Wolaita Sodo University

@wolaitasuniversity


This is the official telegram channel of Wolaita Sodo University


Our Official Website :
http://www.wsu.edu.et/

Our Official Facebook page :
https://m.facebook.com/Wolaita-Sodo-University-246568056057804

Wolaita Sodo University

21 Jan, 00:25


ከአካል ጉዳተኝነት ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የሁሉንም ባለድርሻ አካለት ተሳትፎ እና የጋራ ርብርብ እንደሚያስፈልግ ተጠቆመ!!

አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች በአካቶ ትምህርት ትግበራ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ከሁሉም የሚጠበቅና ተቀዳሚ ተግባር መሆን እንዳለበትም ተገልጿል::

******** ************

ይህ የተገለጸው የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ልዩ ፍላጎት ዳይሬክቶሬት ከEthiopian Center for Disability and Development/ECDD/ ጋር በመተባበር ከፊንላንድ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ህበረት (SYL) እና ከፊንላድ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተገኘ ድጋፍ ለዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ ከኮሌጆች፣ ከት/ም ቤቶችና ከየዲፓርትመንት ለተወጣጡ መምህራንና ሠራተኞች እንዲሁም ልዩ ፍላጎት ላለባቸው አካላት ሰሞኑን ለሁለት ተከታታይ ቀናት በተሰጠው የስልጠና መድረክ ላይ ነው፡፡

በመርሃ ግብሩ ላይ የዩኒቨርሲቲ ልዩ ፍላጎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ጳውሎስ ዴኣ ለተሳታፊዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈው "Disability Rights, Disability Inclusion and Awareness and Sexual Reproductive Health Training for students with Disability" የሚሉት የሥልጠናው ዋና ዋና ርዕሰ ጉዳዮች መሆናቸውን አስቀምጠዋል፡፡


ከአካል ጉድልተኝነት ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የሁሉንም ባለድርሻ አካለት ተሳትፎ እና የጋራ ርብርብ የሚያስፈልግ በመሆኑ ዘላቂነነት ባለው አግባብ በትብብር መስራት ተገቢ መሆኑን ዳይሬክተሩ አመላክተዋል።

አካል ጉዳተኞች ምንም ሳያግዳቸው በነፃነት አደባባይ ላይ ወጥተው ራሳቸውን እንዲገልጹ፣ ከማኅበረሰቡ እንዲቀላቀሉ እና የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ለማስቻል የተለያዩ ጥረቶች ያስፈልጋል ያሉት ዶክተር ጳውሎስ ዴኣ በተለያዩ የሥራ መስኮች በመሳተፍም ራሳቸውን ለመቻል የሚያደርጉትን ጥረት ማበረታታት ተገቢ ነውም ብለዋል ።


በመድረኩ ከEthiopian Center for Disability and Development/ECDD/ ወክለው የተገኙት አቶ ዮሃንስ ተክላይ በበኩላቸው የራሳቸውን የህይወት ልምድ ለተሳታፊዎች አጋርተው ዛሬም በርካታ አካል ጉዳተኞች ለተለየዩ ችግሮች ተጋላጭ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡

በከፍተኛ በትምህርት ተቋማት ረገድ ዘርፈ ብዙ ፈተናዎች እየገጠሟቸው እንደሚገኝም ያብራሩት አቶ ዮሐንስ ECDD ይህንን ክፍተት ለመሙላት ከተለያዩ የመንግስት ተቋማት ጋር እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

አካል ጉዳተኞችን በተመለከተ የወጡ የሕግ ማዕቀፎች በሙላት እንዲተገበር በማድረግ አገሪቱ ከምትከተለው እኩል የትምህርት ዕድል መርህ ጋር በሚጣጣም መልኩ ምቹ የመማር ማስተማር ዕድል የሚፈጥር እና በሥራ ላይ የሚደርስባቸውን መድሎ መከላከል እንዲቻል ቁጥጥሩ የበለጠ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል አቶ ዮሐንስ።

በስልጠናው በሁለት ቀናት ቆይታው የተለያዩ ሰነዶች የቀረቡ ሲሆን ተሳታፊዎች ሰፊ ውይይት በማድረግና ስልጠናው በስፋት ለሁሉም አካላት በመስጠት በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የሁሉንም ባለድርሻ አካለት ተሳትፎ እና የጋራ ርብርብ እንዲደረግ በማውሳት ስልጠናው መቋጫውን አግኝቷል ።

«ዕውቀትን በተግባር!!»

የዩኒቨርሲቲው ህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ቢሮ

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ትክክለኛውን የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ሶሻል ሚዲያ በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/Wolaita-Sodo-University-246568056057804/
ቴሌግራም፡https://t.me/WolaitaSUniversity
ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/.../UC6VukdZbl5iVgZGXG8BkMdw/videos
ዌብሳይት፡ http://www.wsu.edu.et/
ትዊተር፡ https://twitter.com/WSodoUniversity...
ኢንስታግራም፡ https://instagram.com/wolaita_sodo_university?igshid=YmMyMTA2M2Y=

አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን

Wolaita Sodo University

21 Jan, 00:22


ሴት ተማሪዎች ለበርካታ ተፈጥሮአዊና ሰው ሰራሽ ችግሮች ስለሚጋለጡ በትምህርት ውጤታማ እንዲሆኑ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ደርጅቶች መደገፍ እንዳለባቸው ተጠቆመ፡፡

"African Empowerment UK in Collaboration with Lehlina Project" ከወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ለሴት ተማሪዎች የንጽህና መጠበቂያ አቀረበ፡፡

*************** **********************

በመርሃ ግብሩ ላይ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ተወካይና የተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ታምራት ሰሎሞን፤ ሴት ተማሪዎች በተለያዩ በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ ችግሮች በመማር ማስተማር ሥራ ላይ ደካማ ውጤት እንዳያስመዘግቡ እገዛ ማድረግ ተገቢ ነው ብለዋል፡፡

ዶ/ሩ አክለውም ዩኒቨርሲቲው ከመሰል ድርጅቶች ጋር በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን ጠቅሰው "African empowerment UK in collaboration with Lehlina Project" ለሴት ተማሪዎች ስላቀረቡት የንጽህና መጠበቂያ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

ሴት ተማሪዎች ትምህርትን ለሚያደናቅፉ ለተለያዩ ችግሮች እጅ ሳይሰጡ ጥረታቸውን በትምህርት ብቻ ላይ አድርገው መልካም ውጤት እንዲያስመዘግቡ መክረዋቸዋል ተወካዩ፡፡

የዩኒቨርሲቲው ሴቶች ማህበራዊ ጉዳች አካትቶ ትግበራ ሥራ አስፈታሚ የሆኑት ወ/ሮ አትክልት ጌታቸው በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው 1999 ዓ.ም ከተቋቋመ ጀምሮ ለሴት ተማሪዎች በተለያዩ ጉዳዮች ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መቆቱን ገልፀው በዛሬው ዕለት ለሴት ተማሪዎች የቀረበው የንጽህና መጠበቂያ ለትምህርታቸው ትኩረት ሰጥተው እንዲማሩ የሚያግዝ ነው ብለዋል፡፡

በመርሃ ግብሩ ላይ African empowerment UK in collaboration to Lehlina Project ለሴት ተማሪዎች የንጽህና መጠበቂያ ማቴሪያልስ ማቅረቡ የሚያስመሰግን መሆኑ የተነሳ ሲሆን ሴት ተማሪዎች ለበርካታ ተፈጥሮአዊና ሰው ሰራሽ ችግሮች የሚጋለጡ ስለሆነ በትምህርት ውጤታማ እንዲሆኑ መሰል ድጋፎች መቀጠል እንዳለበት ተጠቁሟል፡፡

በመርሃ ግብሩ ላይ የንጽህና መጠበቂያ አሰራርና አጠቃቀም በተመለከተ የለህሊና ፕሮጀክት እና የአጅየት ፓድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ በሆኑት ህሊና ተክሉ ገለፃ ተደርጎላቸዋል፡፡


«ዕውቀትን በተግባር!!»

የዩኒቨርሲቲው ህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ቢሮ

ጥቅምት 09/2017 ዓ.ም

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ትክክለኛውን የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ሶሻል ሚዲያ በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/Wolaita-Sodo-University-246568056057804/
ቴሌግራም፡https://t.me/WolaitaSUniversity
ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/.../UC6VukdZbl5iVgZGXG8BkMdw/videos
ዌብሳይት፡ http://www.wsu.edu.et/
ትዊተር፡ https://twitter.com/WSodoUniversity...
ኢንስታግራም፡ https://instagram.com/wolaita_sodo_university?igshid=YmMyMTA2M2Y=

አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን

Wolaita Sodo University

21 Jan, 00:22


#ማስታወቂያ

በክፍት የኃላፊነት ቦታዎች የተወዳደራችሁ መምህራን በሙሉ፤

በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ክፍት የኃላፊነት ቦታዎች ለውድድር በወጣው ማስታወቂያ መሰረት የተወዳደራችሁና ስማችሁ ከዚህ በታች የተዘረዘረው በሙሉ ከታች በሰንጠረዡ በተገለፀው መርሀ ግብር መሰረት ስትራቴጂክ ዕቅድ የምታቀርቡ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

#ማሳሰቢያ ዕቅዱ በሚቀርብበት ዕለት ጧት 2፡00 ላይ አጭር ማብራሪያ ስለሚሰጥ በዕለቱ የሚያቀርቡ ሁሉም ተወዳዳሪዎች በካውንስል አዳራሽ እንዲገኙ እናሳስባለን፡፡

ወላይታ ሶዶ ኒቨርሲቲ

Wolaita Sodo University

21 Jan, 00:21


#ድጋሚ ማስታወቂያ

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በ2017 የትምህርት ዘመን ሀገራዊ የድኅረ ምረቃ መርሃ-ግብር መግቢያ ፈተና (NGAT) ያለፉ አመልካቾችን ተቀብሎ ለማስተማር እስከ መስከረም 25/2017 ዓ.ም ድረስ ምዝገባ የሚያካሂድ መሆኑን መግለጹ ይታወቃል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ለበርካታ አመልካቾች ዕድል ለመስጠት በማሰብ የማመልከቻ ጊዜ እስከ ጥቅምት 16/2017 ዓ.ም እንዲራዘም ወስኗል፡፡

በመሆኑም የምዝገባ ጊዜ እስከ 16/02/2017 ዓ.ም ድረስ የተራዘመ መሆኑን አውቃችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናስታውሳለን፡፡

የዶርም አገልግሎት ለሚፈልጉ መደበኛ 2ኛ እና 3ኛ ዲግሪ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው በተመጣጣኝ ክፍያ የተዘጋጀ መሆኑንም በድጋሚ እናሳውቃለን።


«ዕውቀትን በተግባር!!»

የዩኒቨርሲቲው ህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ቢሮ

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ትክክለኛውን የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ሶሻል ሚዲያ በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/Wolaita-Sodo-University-246568056057804/
ቴሌግራም፡https://t.me/WolaitaSUniversity
ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/.../UC6VukdZbl5iVgZGXG8BkMdw/videos
ዌብሳይት፡ http://www.wsu.edu.et/
ትዊተር፡ https://twitter.com/WSodoUniversity...
ኢንስታግራም፡ https://instagram.com/wolaita_sodo_university?igshid=YmMyMTA2M2Y=

አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን

Wolaita Sodo University

21 Jan, 00:21


ማስታወቂያ በግል ከፍሎ ለመመር ለሚፈልጉ ተማሪዎች በሙሉ

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በሳምንት መጨረሻ፣ በማታና በግል መደበኛ እንዲሁም በአቅም ማሻሸያ ፕሮግራሞች በመጀመሪያ ድግሪ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል፡፡

በመሆኑን የቅበላ መስፈርት የምታሟሉት፤

1. በሳምንት መጨረሻ፣ በማታና በግል መደበኛ ፕሮግራሞች ከፍሎ ለመማር እስከ ጥቅምት 30/2017 ዓ.ም ድረስ ማመልከት የምችሉ መሆኑን እና

2. በተከታታይ ትምህርት ፕሮግራም የአቅም ማሻሸያ (Remedial) ፕሮግራም ከፍሎ ለመማር እስከ ህዳር 30/2017 ዓ.ም ድረስ ማመልከት የምችሉ መሆኑን እናስታውቃለን፡፡

የማስታወቂያውን ሙሉ መስፈርት ከታች ባለው መረጃ ይመልከቱ!!


«ዕውቀትን በተግባር!!»

የዩኒቨርሲቲው ህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ቢሮ

ጥቅምት 08/2017 ዓ.ም

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ትክክለኛውን የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ሶሻል ሚዲያ በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/Wolaita-Sodo-University-246568056057804/
ቴሌግራም፡https://t.me/WolaitaSUniversity
ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/.../UC6VukdZbl5iVgZGXG8BkMdw/videos
ዌብሳይት፡ http://www.wsu.edu.et/
ትዊተር፡ https://twitter.com/WSodoUniversity...
ኢንስታግራም፡ https://instagram.com/wolaita_sodo_university?igshid=YmMyMTA2M2Y=

አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን