)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

25 Jan, 16:23


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

25 Jan, 16:22


Live stream finished (1 minute)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

25 Jan, 16:21


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

25 Jan, 16:20


Live stream finished (1 minute)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

25 Jan, 16:20


ሳምንተዊ የቁሪኣን ተፍስር ልጀምር ነዉ
ገባ
       ገባ
                በሉ
https://t.me/abuhatimaselefiy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

25 Jan, 16:19


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

24 Jan, 17:20


Live stream finished (21 minutes)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

24 Jan, 17:00


👉 እነርሱም ተውሒድ ያስተምራሉ ።

የነሲሓዎች ሙሪዶች ግራ ተጋብተው ሌሎችንም ግራ ከሚያጋቡበት ብዥታ አንዱ የነሲሓ ዱዓቶች እናንተ የምታስተምሩትን አይነት ተውሒድ ያስተምራሉ ታዲያ ልዩነታችሁ ምንድን ነው የሚል ነው ። !!!!!
ይህ ብዥታ በርግጥ ብዙዎችን ግራ የሚያጋባ ሊሆን የሚችል ሲሆን እውነታው ግን የሰማይና የምድር ያክል ርቀት ያለው ነው ። ነሲሓዎች ምስኪኑን ለመሸንገል ኪታቡ ተውሒድን ፣ ዋሲጢያን ፣ ተድሙሪያን ፣ አል ኢርሻድንና ከሽፉ ሹቡሃትን የመሳሰሉ ኪታቦች ሊያስቀሩ ይችላሉ ። ታዲያ ልዩነታችሁ ምንድን ነው ለሚለው ጥያቄ መልሱ የሚከተለው ሲሆን ምናልባት የእንቅልፉ ክኒን የዘጋውን ዐቅላችሁን ለመክፈት ይረዳችሁ ዘንድ ጭንቅላታችሁን ከአንገታችሁ በላይ ግራና ቀኝ በማወዛወዝ ነቅነቅ አድርጉትና አይናችሁን ዘግታችሁ ክፈቱት ።
ወደ መልሱ : –
ልዩነታችን እኛ ኪታቡ ተውሒድን ስናስቀራ " ከዚህ ኡመት ውስጥ ከፊል ጣኦት አምላኪያኖች አሉ " የሚለውን ባብ አሁን ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር አገናኝተን አልከሶ ፣ ቃጥባሬ ፣ አብሬት ፣ ዳና ፣ ከረም ፣ ጌታው ሸኽዬ ሐድራ ፣ ጀማ ኑጉስ ፣ ዓንዬ ሐድራ ፣ ሸከና ሑሴን ባሌ ፣ አባድር ሐድራ ሐረር የሚሰራውን ከእስልምና የሚያወጣ ሽርክ የሚመለከት መሆኑን ገልፀን እናስጠነቅቃለን ። እነዚህና ሌሎችም ከአላህ ውጪ ያሉ አካላት የሚመለኩባቸው አካባቢዮች ላይ ይህን ተግባር የሚፈፅሙትን አላህን ፍሩ የሽርክና ኩፍር ተግባር እየፈፀማችሁ ነው ። ተውበት ሳዳደርጉ ወደ አኼራ ከሄዳችሁ የሚጠብቃችሁ ዘላለማዊ ክስረት ነው እንላለን ።
ነሲሓዎች ዘንድ እንደነዚህ አይነት ባቦች ለበረካና ኡማውን ለመሸንገል ነው የሚቀሩት እንጂ ከላይ የተጠቀሱ አካባቢዮችን ስም ጠርቶ እዛ አካባቢ የሚፈፀሙ ሽርኮችን ማውገዝና ማስጠንቀቅ ራሱ የተወገዘና ሽብርተኝነት ፣ ሒክማ አልበኝነት ፣ አክራሪነት ፣ በታታኝነት ነው ። እነዚህን አካባቢዮችና ከአላህ ውጪ የሚመለኩትን መሻኢኾች ስም ማንሳት ሰዎችን የሚያርቅ ስለሆነ አያስፈልግም የሚል ፍልስፍና ለተከታዮቻቸው ይግታሉ ።
ሱፍዮችና ኢኽዋኖች ተውሒድ ተውሒድ አትበሉ ሰዎችን ያርቃል ይሉ ነበር ። አሻዒራዎች ዐዋሞች ዘንድ ቁርኣን መኽሉቅ ነው አትበሉ ይልቁንም ቃለላሁ በሉ ምክንያቱም ቁርኣን መኽሉቅ ነው ማለት ዐዋሙን ስለሚያርቅ ይላሉ ። አሁን ደግሞ ሰለፍይ ነን ባዮች ሽርክ የሚፈፀምባቸው ቦታዎችና ሽርክ የሚፈፅሙ አካላትን ስም አትጥሩ እንደውም በግልፅ ከአላህ ውጪ የሚመለኩትንም ስም አታንሱ ምክንያቱም ሰዎች ይሸሻሉና እያሉ ነው ።
ነሲሓዎች ዐቂደቱል ዋሲጢያና ተድሙሪያን ሲያስቀሩ አሻዒራ ፣ ማቱሪዲያ ፣ ኩላቢያዎች አስማእ ወስሲፋት ላይ ሙዓጢላዎች ( የአላህን ከፊል ስምና ባህርይ ውድቅ የሚያደርጉ)ና በዚህም አህሉ ሱናን የኻለፉ የቢዳዐ አንጃዎች መሆናቸውን አይገልፁም ። ይልቁንም በድፍኑ በገሀዱ ዐለም ላይ ያሉ እስከማይመስሉ ለተበሩክና ለሽንገላ ነው የሚያስቀሩት ። የትኛውንም የዐቂዳ ኪታብ ሲያስቀሩ አሁን ካለው አንጃ ጋር አያገናኙትም ። ምክንያታቸው ይህን ቢያደርጉ ከኢኽዋን ፣ ሱፍይና አሕባሽ ጋር ስለሚጣሉ ነው ።
እስኪ በየአካባቢያችሁ ያለውን የቀብር አምልኮ ተመልከቱና የነሲሓ ዱዓቶች የሚያደርጉትን ዳዕዋ ስሙ በፍፁም በዛ አካባቢ ያለውን የቀብር አምልኮ አይናገሩም ። የአልከሶ ሸይኽ ነስሮ ከሸይኽ ዐ/ሐሚድ ጋር ሲነጋገሩ እኔ ስለ አብሬት እናገራለሁ ነገር ግን አልከሶ ላይ ስላለው ሽርክ አልናገርም ነው ያለው ።
የነሲሓዎች መሪ አዩብ ደርባቸው እንኳን ከቃጥባሬና አብሬት ሊያስጠነቅቅ አረቅጥ ላይ በአብሬት ሸይኾች ስምና በቃጥባሬ ሸይኾች ስም መቶ መቶ ሺህ ብር ቃል ገብቶ ሙሪዶችን ነው ያስጨፈረው ።
በነሲሓዎች ኪታቡ ተውሒድ ማስቀራት ለተሸወዳችሁ እውነታው ይህ ነው ። አላህ ከልቦና አይናችሁ ላይ ሒጃቡን ይግፈፍላችሁ ።

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

19 Jan, 20:13


👉 ከላይ ሆኖ መጮህ

" ሐቅና ባጢል ተጣልተው ባጢል ሐቅን ጥሎት ከላይ ሆኖ ኡኡ ኡኡ እያለ ይጮሃል ። የአካባቢው ማህበረሰብ ምን ተፈጠረ ብሎ እየተጣደፈ ሲመጣ ባጢል ከላይ ሆኖ እየጨኸ ነው ። በጣም በመገረም ምን ሆነህ ነው ከላይ ሆነህ የምትጮኸው ይሉታል ። ባጢልም አዪዪ የምጮኸውማ እንደ ሚገለብጠኝ ስለማውቅ ቀድማችሁ እንድትደርሱልኝ ብዬ ነው ። !!!!! አለ ይባላል ።
የኢኽዋንና የሙመዪዓ ጥምሮችና ቲፎዞዎቻቸው ሰለፍዮች በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በሚያደርጉት የተውሒድ ችግኝ ተከላ ዘመቻ ላይ ከላይ ሆነው እየጮኹ ነው ።
ሶሞኑን ከሓራና ሀሮ ፕሮግራም በኋላ በስልጤ ዞን አሊቾ ወረዳ ጮል ቀበሌ ሰለፍዮች በጣም አስደንጋጭ በሆነ መልኩ ባደረጉት የተውሒድ ችግኝ ተከላ የዳዕዋ ፕሮግራም እንዚሁ አካላት ድንብርብራቸው ወጥቷል ። ከላይ ሆነው ለተለያዩ ከበታቾቻቸው ላሉ አካላት አስቁሙ የሚል ትእዛዝ አስተላልፈው የነበረ ቢሆንም ምኞታቸው ሳይሳካ መና ሆኖ ቀርቷል ። የወረዳው አስተዳዳሪ ሴት ከበላይ የመጣውን ትእዛዝ ለማስፈፀም በፀጥታ ሀይል ታጅበው ቦታው ሲደርሱ ከየአካባቢው የመጣው ማህበረሰብ መስጂዱ አልበቃው ብሎ ዳስ ውስጥ ሞልቶ ቁርኣንና ሐዲስ በሰለፍይ መሻኢኾች ሲማር በማየታቸው ሀሳባቸውን ቀይረው ተመልሰዋል ። ቁርኣንና ሐዲስን እንዲሁም የህገመንግስቱን መርህ ጥሶ ስልጣንን ለግል አመለካከት ለመጠቀም ትእዛዝ ያስተላለፈውን የበላይ አካል ፍላጎት ወደ ጎን በመተው የተጣለባቸውን የህዝብ አደራና የህገመንግስቱን መርህ መሰረት በማድረግ ፕሮግራሙ እንዲቀጥል የፀጥታ ሀይል በመመደብ ያለ ምንም ስጋት ፕሮግራሙ እንዲካሄድ አድርገዋል ። በዚህም እነዚህ አካላት የመንግስት ሴክትር መ/ቤት አመራሮች ከኛ ፍላጎት ውጪ አይወጡም ስለዚህ በእጅ አዙር ዞኑን እኛ እንመራዋለን የሚለውን ከንቱ ምኞት አድርገው አሳይተዋል ። ሌሎቹም የዞኑ የመንግስት አመራሮች ፈለጋቸውን እንዲከተሉና የዞኑን ገፅታ ወደ ነበረ ታሪኩ እንዲመልሱ አደራ ለማለት እውዳለሁ ።
አመራርዋ ለዚህ ፍትሀዊነታቸው ምንዳቸውን አላህ ይክፈላቸው የሚለው ዱዓኤ ነው ። የሚያሳዝኑት ከላይ ሆነው ጯሂዮች የፈሩት በመድረሱ ጩኸታቸውን ያቆሙ ይሆን ወይስ ይብስ ይሆን ? ለማንኛውም የምናየው ይሆናል ።
በአላህ ፈቃድ ሰለፍዮች የተውሒድን ችግኝ መትከላቸውንና ችግኙን የሚያቀጭጩና የሚያጠወልጉ አረሞችን ምንነት ግልፅ ማድረጋቸውን ይቀጥላሉ ። ችግኙም መፅደቁና ፍሬ መስጠቱም ይቀጥላል ። ለጩኸታሞቹ የምንለው ሂዳያ የሚገባችሁ ከሆነ አላህ ይምራችሁ ካልሆነ በቁጭታችሁ ሙቱ ነው ።

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

19 Jan, 20:12


👆👆👆
#በመሐመድ ሲራጅ ላይ ምላሽ እና በማለባበሱ ዙሪያ ማብራሪያ

🔶
በአዲስ አበባ አል- ወሰጢየህ መርከዝ እና መድረሳ ከሚሰጥ ደርስ የተወሰደ።

🎙በኡስታዝ ሻኪር ቢን ሱልጣን (ሀፊዘውላህ)

🌐 https://t.me/shakirsultan

Abu hatim Abduselam Assalefiy

19 Jan, 20:12


🔶#በመሐመድ ሲራጅ ላይ ምላሽ እና በማለባበሱ ዙሪያ ማብራሪያ


🔈 - الرد على محمد سراج وبيان تلبيساته

 19 رجب, 1446 هـ
الموافق ، 19 يناير  2025 م


🔗 የዳውንሎድ ሊንኩን ይጫኑ Mp3
https://is.gd/la8yQt

🔶 በአዲስ አበባ አል- ወሰጢየህ መርከዝ እና መድረሳ ከሚሰጥ ደርስ የተወሰደ።


🎙 أستاذ شاكر بن سلطان - حفظه الله تعالى

🎙በኡስታዝ ሻኪር ቢን ሱልጣን (ሀፊዘውላህ)

📌 ትምህርቱን ለመከታተል ይህን ቻናል ይቀላቀሉ

👇👇👇
🌐 https://t.me/shakirsultan

Abu hatim Abduselam Assalefiy

17 Jan, 14:43


 ታላቅ የዳዕዋና ኮርስ ኮንፈረንስ በስልጤ ዞን

      በአላህ ፈቃድ የዲን ትምህርት ድግስ ከዛሬ እለተ ጁምዐህ ጥር 9/5/2017  እስከ እለተ እሁድ ጥር 11 ለተከታታይ 3 ቀናቶች ተዘጋጅቷል

ተጋባዥ እንግዶች:-
ሸይኽ ዐብዱልሐሚድ ቢን ያሲን አል-ለተሚይ (ሀፊዘሁላህ)
ሸይኽ ዶ/ር ሁሰይን ሙሐመድ አስልጢይ  (ሀፊዘሁላህ) ከአዲስ አበባ
ሸይኽ አቡ ዘር (ሀፊዘሁላህ) ከሳዑዲ ዐረቢያ በ online
ሸይኽ ሙሐመድ ሀያት (ሀፊዘሁላህ) ከወሎ
ሸይኽ ሁሰይን ከረም (ሀፊዘሁላህ) ከወሎ
ሸይኽ ሙሐመድ ጀማል (ሀፊዘሁላህ) ከኮምቦልቻ
ሸይኽ አህመድ አወል (ሀፊዘሁላህ) ከአዲስ አበባ
ሸይኽ ሙባረክ አል-ወልቂጢይ (ሀፊዘሁላህ) ከወልቂጤ)
ሸይኽ መህቡብ (ሀፊዘሁላህ) ከሳንኩራ
ሸይኽ አወል (ሀፊዘሁላህ) ከዳሎቻ

ኡስታዝ ባሀሩ ተካ (ሀፊዘሁላህ) ከአዲስ አበባ
ኡስታዝ አብራር አወል (ሀፊዘሁላህ) ከአዲስ አበባ
ኡስታዝ ሰይፈዲን ሳኒ (ሀፊዘሁላህ) ከወላይታ
ኡስታዝ ሸምሱ ጉልታ (ሀፊዘሁላህ) ከአዲስ አበባ እነዚህና ሌሎችም በርካታ ኡስታዞች፣ዱዓቶችና ታዋቂ ወንድሞች የሚሳተፉበት በተለያዩ ቋንቋዎች ታላቅ ዝግጅት ስለሆነ እንዳያመልጦት!!

አድራሻ:- አሊቾ ዊሪሮ ወረዳ ገድራት ቀበሌ ልዩ ስሙ ጮል በተሰኘችው መንደር በአል-አቅሳ መስጂድና መድረሳ ነው
(አካባቢው ብርዳማ ስለሆነ አስፈላጊውን የመኝታ ልብስ መያዝ አትዘንጉ)
የፕሮግራሙ አዘጋጅ:- የገደራት ቀበሌ አል-አቅሷ መስጂድ እና መድረሳ ማህበረሰብ እና የአካባቢው ተወላጆች
ማሳሰቢያ:- ሁላችሁም ማንነታችሁን የሚገልፅ መታወቂያ እና የማታ ልብስ እንዳትዘንጉ።

ሁሉም በአክብሮት ተጋብዟል


ለበለጠ መረጃ
+251913890385
+251716270733
+251938306021
#join ⤵️ ቴሌግራም ቻናል
https://telegram.me/IbnShifa

Abu hatim Abduselam Assalefiy

14 Jan, 12:34


👉 የአሜሪካና ግብረ አበሮቿ የአላህን ቅጣት ለመከላከል መታተር ።

አሜሪካ ክንዷን ለማሳየት በፍሊስጢን ምድር ላይ በጦር ጀቶቿ የምትወረውራቸው የነበሩ ቦንቦች ይፈጥሩት የነበረ አይነት እሳት ዛሬ በአላህ ትእዛዝ በተፈጠረ የቁጣ እሳት እየተናወጠች ነው ። ይህን ለመከላከል ግብረአበሮቿ ያለ የሌለ ሀይላቸውን ቢጠቀሙም የአላህን ቁጣ ሊያስቆሙ አልቻሉም ። ሎስ አንጀለስ ከነያዘችው ነገር እየነደደች ነው ። ይህን የአላህ ቅጣት አላህ የፈለገው ቦታ እስኪደርስና አላህ በቃ እስከሚለው ማንም ማስቆም አይችልም ።
የዚህ መራራ ፅዋ እንድትጋት ያደረጋት ምድርን እኔ ነኝ የማስተዳድረው ያልፈለኩትን አጠፋለሁ ማንም አያስቆኝም የሚለው ትምክህቷ ነው ። በሷ የግፍ በትር ደካሞች ሲሰቃዩ ፣ ሰሚ የሌለው የይድረሱልኝ ዋይታ ድምፅ ሲያሰሙ ከላይ ሆና እስኪ ማን ነው ስትል እንደነበረው ዛሬ በተራዋ በፍትህ በትር እየተገረፈች ነው ። ይህ ክስተት ለአእምሮ ባልተቤቶች ብዙ ሚስጢር የያዘ አስተማሪ ክስተት ነው ። ማን አለብኝ ባዮች ቆም ብለው ማስተዋል ከቻሉ ብዙ ይማሩበታል ። የፍጥረተ ዐለሙ አስተናባሪ የሀያሎች ሀያል የሆነው አላህ ከያዘ አያያዙ የበረታ ነው ። አዘናግቶ ሊዛቸው ዝም ሲላቸው የሌለ የሚመስላቸው ዐቅ ቢሶች በተዘናጉበት ዪዛቸዋል ።
በአሜሪካ ላይ የወረደው መቅሰፍት በሷ አይነት እብሪት ከተሞሉት የራቀ አይደለም ። ምላሳቸውንና እጃቸውን ካልሰበሰቡ በዚሁ በትር መገረፋቸው አይቀርም ። አሁን አሜሪካ ላይ ባለው ነገር መደሰት ባይቻልም ፍትሀዊ የሆነው አምላክ የሚገባቸውን እየሰጣቸው መሆኑን ማመን ግድ ይላል ። መደሰት አይቻልም ያልኩት የአላህ ቁጣ ሲመጣ ግፈኞቹን ብቻ ለይቶ ስለማይመታ ነው ።
በምድር ላይ ግፍ ሲሰራ ግፈኞቹን ተዉ ብሎ የሚያስቆም ከሌለ ዱንያ ላይ መቅሰፍቱ ሲመጣ ሁሉንም ያጠፋል ። አላህ አኼራ ላይ የሚለየው ቢሆንም ለዚህ ነው አላህ በሚቀጥለው በተከበረው ቃሉ ለይታ የማትመታዋን ፈተና ተጠንቀቁ የሚለን : –

« وَاتَّقُوا فِتْنَةً لَّا تُصِيبَنَّ الَّذِينَ ظَلَمُوا مِنكُمْ خَاصَّةً وَاعْلَمُوا أَنَّ اللَّهَ شَدِيدُ الْعِقَابِ »
الأنفال ( 25 )
" ከናንተም ውስጥ እነዚያን የበደሉትን ብቻ ለይታ የማትነካን ፈተና ተጠንቀቁ ፡፡ አላህም ቅጣቱ ብርቱ መኾኑን እወቁ ፡፡"
አሁንም አሜሪካን በተለይ ሉስ አንጀሎስን ወደ አመድነት እየቀየረ ያለው የቁጣ እሳት ለይቶ አይደለም እያጠፋ ያለው ። በመሆኑም የአላህን ሀያልነትና ረቂቅ ስራ አመላካች የሆነውን መቅሰፍት የምናየው በእዝነትና በቀደር አይን ሲሆን በሸሪዓ አይን ካየነው ሀያላን ነን ባዮች ከአላህ የእጃቸውን ማግኘታቸው እሰይ ያሰኘናል ። ለማንኛውም የምእራባዊያን እብሪት ትርፉ ክስረት መሆኑን የሚነግራቸው ቢያገኙ ጥሩ ነበር እንላለን ።

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

14 Jan, 12:33


♨️ #የተመዩዕ_አደጋ
♨️
#كلمة_في_خطر التّمييع

🎙 لفضيلة الشيخ أبو الفضل الصويعي حفظه الله :

↩️ "الشّباب اليوم أصبحوا يخافون من المميّعة أن يصفونهم بأوصاف الحداديّة و المتشدّدين و غير ذلك من الأوصاف المنتشرة اليوم ،
↪️ የአሁኑ ጊዜ ወጣቶቻችን ከሙመይዓዎች
👉 በሀዳዲይነት
👉 በአጥባቂነት፣
👉 እና በሌሎችም በዚህ ዘመን የተስፋፉ
በመሆኑ መገለጫዎች አንዳይገልጿቸው የሚፈሩ ሆኑ!

↩️ فوقعوا بسبب مجاراتهم الخوف في التّمييع معهم وخافوا من إرهاب هؤلاء فأصبح عندهم ضعف،
↪️ ፍራቻ በመጎራበቱ ምክንያት ከነሱ ጋር በተመዩዕ ላይ ወደቁ! የነዚህን ሰዎች ማስፈራሪያ በመስጋት እነሱ ዘንድ ድክመት ተረጋገጠ።

↩️ فنصيحة لنفسي و لكم لا تخافوا من هؤلاء فلا عندهم حجّة إلّا الكذب وادّعاء الحكمة
↪️ ለእኔም ለእንናንተም የምመክረው ከነዚህ ❴ሙመይዓዎች❵ አትፍሩ! እነዙ ዘንድ ውሸት እና በጥበብ መሞከት እንጂ መረጃ የለም

↩️ وهم أضحوكة لأهل البدع ، فارفعوا رؤوسكم بالسنّة واصدعوا بها
 ↪️ እነሱ ❮ሙመይዓዎች❭ የቢድዓ ሰዎች ኮሜዲያን ወይም መጠቀሚያ ናቸው ናቸው። በሱና ራሳችሁን ቀና አድርጉ! ሱናንም አብራሩ
.৲
.৲
🔎 እያሉ ይቀጥላሉ አዳምጠውማ ሀቢቢዋ! የዘመናችንን ቫይረሶች {ሙመይዓዎችን} አጣጥበው ጠምዘዋቸዋል

🏝 ••⇣⇣.  🏖   ••⇣⇣ 
╰𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞.   ╰𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞

---------------⫷⫸-----------------
🖥️ በ 𝐓𝐞𝐥𝐞𝐠𝐫𝐚𝐦~𝐂𝐡𝐚𝐧𝐧𝐞𝐥
🏝 ⇣⇣⇣🍭⇣⇣⇣📲 ⇣⇣⇣↙️
https://t.me/AbuImranAselefy/9627

Abu hatim Abduselam Assalefiy

13 Jan, 06:38


የተውሂድ እና ሽርክ ዳዕዋ
በሽርክ ከምትታወቀው ሀገር
ከጉራጌ  ዞኗ ቃጥባሬ ምድር
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯

🏝 በለቅሶ የታጀበ ለሙዎሂዶች እርግጠኝነትን የሚጨምር ታላቅ የተውሂድ ዳዕዋ
=> በሙሐደራው፦
➩ የቀብር አምልኮ በቃጥባሬ
የቃጥባሬ ሸይኾች ፍጡር ናቸው አይመለኩም
➩ ታጥበው ተከፍነው ተሰግዶባቸው የተቀበሩ ፍጡር ናቸው።
➪ የሸይኾቹ ቀብር እንደ ካዕባ ተገንብቶበት የካዕባ ልብስ ለብሶ ጠዋፍ ይደረግበታል።
ስለት ይሳሉበታል።
➪ ሰዎች ችግራቸውን በእንብርክካቸው ሄደው ለቀብር ይነግራሉ መፍትሄ ይጠብቃሉ።
እነዚህ ተግባሮች ኩፍር ናቸው ተውበት ያስፈልጋቸዋል
የቃጥባሬ አካባቢ ሙስሊሞች ይህን ማውገዝና ማስቆም አለባው።
በዚህ ላይ የሚሳተፉና የሚመሩ ሞት ሳይቀድማቸው መመለስ አለባቸው
➪ ይህ ተግባር የነብዩን ዲን መውጋት ነው።
➩ ይህ ተግባር ሸሪዓን ማጥፋት ነብዩና ሶሓቦች ዋጋ የከፈሉለትን እስልምና ማጥፋት ነው።
በየቦታው ያሉ የሽርክ ማእበሎች አላህ ያድርቃቸው። እኛን አላህ ሰበብ ያድርገን።

👉 ይህ ዳዕዋ በትክክለኛ አገላለጽ በትክክለኛ ቦታ ተገቢ በሆነ ቦታ ቀርቧል። ይህ ዳዕዋ ለቃጥባሬ አካባቢ ህዝብ በታላቅ ስፒከር ሁልጊዜም ሊያዳምጡት ይገባል።

🎙 آلأُسْتَاذ بَحْرُو تَكَا أَبُو عٌبَيْدَة «حَفِظَهُ اللَّهُ»
🎙 በኡስታዝ ባህሩ ተካ አቡ ዑበይዳህ አላህ ይጠብቀው!


🗓 በ25/3/2015

🏝 ••⇣⇣.  🏖   ••⇣⇣ 
╰𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞.   ╰𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞

---------------⫷⫸-----------------
🖥️ በ 𝐓𝐞𝐥𝐞𝐠𝐫𝐚𝐦~𝐂𝐡𝐚𝐧𝐧𝐞𝐥
🏝 ⇣⇣⇣🍭⇣⇣⇣📲 ⇣⇣⇣↙️
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy
⫷⫸⫷~⫸⫷⫸⫷~⫸⫷⫸⫷~⫸

Abu hatim Abduselam Assalefiy

13 Jan, 06:38


👉 ሰዎች ወደ አብሬት ለምን ይጓዛሉ ?

የኢስላም ጠላቶች የእስልምና ጮራ ከፈነጠቀበት ጊዜ አንስተው ብርሀኑን ለመግታት ከቻሉም ለማጥፋት ብዙ ሞክረዋል ። በተለይ የመጀመሪያው ትውልድ የኢስላምን አድማስ እያሰፋ በነበረበት ጊዜ በዐለም ላይ የነበሩ ሀያላን የሚባሉ ሀገራት ከኢስላሙ ብርሀን ፊት ለመቆም ብዙ ዋጋ ከፍለዋል ። ግን ልፋታቸው ያ ትውልድ ከአላህ ጋር በነበረው ጥብቅ ትስስር ምክንያት መክኖ እንዲቀር አድርጎታል ።
ተስፋ የማይቆርጠው የሸይጣን ሰራዊት አንዱ ሜዳ ላይ ሲሸነፍ ሌላ ሜዳ ፊቱን እያዞረ ከአራሕማን ሰራዊት ጋር ሲፋጠጥ ምኞቱ ከስሞ ቅስሙ ተሰብሮ መመለስ እንጂ ወደ ፊት መቀጠል አልቻለም ። የዚህ አይነቱ ሽንፈት ሚስጢር ሳይገባቸው በማያውቁት ነገር የኪሳራ ካባ ሲደራርቡ ሚስጢሩን ማወቅ አለብን አሉ ።
በዚህም ቆም ብለው ያሳለፉትን በህሊናቸው መስኮት እያማተሩ ሲያዩ ብዙ ሰራዊት በቁጥርም በትጥቅም የማይገናኝ ከጥቂቶች ፊት መቆም እንዲያቅተው ያደረገው በአራሕማን ሰራዊት ልብ ውስጥ የነበረው የኢማን ሀይል መሆኑን አወቁ ።
እየተሸነፉ ያሉት በመሳሪያና በሰራዊት ብዛት እንዳልሆነ ይልቁንም ትንሹ ሰራዊት ከአላህ ጋር ባለው የጠበቀ ትስስር በአላህ እርዳታ መሆኑን ገባቸው ። እያሸነፋቸው ያለው የተውሒድ አቅም እንጂ የሰራዊት አቅም አለመሆኑን አመኑ ።
የዚህን ጊዜ እስትራቴጂ መቀየር አስፈላጊ ሆነ ። ጦርነቱ ከኢማን ጋር ከተውሒድ ጋር ሆነ ለዚህም ሰራዊት መመልመል ጀመሩ ። የአሁኑ መሳሪያ በጀርባ አዝለውት በትከሻ ተሸክመውት የሚሄዱት አይደለም ። ቀላል ሆኖ በጣም አጥፊ መሳሪያ ነው ። በሙስሊሞች ልቦና ውስጥ ያለውን ተውሒድ የሚያጨልም ኢማናቸውን የሚያቀልጥ የሹብሃ መሳሪያ የስሜት መከተል መሳሪያ መታኮስ መሳየፍ የማያስፈልገው በጥቂት ቃላቶች የሚገለፅ ቶሎ ልብ ላይ የሚሰርፅ መሳሪያ መጠቀም ጀመሩ ።
የጦርነቱ ሜዳ ከበረሀ ወደ ሽርክና ቢዳዓ ፋብሪካ ተዛወረ ። ከሙስሊሙ ውስጥ ለዚህ ፋብሪካ ሰራዊት መለመሉ ከበላይ የሚመራው የዐብዱላሂ ኢብኑ ሰበእ አልየሁድይ ሀላፊነቱ የተወሰነ የኩፍር ማህበር ሆነ ። የሺዓ ፋብሪካ ተከፈተ በወልይ ስም ሙታኖች ይጠቅማሉ ፣ ይሰማሉ ፣ ይረዳሉ ፣ አላህ ስልጣን ሰጥቷቸዋል በሚል አላህን ትቶ እነርሱን መጥራት ተንሰራፋ ። ጎን ለጎን የተለያዩ የቢዳዓ ፋብሪካዎች እየተከፈቱ የሙታን መንፈስ ማምለኩ አድማሱ እያሰፋ ቅርንጫፉ እየበዛ ለዓለም ተዳረሰ ። የሱፍያው እህት ኩባንያ ይህን ሽርክ የማስፋፋቱ ስራ በሰፊው ተያያዘው ።
በዚህም በቀላሉ ከሙስሊሙ ማህበረሰብ አላህ ያዘነለት ሲቀር ከውስጡ በአላህ ማመን የሚባለውን ማውጣት ቻሉ ። በዚህም አብዛኛውን ሙስሊም ኮፍያ ጥምጣምና ጀለብያ የለበሰ ቆሞ የሚሄድ ውስጡ ባዶ የሆነ እስከሌተን አደረጉት ።
የኢስላም ጠላቶች ሀገራችን ላይ ሙስሊሙን ከኢማኑ ለማራቆት ከከፈትዋቸው የሽርክ ፋብሪካዎች አንዱ አብሬት ያለው ሀድራ ነው ። ቅርንጫፉ ጠቅላይ ቢሮ የሚባለው አ/አ ነው ።
ሰዎች በየአመቱ ወደ አብሬት የሚገርፉት በአላህ ላይ ለማጋራት ውስጣቸውን አላህ ይጠቅማል ከሚለው ኢማን ባዶ አድርገው ያብሬት ሸይኾች ይጠቅማሉ በሚል ቀይረው ለሳቸው ችግራቸውን ለመንገር ነው ።
አው አብሬት የሚሄድ ሙሪድ ኮፍያ ያደረገ ፣ ጀለብያ የለበሰ ፣ ጥምጣም የጠመጠመ ወይም ስሙ ሙሐመድ ፣ አሕመድ ፣ ከማል ፣ ሰፋ ፣ ጀማል የሆነ የሙታን መንፈስ አምላኪ ነው ። ሀድራውን የሚመሩት ጫት ናላቸውን ያዞራቸው ጠንቋዮች ናቸው ። ህዝቡን ቁርኣንና ሐዲስ ሳይሆን ያብሬትዬ የሚሉት ሸይጣን ወሕይ የሚያደርግላቸው ገድል ነው ።
አብዛኛው አብሬትዬ ይመጣሉ በሚል ከሀገሩ የወጣ ነው ። ዱዓእ ሲያደርጉ በሀድራቸው አላህ ያስገባቸው የሚል ነው ። ይህ ተራውን ህዝብ የሚያስተኙበት እንጂ ገስግስ እንደገደላቸው ያውቃሉ ። የራሳቸው ልጆች አንዱ ሌላውን አባታችንን አስገድለዋል በሚል ክስ ላይ ናቸው ። ይህ ከመሆኑ ጋር ወደ አብሬት የሚጎርፈው ህዝብ ችግሩን ለአብሬትዬ ይናገራል ። ዘር ስጡኝ ፣ ከጭንቅ አውጡኝ ፣ ድረሱልኝ ፣ ለማን ተውኝ ይላል ። መከራውን ፣ ችግሩን ፣ ሐዘኑን ፣ ማጣቱን ፣ መጎዳቱን ፣ ፍርሀቱን ለሳቸው ይናገራል ። እርዱኝ ፣ አክብሩኝ ፣ እጄን ያዙኝ ይላል ።
ኧናገራ ያለውን የአባታቸው ቀብር ( ኧቁባይ ) ሄዶ አፈር ይበላል ። በእንብርክኩ ወደ ቀብሩ ይደርሳል ። ስልኩን አጥፍቶ ጫማውን ከሐረሙ ( ከጊቢ ) ውጪ አስቀምጦ በእንብርክክ ሄዶ ቀብሩ ጋር ስጁድ አድርጎ በጠዋፍ ዞሮ ለአላህ እንጂ የማይገባ አምልኮ ያደርጋል ። ጉዱ በዚህ አይቆምም በየአመቱ የሚሄዱ አንድ ላምስት ተደራጅተው ወደዚህ ቀብር አምልኮ ለመጣራት ተስማምተው ይመጣሉ ።
አሕባሽና ሱፍዮች የዚህ አይነቱን የሽርክና የኩፍር ተግባር በገንዘብ በመርዳት አድማሱ እንዲሰፋና ሙስሊሞች ቀብር አምላኪ እንዲሆኑ ቀንና ለሊት ይሰራሉ ። ይህ ከእስልምና የሚያወጣ ሽርክ ነው ተብሎ ስፍር ቁጥር የሌላቸው የቁርኣን አንቀፆች ሲነገራቸው ለከሀዲያን የወረዱ የቁርኣን አንቀፆች ለሙስሊሞች ያደርጋሉ ይላሉ ።
እነዚያ አላህ ሙሽሪክ ያላቸው ከሀዲ ያላቸው ሰዎች ጥቁር ፣ቀይ ፣ ዐረብ ፣ ዐጀም ፣ አጭር ፣ ረዥም ፣ ስለነበሩ ነው ወይስ የሚሰሩት የነበረው ተግባር የኩፍርና የሽርክ ተግባር ስለነበረ ነው ? በእነዚ አባባል ስለ ሶላት ፆምና ዘካ የሚናገሩ አንቀፆች ለእነዛ በዛ ዘመን ለነበሩት ብቻ ነበር አሁን አይሰራባቸውም ማለት ነው ።
ሁሉም በየትኛውም ጉዳይ የመጡ የቁርኣንና የሐዲስ መረጃዎች በየትኛውም ዘመን የትም ቦታ ይሰራሉ ። ሙሽሪኮቹ ሲሰሩት የነበረውን ሺርክ የሚሰራ ሙሽሪክ ይባላል ። ከሀዲያን የሚሰሩትን የኩፍር ተግባር የሚሰራ ካፊር ይባላል ። በግለሰብ ላይ ብይኑን ለመስጠት የሚያስችሉ መስፈርቶች ተሟልተው ከልካዮች ሲወገዱ መረጃው ሲደርስ ያግለሰብ ካፍር ነው ይባላል ። የቁርኣን ህጎች በወረዱበት ምክንያት የተገደቡ አይደሉም ። ቃሉ በያዘው ብይን እስከቂያማ ይሰራሉ ።
በመሆኑም እናትና አባቶቻችንን ከአሕባሽና ሱፍዮች እጅ ለማውጣትና ወደ ተውሒድና ትክክለኛ እስልምና ለማምጣት የምንችለውን ማድረግ ይጠበቅብናል ።

አላህ ይወፍቀን ።

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

13 Jan, 06:38


🚫 የአላህ ታአምር በአሜሪካ ምድር

አሜሪካ ትላንት በሰው ሰራሽ እሳት የፍልስጢንን ምድር ስታቃጥል አዛውንትና ህፃናትን መኖሪያቸው ቀብራቸው እንዲሆን አድርጋ ከፍርስራሽ ስር ጀናዛ ስትቀብር የምእራቡ ዐለም በድል አድራጊነት ቁጭ ብሎ እያየ ነበር ከተሞች ወደ ምድረበዳነት ሲቀየሩ እርጥብና ደረቅ ሲቃጠል ማን አለብኝ ባይዋ አሜሪካ ገና ነው ጠብቁ ትል ነበርፍልስጢናዊያን አቅመ ደካሞች ነፍሳቸውን ማዳን የቻሉት ሲሰደዱ ደካሞቹ የሰው ሰራሹ እሳት በላያቸው ላይ ሲለኮስ የዛሬዎቹ ደም እንባ አልቃሽ የሆሊዩድ አክተሮች በሉዋቸው ሲሉ ነበር። የእናታቸው ጡት እንደጎረሱ ከፍርስራሽ ስር የቀሩ ህፃናትን ጀናዛ ማውጥት እንዳይቻል የአሜሪካ የጦር ጀቶች የቦንብ ናዳ ሲያወርዱ የአሜሪካ ባለስልጣናት ውስኪ ያገሱ ነበር። የፍልስጢን ሰማይ በሰው ሰራሽ እሳትና በአቅመደካሞች ደም ከለሩ ሲቀየር የዛሬዎቹ የሆሊዩድ አክተሮች ፊልም ይሰሩበት ነበር።
ምንዳ በሰሩት ስራ ልክ ነውና ዛሬ እብሪተኛዋ፣ ትምክህተኛዋ፣ ማን አለብኝ ባይዋ፣ አንባ ገነኗ አሜሪካ የስራዋን ውጤት ለማየት ተገዳለች። ፍልስጢንን ለማውደም በቢሊየን ዶላይ የመደበው ባይደን ዛሬ የደረሰበትን ውድመት ለማስቆም የሚችል ዶላርም፣ መሳሪያም፣ የምርምር ተቋምም፣ የጦርም ይሁን የተማረ ሀይል አጥቶ የሚሆነውን በቁጭት ለማየት ተገደደ።
ከአላህ የተላከው እሳት ሎስ አንጀለስ ላይ ከፊቱ የሚቆም ሀይል የለም በቃህ ባይ የለውም ሁሉንም ነገር ያቃጥላል ያወድማል ያከስማል፣ ከተማን ወደ አመድነት ይቀይራል ። ዝነኞቹ የሆሊዩድ አክተሮች ማን ይወዳደረዋል ከሚባልለት መኖሪያቸው ባዶ እጃቸውን ወጥተው የሲቃ እንባ እያነቡ አለኝ የሚሉት ነገር እሳት ሲበላው እያዩ ነው። የአሜሪካ ባለ ስልጣናት የስብእና ዝቅጠትና የማንነት ማዝቀጫ ፋብሪካ የሆነውን ሆሊዩድን እሳቱ ሲበላው ለማየት እየተገደዱ ነው። ያ የዝቅጠት ፋብሪካ ሆሊዩድ ያ ፈጣሪ የሚባል ነገር የለም የሚሉ አክተሮች የሞሉበት የኩፍር መናሃሪያ የሆነው ሆሊዩድ እሳቱ ደረስኩ እያለው የይድረሱልኝ ጣር እያሰማ ሲሆን ጣኦቱ ባይደን የለምና ድንጋይ ቆሞ ከመቅረት ውጪ አማራጭ አጥቷል።
የትኛውን የጦር ጀት ወዴት ያሰማራ? ወደ ማን ይተኮስ ይበል? በማን ላይ ያቧርቅ? በድን ሆኖ መቅረትና የሚሆነውን ከማየት ውጪ መላ የለውም። ለመሆኑ ባይደን የትላንቱን የፍልስጢንንና የኑፁሃን ህዝቦቿ ዋይታና ሲቃ በአይነ ህሊናው ይቃኝ ይሆን? ሊሆን አይችልም ምክንያቱም ህሊናው እብሪት ጋርዶታልና ዛሬ በንፁሀን ደም የጨቀየው እጁ የዘራውን እያጨደ ነውና ልቦናው ታውሯል። በድን ሆኖ የሚሆነውን ከማየት ውጪ አማራጭ የለውም እሱም አጋሮቹም ሺ ጊዜ አምሳያቸው ቢጨመርም ምንም ማድረግ አይችሉም ምክንያቱም የአላህን ሰራዊት የሚገጥም የለምና
የፊራኦንን ሰራዊት በውሃ ያሰመጠ፣ የኑሕ ዘመን እብሪተኞችን ከሰማይና ምድ በታዘዘ ፍል ውሃ ያጠፋ የመድየንን የሉጥንና የሰሙድን ህዝቦች በመላኢካ ጩኸት ያጠፋ አምላክ በዛሬዎቹ እብሪተኞች ላይ ከሰራዊቱ መካከል የሆነውን እሳትና አውሎ ነፋስ ልኮ አሜሪካን እያመሰ ይገኛል። የጌታህ ሰራዊት እሱ እንጂ ማንም አያውቀውም

«وَمَا جَعَلْنَا أَصْحَابَ النَّارِ إِلَّا مَلَائِكَةً ۙ وَمَا جَعَلْنَا عِدَّتَهُمْ إِلَّا فِتْنَةً لِّلَّذِينَ كَفَرُوا لِيَسْتَيْقِنَ الَّذِينَ أُوتُوا الْكِتَابَ وَيَزْدَادَ الَّذِينَ آمَنُوا إِيمَانًا ۙ وَلَا يَرْتَابَ الَّذِينَ أُوتُوا الْكِتَابَ وَالْمُؤْمِنُونَ ۙ وَلِيَقُولَ الَّذِينَ فِي قُلُوبِهِم مَّرَضٌ وَالْكَافِرُونَ مَاذَا أَرَادَ اللَّهُ بِهَٰذَا مَثَلًا ۚ كَذَٰلِكَ يُضِلُّ اللَّهُ مَن يَشَاءُ وَيَهْدِي مَن يَشَاءُ ۚ وَمَا يَعْلَمُ جُنُودَ رَبِّكَ إِلَّا هُوَ ۚ وَمَا هِيَ إِلَّا ذِكْرَىٰ لِلْبَشَرِ »
المدثر ٣١
"የእሳትንም ዘበኞች መላእክት እንጅ ሌላ አላደረግንም፡፡ ቁጥራቸውንም ለእነዚያ ለካዱት መፈተኛ እንጅ አላደረግንም። እነዚያ መጽሐፍን የተሰጡት እንዲያረጋግጡ፣ እነዚያም ያመኑት እምነትን እንዲጨምሩ፣ እነዚያም መጽሐፍን የተሰጡትና ምእምናኖቹ እንዳይጠራጠሩ፣ እነዚያም በልቦቻቸው ውስጥ በሽታ ያለባቸው (መናፍቃን)፣ ከሓዲዎችም አላህ በዚህ (ቁጥር) ምን ምሳሌ ሽቷል? እንዲሉ (እንጅ አላደረግንም)፡፡ እንደዚሁ አላህ የሚሻውን ያጠምማል የሚሻውንም ያቀናል የጌታህንም ሰራዊት (ልክ) ከርሱ በቀር ማንም አያውቅም። እርሷም (የሰቀር እሳት) ለሰዎች መገሰጫ እንጅ ሌላ አይደለችም።"

ይህ ዛሬ በአሜሪካ ባለስልጣናት ላይ ምፅዓት የሚመስለው እሳት አኼራ ላይ ከሚጠብቃቸው አንፃር ኢምንት ነው። ሩቅ ይመስላቸዋል ግን ቅርብ ነው። ወደ አላህ ተመልሰው ለአላህ ትእዛዝ እስካላደሩ ድረስ። እስኪ የዛን ቀን ሁኔታ በቁርኣን ገለፃ እናስተውለው፦

إِنَّهُمْ يَرَوْنَهُ بَعِيدًا
እነርሱ (ያንን ቀን) ሩቅ አድርገው ያዩታል።
وَنَرَاهُ قَرِيبًا
እኛም ቅርብ ኾኖ እናየዋለን፡፡
يَوْمَ تَكُونُ السَّمَاءُ كَالْمُهْلِ
ሰማይ እንደ ዘይት አተላ በምትኾንበት ቀን
وَتَكُونُ الْجِبَالُ كَالْعِهْنِ
ጋራዎችም በተለያዩ ቀለማት እንደ ተነከረ ሱፍ (ነፋስ እንደሚያበረው) በሚኾኑበት ቀን
وَلَا يَسْأَلُ حَمِيمٌ حَمِيمًا
ዘመድም ዘመድን በማይጠይቅበት ቀን፤ (መላሽ የለውም)
يُبَصَّرُونَهُمْ ۚ يَوَدُّ الْمُجْرِمُ لَوْ يَفْتَدِي مِنْ عَذَابِ يَوْمِئِذٍ بِبَنِيهِ
(ዘመዶቻቸውን) ያዩዋቸዋል፡፡ አመጸኛው ከዚያ ቀን ስቃይ (ነፍሱን) በልጆቹ ሊበዥ ይመኛል፡፡
وَصَاحِبَتِهِ وَأَخِيهِ
በሚስቱም በወንድሙም፡፡
وَفَصِيلَتِهِ الَّتِي تُؤْوِيهِ
በዚያችም በምታስጠጋው ጎሳው፡፡
وَمَن فِي الْأَرْضِ جَمِيعًا ثُمَّ يُنجِيهِ
በምድርም ላይ ባለው ሁሉ (ሊበዥ) ከዚያም ሊያድነው (ይመኛል)፡፡
كَلَّا ۖ إِنَّهَا لَظَىٰ
ይተው! እርሷ (እሳቲቱ) ለዟ ናት፡፡
نَزَّاعَةً لِّلشَّوَىٰ
የራስን ቅል ቆዳ የምትሞሽልቅ ስትኾን፡፡

تَدْعُو مَنْ أَدْبَرَ وَتَوَلَّىٰ
(ከእምነት) የዞረንና የሸሸን ሰው (ወደእርሷ) ትጠራለች።

ሱረቱል መዓሪጅ ከአንቀፅ 6 –17

እነዚያ የአላህን ባሮች የሚፈትኑ አካላት ተውበት አድርገው ካልተመለሱ ምን እንደሚጠብቃቸው በሚከተለው የአላህ ቃል እናያለን፦
«إِنَّ الَّذِينَ فَتَنُوا الْمُؤْمِنِينَ وَالْمُؤْمِنَاتِ ثُمَّ لَمْ يَتُوبُوا فَلَهُمْ عَذَابُ جَهَنَّمَ وَلَهُمْ عَذَابُ الْحَرِيقِ»
    البروج ١٠
"እነዚያ ምእምንንና ምእምናትን ያሰቃዩ ፣ ከዚያም ያልተጸጸቱ ለእነርሱ የገሀነም ቅጣት አልላቸው። ለእነርሱም የመቃጠሉ ስቃይ አልላቸው፡፡"
     
ለማንኛውም እኛ ለእነዚህ አካላት የምንለው ሂዳያ የሚገባቸውን አላህ ሂዳያ ይስጣቸው። ሂዳያ የማይገባቸውን ደግሞ በጥበቡና ፍትሀዊነቱ የሚገባቸውን ይስጣቸው ነው

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

13 Jan, 06:38


አሰላሙአለይኩም  ወረህመቱላሂ ወበረካቱህ

📢 አዋጅ አዋጅ አዋጅ ስሙ ላልሰማም አሰሙ ‼️

ውድና የተከበራቹህ በሀራና በሀሮ  እንድሁም በጥልፌና  አከባቢዋ  ለምትኖሩ   ሰለፍዮች በሙሉ  እነሆ የፊታችን እሮብ በሰሜን ወሎዞን በሃብሩ ወረዳ (028)ቀበሌ ዶዶታ ላይ በአይለቱ ለየት ያለ  የዳዕዋ ፕሮግራም ተደግሷል ብለን ስናበስራችሁ በታላቅ ደስታ ነው  ።

አስታውሱ እንዳትረሱ የፊታችን  እሮብ ማለትም 🗓ጥር  ቀን/7 /5/2017 /ታላቅ የዳዕዋ ዝግጅትና ሂደት ተዘጋጅቶ  ላችኋል  ስለሆነም  እንኳን  መቅርትና  ማርፈድ ራሱ  ያስነድማል

በተባለው ቀንና ቦታ ላይ በመገኘት የዳዕዋው ተካፋይና ተቋዳሽ እንድትሆኑ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል
 
🪑ተጋባዥ እንግዶቻችነን እነሆ ብለናል  ሹፉ

1.🎙ሸይኽ  ሙሀመድ ሀያት ከሀራ
2.🎙ሸይኽ  ሁሴን  ከረም  ከሀራ
3.🎙ሸይኽ  ሙሀመድ  ሲራጅ  ከሀሮ
4.🎙ኡስታዝ  መሀመድ  ሰልማን  ከሀራ
5.🎙ኡስታዝ  አቡ  ሙጃሂድ  ሱልጧን  ከሀራ

🪑በቦታው ላይ ሌሎችም ተጋባዥ እንግዶች ይኖሩናል የወሳኝ ምክርና ከተለያዩ በዥታዎች ለመከላከል   ክትባትና እርጭት ያስፈልጋል

🌎በሰሜን ወሎ ዞን  በሀብሩ  ወረዳ  ቀበሌ (028)ከጥልፌ  4 ኪ/ሎ ሜትር እርቀት ገዳማ ያላች ሲሆን  ገጠራማ  መንደር ነች  መጠሪያ ሱሟ    ዶዶታ በማለት ትታዎቃለች ከመኢቲ ከፍ ያለች ሰፈር ነችና ሁላችሁም እንዳትቀሩ በማለት ታድማችኋል

የዝግጅቱ አዳሚና አስተባባሪ የዶዶታ ሰለፍያ ወጣቶች ናቸው

https://t.me/hussenhas

Abu hatim Abduselam Assalefiy

10 Jan, 17:13


Live stream finished (1 hour)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

10 Jan, 16:16


👉 የነሲሓዎች የአደባባይ ዝቅጠት ለአደባባይ ክስረት

ነሲሓዎች የነበሩበት መንገድ ለዱንያዊ ክብረት እንደማይሆን ሲያውቁ ሸይኻቸው ኢልያስ አሕመድ ህዝቡን አስተኝቶላቸው ከኢኽዋን ጋር ተቀላቅለው መስራት እንዳለባቸው ከወሰኑ በኋላ በ30 የእንቅልፍ ክኒን ወጣቱን አስተኛላቸው ። ቀጥለው የተኛው ህዝብ ሳይነቃ ቶሎ ወደ ሚፈልጉበት ለመድረስ ሩጫ ጀመሩ ። ሩጫቸው ታርጌት ያደረገው የእንጀራ አባቶቻቸው ኢኽዋኖችን ማስደሰት ላይ ነበር ። በዚህም ሸይኻቸው ዶ/ር ጀይላንን ከማወደስ ጀምሮ የተለያዩ ደረጃዎችን በፍጥነት እየተንደረደረ ነጎደ ።
አደባባይ እየወጣ ከነ ካሚል ሸምሱ ፣ አቡ በከር አሕመድ ፣ ያሲን ኑሩ ፣ ሙሓመድ ሓሚዲን ፣ ሓሚድ ሙሳና ሌሎችም ዋና ዋና መሪዮች ጋር በተለያዩ ፕሮግራሞች አብሮነታቸውን አሳየ ። እሱ መርጂዓቸው ስለሆነ እንጂ እነ አዩብ ደርባቸውም በፊናቸው በተለያዩ መድረኮች አብሮነታቸውን አረጋግጠዋል ። ይህ ሁሉ ሲሆን በ30 የእንቅፍ ክኒን እንዲተኙ የተደረጉ ሙሪዶች አልነቁም ነበር ። ይልቁንም እኛ ስለማናውቅ ነው እንጂ እነርሱ ያለ መስላሓ አይሰሩም የሚል የጋራ ድምፅ ያሰሙ ነበር ።
ኢልያስ አሕመድ 30 የእንቅልፍ ክኒን ሲሰጥ አብዛኛው ወጣት ኢኽዋኖችን ያለእውቀታችን በናንተ ላይ ተናግረን ነበር አሁን ተመልሰናል አውፍ በሉን ብሎ ነበር ። ያኔ የ30 ክኒኖቹ ሚስጢር የገባቸው ሰዎች ውስጣቸው እያረረ ኢኽዋኖች በድል አድራጊነት ስሜት ይጎርሩ ነበር ። መሻኢኾችና የተወሰኑ ወንድሞች ያደረጉት የነሲሓዎችን አካሄድ የማጋለጥ ትግል ብዙ ፍሬ ያፈራ የነበረ ቢሆንም የአሁኑ አይነት ድል ይገኛል ብሎ ያሰበ አልነበረም ።
በሚገርም መልኩ ብዙ ወንድምና እህቶች የነሲሓዎች ሸይኽ ሶሞኑን የሱፍያና ኢኽዋንያ ሚንሀጅ እስፕሪስ ጭማቂ ከሚያንቃርረው ሙሐመድ ዘይን ዘህረዲን ጋር የነበረውን ፕሮግራም ካዩ በኋላ አውፍ በሉን ነገሩ በዚህ መልኩ አልመሰለንም ነበር እያሉ ነው ።
ለእነዚህ ወንድምና እህቶች እንዲሁም ለሌሎችም የምንለው መጀመሪያ ምስጋና ሐቅን ላሳወቃችሁ አምላካችን አላህ ይገባው ። ቀጥሎ እኛን በግል በሰድብም ይሁን ስም በማጥፋት ላደረሳችሁት በደል በቅድሜያ እኔ በግሌ አውፍ ብያለሁ መሻኢኾችም ይሁን ሌሎች ወንድሞች ከዚህ የተለየ እይታ ይኖራቸዋል አልልም ። ምክንያቱም ሁላችንም ነብዩን ነውና የምንከተለው ። የአላህ መልእክተኛ አላህ መካን እንዲከፍቱ ድል ሲሰጣቸው እነዚያ መተተኛ ፣ ጠንቋይ ፣ ገጣሚ ፣ እብድ ሲሏቸው የነበሩ የመካ ሹማምንቶች ተሰብስበው ፍርዳቸውን ለመቀበል ሲጠብቋቸው ሂዱ እናንተ ነፃ ናችሁ ነበር ያሉዋቸው ። ነብዩላሂ ዩሱፍም ጉድጓድ ውስጥ የወረወሩዋቸውን ወንድሞቻቸው አላህ ድል ሰጥቶ የበላይ አድርጓቸው አንገታቸውን ደፍተው ይቅርታ ሲጠይቋቸው ሂዱ አላህ ምህረቱን ይስጣቸሁ ነበር ያሉዋቸው ። የሚፈለገው ሐቅን አውቆ ወደ አላህ መመለሱ ነውና የሰዎች ክብር የተነካው በአላህ መንገድ ላይ እስከሆነ ድረስ ከፍታ እንጂ ዝቅታ ስላልሆነ ቦታ አይሰጠውም ። ይልቁንም ይህን ወንጀል ከመስራታችሁ በፊት ከነበራችሁ ደረጃ ይጨምርላችኋል ። ምክንያቱም አላህ ዘንድ አንድ ሰው ወንጀል ሳይሰራ በፊት ከነበረው ደረጃ ወንጀል ሰርቶ ተውበት አድርጎ ሲመለስ ያለው ስለሚበልጥ ።
አሁንም ኢልያስም ሆነ ሌሎች በየቀኑ እየዘቀጡ ማየታችን ለኛ ህመም እንጂ ደስታን አይፈጥርም ። የወንድምና እህቶች መመለስ የሚፈጥረው ደስታ የነሲሓዎች ዝቅጠት ያደበዝዘዋል ። ሙሉ ደስታ የሚሰጠው ሙኻሊፎች ባጠቃላይ ተውበት አድርገው ወደ አላህ መመለሳቸው ነው ። አሁንም ለነሲሓዎች የምንለው በየቀኑ በአደባባይ የምታሳዩት ዝቅጠት ወደ አደባባይ ክስረት እየተቀየረባችሁ ነውና ቆም ብላችሁ አስቡና ተመለሱ ነው ።

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

10 Jan, 16:07


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

10 Jan, 16:06


ሳምንተዊ የቁሪኣን ተፍስር ልጀምር ነዉ
ገባ
       ገባ
                በሉ
https://t.me/abuhatimaselefiy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

07 Jan, 19:14


👉 ተውሒድ በሰሜን ወሎ

ወሎ ዞን የሽርክ ግሳንግስና ኮተት ማከማቻና ማከፋፈያ የነበረ ሲሆን የሰሜኑ ክፍል ይህን ታሪክ ለመቀየር እየሰራ ነው ። በአሁኑ ሳአት በሰሜን ወሎ ሓራ ከተማ የሰፋ መስጂድ ኢማም በሆኑት ሸይኻችን ሸይኽ ሙሐመድ ሐያት የበራው የተውሒድ ፓውዛ ብርሃኑን ለአጎራባች ሀገሮች ማከፋፈል ጀምራል ። በዚህም ሰሜን ወሎ ያጠቃላይ ወሎን ታሪክ ለመቀየር የቆረጠች ትመስላለች ። በየቦታው ያሉ የነሕውና የፍቅህ እንዲሁም የተፍሲር ዑለሞች አይናቸውን ጋርዶት የነበረው የሱፍያ ዐቂዳ ለተውሒድ ዳዕዋ ቦታውን አስረክቦ ላይመለስ ተሰናብቶ ሄዶ የሱና ዑለሞች ሆነዋል ።
እነዚህ መሻኢኾች በአሁኑ ሳአት ትላንት የነበሩበትን ያ የጨለማ ህይወት በአይነ ህሊናቸው አማትረው እያዩ ፍፁም በሆነ ፀፀት ተውሒድና ሱናን ለመኻደም እየተጉ ይገኛሉ ። በቁጭት ከአንደበታቸው የሚወጡት ቃላቶች አጥንትን ሰርስረው ይገባሉ ።
ለዚህ አስገራሚ የሰሜን ወሎ ለውጥና የሰለፍያ ዳዕዋ ፍሬ ማፍራት ሰበቡ ሸይኽ ሙሐመድ ሐያት መሆናቸው የአላህ ስራ ረቂቅነት ማሳያ ነው ። ምክንያቱም ሸይኻችን የመውሊድ መንዙማ ንጉስ ነበሩና ከዛ ጉድ አውጥቶ የተውሒድና ሱና መሪ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል ።
የወሎ ገራገር ህዝብ ሱፍዮች እየነዱ ድስቱር እያሰኙት የሸይኾች ገድል በሚሉት ጆሮውንና ዐቅሉን አደንቁረው ከቁርኣንና ሐዲስ አርቀውት ነበር ። ዛሬ አላህ እንዲህ ብሏል ነብዩ ይህን አዟል ሲባሉ በለቅሶ ነው የሚቀበሉት ። ለፍጡር ከመገበር ወጥተው ፈጣሪን ሲያውቁ የበፊቱን ተግባር ከቶ እየናቁ ለብቸኛው አምላክ ለአላህ የሚዋደቁ ሆነዋል ። ላያቸው ጉድ የሚያሰኙ የአላህ ባሮች ናቸው ። ከዚህ በፊት ለዳና ለከረም ፣ ለጫሌ ለሸንኬ ፣ ለዐንይና አማን አንብይ ፣ ለጡሩ ሲና ጀማ ንጉዝ ሲገብሩት የነበረውን ቁርባን ወደ አላህ ቤት እየነዱ ይገኛሉ ።
ይህ ከሓራ የሚከፋፈለው የተውሒድ ችግኝ በየቦታው በቅሎ ፍሬ እየሰጠ ነው ። የወሎ ወንድምና እህቶች ባጠቃላይ የሰሜን ወሎ በተለይ ከዚህ ዳዕዋ ጎን እንድትቆሙና ሸይኽ ሙሐመድ ሓያትን አብሽ እንድትሉ ለማስታወስ እወዳለሁ ።

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

07 Jan, 19:14


🔷 በዚ ዘመን ነው እንዴ የሚያሰኝ ታሪክ

በሶሞኑ የሓራና ሀሮ ጉዞዬ በጣም የሚገርምና በሐዘንና የአድናቆት የተደበላለቀ ስሜት የእንባ ቧንቧ የሚከፍት እውነተኛ ታሪክ ሰምቼ ላካፍላችሁ ወደድኩኝ ። ታሪኩንም እንደሚከተለው አቀርብላችኋለሁ : –
ክስተቱ በወሎ ዞንተንታ በምትባለው የሀገራችን ክፍል የተከሰተ ነው ። እንደሚታወቀው ሀገራችን ውስጥ በተለያዩ ክልሎች የተለያዩ የሽርክ አይነቶች ይሰራሉ ። ሽርክ ደግሞ ደረካቱ ይለያያል ። የሽርክ አይነቶች ሁሉ እኩል አይደሉም ። በጣም አሰከፊ የሽርክ አይነት ከሚካሄድባቸው አካባቢዮች አንዱ የወሎ ዞን ነው ። ወሎ አካባቢ የሽርክ ኮተትና ግሳንግስ ሲሆን የሚሰሩ የሽርክ አይነቶች የህፃናት ፀጉር የሚያሸብቱ ናቸው ። ሽርክ መሰራቱ ብቻ ቢሆን ባልከፋ ነበር ነገር ግን እነዚህ የሽርክ ተግባር የሚሰሩ አካላት ከእነርሱ ጋር አብሮ ያልሰራን ወሀብይ በሚል የሚችሉትን ሁሉ በማድረግ ባይተዋር እንዲሆን ማእቀብ በመጣል ራሱን እንዲጠላ ያደርጋሉ ።
የዘህ ግፍና በደል ገፈት ቀማሽ ከሚሆኑት የአላህ ባሮች ውስጥ ከላይ በተጠቀሰው ደቡብ ወሎ ተንታ በምትባለዋ መንደር ውስጥ ነዋሪ የሆኑት ሸይኽ አሕመድ ዐ/ወሀብ አንዱ ናቸው ። እኝህ ሸይኽ ሽርክን በአይነቱ አውግዘው አድባር ቆሌ አልገዛም ፣ የሙታንን መንፈስ አልለማመንም ፣ ፍጡርን ድረሱልኝ ብዬ ከጌታዬ ደጃፍ መባረር አልመርጥም ፣ በቂዬ አላህ ነው እሱን ብቻ ነው የማመልከው ፣ የምከጅለውና የምለምነው ፣ ከጭንቅ አውጣኝ ፣ ተምኪን ፈልጌያለሁ ብዬ እጄን ምዘረጋው ወደርሱ ብቻ ነው በማለታቸው ከአካባቢ ማህበረሰብ እንዲገለሉ ተደረጉ ። በዚህ አላበቃም ማእቀቡ ቢታመሙም ቢታመምባቸውም እንዳይጠየቁ ፣ ቤተሰባቸውም ሆነ እሳቸውም ከማንም ጋር እንዳይገናኙ ፣ ቢሞቱ እንዳይቀበሩ ፣ ቢሞትባቸውም እንዳይቀበርላቸው ፣ ምንም አይነት ችግር ቢገጥማቸው ማንም እንዳይረዳቸው ተወሰነባቸው ።
ይሁን እንጂ እኚህ ሸይኽ ከማህበሰቡ የተጣለውን ማእቀብ ከቁብ ሳይቆጥሩ ልጆቻቸውንና ባለቤታቸውን ይዘው በማህበረሰቡ የተወገዙና የተረገሙ እየተባሉ አላህ በቂያችን ነው ብለው የህይወትን ጉዞ ጀመሩ ። ይህ ሲሆን የሱና ሰዎችን ለማግኘት ደርሶ መልስ የ6 ሳአት መንገድ የሚሆን ቦታ ሄደው እየመጡ የባይተዋርነት ስሜታቸውን እያቀጨጩ ነበር ።
እኚህ ጉደኛ ሸይኽ አላህ ይህን ፅናታቸውን የሚፈታተን ፈተና እንዲገጥማቸው ፈለገ ። ልቻቸው በጠና ታመመ ። ልጃቸውን ሐኪም ቤት አስገብተው ያለ ጠያቂና ያለ ተተኪ ሲያስታምሙ ቆዩ ። የአላህ ውሳኔ ሆነና ልጃቸው ወደ አኼራ ሄደ ። ቤታቸው ከሐኪም ቤቱ በእግር የ3 ሳአት መንገድ ያስኬዳል ። መኪና ለመከራየት አቅም አልነበራቸውም ። አብሽር ብሎ የሚያፅናና ቤተሰብም ሆነ ጎረቤት አጠገባቸው የለም ። የልጃቸውን ጀናዛ ተሸክመው የሶስት ሳአት መንገድ ተጉዘው ቤታቸው ደረሱ ። እናትና አባት የልጃቸውን ጀናዛ አጥበው ከፍነው ተሸክመው ወስደው ቀበሩ ።ሱብሓነ ላህ ለስሙ በሙስሊም ማህበረሰብ ውስጥ ነው ያሉት ነገር ግን አላህ በቂያችን ነው እንዴት ትላላችሁ ተብለው በዚህ መልኩ ታሪክ የማይረሳው አላህ ፊት አሳፋሪ የሆነ ተግባር ተፈፀባቸው ።
እኚህ ጉደኛ አባትና እናት ልጃቸውን ቀብረው ተመልሰው አላህ በቂያችን ነው ይህ ለተውሒድ ከሚከፈል ዋጋ አንፃር ኢምንት ነው አሉ ። አላህ የፈለገውን ይሰራል ልጃችንን እኛ ቀብረነዋል ሁላችንም ሞተን ሬሳችን አውሬ ቢበላውም አላህን ከማምለክ ሊያግደን የሚችል አይኖርም ይላሉ ።
ከዚህ መራራ ፈተና በኋላ ግን ሶብራቸውና ፅናታቸው ፍሬ አፍርቶ ትላልቅ መሻኢኾች እንደነ ሸይኽ ኢስማኢል ፣ ሸይኽ ዐ/ ሰመድ ፣ ሸይኽ ሙሐመድ ሓያትና ሌሎችም ወደ ተውሒድ ተመልሰው በአሁነ ሳአት ተንታ አካባቢ በሸይኽ ኢስማኢል አማካይነት የተውሒድና ሱና ዳዕዋ እየተስፋፋ ነው ። ኪታቦች ይቀራሉ ፣ ሙሓደራዎች ይደረጋሉ ፣ ልጆች ተውሒድና ሱና ይማራሉ ፣ ባጠቃላይ የሰለፍያ ዳዕዋ ችግኝ እያበበ ነው ።
ይህ የሆነው በተጣለባቸው የግፍ ማእቀብ ለ30 አመት አካባቢ በፅናት የታገሉት ሸይኽ አሕመድ ዐ/ወሃብ በህይወት እያሉ ነው ። በአሁኑ የሓሮ ፕሮግራም ላይ ለመሳተፍ እንደሚመጡ ሸይኽ ሙሐመድ ሓያት ደውለው ከነገሯቸው በኋላ ጉዳይ ገጥሟቸው መጥተው ለማየት ሳንታደል ቀርተናል ። እስኪ ይህን ታሪክ የምናነብ ወደራሳችን እንመልከት እኛ ለነብዩ ዲን ምን የከፈልነው ዋጋ አለ ? አላህ ይዘንልን ።

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

07 Jan, 19:14


🔷 የመጅሊስ አመራሮች ለሙስሊሙ መብት ወይስ በሙስሊሙ መብት ⁉️

👉 የመጅሊሱን ስልጣን በበላይነት የተቆጣጠሩት የሀገራችን የኢኽዋን አንጃ ዋና መሪዮች የሙስሊሙን መብት ያስጠብቃሉ ማለት ኢኽዋን ማለት ምን ማለት እንደሆነ የማያውቅ ምስኪን ምኞት ነው። ኢኽዋን ማለት እንደ እስስት ራሱን የሚቀያይር የፖለቲካ አነፍናፊ የማፊያ ቡድን ነው። አላማው ስልጣን ነው በሙስሊሞች ላይ የሚደርሱ ግፎችን ለማስቆም ቀርቶ ማሰቡ ራሱ ለስልጣናቸው አደጋ መስሎ ነው የሚታያቸው። በመሆኑም ወንበራቸው ላይ ሆነው ይህን ብንናገር ምን ይመጣ ማን ይቆጣ ይሆን በሚል ስለ ወንበራቸው የሚጨነቁት። አልፎ ከሄደም የህዝቡን እንቅስቃሴ አይተው መልካቸውን ቀይረው በህዝቡ ጩኸት ተከልለው የሆነ መግለጫ ያወጣሉ።
♻️ በተቃራኒው ከፌዴራል እስከ ቀበሌ በተዋረድ ተውሒድና ሱና ያለባቸውን መስጂድና መድረሳዎችን ለማዘጋት ያለ እንቅልፍ ይሰራሉ። በአሁኑ ሳአት በተለይ በስልጤ ዞን ያሉ የመጅሊስ አመራሮች በዚህ ተግባራቸው የሚያውቁዋቸው የመንግስት ባለስልጣናት ስለሙስሊሞች መብት ቢያነሱ እንኳን ከቁብ አይቆጥሯቸውም። በተግባራቸው ንቀውዋቸዋልና ለሙስሊሞች ሳይሆን ለጥቅማቸው የቆሙ ስለሆኑ የሚፈልጉትን ሊያስፈፅሙላቸው እንጂ የሙስሊሙ መብት እንዲሏቸው አይፈቅዱላቸውም። ይሁን እንጂ እነዚሁ አካላት የተውሒዱን ዳዕዋ ለማደናቀፍና ሱናን ለማዳፈን በሚያደርጉት ርብርብ ያዘዙትን ይፈፅሙላቸዋል። ያስሩላቸዋል መድረሳዎችና መስጂዶችን ያሽጉላቸዋል።
     
ታዲያ በዚህ መልኩ የነብዩንና የሶሓቦችን ትክክለኛ ዲን ለማጥፋት እንቅልፍ አጥቶ የሚሮጥ አካል በምን ሞራል ነው የሙስሊሞችን መብት የሚያስጠብቀው። እነዚህ አካላት በድምፃችን ይሰማ ሸሪዓን የበላይ ለማድረግ ነው ብለው ሙስሊሙን ከዳር እስከዳር አነቃንቀው ባለሀብቱን እንደ ፈንጅ ላም አልበው ቤታቸው ቤተመንግስት ካስመሰሉና በቪ 8 መሄድ እየሄዱ የመጅሊስ ወንበር ላይ ሲወጡ እንኳን ኢትዮዽያ ላይ ሸሪዓ ማወጅ አይደለም ማሰቡም ወንጀል ነው ነበር ያሉት። ይህ በአለም ላይ ያሉ ኢኽዋኖች አቋም ነው።
   
🔎 ሙሐመድ ሙርሲ ግብፅ ላይ ወንበር ሲይዝ እኛ አላማችን መደንይ (የዲሞክራሲ) ስርኣት ማምጣት ነው ሸሪዓ አይደለም ነው ነበር ያለው። ከወንበሩ መነሳቱ ላይቀር አላህን የሚያስቆጣ ንግግር ተናግሮና መመሪያ ሰጥቶ ተነሳ። ከወንበሩ መነሳቱ አይደለም ከዱንያም ለመነሳቱ ሰበብ ሆነው። እናንተ ኢኽዋን እስልምናን የበላይ ያደርጋል የሙስሊሞችን መብት ያስጠብቃል ብላችሁ የምትጃጃሉ ምስኪን ሙስሊሞች ከንቅልፋችሁ ንቁ። ታሪካቸው በተቃራኒው ነው ስልጣን የሚፈልጉት ኪሳቸውን ለማደለብ ሲሆን ወንበራቸውን ለማስጠበቅ አረቄ እየገዙ ለባለስልጣኖች እጅ የሚነሱ ናቸው። ሰሩ ከተባለ በሙስሊሞች ላይ እንጂ ለሙስሊሞች አይደለምና ልብ በሉ።
    
ለዚህ ማረጋገጫው በቅርቡ መደረጉ ላይቀር አ/አ ሚሊኒየም አዳራሽ ላይ ተዘጋጅቶ የነበረው የሰለፍዮች ኮንፈረስ እንዲደናቀፍ የሄዱበት ርቀትና የከፈሉት ዋጋ ነው። ይህ ተግባራቸው በባለስልጣናቱ ዘንድ ትዝብት እንዲያተርፉ አድርጓቸዋል። አሁን የመጅሊስ አመራሮችን የምታወግዙና የምትረግሙ የኢኽዋን አክቲቪስቶች እናንተም የመጅሊሱን ስልጣን ብትይዙ ያው ናችሁ ምክንያቱም መርሃችሁ አንድ ነውና። ጉዳይ የጉልቻ መቀያየር ነው የሚሆነው።
    
➲ ሙስሊሞች ሆይ በስማችሁ የሚነግደውን ኢኽዋን አንቅራችሁ ተፍታችሁ ቁርኣንና ሐዲስን በሶሓቦች ግንዛቤ ተከተሉ ተውሒድና ሱና የበላይ እንዲሆን በራሳችሁ ላይ ሸሪዓን ተግባራዊ አድርጉ የዛኔ የአላህ እርዳታ ታገኛላችሁ እላለሁ አላህ ይርዳን።

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

07 Jan, 19:14


አይ ኢልያስ አህመድ!!!
➬➬➬➬➬➬

🏝 ከሰሞኑ ሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ዘህረዲን የነሲሃ ቲቪ እና የአፍሪካ ቲቪ ዱዓቶች  ❴በሙመይዓዎች እና በኢኽዋኖች❵ መካከል ምንም ልዩነት የለም። ስለዚህ በአንድ ላይ መገኘት አለባቸው እያለ ተናገረ!

🎙     ➘➴➘➴➘
https://t.me/AbuImranAselefy/9437

♻️ ንግግሩ መሬት ጠብ ማለት የለበትም ብሎ የሙመይዓዎቹ ተወካይ የሆነው ኢልያስ አህመድ ይሄው ቃሉን ሞላለት! አቤት መከባበር ¡ አቤት ውደታ¡ አቤት ቃል አጠባበቅ¡

👉 ሰዎቹ በደንብ ለይቶላቸዋል ገና ከዚህም የባሱ ጉዶችን እንፈፅማለን የሚሉ ይመስላል። ጉድኮ ነው! ኧረ ከጉድም በላይ!

🔎 አምና ከነካሚል ሸምሱ ከነአህመዲን ጀበል ከነሙሐመድ ሀይሚድን ጋር ሲገናኝ ኧረ ለግል ጉዳይ ነው። ኧረ ለለቅሶ ነው ኧረ.... እያላችሁ ኡዝር ስትደረድሩ የነበራችሁ ሙሪዶች ሆይ! አሁንስ ታለቅሱ ወይስ? መቼስ ለለቅሶ ሄዶ ነው አትሉም ኣ¡

➲ አንዳንድ ታማኝ ሙሪዶችማ «ለመስለሃ እንጂ...» አይይ ሚስኪን! እስከመቼ በዚህ መልኩ ራሳችሁን ትሸውዳላችሁ ኣ!? ዲንን እና ኢልያስን ለዩንጂ ሰዎች!

አጥፊዎች በጥፋት እስከዘወተሩ ድረስ እኛም በማጋለጥ እንዘወትራለን። ያበጠው ይፈንዳ ሲፈልግ ይተርተር፤ እውነት ይነገራል ቢጣፍጥም ቢመር! አለቀ!

👌              ➴➘➴
https://t.me/AbuImranAselefy/9437

Abu hatim Abduselam Assalefiy

05 Jan, 16:55


Live stream finished (50 minutes)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

05 Jan, 16:04


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

05 Jan, 16:03


ሳምንተዊ የቁሪኣን ተፍስር ልጀምር ነዉ
ገባ
       ገባ
                በሉ
https://t.me/abuhatimaselefiy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

04 Jan, 17:23


Live stream finished (37 minutes)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

04 Jan, 16:46


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

04 Jan, 16:46


Live stream finished (5 minutes)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

04 Jan, 16:40


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

04 Jan, 16:39


Live stream finished (29 minutes)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

04 Jan, 16:10


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

04 Jan, 16:08


ሳምንተዊ የቁሪኣን ተፍስር ልጀምር ነዉ
ገባ
       ገባ
                በሉ
https://t.me/abuhatimaselefiy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

04 Jan, 12:13


  ልዩ የዳዕዋ ፕሮግራም
          🏘 በሃሮ ከተማ


👉🏝 ➴➴➴➴
https://t.me/AbuImranAselefy/9572

🏝 ውድ የሱና ቤተሰቦቻችን የነብያት ውርስ የሆነው የተውሒድ ዳዕዋ በሰሜን ወሎ የነብያት አደራ ተረካቢ በሆኑ መሻኢኾች እያበበና አድማሱን እያሰፋ መሆኑ ይታወቃል።

አሁን ደግሞ የፊታችን እሁድ ታህሳስ 27/04/2017 በሀሮ ከተማ የተውሒድን ችግኝ ለመትከል ቀጠሮ ተይዟል። በዚህ ልዩ የዳዕዋ ፕሮግራም ላይ ከሰሜን ወሎ መሻኢኾች በተጨማሪ ሌሎች መሻኢኾችና ኡስታዞች ይካፈላሉ።
    
👉 እነማን ካላችሁ የሚከተሉት ይገኙበታል።
1 🪑🎙 ሸይኽ ዐአብዱልሐሚድ አልለተሚ
         🛖 ከደቡብ ስልጤ ዞን
2 🪑🎙 ሸይኽ ሙባረክ ሑሰይን

         🛖 ከደቡብ ወልቂጤ ከተማ
3 🪑🎙ሸይኽ ሙሐመድ ጀማል
         🏢 ከኮምቦልቻ ከተማ
4 🪑🎙 ሸይኽ ሙሐመድ ሐያት
       🏠 ከሰሜን ወሎ ሓራ ከተማ
5 🪑🎙 ሸይክ ሑሰይን ከረም
       🏠 ከሰሜን ወሎ ሓራ ከተማ
6 🪑🎙 ሸይኽ ኢስማኢል ዘይኑ
        🏡 ከደቡብ ወሎ ተንታ ከተማ
7 🪑🎙 ሸይኽ ሑሰይን ዐባስ 
         🏠 ከሰሜን ወሎ ወርቄ
8 🪑🎙 ሸይኽ ሙሐመድ ሲራጅ
          🏡 ከሰሜን ወሎ ሃሮ
9 🪑🎙 ሸይኽ ሰዒድ ሙሐመድ
         🏘 ከሰሜን ወሎ ሓራ ከተማ
10 🪑🎙 ኡስታዝ  ሙሐመድ ኑር
         🏢 ከኮምቦልቻ ከተማ
11 🪑🎙 ኡስታዝ ባሕሩ ተካ
          🏫 ከአዲስ አበባ ከተማ
12 🪑🎙 ኡስታዝ አቡበክር ዩሱፍ
         🏞 ከባሕር ዳር ከተማ
13 🪑🎙 ኡስታዝ ዐብዱራሕማን

         🏘 ከሰሜን ወሎ መርሳ ከተማ
14 🪑🎙 ኡስታዝ ኸድር ሐሰን
        🏢 ከወሎ ኮምቦልቻ ከተማ
15 🪑🎙 ኡስታዝ ኑር አዲስ
         🏘 ከሰሜን ወሎ መርሳ ከተማ
16 🪑🎙 ኡስታዝ ሙሐመድ ሰልማን
         🏘 ከሰሜን ወሎ ሓራ ከተማ
17🪑🎙ኡስታዝ ሙሐመድ አሚን
     🏣 ከይፋት ምድር ሸዋሮቢት ከተማ

🏖 በዚህ ፕሮግራም ላይ የሃሮ አልፉርቃን መስጂድን ለማቋቋሚያ የሚሆን ተጨማሪ ፕሮግራም ይኖራል። በመሆኑም የሱና ቤተሰቦች በተዘጋጀው ፕሮግራም ላይ በመሳተፍ  አሻራችሁን አኑሩ ይላል ጀማዓው።

ለሴቶች በቂ ቦታ ተዘጋጅቷል እንዳታስቡ።

አላህ ካለ ፕሮግራሙ የሚጀመረው
    ከጠዋቱ  2 : 30 ይሆናል።
    

🚥 የእሁድ ፕሮግራማችን ከነቤተሰባችን ሃሮ ፉርቃን መስጂድ እናድርግ

♻️ ለበለጠ መረጃ፦
📞☎️  ስልክ ቁጥር 
      📲 +251920474161
      📲 +251929732296
      📲 +251935212614

🎞 t.me/heroselefi

▵▮▱▰▱▰▱▰▱▰▱▰▯▴
📝 أَبُـــو عِـمْــرَان ❨𝕒𝕓𝕦 𝕚𝕞𝕣𝕒𝕟❩

🏝 ••⇣⇣.  🏖   ••⇣⇣ 
╰𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞.   ╰𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞

🖥️ በ 𝐓𝐞𝐥𝐞𝐠𝐫𝐚𝐦~𝐂𝐡𝐚𝐧𝐧𝐞𝐥
🏝 ⇣⇣⇣🍭⇣⇣⇣📲 ⇣⇣⇣↙️
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

04 Jan, 12:13


🔷  ተውሒድና ሱና ሐራ ላይ

ለትውስታ

   ውድና የተከበራችሁ ወንድምና እህቶች ሐራ ማለት በአማራ ክልል በሰሜን ወሎ ከወልዲያ 24 ኪሎ ሜትር ርቃ የምትገኝ ከተማ ናት ። እቺ ከተማ በሰሜኑ ክፍል ከእስልምና የሚያወጣ ሽርክ በሚከናወንባቸው ቦታዎች የተከበበች ነች ። ከእነዚህ ውስጥ ዳናና ከረም በዋነኝነት ይጠቀሳሉ ። እንደሚታወቀው በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ያሉ የቀብር አምልኮ ቦታዎች ሰዎች ከየቦታው ሲተሙና በቀብር ዙሪያ ሲርመሰመሱ ማየት የተለመደ ነው ። ወደ ዳናና ከረምም ይኸው ነበር እየሆነ የነበረው ። ብዙ ሰዎች ( ሙስሊሞች ) ችግራቸውንን ፣ መከራቸውን ፣ ማጣታቸውን ፣ መሀን መሆናቸውን ( ዘር ማጣታቸውን )  ፣ ድህነታቸውን ፣ ከጠላት የሚደርስባቸውን ግፍና በደላቸውን ለመንገርና መፍትሄ ፍለጋ እየመጡ ፍፁም በሆነ መተናነስና ራስን ዝቅ በማድረግ ችግራቸውን ዘርዝረው መፍትሄ ካገኘን ይህን እናደርጋለን በሚል የተለያየ ስለት አድርገው መፍትሄ አገኘን እያሉ ከአላህ ውጪ ላለ አካል እየተንበረከኩ ፣ እየሰገዱ ፣  እየዳሁ እየሄዱ ስለታቸውን የሚያደርሱባቸው ቦታዎች ናቸው ። 
     ያሻውን ሰሪ ብቻውን ቀሪ የሆነው አላህ ይህን ታሪክ ቀይሮ የተውሒድና የሱና ባልተቤቶች ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ተውሒድና ሱናን ፍለጋ ወደ ሐራ እንዲተሙና በመስጂድ አስሰፋ ዙሪያ እንዲርመሰመሱ አድርጓል ። ወደ ዳናና ከረም መውሊድ ሲሄዱ የነበሩ ግመልና በጎች ወደ ተውሒድ ጥሪ ማእከል ወደ ሰፋ መስጂድ እንዲነዱ አድርጓል !!!!!። ሐራ ከየቦታወ በተመሙ የተውሒድ ሰራዊቶች ትንፋሽ አጥሯት ተጨናንቃለች ። ከሰፋ መስጂድ በሚወጣው የተውሒድና ሱና መአዛ አካባቢዋ ታውዶ ይገኛል ። የሰፋ መስጂድ ስፋት በተራ ጊዜ መጥቶ ላየው ማን ሊሰግድበት ነው በዚህ መልኩ ተዘርጥጦ የተሰራው ያስኛል ። አንድ ጥግ ቁጭ ያለ ሰው ሌላኛው ጥግ ላይ ያለው ማን እንደሆነ መለየት አይችልም ። ከመሆኑም ጋር አሁን ግን እግር ማስቀመጫ በማይገኝበት ሁኔታ በተውሒድና ሱና ናፋቂ ሰለፍዮች ተጨናንቋል ። የመስጂዱ ጊቢ ስፋት አንድ ቀበሌ ነው እንዴ ያሰኛል ። በከተማዋ መሀል ዋና መንገድ ላይ ነው የሚገኘው ።
     የሐራ መስጂድ አሁን ያለበት ሁኔታ ይህን ሲመስል  ከተወሰኑ አመታት በፊት ድቤ የሚደለቅበት ፣ ወንድና ሴት ተቀላቅሎ የሚጨፍርበት ፣ በጋጃ አድሩስ አየተጨሰ ጫት የሚቃምበት ፣ መውሊድ የሚከበርበት መስጂድ ነበር ። ይህን ያደርጉ የነበሩት የዳና ሙሪዶች ነበሩ ። መስጂዱን ያሰራው አንድ ወደ ሱና የቀረበ ሰው እንደበርና ሰርቶ ሲጨርስ ወሀብይ ነህ ተብሎ ወደ አካባቢው እንዳይደርስ እንደ ተደረገ ነው የሰማነው ። የሚያሳዝነው አሁን በህይወት የሌለና ይህን የአላህ ተአምር አለማየቱ ነው ። አላህ ይዘንለት አላህ የጀነት ያድርገው ። መስጂዱ ከዛ የሽርክና የቢዳዓ ማእበል ወጥቶ ወደ ተውሒድ እንዲቀየር ሰበብ የሆኑት ከአላህ ቶፊቅ በኋላ ሸይኻችን ሸይኽ ሙሐመድ ሐያት ናቸው ። የአካባቢው ወጣት ከሳቸው ጎን ቆመው መሳሪያ ተማዞ ነው ወደ ተውሒድ መስጂድነት የተቀየረው ።  አላህ እሳቸውንም እኛንም በተውሒድና ሱና ላይ ፀንተን ኖረን በዛ ላይ ሞተን በዛ ላይ የምንቀሰቀስ ያድርገን ።
     ይህ ካለው ሁኔታ አንፃር በጣም ጥቂት ማሳያ ነው ። አላህ ይህን ሳያሳየኝ ስላልገደለኝ ለሱ የሚገባ ምስጋና ይገባው እላለሁ ።
የጌታውን ምህረት ከጃይ ደካማ ባሪያው ወንድማችሁ ባህሩ ተካ ።

     https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

31 Dec, 14:01


👉  ልዩ ቆይታ

    ለሱና ቤተሰቦቻችን በሙሉ ዛሬ ታሕሳስ 22/04/2017 በኢስላም ብርሃን የእውቀት ማእድ ከሸይኻች ሸይኽ ዐ/ሐሚድ ጋር የኦን ላየን ልዩ የሙሓደራ ፕሮግራም የሚኖረን መሆኑን ስናበስራችሁ ከታላቅ ደስታ ጋር ነው ።

   ርእስ : የሊንና ሺዳ ለሰለፍያ ዳዕዋ
             አስፈላጊነት የሚል ይሆናል ።
             አላህ ካለ መቼና በነማን ላይ ስራ ላይ መዋል እንዳለባቸው በሰፊው ይዘረዘራል ።

https://t.me/YeIslam_brhan_ye_ewket_maed

Abu hatim Abduselam Assalefiy

29 Dec, 16:03


👉 ሀገሪቷን ማን በየትኛ ህግ ነው የሚያስተዳድራት ?

ሀገራችን ኢትዮዽያ የምትመራበት ህገመንግስት አንቀፅ 27 የዜጎች የእምነት ነፃነትን ያውጃል ። የዜጎች ሲባል እየአንዳንዱ ዜጋ ማለት ነው ። ይህ ማለት አንድ ሰው የፈለገውን እምነት የመቀበል ፣ እምነቱ የሚያዘውን ነገር የመተገብር መብቱ ማንም ሊነጥቀው የማይችል ወይም በማንም መልካም ፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ አለመሆኑና ይልቁንም የዜግነት መብቱ መሆኑን ነው የሚያሳየው ።
በሀገራችን በየትኛውም ደረጃ ያሉ ክልሎችም ይሁን ዞንና ወረዳዎች በዚህ ህገመንግስት ስር ሆነው ነው ክልላቸውን ወይም ዞንና ወረዳቸውን ማስተዳደር ያለባቸው ። ከላይ ያየነው አንቀፅ የአንድን ግለሰብ መብት የሚያስጠብቅ ከሆነ በሺዮች ወይም በመቶ ሺዮች የሚቆጠሩ ዜጎች ሲሆኑ ደግሞ ምን ሊሆን እንደሚችል ግልፅ ነው ። ማንም ተነስቶ የግለሰብን እንኳን ህገመንግስታው መብት የሚጥስ መመሪያ ማውጥት የማይችል ከሆነ የህዝቦችን መብት የሚጥስ መመሪያ ማውጣት አለመቻሉ ከበጋ ፀሀይ የበለጠ ግልፅ ነው ማለት ነው ።
የህገ መንግስቱ መመሪያ ይህ ከሆነና መንግስት የሚሰራው በዚህ ከሆነ በምን ሒሳብ ነው ይህን የህዝቦች መብት ያረጋግጣል የተባለውን መመሪያ አሻፈኝ ብሎ ይህን የሚፃረር መመሪያ ስራ ላይ በማዋል የዜጎች መብት የሚረገጠው ?
በአሁኑ ጊዜ ሀገራችን ላይ በተለያዩ ክልሎች በግልፅ ይህን ህገመንግስታዊ የዜጎች መብት በጣሰ መልኩ የራሳቸው ህግ በማርቀቅ መብት የሚረግጡ መኖራቸው የአደባባይ ሚስጢር እየሆነ ነው ። ለመሆኑ እነዚህ አካላት ህገ መንግስቱ እኛን አይወክልም የራሳችን ህገመንግስት አለን ባዮች ናቸው ወይስ ከህገ መንግስቱ ውስጥ ለኛ የሚስማማውን ወስደን የማይስማማውን እንተወዋለን ማን ምን አገባው ባዮች ናቸው ? ወይስ ጠያቂ የለም ነው ነገሩ ። ለማንኛውም እንዲህ አይነት ፅንፈኝነት ለማንም አይጠቅምም ።
የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ማንኛውም ተማሪ ሀይማኖትን የሚያንፀባርቅ ነገር ማድረግ የለበትም በሚል ሙስሊም ሴት ተማሪዮችን ሒጃብ ለብሰው ወደ ትምህርት ቤት እዳይገቡ መከልከሉ ጉድ ሳይሰማ መስከረም አይጠባም እንደሚሉት ነው ። ለመሆኑ እነዚህ አካላት አንገታቸው ላይ ክር አስረው ክርስቲያን መሆናቸውን የሚገልፅ ነገር ያደረጉትንም ጭምር ነው ያባረሩት ወይስ የሙስሊሞችን እስልምና የሚገልፅ ነገር ነው ወንጀል የሆነው ? ለመሆኑ በትግራይ ክልል እንደ አፄዎቹ ዘመን የሙስሊም ኮፍያ መልበስም ወንጀል ነው ? በአክሱም ከተማ እስልምናን የሚገልፅ ነገር እንደ ኮፍያ ፣ ሒጃብ ፣ ጅልባብና የመሳሰሉ መገለጫዎችን የሚያደርጉ ሙስሊሞች አይደለም በሴክተር መስሪያ ቤት ሊሰሩ ለጉዳይም መግባት አይችሉም ሊሉ የሚፈልጉ ይመስላል ።
የሚገርመው በሒጃብ ዙሪያ እንደሀገር ሙስሊም ሴት ተማሪዮች ከዩኒፎርም ጋር የሚመሳሰል ሒጃብ ለብሰው መማር የሚችሉ መሆኑን የሚገልፅ መመሪያ እንደ ኢትዮዽያ አቆጣጠር በ2000 ወጥቶ በስራ ላይ የዋለ መመሪያ አለ ። ይህ ከህገመንግስቱ የፈለገችውን የመልበስ መብት ማረጋገጥ በተጨማሪ ማለት ነው ። ታዲያ የአክሱም ከተማ ፅንፈኞች ለየትኛው ህግ ይሆን የሚገዙት ? ወይስ የኋሊዮሽ ተመልሰው የአፄዎቹ ዲስኩር መንዛት ነው የተያያዙት ?
በአሁኑ ጊዜ የዜጎች መብት መረገጥ በሌሎችም የእምነት ተቋማትም እየታየ ነው ። ከላይ የተጠቀሰውን አንቀፅና እንዲሁም ማንኛውም ዜጋ ለህጋዊ አላማ የመደራጀት መብቱ የተጠበቀ ነው የሚለውን የህገ መንግስቱ አንቀፅ 32 እንዲሁም መጅሊሱ በአዋጅ ሲፀድቅ ከዚህ በፊት የተቋቋሙ ወይም የተደራጁ ማህበራትን መከልከል አይችልም የሚለውን አዋጅ በመፃረር የአሁኑ የመጅሊስ አመራሮች በቁርኣንና ሀዲስ ሳይሆን በራሳቸው ልብ ወለድ የሚመሩት መጅሊስ ስር ያልሆነን ዜጋ አይደለም እስከ ማለት ደርሰዋል ። እነዚህን ከላይ የተገለፁ የዜጎችን መብት የሚረግጡ መመሪያዎችን የሚቃረን መመሪያ በማውጣት ይህን ተቀብሎ ተግባራዊ የማያደርግ በዚህች ሀገር መኖር አይችልም ሀገሩን ይፈልግ እስከማለት ደርሰዋል ።
ይህ ነው ይህች ሀገር ማን በየትኛው ህግ ነው የሚያስተዳድራት የሚል ጥያቄ የሚያስነሳው ። ዜጎች በጣም በሚገርም ተስፋ የጠበቁት ብልፅግና እንደነዚህ አይነት ተግዳሮቶችን በመዋጋት ወረቅት ላይ ያሉትን ፍትህ የናፈቃቸው ቃላት መሬት ላይ ወርደው ስራ ላይ እንዲውሉ ማድረግ የመጀመሪያ ተግባሩ ሊሆን ይገባል እላለሁ ።

ፍትህ ለአክሱም ሙስሊም ሴት ተማሪዮች ።

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

28 Dec, 17:14


Live stream finished (1 hour)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

28 Dec, 16:08


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

28 Dec, 16:08


ሳምንተዊ የቁሪኣን ተፍስር ልጀምር ነዉ
ገባ
       ገባ
                በሉ
https://t.me/abuhatimaselefiy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

27 Dec, 17:29


Live stream finished (59 minutes)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

27 Dec, 16:29


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

27 Dec, 16:02


ሳምንተዊ የቁሪኣን ተፍስር ልጀምር ነዉ
ገባ
       ገባ
                በሉ
https://t.me/abuhatimaselefiy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

26 Dec, 19:36


🔊📢 ዳዕዋ ዳዕዋ ዳዕዋ ‼️

ታላቅ የዳዕዋ ጅሃድ በተለያዩ በገጠር በከተማ ቀበሌዎችና ወረዳዎች ላይ እየተስፋፋ በመቀጠሉ ምክኒያት ተውሃድና ሱና በየቤቱ እየገባ ደጃፍ እየቆረቆረ ይገኛል

📡 ስለሆነም የፊታችን ሰኞ ታህሳስ ቀን /21/4/2017//ቀበሌ/022/ወሬጉ ጎደ በምትባል መንደር ጥሪው ይዘልቃል

🌎  በሰሜን ወሎ ዞን በሃብሩ ወረዳ ቀበሌ /022/  ከቦፋና   ከጉባ መካከል የምትገኝ ወሬጉ ጎደ የምትባል መንደር ስትሆን ኑና በአይነቱ ለየት ያለ የዳዕዋ ዝግጅትና ፕሮግራም ተደግሷል በተባለው ቦታና ቀን በመገኘት የዳዕዋው ተካፋይና ተቋዳሽ ይሁኑ ኑኑኑ

✳️ በቦታው ላይ በቂ የሴቶችም ቦታ ስለተመቻቸ ማንን ይዞ ጉዞ ነውና ነገሩ የቅርብ ወዳጅ ዘመዳችሁን ሚስቶቻችነን ይዘን እንምጣ በቦታው ላይ እንገናኝ

🪑 የእለቱ ተጋባዥ እንግዶቻችነን  እነሆ ብለናል ዕርሱ በቦታውላይ ይነገራል

➢1.🎙ሸይኽ ሙሐመድ ሃያት ከሃራ
➢2.🎙ሸይኽ ሙሐመድ ሲራጅ ከሃሮ
➢3.🎙ሸይኽ ሁሴን ከረም       ከሃራ
➢4.🎙ሸይኽ ሰይድ ሙሐመድ  ከሃራ
➢5.🎙ኡስታዝ ሙሐመድ ሰልማን ከሃራ
➢6.🎙ኡስታዝ አብዱረህማን  ከመርሳ
➢7.🎙ኡስታዝ ኑራድስ           ከመርሳ
[አላህ ሁላቸውንም ከክፉ ነገር ይጠብቃቸውና ]ተዘጋጅተው የሚጠብቋችሁ መሆናቸውን ስናበስራችሁ በታላቅ ደስታ ነው

➲እነዚህና ሌሎችም በበቦታው ላይ ተጋባዥ እንግዶች ስለሚኖሩን ያስታውሱ እንዳይረሱ

🌐 ውድና የተከበራችሁ የወሬጉ ጎደና የአካባቢው ኗሪዎች ሆይ ተገኙ በውጭም በሃገር ውስጥም ያላችሁ ይሄ የተባረከ መልዕክትና ጥሪ የደረሳችሁ ሁሉ ችላ እንዳትል ወዳጅ ዘመዶቻችነን በመንገር ጥሪውን እናሰማቸውና እኛም ተጠቅመን እነሱንም እንጥቀም ስልክ በመደዎል ጥሪውን በማድረስ ላይ እንተባበር የዳዕዋ ጀሃድ ለሙስሊሙ ኡማ ጥሪውን እናሰማ አዋጅ ይድረስ

አዘጋጅና ደጋሽ ጠሪ ዋና አስተናባሪ
የወሬጉ ጎደ ሰለፍዮች ናቸው ።

🗓 ታህሳስ ቀን/21/4/2017/እለተ/ሰኞ

https://t.me/hussenhas

Abu hatim Abduselam Assalefiy

25 Dec, 06:56


ኢብኑ ሙነወር በራሱ ብዕር የሚከተሉትን መስክሯል፦
👉 ኢብኑ ሙነውር ድንበር አላፊ መሆኑን
👉 ኢብኑ ሙነውር አስቀያሚ ባህሪ እንዳለው
👉 ኢብኑ ሙነውር ነውረኛ ግለሰብ መሆኑን በአግባቡ ተናግሯል።

ምክንያቱም ሰሞኑን ሸይኽ አብዱልሐሚድ ባስተካከሉት ነጥብ «ብየም ከሆነ ተመልሻለሁ» ባሉበት ነጥብ መነሻ አድርጎ “ወፈፌ” እያለ የአደበ-ቢስ ወይም ስርዓት-አልባ ሰው ገለፃ አስቀምጧል። ስለዚህ ራሱ እንዳለው «ድንበር አላፊ መሆኑን፣ አስቀያሚ ባህሪ እንዳለው፣ ነውረኛ ግለሰብ እንደሆነ አረጋግጠናል።

بَلِ الْإِنسَانُ عَلَىٰ نَفْسِهِ بَصِيرَةٌ
በእርግጥም ሰው በነፍሱ ላይ አስረጅ ነው፡፡
[አል-ቂያማህ - 14]

የሚነሳ ማምታቻ፦
👉 ምናልባት ሸይኽ አብዱልሐሚድ የሰጡት ማስተካከያ ሳይደርሰው ቢሆንስ? የሚል ሀሳብ ከተነሳ የሚከተሉትን እላለሁ፦
❶ኛ በኔ ግምት ይደርሰዋል ብዬ አምናለሁ። ምክንያቱም ከማንም በላይ ለሚዲያ Active ነውና። በተጨማሪም ይህንኑ ተግባር ከዚህ በፊት ፈፅሞ ሰዎችን እንዲጠሉ ለማድረግ ተጠቀመበት እንጂ ማስተካከያ አላደረገም። ስለዚህ የሸይኽ አብዱልሐሚድ ማብራሪያ ያልደረሳቸውን ሰዎች ሸይኹን እንዲጠሉ ማድረግ ዋና ፍላጎቱ ነው።

ኢብኑ ሙነወርና ግብረአበሮቹ ከዚህ በፊት ልክ የአሁኑን አምሳያ ማጭበርበሪያ ሲያሰራጩ አላህን ፍሩ በተመለሱበት አትውቀሱ ብለናቸው ነበር ግን ግፋቸውን አላስተካከሉም።
ተመልከቱ ➴➴➴➴
https://t.me/AbuImranAselefy/8723

ሌላኛውን እዩት ➴➴➴
https://t.me/AbuImranAselefy/7993

👌 ስለዚህ ሰዎቹ እንደምንም ተፍጨርጭረው የመረጃ እጥረት ያለባቸውን ሰዎች ማታለል ዋና አላማቸው ነው።

❷ ሸይኹ ያስተካከሉበት ካልደረሳቸው ይሄው ልከንላቸዋልና ያስተካክላሉ። ካልሆነ ግን እንዳሉትም ነውረኞች ናቸው!

Abu hatim Abduselam Assalefiy

24 Dec, 14:10


🔷  የዶክተር ጀይላን ጓደኛ

የመካ ሐረም ገጠመኜ ትውስታ

      ዛሬ ጀማደ ሳኒ 21/1444 በተከረው ከተማ መካ ሐረም ላይ ከዐስር ሶላት በኋላ አንድ ከጎኔ የሰገደ እድሜው 70ዎቹ አካባቢ የሆነ ፂሙ ነጭ ሆኖ በጣም ደስ የሚል ዐረብ ስሙ ኩንያው አቡ አሕመድ ስሙ ሙሐመድ የሆነ ስው ሞቅ ባለ ፈገግታ ሰላም አለኝ ። እኔም በተመሳሳይ መለስኩለት ።
    ቀጥሎ ከየት ሀገር ነህ አለኝ ከኢትዮዽያ አልኩት ። ከመጀመሪያው በበለጠ ፈገግታ ከዋና ከተማው ወይስ ከገጠሩ አለኝ እኔም ገጠር ተወልጄ ከተማ ነው ያደኩት አልኩት ። ቀጠለና ከየትኛው አቅጣጫ አለኝ ከደቡብ አልኩት ።
     ወሬው ሞቅ ብሎ ቀጠለ ደቡብን አላውቀውም ወራቤን ነው የማውቀው አለኝ ።  እኔም ወራቤ እኮ በደቡብ ነው ያለው አልኩት ። ጊዜ ማጥፋት የፈለገ አይመስልም ዶክትር ጀይላንን ታውቀዋለህ ወይ አለኝ ። እኔም በማወቅ ደረጃ አውቀዋለሁ ግን እቃረነዋለሁ አልኩት ። ያ ፈገግታ ደመና ወረሰው ።
   ለምን አለኝ ከአሕባሽና ሱፍይ ጋር ስለተደመረ አልኩት ። በቃ አታውቀውም ማለት ነው ። እሱ እኮ የሐበሻ ሙፍቲ ነው አለኝ ። ደግሞም ከጃሚዓ ተመርቋል አለኝ ። እኔም ያውም በዶክተርነት ከዐቂዳ ፋካሊቲ ነው አልኩት ።
     ቀጠለና አንተ ማንን ነው የምትከተለው አለኝ ? እኔም ሰለፎችን ነው አልኩት ። በጣም በሚገርም መልኩ የሰለፎች መዝሀብ ማን ነው የደነገገው አለኝ ? ሰለፎች የራሳቸው መመሪያ የላቸውም መመሪያቸው ቁርኣንና ሐዲስ ነው አልኩት ። በሙሉ ድፍረት አይደለም እናንተ ሰለፎችን ሙሸሪዕ አድረጋችኋል በዚህም ሙሽሪኮች ናችሁ አለኝ ።
      እኔም ልቆጣጠረው የማልችለው ስሜት እየታገለኝ እንደምንም ራሴን ተቆጣጥሬ ያንተ መዝሀብ ምንድነው አልኩት ።
   በቀላሉ የኢኽዋነል ሙስሊሚን መዝሀብ ነው አለኝ ።  ከዛ ቀጠለና አላህ ሙስሊሞች ብሎ ጠርቶናል ብሎ የቁርኣን አንቀፆችን ደረደረ ። እኔም በዐለም ላይ ያሉ ሙስሊሞች ሁሉ እስልምናቸው አንድ አይነት ነው ወይ አልኩት ? እሱም በሙሉ ድፍረት አው አለኝ ።
   እሺ አሁን እዚህ ካዕባ ጋር ሆነው ከአላህ ውጪ ሙታኖችን የሚጠሩ አሉ የእነርሱ እስልምናና ያንተ እስልምና አንድ አይነት ነው ወይ አልኩት ? እሱም አይ የእነሱ ሽርክ ነው አለኝ ። ካፊሮች ናቸው ወይስ ሙስሊሞች ናቸው አልኩት ? እሱም እኔ ማንንም አላከፍርም አለኝ ። እሺ ሙስሊሞች ናቸው ማለት ነዋ አልኩት ። አው ጃሂሎች ናቸው እናስተምራቸዋለን አለኝ ።
   በጣም ቆንጆ የጥያቄዬን መልስ ስጠኝ ያንተ እስልምናና የእነርሱ እስልምና አንድ ነው ወይ አልኩት ? ግግም ብሎ አላህ ሙስሊሞች ብሎናል አለኝ ። አው ግን ምን አይነት ሙስሊም አልኩት ? ይህ የናንተ ቢዳዓ ነው አላህ የዚህ አይነት የዚህ አይነት አላለም አለኝ ።
   እኔም የኛ ቢዳዓ አይደለም የአላህ ትእዛዝ ነው ምክንያቱም አላህና መልእክተኛው እኛን የሙሀጂሮችንና የአንሷሮችን መንገድ እንድንከተል አዘውናል ብየው የሚከተለውን የቁርኣንና ሐዲስ መረጃ አመጣሁለት : –

وَالسَّابِقُونَ الْأَوَّلُونَ مِنَ الْمُهَاجِرِينَ وَالْأَنصَارِ وَالَّذِينَ اتَّبَعُوهُم بِإِحْسَانٍ رَّضِيَ اللَّهُ عَنْهُمْ وَرَضُوا عَنْهُ وَأَعَدَّ لَهُمْ جَنَّاتٍ تَجْرِي تَحْتَهَا الْأَنْهَارُ خَالِدِينَ فِيهَا أَبَدًا ۚ ذَٰلِكَ الْفَوْزُ الْعَظِيمُ
                         التوبة (  100)
" ከስደተኞቹና ከረዳቶቹም ሲኾኑ የመጀመሪያዎቹ ቀዳሚዎች እነዚያም በበጎ ሥራ የተከተሏቸው አላህ ከእነሱ ወዷል ከእርሱም ወደዋል ፡፡ በሥሮቻቸውም ወንዞች የሚፈሱባቸውን ገነቶች በውስጣቸው ዘለዓለም ነዋሪዎች ሲኾኑ ለእነርሱ አዘጋጅቶላቸዋል ፡፡ ይህ ታላቅ ዕድል ነው "፡፡

« وَمَن يُشَاقِقِ الرَّسُولَ مِن بَعْدِ مَا تَبَيَّنَ لَهُ الْهُدَىٰ وَيَتَّبِعْ غَيْرَ سَبِيلِ الْمُؤْمِنِينَ نُوَلِّهِ مَا تَوَلَّىٰ وَنُصْلِهِ جَهَنَّمَ ۖ وَسَاءَتْ مَصِيرًا »

النساء ( 115 )

" ቅኑም መንገድ ለእርሱ ከተገለጸ በኋላ መልክተኛውን የሚጨቃጨቅና ከምእምኖቹ መንገድ ሌላ የኾነን የሚከተል ሰው (በዚህ ዓለም) በተሾመበት (ጥመት) ላይ እንሾመዋለን ፤ ገሀነምንም እናገባዋለን ፡፡ መመለሻይቱም ከፋች ! "
ከምእምኖች መንገድ ሌላ የተባለው ከሶሓቦች መንገድ ሌላ ለማለት ነው የነኛ ሰለፎች ሶሓቦች ናቸው ። የዶክተር ጓደኛ ግን ሰለፉ ሐሰነል በና ነው ።!!!
ሌላኛው እነ አቡበከርና ዑመርን መከተል ግዴታ መሆኑ ከሚያመላክቱ ሐዲሶች ውስጥ የሚከተለውን አንድ ሐዲስ ማየት በቂ ነው : –

عن العرباض بن سارية رضي الله عنه،
قال: صلى بنا رسول الله – صلى الله عليه وسلم–
" الصبح ذات يوم، ثم أقبل علينا، فوعظنا موعظة بليغة، ذرفت منها العيون، ووجلت منها القلوب، فقال قائل: يا رسول الله، كأن هذه موعظة مودع، فأوصنا،
فقال :
«أُوصِيكُمْ بِتَقْوَى اللَّهِ، وَالسَّمْعِ وَالطَّاعَةِ، وَإِنْ كَانَ عَبْدًا حَبَشِيًّا، فَإِنَّهُ مَنْ يَعِشْ مِنْكُمْ بَعْدِي فَسَيَرَى اخْتِلَافًا كَثِيرًا، فَعَلَيْكُمْ بِسُنَّتِي وَسُنَّةِ الْخُلَفَاءِ الرَّاشِدِينَ الْمَهْدِيِّينَ، تَمَسَّكُوا بِهَا، وَعَضُّوا عَلَيْهَا بِالنَّوَاجِذِ، وَإِيَّاكُمْ وَمُحْدَثَاتِ الْأُمُورِ، فَإِنَّ كُلَّ مُحْدَثَةٍ بِدْعَةٌ، وَكُلَّ بِدْعَةٍ ضَلَالَةٌ».

أخرجه الإمام أحمد وأبو داود وغيرهما

    ቀጥዬ የነብዩ ሱና ትክክለኛ እስልምና መሆኑን ታምናለህ ወይ አልኩት? አው አለኝ ። የኹለፋዎቹስ አልኩት ?  ይህ የናንተ ተፍሲር ነው የሰለፎች መዝሀብ እሱ አይደለም አለኝ ።
    ሰለፍ ማለት ምን ማለት ነው አልኩት ሊመልስልኝ ፈቃደኛ አልነበረም ። በጣም በሚያስጠላ መልኩ እናንተ ሰለፎችን ነው የምትገዙት በአላህ ዲን ላይ ደንጋጊ አደረጋችኋቸው አለኝ ።
     እኔም አንተ የምትፈልገው ሙስሊሞችን ከአቡበከር ፣ ዑመር ፣ ዑስማንና ዐልይ ረዲየላሁ ዐንሁም  መንገድ አውጥተህ ወደ ሐሰነል በናና ሰይድ ቁጥብ ፍልስፍና ማስገባት ነው ብዬው ተለያየን ።
    ይህ ነው የዶክተር ጀይላን ጓደኛና ኢትዮዽያ ላይ ያሉ ሙስሊሞች ዶክተር ጀይላንን እንዲከተሉ የሚጣራው ጉደኛ
      አላህ ሐቅን አውቀን የምንከተለውና ባጢልን አውቀን የምንርቀው ያድርገን ።

ከተወሰነ ጭማሪ ጋር በድጋሚ የተለቀቀ ።

 https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

23 Dec, 08:13


ተለቀቀ‼️

📌📚📖አዲስ መፅሐፍ 📖📚📌

"አል ኢርሻድ - ወደ ትክክለኛ እምነት መምራትና በማጋራትና በጥመት ባለቤቶች ላይ ምላሽ መስጠት"


الإرشاد إلى صحيح الإعتقاد والرد على أهل الشرك والإلحاد

በሸይኽ ዶክተር/ሷሊሕ ብን አል'ፈውዛን ሐፊዞሁሏህ ተዘጋጅቶ

በአቡ ዓብዲልዓዚዝ/ዩሱፍ አሕመድ ሐፊዞሁሏህ ወደ አማርኛ የተመለሰ

በዚሁ ቻናል በPDF ተዘጋጅቶ ለአንባቢያን የሚተላለፍ ይሆናል ተብሎ ቃል በተገባው መሰረት እነሆ የአላህ ፈቃድ ሆኖ ለአንባቢያን ቀርቧል‼️

ሼር በማድረግ የአጅሩ ተካፋይ እንሁን‼️
አላህ አንብበው ከሚጠቀሙት ያድርገን‼️
የባህር ዳር አህለሱና መሻይኾች ገፅ

كن على بصيرة

https://t.me/alateriqilhaq

Abu hatim Abduselam Assalefiy

21 Dec, 17:23


Live stream finished (1 hour)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

21 Dec, 15:46


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

21 Dec, 15:33


ሳምንተዊ የቁሪኣን ተፍስር ልጀምር ነዉ
ገባ
       ገባ
                በሉ
https://t.me/abuhatimaselefiy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

20 Dec, 17:21


Live stream finished (1 hour)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

20 Dec, 15:50


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

20 Dec, 15:45


ሳምንተዊ የቁሪኣን ተፍስር ልጀምር ነዉ
ገባ
       ገባ
                በሉ
https://t.me/abuhatimaselefiy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

20 Dec, 13:53


👉 የከሰሩ ነሲሓዎች ክስረት

አል ሂዳያ በሚል በጉራጌ ዞን የሚንቀሳቀሱት የድሮዎቹ ሙመዪዓዎች የአሁኖቹ ኢኽዋኖች ባለፈው ሳምንት ጉንችሬ ማዞሪያ ዑመር መስጂድ ላይ ነጭ ነጩን እንቅጭ እንቅጩን በማስቀመጥ የተደረገው ዳዕዋ የቁም ቅዠት ውስጥ ከቷቸው እነሞር ላይ ዳዕዋ ብሎ ማስተዋወቅ በኪሳራ ላይ ኪሳራ እየጨመረብን እንጂ እየጠቀመን አይደለም ። ስለዚህ ወጣት ሽማግሌ አዛውንት ጎልማሳው እንዲሁም ወንድና ሴቱንም የምናገኘው በጁሙዓ ስለሆነ ለዘብተኛ ዳዒዮችን እየጋበዝን ህዝቡን መያዝ እንችላለን የሚል እስትራቴጂ ነድፈው ይህንንም በዛሬው ጁሙዓ ተግባራዊ አድርገውታል ። ዳዒዮቻቸው እነባሕሩ የማለት ሞራሉ ስለሌላቸው የሙስሊሞቹን አንድነት የሚበታትኑ ሰዎች አሉ ተጠንቀቁ በሚል ተሕዚር መለማመድ ጀምረዋል ።
ለነሲሓዎችና ሙሪዶቻቸው እንዲሁም ዱዓቶቻቸው ማለት የምንፈልገው ድሮም በሐቅ ሰዎች ላይ ተሕዚር ተለማመዱና ከባጢል ሰዎች ለማድረግ መግቢያ ይሆናችኋል ብለናል ። ነገር ግን አሁንም ማረጋገጥ የምንፈልገው አው እኛ በቀብር አምላኪና አላህን በሚያመልክ መካከል አንድነት የለም ነው የምንለው ።
አንድ ለመሆን ቀብር አምላኪ ሆኖ በሽርክ ወይም አላህን አምላኪ ሆኖ በተውሒድ ነው መሆን የሚቻለው እንላለን ። ቀብር አምላኪና አላህን አምላኪ አንድ ማድረግ ከባድ ወንጀል ነው ። ይህን አስመልክቶ አላህ በተከበረው ቃሉ እንዲህ ይላል : –

« أَفَنَجْعَلُ الْمُسْلِمِينَ كَالْمُجْرِمِينَ »
القلم ( 35 )
" ሙስሊሞቹን እንደ ከሓዲዎች እናደርጋለን ?"

« مَا لَكُمْ كَيْفَ تَحْكُمُونَ »
القلم ( 36 )
" ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ ፡፡

ሙስሊም ማለት አላህን የሚያመልክ ነው ። ቀብርን ፣ ወልይን ፣ ቀንን ፣ ቆሌን ፣ አድባርን ፣ ሸይኽን …… ወዘተ የሚያመልክ ሙስሊም አይደለም ። ስለዚህ አንድ ሊሆኑ አይችሉም ። አንድ ለማድረግ ቀብር አምላኪዮች ተውበት አድርገው ሊመለሱ ይገባል ። ቀብር ማምለክ ፣ ወልይ ማምለክ ፣ ሸይኽ ማምለክ ወይም እነዚህን አካላት እርዱኝ ፣ ድረሱልኝ ፣ አክብሩኝ ፣ አሽሩኝ ፣ ሞሽሩኝ ፣ ዘር ስጡኝ ፣ ከጭንቅ አውጡኝ ማለት ከእስልምና የሚያወጣ ሽርክ መሆኑን መንገር ይገባል እንላለን ።
አላማቸው የማንም ቁስል ሳይነካ ህዝብ መሰብሰብና በዲን መነገድ ያደረጉ ነሲሓዎች የሚልኩዋቸው ዳዒ ተብዬዎች ይህ ያሳምማቸዋል ያስቆጣቸዋል ። በዚህ መልኩ ዳዕዋ የሚያደርጉትን በታታኝ ይሉዋቸዋል ። በመሆኑም በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል ያላችሁ የሱና ሰዎች ባጠቃላይ እነሞር ላይ ያላችሁ በተለይ እነዚህን ሆድ አምላኪ ተላላኪዮች አሳፍራችሁ ልትመልሱና ኪሳራቸውን ልታስቀጥሉ ይገባል ። በቁጭታችሁ ሙቱ እንጂ የተውሒዱ ዳዕዋ ያብባል የናንተ ማንነት ለህዝቡ ይነገራል እንላቸዋለን ።

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

19 Dec, 17:51


👉 ወላጆች ልጆቻችሁን ጠብቁ

የሀገራችን ዜጎች ከምእራባዊያን ጠቃሚ ነገሮች ወስደው ራሳቸውን ቢለውጡ ጥሩ ነበር ። ነገር ግን አንዳንድ ሰርቶ መለወጥ ያቃታቸው አካላት ከምእራባዊያን ጭራቃዊ ባህርይን በመውረስ ህፃን ከወላጁ በመለየት ይህን ያክል አምጡ ካልሆ ጀናዛው ይመጣላችኋል ይላሉ ።
ለመሆኑ እነዚህ አካላት ልጅ ይኖራቸው ይሆን ? ምክንያቱም በሰፈሩት ቁና መሰፈር አይቀርምና አሁን በወላጆች ላይ እያደረሱት ያለው ሰቀቀን በእነሱም ላይ መድረሱ መጠበቅ ይኖርባቸዋል ። በጣም የሚገርመው እነዚህ አካላት ለሚሰሩት ጭራቃዊ ወንጀል ወላጆች የህግ ከለላ ፍለጋ እንዳይሞክሩ ያስጠነቅቃሉ ። ምን ማለት እንደሆነ ግራ የሚያጋባ ቢሆንም ለየትኛውም የህግ አካል ብታሳውቁ ወዲያው የት ለማን እንዳሳወቃችሁ እንነግራችኋለን ይላሉ ።
ለማንኛውም ወላጆች ጠባቂው አላህ ከመሆኑ ጋር ሰበብ ማስገኘቱ ጥሩ ነው ። አላህ ራሳችንንና ቤተሰባችንን እንዲጠብቅልን በመልካም ስራ ወደርሱ መቃረብ ይኖርብናል ። ልጆቻችን ተነጥቀን ሶስት አራት ሚሊየን ብር ሳንወድ በግዳችን ከምንከፍል ለአላህ ብለን አንድ መቶ ሺብር ብናወጣ በአላህ ጥበቃ ስር እንሆናለን ። በየቦታው ያሉ መድረሳዎችና መስጂዶች ተመልካች አጥተው ባይተዋር በሆኑበት ለዘራፊዮች በሚሊየኖች ከመክፈል ለአላህ ዲን ወጪ ብናደርግ የሁለት ሀገር ስኬት ባለቤት እንሆናለን ። ከዚህ ጎን ለጎን ልጆቻችንን ለመጠበቅ ሰበብ ማድረስ የግድ ነው ። ሙሉ አደራውን ለአላህ ከመስጠት ጋር ።
አላህ በስሞቹና ባህርያቶቹ ይሁንበት ከሰው በላ ሰው መሳዮች ይጠብቀን ።

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

19 Dec, 17:51


ኢብኑ ሙነወር የመከራችሁን ተቀበሉ!

ከ Facebook ባገኘሁት ትክክለኛ መረጃ መሰረት Dawit Ali Abuabdurahmann የተባለ ወንድም ኢብኑ ሙነወርን ኢልያስ አህመድ ስላቀረባቸው 30 ምክሮች ይጠይቀዋል። የጥያቄው አቀራረብም «ሰዎች ሰላሳ ምክሮችን ስህተት አለበት ይላሉ ግን ስህተቱ አልታየኝም እና እስኪ አብራርተህ ፃፍልን» ይለዋል
ኢብኑ ሙነወርም
❝ወንድም ሁሰይን ሙሐመድ የሰጠውን ምላሽ አንብበው❞ በማለት ወደ ሸይኽ ሁሰይን ሙሐመድ አስልጢ ረዶች ጥቆማ አደረገ

በጣም ጥሩ አዎ ሁላችሁም የሸይኽ ሁሰይንን ማብራሪያ አንብቡ በውስጣችሁ ያለው የኢልያስ ውደታ የጋረደው ሀቅን የመቀበል ፍላጎት ቦግ ይልላችኋል

አዎ ከሸይኽ ሁሰይን በኩል የተሰጡ ረዶችን አንብቡ አዳምጡ ወላሂ ከተመዩዕ ቫይረስ ለመዳን ሰበብ ሊሆናችሁ ይችላል

አዎ አዳምጡ አንብቡም። ሸይኽ ሁሰይን እያንዳንዱ ሙኻሊፍ ስለሚያመጣው ማምታቻ በቂ ምላሽ ሰጥተዋል።

በነገራችን ላይ በዛው የFacebook Comment ሳጥን ላይ የምናገኝበትን ሊንክ ስጠን እያሉ የጠየቁ ሰዎችን አይቻለሁ። ለነሱም ለሌሎችም ይጠቅም ዘንድ በሚከተለው መልኩ በየክልሉ አዘጋጀሁላችሁ።

በኢልያስ አሕመድ "30 ምክሮች ለወሰን አላፊዎች" በሚል ሙሐደራ ላይ በሸይኽ ዶክተር ሑሰይን ቢን ሙሐመድ አስሲልጢ ከዓመታት በፊት የተሰጠ ምላሽ

ክፍል ❶ ➴➴➴
https://t.me/AbuImranAselefy/7455

ክፍል ❷ ➴➴➴
https://t.me/AbuImranAselefy/7611

ክፍል ❸ ➴➴➴
https://t.me/AbuImranAselefy/7708

ክፍል ❹ ➴➴➴
https://t.me/AbuImranAselefy/7761

ክፍል ❺ ➴➴➴
https://t.me/AbuImranAselefy/8095

ክፍል ❻ ➴➴➴
https://t.me/AbuImranAselefy/8411

Abu hatim Abduselam Assalefiy

19 Dec, 17:51


🔹 ወንድሜ ኢብኑ ሽፋ ባነሳው ሐሳብ ላይ ትንሽ ለማከል የመርከዙ ሰዎች በኢብኑ መስዑድ ስም የሰበሰቡት ገንዘብ የመስራቾቹ የግል ሀብት እንጂ የሰለፍዩ ማህበረሰብ ንብረት አይደለም ። ለዚህ ማረጋገጫው ለህብረተሰቡ ለመርከዙ ነው ተብለው የተገዙ ቦታዎችም እንዲሁም መኪኖችና የባንክ አካውንቶችንም ጨምሮ በመስራቾቹ ስም ነው የሚገኙት ። አል አፊያ አከደሲዮን የያዘው ድርሻ የኢብኑ መስዑድ መርከዝ እንደሆነ ቅርበት ያላቸው ሁሉ ያውቃሉ ። ዛሬ ግን ከእነዚህ መስራቾች የግል ሀብትነት ማውጣት የሚቻልበት የህግ አግባብ ያለ አይመስለኝም ። ምክንያቱም መሪዮቹ በዚህ ጉዳይ የተካኑ ስለሆኑ ። የዛሬ 10 አመት አካባቢ ሸይኽ ዐ/ ባሲጥ በነበሩ ጊዜ ዛሬ በጉያቸው ከከተቱዋቸው ዳዒዮቻቸው ውስጥ ሁለቱ ኢብኑ መስዑድ ላይ ባነሱት ቅሬታ ፉሪ ሐጂ ሪል እስቴት አካባቢ የተወሰኑ ወንድሞች በወንድም ዙበይር ቤት ተሰብስበው የእስትራክቸር ለውጥ መደረግ አለበት ብለው ኢልያስ አሕመድን መልእክት እንዲያደርስ ልከው ቀጠሮ ተይዞ ተገናኝተን ኢልያስ አወል ለተሰብሳቢው ኢብኑ መስዑድ ማለት እኮ ንብረት ነው ለማን እንድናስረክብ ነው የምትጠይቁት ነበር ያለው ።
ይህ ማለት የዛኔ ራሱ ኢብኑ መስዑድ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር እንጂ የሰለፍዩ ማህበረሰብ አልነበረም ። ዛሬማ በዐቂዳ እንጂ በገንዘብ ከማይገናኙዋቸው ሌሎች ድርጅቶች ጋር ተደምረዋል ። ሁሉም የሰበሰበውን ይወስዳል ባይሆን አንዱ ሌላውን እንዳያሸንፍና እንዳይበልጥ ፍልሜያ ነው ያለው ።
የመርከዙ ሰዎች በተጠና መልኩ ከኢትዮዽያ 20 ባሀብቶች ተርታ ለመመዝገብ በሚያደርጉት ሩጫ የተለያዩ ገንዘብ መሰብሰቢያዎችን በመሀል ከተማ በክ/ሀገርና በውጭ ሀገር ይነድፋሉ ። ከእነዚህ ውስጥ ነሲሓ ቲቢ ፣ ነሲሓ በጎ አድራጎት ፣ አልሂዳያ እና የመሳሰሉት ይገኙበታል ። የዛሬ አመት አካባቢ በጉመር ወረዳ አረቅጥ አካባቢ ባስገነቡት መርከዝ አማካይነት ገንዘብ ለማሰባሰብ ከላይ ወንድሜ ኢብኑ ሺፋ የጠራቸው አይነት የተለያዩ ባለብትና ነጋዴዎችን እንዲሁም ያብሬት ሸይኽና የቃጥባሬ ሸይኽን የሚያመልኩ ገበሬዮችና ሙሪዶች በተሰበሰቡበት አቶ አዩብ ደርባቸው ፣ ሰላሁዲን መለስና ዐ/ካፊ መሐመድ መድረክ መሪ የነበሩ ሲሆን አዩብ ደርባቸው በአብሬት ሸይኾች ስም መቶ ሺህ ብር በቃጥባሬ ሸይኾች ስም መቶ ሺህ ብር በማለት ቀብር አምላኪው ሱፍዩና አሕባሹም ጭምር እያስጮኸ ነበር ያስነየተው ።
እነዚህ አካላት አጋጣሚዮችን በመፍጠር ወላእና በራእን በማጥፋት ሁሉም የእነርሱን ኪስ እንዲያደልብ መስራታቸውን ከጊዜ ወደ ጊዜ ስልቱን እየቀያየረ የመጣ ጉዳይ ነውና የነሲሓ መዘጋት አጀንዳም የዚህ እስትራቴጂ አንዱ ክፍል ነው ለማለት እወዳለሁ ።

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

19 Dec, 17:49


ነሲሃ ቲቢ በገንዘብ እጥረት ተዘግቶ አይዘጋም! የሙስሊሙ ህብረተሰብ ኪስ ይበዘበዝበታል እንጂ!!
—————ክፍል አንድ
በ ኢብኑ መስዑድ መርከዝ ስር የሚተዳደረው የሙመይዓ - ኢኽዋኑ ነሲሃ ቲቢ ተዘጋ በሚል ሙሾ አውራጅና አስለቃሽ ጭፍን ተከታዮች በየ ማህበራዊ ሚዲያው በዝተው እየተመለከትኩ ነው። የኢኽዋንና የሙመይዓ የጥምር የጥመት ቡድኖች የሆነው ነሲሃ ቲቢ መስኮት አንዳንድ ምስጢሩ ያልገባቸው ሰዎች በገንዘብ እጥረት ተዘጋ ሲባሉ እውነት መስሏቸዋል። አብዘሃኞቹ ደግሞ አፈቀላጤ የሆኑ ጭፍን አራጋቢ ሙሪዶችን አዘጋጅተው እያስጮሁ ስለሆነ ተጨባጩ ቢነገራቸውም እውነት ብለው ለመቀበል ሊከብዳቸው ይችላል።

በቅድሚያ ነሲሃ ቲቢ እውነት በገንዘብ እጥረት ነው የተዘጋው ወይ? በሚለው ነጥብ ላይ የተወሰነ ልበል።
ነሲሃ ቲቢ በየትኛውም ስሌት በገንዘብ እጥረት ሊዘጋ አይችልም!!።

ምክንያት አንድ:- በተለያየ መንገድ ገንዘብ ለመሰብሰብ እንቅልፍ የማይተኙ በመርከዟ አመራርነት ደረጃ የተቀመጡ ሰዎች በርካታ ቁጥር ያላቸው ከፍተኛ ባለ ሀብቶችን እና በየ ደረጃው የሚገኙ ነጋዴዎችንና በደሞዝ የሚተዳደሩ ደሞዝተኞችን ሳይቀር በተለያየ መንገድ በማጥመድ ለቲቢዋ ድጋፍ እንዲያደርጉ ከስራቸው አድርገዋል። ከነዚያ ባለ ሀብቶች ከፊላቸው በየ ወሩ መዋጮ በማድረግ ከፊላቸው ደግሞ በየ አመቱ ከፍተኛ የሆነ (ተራ ብር እንዳይመስላችሁ እያንዳንዱ ባለ ሀብት በሚሊየን ቤት) መዋጮ እንዲያደርግ አድርገዋል። ልብ በሉ! ገንዘቡ ሳይሰበሰብ እንዳይቀር ሰዎቹ ፖለቲካዊ ጫወታው ላይም የተዋጣልን አካሄድና የብር መሰብስብ ብቃት ያለን ብልጦች ነን ብለው ስለ ሚያስቡ ለባለ ሀብቶች ባለ ሀብት አስተባባሪዎችን ነው ያሰማሩት። ለሌሎች ደግሞ በየ ደረጃቸው በዘመድ፣ በአከባቢ ልጅነት፣ በየ ደርስ ቦታው… ወዘተ በየ ደረጃቸው ተመድቦላቸዋል። የተሰማሩ ባለ ሀብቶች ደግሞ በመሪያቸው ፍቅር ያበዱ የእነሱ ቀንደኛ ተላላኪና እራሳቸው ከፍተኛ የሆነን ገንዘብ ነይተው ሌሎችን በፉክክር የሚያስነይቱ ናቸው። ከባለ ሀብቶቹ ስለ ሚንሃጅ ብዙም ግንዛቤ የሌላቸው ኢኽዋኑም ሙመይዓውም… ሌላውም ለመልካም ነገር (ለዲን) ነው በሚል ስም እንዳሻው የሚያልባቸው አሉ፣ ከጅህልናቸውም ጋር በተለያየ ፊክራ የተዘፈቁ አሉ፣ ከነዚህም ውስጥ በኢኽዋን ፊክራ የተዘፈቁ ሆነው የመርከዙ ሰዎች ከእኛው ጀመዓ (ከኢኽዋኑ) ጋር አንድ ሆነዋል መደገፍ አለብን በሚል ስሜት የሚደግፉ አሉ፣ ቀደም ሲልም መርከዟን ባለ በሌለ ሀይላቸው ለዚህ ደረጃ እንድትበቃ ያደረጉ ለደዕወቱ ሰለፊያ ጉጉት የነበራቸው አሁን የመርከዙ አመራሮች ሲቀልጡ ይዘዋቸው የቀለጡና የሟሙ ከፍተኛ አቅም ያላቸው ባለ ሀብቶች አሉ። አይደለም እንዲህ ተረባርበው ይቅርና ብቻቸውን የቲቢውን ወጪ መሸፈን የሚችሉ ጠንካራ አቅም ያላቸው ባለ ሀብቶች ባሉበት "በገንዘብ እጥረት ተዘጋ" ብለው አስለቃሾችን ቀጥረው ሙሪዶችን አደራጅተው ማስጮሃቸው አሁንም ምስጢራቸውን ያላወቀውን ሙስሊሙን ማህበረሰብ "ና! አይንህን ጨፍንና እናሙኝህ" እያሉት ነው። ልብ ያለው ልብ ይበል!!

ምክንያት ሁለት:- ይህ መርከዝ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ከላይ እንደጠቀስኩላችሁ ገንዘብ ለማግበስበስ ሌት ከቀን እንቅልፍ በሌላቸው አመራሮቹ አማካኝነት ከፍተኛ የሆነ የእራሱ የገቢ አቅም አለው። ይህ የገቢ አቅምም አዲስ አበባ ላይ ብዙዎች የሚያውቁት አል-ዓፊያ አክሲዮን ማህበር ነው። ማህበሩ በተለያዩ ቦታዎች ጠንከር ያለ ክፍያ እያስከፈ ከሌሎች የግል ትምህርት ቤቶች ጋር የሚወዳደር ከፍተኛ ገቢ ያላቸው ት/ቤቶች አሉት። የእራሱን ቦታ ገዝቶ የገነባውን ሆስፒታል ጨምሮ ሌሎችም አቅሞች ያሉት አክሲዮን ነው። ብዙ ሰዎች ይህን አክሲዮን ከመርከዙ ለይተው ሲመለከቱት ይስተዋላል። አይፈረድባቸውም 1ኛ, እነዚህ በመሪነት ደረጃ ያሉ አካላት ወሳኝ በሆኑ ቦታዎች ካልሆነ በስተቀር ስሙን ከመርከዟ ጋር አያይዘው ማንሳት አይፈልጉም። 2ኛ, ብዙ ሰዎች አመሰራረቱንና አሁን ከሚያስተዳድሩት ሰዎች ጋር ምን ያህል ትስስር እንዳለው በቅርበት የሚያውቁት ነገር ስለ ሌለ እራሱን የቻለ የንግድ ተቋም አድርገው ይመለከቱታል።
መጋቢት 29/2010 ላይ 18 አካባቢ በሚገኘው በመርከዙ ዋና ህንፃ "ከመጅሊሱ ተቀላቅለን ልንሰራ ስላሰብን እንዲሁም ቲቪ ለመክፈት ፕሮሰስ ጨርሰን እቃዎቹን እያስገባን ስለሆነ ልናወያያችሁ አስበን ነው" የሰበሰብናችሁ በማለት ከተለያዩ ቦታዎች በኡስታዝነት ደረጃ ተቀምጠው በስራቸው የሚገኙ ሰዎችንና የሱሩሪያ ፊክራ የነበራቸውን ሰዎች በሰበሰቡበት ወቅት ከመርከዙ በዋና አመራርነት ከሚጠቀሱ ሰዎች አዩብ ደርባቸው የሚባለው አል-ዓፊያ አክሲዮንን አስመልክቶ የመርከዙ ዋና ሀብትና የገቢ ምንጭ መሆኑን ተናግሯል። ይህን መናገሩን ያስታውስ አያስታውስ አላውቅም እንጂ በወቅቱ ወንድሜ ኡስታዝ ሸምሱ ጉልታ (አቡ ሀመዊየህ) ከሀዋሳ መጥቶ ተሳትፎ ነበር። ይህን እውነታ በተጨማሪ አክሲዮኑ ሲመሰረት የነበሩ አንዳንድ በገንዘባቸውም ጭምር ያገዙ ባለ ሀብቶች አጫውተውኛል። ታዲያ ይህ ሁሉ አቅምና የገቢ ምንጭ እያለ ቲቢዋን ዘግቶ የሙስሊሙን ማህበረሰብ ገንዘብ መበዝበዙ ለምን አስፈለገ? ህዝበ ሙስሊሙን መንሀጁንና ገንዘቡን አጭበርብረውት የት ሊያደርሳቸው ይሆን?!

በነገራችን ላይ በመጋቢት 29/2010 ስብሰባ ላይ የነበሩት አብዘሃኞቹ ተሰብሳቢዎች በቅርበት የማውቃቸው ሲያኮርፉና ሲያሻቸው ወደ ሱሩሪዮች ሲላቸው ወደ መርከዟ ልጥፍ የሚሉ የነበሩ የዛኔም ሚናቸውን ያልለዩ በሁለት ማሊያ እየተጫወቱ የነበሩ ሰዎች ነበር የሞሉት። እኔና ወንደሜን አቡ ሀመዊያን ጨምሮ አንድ ከሀረር የመጡ አሁን በትክክል ስማቸውን የማላስታውሳቸው ከመጅሊስ ስለ መስራት ሲነሳ በቁጣና በጩሀት አውግዘው ከተናገሩ በኋላ ጥለው የወጡ ሸይኽና ከባህር ዳር የመጡ በወቅቱ በእጅጉ አውግዘው በመናገር "ለምን እራሳችንን ችለን አንጓዝም?፣ ለሰለፊያ ደዕዋ እንዲህ ያለ መሰረት ካገኘን በኋላ (ህንፃውን ማለታቸው ነው) ለምን ትላንት ስናወግዛቸው ከነበሩት ከኢኽዋንና ከሱፊይ እንጨመራለን?!" በማለት ቁጣ አዘል ጥያቄ ያቀረቡ ሸይኽና በሰለፊያው ጀመዓ የሚታወቁ ጥቂት ሰዎች ብቻ ነው የነበሩት። ከስብሰባው በኋላ በተለምዶ (አባ ዱላ) በሚባለው በመርከዙ መኪና ወደ አየርጤና ስንሄድ ከመርከዟ አመራሮች አንዱ የሆነውን ኤልያስ አወልን በጠንካራ አቋማቸው የማውቃቸውን ሰዎች ስም ጠቅሼ ለምን አልመጡም?፣ ለምን አልተሳተፉም ወይስ አልጠራችኋቸውም ነው አልኩት? ምንም እንኳን ጥያቄ ምቾት ባይሰጠውም ሳይመልስልኝ ማለፍ አልቻለምና "እነ ባህሩ ተካን ማለትህ ነው አለኝ?" አዎ፣ ሌሎችም ብዬ የአሁኖቹን የአዲሶቹን ሙመይዓዎችንም ስም ጠቃቀስኩለት። "እነሱ ቢመጡም አንግባባም፣ ይልቁንም ሌላውንም ያስበረግጉብናል" አለኝ። እኔም:- ታዲያ በዚህ መልኩ መጓዝ ይሻላል? አልኩት። "አዎ በተለያየ ጊዜ እንወያይ ብለን ስንገናኝ ትርፉ ጭቅጭቅ ነው፣ ዝም ብለን ስራ ብንሰራ ይሻላል" አለኝ። እኔም ትዝብቴን ይዤ በጭንቅላቴ የሚመላለሱ ጥያቄዎችን ከዚህ በላይ መቀጠል ስላልፈለግኩ ዝምታዬን መርጬ አየርጤና ስንደርስ አውርዱኝ ብዬ ወደ ፉሪ ጉዟቸውን ቀጠሉ።

Abu hatim Abduselam Assalefiy

19 Dec, 17:49


ወደ ርእሴ ልመልሳችሁ…
ምክንያት ሶስት:- ሌላኛው የገንዘብ መበዝበዢያ መንገድ ብዙዎቻችን ከሁለት አመት በፊት በአደባባይ ሲሰበስቡ የተመለከትነው "ዳሩ ተውሒድ ፕሮጀክት" በሚል ስም ግዙፍ ህንፃ ገንብቶ ለማከራየት ሲሰበሰብ የነበረው ከፍተኛ ገንዘብ ነው። ይህ ህንፃ ተገንብቶ ከተከራየ ገቢው በቁጥር 1 ለነሲሃ ቲቢ… ወዘተ ወጪ መሸፈኛ ብለው ነው ሲያስተዋውቁት የነበረው። ገንዘቡ 100 ሚሊዮን ብር እንደሚያስፈልጋቸው አስተዋውቀው ስለነበር ብዙ ሰዎች ለዲን ነው በሚል ስም መኪናቸውንና መሬታቸውን ሁሉ ሳይቀር አስረክበዋቸው ካሰቡት በላይ ከፍተኛ ገንዘብ እንደሰበሰቡና የህንፃው ማሳረፊያ ቦታ እንደገዙ በተጨባጭ አውቃለሁ፣ ይህ ብዙዎች የሚያውቁትም የቅርብ ጊዜ እውነታ ነው። ታዲያ በየትኛው ስሌት ገንዘብ አጥቶ ተዘጋ?!

ምክንያት አራት:- ይሀው ልክ በዚህ መልኩ "ነሲሃ ቲቢ ተዘጋ፣ ሊዘጋ ነው…" እያሉ ስንት ጊዜ ነው ብር ያግበሰበሱት? ስንት ጊዜ ነው በዲን ስም ለዲኑ ሲባል በየዋህነት ምስጢሩን ባላወቀው ነገር ያለውን ጠራርጎ የሚሰጠው ህዝበ ሙስሊም ከፍተኛ ገንዘብ ያዋጣው? በቲቢዋ ስም ብቻ ህዝቡን ኪሱን የበዘበዙት ያ ሁሉ ገንዘብ የት ገብቶ ነው አሁንም ተዘጋ ብለው ህዝቡን ሊበዘብዙት የተነሱት?? ልብ ያለው ልብ ይበል!
በአላህ ፈቃድ ይቀጥላል…
✍🏻ኢብን ሽፋ (t.me/ibnshifa)
የተለያዩ ት/ቶችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችን ⤵️ #join በማድረግ ይቀላቀሉ
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa

Abu hatim Abduselam Assalefiy

19 Dec, 17:49


👇
ነሲሃ ቲቢ
——
ዛሬ አንድ ቦታ ቁጭ ብዬ ስልኬ ላይ አንድ ፅሁፍ እየፃፍኩ አንድ የምንተዋወቅ ነጋዴ ባለ ሀብት ሰላም ብሎኝ ከአጠገቤ ቁጭ አለ፣ አጋጣሚ ቤቱ ላይ አንድ የኢኽዋኔይና የሱፊይ የሆነ ቲቢ ተከፍቶ ተመለከተና ቆይ ነሲሃ ቲቢ ሲዘጋ እነዚህ ያልተዘጉት እስፖንሰር ስላላቸው ነው አይደል? አለኝ፣ እኔም ነሲሃ ቲቢስ ቢሆን ምስጢሩ ሌላ ነው እንጅ የምር በገንዘብ እጥረት ነው የተዘጋው ብለህ ታምናለህ? በቀላሉ አልኩትና (አንድ ሁሉም የሚያውቀውን ትልቅ የሆነ የገቢ ምንጫቸውን) ጠቅሼለት እሱ ብቻ አይሸፍነውም እንዴ አንተ ነጋዴ ባለ ሀብት ነህ፣ ነገሮችን ታውቃለህ ብዬው ለሶላት ኢቃም ብሎ ነበርና ብድግ አልኩ፣ ጭንቅላቱን ደጋግሞ እየነቀነቀ ለነገሩ እውነትህን ነው… ልክ ነህ… ልክ ነህ…አለኝ።

እየፃፍኩት የነበረውንም ፅሁፍ እንደሚከተለው ጋብዣችኋለሁ መልካም ንባብ!

✍🏻ኢብን ሽፋ

የተለያዩ ት/ቶችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችን ⤵️ #join በማድረግ ይቀላቀሉ
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa

Abu hatim Abduselam Assalefiy

15 Dec, 17:24


Live stream finished (1 hour)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

15 Dec, 16:04


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

15 Dec, 15:50


ሳምንተዊ የቁሪኣን ተፍስር ልጀምር ነዉ
ገባ
       ገባ
                በሉ
https://t.me/abuhatimaselefiy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

07 Dec, 11:02


ተጨማሪ ብስራት ለዕውቀት ፈላጊዎች በሙሉ
=============================

(دعائم منهاج النبوة...)
የሸይኽ ረስላን ኪታብ ለባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከሚሰጠው በተጨማሪ
ጁሙዓና ቅዳሜ ከ10:45 እስከ 11:30 ድረስ በተከበሩ ይኽ ሐሰን ብን ገላው ድጋሜ የሚሰጥ መሆኑን ስናበስራችሁ በታላቅ ደስታ ነው። ስለዚህ መማር የምትፈልጉ ከወዲሁ ፕሮግራሞቻችሁን አመቻችታችሁና አስፈላጊውን ዝግጅት አድርጋችሁ እንድትከታተሉ ለማስታወስ እንወዳለን።

📚كتاب:-دعائم منهاج النبوة...

كتاب تأليف:- فضيلة الشيخ أبي عبد الله محمد بن سعيد رسلان حفظه الله

📚የሚሰጠው ኪታብ:- ደዓኢሙ ሚንሃጁል ነበዋ

የኪታብ ዝግጅት:-በተከበሩ ሸይኽ ሙሐመድ ሰዒድ ቢን ረስላን (አቡ ዓብዲላህ) ሀፊዞሁሏህ

🎤ማብራሪያ:-በተከበሩ ሸይኽ ሐሰን ብን ገላው ብን ሐሰን ሀፊዞሁሏህ

👩‍🎓🧑‍🎓ደረሱ የሚሰጠው:-ለባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች

🕌ደርሱ የሚጥበት ቦታ:- ሰለፍያ መስጂድ

📆ደርሱ የሚሰጥበት ቀን:- ጁሙዓ እና ቅዳሜ

🧭 ሰኣት:-ከ11:15 እስከ 11: 30 ድረስ

🌐ባህር ዳር፣ ኢትዮጲያ

🪀በአካል መከታተል ለማይችሉ በየቀኑ የሚቀራው ቂርአት ሪከርዱ በባህር ዳር የአህለሱና መሻይኾች ገጽ ይለቀቃል።
➴➴➴➴➴
====================
➴➴➴➴➴
share እያደረጋችሁ፣ በቂ ዝግጅት እያደረጋችሁ በቅርበት ተከታተሉ
=============
share/ሼር/አድርጉ ባረከሏሁ ፊኩም።
➴➴➴➴➴
የኪታቡን pdf ለማገኘት
➴➴➴➴➴
https://t.me/c/1435924812/31727
=============

የባህር ዳር አህለሱና መሻይኾች ገፅ

https://t.me/alateriqilhaq

كن على بصيرة

Abu hatim Abduselam Assalefiy

06 Dec, 20:53


👆👆👆
🔈
#የሙዚቃ እርምነት እና በሱዑዲያህ በተከሰተው  መረጃ ለሚያደርግ ምላሽ

🔶
በማአከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በስልጤ ዞን በምስራቅ አዘርነት በርበሬ በቅልጦ  ወረዳ በሾሞ ቀበሌ ከተሰጠው ሙሐደራ የተወሰደ።

🎙በኡስታዝ ሻኪር ቢን ሱልጣን (ሀፊዘውላህ)

📌 ትምህርቱን ለመከታተል ይህን ቻናል ይቀላቀሉ
👇👇👇
🌐 https://t.me/shakirsultan

Abu hatim Abduselam Assalefiy

06 Dec, 16:43


Live stream finished (50 minutes)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

06 Dec, 16:40


🚫 ጥምር የመጅሊስ አመራሮች ምን እየሰሩ ነው ?

ከአሕባሽና ሱፍይ ጋር የተደመሩት ኢኽዋንና ሙመዪዓዎች የመጅሊስ ወንበር ላይ ሲፈናጠጡ ለእስልምናና ሙስሊሞች እንደሚሰሩ ሲደሰኩሩ ሰፊሁ ህብረተሰብ በሐሴት ተሞልቶ ነበር ። ደስታቸውን በተለያየ መንገድ ሲገልፁ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው ። በተለይ የኢኽዋን የእንጀራ ልጆች የሆኑት ነሲሐዎች ደስታቸውን የገለፁበት መንገድ የሚገርም ነበር ።
የተውሒድና ሱና የበላይነት የሚረጋገጥበት እድል እንተገኘ በማስመሰል በዚህ ያልተደሰተ ሙናፊቅ ነው እስከማለት የተደረሰበት ንቅናቄ እያደረጉም ነበር ። እንዳይፈረድባቸው የእንጀራ አባቶቻቸው በስሜት ስካር ውስጥ ሆነው " እንግዲህ እድሉ መጥቶልናል አሁን ያገኘነው እድል ሙሳም ቢመጡ ፣ ዒሳም ቢመጡ ፣ ነብዩና ሙሐመድም ቢመጡ ይህን እድል …… " አናገኘውም ነበር በሚል መሀላ ሲደረድሩ ከዛሬ ጀምሮ ከናንተ ከኮሚቴዬች አንስቶ ሱፍይ ፣ ሰለፍይ ፣ ኢኽዋንይ የሚለውን መስማት አንፈልግም እኛ የኢትዮዽያ ሙስሊሞች ነን ሲሉ መስማታቸው እነርሱንም አስክሯቸው ሊሆን ይችላል የሚለው ዑዝር ይከለክላል ።
የኢኽዋን መሪዮች የመጅሊሱን ወንበር ገና ከመፈናጠጣቸው የፈለገ መውሊድ ያውጣ የፈለገ ጫት ይቃም ብለው በአደባባይ በማወጅ አላማቸውና ፍላጎታቸው ምን እንደሆነ ሲገልፁ የስልጣን ፍርፋሬ የደረሳቸው ነሲሐዎች ምን እንደተሰማቸው ራሳቸው ይወቁ ። በአብዛኛው ምስኪን ተስፋ ላይ ግን ውሃ ቸለሱበት ። ራሱን እንዲጠይቅም አደረጉት ። ነገር ግን ማን ምን ሊያመጣ ዋናውን ስልጣን የተቆጣጠረው የኢኽዋን አንጃ ስልጣኑን ለማቆየት ኡማውን ቀብር አምላኪና ስሜቱን ተከታይ ማድረግ እንዳለበት ስለሚያውቅ ይህን ወደ መተግበር ገባ ።
አመራሮቹ የተውሒድ ዳዒ የሚባል ነገር መስማት አንፈልግም አሉ ። መጀመሪያውኑ እንደገለፁት አሕባሽ ፣ ሱፍይ ፣ ኢኽዋንይ የሚል ድምፅ ማጥፋት ዋና ተግባራቸው ሆነ ። የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው በሚል ስሜት ይህን እድል ተጠቅመው የነሲሓ ርዝራዦች ከመጅሊስ ባገኙት የስልጣን ፍርፋሬ ሰለፍዮችን ማፈናቀልና ማባረር ዋነኛው ስራቸው አድርገውታል ። በተለይ በስልጤ ዞን በስብጥር ከላይ እስከታች የተቀመጡ የመጅሊስ አመራሮች በጣም አሳፋሪ በሆነ መልኩ ኢኽዋኖችና ነሲሓዎች ከአሕባሽና ሱፍዮች ጋር በመሆን በተለያየ የመንግስት ተቋማት ላይ ያሉ አመራሮችን መጠቀሚያ በማድረግ የሕብረተሰቡን ህገ መንግስታዊ መብት በመርገጥና በመጣስ በሀይል መስጂዶችን መንጠቅና ኢማሞችንና ኡስታዞችን ማፈናቀልና ማባረር የሚቋወም ኮሚቴም ሆነ የሕብረተሰብ አካል ካለ ማሰር ግንባር ቀደም ተግባር እንዲሆን አድርገዋል ።
ስልጤ ዞን ላይ ያሉ የመንግስት ተቋም አመራሮች የተጣለባቸውን ህገመንግስታዊ አደራ ወደ ጎን በማለት ስልጣንን ለግል ስሜትና አመለካከት ማስፈፀሚያ እያደረጉ ይገኛሉ ። የሚገርመው የዚህ አይነት አፈናና የመብት ጥሰት በብልፅግና ዘመን ላይ መሆኑ ነው ።
በኢሀዲግ ዘመን የፀደቀው ህገ መንግስት አይደለም የህዝብ የግለሰብም የእምነት ነፃነት ይረጋገጣል የሚል ነው ። እንደሚታወቀው በኢሀዲግ ዘመነ መንግስት በሙስሊሙ ማህበረሰብ ላይ የማይፈልገውን አመለካከትና እምነት በመጅሊስ አማካይነት በመጫን ትላልቅ የመንግስት ተቋማቶች ያስፈፅሙ ነበር ። የህገ መንግስቱ የዜጎች መብት የሚያትቱ ህይወት አጥተው ወረቀት ላይ የነበሩ ቃላቶችን እንባ የሚጠርግም ሆነ የህዝቡን ጩኸት የሚሰማ አልነበረም ።
የዶ/ር አብር የብልፅግና ዘመን ሲቀየር ግን ሁሉም እነዚህ ህይወት አልባ ሆነው ወረቀት ላይ የቀሩ መብቶች ህይወት ዘርተው እውን እንደሚሆኑ ባለ ሙሉ ተስፋ ነበር ። ነገር ግን በየደረጃው ያሉ የኢሀዲግን ጃኬት አውልቀው የብልፅግና ጃኬት ያጠለቁ የህዝብን መብት ማክበር የሚለውን መርሕ ያልተቀበሉ አመራሮች አሁንም ተመሳሳይ ድራማ እየሰሩ ይገኛሉ ።
አብዛኛዎች ከላይ እስከታች በመንግሰት መዋቅር ያሉት አመራሮች ሀገሪቷንና ሕዝቦቿን እያስተዳደሩ ያሉት በህገ መንግስቱ ሳይሆን ከመጅሊስ አመራሮች በሚመጡ መመሪያዎችና ደብዳቤዎች ይመስላል ።
የትኛውም የመንግስት አመራር በየትኛውም ቢሮ ወንበር ላይ ሲቀመጥ የግል እምነቱን አመለካከቱንና ስሜቱን ከቢሮ በራፍ ውጪ አስቀምጦ ሁሉንም ህዝብ ህገ መንግስቱ ባስቀመጠው መመሪያ መሰረት መብቱን እንዲያገኝና ግዴታውን እንዲወጣ በማድረግ ማገልገል ይኖርበት ነበር ። ነገር ግን ይህ የሚታሰብ አይመስልም ። አብዛኛው በሀላፊነት ቦታ የተቀመጡ አመራሮች ማን ይጠይቀኛል የፈለኩትን መስራት መብቴ ነው የሚሉ ይመስላሉ ።
በተለይ የፀጥታ አካላት ከማንም በላይ የሀገርና ህዝብ አደራ የተሸከሙ ከመሆናቸው አንፃር የሀገርና የህዝብን ሰላም በማስጠበቅ ፍትህን ማስፈን አላማቸው አድርገው ሊንቀሳቀሱ ይገባል ። የሚያሳዝነው ግን በስልጤ ዞን ላይ በሚደርሰው የዜጎች መብት ረገጣ ድራማና ተውኔት ላይ አብዛኛዎች የድራማና ተውኔቱ ገፀ ባህሪ ጥቂቶች ደግሞ የድራማው ደራሲ ሆነው እያየን ነው ።
በስልጢ ዞን ቅበት አካባቢ እየሆነ ያለው ይህ ነው ። ሰላማዊ የሆኑ መስጂዶችና ጀማዓዎች ላይ ችግር አለ የሚል ድራማ እየሰሩ ለምን የሚልን ሰብስበው ማሰር ምን ይሉታል ። የህግ አካል ችግር አለ ከተባለ የመጀመሪያው እርምጃ በሰከነ ሁኔታ ነገሮቹን ማጣራትና መለየት ነበር የሚያስፈልገው ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አጣርተን ነው የምናስረው አስረን አናጣራም ሲሉ ያልተደመመ አልነበረም ። ይህ ማለት እሳቸው ስልጤ ዞን የሆነ ቀበሌ ላይ ወርደው ይፈፅሙታል ሳይሆን እሳቸው የሚመሩት ፓርቲ መርህ ነው ተብሎ ነው ስለሚታመን ነው ። በመሆኑም በየደረጃው ያሉ የፀጥታ ሀይሎች ይህን መርህ ተከትለው ይሰራሉ የሚል አንድምታ ስለተወሰደ ነው ቃሉን ሁሉም በአግራሞት የተቀበለው ።
ለመሆኑ የመጅሊስ አመራሮች እንዳሉትም የሀገር መሪዮች ናቸው ወይስ የአንድ የሌሎችን መብት መከልከል የማይችል ተቋም መሪዮች ? የአሁኑ ተግባራቸው ንግግራቸውን እውነት ነው እንዴ እንዲባል የሚያደርግ ነው ። ከክልል ጀምሮ እስከ ፌዴራል ድረስ አንዳንድ ተቋማትን ህገ መንግስቱን በተቃረነ መልኩ በደብዳቤ ሲያዙና ተፈፃሚ እንዲሆን ሲያስደርጉ እየታየ ስለሆነ አንድ ሊባሉ ይገባል ። በልካቸው እንዲቆሙ ካልተደረገ ሀገሪቷን እየመራ ያለውን ፓርቲ ገፅታ የሚያበላሽ ተግባር መፈፀማቸውን መቀጠላቸው አይቀርም ።
ለማንኛውም የሀገራችን ሙስሊሞች ባጠቃላይ ሰለፍዮች በተለይ የመጅሊስ አመራሮች ተውሒድና ሱናን የበላይ ያደርጋሉ ብላችሁ እንዳትጠብቁ ። ይልቁንም ትልቁ ጠላታቸው አድርገው የያዙት የተውሒድ ዳዕዋና የተውሒድ ዱዓቶችን ነው ።
➴➴ ቀጥሏል ↙️↙️↙️
https://t.me/bahruteka/5580

Abu hatim Abduselam Assalefiy

06 Dec, 16:40


🚫 ጥምር የመጅሊስ አመራሮች ምን እየሰሩ ነው?

➴➴➴ ከዚህ የቀጠለ ↙️
https://t.me/bahruteka/5579

በእነርሱ መዝሀብ ሁሉም የፈለገውን ማራመድ ይችላል ከተውሒድ ተጣሪዮች በስተቀር ። ማንም የፈለገውን መርዳት ይችላል የተውሒድ ተጣሪዮችን መርዳት ካልሆነ በስተቀር ። በስልጤ ዞን የዞኑ መጅሊስ ያወጣው መግለጫ ይህን እውነታ የሚያረጋግጥ ነው ። በየትኛውም መስጂድ ሰለፍዮች ዳዕዋ ማድረግ አይችሉም እገሌ እንዲህ ነው ብሎ መናገር አይፈቀድም ። የአሕባሽንም ስም ማንሳት አይቻልም ሁላችንም ሙስሊሞች ነን ። ማንም ሰው ደረሶችን እንዳይቀልብ ደረሳ ሲመጣ የማን ተማሪ ነህ መባል አለበት ብለው ይህንኑ በየመስጂዱ በኽጥባ እንዲነገር ተደርጓል ።

የአሕባሽ የመጅሊስ አመራሮች ይህን አላደረጉም ። የስልጤ ህዝብና የወሎ ህዝብ ከሚታወቅበት ትልቁ መለያው ደረሳ መቀለብ ነው ። ይህ ተግባር እነዚህን ህዝቦች ብቻ ሳይሆን ሀገርና ሁሉም ህዝብ ከአላህ በላእ እንዲጠበቅ ከሚያደርጉ ተግባሮች አንዱ ነው ። የጥምር መጅሊስ አመራሮች ግን ይህን ታላቅ ኢስላማዊ እሴት ለማጥፋት ተስማምተው ለህዝብ መመሪያ እንዲተላለፍ አድረገዋል ። ይህን ያደረጉት የተውሒድን አስተምሮ ለመግታት እንደመፍትሄ በማየት ነው ። ይህ የአላህን ብርሃን ለማጥፋት መፈለግ ነውና ተውበት አድርጋችሁ ተመለሱ ነው የምንለው ።
ለማንኛውም የመጅሊስ አመራሮች ዛሬ እገሌ አሕባሽ ነው እገሌ ሱፍይ ነው እገሌ ኢኽዋንይ ነው ማለትን ወንጀል አድርገዋል ። ነገ እገሌ ነስራንይ ነው እገሌ የሁድይ ነው ማለት ወንጀል ነው እንዳይሉ ነው የምንሰጋው ።
አላህ ሆይ ከመራኸን በኋላ ልባችንን አትቀይርብን ብለን መለመን ይኖርብናል ።

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

06 Dec, 15:53


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

06 Dec, 15:52


ሰምንተዊ የቁሪአን ተፊስር ልጀምር ነዉ
ገባ
       ገባ
                በሉ
https://t.me/abuhatimaselefiy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

05 Dec, 11:14


🟢መጅሊሳችሁን ገምግሙት

በአንድም ይሁን በሌላ መልኩ መጅሊስ የቋቋማችሁ ፣ የምትመሩት ባለስልጣናቱ ፣ አባላቱ ፣ አጋሮቹ እና ደጋፊዎቹ ሁሉ : መጅሊሳችሁ ከሚስተዋሉበት ጥፋቶች ውስጥ:-

1⃣ሰለፊያን ቀብሮ ሱፊያን አክብሮ ለመንገስ የቆረጠ መጅሊስ

በተደጋጋሚ የመጅሊሳችሁ መሪዎችና ተቀጣሪዎች የነቢያት ፣ የሰሃቦች እና የዑለማዎች መንገድ የሆነውን የሰለፊያን ደዕዋ ለማጥፋት ቆርጠው መነሳታቸውን በግልፅ አውጀዋል:: ተቋማቸውም በተግባርም የሚችለውን ሁሉ እየጣረ ነው::የተዊሂድ ደእዋ ይከለክላል ፣ ቂርኣት ያግዳል ፣ ሀቅ ተናጋሪ ኢማሞችን እና ኡስታዞችን  ያባርራል እንዳይንቀሳቀሱ ያግዳል:: ይባስ ብሎም ለእስርና እንግልት አሳልፎ ይሰጣል :: በአላህ ይሁንብኝ ባጢል ሀቅን አያጠፋም:: ሱፊያ እና ድምሮቹ ፊርቃዎች ልብ ወለድ  ሲሆኑ ሰለፊያ ግን የአላህ ዲን ነውና የበላዓይነቱ የፀና ነው❗️
ነቢዩ (ﷺ) እንደተናገሩት:
( ... وَتَفْتَرِقُ أُمَّتِي عَلَى ثَلَاثٍ وَسَبْعِينَ مِلَّةً كُلُّهُمْ فِي النَّارِ إِلَّا مِلَّةً وَاحِدَةً ، قَالُوا : وَمَنْ هِيَ يَا رَسُولَ اللَّهِ ؟ قَالَ : مَا أَنَا عَلَيْهِ وَأَصْحَابِي )
(ህዝቦቼ ወደ ሰባ ሶስት መንገዶች ይላያያሉ:: አንዲት መንገድ ብቻ ስትቀር : ሁላቸውም የእሳት ናቸው:: ሰሃቦችም አሉ " ማነች እርሷ ያ ረሱለላህ ?"
አሉ : እኔና ባልደረቦቼ ያለንበት መንገድ::)

2⃣መውሊድን አድምቆ አክባሪ መጅሊስ
የሺርኮች እና ቢድዓዎች መናኸሪያ የሆነውን መውሊድን በድፍረትና በተደጋጋሚ ደምቆ እንዲከበር የሚሰራ መጅሊስ መሆኑን አሳያችሁ::
ነቢዩ (ﷺ) እንደተናገሩት:
(...وشرًّ الأمورِ محدثاتُها وكلَّ بدعةٍ ضلالةٌ  وكلَّ ضلالةٍ في النارِ )
(...የነገሮች ክፉ ፈጠራዎች ናቸው::ሁሏም ቢድዓህ ጥመት ነች ::ሁሏም ጥመት እሳት ውስጥ ታስገባለች::)

3⃣ሁሉም ለስሜቱ የመሰለውን እንዲሰራ የሚፈቅድ መጅሊስ
የፈለገ መወሊድ እንዲያወጣ ፣ የፈለገ ጫት እንዲቅም ያልፈለገ ሳይቃወም ሊተው ወዘተ እያለ ሸሪኣ በመደንገግ ከአላህ ጋር የሚፎካከር ደፋር ተቋም ነው::
قوله تعالى: ﴿أَمْ لَهُمْ شُرَكَاءُ شَرَعُوا لَهُمْ مِنَ الدِّينِ مَا لَمْ يَأْذَنْ بِهِ اللَّهُ وَلَوْلا كَلِمَةُ الْفَصْلِ لَقُضِيَ بَيْنَهُمْ وَإِنَّ الظَّالِمِينَ لَهُمْ عَذَابٌ أَلِيمٌ ﴾
4⃣ በሸሪኣም ሆነ በሀገር ህግ ባልተሰጠው ስልጣን የሚጨቁን አምባገነን መጅሊስ

በመሰረቱ መጂሊሳችሁ አንድ ተቋም እንጂ አሚር ወይም መንግስት አልነበረም:: ነገር ግን መስጂዶችን አስገድዶ በቁጥጥሩ እያስገባ ፣ መድረሳዎችን እያዘጋ ፣ የግለሰብ መስጂዶችን ጭምር በጉልበት እያዘዘ ፣ ትእዛዙን አልቀበል ያለን እያሸማቀቀ ፣ ኡስታዞችና ደረሶችን እያስደበደበ ፣ እና እያሳሰረ በግፍ የተሞላ ጥቁር ታሪክ እያስመዘገባላችሁ ነው::

በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ  አጋዦች ፣ አድናቂዎች እና አጋሮች ሆነው ሲያበቁ መሰል የመጅሊሱን ጥፋቶችና ጉዶችን "እኛ አልሰራነውም" የሚሉ አይጠፋም:: በጋራ የገነባችሁት ቤታችሁ መሆኑን አትርሱ::

የሞተው ወንድምሽ
የገደለው ባልሽ
ሀዘንሽ ቅጥ አጣ
ከቤትሽም አልወጣ

አላህን ፈርታችሁ ተመለሱ :: በምድር ላይም አታበላሹ:: ከግፈኞች ታሪክ ተማሩ::

  ሸምሱ ጉልታ (አቡ ሀመዊያ)
http://t.me/Abuhemewiya

Abu hatim Abduselam Assalefiy

04 Dec, 07:34


ሸይኽ ረቢዕ
~~


መድኸልዮች ብለው ሊያሳቅቁን
ከሸይኹ ጋር በጥብቅ አስተዋወቁን
ሸይኽ ረቢዕ ኢማም ናቸው በተየቁን


¶  አረብኛ የምትችሉ ይችን ጥንቅር ቀስ ብላችሁ ስሟት ስለ ሸይኽ ረቢዕ ብን ሃዲ አልመድኸሊ ገራሚ ሁኔታ ትረዳላችሁ።

➻ አላህ በየዘመኑ የሸይኽ ረቢዕ አይነት ጀግኖችን ያብዛልን። ዲናችን በአላህ የሚጠበቀው በሳቸው አይነት ጀግኖች ሰበብ ነው።

🏝 በሸይኽ ረቢዕ የቢድዓ ሰዎች እንደሚቃጠሉት ሁሉ የሱና ሰዎች ደግሞ በጣም ይደሰታሉ!!!

📝 أَبُـــو عِـمْــرَان ❨𝕒𝕓𝕦 𝕚𝕞𝕣𝕒𝕟❩

🏝 ••⇣⇣.  🏖   ••⇣⇣ 
╰𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞.   ╰𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞

🖥️ በ 𝐓𝐞𝐥𝐞𝐠𝐫𝐚𝐦~𝐂𝐡𝐚𝐧𝐧𝐞𝐥
🏝 ⇣⇣⇣🍭⇣⇣⇣📲 ⇣⇣⇣↙️
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

02 Dec, 07:26


🔷 የጭፍን ተከታይነት ሙርከኛ አትሁን !


قال العلامة المحدث محمد بن علي آدم
الإثيوبي - رحمه الله -:

" فيا أيُّها العاقل اللبيب لا تكن أسير التقليد، فإنه حُجّة البليد، وملجأ العنيد، بل كنْ مع الحقِّ، ودُرْ معه حيثما دار؛ تنجُ من مخازي دار البَوارِ، أعاذنا الله منها الرّحيم الغفّار ".

        البحر المحيط الثجاج (1/418)

    🔷  ታላቁ የሐዲስ ሊቅ ኢትዮዽያዊ ዓሊም ሽይኽ ሙሐመድ አሊ ኣደም – ረሒመሁላሁ– እንዲህ ይላሉ : –

" አንተ የአቅል ባልተቤት ጮሌ ሆይ የጭፍን ተከታዩነት ሙርኮኛ አትሁን ።
ጭፍን ተከታይነት የቂሎች መረጃ ነው ።
የእንቢተኛ መሸሸጊያ ነው ።
ይልቁንም ከሐቅ ጋር ሁን ።
የትም ቢዞር ከሱ ጋር ዙር ።
ከመጥፈያው ሀገር ውርደት ትድናለህ ።
አላህ አዛኙና መሓሪው ከሷ ይጠብቀን "።


https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

01 Dec, 17:17


Live stream finished (1 hour)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

01 Dec, 15:46


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

01 Dec, 15:45


ሰምንተዊ የቁሪአን ተፊስር ልጀምር ነዉ
ገባ
       ገባ
                በሉ
https://t.me/abuhatimaselefiy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

29 Nov, 17:24


Live stream finished (1 hour)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

29 Nov, 15:55


ሰምንተዊ የቁሪአን ተፊስር ልጀምር ነዉ
ገባ
       ገባ
                በሉ
https://t.me/abuhatimaselefiy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

29 Nov, 15:53


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

29 Nov, 07:38


ከረድ ዝግጅት ወደ አድናቆት
🏝🏝🏝🏝

📝 የዐቂደል-ዋሲጢየህ ሸርህ ባለቤት የሆኑት ሸይኽ ሙሀመድ ኸሊል ሃራስ አል-አዝሀሪይ አላህ ይዘንላቸውና ከአዝሃር ተመርቀው የወጡ ናቸው። በፍልስፍና፣ በመንጢቅ እና በዒልመ-ልከላም (Logic) ስፔሻላይዝድ አድርገዋል።

በመቀጠል በሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያህ ላይ ረድ እንዲጽፍ እና በዚህ ላይ ዶክትሬቱን እንዲሰራ አዘዙት!። ምክንያቱም እሱ የዒልመል ከላም የመንጢቅ(Logic) የፍልስፍና ጠላት ስለሆነ ከሸይኹል ኢስላም መጽሀፎች ከእጄ ያሉትን ሰበሰብኳቸው እና ለሶስት ወር ያክል ተማርኩ ይላል ከዚያም ውጤቱ ሳነባቸው እኔ በቃ ከዚህ በፊት እስልምናን እንዳልተረደሁ ገባኝ።

🔎 ከዚያም ኢብኑ-ተይሚየህ አስ-ሰለፊይ የሚል መጽሀፍ ጻፈ። ዶክተሬቱንም ሰለፊዩ ኢብኑ-ተይሚየህ በሚለው መጽሀፉ ሰራ። በሱ መልስ ለመስጠት ተዘጋጅቶ ነገሩ ተገለበጠ እና አል-አሽዐሪይ አል-ፈይለሱፍ አል-መንጢቂይ የነበረው በሸይኹል-ኢስላም እምነት አመነ

🎙 منقول عن محاضرة الشيخ محمد أمان الجامي رحمه الله

              قلت ➴➴➴➴➴
💡 እኔ የሚገርመኝ የሸይኹል ኢብኑ ተይሚየህ እውቀት ነው። የባጢል-ባለቤቶች ያላቸውን የባጢል እውቀት እሱ ከነሱ በላይ ያውቀዋል።


🏝 ለዚህም እኮ ነው ሸይኽ ሙሐመድ ኸሊል ሃራስ በዒልመል ከላም ወልመንጢቅ ሸይኹል ኢስላም ከሱ በላይ እንደሆነ የተረዳው።

🚥 ሸይኹል ኢስላምን በሆነ በዲን ካሉ ዲፓርትመንቶች ያገኘው ሰው ሁሉ በዚያ specialized እንዳደረገ ይናገራሉ።

👉 በዘመናችን የነበሩ እና ያሉትን ታላላቅ ዑለሞችን በምንመለከት ቃለ ሸይኹል ኢስላም ከማ ፊመጅሙዒል ፈታዋ... ከማለት አይወገዱም። በቃ እሱ በኛ ዘመን ያለ ነው የሚመስል።

♨️ ጠላቶቹ እራሱ በእውቀቱ ይመሰክራሉ። ህይወቱን በአጠቃላይ የአላህ ዲንን በመኸደም ጨረሰው።

በየሁዳ፣ በነሷራ፣ በጀህሚያ፣ በሙዕተዚላ፣ በአሽዐሪያ፣ በማቱሪደያ... በመሳሰሉት የጥመት አንጃዎች አሏህ በለገሰው እውቀት መልስ በመስጠት እና በማስጠንቀቅ ሀያቱን ጨረሰው።

📿 ዚክር በማድረግ እና በተለያዩ አምልኳቸውም ጠንካራ እንደነበሩ ደረሶቻቸው ይመሰክሩላቸዋል።

🛏 رحمه الله رحمة واسعة واسكنه فسيح جناته!

📝 t.me/sead429
❴ከተወሰነ ማስተካከያ ጋር❵

🏝 ••⇣⇣.  🏖   ••⇣⇣ 
╰𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞.   ╰𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞

🖥️ በ 𝐓𝐞𝐥𝐞𝐠𝐫𝐚𝐦~𝐂𝐡𝐚𝐧𝐧𝐞𝐥
🏝 ⇣⇣⇣🍭⇣⇣⇣📲 ⇣⇣⇣↙️
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

28 Nov, 13:37


🚫   ምቀኝነትን ተጠንቀቅ

   ምቀኝነት የልብ በሽታ ሲሆን አላህ ለባረያው የሰጠውን ፀጋ እንዲወገድ መመኘትና ለዚህም አስባብ ማድረስ ነው ። የዚህ አይነቱ ምቀኝነት በክፋት የመጨረሻው ደረጃ የደረሰው አይነት ሲሆን መጨረሻ ላይ የሚጎዳው ባለቤቱን ነው ። ምክንያቱም የአላህን ውሳኔ ለመቀየር መታገል ስለሆነ አይሳካምና ። አላህ ከባሮቹ ለሻው በሚሻው ነገር ይለየዋል ወይም ስኬታማ ያደርገዋል ። ይህ ማለት በሰዎች እይታ ነው ምክንያቱም የመጨረሻው ስኬት ከጀሀነም ተጠብቆ የጀነት መሆን ስለሆነ ። ይኼኛውን ስኬት ደግሞ ከአላህ ውጪ የሚያውቀው የለም ። ነገር ግን በምቀኝነት በሽታ የተለከፈ ሰው ይህን ፀጋ በሚያይ ጊዜ ውስጡ በምቀኝነት እሳት ይነዳል ። ከዚህ በላይ ምን አይነት ጉዳት ይኖራል ።
      ምቀኝነተ በሁሉም ላይ ሊኖራ የሚችል አስቀያሚ ባህርይ ሲሆን አንዳንድ ሰዎች ታግለው ይደብቁታል ። ግልፅ አያደርጉትም ለዚህም አላህን በመፍራት ይታገዛሉ ። የተበላሸ መንፈስ ያላቸው ወራዶች ግን ከላይ ለመግለፅ በተሞከረው መልኩ የአላህን ውሳኔ ወይም መሺአ ለመቀየር ይታገላሉ ። እንቅልፍ ያጣሉ ፣  ይብከነከናሉ ፣ ጨጓራቸውን ይልጣሉ በዚህም የዱንያ ላይ ቅጣት ያገኛሉ ።
    የእነዚህ ሰዎች ምሳሌ እንደ አይጥ ነው ። አይጥ ጥሩ ነገርን  ከስር እየቦረቦረች ለማጥፋት ትዳክራለች ። ይሁን እንጂ ሀሳቧ ሳይሳካ የወጥመድ እራት ትሆናለች ። የምትያዘውም አንገትዋ ወይን አፏ ነው ።
    ምቀኝነት መጀመሪያ የጀመረው ኢብሊስ ነው ። በአባታችን ኣደም ላይ በመመቅኘት ። አላህ አባታችን ኣደምን ከጭቃ ከፈጠረው በኋላ ለመላኢካዎች ስገዱለት አላቸው ። መላኢካዎችም የጌታቸውን ትእዛዝ ተቀብለው ሰገዱ ። ከእነርሱ ጋር የነበረው ኢብሊስ ግን አልሰግድም አለ ። እንዳይሰግድ የከለከለውም ምቀኝት መሆኑን እንዲህ ብሎ መሰከረ : –

« وَإِذْ قُلْنَا لِلْمَلَائِكَةِ اسْجُدُوا لِآدَمَ فَسَجَدُوا إِلَّا إِبْلِيسَ قَالَ أَأَسْجُدُ لِمَنْ خَلَقْتَ طِينًا »

                         الإسراء  ( 61 )

" ለመላእክትም ለአደም ስገዱ ባልናቸው ጊዜ (አስታውስ) ፡፡ ወዲያውም ሰገዱ ፤ ኢብሊስ ብቻ ሲቀር ፡፡ «ከጭቃ ለፈጠርከው ሰው እሰግዳለሁን» አለ ፡፡ "

« قَالَ أَرَأَيْتَكَ هَٰذَا الَّذِي كَرَّمْتَ عَلَيَّ لَئِنْ أَخَّرْتَنِ إِلَىٰ يَوْمِ الْقِيَامَةِ لَأَحْتَنِكَنَّ ذُرِّيَّتَهُ إِلَّا قَلِيلًا »

                 الإسراء   ( 62 )

«ንገረኝ ይህ ያ በእኔ ላይ ያበለጥከው ነውን
እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስ ብታቆየኝ ዘሮቹን ጥቂቶች ሲቀሩ ወደ ስህተት በእርግጥ እስባቸዋለሁ» አለ ፡፡"
        ኢብሊስ ሊሰግድ የከለከለው ሁለት ነገር ነበር ። ኩራትና ምቀኝነት ። ኩራቱን ከጭቃ ለፈጠርከው ልስገድ ወይ በማለት ገለፀው ። ምቀኝነቱን ደግሞ ይህ ነውን ከኔ ያስበለጥከው በማለት ገለፀው ። በዚህም ከአላህ እዝነት የተባረረና እስከቂያማ የሚረገም ሆነ ።
     ምቀኝነት አላህ ለባሪያው የሰጠውን ፀጋ እንዲፃረር ያደረገው ሰው በመፃረሩ ልክ ከአላህ እዝነት የመራቅና የመረገም ድርሻ አለው ።

       አላህ በዱንያ ላይ በምቀኝነት እሳት ከመንደድ ይጠብቀን ።

አንገብጋቢ ስለሆነ በድጋሚ የተለቀቀ

  https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

27 Nov, 14:22


↪️ ልዩ የኮርስ ዝግጅት በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ!

ኮርሱ መንሀጅ ነክ እና ከግዜያቺን የፊትና ሰዎች የሆኑት ሙመይዓዎች ጋር በተያያዘ የሚሰጥ ትምህርት ነው።

📗 ኮርሱ የሚሰጥበት ኪታብጂናየቱ ተመዩዕ አለል መንሀጂ ሰለፊይ

📙 عنوان الرسالة: جِنَايَةُ التَّمَيُّعِ عَلَىٰ الْمَنْهَجِ السَّلَفِيِّ لِفَضِيلَةِ الشَّيْخِ عُبَيْدِ بْنِ عَبْدِ اللهِ بْنِ سُلَيْمَان الجَابِرِيِّ

አዘጋጅ:- ሸይኽ ዑበይድ ቢን ዐብዲላህ ቢን ሱለይማን አል-ጃቢሪይ (ረሒመሁላህ)

🎙 ኮርስ ሰጪ:-  ወንድም አቡ ዘከሪያ ሙሀመድ ዐብዲላህ አል-ወልቂጢይ (ሀፊዘሁላህ)

🕰 ቅዳሜ እና እሁድ ኅዳር 21 እና 22 2017

አድራሻ:- ጉብሬ ክፍላ ከተማ በኤዋን ቀበሌ ከኤዋን እንፃ በግራ በኩል ገባ ብሎ በሸህ መንደር ሰዓድ መስጂድ

ለተጨማሪ መረጃ:- +251921788881
የተማሪዎች የቴሌግራም 👇👇 ቻናል #join በማድረግ ይቀላቀሉ
https://t.me/Deawaaselefiyah
https://t.me/Deawaaselefiyah

Abu hatim Abduselam Assalefiy

27 Nov, 14:05


🔷 የተብሊግ ጀማዓዎች ማን ናቸው ?

ክፍል ሰባት

20 አዳቦች

እንደ ሚታወቀው ኢስላም የራሱ የሆነ መለኮታዊ የህይወት መመሪያ ያለው የአላህ ዲን ነው ። በኢስላም ህግ የማፅደቅም ሆነ መተዳደሪያ ደንብ የማውጣት መብት ለማንም አልተሰጠም ። ይልቁንም የአላህና የመልእክተኛው ነው ። የመልእክተኛው ሲባል ኢስቲቅላለን ሳይሆን ተበዓን ነው ። ምክንያቱም የአላህ መልእክተኛ ከራሳቸው አንዳችም ስለማያደርጉና ከአላህ የተላለፈላቸውን ሸሪዓ ስለሚያደርሱ ነው ። ይህ እንግዲህ ብቸኛው የኢስላም መለያ መርህ ነው ።
ዲኑ ሙሉ ነው የማንንም የአእምሮ ጭማቂ አይፈልግም ። አላህ ዲኑን ለማንም አመለካከትና አስተሳሰብ አልተወውም ይልቁንም እንከን የለሽ ሙሉ አድርጎት ነው መልእክተኛውን ወደርሱ የወሰዳቸው ። ሙስሊሞች ከአምላካቸው የመጣላቸውን ወሕይ ነው መከተል ያለባቸው ።
የተብሊግ ጀማዓዎች ግን ይህን ታላቅ የኢስላም መርህ በመናድ ነው ለራሳቸው ህግ በማፅደቅ ከዚህ ውጪ መውጣት አይቻልም ብለው በዛ ላይ ጠላትነትና ወዳጅነት የሚመሰርቱት ። ከእነዚህ መተዳደሪያ ህጎች ውስጥ አንዱ የሆነው 20 አዳቦች የሚባለው ነው ። እነዚህ አዳቦች በአምስት ይከፈሉና እየአንዳንዳቸው አራት አራት ነጥቦችን ይይዛሉ ።
ለምሳሌ : – " የምናበዛቸው ፣ የምንቀንሳቸውና የማንገባባቸው …… " የሚሉት ይገኙባቸዋል ። ከእነዚህ ውስጥ በዋነኝነት ለማየት የፈለግሁት የማንገባባቸው የሚለውን ነው ። ይህ ደንብ በውስጡ የሚዛቸው አራት ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው : – 1ኛ – በፖለቲካ አንገባም ።
2ኛ – የአካባቢው ሰው በሚወደው ነገር አንገባም ።
3ኛ – በአራቱ መዝሀቦች አንገባም ።
4ኛ – በመስጂድ ሐቅ አንገባም የሚሉ ናቸው ።
ይህ ማለት የሆነ ጀማዓ ተመድቦ ለዳዕዋ ወደየትኛውም አካባቢ በሚሄድበት ጊዜ ነው ። የሁለተኛውን ነጥብ ብንመለከት ለዳዕዋ የወጣ ጀማዓ ነው ተብሎ ያ ጀማዓ በሄደበት አካባቢ ያለው ማህበረሰብ ቀብር አምላኪ ቢሆን ፣ በቢዳዓ ተግባር የታወቀ ቢሆን ፣ ዝሙት በአካባቢው የተለመደ ቢሆን ፣ ኸምር በአደባባይ ቢጠጣ ፣ በንግድ ቦታ ወለድ ቢቀየርና የትኛውም አይነት ወንጀል በማህበረሰቡ ቢንሰራፋ ክልክል ነው ማለት ራሱ ክልክል ነው ። ምክንያቱም ህጋቸው ስለሚከለክል ነው ። ይህ ቁጥር ስፍር የሌላቸውን የቁርኣንና ሐዲስ መረጃዎችን የሚቃረን ሲሆን ትልቁን የነብዩ ኡማ መለያ የሆነውን በመልካም የማዘዝና ከመጥፎ የመከልከል መርህን የናደ ነው ። ከእነዚህ መረጃዎች ውስጥ ይህን ተግባር መተው የሚያስከትለውን አደጋ የሚናገሩ በጣም አስፈሪ የሆኑ አንቀፆችን ብቻ እንመልከት :–

« لُعِنَ الَّذِينَ كَفَرُوا مِن بَنِي إِسْرَائِيلَ عَلَىٰ لِسَانِ دَاوُودَ وَعِيسَى ابْنِ مَرْيَمَ ۚ ذَٰلِكَ بِمَا عَصَوا وَّكَانُوا يَعْتَدُونَ »
المائدة ( 78 )
" ከእስራኤል ልጆች እነዚያ የካዱት በዳውድና በመርየም ልጅ በዒሳ ምላስ ተረገሙ ፡፡ ይህ ትእዛዝን በመጣሳቸውና ወሰንን የሚያልፉ በመኾናቸው ነው " ።

« كَانُوا لَا يَتَنَاهَوْنَ عَن مُّنكَرٍ فَعَلُوهُ ۚ لَبِئْسَ مَا كَانُوا يَفْعَلُونَ »

المائدة ( 79 )
" ከሠሩት መጥፎ ነገር አይከላከሉም ነበር ፡፡ ይሠሩት የነበሩት ነገር በእርግጥ ከፋ ! "

ይህ ከመሆኑ ጋር ግን የተብሊግ ጀማዓዎች የፈለገው ወንጀል ሲሰራ ቢያዩ አይከለክሉም ። ይልቁንም ራሳቸውም በሽርክና ቢዳዓ ተግባር ተሳታፊዮች ናቸው ።

ያለፉትን ክፍሎች ለማግኘት
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

https://t.me/bahruteka/5552

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

27 Nov, 07:32


አዲስ ወሳኝ ሙሓደራ

🌷ዛሬ ከመግሪብ እስከ እሻዕ በሳንኩራ በአለም ገበያ ካተማ የተሰጣው ዉብ ሙሓደራ

🕌 በፍትህ መስጅድ

↪️ ርእስ፦ "የዘካ"አሳሳቢነት

🎙 አቅራቢ፦ ሸይኽ ዐብዱል ሀሚድ ያሲን አል-ለተሚይ ሀፊዘሁላሁ ተዓላ

ቀን 17/3/17


ተጨማሪ ትምህርቶችን ለማግኘት ወደ ቻናላችን #ጆይን ይበሉ 👇👇👇
https://t.me/Ibnushaffi
https://t.me/Ibnushaffi
https://t.me/Ibnushaffi

Abu hatim Abduselam Assalefiy

26 Nov, 07:44


አዲስ የፈትዋ ፕሮግራም በሀላባ

        ጠቅላይ ፈትዋ በአል’ለተሚይ
             

      ↪️ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀላባ ዞን በቁሊቶ ከተማ በሠለፊያ መስጂድ መድረሰቱ አል’ፋጢማ ማክሰኞ ማለዳ : 17/03/2017 ዓ.እ ከመግሪብ በኋላ የተደረገ አዲስ ሙሓደራ ።

🎤🎤  በፈትዋው የተነሱ ነጥቦች

✓ ሠለፊዮች ከሙብተድዖች የሚለዩባቸው ባህሪያት
✓ አንዳንዶች መስጂድ ሁሉ የአሏህ አይደለም እንዴ?? ታዲያ እናንተ ለምን በራሳችሁ መስጂድ እንጂ አትሰግዱም ይላሉ
✓ አሕባሾች አላህ ከዓርሽ በላይ በመሆኑ ዙሪያ ሙስሊሞችን ለማጠራጠር የሚያነሱትን ከንቱ ሹቡሃዎችን በመረጃ ማፈራርስ እና ሌሎችም ነጥቦች ተብራርቷል ።

🎙 አቅራቢ :– ሸይኽ ዐብዱል ሐሚድ ያሲን አል’ለተሚይ ሐፊዘሁሏሁ ተዓላ

🕌 ቦታ :– በሀላባ ዞን በቁሊቶ ከተማ በሠለፊያ መስጅድ መድረሳቱ አል’ፋጢማ

https://t.me/Ibnu_Mekino_Al_Halaby/3127

Abu hatim Abduselam Assalefiy

26 Nov, 05:26


Live stream finished (2 hours)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

26 Nov, 04:12


ፈታዋ ልጃምር ነው

Abu hatim Abduselam Assalefiy

26 Nov, 02:51


ልጃምር ነው ገባ ገባ በሉ

Abu hatim Abduselam Assalefiy

26 Nov, 02:32


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

20 Nov, 07:12


ኒቃቢስት ከሆነች ተሸነፍላት
👌👌👌👌

ከሸይኽ አብዱልሃሚድ ጋር ፈገግ ይበሉ!ከፈገግታው ጀርባ ግን ታላቅ ቁም ነገር ትማሩበታላችሁ አስተውሉ!❵

~> ሶስቱንም ጥይት አስተኮሰችው! አሉ ሸይኽ

➧ አንድ ሰው ነበር አላህ ሶስት ዱዓወችን ሊቀበለው ወስኖለታል። ሚስቱ ቆንጆ እንዲሆን ዱዓ አድርግልኝ አለችው [ሴቶችኮ የቁንጅናቸው ነገር...]
➧ እሱም ሴት የላከው ሞት ❨ጅብ❩ አይፈራም ነውና ዱዓ አደረገላት ከዛም ከበኒ ኢስራል ሴቶች ሁሉ ቆንጆ ሆነች! ግን ናቀችው ❮ጉድኮ ነው❯
➧ በድርጊቷ ተናዶ እንዲህ አለ «ጌታዬ ሆይ የምትጮህ ውሻ አድርጋት» አለ ሆነችም።

➧ ልጆቹ የውሻ ልጅ እንባላለን ሲሉት ወደነበረችበት እንዲመልሳት ዱዓ አደረገና ተመለሰች

↪️ ሶስቱንም ዱዓዎቹን አጠናቀቀ!!!

👌 ቁም ነገሩ ለሴቶች ቁንጅና አትንበረከክም ለእምነቷ መስተካከል ትኩረት አድርግ። ያቺን አደበኛ የጌታዋን ትዕዛዝ አክባሪ ሌሎች በተገላለጡበት መገላለጡንም ስልጣኔ ብለው በሰየሙት ዘመን በኒቃብ ለተዋበችው እንቁ ትኩረት ስጥ!!!

🏝 ••⇣⇣.  🏖   ••⇣⇣ 
╰𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞.   ╰𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞

🖥️ በ 𝐓𝐞𝐥𝐞𝐠𝐫𝐚𝐦~𝐂𝐡𝐚𝐧𝐧𝐞𝐥
🏝 ⇣⇣⇣🍭⇣⇣⇣📲 ⇣⇣⇣↙️
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

20 Nov, 06:17


📌 ታላቅ የኮርስና የዳዕ ፕሮግራም በስልጢ ወረዳ ለአሳኖ ቀበሌ እና አከባቢዋ ሰለፊዮች በሙሉ
       🪴🪴🪴🪴🪴🪴🪴

       የፊታችን ዓርብ ጥቅምት 8/ 2/2017 ከአስር ሰላት ጀምሮ እስከ ቅዳሜ 10:00 ሰዐት ድረስ በስልጢ ወረዳ በአሳኖ ቀበሌ በፈትሕ መስጅድ ላይ ታላቅ የዳዕዋና ኮርስ ፕሮግራም ተዘጋጅቶ ይጠብቃችኃል።

            
ተጋባዥ ዱዓቶች

1– ታላቁ ሸይኽ አብዱል ሐሚድ ኢብን ያሲን አስ–ሰለፊይ ሐፊዘሁሏህ

2— ኡስታዝ ኑራዲስ ስራጅ ( አቡልበያን) ከቡታጅራ

3 – ኡስታዝ ስራጅ ከወራቤ

4 – ኡስታዝ ዘይኑ ከመነከሪያ

👌 በዚህ ፕሮግራም ላይ ጠቅላላ ሙስሊም ማህበረሰብ የተጋበዘ ሲሆን በተለይም ደግሞ አጎራባች ቀበሌዎች፣ አልከሶ ሰለፊያ ጀመዓ፣መነከሪያ ከተና፣ ወራቤ ጀመዓ፣ ገርቢበር ጀመዓ፣ ቡተጅራ ጀመዓ፣ ስልጢ ቅበትን ጨምሮ ሌሎች በዙርያ ያላችሁ ሙስሊም ማህበረሰቦች ተጋብዛቹሀል።

ልብ በሉ የኮርስ ኪታብ በቦታው ስለተዘጋኛ እዛው ስለምተወስዱና በተጨማሪም ምግብ እና ማደሪያ በጀመዓው በኩል የተዘገጀ ስለሆነ እናንተው ለወገኖቻቹው በማሰማት በደዕዋው ለመጠቀምና ግልፅ ያልሆኑለቹሁን ጉዳዩች ፈትዋዎችን በመጠየቅ መረዳት ትችለለችሁ።

ለሴቶች በቂ ቦታ ተዘገጅቷል።

አድረሻ:— ከቡተጅራ ወደ ወራቤ በሚወስደው ጥቁር አስፐልት አጠገብ አሳኖ ቀበሌ በተለምዶ አስፓልት ዳር ከቲቲ ጎራ ት/ቤት ከፍ ብሎ አጠገብ 5 ሜትር ገባ ብለችሁ መስጅዱ ነው።

📞ለመደወል📞
ኡስታዝ አብዱረዛቅ  0954047289
አቡ አብዱል ወዱድ
0921892212

የተለያዩ ት/ቶችን ለማግኘት የቴሌግራም ግሩፕ እና ቻናለችንን ጆይን ይበሉ:—
https://t.me/TawheedandSunnahPromoter/2344

Abu hatim Abduselam Assalefiy

17 Nov, 17:11


Live stream finished (1 hour)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

17 Nov, 15:41


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

17 Nov, 15:40


ሰምንተዊ የቁሪአን ተፊስር ልጀምር ነዉ
ገባ
       ገባ
                በሉ
https://t.me/abuhatimaselefiy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

16 Nov, 18:46


👉 ለሞተ ሰው ሶደቃ ማድረግ

ለሞተ ሰው ሶደቃ ማድረግ የሚቻል ለመሆኑ በሙስሊሞች መካከል ኺላፍ የለም ። በተቃራኒው ደግሞ የሟች ቤተሰብ የሞተባቸው ቀን ሙስሊሞች ሰርተው ሊያበሉዋቸው ነው ሸሪዓችን ያዘዘው ። እንደዚሁ ሶስተኛ ቀን ፣ ሰባተኛ ቀን ፣ አርባኛ ቀን ብሎ ማረድ የተከለከለ ነው ። ወደ ሞተ ሰው ለመቃረብ ብሎ ማረድ ወይም ቀብር ጋር ወስዶ ማረድም አይፈቀድም ። እነዚህ ተግባራት በቀጥታ ሽርክ አሊያም ወደ ሽርክ መዳረሻ ይሆናሉ ። ከዚህ ውጪ በማንኛውም ቀን የሞተውን ሰው አላህ እንዲምረው ነይቶ አርዶ ቢያበላ ለሟቹም ሆነ ለሶደቃ አድራጊው የሚጠቅም ለመሆኑ ዑለሞች ያረጋገጡት ነው ። ይህን አስመልክቶ ሸይኽ ኢብኑ ባዝ እንዲህ ይላሉ : –

سؤال : إن أنا تصدقت عن والدي، فهل يصيبني نفس الأجر، حيث أن والدي متوفى، وأرجو بيان الأوجه التي يمكن الإنفاق فيها عن الميت، وهل الدعاء أفضل من هذا كله

الجواب :

الصدقة عن الميت مشروعة ومفيدة ونافعة للميت، وقد ثبت في الصحيحين عن النبي ﷺ أنه سئل عن ذلك قال له رجل: «يا رسول الله! إن أمي ماتت أفلها أجر إن تصدقت عنها، قال: نعم فالصدقة تنفع الميت، ويرجى للمتصدق مثل الأجر الذي يحصل للميت؛ لأنه محسن متبرع، فيرجى له مثل ما بذل، كما قال عليه الصلاة والسلام: من دل على خير فله مثل أجر فاعله.
فالمؤمن إذا دعا إلى خير، أو فعل خيرًا في غيره يرجى له مثل أجره، فإذا تصدق عن أبيه، أو عن أمه، أو ما أشبه ذلك، فللمتصدق عنه أجر وللباذل أجر، وهكذا إذا حج عن أبيه أو عن أمه فله أجر ولأبيه وأمه أجر، ويرجى أن يكون مثلهم أو أكثر؛ لفعله الطيب وصلته الرحم وبره لوالديه، وهكذا أمثال ذلك فضل الله واسع.
وقاعدة الشرع في مثل هذا أن المحسن إلى غيره له أجر عظيم، وأنه إذا فعل معروفًا عن غيره يرجى له مثل الأجر الذي يحصل لمن فعل له ذلك المعروف، وقد قال عليه الصلاة والسلام: إذا مات ابن آدم انقطع عمله إلا من ثلاث: صدقة جارية، أو علم ينتفع به، أو ولد صالح يدعو له.
فأنت -يا عبد الله- في صدقتك عن والديك، وفي إحسانك إلى عباد الله بما تفعله من المعروف لك فيه أجر عظيم، ولمن أحسنت إليهم بأن علمتهم وقبلوا منك، وأرشدتهم وقبلوا منك، ودللتهم على الخير وقبلوا منك لهم أجر أيضًا ولك مثلهم. نعم.

نور على الدرب

በኡለሞች መካከል ኺላፍ ያለው አንድ ሰው ለሞተ ሰው ሶደቃ አድርጎ ሰዋቡን ለእገሌ ይሁን ማለት ይችላል ወይስ አይችልም በሚለው ነው ። ነገር ግን ጁሙሁሮቹ ዑለሞች እንደ ሐንበሊዮች ፣ ሐነፊዮች ፣ ማሊኪዮችና ከፊል ሻፊዒዮች ይቻላል ይላሉ ። ቀጥለን የተወሰኑትን የዑለሞች ንግግር እናያለን : –
 
قال الإمام أحمد :
" الميت يصل إليه كل شيء من الخير للنصوص الواردة فيه، ولأن المسلمين يجتمعون في كل مصر، ويقرءون، ويهدون لموتاهم من غير نكير، فكان إجماعاً، وكالدعاء والاستغفار".
المبدع في شرح المقنع (2/281)

وقال شيخ الإسلام ابن تيمية – رحمه الله تعالى – : 
" وقد صح عن النبي صلى الله عليه وسلم أنه أمر بالصدقة على الميت، وأمر أن يصام عنه الصوم، فالصدقة عن الموتى من الأعمال الصالحة، وكذلك ما جاءت به السنة في الصوم عنهم، وبهذا وغيره احتج من قال من العلماء،………… " انتهى من الفتاوى

وقال ابن قدامة رحمه الله :
" وَأَيُّ قُرْبَةٍ فَعَلَهَا , وَجَعَلَ ثَوَابَهَا لِلْمَيِّتِ الْمُسْلِمِ , نَفَعَهُ ذَلِكَ , إنْ شَاءَ اللَّهُ " انتهى
من المغني (2/226) .

ሰዋቡን ለእገሌ ማለት አይቻልም የሚሉ ዑለሞች ያሉ ሲሆን ከመረጃ አንፃር ተመዛኝ ነው ። ሀገራችን ላይ በተለይ በሰሜኑ ክፍል ሰው ሲሞት በሶደቃ ስም ከሽርክና ቢዳዓ ጋር የተገናኘ ተግባር በብዛት የሚፈፀም ሲሆን በሌሎቹም የሀገራችን ክፍሎች ከዚህ ጋር በተገናኘ ሙኻለፋዎች አሉ ። ይሁን እንጂ እነዚህን ሙኻለፋዎች ለይቶ ማውገዝና ማስተማር ሲገባ በጥቅሉ ለሞተ ሰው ሶደቃ የለም የሚሉ እንደውም የሱና ኡስታዞች ከሚባሉትም ጭምር መኖራቸውን እየሰማን ነው ። ከዚህም አልፎ ከላይ ከተጠቀሱት ሙኻለፋዎች በፀዳ መልኩ አርዶ በማብላት ሶደቃ ያደረገን ሰው ከሱና እስከማስወጣት ይደርሳሉ እየተባለ ነው ። ለእነዚህና ለሌሎችም ወንድሞች ይጠቅም ዘንድ የዑለሞችን ንግግር መሰረት ባደረገ መልኩ ይህችን ማስታወሻ ጀባ ብያለሁ አላህ የምትጠቅም ያድርጋት ።

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

16 Nov, 17:06


Live stream finished (1 hour)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

16 Nov, 15:47


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

16 Nov, 15:45


ሰምንተዊ የቁሪአን ተፊስር ልጀምር ነዉ
ገባ
       ገባ
                በሉ
https://t.me/abuhatimaselefiy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

16 Nov, 12:09


🔷 የተብሊግ ጀማዓዎች ማን ናቸው

ክፍል ሰባት

ዳዕዋ ኢለላህ

የተብሊግ ጀማዓ አጠቃላይ እንቅስ ቃሴያቸውን በህይት አንድ ጊዜ አራት ወር ፣ በአመት አርባ ቀን ፣ በወር ሶስት ቀንና በአካባቢ መቃሚና ኢንቲቃሊይ ፣ እንዲሁም በአካባቢ መስጂድ ላይ ተዕሊም በሳምንት ጀውላ በሚል ይከፋፍላሉታል ።
በቁጥር ስድስት ላይ እንዳየነው አንድን ሰው አሳምነው ይዘውት ለሶስት ቀን ካወጡት በኋላ ሰው ፊት ቆመህ አስተምር አላህ ያናግርሀል ይሉታል ። ከላይ ያየናቸው በህይወት ፣ በአመትና በወር የሚሉ ክፍልፍሎች ምንም መረጃ የሌላቸው ሲሆን የዳዕዋ መሻኢኾት ተርቲብ ነው ይላሉ ።
በወር ለሶስት ቀን ሲወጡ በየምደባቸው ከአሚራቸው ጋር ወደ ተመደቡበት አካባቢ ሄደው የ24 ሰአት የስራ ምደባ ያደርጋሉ ። በዚህ ምደባ ኻዲም ይመደባል ፣ ኢዕላን የሚያደርግ ይመደባል ፣ ከመጝሪብ እስከ ዒሻእ በያን ( ሙሓደራ ) የሚያደርግ በመመደብ ይከፋፈላል ። ዐስር ሶላት ላይ ከጀማዐው አንዱ ተነስቶ " ዛሬ በአዱንያ ነገ በአኼራ ፈላሕና ነጃ የምንወጣው የአላህን ትእዛዝ በነብዩ መንገድ በመፈፀም ነው " ይህን በተመለከተ ከሶላት በኋላ በያን ተደርጎልን ጀውላ እናደርጋለን እኛ ሙሀጂሮች እናንተ አንሷሮች ሆነን በጋራ እንሰራለን ለአካባቢው እውሮች ስለሆንን የማይሰግዱና የታመሙ ሰዎች ቤትና እንዲሁም የአዛውንትና ዑለሞች ቤት የሚያዘይረን እንፈልጋለን ይላል ። ከሶላት በኋላ ለጀውላ ( አጃባቢ ላይ ለመዞር) ሰው ይመደባል ።
ጀማዓው በሶስት ወይም በአራት ተከፍሎ አሚር ፣ ደሊል ( ቤት የሚያሳይ)ና ሙተከሊም ( ተናጋሪ ) ተብሎ ይሄዳል ። ለዚህ ለወጣው ጀማዓ ኢስቲጝፋርና ዱዓእ የሚያደርግ አንድ ሰው ተመድቦ መስጂድ እንዲቀመጥ ይደረጋል ። ይህ የተቀመጠው ሰው ለወጣው ጀማዓ እንደ ዲናሞ ( አንቀሳቃሽ ) ነው የሚል እምነት አለ ። በዚህ ሰውና በወጣው ጀማዓ መካከል ተዋሱል ( በውስጥ መገናኘት) አለ ይላሉ ። የወጣው ጀማዓ የሆነ ችግር ከገጠመው ሞተሩ ጠፍቷል ፣ እንቅልፍ ወስዶታል ፣ ወይም ወሬ እያወራ ነው ሶኬቱ ተነቅሏል ብለው ያምናሉ ።
የዚህ አይነቱ እምነት ዐቂዳን የሚነካ ከባድ ሽርክ ነው ። ከዚህም ውጪ በቀዳእና ቀደር እምነት ላይ አደጋ ነው ። ማንኛውም ነገር የሚሆነው በአላህ ውሳኔ ሲሆን የእገሌ መተኛት ወይም ወሬ ማውራት ውጤት ከዚህ ጋር ግንኙነት የለውም ። በውስጥ መገናኘት የሚባል እምነት የሱፍዮች ሲሆን ከእስልምና አስተምሮ የራቀ ነው ።
ተመድቦ የወጣው ጀማዓ በሄደበት ቦታ ምንም አይነት ሙንከር ቢያይ ኢንካር ማድረግ አይችልም ። ለምሳሌ ወንድና ሴት አንድ ላይ ቁጭ ብለው ሙዚቃ ከፍተው ጫት ሲቅሙ ቢያዩ ይሄ ተግባር ክልክል ነው አይሉም ምክንያቱ ደግሞ በዳዕዋ አዳብ አይፈቀድም የሚል ነው ። ይህን ሙንከር እያዩ ዛሬ በአዱንያ ነገ በአኼራ ፈላሕና ነጃ የምንወጣው ብለው ይህን በተመለከተ ከመጝሪብ በኋላ በያን ስላለ ብትመጡ ምን ይመስላችኋል ይላሉ ። ቶሎ በሄዱልን የሚሉት ጎረምሶች ኢን ሻ አላህ ብለው በመጮ ቶሎ ሂዱልን ብቻ የሚል መልእክት ያስተላልፋሉ ። ይህ ደግሞ የእስልምናን ትልቅ መርህ የሚጥስ ነው ። አላህ በተከበረው ቃሉ ስለ ነብዩ ኡማህ ምርጥነትና ምርጥ ያደረገው ምን እንደሆነ በተከበረው ቃሉ እንዲህ ብሎ ነግሮናል :–

« كُنتُمْ خَيْرَ أُمَّةٍ أُخْرِجَتْ لِلنَّاسِ تَأْمُرُونَ بِالْمَعْرُوفِ وَتَنْهَوْنَ عَنِ الْمُنكَرِ وَتُؤْمِنُونَ بِاللَّهِ ۗ وَلَوْ آمَنَ أَهْلُ الْكِتَابِ لَكَانَ خَيْرًا لَّهُم ۚ مِّنْهُمُ الْمُؤْمِنُونَ وَأَكْثَرُهُمُ الْفَاسِقُونَ »
آل عمران
" ለሰዎች ከተገለጸች ሕዝብ ሁሉ በላጭ ኾናችሁ በጽድቅ ነገር ታዛላችሁ ፤ ከመጥፎም ነገር ትከለክላላችሁ ፤ በአላህም (አንድነት) ታምናላችሁ ፡፡ የመጽሐፉም ሰዎች ባመኑ ኖሮ ለነርሱ የተሻለ በኾነ ነበር ፡፡ ከነርሱ አማኞች አሉ ፡፡ አብዛኞቻቸው ግን አመጸኞች ናቸው "፡፡

የተብሊግ ጀማዓዎች ይህንና መሰል አንቀፆች ቦታ አይሰጡዋቸውም ። ከዚህ ይልቅ መሻኢኽ የሚሏቸው የሚናገሩትን ነው ቦታ ሰጥተው ስራ ላይ የሚያውሉት ። ከመጝሪብ እስከ ዒሻእ በሚደረገው ሙሓደራ አላህ ያናግርሀል የተባለው ስው ፊት ቆሞ ላብ በላብ ሆኖ ፀጉሩን እያከከ ምንም አላውቅም የአሚር ትእዛዝ ሆኖብኝ ነው የተነሳሁት ሲል ጀማዓው አላህ እንዲያናግረው ሁሉም አይኑን ጨፍኖ አስተጝፊሩላህ ይላል ።
ምናልባት የተመደበው ሰው የሶሓባ ባህሪይ የሚሏቸውን ስድስቱ ነጥቦች የሸመደደ ከሆነ የነጥቦቹን ቱሩፋቶች እየዘረዘረ ስድስተኛው ላይ ሲደርስ የቻለውን ሁሉ ብሎ ለዳዕዋ እንዲነይቱ ያደርጋል ። በፈላ ውሃ የገባው በሚቀጥለው ዙር ህዝብ ፊት ቆመህ ተናገር ሊባል ይችላል ።
ይህ የተብሊግ ጀማዓ የዳዕዋ ነጥብ ያየንበት ሲሆን 20 አዳብ የሚባሉትን ጀማዓው እንዳጠቃላይ የሚመራበት መርህ አላህ ካለ በሚቀጥለው የምናየው ይሆናል ።

አላህ ካለ ይቀጥላል ።

ያለፉትን ክፍሎች ለማግኘት

https://t.me/bahruteka/5550

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

15 Nov, 19:21


🟢በአንድ ድንጋይ ሁለት ሂዝቢይ

ከላይ ያለውን ድምፅ ሙመይዑ ኢብኑ ሙነወር
"ሐጃዊራ እና ሸይኽ ረቢዕ" ብሎ በለቀቀበት፡
እነ አብራር ሸይኽ ረቢዕን አስመልክቶ  ያንፀባረቁትን ሂዝቢያ ሲኮንን እንዲህ ብሎ  ነበር:"በአሁኑ ሰዓት የሐጁሪ ጭፍራዎች አጥብቀው ከሚኮንኗቸው ዑለማዎች ውስጥ ሸይኽ ረቢዕ አንዱ ናቸው። የውግዘታቸው ቀዳሚ ምክንያት ሸይኽ ረቢዕ የሕያ አልሐጁሪን ክፉኛ ማብጠልጠላቸው ነው። ይሁን እንጂ ለጀምዒያ ጉዳይ ሲሆን የኚህን ክፉኛ የሚያብጠለጥሏቸውን ሸይኽ ንግግር ከነ ኢብኑ ባዝ፣ ከነ ኢብኑ ዑሠይሚን እና መሰል ብዙሃን ዑለማኦች አቋም በተለየ ያስጮሃሉ። ለምን? የሳቸው ንግግር ለተብዲዕ ጥማታቸው ግብአት ይሆነናል ብለው ስለሚያስቡ። ደግሞኮ ንግግራቸውን በልኩ በተጠቀሙ። ..."

በአሁኑ ሰዓት ጠማማዎቹ ሙመይዓዎች ሸይኽ ረቢዕን እና መሰል የጀርህ ወተዕዲል ዑለሞችን የሚያጣጥሉበት ሚስጥር የመሪዎቻቸውን ጥመት አበጥረው በመረጃ ስላጋለጡ የተሀዙቡ ተቆርቋሪነት ይዟቸው ነው። እነ ኢሊያስና  ኢብኑ ሙነወር ራሱ፣መሰሎቻቸውም በተለያዩ አጋጣሚዎች የሚተፋት ይሀው ለሙብተዲኦች  ያላቸውን ጥብቅና ነው። አቅምና አቋም ያለው ሸይኹ የለመረጃ የተቹትን ሰው በፍትህ ያምጣ።አልቻሉም አይችሉም።
ሚዛናዊ መሳይ የሙብተዲዕ ጠበቆች ሙግት ግን  ከንቱ ተሀዙብ መሆኑ ከተጋለጠ ውሎ አድሯል።
በዘመናችን ለሰለፊየህ ዘብ የቆሙ ፣ ለሂዝቢያ የእግር እሳት የሆኑ ታጋይ ኡለማዎችን የሚያንቋሸሽና የሚያማቃልል ሁሉ ማንነቱን እያጋለጠ እንደሆነ ልብ ይሏል።
قال أبو حاتم الرازي:
«علامةُ أهل البدع الوقيعةُ في أهل الأثر،...»[عقيدة السلف (١٠٥)]
"የቢድዐህ ሰዎች ምልክት ሀዲስና የሰለፎችን ፈለግ የሚከተሉትን (አህሉልአሰርን) ማንቋሸሽ ነው።"
https://t.me/Abuhemewiya/3609

Abu hatim Abduselam Assalefiy

15 Nov, 19:21


🔷 የተብሊግ ጀማዓዎች ማን ናቸው

ክፍል ስድስት

ዳዕዋ ኢለላህ

የተብሊግ ጀማዓዎች ትልቁ ትኩረታቸው ኹሩጅ ፊ ሰቢሊላህ የሚል ነው ። እንደሚታወቀው እነዚህ ጀማዓዎች የዳዕዋቸው ዋናው ነጥብ ፈዳኢልን ( ቱሩፋትን ) ማሳወቅ ነው ። ዳዕዋቸው ትኩረቱ ፈዳኢል ላይ ያተኩራል ። ይህ ማለት ደግሞ አላህ የሰው ልጆችን ከኩፍርና ሽርክ ጨለማ ለማውጣት 124 ሺህ ነብያት የላከበትን መርህ ይቃረናል ። ምክንያቱም አላህ ነብያቶች የላከው ለህዝቦቻቸው አልህን ብቻ እንዲያመልኩና ጣኦታትን እንዲርቁ እንዲያስተምሩ ስለሆነ ነው ። ይህን አስመልክቶ ቁጥር ስፍር የሌለው የቁርኣን አንቀፆች መጥቷል ። ከእነዚህ ውስጥ የተወሰኑትን እንይ : –

« وَلَقَدْ بَعَثْنَا فِي كُلِّ أُمَّةٍ رَّسُولًا أَنِ اعْبُدُوا اللَّهَ وَاجْتَنِبُوا الطَّاغُوتَ ۖ فَمِنْهُم مَّنْ هَدَى اللَّهُ وَمِنْهُم مَّنْ حَقَّتْ عَلَيْهِ الضَّلَالَةُ ۚ فَسِيرُوا فِي الْأَرْضِ فَانظُرُوا كَيْفَ كَانَ عَاقِبَةُ الْمُكَذِّبِينَ »
النحل ( 36 )
" በየሕዝቡም ሁሉ ውስጥ «አላህን ተገዙ ፤ ጣዖትንም ራቁ» በማለት መልክተኛን በእርግጥ ልከናል ፡፡ ከእነሱም ውስጥ አላህ ያቀናው ሰው አልለ ፡፡ ከእነሱም ውስጥ በእርሱ ላይ ጥመት የተረጋገጠበት ሰው አልለ፡፡ በምድርም ላይ ኺዱ ፤ የአስተባባዮችም መጨረሻ እንዴት እንደ ነበረ ተመልከቱ "፡፡

« لَقَدْ أَرْسَلْنَا نُوحًا إِلَىٰ قَوْمِهِ فَقَالَ يَا قَوْمِ اعْبُدُوا اللَّهَ مَا لَكُم مِّنْ إِلَٰهٍ غَيْرُهُ إِنِّي أَخَافُ عَلَيْكُمْ عَذَابَ يَوْمٍ عَظِيمٍ »
الأعراف ( 59 )
ኑሕን ወደ ወገኖቹ በእርግጥ ላክነው፡፡ አላቸውም፡- «ወገኖቼ ሆይ! አላህን ተገዙ፡፡ ለእናንተ ከርሱ ሌላ ምንም አምላክ የላችሁም፡፡ እኔ በእናንተ ላይ የከባድ ቀንን ቅጣት እፈራላችኋለሁ፡፡»

« وَإِلَىٰ مَدْيَنَ أَخَاهُمْ شُعَيْبًا ۗ قَالَ يَا قَوْمِ اعْبُدُوا اللَّهَ مَا لَكُم مِّنْ إِلَٰهٍ غَيْرُهُ ۖ قَدْ جَاءَتْكُم بَيِّنَةٌ مِّن رَّبِّكُمْ ۖ فَأَوْفُوا الْكَيْلَ وَالْمِيزَانَ وَلَا تَبْخَسُوا النَّاسَ أَشْيَاءَهُمْ وَلَا تُفْسِدُوا فِي الْأَرْضِ بَعْدَ إِصْلَاحِهَا ۚ ذَٰلِكُمْ خَيْرٌ لَّكُمْ إِن كُنتُم مُّؤْمِنِينَ »
الأعراف ( 85 )
" ወደ መድየንም (ምድያን) ወንድማቸውን ሹዓይብን (ላክን)፤ አላቸው ፡- «ወገኖቼ ሆይ! አላህን ተገዙ ፡፡ ከእርሱ በቀር ምንም አምላክ የላችሁም ፡፡ ከጌታችሁ ዘንድ ግልጽ ማስረጃ በእርግጥ መጥታላችኋለች ፡፡ ስፍርንና ሚዛንን ሙሉ፡፡ ሰዎችንም አንዳቾቻቸውን (ገንዘቦቻቸውን) አታጉድሉባቸው ፡፡ በምድርም ውስጥ ከተበጀች በኋላ አታበላሹ ፡፡ ይህ ምእምናን እንደኾናችሁ ለእናንተ የተሻለ ነው ፡፡»

« وَإِلَىٰ ثَمُودَ أَخَاهُمْ صَالِحًا ۚ قَالَ يَا قَوْمِ اعْبُدُوا اللَّهَ مَا لَكُم مِّنْ إِلَٰهٍ غَيْرُهُ ۖ هُوَ أَنشَأَكُم مِّنَ الْأَرْضِ وَاسْتَعْمَرَكُمْ فِيهَا فَاسْتَغْفِرُوهُ ثُمَّ تُوبُوا إِلَيْهِ ۚ إِنَّ رَبِّي قَرِيبٌ مُّجِيبٌ »
هود ( 61 )
" ወደ ሰሙዶችም ወንድማቸውን ሷሊህን (ላክን) ፡፡ «ሕዝቦቼ ሆይ! አላህን ተገዙ ፡፡ ከእርሱ ሌላ ለእናንተ አምላክ የላችሁም፡፡ እርሱ ከምድር ፈጠራችሁ ፡፡ በውስጧ እንድታለሟትም አደረጋችሁ ፡፡ ምሕረቱንም ለምኑት፡፡ ከዚህም ወደእርሱ ተመለሱ፡፡ ጌታዬ ቅርብ (ለለመነው) ተቀባይ ነውና» አላቸው " ፡፡

እነዚህ ከብዙ ነብያቶች ለምን እንደተላኩ ከሚገልፁ አንቀፆች ጥቂቶቹ ናቸው ። ነብያቶች ስራቸው ዳዕዋ ነበር ስለዚ ዳዕዋ አደርጋለሁ የሚል አካል ዳዕዋው ነብያቶች ያደረጉት ዳዕዋ መሆን ይነርበታል ። ወደ ተውሒድ መጣራትና ከሽርክ ማስጠንቀቅ ። የተብሊግ ጀማዓዎች ግን በተቃራኒው ወደ ተውሒድ የሚጣሩትን ጠላት አድርገው ሰው እንዳይሰማቸው ያስጠነቅቃሉ ። ወሀብይ እያሉ ያጠለሻሉ ። ዳዕዋ ብለው ይወጡና መሻኢኾች ያስቀመጡት አዳብ ብለው በስድስቱ የሶሓባ ባህሪይ በሚሉዋቸው ነጥቦች ብቻ ሙሓደራ ያደርጋሉ ።
አብዛኞቹ ዳዕዋ ብለው የሚወጡ ሰዎች ከተለያየ ቦታ የሚሰበሰቡ ስለሆኑ ስለእስልምና እንኳን በቂ ግንዛቤ የሌላቸው ናቸው ። እነዚህ ሰዎችን አሳምነው እንዲወጡ ያደርጉዋቸውና ተመድበው የሆነ መስጂድ ይሄዳሉ ። እዛ ከደረሱ በኋላ አሚር ተብሎ በተመደበው ሰው አማካይነት የስራ ክፍፍል ሲደረግ ለመጀመሪያ ጊዜ በስንት ጭቅጭቅ የወጣውን ሰው ዛሬ በያን ( ሙሓደራ) አንተ ታደርጋለህ ይባላል ። ሰውየው ላብ በላብ ሆኖ እኔ ምንም አላውቅም እንዴት ሰው ፊት እቆማለሁ ሲል አብሽር አላህ ያናግርሃል መርሀባ በል የአሚር ትእዛዝ ነው ይባላል ።

አላህ ካለ ይቀጥላል ።

ክፍል አንድን ለማግኘት

https://t.me/bahruteka/5508

ክፍል ሁለትን ለማግኘት

https://t.me/bahruteka/5510

ክፍል ሶስትን ለማግኘት

https://t.me/bahruteka/5519

ክፍል አራትን ለማግኘት

https://t.me/bahruteka/5530

ክፍል አምስትን ለማግኘት

https://t.me/bahruteka/5537

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

15 Nov, 19:21


 አስሰላሙዓለይኩም ወራሕመቱላሂ ወበረካቱሁ

አዲስ ኦንላይን (የቀጥታ ስርጭት)የቂርኣት ፕሮግራም ለሴቶች ብቻ ከአልኢስላሕ መድረሳ

እነሆ አልኢስላሕ መድረሳ በተለያዩ ቦታዎች ከሀገር ውስጥም ከውጭም የሚገኙና በአካል ደርስ መከታተል ለማይችሉ እህቶች በቴሌግራም የቀጥታ ስርጭት (ኦንላይን) ደርስ አዘጋጅቶ ለማስተማር ዝግጅቱን አጠናቋል። በመሆኑም በቀጥታ ስርጭቱ ደርስ ተሳትፋችሁ መማር የምትችሉ እህቶች መድረሳው በሚያስቀምጠው መስፈርት ተመዝግባችሁ መማር የምትችሉ መሆኑን ለመግለፅ እንወዳለን።

አጠቃላይ የኪታብ ማስተማሪያ ግሩፑ ከታች ያለው ሲሆን የእያንዳንዱ ሙስተዋ ተማሪ የራሱ ግሩፕ ይኖረዋል።

https://t.me/alislaahwomenonlineders

ማስታወሻ:-

1) ይህ የቂርኣት ፕሮግራም በአልኢስላሕ መድረሳ አስተባባሪነት የመድረሳውን ትምህርቶች በአካል መከታተል ለማይችሉ እህቶች የተዘጋጀ ነው።

2) በዚህ ቂርኣት ፕሮግራም የሚሳተፉት ሴቶች ብቻ ናቸው።

3) በዚህ ፕሮግራም ኦንላይን የሚሰጡ ቂርአቶችን ከሚማሩ ተማሪዎች ምንም አይነት ክፍያ መድረሳው አይጠይቅም። አይሰበስብም።

4) ማንኛዋም ተማሪ መድረሳው በሚሰጠው ትምህርት ላይ ለመሳተፍ መመዝገብ ግዴታ ነው። ያልተመዘገበ ተማሪ አይማርም።

5) ማንኛውዋም ተማሪ የምትማረው ያለችበት የቂርኣት ደረጃ (ሙስተዋ) ተለይቶ ስለሆነ ትክክለኛ ያለችበትን ሙስተዋ ለመለየት እንዲያግዝ ስለራሷ የቂርኣት ደረጃ ትክክለኛ መረጃ መስጠት አለባት።

6) በጠቅላላ ሁሉንም ሙስተዋ የሚመለከቱ የኪታብ ደርሶች የሚሰጡት በወንድ ኡስታዞች ይሆናል።

7) የቁርኣን፣ የተጅዊድና ከዚህ ጋር ተያያዥ የሆኑ ቂርአቶች የሚሰጡት በሴት አሳቲዛዎች ብቻ ይሆናል።

8) ተማሪዎች በየጊዜው የሚሰጠውን የሙከራ ፈተና በስርዓት መፈተን ይኖርባቸዋል።

ለመመዝገብና ለመማር የምትፈልግ ማንኛዋም ተማሪ ከታች ያለውን ፎርም በትክክል በመሙላት መላክ ይኖርባታል።
👇👇👇

https://docs.google.com/forms/d/1PJwh0gz-gENe7JABvDeXlYjx3r0YvBc3979-OnoN-eI/edit?usp=drivesdk

Abu hatim Abduselam Assalefiy

15 Nov, 19:18


👆👆👆
#በአላህ ﷻ ላይ የማጋራት አፀያፊነት በ13 አቅጣጫዎች የሚለው ሪሳላህ ማብራሪያ ክፍል 1

የኪታቡን PDF ለማግኘት
https://t.me/shakirsultan/1903

🔶
በማአከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በቀቤና ልዩ ወረዳ ቃጥባሬ ቀበሌ ታላቁ አሊፍ መስጂድ የተሰጠ ኮርስ ።

🎙በኡስታዝ ሻኪር ቢን ሱልጣን (ሀፊዘውላህ)

🌐 https://t.me/shakirsultan

Abu hatim Abduselam Assalefiy

15 Nov, 17:20


Live stream finished (26 minutes)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

15 Nov, 16:53


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

15 Nov, 16:53


Live stream finished (1 hour)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

15 Nov, 15:44


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

15 Nov, 15:41


ሰምንተዊ የቁሪአን ተፊስር ልጀምር ነዉ
ገባ
       ገባ
                በሉ
https://t.me/abuhatimaselefiy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

12 Nov, 20:02


  ለሰርግ ብሎ ግሩፕ መክፈት

       አላህ ለሙስሊሞች ለደስታቸውም ለሐዘናቸውም ገደብ አድርጓል ። ሐዘን ሲገጥማቸው ወደ አላህ እንዲመለሱ ነገሮች ሁሉ የሚሆኑት በሱ ፍላጎትና ትእዛዝ እንደሆነ አውቀው ለሱ እጅ መስጠት እንዳለባቸው መክሯል ።
      በደስታቸው ጊዜ ደግሞ ደስታቸው እሱ በፈቀደው መንገድ እሱን በሚያስወድድ ሁኔታ መሆን ይኖርበታል ። ያ የደስታቸው ምንጭ የአላህ ኒዕማ ውጤት መሆኑን አውቀው ኒዕማውን በማስታወስ የኒዕማውን ባለቤት በማመስገን እሱ በሚወደውና በሚፈቅደው መልኩ መሆን አለበት እንጂ ሙስሊሞች ደስታቸውን ሲገልፁ ከአላህ ጋር በሚያራርቅ ሁኔታ መሆን የለበትም ።
     አንድ ሰው አላህ ዘር ሰጥቶት በሰላም ለወግ ማእረግ ሲበቃ ከምንም በላይ አላህን ሊያመሰግን ይገባል ። ልጅ አድርሶ ለትዳር በቅቶ ማየት የሚያስደስት ነገር ነው ። ታዲያ ለዚህ ያበቃንን አላህ በዛን ቀን ማመስገን እንጂ ማመፅ አይገባንም ።
      በኢስላም አንድ ወንድ ሲያገባ መደገስ የተወደደ ሱና ነው ። ይህ ታዲያ ወንዱ ቤት ነው ሱና ነው የሚባለው እንጂ ሴቷ ቤት አይደለም ። ምናልባት ሴቷ ቤት ሙባሕ ነው የሚሆነው ። በሰርጉ ቀን ሰርጉን ኢዕላን ማድርግ ( ማሳወቅ) አስፈላጊ ነው ። ኢዕላን የሚደረገው ሸሪዓውን በማይኻልፉ ሰርግ መሆኑ በሚታወቅባቸው ነገሮች ነው ። ከዚህ ውስጥ የሴቶች ከበሮ እየመቱ መጫወት ይገኝበታል ። ሴቶች መጫወት የሚችሉት በሙሽራዋ ቤትና በሙሽራው ቤት ሲሆን ከወንድ ተገልለው ለብቻቸው ሆነው ነው ። ሰርግ ነው ብሎ ዘፈንም ሆነ ነሺዳ መክፈት አይፈቀድም ። አንዳንድ አካባቢዮች ላይ የሚሰሙ አላስፈላጊ ግጥሞችን መጠንቀቅም ያስፈልጋል ።
      ሴቶች መጫወት ይችላሉ ሲባል ከላይ እንደተገለፀው በሙሽራዋና ሙሽራው ቤት የተጠሩ ቤተሰቦችና የልጅቷ ጓደኞች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዮችን ነው የሚያካትተው ።
      በኒካሕ ሰበብ ግሩፕ ከፍቶ ከተለያየ ሀገር በግሩፑ ተገናኝቶ ሰርግ ነው እንጨፍራለን ማለት ሸሪዓም ዐቅልም የማይቀበለው አዲስ መጤ ተግባር ነው ። ምክንያቱም በሸሪዓ ሙሽራዋ የጠራቻቸው ወይም ቤተሰብ የጠራቸው ሴቶች እዛው ተገኝተው መጫወት ይችላሉ ነው የተባለው እንጂ ሙሽራዋ ግሩፕ ከፍታ ግሩፕ ላይ ተሰባሰቡ ትበል አይደለም ። ከዚህ የሚገርመው ደግሞ ከሙሽራዋ ውጪ የሆኑ ሴቶች ለእገሊት ሰርግ እንጨፍር ብለው ግሩፕ ከፍተው ተሰባሰቡ ማለታቸው ነው ። የት ሆነው ነው የሚጨፍሩት ። ጅዳ ላለ ሰርግ ኩዌት ፣ በሕሬን ፣ ቤሩት ፣ ሪያድ ፣ መዲና ፣ ከዚህ አልፎ አሜሪካና ካናዳ ሆነው ነው ? ማን ቤት ያለው ጭፈራ ነው ለሰርጉ ተጠርተው ነው የምንለው ። በግሩፕ ላይ መጨፈር ማለት በእነዚህ ሀገሮች ላይ ያሉት ጭፈራዎች በኦንላየን ይተላለፋሉ ማለት ነው ። የዚህ ትልቁ መፍሰዳ እዚ ግሩፕ ውስጥ ካፊር ሴት ገብታ ጭፈራውን በኦንላየን ለወንዶች ልታሰማ ትችላለች ። አሌያም ሙስሊም ሆናም በስም ብቻ የሆነች ለተሰበሰቡ ወንዶች እንደመዝናኛ ልታቀርበው ትችላለች ። ይሄ በግሩፑ ላይ ወንዶች ከሌሉ ነው ። ነገር ግን በሴት ስም ወንዶችም ሊገቡ ይችላሉ ።
     በየትኛውም ዘመን የነበሩ ሰለፎች እኛ ዘንድ ሰርግ ስላለ እናንተ በያላችሁበት ተሰባስባችሁ ጨፍሩ አላሉም ። አሁን ባለንበትም ዘመን ኢስላምን ተረድተናል የሚሉ ሙስሊሞችም ሰርግ ሲኖራቸው ዘመድ አዝማድ ጓደኛ ጎረቤት ጠርተው ሴቶች ከወንዶች ርቀው እንዲጫወቱ ያደርጋሉ እንጂ በዐለም ላይ ያላችሁ ተሰባስባችሁ በያላችሁበት ጨፍሩልን አይሉም ። እንደርሱ አይደለም ካላችሁ ግሩፕ ከፍቶ መጨፈር የሚባል ነገር የለም ። ግሩፕ ከፍቶ አንድ ላይ መጮህ ካልሆነ በስተቀር ። በመሆኑም የዚህ አይነቱ ተግባር በየትኛውም መመዘኛ ወደ ኢስላም ማስጠጋት አይቻልም ። ኢስላም የሚያውቀው ስላልሆነ ። ይልቁንም ከላይ ለመግለፅ እንደተመኮረው ለብዙ ወንጀል በር ከፋች ነው የሚሆነው ።
     ስለዚህ እህቶች በያላችሁበት አንዷ ጓደኛችሁ ስታገባ እሷ ጋር ሄዳችሁ መጫወት ይናርባችኋል እንጂ ለእንደዚህ አይነት ፈሳድ በር እንዳትከፍቱ እላለሁ ።

          ወላሁ አዕለም ።

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

12 Nov, 13:55


👉በቢደዕ ሰዎች መስጂድ ማስተማር እነ ተመዩዝ

በቢደዕ ሰዎች ምላሽ መስጠት ለሙስሊሙ ማህበረሰብ ጥፋታቸውን በማብራራት ከቢደዐቸው በግልጽ ማስጠንቀቅ ግዴታ ስለመሆኑ ከቁርኣን ከሐዲስ ከደጋግ ቀደምቶች ግንዛቤ መረጃ ያለው ግልጽ ጉዳይ ነው ።

እንዲሁም ከቢደዕ ሰዎች መለየት ፣ እነሱን በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ አለመደገፍ ፣ አለመተባበር እነ በነሱ ላይ ረድ በሚደርግ ሰዐት መደገፍ አለመጥላት የደዕዋህ ሰለፊያ ትልቁ መሰረት ነው ።

ወደ ርዕሴ ስመለስ በሙተዲዕ መስጂድና መድረሳ ደርስ መስጠት በተመለከተ እጅግ በጣም ጥንቃቄ ያስፈልጋል ። የቢደዕ ሰዎች ሰለፊዮችን ሊበታትኑበት ፣ በሰለፊዮች መካከል መተማመን እንዳይኖር ለማድረግ ፣ ሙስሊሞችን ሊያድኑበትና ትክክለኛ መንገድ ያሉ ለማስመሰል መስጂዳቸውንና መርከዞቻቸውን የሰለፎችንና የሰለፊያ ዑለሞችን ኪታብ ደርስ እንዲሰጥ በራቸውን ክፍት ልያደርጉ ይችላሉ ።

የሱና ትምህርት የሚሰጥ ኡስታዝ የትኛውም ቦታ ያስተምር መርህ አይለቅም የቢደዕ ሰዎችን ቢደዐና ስማቸውን እያነሳ  በዝርዝር በሚገባ መልኩ ለደረሳዎቹም ለታዳሚዎቹም ማስረዳት አለበት በተለይ ደግሞ በቢደዕ ሰዎች መስጂድ የሚያስተምር ከሆነ ቢድዒዮች የሚያስተምሩበት መስጂድ ውስጥ የሚያስተምር ከሆነ ሹብሃቸውን የሚበትኑበት መስጂድ ለይ የሚያስተምር ከሆነ ደርስ በሚሰጥበት ሰዐት የቢድዒዮችን ስምና ማምታቻቸውን አንስቶ እኽዋኒይ ከሆኑ እኽዋኒይ ናቸው ሙመይዕ ከሆኑ ሙመይዐህ ናቸው በማለት በግልጽ ጥሜታቸውን እያብራራ ደረሳዎችንና ታዳሚዎችን ማስጠንቀቅ ግዴታ ይሆንበታል ። ይህን ካደረገ ደርስ መስጠቱን የማይፈቅዱ ከሆነ መስጂዳቸውን ጥሎላቸው በመውጣት በቻለው በአቅሙ ያህል ግዴታውን መወጣት አለበት እንጂ ስህተታቸውን እያየ ሰውን እያጠመሙ ዝም ብሎ ከነሱ መተሻሸት የለበትም ።

ቀድሞውንም ደርስ እንዲሰጥ  የፈቀዱለት   በነሱ ላይ ረድ ስለማያደርግ ነው እንጂ ሙመይዖች እኽዋኖች ናቸው እያለ ረድ ብያደርግማ በጭራሽ አይፈቅዱለትም ነበር

በጥቅሉ በሙመይዐዎች ፣ በእኽዋኖችና በተብሊጞች  መስጂድ ደርስ የምትሰጥ ሰለፊይ ነኝ ባይ ኡስታዝ ሆይ የጥሜታቸውን ምስጥርና ሁኔታ ስማቸውን አንስተህ አስጠንቅቅ !
ይህ ሳይሆን ከላይ ከላይ ለብለብ እያደረግክ የምታስተምር ከሆነ ጀመዐህን እያተለልክ ማለት ነው ! ቶሎ ሚናህን ላይና አቋምህን ግልጽ አድርግ ።

       በጦራ ከተማ አስተዳደር በቢድዒዮች  መስጂድ ደርስ የምትሰጡ ኡስታዞች አሁን ከአሁን ለውጥ ይመጣል እያልን ብዙ ትእግስት አድርገናል አላህን ፍሩ ሚናችሁን ለዩ ከቢደዕ ሰዎች ተመዩዝ አድርጉ ።
ከቢደዕ ሰዎች ያልተለያችሁ ለሚንሓጅ ሰለፍ   ምንም አስተዋጽኦ ሳታደርጉ ነገር ግን ሌሎች በሰሩት መመስገን ፈልጋችሁ ቅጥፈትን የምታሰራጩ  በሙመይዐዎች ከመናገር ምላሳችሉ የተከረቸመ  አንዳችሁ ሌላውን በጥፋትና ቅጥፈት እከክልኝ ልከክልህ ጉዞ ለይ የሆናችሁ ኡስታዞች ተው ተመለሱ ?
ይህ ተግባራችሁ ስህተት እንደሆነ  ተናግሬአለሁ በመሻይኾችም አስመክሬያለሁ !
ሰለፊይ ነን የምትሉ ነገር ግን ከሙመይዐህ ጋር በተለያዩ መንገዶች አብራችሁ ያላችሁ ወንድሞች ተው ተመለሱ አላህን ፍሩ ?
ከአሁን በኋላ ከዚህ ተግባራችሁ የማትመለሱ ከሆነ ከእናንተ ስማችሁን በማንሳት የምናስጠነቅቅ መሆኑን በግልጽ አሳውቃለሁ ።

📝ተጨማሪ  ትምህርቶችን   ለማግኘት
   ቻነሉን    ይቀላቀሉ
➘➷➴➘➷➴➘➷➴➘➷➴
https://t.me/MisbahMohammed

Abu hatim Abduselam Assalefiy

12 Nov, 07:42


👉 ቀን ጥሎኝ ብታየኝ
­¯¯¯¯¯¯---_

👌 አንዳንድ ንግግሮች ባለቤታቸው ቦታ ሳይሰጣቸው ይናገራቸውና ዱንያውንም አኼራውንም የሚያበላሹ ይሆናሉ። ከእንደነዚህ አይነት ንግግሮች ውስጥ ምን ታረገው ቀን ጥሎኝ አይተኸኝ የሚለው ሲሆን ሀብታም የነበረ ወይም በጀግንነቱ የሚታወቅ የነበረ ወይም ትልቅ ስልጣን የነበረውና በኋላ ሁኔታዎች የተቀየረበት ሰው የሚናገረው ይገኝበታል። እንደዚሁ አንዳንድ እህቶች በተለይ ዐረብ ሀገር ያሉ ስራ ፈተው ለብዙ ጊዜ በመቀመጥ ሲቸገሩና ሲከሱ ሲጎሳቆሉ ይህን ንግግር ይጠቀማሉ።

በእነዚህና በሌሎችም ምክንያቶች የዚህን አይነት ንግግር መናገር ወንጀሉ በጣም የከፋ የሚያደርገው ደግሞ ከዐቂዳ ጋር የሚገናኝ በመሆኑ ነው።

በመጀመሪያ አንድ ሙስሊም የሚናገረውን ንግግር አስቦና የሚያመጣውን ጥቅምና ጉዳት አመዛዝኖ መናግር ነው ያለበት። የአላህ መልእክተኛ ሳያመዛዝን የሚናገር ሰው ንግግሩ የሚያመጣውን መዘዝ ሲናገሩ እንዲህ ይላሉ፦
عَنْ أَبي هُرَيْرَةَ أَنَّهُ سَمِعَ النَّبيَّ – ﷺ – يَقُولُ : "إنَّ الْعَبْد لَيَتَكَلَّمُ بِالكَلِمةِ مَا يَتَبيَّنُ فيهَا يَزِلُّ بهَا إِلَى النَّارِ أبْعَدَ مِمَّا بيْنَ المشْرِقِ والمغْرِبِ".
📚 متفقٌ عليهِ
"አንድ ሰው አንዲትን ንግግር የሚያስከትለውን ሳያውቅ ይናገርና ከፀሀይ መውጫ እስከ ፀሀይ መግቢያ ርቀት ወዳለው እሳት ይወድቃል።"

🏝 ተመልከቱ እንደቀልድ በተናከርነው አንድ ንግግር የሚመጣው ውጤት። ቀን ጥሎኝ የሚለው ንግግር ደግሞ በጣም አደገኛና ዱንያንም አኼራንም የሚያጠፋ ነው። አንድ ሰው ይህን ንግግር ሲናገር ቀን መጣልና ማንሳት (ማበልፀግና ማደህየት) ይችላል የሚል እምነት ኖሮት ከሆነ ይከፍራል ከእስልምናም ይወጣል። ነገር ግን ይህ እምነት ሳይኖረው እንደቀልድ ከሆነ የተናገረው ትንሹ ሽርክ ነው። ይህ ማለት ከከባባድ ወንጀሎች ይመደባል። ምክንያቱም ቃሉ ቀን መጣል ይችላል የሚል መልእክት ስለያዘ።

🔦 በመሆኑም ሙስሊም የሆነ ሰው ከመናገሩ በፊት ስለሚናገረው ነገር ማወቅና ማመዛዘን ይኖርበታል። ከዚህ በተጨማሪ ቀኑን በመኮነን መልኩ ከሆነ ሌላ ጥፋት ነው። ምክንያቱም ቀን ምንም ነገር ማድረግ አይችልም። የአላህ ስራ የሚያርፍበት ብቻ ነው። ይህ ከሆነ የምንኮንነው አላህን ነው ማለት ነው። ቀን ይነጋል ይመሻል የሚያመሸውና የሚያነጋው አላህ ነው። ለዚህ ነው ዘመንን አትስደቡ የተባለው። ምክንያቱም ዘመን የአላህ ስራ ማረፊያ ከሆነና በቀኑ ውስጥ የሚከሰቱ ነገሮች የሚያስከስታቸው እሱ ከሆነ የምንሰድበው አላህን ነው ማለት ነው!!! ይሄ ደግሞ ዱንያንም አኼራንም የሚያጠፋ ወንጀል ነው።

🔍 አንድ ሰው በየትኛውም ጊዜ ምንም ነገር ቢደርስበት ይህ ነገር በአላህ ውሳኔ ነው የደረሰው ብሎ ማመን አለበት። ይህ በቀደር ማመን ይባላል። በቀደር ማመን ደግሞ የኢማናችን አስኳል ነው። በሌላ አባባል አሁንም ቀን ጥሎኝ የሚለው ንግግር ከቀደር ጋር ያጋጨናል ማለት ነው። ምክንያቱም በአላህ ውሳኔ ያመነ ሰው በማንም በምንም አያማርም። ይልቁንም አላህ ወስኖ ያሻውን ሰራ ነው የሚለው። በዚህም ወደ አላህ ይቃረባል የአላህንም ውዴታ ያገኛል። በቀን ማማረር ትርፉ ኪሳራ ነው።

👉 ሌላው መከራም ይሁን ችግር የሚያገኘን በሰራነው ወንጀል መሆኑን ማመን ይኖርብናል። የበሽታና የርዝቅ እጥረት መንስኤ የራሳችን ወንጀል ነው። በተለይ ዐረብ ሀገር ያላችሁ እህቶች መጀመሪያ ከሀገር ያለ መሕረም ስትወጡ ጀምሮ ወንጀል ላይ ወድቃችኋል። እዛ ሆናችሁ አላህን ፈርታችሁ ላለፈው ተፀፅታችሁ ወደ አላህ መቅረብ ይኖርባችኋል። በተለይ ኢጃዛ በምትወጡ ጊዜ አላህ ካዘነላት ውጪ አብዛኛዎች እህቶች ወንጀል ላይ ነው የሚዘፈቁት። ከአጅ ነብይ ወንድ ጋር አብረው ነው የሚሆኑት የዝሙትና የተለያዩ ወንጀል አይነቶች ይፈፀማሉ።

▷ አላህን ፈርተናል የሚሉ እህቶችም ቢሆን በራሳቸው ቤት መከራየት ስለማይችሉ አንድ ወንድ ከ20 – 30 ሴቶችን ይሰበስብና ያችንም እቺንም አገባሻለሁ እያለ እየበዘበዘ አላህን ካመፀ በኋላ እነርሱንም አይናችሁ ላፈር ይላል። በአብዛኛው እንደነዚህ አይነት ወንዶች የሚፈልጉዋቸውን እህቶች በተለያየ የኢጃዛ ጊዜ እንዲመጡ በማድረግ ነው የሚፈልጉትን የሚሰሩት። ያቺም ከኔ ጋር ነው ትላለች እቺም ከኔ ጋር ነው ትላለች እሱ ግን ከማናቸውም ጋር አይደለም ከገንዘባቸውና ከሸህዋው ጋር ነው። የዚህ ወንጀል መጨረሻ እህቶችን ቀን ጥሎኝ ነው ብለው ሌላ ወንጀል ውስጥ እንዲገቡ ያደርጋቸዋል።

ለማንኛውም አላህን ፈርተን ቀንን ከመተቸትና አላህን ከሚያስቆጣ ወንጀል እንውጣ።

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

12 Nov, 07:41


የጥልፌ ድረቆሌ የዳዕዋ ጥሪ ለታ ወሳኝ ምክር በሃጁሪያዎች ላይ በቂ ምላሽ

ርዕስ"
ሃጁሪያዎችና ሓዳድዮች ልዩነታቸው የት ላይ ነው
👈   مَنْ هُمْ الْفِرْقَةُ الْحَجُورِيِّةُ ؟
⌛️የሃጁሪያ ፊርቃዎች እነማን ናቸው
👈  مَنْ هُمْ جماعةُ  الْحَدَّادِيَّةِ ؟
  የሃዳድያ ጀመኣዎች እነማን ናቸው

📟 የሃጁሪዮች አቋም ድሮና ዘንድሮ እንደት ነበሩ
የነሱ አቋም በአመት በዎራት በቀናት የሚታደስና የሚለሰልስ ሂደትና ይዘት ሁሉ አለው በሸይኻቸው ላይ ደንበር በማለፍ በእውቀት ባልቤቶች ላይ ምላሳቸውን ይሰነዝራሉ ጎራን አፍርሰው ሜዳላይ በሰሜት ለመጋለብ ኮርቻ ይጭናሉ

🧣እርስ በርሳቸው ምላሽ ረድ ሲደራረጉ ሸሪኣን የሚነቅፍና የሚቃረን በግላውይ ጉዳይ ላያ ያጠነጠነ  በቀልና ህስደትን ቅናትን ያነገበ ጥሪ የሚናገሩ ነው።

🕶በስሜት የሰዎችን ስስ ብልትና ክፍተት በመመልከት ቁስል በመነካካት ማነዎር ማሽሟጠጥ ዋና ስራቸው ናቸው።

📝እነሱን መገደፍን የገደፈ ከነሱጎን የቆመ ሰለነሱ መልካም ነገር የፃፈ ሸይኻቸውን ያልነካ ሁሉ ከአላህ ውጭ እንኳን ቢያጋራ ቢዳዓ ቢሰራ ጉዳያቸው አይደለም አይነካም

ሸይኽ የህያን የተናገረ በሱላይ ጠንከር ያለ ምላሽ የሰጠ ከሱ ያስጠነቀቁ ኡለማዎችን  ሁሉ የቢዳ ሰውዎችናው የቢዳ ሰዎች እንጅ የኛን ሸይኽ አይነኩም የሚነካም የለም በማለት ደንበር ያልፋሉ

በውስጡ የሱና ኡለማዎች በየህያ አል ሃጁሪ ምን አይነት በቂ ምላሽ እንደሰጡት ተብራርቶበታል ተዎስቶበታል

🎙 በኡስታዝ ሙሀመድ ሰልማን
{ሃፊዘሁሏህ}

🕌 መስጅዴ ረህማን ጥልፌ ድረቆሌ

ጥቅምት ቀን /25/2017/እለተ/ሰኞ ወሳኝ ምክር /ክፍል /ሶስት/(3)ይቀጥላል
https://t.me/hussenhas

Abu hatim Abduselam Assalefiy

10 Nov, 17:33


Live stream finished (1 hour)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

10 Nov, 15:43


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

10 Nov, 15:42


ሰምንተዊ የቁሪአን ተፊስር ልጀምር ነዉ
ገባ
       ገባ
                በሉ
https://t.me/abuhatimaselefiy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

10 Nov, 13:24


#ታላቅ_የሙሃደራ_ግብዣ በአዳማ ከተማ
============>

🏝 በጣም አጓጊ እና ተናፋቂው የሰለፊዮች የዳዕዋ ድግስ በጣም ተናፋቂ በሆኑ ኡስታዞች ለየት ባለ እና በማረ መልኩ ተደግሶ ይጠብቀናል።


🪑ተጋባዥ እንግዶች

1ኛ  ተወዳጁ ኡስታዝ ባሕሩ ተካ አቡ ዑበይዳህ አላህ ይጠብቀው

2 ተወዳጁ ኡስታዝ አቡ ሀመዊየህ ሸምሱ ጉልታ አላህ ይጠብቀው

3ኛ ኡስታዝ አቡ አብዱረህማን አብዱልቃዲር አላህ ይጠብቀው
ሌሎችም ተጋባዥ እንግዶች ይጠበቃሉ


    📅  የፊታችን እሁድ 08/03/2017

🕌 ቦታ፦ አዳማ 01 ቀበሌ በኢብኑ ተይሚያ መስጂድ

ሰዓት ከ 🕰2:30 ጀምሮ እስከ ዙህር

https://t.me/abuabdurahmen

Abu hatim Abduselam Assalefiy

10 Nov, 13:24


🔷 የተብሊጎ ጀማዓዎች ማን ናቸው

ክፍል አምስት

ሙስሊሞችን ማክበር

ተብሊጎች ስድስት የሶሓባ ባህሪይ ከሚሏቸው የዳዕዋ ነጥቦች ውስጥ አራተኛው ሙስሊሞችን ማክበር ( ኢክራሙል ሙስሊሚን) የሚል ነው ። አላህ ካለ ወደ ፊት በምናያቸው 20 አዳቦች ውስጥ የአካባቢው ሰው በሚወደው ነገር አንገባም የሚለው መርሃቸውና ይኼኛው ነጥብ ተብሊጎች በስም ብቻ ሙስሊም የሆነ ማንኝውም ሰው እንዲወዳቸው አድርጎላቸዋል ።
ሙስሊሞችን ማክበር ማለት ለሱ ስጦታ መስጠት የማይፈልገውን ነገር አለመናገር መጥፎ ነገር ሽርክም ቢሆን ሲሰራ ለምን ትሰራለህ አለማለት ነው ። በጣም የሚገርመው እነዚህ ጀማዓዎች ለዳዕዋ ብለው በሄዱበት አካባቢ ቀብር ፣ ቀን ፣ ወልይ የሚያመልኩ ሰዎች በአላህ ቤት ላይ በየሳምንቱ ወይም በየወሩ አሊያም በየአመቱ ተሰብስበው ሽርክና ቢዳዓ የሚሰሩ ሰዎች አሉ ከተባሉ በዚያን ቀን ከጀማዓው ሰው ተመርጦ የተለያየ ስጦታ ይዘው ጫትም ሊሆን ይችላል ይሄዳሉ ። እነዚህ ለዳዕዋ መጣን የሚሉ አካላት የተሰበሰበው ሰው የሚሰራውን ሙንከር አያወግዙም ኢንካርም አያደርጉም ። ይልቁንም ይዘውት የሄዱትን ስጦታ ሰጥተው ከዚህ ቦታ የመጣን ጀማዓዎች ነን እገሌ የሚባል መስጂድ አርፈናል ብለው ራሳቸውን አስተዋውቀው ከአሚሩ ከተፈቀደላቸው ጫትም ቢሰጣቸው ተቀብለው ይመለሳሉ ወይም አብረው ይቀመጣሉ ።
ይህ ነው ሙስሊሞችን ማክበር ተብሊጎች ጋር ። በዚህ ተግባራቸው ቁጥር ስፍር የሌላቸው የቁርኣንና የሐዲስ መረጃዎችን ውድቅ ያደርጋሉ ። በኢስላም በመልካም ማዘዝና ከመጥፎ መከልከል ፣ በመልካም መተባበርና በወንጀል አለመተባበር ፣ በሐቅ አደራ መባባል ትላልቅ መሰረቶች ናቸው ። አላህ ከበኒ ኢስራኢሎች ውስጥ ከመጥፎ ነገር ባለመከልከላቸው የተረገሙ መኖራቸውን ሲነግረን እንዲህ ይላል : –
« لُعِنَ الَّذِينَ كَفَرُوا مِن بَنِي إِسْرَائِيلَ عَلَىٰ لِسَانِ دَاوُودَ وَعِيسَى ابْنِ مَرْيَمَ ۚ ذَٰلِكَ بِمَا عَصَوا وَّكَانُوا يَعْتَدُونَ»
المائدة ( 78 )
" ከእስራኤል ልጆች እነዚያ የካዱት በዳውድና በመርየም ልጅ በዒሳ ምላስ ተረገሙ ፡፡ ይህ ትእዛዝን በመጣሳቸውና ወሰንን የሚያልፉ በመኾናቸው ነው " ፡፡

كَانُوا لَا يَتَنَاهَوْنَ عَن مُّنكَرٍ فَعَلُوهُ ۚ لَبِئْسَ مَا كَانُوا يَفْعَلُونَ
المائدة ( 79)
" ከሠሩት መጥፎ ነገር አይከላከሉም ነበር ፡፡ ይሠሩት የነበሩት ነገር በእርግጥ ከፋ "!

የነብዩን ኡማ ደግሞ በመልካም ለማዘዝና ከመጥፎ ለመከልከል የታዘዘ መሆኑን እንዲህ በማለት ነግሮናል : –

« كُنتُمْ خَيْرَ أُمَّةٍ أُخْرِجَتْ لِلنَّاسِ تَأْمُرُونَ بِالْمَعْرُوفِ وَتَنْهَوْنَ عَنِ الْمُنكَرِ وَتُؤْمِنُونَ بِاللَّهِ ۗ وَلَوْ آمَنَ أَهْلُ الْكِتَابِ لَكَانَ خَيْرًا لَّهُم ۚ مِّنْهُمُ الْمُؤْمِنُونَ وَأَكْثَرُهُمُ الْفَاسِقُونَ»
آل عمران ( 110 )
" ለሰዎች ከተገለጸች ሕዝብ ሁሉ በላጭ ኾናችሁ በጽድቅ ነገር ታዛላችሁ፤ ከመጥፎም ነገር ትከለክላላችሁ፤ በአላህም (አንድነት) ታምናላችሁ፡፡ የመጽሐፉም ሰዎች ባመኑ ኖሮ ለነርሱ የተሻለ በኾነ ነበር፡፡ ከነርሱ አማኞች አሉ፡፡ አብዛኞቻቸው ግን አመጸኞች ናቸው " ፡፡

ይህ ነው ኢስላማዊው መርህ ነገር ግን በተብሊጎች አስተሳሰብ ይህ ሙስሊሞችን ከማክበር ጋር ይጋጫል ። ለዚህ ነው ወልዮች የሚሏቸውን ማምለክ አይገባም ። ለአላህ የሚገባን ሐቅ ለእነርሱ መስጥት ከእስልምና ያወጣል ሲባሉ ወልዮችን ይሳደባሉ የሚሉት ። !!! ሸይጣን ተውሒድን ሽርክ ሽርኩን ተውሒድ አድርጎ አሳይቷቸው አሳሳታቸው ።

ንያን ማስተካከል

ሌላኛው የተብሊጎች የዳዕዋ ነጥብ ንያን ማስተካከል የሚል ነው ። ንያን ማስተካከል ማለት ከይስሙልኛና እዩልኝ ስራን ማራቅ ነው ። ነገር ግን ተብሊጎች ዘንድ ሱሙዓና ሪያእ ምን እንደሆነ ስለማይታወቅ በድፍኑ ኢኽላስ መኖር አለበት የሚል ተርጊብ ነው የሚደረገው ። በዚህ ዙሪያ የመጡ መረጃዎች ስለማይታወቁ ቦታ የላቸውም ። ምክንያቱም አጠቃላይ ዳዕዋቸው ከመረጃ የራቀ ነውና ። አንዳንድ ዐረቦች መረጃ ለመጥቀስ መሞከራቸው በጀማዓው መርህ ላይ የሚያመጣው ለውጥ የለም ። ምክንያቱም ጀማዓው የሚመራው በተቀመጠለት አዳብ ስለሆነ ።
በመሆኑም ኢኽላስ የሚባለው ነገር ተብሊጎች ዘንድ ሩሕ የሌለው ጀሰድ ነው ። እንዴት በቀብር አምልኮ ላይ የተመሰረተ ጀማዓ ኢኽላስ ይኖረዋል ? ምናልባት ኢኽላስ ማለት ምን ማለት እንደሆነ የማያውቅ አካል ዘንድ ካልሆነ በስተቀር ።
አላህ ዲናችንን በእውቀት ላይ ሆነን የምንይዝ ያድርገን ።

አላህ ካለ ይቀጥላል ።

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

10 Nov, 05:19


🔷#የኢሊያስ_ሙሪዶች_ኧረ_የክኒኒው_እንቅልፍ_ይብቃችሁ _ንቁ ❗️

👉በሀበሻ ምድር የተምይዕ ባንዲራ ተሸካሚ የሆነው ኢሊያስ አህመድ የኔ በጤንነቱ ሰዐት ስለ ኢኽዋኖች የተናገረው

👉ኢኽዋኖች የተለያዩ ጥፋቶች ለይ እያሉ የሉባቸውን ስህተቶችን በጠቃለይ ለመቀበል ዝግጁ እንደማይሆኑ ።

👉የሰዎችን ስም ማንሳት ሱስ ሆኖብን አይደለም ከቢደዕ ሰዎች የምናስጠነቅቀው

👉 እንዲህ አይነት ሰዎች ስማቸው ተጠቅሶ ያሉባቸው ስህተቶች ለህብረተሰቡ ስነገር ለምንድንነው የሚያንገሸግሻቸው

👉ሀቅን መናገር ከቃተህ ባጢልን አትናገር ከቢደዕ ሰዎች ማስጠንቀቅ ካልቻልክ የሚያስጠነቅቁትን ሰዎችን አትቃወም

👉የዛሬው ኢሊያስ ግን ከነኢብራሂም ቱፋ ከመሐመድ ሐሚዲን ከሌሎችም ከዋና ዋና የቢደዕ ሰዎች ቁንጮ ጋር ሆኖ ሰለፊያን መዋጋት የጀመረው 30 ኪኒኖችን ከሰራጨ በኃላ አይደለምን ?
ኧረ ተው የኢሊያስ ሙሪዶች ተመለሱ እራሳችሁን አግኙ ?
أبو نوح السلطي
https://t.me/MisbahMohammed

Abu hatim Abduselam Assalefiy

09 Nov, 17:22


Live stream finished (1 hour)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

09 Nov, 15:48


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

09 Nov, 15:46


ሰምንተዊ የቁሪአን ተፊስር ልጀምር ነዉ
ገባ
       ገባ
                በሉ
https://t.me/abuhatimaselefiy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

09 Nov, 06:30


የኸይር ስራ ፈላጊ እህት ወንድሞቻችን ሆይ፦

ሸሪአችንን "በዚህች ምድር የወንድሙን ወይም የእህቱን እንዲሁም የእህቷን ወይም የወንድሟን ጭንቀት ያስወገደ/ች አላህ በአኸይራህ (በመጪው አለም) የሱን/ሷን ጭንቀት ያስወግድለታል" በማለት በኸይር ስራ አነሳስቷል። በመቀጠል ወደ መልካም ስራ እናመላክታችሁ። እሱም አንድ እህታችን የወንድም እህቶቿን እገዛ ትፈልጋለች።

እህታችን አጢባ ነጋሽ ትባላለች። በወራቤ ከተማ 02 ቀበሌ ነዋሪ ስትሆን በደረሰባት የልብ ህመም የወራቤ ኮምፕሬሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ወደ ህንድ ሀገር ሄዳ እንዲትታከም ፅፎላታል። ለህክምናውም 2,000,000 [ሁለት ሚሊዮን ብር] ያስፈልጋል ተብላለች። ነገር ግን በግል ህክምናውን ለመከታተል አቅም የሌላት በመሆኑ ከሀያሉ ጌታ ቀጥሎ የናንተን ወንድም እህቶቿን ድጋፍ ትፈልጋለች።

ይህች እህታችን ለበርካታ ጊዚያት በበሽታ እየተሰቃየች መሆኑን ተደጋግሞ እየሰማን ነው። አላህ ሁላችነንም ቤተሰቦቻችነንም እኛንም ከዱንያም ከአኸይራም ችግር ይጠብቀን!  በመሆኑም አላህ የመዋረጃው ቀን ጭንቀት ጊዜ ዘወር እንዲያደርገለት የፈለገ በተቻለው ይርዳት በማለት መልእክቱን ለማላስተላለፍ እንወዳለን።

❝ አንዳችሁንም ሞት ሳይመጣውና ጌታዬ ሆይ! እንድመጸውትና ከደጋጐቹም ሰዎች እንድኾን ወደ ጥቂት ጊዜ ብታቆየኝ ኖሮ እመኛለሁ ከማለቱ በፊት ከሰጠናችሁ ሲሳይ ለግሱ፡፡ ❞

በዚህ መልካም ስራ መሳተፍ የምትፈልጉ በሙሉ የሚከተሉትን አካውንቶች መጠቀም ትችላላችሁ

የአካውንት ቁጥር
Commercial Bank of Ethiopia
1000036881589

Zamzam Bank
0050265620101

Awash Bank
01425562027700

የአካውንት ስም Hatiba Nagash Aman

ተጨማሪ መረጃ
📱 +251912011954
           ሐጢባ ነጋሽ አማን

Abu hatim Abduselam Assalefiy

09 Nov, 06:30


🔷  የተብሊግ ጀማዓዎች ማን ናቸው

               ክፍል  አራት

        ሶላት በኹሹዕና ኹዱዕ

     ከተብሊግ ጀማዓዎች የዳዕዋ ነጥቦች ውስጥ አንዱ የሆነው ሶላት በኹሹዕና ኹዱዕ የሚለው ነው ። ሶላት የራሱ የሆኑ ሹሩጦች ፣ አርካኖች ፣ ዋጂባቶች ፣ ሙብጢላቶች ፣ ሱናዎችና ኣዳቦች ያሉት ሲሆን ተብሊጎች ጋር እነዚህ የእውቀት አይነቶች አይታወቁም ። ነገር ግን ሶላት በማዛብት ላይ ቱክረት ይደረጋል ። ምን ሶላቱን እንደሚያጠፋው ወይም እንደሚያበላሸው ማስተማር አይታሰብም ። ምክንያቱ ደግሞ እውቀት ከጁሁድ ወደ ኋላ ያስቀራል የሚል ነው ።
     በመሆኑም ስለሶላት ዝርዝር ህግጋቶችም ሆነ ሌሎች የሸሪዓ እውቀቶች ቦታ የላቸውም ። ኢማን በልፋት ነው የሚል መርህ አንግበው ስለሆነ የሚንቀሳቀሱት ትኩረታቸው ኹሩጅ ላይ ነው ። አላህ በተከበረው ቃሉ እሱን የሚፈሩት ከባሮቹ ዐዋቂዮቹ መሆናቸውን በግልፅ ነግሮናል ። ተብሊጎች ግን አይደለም ኹሩጅ የሚወጣ ነው ይሉናል ።
      ሶላትን በተመለከተ በኹሹዕና ኹዱዕ ሲሉ ኹሹዕ ማለት በአካል መተናነስ የሚል ትርጉም ሰጥተውት ሰውነታቸውን በማኮማተርና በመሰብሰብ አይናቸውን ጨፍነው ነው በመስገድ ይገልፁታል ። ይህ ስህተት መሆኑ የሚያውቅ የለምና አስተካክሉ አይባልም ። ይልቁንም እንዲህ አይነት ሶላት የሚሰግድን ሰው በጣም አላህን የሚፈራ ተደርጎ ይወሰዳል ።!!!
     ነገር ግን በኢስላም አስተምሮ ኹሹዕ ማለት በሶላት ውስጥ ቀልብን ተቆጣጥሮ ልብን ንፁህ አድርጎ የአላህን ትልቅና በማሰብ እሱ ፊት ቆሜያለሁ ብሎ ትልቅነቱን ከፊት ለፊት ማድረግና በልብ መተናነስ ነው ። ይህ እሳቤ አካል ቀጥ ብሎ ቆሞ የቀኝ እጅን መዳፍ  በግራ እጅ ላይ በማድረግ ቀልብን ሰብስቦ አይንን ከፍቶ የስጁድ ማድረጊያን ቦታ  መመልከትን ሲያመጣ ኹዱዕ ይባላል ።
     የተብሊግ ጀማዓ ዘንድ ይህ አይታወቅም ። በየአካባቢያችሁ ያሉ ተብሊጎች ሶላት ላይ እንዴት እንደሚቆሙ ተመልከቱ እውነታውን ታያላችሁ ።
       በሶላት ላይ አይን መጨፈን የነብዩን አስተምሮና ተግባር የሚፃረር ነው ። ምክንያቱን የአላህ መልእክተኛ አንድ ሰው ሱትራ አድርጎ እየሰገደ እያለ ከፊት ለፊቱ የሚያቋርጠው ከመጣ ይከልክለው እንቢ ካለ ይጋደለው ሸይጣን ነውና ብለዋል ።  ታዲያ አይኑን ከጨፈነ እንዴት ነው የሚያየው ? !!! የሰሯቸው ተግባራትን ምን ይሉዋቸዋል ? ሶላትን በተመለከተ ቱሩፋቶቹን እንጂ ህግጋቶቹን መማር የለም ። ህጉ ያልተጠበቀ ሶላት ቱሩፋቱ ኬት ይመጣል የሚለው ጥያቄ መልስ ይፈልጋል ።

          አል ዒልሙ መዓ ዚክር

          ሌላኛው የዳዕዋቸው መርህ ዒልምና ዚክር የሚል ነው ። የተብሊግ ጀማዓዎች ሐቂቃውን ስናይ ከዒልም ጋር ጥለኛ ናቸው መታረቅም አይፈልጉም ። ምክንያቱ ደግሞ ከላይ እንዳየነው ከጁሁድ ወደ ኋላ ያደርጋል የሚል የተሳሳተ እይታ ነው ። ተብሊጎች ጋር ዒልም የሚባለው ፈዳኢሉል አዕማል ( የስራ ቱሩፋቶች) ላይ ብቻ ያተኮረ ነው ። ከቁርኣን አንቀፆች 10ሩን ብቻና ካጠቃላይ ሸሪዓ ሪያዱ ሳሊሒን ከሚለው ኪታብ ውስጥ ኪታቡል ፈዳኢል የሚለው ብቻ ነው ። ከዚህ ውጪ ሓያቱ ሶሓባና ተብሊጊዩ ኒሷብ የሚባሉ በመውዱዕ ሐዲሶች የተሞሉ ኸዋስ የሆኑት የሚያዩዋቸው ኪታቦች አሉ ። ከኪታቡል ፈዳኢል ውስጥ ፈድሉ ቂራኣቲል ቁርኣን ( የቁርኣን መቅራት ቱሩፋት) ፣ ፈድሉ ሶላት ( የሶላት ቱሩፋቶች )ና የመሳሰሉት ናቸው የሚቀሩት ። ስለ ዐቂዳ ፣ ስለፊቅህ ፣ ስለ ተፍሲር ፣ ስለሐዲስ ፣ ስለውርስ ፣ ስለቡዩዕ ፣ ስለ ጂናያት ፣ ስለ ቂሷስ ፣ ስለ ሐላልና ሐራም ፣ ስለ ተውሒድና ሽርክ ፣ ስለ ሱናና ቢዳዓ መማርም ሆነ ማስተማር ጊዜ ማባከን ነው ይላሉ ። በመሆኑም አንድ ሰው በተብሊግ 30 ወይም 40 አመት ቢቆይም ከእነዚህ ውጪ ማወቅ አይችልም ። ቢያውቅም ማስተማር አይፈቀድለትም ። ለዚህ ነው ተብሊጎች ጋር የተለያዩ የሽርክ ፣ የቢዳዓና የፊስቅ ተግባሮችን የምናየው ። ብዙ አመት ተብሊግ ላይ የቆየ አንድ ሰው አጅ ነብይ ሲጨብጥ አብሮ ሲበላና ሲጠጣ ማየት የተለመደ ነው ። ከዚህ በላይ ቀብር በሚመለክባቸው ቦታዎች ላይ ከፊት ለፊት ታገኛቸዋለህ ። ወንድና ሴት አብረው ቁጭ ብለው ጫት ሲቅሙ ታያለህ ይህ ለእነርሱ ምንም አይደለም ። ሐራም ነው ካልክ ወሀብይ ትባላለህ ። !!!
      ዒልምን አስመልክቶ ቁርኣንና ሐዲስ ላይ የመጡ መረጃዎችና የኢስላም ሊቃውንቶች ንግግሮች ተብሊጎች ዘንድ ቦታ የላቸውም ። ሰው በጁሁድ ነው ኢማኑ የሚጨምረው የሚለው ያልተገደበ ልቅ እሳቤ ይዟቸው እየጠፋ መሆኑን አያውቁም ።
      ያለ እውቀት የሚሰራ ስራ ትርፉ ድካም መሆኑ የኢስላም ጮራ ከመፈንጠቁ ነው የታወጀው ። ለዚህ ነው የኢስላም ሊቃውንቶች ያለ እውቀት የሚሰራ ሰው ከነሳራዎች ጋር አውቆ የማይሰራ ደግሞ ከአዩሁዶች ጋር ይመሳሰላል የሚሉት ። በመሆኑም ዒልም ( እውቀት)  ከንግግርም ከተግባርም ይቀድማል ብሎ ታላቁ የሐዲስ ሊቅ ኢማሙል ቡኻሪይ በሶሒሑ ላይ ባብ ያደረገው ። ይህ ከመለኮታዊው የሕይወት መመሪያ ከሆነው የአላህ ቃል የተወሰደ ነው ። አላህ መጀመሪያ በነብዩ ላይ ያወረደው ቃል 
اقْرَأْ بِاسْمِ رَبِّكَ الَّذِي خَلَقَ

" አንብብ በዚያ (ሁሉን) በፈጠረው ጌታህ ስም "  ፡፡
በሚል የመጣው ። ይህ የኢስላም አስተምሮ ለእውቀት ያለውን ቦታ ምን እንደሚመስል የሚያሳይ ነው ። ተብሊጎች ይህን መርህ ትተው በራሳቸው ፍልስፍና ልፋት እንጂ እውቀት አያስፈልግም ብለው ኢስላምን ከስሩ እየናዱት ይገኛሉ አላህ ይመልሳቸው ።
        አላህ ሐቅን አውቀው ከሚከተሉና ባጢልን አውቀው ከሚርቁ ባሮቹ ያድርገን ።

       አላህ ካለ ይቀጥላል ።

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

08 Nov, 18:47


Live stream finished (3 hours)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

08 Nov, 15:39


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

08 Nov, 15:39


ሰምንተዊ የቁሪአን ተፊስር ልጀምር ነዉ
ገባ
       ገባ
                በሉ
https://t.me/abuhatimaselefiy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

07 Nov, 15:49


የስነ-ምግባር ብልሽት
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯


🏝 በዚህ ዘመን ወጣቶች በተለያዩ ተፅዕኖዎች ምክንያት የስነ-ምግባር ቀውስ ውስጥ ገብተናል። አዎ በሽታችንን ለመደበቅ መሞከር የለብንም። ‟በሽታውን የደበቀ ሞቱ ግልፅ ያደርግለታል„ ከሚባሉት መሆን የለብንም። እንደውም ከራሳችን ጋር ተሳስበን ወደ አላህ መመለስ እና የፀባይ ለውጥ ማድረግ አለብን።

በዚህ ዘመን አንድ ወንድም እንደ አይን ብሌን የሚሳሳላት የእናትቱ ልጅ ትንሽ እህቱ ❝ወንድሜ ሆይ! ጥሩ ባል ፈልግልኝ❞ ብትለው «እሽ እህቴዋ ኢንሻአላህ» ለማለት ይሳቀቃል። ምክንያቱም ወጣቱ በሀይለኛው በምግባር ብልሽት ወረርሽኝ ተለክፏል። ለአቂዳችን ጤነኝነት ለመንሃጃችን መስተካከል የምንጓጓውን ያክል ስነ-ምግባራዊ ለውጥ ለማምጣትም ጥረቶችን ማድረግ አለብን።

👌 በዚህ ጉዳይ ብዙ ከማለት የሚያብቃቃኝ የሚቀጥለው የኡስታዝ ባህሩ ተካ ምክር ነው።

👌 በዚህ ጉዳይ ብዙ ከማለት የሚያብቃቃኝ የሚቀጥለው የኡስታዝ ባህሩ ተካ ምክር ነው።
👉 የሰለፍይ ስነ-ምግባር
➪➩➪➩➪➩➪➩➧

የተከበራችሁ ውድ ሰለፍይ ወንድምና እህቶች አብዛኞቻችን የሰለፍያ ዐቂዳን የተረዳንበት መንገድ ትክክል ነው ለማለት የሚያስደፍር ስለማይመስል ለግንዛቤ ይሆን ዘንድ ስነ-ምግባርና ተያያዥ ባህርያቶች ከዐቂዳችን ጋር ያላቸው ግንኙነት ለመግለፅ ወደድኩኝ

➜ የሰለፍያ ዐቂዳ ለዋዚሞችና ፍሬዎች እንዳሉት ማወቅ በሁላችንም ላይ ግዴታ ነው። አንድ ሰው ዐቂዳው የተስተካከለ ከሆነ ይህ የተስተካከለ ዐቂዳ ግድ የሚላቸውና የሚያፈራቸው ፍሬዎች ይኖራሉ። የተስተካከለ ዐቂዳ ግድ ከሚላቸው ባህሪያቶች ውስጥ ጥቂቶቹን ለማየት፦
➩ ከውሸት፣
➪ ከማታለል፣
➩ ከሌብነት፣
➪ ወሬ ከማቀበል፣
➩ ሰው ከማጣላት፣
➪ ከሀሜት፣
➩ እምነት ከማጉደል፣
➪ ቃል ከማጠፍ፣
➩ ቀጠሮ ከማፍረስ፣
➪ የወላጆችን ሀቅ ካለመጠበቅ፣
➩ ጎረቤትን አዛ ከማድረግ፣
➪ ጓደኛን ከማስቀየም፣
➩ ከምቀኝነትና
ከመሳሰሉ ተግባሮች መራቅ ይገኙበታል።

የተስተካከለ ዐቂዳ ከሚያፈራቸው ፍሬዎች ጥቂቶቹን ለማየት
➫ መልካም ስነምግባር፣
➬ አዛኝነት፣
➫ ሰውንማክበር፣
➬ በትንሹ መብቃቃት፣
➫ እውነተኝነት፣
➫ ታማኝነት፣ እንዲሁም ከላይ የጠቀስናቸው ባህሪያት ተቃራኒያቸውን ማስገኘት ይገኙበታል።
በመሆኑም አሁን የምናያው የአብዛኛውዎች ሰለፍዮች ስነምግባር ከዚህ በእጅጉ የራቀ መሆኑ ትክክለኛ ዐቂዳ ምን እንደሆነ ካለመረዳት የመነጨ እንደሆነ ያመለክታል። ትክክለኛ ዐቂዳ ሙሉ እንዲሆን እየጨመረ እንዲሄድ እነዚህ ስነ-ምግባሮች ጉልህ ሚና ይጫወታሉ። በተቃራኒው የእነዚህ ስነ-ምግባሮች አለመስተካከል ዐቂዳች ሩሕ የሌለው በነዘሪያት (ከተግባር ባገለለ እይታ) ላይ የተመሰረተ እንዲሆን ያደርገዋል። ትክክለኛ ዐቂዳ መልካም ስነምግባር ቅባቱ ነው። ይህ ካልሆነ ዐቂዳችን ጎምዛዛ በሰዎች ላይ ተፅኖ የማይፈጥር ይልቁንም ሰዎችን ከትክክለኛ ዐቂዳ እንዲርቁ የሚያደርግ ሊሆን ይችላል። ለዚህ ነው መልካም ስነምግባ በእስልምና በጣም ትልቅ ቦታ የተሰጠው። አንድ ሰው በምንም ነገር ሊደርሰው የማይችለውን የኢማን ማማ ላይ እንዲደርስ የሚያስችለው መልካም ስነምግባር ነው የተባለው። በመሆኑም አብዛኞቻችን ራሳችንን መፈተሽ ይገባናል።

➨ ሰለፍይነት በሙኻሊፍ ላይ መልስ መስጠት፣ ከእነርሱ ማስጠንቀቅ፣ እነርሱን መጥላት ብቻ አይደለም። ይህ በጣም ተፈላጊ ከመሆኑ ጋር ስነምግባራችን እንደ አባጨጓሬ የሚኮሰኩስ ከሆነ ለሰዎች ሂዳያ ሰበብ ልንሆን አንችልም። ይልቁንም ሰዎች የሰለፍያን ዳዕዋ እንዲጠሉ ሊያደርጋቸው ይችላል። ከዚህ የከፋው ደግሞ በእጃችን ላይ ያሉ ወንድሞች በከፊሎቻችን ያልተገባ ስነምግባር ከእጃችን ሊወጡ ይችላሉ ይህ ደግሞ ካፒታልን ማጣት ማለት ነው።

እንደሚታወቀው ካፒታልን መጠበቅ ትርፍ ከመፈለግ ቅድሜያ የሚሰጠው ተግባር ነው። እየአንዳንዱ ሰለፍይ ሌላውን የመጠበቅ ሀላፊነት አለበት። ክፍተት ሲኖር ክፈተቱን መዝጋት፣ ድክመቱን ለማስወገድ መጣር በጣም አስፈላጊ ነው። በኛ አላስፈላጊ ስነምግባር የሰለፍያ ገፅታ መበላሸት የለበትም ለዚህ ሰበብ ከመሆን መጠንቀቅ አለብን አላህ ይርዳን።

📝 በኡስታዝ ባህሩ ተካ አቡ ዑበይዳህ አላህ ይጠብቀው @bahruteka

ወዳጄ ሆይ! ሰለፎቻችንን መከተል ማለት በሁሉም ነገራችን እንጂ በከፊሉ ማንነታቸው ጠንካራ ሆነን ልንኮፈስ አይደለም። የሰለፎችን ህይወት 100% ማሟላት እንደማንችል ግልፅ ነው። ነገር ግን በሁሉም የህይወት እንቅስቃሴዎቻቸው ለመመሳሰል መሞከር አለብን። እራሳችንን እንተሳሰብ! እስኪ ማንነታችንን እንፈትሽ! ወደ አላህ እንመለስ! ስነ-ምግባርን ማስተካከል የማይቻል ተፈጥሯዊ ችግር አይደለም። ልክ እንደአቂዳህ እንደመንሃጅህ የምታስተካክለው ጉዳይ ነው። አብሽር ወደ አላህ እንቅረብ እንጂ እንስተካከላለን።

📝 ያንተንም የሱንም መስተካከል የሚመኘው ወንድምህ አቡ ዒምራን!

በ 𝐓𝐞𝐥𝐞𝐠𝐫𝐚𝐦~𝐂𝐡𝐚𝐧𝐧𝐞𝐥
🏝 ⇣⇣⇣🍭⇣⇣⇣📲 ⇣⇣⇣↙️
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

06 Nov, 18:39


ህገ መንግስቱና የመጅሊስ ደብዳቤ

የዛሬ 12 አመት 2005 አካባቢ የኢሀድግ መንግስት ከሉብናን የአሕባሽን አስተሳሰብ አስመጥቶ የኢትዮዽያ ሙስሊሞች ይህን አስተሳሰብ መቀበል አለባቸው ብሎ በእጅ አዙር መጅሊሱን ይመራው በነበረ ጊዜ ከታሰሩት ውስጥ ነበርኩ ። በወቅቱ ሳሪስ ብሄረ ፅጌ አካባቢ እኖር ነበር ። እግሬ ተሰብሬ በተኛሁበት የመሰጂድ ሀላፊ የነበረ ሙሐመድ አማን የሚባል ግለሰብ ከትላልቅ የዐለም አሸባሪዮች ጋር ግንኙነት ያለው የሀገር ስጋት የሆነ አሸባሪ ነው ብሎ በፀጥታ ሀይሎች እንድያዝ ያደርጋል ።
እነዚህ ጭንቅላታቸው ውስጥ አስፈሪ ስእል የተሳለባቸው ሲቪል የፀጥታ አካላት ተከራይቼ ወደ ምኖርበት ቤት መጥተው በከፍተኛ ጥንቃቄ አስጠርተውኝ ስወጣ ሁለቱ ከጊቢው በር ግራና ቀኝ ሁለቱ ከፊት ለፊ ሆነው የተቀባበለ ሽጉጥ ጣታቸውን ቃታው ላይ አድርገው ይዘው ይጠብቁ ነበር ። ቢጃማ ለብሼ ጀሶ የታሰረበትን የተሰበረው እግሬን እየጎተትኩኝ ሲያዩ በመደናገጥ ስሜት ኡስታዝ ባህሩ አንተ ነህ ወይ አሉኝ ። አው አልኳቸው ሁሉም እጃቸውን ወደ ኪሳቸው በመክተት መሳሪያቸውን ደበቀው አንዴ ለጥያቄ ተፈልገህ ነበር አሉኝ ። እኔም እሺ ልብስ ልቀይር ከፈቀዳችሁልኝ አልኳቸው ። እነርሱም አይ መቀየር አያስፈልግም ትመለሳለህ ና አሉኝ ። እሺ መታወቂያ ልያዝ አልኳቸው ነገር ግን ወደ ቤት ልገባ ሊፈቅዱልኝ አልቻሉም ። መታወቂያ አምጡልኝ ብዬ ወደ ቤት ስልክ በጣም ተደናግጠው ስለነበረ የሐኪም ቤት ካርድ ላኩልኝ አዩትና በቂ ነው አሉኝ ። ተያይዘን ወጣን ቀስ እያልኩ እንደምሄድና ቶሎ መሄድ እንደማልችል ነገርኳቸው ። እነርሱም በተረጋጋ ስሜት ና ብለውኝ ከፊት ፊት እያወሩ መሄድ ጀመሩ ። ቆየት እያሉ ዞር ብለው ያዩኛል እኔም እከተላቸዋለሁ ። በዚህ ሁኔታ ሳሪስ ፖሊስ ጣቢያ ደረስን ። ሁለቱ ወደ ውስጥ ገብተው ሁለቱ ከኔ ጋር ቆዩ ። የገቡት ተመልሰው መጥተው ወደ ፔፕሲ ፖሊስ ጣቢያ ደርሰን እንመጣለን አሉኝ ። አስረክባችሁኝ ወደ ስራችሁ እንደምትሄዱ አውቃለሁ ችግር የለም አልኳቸው ። መኪና ውስጥ ገባን ፔፕሲ ደርስን ቀድመው ወርደው ቀስ ብዬ እስከ ምወርድ ጠብቀው ወደ ምርመራ ክፍል ማምራት ጀመርን ። ብዙ ፖሊሶች ባሕሩ ተያዘ እያሉ ጮኹ !!! ማንን ነው እኔን ወይስ ሌላ ባሕሩ ብዬ ራሴን ጠየቅሁ ግን ወዲያው እኔን እንደሆነ ገባኝ ።
እንዳልኩትም አስረክበውኝ ወጡ ። ሶስት መርማሪዮች እየተቀያየሩ ለሁለት ሰአት ተኩል ያክል በጥያቄ አቆዩኝ ። የተከሰስኩት ያለ ፈቃድ በማስተማርና በካፊር መንግስት አንመራም ተነሱ ጂሀድ ውጡ ብለህ በጁሙዓ ቀን ቀስቅሰሀል በሚል ነበር ። ያለ ፈቃድ ማስተማሬን አምኜ ሁለተኛውን ክስ መሰረተ ቢስ መሆኑን አስረግጬ ተናገርኩ ። ለዚህ ትልቁ ማሳያ ያደረኩት ቀስቅሰሀል የተባልኩት ከሶስት ወር ከ15 ቀን በፊት ነው የሚል መሆኑ ነበር ። ውድቅነቱን ሳስረዳ ይህ እውነት ከሆነ መንግስት የለም ማለት ነው ። መንግስት ቢኖር ኖሮና የተባለው እውነት ቢሆን ወዲያው ተይዤ ለምርመራ መቅረብ ነበረብኝ አልኩኝ ። ይህ እውነታ የዚህን ክስ ጭብጥ ወዲያው ህይወት አልባ እንዲሆን አድርጎት ነበር ።
ቅዳሜ ስለነበር የተያዝኩት ሰኞ ፍርድ ቤት ቀረብኩ ጁማዐለት ላፍቶ መስጂድ ላይ ድምፃችን ይሰማ ብላችኋል ተብለው የተያዙ ብዙ ሙስሊሞች ስለነበሩ ተራ እስኪደርሰኝ ቆይቼ ነበር ። ተራ ደርሶኝ ዳኛ ፊት ቀረብኩ ዳኛው ማናገር ጀመረ : –
– አቶ ባሕሩ የተከሰሱበትን ጉዳይ ያውቃሉ ወይ አለኝ ።
– አው አልኩኝ ።
– ምንድነው አለኝ በካፊር መንግስት አንመራም ጂሃድ ተነሱ ብሎ በመቀስቀስና ያለ ፈቃድ ማስተማር የሚል ነው አልኩኝ ።
– ያለ ፈቃድ ታስተምራለህ ወይ ተባልኩ ።
– ክቡር ዳኛ ከዚህ የመጀመሪያው ክስ እኮ ነው ከባዱ ስለሱ አይጠይቁኝም ወይ አልኩኝ ።
– እሱን ተወው ተባልኩ ።
– ክሱ ውዳቂ እንደሆነ ተረዳሁ ወደ ፈቃዱ ተመልሼ መልስ መስጠት ጀመርኩ ።
– ያለፈቃድ ታስተምራለህ ወይ የሚል ጥያቄ ተደገመ ።
– አይ ፈቃድ አለኝ አልኩኝ ።
– አቶ በሕሩ ማሳየት ትችላለህ ወይ ተባልኩ ።
– እኔም ክቡር ፍርድ ቤት ህገ መንግስቱ ለዜጎች የሰጠው እምነትን በነፃነት የመማር ማስተማር መብት አለኝ አይደለም ወይ ከዚህ ሌላ ምን አይነት ፈቃድ ያስፈልገኛል አልኩኝ ።
– ዳኛው መርማሪውን ቀና ብሎ አይቶ ሌላ የምን ፈቃድ ነው የሚያስፈልገው ብሎ ጠየቀው
– መርማሪውም መጅሊሱ ማንም ሰው ያለኛ ፈቃድ ማስተማር አይችልም ብሎ ደብዳቤ ፅፎልናል አለ ።
– ዳኛው እየፃፈ እያለ ክቡር ዳኛ ህገ መንግስቱ ለዜጎች የሰጠው መብት በመጅሊስ ደብዳቤ ከተሻረ የሚሆውን ለመቀበል ዝግጁ ነኝ አልኩኝ ።
– ዳኛው አይ አልተሻረም መብትህ ነው ብሎኝ በ1500 ብር ዋስ ከእስር እንድፈታ ትእዛዝ ሰጥቶ ወጣሁ ።
አሁንም በየደረጃው ያሉ ባለስልጣናት ህገመንግስቱ ለዜጎች የሰጠውን መብት በመጅሊስ ደብዳቤ ተሽሯል የሚል አይነት እርምጃ ከመውሰዳቸው በፊት ቆም ብለው ሊያጤኑት ይገባል እላለሁ ።

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

05 Nov, 07:41


እዚህ ጋር አንድ ገጠመኝ ላካፍላችሁ :– አንድ ቀን ሰፈራች ያለ መስጂድ ላይ ፓኪስታኖች መጥተው ነበር ። ከዙህ ሶላት በኋላ አንድ ፓኪስታኒ ተነስቶ ዳዕዋ ማድረግ ጀመረ ። ከጎኑ አንድ የኛ ሰፈር የተብሊግ ጀማዓ አባል የሆነ ልጅ ተነስቶ ማስተርጎም ጀመረ ። እኔ ተነስቼ እየወጣሁ ነበርና በጣም ገርሞኝ ይሄ ልጅ እንዴት ፓኪስታንኛ አወቀ እያልኩ ሳስብ አንድ ሌላ ሰው ተከትሎኝ ወጣ ። እኔም ይሄ ልጅ ፓኪስታንኛ የት አወቀ ብዬ ጠየቅሁት እሱም እየሳቀ ተብሊጎች እኮ የአለም ቋንቋ ያውቃሉ አለኝ ። እንዴት አልኩት ምክንያቱም የእነርሱ ዳዕዋ በይትኛውም ቋንቋ ቢደረግ አንድ አይነት ስለሆነ ተነስተው ያስተረጉማሉ ። በዚህም ሁሉንም ቋንቋ የሚችሉ በማስመሰል ሰውን ይሸውዳሉ አለኝ ።

አላህ ካለ ይቀጥላል ።

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

05 Nov, 07:41


🔷 የተብሊግ ጀማዓዎች ማን ናቸው

ክፍል ሶስት

ስድስቱ የሶሓባ ሲፋዎች

የተብሊግ ጀማዓዎች በዐለም ላይ በየትኛውም ሀገር በየትኛውም ቋንቋ በየትኛም ደረጃ የዳዕዋቸው መሰረት አድርገው የሚጠቀሙበት 6 የሶሓባ ባህሪዮች ከነ መክፈቻቸው የሚሏቸው ነጥቦች አሉ ። እነዚህ ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው : –

አንደኛ – ላኢላሃ ኢልለላህ ( ሚፍታሑል ጀናህ)
ሙሐመድ ረሱሉላህ ( ሚፍታሑል
ሂዳይ )
ሁለተኛ – ሶላት በኹሹዕና ኹዱእ ( ሚፍታሑል
ኸዛኢን)
ሶስተኛ – ዒልምና ( ሚታሑል መዕሪፋ)
ዚክር ( ሚፍታሑል ኸሺያ)
አራተኛ – ሙስሊሞችን ማክበር ( ሚፍታሑል
ቁሉብ )
አምስተኛ – ንያን ማስተካከል ( ሚፍታሑል
ቀቡል)
ስድስተኛ – ወደ አላህ መጣራት ( ሚፍታሑ
ዲን)
ኹሩጅ መውጣት ( ሚፍታሑ ነሽሪ
ዲን)
እነዚህ ስድስት ባሕሪዮች የተብሊግ ጀማዓዎች ዘንድ ዳዕዋ የሚደረግባቸው ነጥቦች ሲሆኑ በየትኛውም የእውቀት ደረጃ ላይ ያለ ሰው ከዚህ መውጣት አይችልም ። መውጣት አለመቻል ብቻ ሳይሆን በጀማዐው መመሪያ መሰረት ከተቀመጠው ማብራሪያ ውጪ ማብራራትና ትርጉም መስጠት አይቻልም ። ለዚህ ማሳያ የመጀመሪያውን ሲፋ ( ባሕሪይ) ብንመለከት : –
– ላ ኢላሃ ኢልለላህ ማለት :–
ኢኽራጁ የቂኒልፋሲዲ ዐኒል አሽያዪ ወኢድኻሉል የቂኒ ሳዲቂ ዓለላህ ( የተበላሸ የቂን ከነገሮች ላይ ማውጣትና እውነተኛ የቂን በአላህ ላይ ማድረግ ) የሚል ነው ። ለዚህ ነው በየትኛውም ዐለም ያሉ የተብሊግ ጀማዓዎች በየትኛውም ቋንቋ ላ ኢላሃ ኢልለላህ ማለት የፈጠረን አላህ ነው ማለት ነው ፣ የሚገለን አላህ ነው ማለት ነው ፣ የሚቀሰቅሰን አላህ ነው ማለት ነው ። የሚያበላን አላህ ነው ማለት ነው ፣ የሚሉት ። ይህ በየትኛውም እምነት ውስጥ ያሉ ሰዎች የሚያምኑበት ሲሆን የመካ አጋሪያኖችም በዚህ ያምኑ እንደ ነበር አላህ በተከበረው ቃሉ በተለያዩ አንቀፆች ላይ ነግሮናል ። ከላይ ለመጥቀስ እንደሞከርኩት የተብሊግ ጀማዓ ዘንድ አንድ ሰው በየትኛውም የእውቀት ደረጃ ላይ ቢሆን ከዚህ መውጣት አይችልም ። በሌላ አባባል ተብሊጎች ጋር ሁሌም አንደኛ ክፍል ነህ ሁለተኛ ክፍል የሚባል ነገር የለም ። ከላይ የተጠቀሱት የላ ኢላሃ ኢልለላህ ትርጉም የሚሉት ፍልስፍና ከቁርኣንና ሐዲስ አስተምሮ ጋር የማይሄድ ሲሆን ነባራዊው ሁኔታ ውድቅ ያደርገዋል ። የአላህ መልእክተኛ የመካ አጋሪያኖችን ላ ኢላሃ ኢልለላህ በሉ ሲሏቸው በመገረም የሰጡዋቸው መልስ አላህ ሲነግረን እንዲ ይለናል : –

« أجَعَلَ الْآلِهَةَ إِلَٰهًا وَاحِدًا ۖ إِنَّ هَٰذَا لَشَيْءٌ عُجَابٌ»
ص ( 5 )
«አማልክቶቹን አንድ አምላክ አደረጋቸውን? ይህ አስደናቂ ነገር ነው» (አሉ)፡፡
ይህ ማለት ሙሽሪኮቹ የላ ኢላሃ ኢልለላህ ትርጉም :–
" ከአላህ በስተቀር በእውነት የሜመለክ ሌላ አምላክ የለም " የሚል መሆኑን ያውቁ ነበር ማለት ነው ። ምክንያቱም ፍጥረተ ዐለሙን የሚያስናብረው አላህ መሆኑን ያውቁም ያምኑም ስለነበር ። ይንም አስመልክቶ ከመጡ አንቀፆች ውስጥ የሚከተለው ይገኝበታል : –

« وَلَئِن سَأَلْتَهُم مَّنْ خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ وَسَخَّرَ الشَّمْسَ وَالْقَمَرَ لَيَقُولُنَّ اللَّهُ ۖ فَأَنَّىٰ يُؤْفَكُونَ»
العنكبوت ( 61 )
" ሰማያትንና ምድርን የፈጠረ ፀሐይንና ጨረቃንም የገራ ማን እንደኾነ ብትጠይቃቸው «በእርግጥ አላህ ነው» ይሉሃል፡፡ ታድያ እንዴት ይመለሳሉ " ፡፡

« وَلَئِن سَأَلْتَهُم مَّن نَّزَّلَ مِنَ السَّمَاءِ مَاءً فَأَحْيَا بِهِ الْأَرْضَ مِن بَعْدِ مَوْتِهَا لَيَقُولُنَّ اللَّهُ ۚ قُلِ الْحَمْدُ لِلَّهِ ۚ بَلْ أَكْثَرُهُمْ لَا يَعْقِلُونَ »
العنكبوت ( 63 )
" ከሰማይም ውሃን ያወረደና በእርሱም ምድርን ከሞተች በኋላ ሕያው ያደረጋት ማን እንደኾነ ብትጠይቃቸው «አላህ ነው» ይሉሃል፡፡ «ምስጋና ለአላህ ነው» በላቸው፡፡ ግን አብዛኞቻቸው አያውቁም " ፡፡
የመካ አጋሪያኖች አላህ ሰማይና ምድርን የፈጠረ ከሰማይ ዝናብ አውርዶ ከምድር ቡቃያ የሚያበቅለው አላህ እንደሆነ ያምኑ ነበር ። ላ ኢላሃ ኢልለላህ ማለት ትርጉሙ ይህ ቢሆን አንቀበልም አይሉም ይልቁንም ታዲያ ከአላ ሌላ ማን ነው ይሉ ነበር ። ነገር ግን ትርጉሙ ከአላ ሌላ የሚመለክ እርዳኝ ፣ ድረስልኝ ፣ ጠብቀኝ ፣ አድነኝ ፣ አክብረኝ ተብሎ የሚመለክ የለም ሲባሉ አይ አለ እነ ሁበል ፣ ላት መናትና ዑዛ ይደርሳሉ ፣ ይረዳሉ ፣ ይሰጣሉ ፣ ያከብራሉ ለጠራቸው ይደርሳሉ የሚል እምነት ስለነበራቸው ነው አማልክቶቹን አንድ አምላክ አደረጋቸው ( ከአላህ ሌላ የሚሰጥ ፣ የሚጠብቅ ፣ የሚደርስ ፣ የሚሰማ ፣ ከጭንቅ የሚያወጣ የለም) አለ ብለው የተገረሙት ።
የተብሊግ ጀማዐዎች በየመስጂዱ በየቋንቋው ተነስተው ቆመው የፈጠረን አላህ ነው ማለት ነው የሚገለን አላህ ነው ማለት ነው ሰማይን የፈጠረው አላህ ነው ማለት ነው እያሉ ከቆጠሩ በኋላ ላ ኢላሃ ኢልለላህ ይላሉ ። ይህ የተሳሳተ ከሽርክና ኩፍር የማያወጣ አስተምሮ ነው ። ዑለሞች ይህ አስተምሮ ተሕሲሉል ሓሲል ( የሚታወቅን ነገር ማሳወቅ ) ነው ይሉታል ። ወይም ይህ ማለት ለአንድ ዑብዱላሂ ፣ አሕመድ, ሰዒድ, ኸድር የሚባሉ ልጆች ላሉት አባት ሄዶ አንተ እኮ ዐብዱላሂ የሚባል ልጅ አለህ ማለት ነው ፣ አሕመድ የሚባል ልጅ አለህ ማለት ነው ፣ ሰዒድ የሚባል ልጅ አላህ ማለት ነው ፣ ኸድር የሚባል ልጅ አለህ ማለት ነው ። እንደማለት ነው ምክንያቱም አባት ልጆቹን ያውቃቸዋል ። አንተ መጥተህ የልጆቹን ስም እንደማያውቅ አድርገህ ስትነግረው ምናልባት አእምሮህ ትክክል አይደለም ሊልህ ይችላል ።
የዚህ የተሳሳተ የላ ኢላሃ ኢልለላህ ትርጉም ነው የተብሊግ ጀማዓዎችን ቀብር አምላኪዮች እንዲሆኑ ያደረጋቸው ። ምክንያቱም አንድ ሰው የነገሮች ፈጣሪ አላህ መሆኑን ካመነ ሙስሊም ነው ኢማን አለው ብለው ስለሚያምኑና የተለያየ የአምልኮ አይነት ከአላህ ውጪ ላለ አካል መስጠት ችግር የለውም ብለው ስለሚያምኑ ። ይህ በመሆኑ ነው የተለያዩ ወልይ ተብለው የሚመለኩ መሻኢኾች ሀድራዎች ላይ ዋና ኻዲም ሆነው የምናገኛቸው ። የተብሊግ ጀማዓዎች ዳዕዋ ወጥና የማይቀየር በመሆኑ የትም ሀገር ሄደህ ዳዕዋ ስታደርግ የዛ ሀገር ቋንቋ ተናጋሪ ተነስቶ ለማስተርጎም ከጎንህ ይቆማል ። ይህ ማለት አስተርጓሚው ያንተን ቋንቋ አውቆ ሳይሆን በየትኛውም ቋንቋ የሚነገረው ዳዕዋ አንድ ስለሆነ ነው ።

Abu hatim Abduselam Assalefiy

05 Nov, 07:41


📌ቢድዓ የሽርክ ጓደኛ ነው

ሽርክ የጌታን ክብር ከማጓደል ጋር የተቆራኘ ነው፡፡ ሙሽሪኩ ወደደም ጠላም ፣ የጌታን ክብር ማጓደሉ  ከእርሱ ጋር የማይላቀቅ ጉዳይ ነው፡፡  በዚህ ምክንያት ሙሽሪክ ፍጹም እንደማይማር ተመስጋኝነቱ ፣ ፈጣሪነቱ ፣ ሙሉነቱ የወሰነው ጉዳይ ሆኗል - የሽርክ ባለቤት ዘወትር በአሳማሚ ቅጣት እንደሚቀጣም እንዲሁ፡፡ ከፍጡራኖች ሁሉ በጣም ጠማማ ያደርገዋል፡፡ አንድን ሙሽሪክ አታገኘውም - በማጋራቱ አላህን አልቃለሁ ብሎ ቢሞግትም - የአላህን ክብር የሚቀንስ ቢሆን እንጅ፡፡

በተመሳሳይ አንድን ሙብተዲእ አታገኘውም ፣ የረሱልን ክብር  የሚያጓድል ቢሆን እንጅ - በቢድዓው ለረሱል ክብር ሰጥቻለሁ ብሎ ቢሞግትም፡፡  ተጎታች ጃሂል ከሆነ ቢድዓ  ከሱና የተሻለች ወይም ከሱና ተቀዳሚ  ወይም  እርሷ ሱና ናት ብሎ ይሞግታል፡፡ ጮሌ ከሆነ ደግሞ በቢድዓው አላህና ረሱልን ይቀናቀናል፡፡

ከአላህ ፣ ከረሱል እና ከአማኞች ዘንድ ጎደሎዎች ፡  የሽርክ ባለቤቶች እና የቢድዓ ባለቤቶች ናቸው፡፡ በተለይም ፣  ‘የአላህና የረሱል ንግግር ባዶ ቃላት እንጅ  ከእውቀት ፣ በእምነት እርግጠኛ ከመሆን የተራቆተ ነው’ በሚል አመለካከት ላይ ዲኑን የመሰረተ አካል ከሆነ፡፡

ልክ እንደዚሁ መመሳሰልን እና ለአላህ የፍጠራንን የመሰለ አካል ሊኖረው ይችላል በሚል ስጋትና ብዥታ ከፈጣሪ ላይ ሙሉ የሆኑትን ባህሪያቶችን ያራቆተ ሰው ፣ አላህ ነፍሱን በገለጸበት የተሟላ ባህሪ ተቃራኒ ጉድለትን አመጣ፡፡ 

ተፈላጊው አላማ ፡   እነዚህ ሁለት ጭፍራዎች በሀቂቃ የአላህን እና የመልክተኛውን መብት አጓዳዮች ናቸው፡፡ ይልቁንም እነዚህ ሁለት ጭፍራዎች ከሰዎች ሁሉ የአላህንና የረሱልን ክብር በማጓደል ከፍተኛውን ድርሻ ይወስዳሉ፡፡ የአላህን ክብር ማጓደልን ፣ ለእርሱ ሙሉ ክብር እንደመስጠት አስመስሎ   ሰይጣን በእነርሱ ላይ አምታታባቸው፡፡  በዚህ ምክንያት ቢድዓ የሽርክ ጓደኛ እንደሆነ በአላህ ኪታብ  ተገልጹዋል፡፡ 


قُلْ إِنَّمَا حَرَّمَ رَبِّيَ الْفَوَاحِشَ مَا ظَهَرَ مِنْهَا وَمَا بَطَنَ وَالْإِثْمَ وَالْبَغْيَ بِغَيْرِ الْحَقِّ وَأَن تُشْرِكُوا بِاللَّهِ مَا لَمْ يُنَزِّلْ بِهِ سُلْطَانًا وَأَن تَقُولُوا عَلَى اللَّهِ مَا لَا تَعْلَمُونَ

“ጌታዬ እርም ያደረገው መጥፎ ስራዎችን ከርሷ የተገለጸውንና የተደበቀውን ሐጢአትንም ያላግባብ መበደልንም ፣ ከርሱ ማስረጃ ያላወረደበትነ (ጣዖት) በአላህ ማጋራታችሁን ፣ በአላህም ላይ የማታውቁትን መናገራችሁን ብቻ ነው” በላቸው፡፡

(አእራፍ፡ 33)

ሐጢያትና ድንበር ማለፍ ጓደኛ ናቸው ፤ ሽርክ እና ቢድዓም ጓደኛ ናቸው፡፡

طب القلوب : - ١٧٩-١٨٠

 https://t.me/alateriqilhaq
كن على بصيرة

Abu hatim Abduselam Assalefiy

05 Nov, 07:41


👉 የነሲሓዎች ጥረት ዲን ማስፋፋት ወይስ በዲን መነገድ ?

ከሶሓባ ስም ምርጡን የዐብዱላሂ ኢብኑ መስዑድ ከሐዲስ ስም ደግሞ ምርጡ የሆነውን አድዲኑ ነሲሓ ከሚለው ስም ወስደው በዲን የሚነግዱት ነሲሓዎች እነሞር ወይም ሞት ያሉ ይመስላል ። ምክንያቱ ደግሞ ከላይ እስከታች በድርጅታዊ አሰራር ኔትወርክ ሰርተው የሚበዘብዙት የሀገር ውስጥና የሀገር ውጪ የእነሞር ተወላጅ ምን እየሰራችሁ ነው የሚለው ጥያቄ ይመስላል ።
ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ ለመግለፅ እንደሞከርኩት ያኔ ከእነርሱ ጋር በነበርኩበት ጊዜ እነሞር ላይ ከነበሩት 72 ቀበሌዎች ውስጥ በ2ቱ ላይ በወር 400 ብር ደሞዝ እየከፈሉ ሁለት ኡስታዝ ቀጥረው 3ተኛ ስጠይቃቸው ማለትም በወር 1200 ሊያወጡ ማለት ነው አንተ የተቋሙን ባጀት እንዳለ ወደ እነሞር ልትወስደው ነው የምትፈልገው ብለውኝ ነበር ። ይህ ማለት እነርሱ በወር ከእነሞር ተወላጆች የሚሰበስቡት ገንዘብ በወር ከ100 ሺህ ብር ይበልጥ ነበር ። !!! በዚህ መልኩ ወደ እነሞር ለማሰብ የማይፈልጉ የነበሩ አካላት ዛሬ ላይ ያለ የሌለ ሀይላቸውን ተጠቅመው በዲን ስም እነሞር ላይ መነገድ ይፈልጋሉ ።
የዚህ እንቅስቃሴ ዋነኛው መሪ አቶ አዩብ ደርባቸው ነው ። አቶ አዩብ ማለት ያብሬት ሼይኽ የሴት ልጅ ልጅ ነው ። አያቱ ስልጤንና ጉራጌን በእስልምና ስም ሲያስገብሩት ነበር ። በልጆቻቸው አማካይነት አሁንም እየገበረ ነው ። አቶ አዩብ የከተማውን የጉራጌና ስልጤ ተወላጅ ዘመናዊ ሙሪድ አድርጎ እያስገበረው ሲሆን ገጠሩ ላይ ባሰበው መልክ አልተሳካለትም ። በተለይ እነሞር ላይ በዲን ስም መነገድ የህልም እንጀራ እየሆነበት ነው ። ይሁን እንጂ ከጎኑ ፖለቲከኞችን ፣ አክቲቪስቶችን ፣ ክ/ሀገር ላይ ኪዮክስ ከፍተው የከሰሩ ፣ ከመምህርነት በብድር ወደ ዱባይ ነጋዴነት ሞክረው ያልተሳካላቸው ፣ መካ ላይ ከ20 በላይ ግሩፕ ከፍተው እህቶችን ሲዘርፉ ቆይተው እዚህ መጥተው የተሸሸጉ አካላትን አሰልፎ እንዲሁም ስለሱ ማንነት የማያውቁ ለዲን ነው በሚል ጎራውን የተቀላቀሉ በሞያቸው ህዝባቸውን መጥቀም የሚችሉ አቅም ያላቸው ወንድሞችን ይዞ የማይቆፍረው ጉድጓድ የማይፈነቅለው ድንጋይ የለም ግን አይሳካም ። ምኞቱ ረፍት ነስቶት እንጂ እንደማይሳካ በተደጋጋሚ አይቶታል ።
የአዩብና ግብረአበሮቹ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የሆነው ነሲሓ በተውሒድና ሱና ስም የሰበሰበውን ወጣት ከኢኽዋን ጋር ተደምሮ ካስረከበ በኋላ በዱንያ ጉዳይ ከኢኽዋን ጋር አልሰራም ብሎ እነሞር ላይ ሌላ ቡድን አቋቋመ ። ኢኽዋኖች ቀደም ብለው ያቋቋሙት ወሄ ሜያ የሚል ቡድን እነሞር ላይ የሚንቀሳቀስ የነበረ ቢሆንም በዐቂዳ አንድ ነን ብሎ የተደመረው የነሲሓ ቡድን በገንዘብ ግን አንድ አይደለንም ብሎ ሂዳያ የሚል ቡድን አቋቁሞ እንቅስቃሴ ጀምሯል ። ከልምድ እንዳየነው ይህ ስብስብ እርስ በርሱ ተበላልቶ የሚበታተን ስብስብ ነው ። ምክንያቱም በዲን ስም ለዱንያ የተሰባሰበ ስብስብ በረካ አይኖረውም ። አውቃለሁ ባይ በበዛ ቁጥር ስራ አይሰራም ። የሁሉም ፍላጎት የተለያየ ስለሆነ ሁሉም ፍላጎቱን ለማሳካት መጓተት መገፈታተር ይመጣል ። ማንም ለውድቀቱ ተጠያቄ መሆን አይፈልግም አንዱ ሌላውን አንተ ነህ ምክንያቱ ይላል ። ይህ በተጅሩባ የተረጋገጠ ነው ። አሁንም ይህ የአዩብ ደርባቸው ስብስብ መጨረሻው ክስረት ነው ። ምክንያቱም አቶ አዩብ የእነሞር እናትና አባት በሽርክ ወደ አኼራ መሄድ አሳስቦት አይደለም እየሮጠ ያለው ። ይልቁንም ሩጫው መቶ ሺህ ብር አውጥቶ የሆነ ነገር ሰርቶ ዶክመንተሪ በማሳየት በመቶ አባዝቶ ብር መሰብሰብ ነው ። ለእነሞር እናትና አባት ወይም ትውልድ አስቦ እንዳልሆነ ከላይ ለማሳየት ሞክሬያለሁ ። ሌላው ማሳያ ሶሞኑን ጉንችሬ አንዋር መስጂድ ላይ ባደረጉት ንግግር ነሲሓዎች እነሞር ላይ እንደ ተብሊጝ የወረደ እንደ ባሕሩም ወሰን ያለፈ ሳይሆን ለዘብተኛ ትውልድ መቅረፅ እንደሚፈልጉ ገልፀዋል ። የባሕሩ ወሰን ማለፍ ማለት ያብሬት ሸይኾችን ማምለክ እንደማይቻል ስም ጠርቶ መናገሩ ነው ። እነርሱ ደግሞ ኡሱሉ ሰላሳንና ኪታቡ ተውሒድ ለተበሩክ ወጣቱን ለመያዝ እያስቀሩ ከነባራዊው ሁኔታ ጋር ሳያገናኙ ትውልዱን ማለዘብ ነው ። ለዚህ ነው አይሳካም የምንለው አቶ አዩብ ተሸወደ እንጂ እነሞር ላይ በሺዎች የሚቆጠሩ ከባሕሩ በጣም የሚሻሉ የአላህ ባሮች ተፈጥረዋል እየተፈጠሩም ነው ። ከዚህ በኋላ ከእነሞር ላይ የተውሒድን ብርሃን አደበዝዛለሁ ማለት የፀሀይን ብርሀን በመዳፌ እከልላለሁ እንደማለት ዘበት ነው ። በስሙ የሚነገድበት ትውልድ አይኖርም ተውሒድ ማለት ከሽርክና ከሙሽሪክ መራቅና ማስጠንቀቅ እንደሆነ የተረዳ ትውልድ ቦታውን ተረክቧል ። በተለይ በእነሞር ምድር ላይ በሰልባጅና በትርፍራፊ ዲኑን የሚሸጥ አይኖርም ።
የተውሒድ ብርሃን ቸሓ ላይ ፣ እዣ ላይ ፣ ጉመር ላይ ፣ ጌቶ ላይም አድማሱን እያሰፋ ነው ። የተውሒድን ባንዲራ ከፍ አድርገው የሚያውለበልቡ የአላህ ባሮች እየወጡ ነው ። ይህን ለማጥፋት የሚደራጅ አካል ራሱ እንደሚጠፋ እርግጠኛ ይሁን ። የተውሒድና ሱና እሳት አንዴ ከተለኮሰ እንደማይጠፋ የማያውቅ ምስኪን ትንፋሽ እስከሚያጥረው እፍ ይበል ።
ለማንኛውም ወንድማዊ ምክር የእነሞር ተወላጅ የሆናችሁ በአዩብ የአል ሂዳያ ቡድን ውስጥ ያላችሁ ቅጥረኛ ተጫዋቾች ጫወታችሁን እንድታቆሙና ማህበረሰባችሁን በምትችሉት ነገር እንድትጠቅሙት እንመክራችኋለን ። በተለይ ከተለያየ ቦታ ከስራችሁና ተደብቃችሁ በመምጣት እዚህ ቡድን ውስጥ የገባችሁ አካላት እንቢ ብላችሁ የምትቀጥሉ ከሆነ ስማችሁን ከነፕሮፋይላችሁ በመዘርዘር ከናንተ የምናስጠነቀቅ መሆናችንን ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ ። አቅም ያላችሁ በተለያየ ሞያ የተመረቃችሁ ወንድሞችን በተመለከተ ያላችሁበት ቡድን እናንተን የማይመጥን የወረደ ግብ ይዞ የሚንቀሳቀስ ቡድን በመሆኑ ራሳችሁን አርቃችሁ አላህ በሰጣችሁ እውቀት ማህበረሰባችሁን የሚጠቅም ስራ እንድትሰሩ አደራ እላለሁ ። በዚህ አጋጣሚ ለሞያችሁ ታማኝና ለዲናችሁ ክብር ያላችሁ እስከሆነ ሁሌም የማከብራችሁና በምችለው ማህበረሰባችሁን ጠቃሚ እንድትሆኑ አላህን የምለምንላችሁ መሆኑን ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ ።
ከተማ ያላችሁ ከትንሽ እስከ ትልቅ አንዳችሁ የሌላውን ሳያውቅ በኔት ወርክ ተጠልፋችሁ እየተበዘበዛችሁ ያለችሁ ነጋዴዎች እኛ ከናንተ የምንፈልገው ነገር እንደሌለና ግን አላህ በሰጣችሁ ገንዘብ የምትጠየቁ ስለሆነ የት ለምንና ለማን እንደምትሰጡ እወቁ ለማለት እወዳለሁ ። ዐረብ አገር የምትኖሩ ሁሉም እንደወተት ላም ሊያልባችሁ የሚመኛችሁ እህቶች ባጠቃላይ ነሲሓ የሚዘርፋችሁ እህቶች በተለይ ለዲን ማውጣት ወደ አላህ መቃረቢያ ሲሆን በዲን ሰም የሚለምን ሁሉ ለዲን አይደምና ተጠንቀቁ እላለሁ ።

አላህ ለመልካሙ ሁሉ ይወፍቀን ።

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

03 Nov, 17:18


Live stream finished (15 minutes)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

03 Nov, 17:03


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

03 Nov, 17:01


Live stream finished (1 hour)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

03 Nov, 15:51


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

03 Nov, 15:50


ሰምንተዊ የቁሪአን ተፊስር ልጀምር ነዉ
ገባ
       ገባ
                በሉ
https://t.me/abuhatimaselefiy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

03 Nov, 13:53


በ ቅ ር ብ ቀን...
📝 አዲስ መፅሐፍ
📔📗📕📘📚
↙️ عنوان: ➴➴➴
↩️ بِدْعَةُ مَذْهَبِ وُجُوْبِ الْمُوَازَنَاتِ

↘️ ርዕስ፦ ➴➴➴
↪️ «የሙዋዘናህ ግተታነት መዝሃብ ቢድዓ»

📝 كَتَبَهُ الشَّيْخ أَبُو طَلْحَةَ أَبُو ذَرَ بْنُ حَسَنِ بْنِ إِمَامٍ الْإِثْيُوْبِي الْوَلْوِي «حَفِظَهُ اللَّهُ»

📝 ዝግጅት፦ ሸይኽ አቡ ዘር ሀሰን አቡ ጦልሃ አላህ ይጠብቃቸው

🏝 በመፅሃፉ
ስለ መጤው ሙዋዘናህ
ሙስሊም ሳሆሆን በሞተ ሰው ተረሑም የማድረግ ብይን
➩ ሙብተዲዕ እና ሙናፊቅ ጀናዛ ላይ ሶላት መስገድ ያለው ፍርድ
በርዕሰ-ጉዳዮቹ ላይ ታላላቅ የኢስላም ሊቃውንት የሰጧቸው ፈትዋዎች እና የመሳሰሉት ተካተዋል።

➴➴➴➴➴
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha

የኪታቡን pdf (soft copy) በቅርቡ ይጠብቁን!

🏝 የትኛውንም ጥቆማና አስተያየት በሚቀጥለው አድራሻ አቀብሉን!
➴➴➴➴➴➴
https://t.me/AbuImranAselefybot

Abu hatim Abduselam Assalefiy

02 Nov, 17:21


Live stream finished (1 hour)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

02 Nov, 16:18


📔 ለኸድር ኬሚሴ የተሰጠ ምላሽ

ተጀምሮ በነበረው ውይይት ላይ

በአረበኛ ቋንቋ የተፃፈውን በደርስ መልኩ

አረበኛ ማንበብ ለማይችሉ ሁሉ

▶️ሙሉ ደርስ (1 እስከ 60) በሊንክ ለማግኘት

በአረብኛ የተፃፈውን ለማግኘት
➷➴➘
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5521

🎙በድምፅ የተደረገውን ማብራሪያ ለማግኘት
➷➴➘
ክፍል አንድ
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5568

ክፍል ሁለት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5577

ክፍል ሶስት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5585

ክፍል አራት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5593

ክፍል አምስት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5602

ክፍል ስድስት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5610

ክፍል ሰባት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5612

ክፍል ስምንት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5620

ክፍል ዘጠኝ
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5628

ክፍል አስር
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5630

ክፍል አስራ አንድ
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5646

ክፍል አስራ ሁለት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5654

ክፍል አስራ ሶስት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5656

ክፍል አስራ አራት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5664

ክፍል አስራ አምስት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5666

ክፍል አስራ ስድስት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5675

ክፍል አስራ ሰባት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5704

ክፍል አስራ ስምንት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5712

ክፍል አስራ ዘጠኝ
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5720

ክፍል ሀያ
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5728

ክፍል ሀያ አንድ
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5750

ክፍል ሀያ ሁለት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5758

ክፍል ሀያ ሶስት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5767

ክፍል ሀያ አራት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5781


ክፍል ሀያ አምስት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5795

ክፍል ሀያ ስድስት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5797

ክፍል ሀያ ሰባት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5805

ክፍል ሀያ ስምንት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5827

ክፍል ሀያ ዘጠኝ
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5829

ክፍል ሰላሳ
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5837

ክፍል ሰላሳ አንድ
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5839

ክፍል ሰላሳ ሁለት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5867

ክፍል ሰላሳ ሶስት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5876

ክፍል ሰላሳ አራት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5884

ክፍል ሰላሳ አምስት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5886

ክፍል ሰላሳ ስድስት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5888

ክፍል ሰላሳ ሰባት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5896

ክፍል ሰላሳ ስምንት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5898

ክፍል ሰላሳ ዘጠኝ
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5900

ክፍል አርባ
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5920

ክፍል አርባ አንድ
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5960

ክፍል አርባ ሁለት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5962

ክፍል አርባ ሶስት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5964

ክፍል አርባ አራት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5966

ክፍል አርባ አምስት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5968

ክፍል አርባ ስድስት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5968

ክፍል አርባ ሰባት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/5998

ክፍል አርባ ስምንት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/6000

ክፍል አርባ ዘጠኝ
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/6002

ክፍል አምሳ
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/6016

ክፍል አምሳ አንድ
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/6018

ክፍል አምሳ ሁለት
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/6020

ክፍል አምሳ ሶስት
👇👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/6022

ክፍል አምሳ አራት
👇👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/6042

ክፍል አምሳ አምስት
👇👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/6044

ክፍል አምሳ ስድስት
👇👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/6046

ክፍል አምሳ ሰባት
👇👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/6054

ክፍል አምሳ ስምንት
👇👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/6056

ክፍል አምሳ ዘጠኝ
👇👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/6058

የመጨረሻው ክፍል ስልሳ (6⃣0⃣ )
👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/6060

Abu hatim Abduselam Assalefiy

28 Oct, 09:12


👉 ለፈገግታ

በመፋቂያ ነው ሚስቴን የመታሁት !!!

ባልና ሚስት ተጣልተው ሚስት ሽማግሌ ሰበሰበች ። ሽማግሌዎቹ ከሁለቱም በኩል የተውጣጡ ነበሩ ። ቁጭ ብለው ነገሩን ማየት ጀመሩ ። ባል ሚስቱን ለምን እንደሚመታት ተጠየቀ ። ባልም ሚስቴን የመታኋት በመፈቂያ ነው አለ ። ሽማግሌዎቹም ሚስትን እውነት በመፋቂያ ነው ወይ የመታሽ ብለው ጠየቋት ሚስትም እስኪ መፋቂያውን አምጣው በሉት አለቻቸው ። እስኪ መፋቂያውን አምጣው ተባለ ሲያመጣው ለካስ ዱላ ነው ።


https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

27 Oct, 11:40


🔴 ከተብሊጎች ዳዕዋ ብልሽነትና አደገኝነት አዲስ ሙሓደራ

🕌በአልበያን መስጂድና መድረሳ ግሩፕ
           የተደረገ ሙሓደራ
                                
      በኡስታዝ አቡል በያን ኑራዲስ ስራጅ
የተደረገ ሙሓደራ 🎵
     
      
                         ▼
https://t.me/+kn_NBJK5YaBkMWZk

Abu hatim Abduselam Assalefiy

27 Oct, 09:36


🔷  ሱፍይና አሕባሾች የዼንጤ ድልድዮች

      በአሁኑ ጊዜ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ዼንጤዮች ጌታዋን የተማመነች ጊደር ጅራትዋን ውጪ ታሳድራለች እንደሚባለው የልብ ልብ ተሰምቷቸው እየዘመቱ ነው ። የአክፍሮት ዘመቻቸው በዋነኝነት ቀብር አምላኪዮችን ትኩረት ያደረገ ነው ።
      ኢስላም ከጅምሩ የተዋጋው ኩፍር ቢኖር ቀብር አምልኮትን ነው ። የሚያሳዝነው ግን አሕባሽና ሱፍዮች ቀብር አምልኮትን ኢስላም አድርገው ለማህበረሰቡ በማቅረብ ዘጠና ከመቶ የሚሆነው ሙስሊም ቀብር አምላኪ እንዲሆን አድርገውታል ።
     አሕባሽና ሱፍዮች ይህን ቀብር አምልኮ የሚቃወምን ከእስልምና የሚያስወጣ ተግባርና ክልክል መሆኑን የሚያስተምሩ የተውሒድ ሰዎችን ካፊር ይላሉ ። ማህበረሰቡ የዚህ አይነቱን አስተምሮ እንዳይሰማ በዚህ የተውሒድ ዳዕዋ የተሰማሩ የነብያት ወራሾችን ወሀብዮች በማለት እንደጭራቅ እንዲታዩ ያደርጋሉ ። ከዚህ አልፎ ተርፎ የተለያዩ አጋጣሚዮችን በመጠቀም እድሉን ሲያገኙ በማሳሰር በማስገረፍ የቻሉትን ይሰራሉ ።
     የሱፍይና የአሕባሽ መሪዮች ወሀብዮች ከአባታችሁ የወረሳችሁትን እምነት ሊያስለቅቁዋችሁ ነው በምትችሉት ታገሏቸው ብለው የተውሒድ ሰዎችን እንዲገሉ ያበረታቱዋቸዋል ። ሞራል ይሰጡዋቸዋል ። ምስኪኖቹ የቀብር አምላኪዮች እስልምናችንን ሊያጠፉብን ነው ብለው የህይወት ዋጋ እስከመክፈል ራሳቸውን ያዘጋጃሉ ።
    አላህን በብቸኝነት ተገዙ የሚሉ ዱዓቶችን ከከሀዲያን የበለጠ ይጠላሉ ። የሚሉትን ለመስማት ቀርቶ ማየት አይፈልጉም ። 124 ሺህ ነብያት ሊዋጉት የተላኩበትን ቀብር አምልኮ ኢስላም ነው ብለው የነብያት ተከታዮችን ይዋጋሉ ። ነብዩ የተወጉለትን ፣ ደማቸው የፈሰሰለትን ፣ የተራቡለትና የተጠሙለትን ፣ የተሰደዱለትን ፣ ሶሓቦች የሞቱለትን ፣ ሰባ ሰማኒያ ቦታቸው የተወጉለትንና የተሰየፉለትን ተውሒድ ኩፍር ነው ይላሉ ።
    በተቃራኒው ያወገዙትና ኩፍር ነው ያሉትን ቀብር አምልኮ ኢስላም ነው ይላሉ ።
     ይህ የሱፍይና የአሕባሽ መሪዮች አስተምሮና ተግባር ለዼንጤዮች ወርቃማ እድል ሆኖላቸዋል ። ይህን ክፍተት ተጠቅመው ቀብር አምላኪ ምስኪኖች ጋር ቀርበው እናንተ ሞቶ የበሰበሰን ከምታመልኩ ዒሳ ጌታ ነው ብላችሁ ለምን አትድኑም ቀናቶችን ከፋፍላችሁ ቁጭ ብላችሁ ጫት በመቃም እድሜያችሁን ከምትጨርሱ የሙታን መንፈስ እያመለካችሁ የሲኦል ከምትሆኑ እየሱስ ጌታ ነው ብላችሁ ለምን አትድኑም ይሏቸዋል ።
    ምስኪኖቹ አንድ ቀን ተውበት አድርገው ወደ አላህ ተመልሰው ዘላለማዊ ሕይወት የሚወርሱበትን እድል ትተው የዘላለማዊ ጀሀነም መሆንን ይመርጣሉ ።
     ዒሳ ሁሉን ቻይ የሆነው ጌታ ኣደምን ያለ አባትና እናት ፣ ሓዋን ያለ እናት እንደፈጠረው ሁሉ ያለ አባት ከእናት ብቻ ሁን በሚለው ቃሉ ፈጥሮ ነብይ ያደረጋቸው መሆኑን የሚያስተምረውን ኢስላም ትተው በመርየም ማህፀን ውስጥ ማንኛውም ህፃን የሚያልፈውን ሂደት አልፈው ተረግዘው የተወለዱትን ዒሳን ፈጣሪ ብለው ይከፍራሉ ።
    እነዚህ ምስኪኖች ዒሳ በመርየም ማህፀን ውስጥ ከረጋ ደም ጀምሮ የነበሩ ሂደቶችን አለረፈው ደሙ ስጋ ሆኖ ፣ ስጋው አጥንት ለብሶ ፣ ስጋና አጥንቱ ቅርፅ ይዞ የተለያየ የሰውነት ክፍል እንደ ልብ ፣ ሳንባ ፣ ጉበት ፣ ኩላሊት ፣ ዐይን ፣ ጆሮ ፣ አፍና አፍንጫ ፣ ጭንቅላትና አእምሮ ፣ እጅና እግር ፣ ሴልና ነርቭ ፣ የውስጥ ሜካኒካል ክፍልና የአእምሮ ኤሌክትሪካል ክፍል ተሟልቶለት ሙሉ ሰው እስኪሆኑ ፍጥረተ ዓለሙን ማን ነበር የሚያስተናብረው ?
    ብለው መጠየቅ አልቻሉም ። እየሱስ ጌታ ነው ሲባሉ እሺ ብለው ተቀበሉ ። ለዚህ የዳረጋቸው ከሱፍያና አሕባሽ የወረሱት የሙታን መንፈስ አምልኮት ነው ።
     እነዚህ የሱፍይና አሕባሽ መሪዮች ወሀብዮችን በሚያስጠቁቁበት ልክ ከዼንጤ አያስጠነቅቁም ። ዼንጤ ልጆቻቸውን ሲከፍር ዱላ ይዘው አይወጡም ። እምነታችሁ ተነጠቀ አይሉም ። ዐቂዳችሁ ተነካ አይሉም ። በምትችሉት ታገሏቸው አይሉም ። የእነርሱ ወኔ በነብያት ወራሽ የተውሒድ ሰዎች ላይ ነው ።
     ለዘህ ነው እነዚህ አካላት የዼንጤዮች ድልድዮች ናቸው ያልኩት ። የአሕባሽና ሱፍዮች የኩፍር ተግባር ነው ምስኪን ቀብር አምላኪያንን ወደ ከፋ ኩፍር ይዟቸው የሚሄደው ።
      በጣም የሚያሳዝነው ነሲሓዎች ከእነዚህ ጋር ነው አንድ ነን ብለው ከኢኽዋንና ሱፍይ እንዲሁም አሕባሽ ጋር አንድነት በመፍጠር እኛ የኢትዮዽያ ሙስሊሞች ነን ያሉት ።
     በየአካባቢያችሁ ያሉትን የነሲሓ ዱዓቶችን ዳዕዋ አዳምጡ የቀብር አፈር በጥብጦ መጠጣት ፣ በአንዬ ፣ ዳንዬ ፣ አልከስዬ ፣ ቃጥባርዬ ፣ አብሬትዬ ፣ አባድርዬ ፣ ሾንክዬ ፣ ሸከና ሑሰይንዬ ፣ ጀማ ንጉስዬ ፣ ከረምዬ ቀብር ላይ ጠዋፍ ማድረግ ከእስልምና የሚያወጣ ሽርክ ነው የሚል የለውም ።
     ይህን ካሉ ከሱፍይና አሕባሽ እንዲሁም ኢኽዋን ጋር ስለሚጣሉ ። እየአንዳንዱን ወልይ ተብለው የሚመለኩ መሻኢኾችን ስም ጠርተው እዱኝ ፣ አክብሩኝ ፣ አሽሩኝ ፣ እጄን ያዙኝ ዋስ ጠበቃ ሁኑኝ ማለት ኩፍር ነው አይሉም ። የአንድነት  ስምምነቱን ስለሚያፈርስ ። በጥቅሉ ሽርክ ከባድ ወንጀል ነው ይላሉ ። ተውሒድ የነብያት ዳዕዋ ነው ይላሉ ። በዚህም ተከታዮቻቸውን ይሸውዳሉ ። የቱ ምን አይነቱ ተግባር ሽርክ እንደሆነ በዝርዝር አይናገሩም ።
     በመሆኑም ሰለፍዮች ሆይ ኡማውን ከቀብር አምልኮና ከአክፍሮት ሀይላት ለማዳን ያለባችሁ ሀላፊነት ከምን ጊዜውም የከበደ ነው ። ከዚህ ጎን ለጎን ይህን የነብያት ተልእኮ ለዱንያዊ ጥቅም ብለው በመተው በኢስላም የሚነግዱትን ነሲሓዎችንና የእንጀራ አባታቸው ኢኽዋኖችን እንዲሁን እንባ ጠባቂዮቻቸው የሙነወር ልጅና ግብረአበሮቹ ማንነት ለሱናው ማህበረሰብ ግልፅ ማድረግ ሌላው ትልቅ ሀላፊነት መሆኑን መዘንጋት የለባችሁም ።
       አላህ ዲኑን ይረዳል ተውሒድም የበላይ ይሆናል ።

ጠቃሚ ስለሆነ በድጋሚ የተለቀቀ ።

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

26 Oct, 17:34


Live stream finished (1 hour)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

26 Oct, 16:35


🔷 የሰለፍያን ዳዕዋ ለምን ይፈሩታል ?

ሰለፍያ ማለት ትክክለኛው እስልምና ማለት ነው ። የሰለፍያ ዳዕዋ ሲባል ወደ ትክክለኛው ኢስላም ነብዩ ፣ ሶሓቦች ፣ ታቢዒኖች ፣ አትባዑ ታቢዒኖችና እነርሱን በመልካም የተከተሉ የኢስላም ሊቃውንቶች ያስተማሩት ኢስላም ማለት ነው ። ሰለፍያ ዳዕዋው ሲሆን ዳዒው ( ወደዛ ተጣሪው) ሰለፍይ ይባላል ። ቃሉ የተወሰደው ሰለፍ ( ቀደምት) ከሚለው ሲሆን ሰለፎች የሚባሉት የመጀመሪያወቹ ኢስላምን በቁርኣንና ሐዲስ አስተምሮ ተግብረው ያሳዩት ናቸው ።
ከዚህ የምንረዳው የሰለፍያ ዳዕዋ ማለት የመጀመሪያው ወደ ትክክለኛ ኢስላም በነብዩና ሶሓቦቻቸው የተደረገው ዳዕዋ ማለት ነው ። ታዲያ ለምን ይሆን ዛሬ የሙስሊም መሪዮች ነን እያሉ ይህን ዳዕዋ የሚፈሩትና የሚጠሉት ? ለምን ይሆን ሁሉም ሙስሊም ነን የሚሉ አንጃዎች ይህን ዳዕዋ ማሰናከል የመጀመሪያ ግባቸው አድርገው የሚንቀሳቀሱት ? ለእስልምና ታስቦ ወይስ ለሙስሊሙ ? ሁለቱም አይደለም ነው መልሱ ። ምክንያቱም እስልምና ማለት ከሰባት ሰማይ በላይ በጅብሪል አማካይነት በነብዩ ላይ ወርዶ ለተከታዮቻቸው በንግግርና በተግባር ያስተማሩት ስለሆነና የሰለፍያም ጥሪ ወደዛው በመሆኑ ። ለሙስሊሞች ታስቦ ነው የሚለው ውድቅ የሚሆነው ሙስሊሞች በቅርቢቱም ሆነ በመጪው ዐለም ስኬት የሚጎናፀፉት የመልእክተኛውን ፈለግ ተከትለው አላህን በብቸኝነት ሲያመልኩ ነውና ።
ስለዚህ የትኞቹም የኢስላም አንጃዎች የሰለፍያን ዳዕዋ የሚፈሩትና የሚዋጉት ዝንባሌያቸውንና ጥቅማቸውን ስለሚነካ ነው ። እነዚህ አካላት ለእስልምናና ለሙስሊሙ ነው የምንሰራው የሚሉት ለሽፋን መሆኑ ይፋ የሚወጣው በኢስላም ስም ቀብር ሲመለክ ፣ በኢስላም ስም መውሊድ ሲደለቅ ፣ በኢስላም ስም ሽርክና ቢዳዓ ሲስፋፋ መብት ነው እያሉ የተውሒድን ዳዕዋ ማሰናከል ግብ አድርገው ሲሰሩና ለዚህም ዋጋ ሲከፍሉ ነው ።
በኢስላማዊ ዳዕዋ ስም ህዝብ ተሰብስቦ ጫት በአይሱዙ በሰለፍ ሲራገፍ እያዩ ምንም ሳይመስላቸው ሰዎችን ከፉጡራን ጋር ሳይሆን ከፈጣሪ ጋር የሚያስተሳስረውን የተውሒድ ዳዕዋን ማጨናገፍን ለኢስላምና ለሙስሊሞች ብለን ነው ማለት ምን የከፋ ቅጥፈት ነው ነው ?
የተውሒድን ዳዕዋ ለማስቆም መሞከር ፀሀይን በእጅ መዳፍ ብርሃንዋን ለመጋረድ እንደሞመከር ነው ። የተውሒድ ዳዕዋ ተቀናቃኞቹ በበዙ ቁጥር እያበበ ይሄዳል ። በደቆሱት ልክ እየጠነከረ ይሄዳል ። ስለዚህ የሰለፍያን ዳዕዋ መዋጋር ትርፉ የሁለት ሀገር ክስረት ነውና ከፍርሃትና ጠላትነት ወጥታችሁ ወደ ሰፉ ግቡ ለበላይነቱ ስሩ እንላችኋለን ።

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

26 Oct, 15:46


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

26 Oct, 15:45


ሰምንተዊ የቁሪአን ተፊስር ልጀምር ነዉ
ገባ
       ገባ
                በሉ
https://t.me/abuhatimaselefiy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

25 Oct, 17:07


Live stream finished (1 hour)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

25 Oct, 15:49


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

25 Oct, 15:48


Live stream finished (1 minute)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

25 Oct, 15:47


Live stream started

Abu hatim Abduselam Assalefiy

25 Oct, 15:44


ሰምንተዊ የቁሪአን ተፊስር ልጀምር ነዉ
ገባ
       ገባ
                በሉ
https://t.me/abuhatimaselefiy

Abu hatim Abduselam Assalefiy

25 Oct, 05:12


👉  በዝርዝር ከሽርክ ማስጠንቀቅ እብደት አይደለም ።

     ተውሒድ የሚለው ቃል የብዙዎችን ጆሮ የሚያሳምም እየሆነ መምጣቱ በጣም አሳዛኝ ነው ። ተውሒድ ማለት ለአላህ በሚገቡ የአምልኮት አይነቶች ባጠቃላይ እሱን ብቸኛ ማድረግ ወይም የአምልኮት አይነቶችን ለአላህ ብቻ አድርጎ እሱን መገዛት ማለት ነው ። እዚህ ውስጥ የአላህ ብቸኛ ፈጣሪነትና ባማሩ ስሞቹና ባህሪያቶቹ እሱን መነጠል ይገባል ።
      ተውሒድ ማስተማር የምርጥ የአላህ ባሮች ተግባር ነው ። እነዚህ ምርጥ የአላህ ባሮች ነብያትና መልእክተኞች ሲሆኑ የተላኩበት ብቸኛ ተልእኮ ተውሒድን ማስተማር ነው ። የሰውን ልጅ ፍጡርን ከማምለክ ፣ ለፍጡር ከመተናነስና ከመዋረድ ፣ ለፍጡር ከማጎብደድ ፣ ለፍጡር ከመስገድና ከማጎንበስ ለፍጥረተ ዐለሙ ፈጣሪ ብቻ መተናነስ ፣ ማጎብደድና ለሱ መዋረድን ሊያስተምሩ ነው ።
    ተውሒድ ማስተማር ሲባል አብዛኛው ማህበረሰብ የሚረዳው አላህ ብቸኛ ፈጣሪ ፣ ሰጪና ነሺ ፣ ህያው አድራጊና ገዳይ ፣ የሚያመሽና የሚያነጋ ፣ ፍጥረተ ዐለሙን የሚያስተናብር መሆኑን ማስተማር ብቻ ይመስለዋል ። ከዚህ ካለፈም በጥቅሉ አምልኮት ለሱ ብቻ ነው ከሱ ውጪ የሚመለክ የለም ብሎ ማስተማር የተውሒድ ጥግ መድረስ ነው ብሎ ያስባል ። የዚህን ጊዜ አብዛኛው ተከታይ ከዚህ ውጪ ምን አይነት ተውሒድ ሊያስተምር ነው ምትፈልገው ማለት ይጀምራል ።
      የትኛውም ተውሒድ አስተምራለሁ የሚል አካል ማወቅ ያለበት ተውሒድ ሲባል ጥቅልና ዝርዝር ነጥቦች ያሉት መሆኑን ነው ። የተውሒድ ጥቅል ነጥቦች አላህ ብቸኛ አምላክ ነው ።ከሱ ውጪ የሚመለክ የለም የሚል ሲሆኑ ዝርዝር ነጥቦቹ ደግሞ እየአንዳንዱ ከአላህ ውጪ የሚመለኩ አካላትን በዝርዝር ስማቸውን በመጥቀስ ሽርክ መሆናቸውን ማስተማር ነው ። ነገሮች በደንብ ግልፅ የሚሆኑት በተቃራኒያቸው ስለሆነ የተውሒድ ተቃራኒ የሆነውን የሽርክ አይነት በዝርዝር ስታስተምር ትክክለኛ ተውሒድ በሰዎች ልቦና ይሰርፃል ። በሀገራችን ከአላህ ውጪ የወልዮች ቀብር ተብለው የሚመለኩ የቀብር ቦታዎች ላይ አንድ ተውሒድ አስተምራለሁ የሚል ኡስታዝ በአላህ ላይ ማጋራት ትልቅ ወንጀል ነው ። በአላህ ላይ ማጋራት የለብንም ። ቀብር ማምለክ አይበቃም ቢል ሁሉም ከንፈሩን እየመጠጠ ሊሰማው ይችላል ። ነገር ግን እዚህ ቦታ የሚደረገው ተግባር ሽርክ ነው ። እዚህ ቀብር ላይ ጠዋፍ ማድረግ ሽርክ ነው ቢል የወልዩን ስም አንስቶ እሳቸውን ድረሱልኝ ፣ እርዱኝ ፣ አክብሩኝ ፣ አሽሩኝ ማለት ከእስልምና የሚያወጣ ከባድ ሽርክ ነው ቢል ግን አላህ ካዘነለት በስተቀር አብዛኛው የዳዒውን ህይወት እስከማጥፋት ሊደርስ ይችላል ። መታወቅ ያለበት ግን እውነተኛ ተውሒድ ማስተማር ማለት ይህ ነው ።
     አላህ መልእክተኛውን ሲልካቸው ከሙሽሪኮቹ ጋር ፀብ ውስጥ የከተታቸው ላት ፣ መናት ፣ ዑዛ ፣ ሁበል አይጠቅሙም ከራሳቸውም ላይ ጉዳት ማስወገድ አይችሉም እነርሱን ትታችሁ አላህን ብቻ ተገዙ ማለታቸው እንጂ ሌላ አይደለም ። ማንኛውም ወደ ተውሒድ እጣራለሁ የሚል አካል ሞዴሉ ነብዩላሂ ኢብራሂምና ነብያችን ሊሆኑ ይገባል ።
    ቁርኣንን በደንብ ተደቡር ያደረገ ዳዒ በነብዩላሂ ኢብራሂምና በነብዩ ሙሐመድ የተውሒድ አስተምሮ በቂ ፋና አለው ። በመሆኑም ጥቅል ተውሒድ ማስተማርና ጥቅል ሽርክን ማስጠንቀቅ የተውሒድ አስተማሪ አያስብልም ። ስንትና ስንት ከንፈራቸውን እየመጠጡ ደርስ ላይ ቁጭ ብለው ሲወጡ በሽርክ የሚጨማለቁ ሞልተዋል ። ይህ ተውሒድና ሽርክን በዝርዝር ያለ ማስተማር ውጤት ነው ። ዛሬ ወደ ሽርክ የሚጣሩ አካላት በዝርዝር ወደ ሽርክ ሲጣሩ ሙስሊሞችን አትከፋፍሉ አልተባሉም ። አንዱ ወደ ዳና ይጣራል ። ሌላው ወደ ከረም, አሁንም አንዱ ወደ ጀማ ንጉስ ይጣራል ሌላው ወደ ዳንግላ አያበቃም አንዱ ወደ ቃጥባሬ ሌላው ወደ አብሬትና አልከሶ ከዚህ በላይ በዝርዝር ወደ ሽርክ ከመጣራት በላይ ምን አለ ? የሚገርመው ግን እነዚህ አካላት አይጠቅሙም ብሎ በዝርዝር ማስተማር ኢኽዋንና ሙመዪዓዎች ጋር ሙስሊሞችን መለያየት ነው ። ከዛም በላይ አሁን አሁን ሱሪ ያሳጠሩና ፂማቸውን ያስረዘሙ የሱና ሰው የሚመስሉትም ጭምር የዚህ አይነቱን ዳዕዋ አድራጊ እብድ ነው እንዴ እስከማለት ደርሰዋል ። ከዚህም አልፎ ቃጥባሬ ፣ አልከሶ ማለት በቁርኣን አልመጣም እየተባለ ነው ። ኢኽዋኖችና የእንጀራ ልጆቻቸው ነሲሓዎች ፊታቸውን ወደ ዱንያና ሰው መሰብሰብ ሲያዞሩና ወደ ተውሒድ በዝርዝር መጣራት ሲተዉ ይባስ ብለው በዝርዝር ወደ ተውሒድ መጣራትና ከሽርክ ማስጠንቀቅ ሙስሊሙን መለያየት ነው ሲሉ ወጣቱ ስለተውሒድ የነበረው ግንዛቤ እዚህ ደርሷል ።
     አንተ የተውሒድ አስተማሪ ሆይ ኪታቡ ተውሒድን ለተበሩክ እያስቀራህ ተውሒድ እያስተማርኩ ነው እንዳትል ። መጀመሪያ ኪታቡ ተውሒድን እራስህ ተረዳው በሚገርም መልኩ ሽርክና ተውሒድን በዝርዝር ያስተምራል ። አፍራደል ሽርክና አፍራደ አትተውሒድን ለዚህ ነው የሸይኽ ሙሐመድ ዳዕዋ ያን ሁሉ የጠላት ብዥታ አልፎ ፍሬያማ የሆነው ።
     አላህ ተውሒድን ተረድተው ወደ ተውሒድ ከተጣሩት ባሮቹ ያድርገን ።

https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

24 Oct, 13:47


🌿🌿🌿🌿🌿🌿

ባለ ፈሳዱ ኢጅቲማዕ
ሲቀጥል ይህ በቡታጀራ የሚደረገው ኢጅቲማዕ መነሻው ከሺርኩ መንደር በሾንኪዬ ሐዲራ እርሳቸው ሲሞቱ ኑዛዜ ባደረጉት መሠረት የሚደረግ ዓለም አቀፍ የቢድዓ የሺርክ የፈሳድ መነሃሪያ የሆነ ኢጅቲማዕ እንደሆነ ሁሉ ሊያውቅ ይገበዋልም።

በሀላባ ቁሊቶ ከተማ ብቻ ከትልቁ ከኑር መስጂድ ጀምሮ ወደ ሀያ(20) መስጂዶች ሁሉ ነበሩ! ግን ለምን አፋቸው ከዚህ ከሺርክ ከቢድዓ ከአሕባሽ ከሱፊያ ከተብሊግ ዓለም አቀፍ የፈሳድ ስብሰባ ኢጅቲማዕ ከመቃወም አፋቸውም ብእራቸውም ተቆለመመ ተሎገመ!?

በሀላባ ቁሊቶ ፋጢማ ሠለፊዮች መድረሳና መስጂድ ሐሙስ ቀን 14/02/2017 ዓ.እ ከዓሱር ሰላት በኋላ በወንድም አቡ መሪየም ታጁዲን ቢን ለራጎ የተደርገ አጭር ምክር

https://t.me/Ibnu_Mekino_Al_Halaby/2948

Abu hatim Abduselam Assalefiy

24 Oct, 13:45


📱 አድስ አፕሊኬሽን ተለቀቀ
     
       ↪️ ሙሀደራዎች🎙

🎙በ ሸይኽ አቡ ዘር ሀሰን አቡ ጦልሃ

ለሌሎች ሼር በማድረግ ላልደረሳቸው እናዳርስ

ሊንኩንም ሼር ማረግን አትርሱ
      👇👇👇👇👇
https://t.me/safya_app

📨 መሰል  ቂራአት እና ሙሀደራወች ለማሰራት የሚከተልውን አድራሻ ይጠቀሙ
      👇👇👇👇👇
  @selfy_app_developer

Abu hatim Abduselam Assalefiy

24 Oct, 12:53


👉   የኢኽዋን መሪዮች የመጅሊስ እንጂ የሀገር መሪዮች አይደሉም ።

     የሀገራችን የኢኽዋን መሪዮች የስልጣን ጥማት በቀን ቁጭ ባሉበት እንዲቃዡ አድርጓቸዋል ። ቅዠቱ በርግጥ በውስጣቸው ሲያልሙት የነበረ መሆኑን ያመላክታል ። የእነዚህ አካላት የቀን ቅዠት ልክ እንደ አንድ በረንዳ አዳሪ ነው ።  በቀን ጎዳና ላይ ቁጭ ብሎ እርጥብ እሳት ( ጫት) እየበላ የምርቃናው ሙቀት በሁለመናው ሲሰራጭ በምናቡ የመዋኛ ቦታ ፣ ሜዳ ቴኒስ ፣ የልጆች መጫወቻ ባለው በተንጣለለ ጊቢ ላይ በተሰራ ቪላ ውስጥ ራሱን አስቀምጦ በሐሴት ማእበል ሲናወጥ ምርቃናው እንደጠፋበት አምሳያ ነው ።
     እነዚህ የሀገራችን የኢኽዋን መሪዮች ለስንት አመት ሲመኙት የነበረውን የመጅሊስ ስልጣን ላይ ሲወጡ የተሰማቸው ሙቀት የሰራ አካላታቸውን ሲቆጣጠረው ቁጭ ብለው የሀገር መሪ ሲሆኑ በቀን በተቀመጡበት በምናብ ዐለም ማየት ጀምረዋል ። የሚገርመው ይህ ህዋ ላይ የሚያንሳፍፋቸው ቅዠት ወደ መሬት ለማውረድ ቆርጠው ተነስተው ማስፈራራት ጀምረዋል ።
    ከዚህ በፊት ሐረር ላይ በነበራቸው ጉባኤ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በሱ " የስልጣን ግዛት " ውስጥ ሰለፍይ የሚባል ነገር መስማት እንደማይፈልግ በመግለፅ ሰለፍዮች ወደዱም ጠሉም በአሁኑ ሳአት እዚህ ሀገር ላይ ( ኢትዮዽያ ላይ ) የሙስሊሙ መንግስት እሱ መሆኑን አውጇል ።
     ገርሞ ገርሞ ይገርማል ። ጆሮ ለባለቤቱ ባዳ ነው እንደሚሉት ወይም ጉድ ሳይሰማ መስከረም አይጠባም ነው ነገሩ ። ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ፣ የሙስሊሞች መሪ ፣  ከዶ/ር አብይ አሕመድ ደግሞ የክርስቲያኖች መሪ  እንዲሆኑና ኢትዮዽያ በሁለት መንግስታት እንድትመራ የተስማሙ ይመስል ። ይህን የሐጂ የቀን ቅዠት በተለይ ኦሮምኛ የምትሰሙ በሚከተለው ሊንክ ገብታችሁ አድምጡ :–
https://drive.google.com/file/d/1VZSVRvGK0tOrUTiP4z7vJXz_Mx28Qqi4/view?usp=drivesdk

     በዚህ ቅዠቱ ላይ በሚገርም መልኩ ሰለፍዮችን ያስፈራራል ። ውሀ ዝም ብሎ ሲሄድ የተኛ ይመስላል እንደሚበላ ሰው አያውቅም የሚል ምሳሌ አምጥቶ ዝም ስላልኩ የማላውቅ አይምሰላችሁ አጠፋችሇለሁ ይላል ።
    እኛ የምንለው መጀመሪያ ዙፋኑን አረጋግጥና ከዛ በኋላ ዛቻውን አምጣ ነው ። አሁንም የምንለው አንተ የአንድ ተቋም መሪ እንጂ የሀገር መሪ አይደለህም ነው ። እንደሙስሊም በቁርኣንና በሐዲስ በሶሓቦች አረዳድ እንደ ሀገር ደግሞ በህገ መንግስቱ ነው የምንመራው ። አንተም እኛም በህገመንግስቱ እኩል ነን ።
     ከኢስላም ሊቃውንቶች ጥበበኛ ንግግር አንዱ " ልኩን ያወቀን አላህ ይዘንለት " የሚል ነው ።
     ይህ የቀን ቅዠት በሱ ላይ ብቻ አላበቃም ዶ/ር ጀይላንም የአሕባሽ ሱፍይና ኢኽዋን ጥምር የሆነው የዑለማእ ፈታዋ ያልተቀበለ ኻሪጅይ ነው ( በመንግስት ላይ መፈንቅለ መንግስት ለማድረግ የወጣ ) ነው ብሎ የጓደኛውን የማይጨበጥ ምናብ አጠናክሯል ።
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
       🔹 ይህ ከላይ ያለው ፁሑፍ ግንቦት 2016 ላይ ተፅፎ የነበር ሲሆን ኢኽዋኖችን በተለይ የመጅሊሱን አመራሮች ያበሳጨ ነበር ። አሁንም የምንለው የኢኽዋን ( የመጅሊስ ) አመራሮች የሙስሊሙ መንግስት አይደሉም ። ኢትዮዽያም በሁለት መንግስት እየተመራች አይደለም ። ነገር ግን ከመንግስት ጋር ሲጠጉ እውነተኛ የሀገር ተቆርቋሪ የህዝቡን ሰላም አስጠባቂ መስለው ከመንግስት ጋር ሲጋጩ ወይም መንግስት ፊት ሲነሳቸው ለግል ጥቅማቸው ህዝቡን ከዳር እስከዳር ቀስቅሰው ሀገር እንዲታመስ የሚያደርጉ እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል ባዮች መሆናቸውን መግለፅ በተለይ ለምስኪኑ ተከታይ በጣም አስፈላጊ ነው ። ታዲያ ከላይ የተጠቀሰውን የሀገር መሪነት የምናብ ስካርና ሰለፍዮችን የማሸማቀቅ ጥማታቸው በፊት ለፊት ሳይሆን በመሰሪ አካሄድ ተግባራዊ ለማድረግ የማይቆፉሩት ጉድጓድ የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም ። ለዚህ ዋነኛ መሳሪያቸው ሰለፍዮችን የሀገር ስጋት የሰላም ፀር እንደሆኑ አደርገው ለመንግስት ባለስልጣናት በማቅረብ ወደ አላማቸው መድረስ ትልቁ ስራቸው አድርገው ይዘውታል ።  ይሁን እንጂ ደመናው በፀሀይ እንደሚገፈፈው ሁሉ እነዚህ አካላት በሰለፍዮች ላይ የሚለጥፉት የስም ማጥፋት ታፔላ ተነስቶ እውነታው ፍንትው ማለቱ አይቀርም ።
     ስሙን ለሰው አወረሰው እንዲሉ ኢኽዋኖች የራሳቸውን ማንነት ለሰለፍዮች በመስጠት ስማቸውን ለማጠልሸት መሞከር በምንም መልኩ የእነርሱን እኛ የሙስሊሙ መንግስት ነን የሚለውን ምኞት አያሳካም ። ለጊዜው ለመንግስት የተሳሳተ ምስል በመስጠት የጥንቃቄ እርምጃ እንዲወስድ ሊያደርጉ ይችላሉ  ። ነገር ግን ይህ ማለት መንግስትን አዘዙ ወይም  ከመንግስት በላይ ሆኑ ማለት አይደለም ። ይልቁንም ማንነታቸውና ድብቅ አጀንዳቸውን እንዲረዳ ነው የሚያደርጉት ። እንኳን ሀገር የሚመራ መንግስት አንድ የቤት አባ ወራም ቢሆን እገሌ እኮ በጣም አደገኛ ነው ካልከው ከሱ ጋር የነበረውን ግንኙነት ቆም አድርጎ በራሱ መንገድ ማንነቱን ያጣራል ። በመጨረሻም ታማኝነቱና እውነትኝነቱን ሲያረጋግጥ በተቃራኒው ያንተን ድብቅ ፍላጎት ለማወቅ ፊቱን ማዞሩ አይቀርም ።
      በመሆኑም የኢኽዋኖች ሰለፍዮችን የማጠልሸት እንቅስቃሴ ለሰለፍዮች ክብርን እንጂ አይጨምርላቸውም ። ሌላው ኢኽዋኖችና የእንጀራ ልጆቻቸው ሊያውቁት የምንፈልገው ሰለፍዮች በመለኮታዊ ቃል የሚመሩ መሆናቸውና ከማንም ምንም ነገር ቢደርስባቸው በመለኮታዊው የሕይወት መመሪያ የአላህ ቃልና በነብዩ ንግግር መዝነው ተግባራዊ የሚያደርጉት መሆኑን ነው ። በስሜት ፈረስ እየጋለቡ ለግል ጥቃማቸው ወጣቱን ከጎናቸው  አሰልፈው ሀገር የሚያምሱ አይደሉም ። ስለዚህ አትድከሙ ህልማችሁ አይሳካም የአላህ ቃል የበላይ ይሆናል እንላቸዋለን ።
      https://t.me/bahruteka

Abu hatim Abduselam Assalefiy

24 Oct, 12:53


🟢ይድረስ ለሰለፈዮች

ይህን የመሰለ ጠቃሚ ምክር ሁሌም ያስፈልጋል።።
نصائح وتوجيهات قيمة من الشيخ
أبي محمد ربيع بن هادي المدخلي حفظه الله تعالى
👆ከአሸይኽ ረቢዕ አልመድኸሊይ ምክሮች

👌 ተቅዋ (ጥንቁቅነት)
👌 ኢኽላስ (ዒባዳን ማጥራት)
👌 ኢስቲቃማ (በሀቅ ላይ መፅናት)
👌 አላህን ከሚያስቆጡ ነገሮች ሁሉ መራቅ
👌 ቁርኣን እና ሀዲስን ከመፃረር መቆጠብ
👌 አኽላቅ (መልካም ስነምግባር)
👌 ለአላህ ብሎ ከልብ መዋደድ
👌 ለሀቅ መተጋገዝና መተሳሰር
👌 የኺላፍና መለያየት ሰበቦችን መራቅ
👌 ሰብር እና ቻይነት
👌 ጀነት የሚያስገባ ኢማን
👌 ከልብ የመነጨ ሰላምታ ተላዋወጡ
👌አላህ የሚጠላቸውን ካፊሮች ፣ ሙሽሪኮች ፣ ሙብተዲዖች መጥላት
👌 ሰለፊዮች እንደ አንድ አካል ናቸው

https://t.me/Abuhemewiya
📝ተጨማሪ  ትምህርቶችን   ለማግኘት
   ቻነሉን    ይቀላቀሉ
➘➷➴➘➷➴➘➷➴➘➷➴
https://t.me/MisbahMohammed

Abu hatim Abduselam Assalefiy

18 Oct, 16:38


Live stream finished (49 minutes)

Abu hatim Abduselam Assalefiy

18 Oct, 15:48


Live stream started

1,618

subscribers

221

photos

23

videos