Tikvah-University @tikvah_university Channel on Telegram

Tikvah-University

@tikvah_university


I blog about marketing and sales

Buy ads: https://telega.io/c/Tikvah_University

Tikvah-University (English)

Welcome to Tikvah-University, your go-to source for all things education and personal development! This Telegram channel is dedicated to providing valuable resources, tips, and insights to help you reach your full potential. Whether you're a student looking to excel in your studies, a professional seeking career guidance, or simply someone who wants to continue learning and growing, Tikvah-University has something for everyone. From study hacks and time management techniques to motivation and self-improvement strategies, this channel covers a wide range of topics to support your academic and personal success. Join our community of like-minded individuals who are committed to continuous learning and growth. Let Tikvah-University be your guide on the journey to becoming the best version of yourself!

Tikvah-University

10 Feb, 14:17


ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ለአቅም ማሻሻያ ትምህርት (Remedial Program) የተመደቡለትን ተማሪዎች በመቀበል ላይ ይገኛል።

በ2017 ዓ.ም ለሪሚዲያል ፕሮግራም ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ ተማሪዎች የካቲት 3 እና 4/2017 ዓ.ም በአካል ሪፖርት እንዲያደርጉ ዩኒቨርሲቲው ይታወቃል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

10 Feb, 14:17


ባለፈው ሳምንት ከተሰጠው ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ጋር በተያያዘ የ Comprehensive Nursing ተፈታኝ ተማሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ አቅርበዋል፡፡

ፈተናው ከBlue Print ውጪ መዘጋጀቱን እንዲሁም የጥያቄ መደጋገም መኖሩን የገለፁት ተፈታኞቹ፤ ትምህርት ሚኒስትር ቅሬታቸውን በማየት በአፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡

ከነርሲንግ ተማሪዎች ጋር ተያይዞ የትምህርት ሚኒስቴር እስካሁን ያለው ነገር የለም፡፡ ቲክቫህ ጥያቄውን ለሚኒስቴሩ ከፍተኛ አመራር ያቀረበ ሲሆን፤ የሚሰጡንን ምላሽ የምናቀርብ ይሆናል፡፡

በሌላ በኩል "ፈተናዎቹ ዘግይተው መሰጠት በመጀመራቸው የሰዓት ዕጥረት እንዲፈጠር ማድረጉ" እንዲሁም "የኔትወርክ እና የመብራት መቆራራጥ ችግሮች" ሌሎች በፈተናው ወቅት የታዩ ችግሮች እንደነበሩ ተፈታኝ ተማሪዎቹ ለቲክቫህ ገልፀዋል፡፡

እንደ ተንቀሳቃሽ ስልክ ያሉ የተከለከሉ ነገሮችን ወደ ፈተና ጣቢያ ይዞ ለመገባት መሞከር በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ማጋጠሙን መግለፃችን ይታወሳል፡፡

ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ሞባይል ስልክ ሲጠቀሙ የተያዙ እና በመፈተኛ ክፍሎች ሞባይል ስልኮችን ይዘው የተገኙ 128 ተማሪዎችን ከፈተና ማዕከሉ እንዲሰናበቱ ማድረጉንና ውጤታቸው እንዲሰረዝ ማድረጉን አሳውቋል፡፡

የሀገር አቀፍ መውጫ ፈተና ውጤት ከዛሬ ጀምሮ ባሉት ጥቂት ቀናት ይፋ እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡

ምስል፦ ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ

@tikvahuniversity

Tikvah-University

10 Feb, 14:17


#TVTI_Exit_Exam

የመውጫ ፈተና የምትወስዱ የፌደራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ሰልጣኞች በኦንላይን ምዝገባ አድርጉ!

ተከታዩን ማስፈንጠሪያ በመጫኑ የምታገኙትን ቅፅ በመሙላት ምዝገባ ያድርጉ 👇
https://forms.office.com/r/3KgnK1esuc

ኦንላይን መመዝገብ የማትችሉ በዋናው ግቢ በአካል በመገኘት በየትምህርት ክፍላችሁ መመዝገብ ትችላላችሁ ተብሏል።

የምዝገባ ጊዜ የሚያበቃው፦
የካቲት 10/2017 ዓ.ም

የመውጫ ፈተናውን #በድጋሜ የምትወስዱ ተፈታኞች ፈተናው በኢንስቲትዩቱ ዋና ግቢ እና በአዲስ አበባ በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ይሰጣል።

የመዝገባ ብር 500 በኢንስቲትዩቱ የንግድ ባንክ አካውንት በማስገባት ክፍያ በመፈፀም ደረሰኝ መያዝ ይጠበቅባችኋል።

የምዝገባ ጥሪው በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የጋርመንት ቴክኖሎጂ ሰልጣኞችንም ይመለከታል።

የመውጫ ፈተናው ከመጋቢት 6-11/2017 ዓ.ም ባለው ጊዜ እንደሚሰጥ ኢንስቲትዩቱ ገልጿል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

08 Feb, 18:36


#ጥቆማ

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በማንኛውም የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ተመድበው "የጀማሪ መርሐግብር የቅድመ ምህንድስና ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ" ተማሪዎች መካከል በዘርፉ የተሻለ ክህሎትና ዝንባሌ ያላቸውን ተማሪዎች #በዝውውር ተቀብሎ #በመጀመሪያ_ዲግሪ ማስተማር ይፈልጋል።

በዝውውር ቅበላ የሚደረግባቸው የትምህርት መስኮች፦

1. ፋሽን ኢንጂነሪንግ (Fashion Engineering)
2. ቴክስታይል ኢንጂነሪንግ (Textile Engineering)
3. ቆዳ ውጤቶች ኢንጂነሪንግ (Leather Products Engineering)
4. ቴክስታይል ኬሚካል ፕሮሰስ ኢንጂነሪንግ (Textile Chemical Processing Engineering )

የትምህርት ካምፓስ፦
በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክስታይል እና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት

ለማመልከት፦
https://forms.gle/gSypn17ttmm8k4746

ለተጨማሪ መረጃ:-
0938882020 / 0918187249

@tikvahuniversity

Tikvah-University

08 Feb, 18:36


በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ ለ108 የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች የእንግሊዝኛ ቋንቋ ማጎልበቻ ነጻ የትምህርት ዕድል ሰጥቷል።

ተማሪዎቹ ከአርባ ምንጭ፣ መቐለ እና ድሬዳዋ ከተሞች የተውጣጡ ናቸው።

English Access Scholarship የተሰኘው ፕሮግራሙ ለሁለት ዓመት የሚቆይ ሲሆን፤ ተማሪዎቹ በትምህርታቸው ስኬታማ እንዲሆኑና ወደፊት የስኮላርሺፕ ዕድሎችን ለመጠቀም የሚያስችላቸውን ክህሎት እንዲያገኙ የሚያደርግ ነው።

ተማሪዎቹ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ስልጠና፣ ዓለም አቀፍ ዜግነት እንዲሁም የአሜሪካ ባህልና ዕሴቶች ላይ ስልጠና እንደሚወስዱ ተገልጿል።

ስልጠናው የተማሪዎቹን የተግባቦት፣ ትብብር እና መሪነት ክህሎቶች በሚያጎለብት መልኩ ይሰጣል ተብሏል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

08 Feb, 18:36


#ጥቆማ

የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ STEM ማዕከል በድሬዳዋ እና አካባቢው ለሚገኙ ከ7-12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሳይንስ የትምህርት አይነቶች (ፊዚክስ፣ ሂሳብ፣ ኬሚስትሪ እና ባይሎጂ) ተግባር-ተኮር ስልጠና አዘጋጅቷል።

ስልጠናው ሙሉ ለሙሉ በተግባር የተደገፈ ሲሆን፤ በቅዳሜና እሑድ መርሐግብር የሚሰጥ ነው፡፡

የስልጠና ዘርፎች፦
- Information Technology
- Electronics

የመመዝገቢያ መስፈርቶች፦
- ከዚህ በፊት በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ STEM ማዕከል በቅዳሜና እሁድ ስልጠና ያልወሰዱ፣
- ከ7-12ኛ ክፍል ተማሪ የሆኑ፣
- በሳይንስ የትምህርት አይነቶች ጥሩ ውጤት ያላቸው፣
- ለ7ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች በGeneral Science ጥሩ ውጤት ያላቸው፣
- የሳይንስ ፈጠራ ተሰጥዎ/ዝንባሌ ያለው/ያላት፣

የመመዝገቢያ አማራጮች፦
- በቴሌግራም ግሩፕ👇
https://t.me/+SIGIdGywKdM3Mzg0
- በስልክ ቁ. 0912233221 ላይ ሙሉ ስም፣ የትምህርት ቤታችሁን ስም እና ክፍላችሁን በአጭር የፅሁፍ መልዕክት ይላኩ።

🔔 ምዝገባው ሰኞ የካቲት 3/2017 ዓ.ም ያበቃል፡፡ የመግቢያ ፈተና የካቲት 8/2017 ዓ.ም ይሰጣል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

07 Feb, 17:21


ሀገር አቀፍ የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም የመውጫ ፈተና ዛሬ ይጠናቀቃል።

ፈተናው 5ኛ ቀኑ ላይ የሚገኝ ሲሆን፤ በዛሬው የጠዋት 2:30 መርሐግብር የነርሲንግ ፈተና እየተሰጠ ነው።

በጁምዓ ምክንያት ጠዋት 5፡30 የሚጀመረው የመውጫ ፈተና ወደ 7፡30 እንዲሁም ከሰዓት 8፡30 የሚጀመረው ፈተና ወደ 10፡30 ተቀይሯል።

የመውጫ ፈተና መጠናቀቅን ተከትሎ በሚኖሩ ቀጣይ ቀናት ውጤት እንደሚገለፅ ይጠበቃል።

በሌላ በኩል በመምህርነት ሙያ ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና በክረምት መርሐግብር ሲከታታሉ የቆዩ #መምህራን የመውጫ ምዘና ነገ ቅዳሜ የካቲት 1/2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ መገለፁ ይታወቃል።

ምስል፦ ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ

@tikvahuniversity

Tikvah-University

07 Feb, 17:21


ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ለአቅም ማሻሻያ ትምህርት (Remedial Program) የተመደቡለትን ተማሪዎች በመቀበል ላይ ይገኛል።

ዩኒቨርሲቲው በ2017 ዓ.ም ለሪሚዲያል ፕሮግራም በትምህርት ሚኒስቴር የተመደቡለትን ተማሪዎች ከጥር 29/2017 ዓ.ም ጀምሮ እየተቀበል ነው፡፡

ዩኒቨርሲቲው በተፈጥሮ እና በማኅበራዊ ሳይንስ መስኮች በአጠቃላይ 2,187 የሪሚዲያል ተማሪዎች ተመድበውለታል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

07 Feb, 17:21


በክረምት መርሐግብር ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ለቆዩ መምህራን የመውጫ ምዘና ነገ ቅዳሜ የካቲት 1/2017 ዓ.ም ይሰጣል።

በመምህርነት ሙያ ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና በክረምት መርሐግብር ለተከታታሉ #መምህራን የመውጫ ምዘና እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወቃል፡፡

ወደ መፈተኛ ማዕከል ስትሔዱ ማንነታችሁን የሚገልፅ መታወቂያ መያዝ የሚጠበቅባችሁ ሲሆን፤ እንደ ተንቀሳቃሽ ስልክ ያሉ የተከለከሉ ነገሮች ይዞ ወደ ፈተና ማዕከል መሔድ አይቻልም፡፡ ፈተናው ከመጀመሩ ከ30 ደቂቃ ቀድማችሁ ልትገኙ ይገባል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

07 Feb, 17:21


ላለፉት አምስት ተከታታይ ቀናት በመላ ሀገሪቱ ሲሰጥ የቆየው 4ኛው የቅደመ-ምረቃ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ዛሬ አመሻሹን ተጠናቋል፡፡

ፈተናው በሀገር አቀፍ ደረጃ በ87 የፈተና ማዕከላት የተሰጠ ሲሆን፤ 176 ሺህ የሚሆኑ ተፈታኞች ለመውጫ ፈተናው ተቀምጠዋል።

በፈተና አሰጣጡ ተንቀሳቃሽ ስልክ ይዞ ወደ ፈተና ጣቢያ ለመገባት መሞከር፣ ዘግይቶ ፈተናውን መስት መጀመር እና የመብራት መቆራራጥ ችግሮች መታየታቸውን ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ የደረሱ መልዕክቶች ያሳያሉ። ከተገለፁት ችግሮች በስተቀር ፈተናው መጠናቀቁን ሰምተናል።

ምስል፦ ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ

@tikvahuniversity

Tikvah-University

06 Feb, 18:06


በአማራ ክልል የ2017 ትምህርት ዘመን የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ተፈታኞች የበይነ መረብ ምዝገባ የካቲት 3/2017 ዓ.ም ይጀምራል።
- የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ

@tikvahuniversity

Tikvah-University

06 Feb, 16:03


#Update

ነገ አርብ ጥር 30/2017 ዓ.ም በሚሰጡ የመውጫ ፈተና ላይ የሰዓት ለውጥ መደረጉን የተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች እየገለፁ ነው፡፡

በዚህም ጠዋት 5፡30 ይጀምር የነበረው ፈተና ወደ ከሰዓት 7፡30 እንዲሁም ከሰዓት 8፡30 ይጀምር የነበረው ፈተና ወደ 10፡30 የተሸጋሸገ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

ምስል፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ፣ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ፣ ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ እና ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ

@tikvahuniversity

Tikvah-University

06 Feb, 16:03


#ተጨማሪ

ነገ አርብ ጥር 30/2017 ዓ.ም በሚሰጡ የመውጫ ፈተና ላይ የሰዓት ለውጥ መደረጉን ዩኒቨርሲቲዎች እየገለፁ ነው፡፡

በዚህም ጠዋት 5፡30 ይጀምር የነበረው ፈተና ወደ ከሰዓት 7፡30 እንዲሁም ከሰዓት 8፡30 ይጀምር የነበረው ፈተና ወደ 10፡30 የተሸጋሸገ መሆኑ ተመላክቷል፡፡ ጠዋት 2:30 የሚጀምረው የነርሲንግ ፈተና ባለበት ይሰጣል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

06 Feb, 16:03


#MoE

አርብ ጥር 30/2017 ዓ.ም ጠዋት 5፡30 የሚጀመረው የመውጫ ፈተና ወደ 7፡30 እንዲሁም ከሰዓት 8፡30 የሚጀመረው ፈተና ወደ 10፡30 የተቀየረ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አረጋግጧል።

የመፈተኛ ማዕከላት በነበሩበት የሚቀጥሉ መሆኑ ተገልጿል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

18 Jan, 14:44


#JimmaUniversity

በ2017 ዓ.ም ለአቅም ማሻሻያ ትምህርት (Remedial Program) ጅማ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ቀናት ጥር 29 እና 30/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

የምዝገባ ቦታ፦
- የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በጅማ ግብርና እና እንስሳት ህክምና ኮሌጅ
- የሶሻል ሳይንስ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው ዋና ግቢ

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

➫ የ12ኛ ክፍል የትምህርት ማስረጃ ዋናውና ኮፒው፣
➫ 3×4 የሆነ ጉርድ ፎቶግራፍ፣
➫ ብርድ ልብስ፣ አንሶላ፣ የትራስ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

18 Jan, 08:59


#ETA

በ2017 ዓ.ም አጋማሽ የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለመጀመሪያ ጊዜ የሚፈተኑ ተማሪዎችን መረጃ ለመሰብሰብ የሚያስችል ቴምፕሌት በትምህርት ሚኒስቴር መዘጋጀቱ ይታወቃል፡፡

ተቋማቱ የተፈታኞቹን መረጃ በሶፍትዌር ቴምፕሌት እንዲያስገቡ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ታህሳስ 30/2017 ዓ.ም በጠየቀው መሰረት የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መረጃዎችን አስገብትዋል፡፡

ይሁን እንጂ በተሰጠው የጊዜ ገደብ መረጃ ያላስገባቹ ተቋማት እና ማስተካከያ እንድታደረጉ ዕድል የተሰጣችሁ ተቋማት በድጋሜ ቴምፕሌቱን በመጠቀም እስከ ጥር 14/2017 ዓ.ም ድረስ እንድታስገቡ ባለሥልጣኑ አሳስቧል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

18 Jan, 08:59


ይመዝገቡ!

5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደርስ ኢንሼቲቭ ነጻ ስልጠናን ለመውሰድ ይመዝገቡ!

የስልጠና ዘርፎች፦

► ዌብ ፕሮግራሚንግ
► አንድሮይድ ማበልፀግ
► ዳታ ሳይንስ

ስልጠናውን በስምንት ሳምንት ያጠናቀቁ ሰልጣኞች ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው ሰርተፊኬት ይሰጣቸዋል።

ለመመዝገብ 👇
https://www.ethiocoders.et/

@tikvahuniversity

Tikvah-University

17 Jan, 13:14


#DebreTaborUniversity

በ2017 ዓ.ም ለአቅም ማሻሻያ ትምህርት (Remedial Program) ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ቀናት ጥር 29 እና 30/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

➫ የ8-12ኛ ክፍል የትምህርት ማስረጃዎች ዋናውና ኮፒው፣
➫ 3×4 የሆነ አራት ጉርድ ፎቶግራፍ፣
➫ ብርድ ልብስ፣ አንሶላ የትራስ ልብስ፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

17 Jan, 13:14


#JigjigaUniversity

ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ በሁለት አዳዲስ የማስተርስ ፕሮግራሞች ትምህርት መስጠት ለመጀመር የውስጥ ማረጋገጫ አውደ ጥናት አካሒዷል፡፡

ዩኒቨርሲቲው አዲስ የሚጀምራቸው የማስተርስ ፕሮግራሞች፦
- MSc in Climate-Smart Dryland Agriculture
- MSc in Sustainable Watershed Management

ፕሮግራሞቹ በሀገሪቱ እየታዩ ለሚገኙ የአካባቢ እና የግብርና ፈተናዎች ምላሽ ለመስጠት ትልቅ አበርክቶ ይኖራቸዋል ተብሏል፡፡

ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ለግብርናና ዘላቂ የተፈጥሮ ሃብት አስተዳደር ትኩረት መስጠቱ በመድረኩ ተገልጿል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

17 Jan, 13:14


#ጥቆማ

የእንግሊዘኛ ቋንቋ ምዘና ፈተና (IELTS Test) በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ይውሰዱ!

ብሪቲሽ ካውንስል ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የ'IELTS' ፈተና የካቲት 1/2017 ዓ.ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ ይሰጣል፡፡

ሁለት አይነት የ'IELTS' ፈተናዎች (IELTS Academic and IELTS General Training) ይሰጣሉ፡፡

ዩኒቨርሲቲው ፈተናውን መውሰድ የሚፈልጉ አመልካቾች ምዝገባ ማድረግ ጀምሯል።

ኦንላይን ይመዝገቡ 👇
https://ethiopia.britishcouncil.org/.../dates-fees-locations

ለበለጠ መረጃ፦
Email: [email protected]
☎️ 0925629589

@tikvahuniversity

Tikvah-University

16 Jan, 14:19


#HaramayaUniversity

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በኅብረተሰብ ጤና የፒ.ኤች.ዲ ፕሮግራም መስጠት ሊጀምር ነው፡፡

በ 'Doctor of Public Health' ፕሮግራም የመጀመሪያ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅት ማጠናቀቁን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡

ተግባር-ተኮር ትምህርት አሰጣጣ የሚኖረው ፕሮግራሙ፤ ለሀገሪቱ የጤና ዘርፍ ጉልህ አበርክቶ የሚኖራቸው ባለሙያዎችን ለማፍራት እንደሚያስችል ዩኒቨርሲቲው ባዘጋጀው የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ ላይ ተገልጿል፡፡

ሁለ-ገብ የሆነው ፕሮግራሙ፤ ሰልጣኞች የአመራር፣ የአስተዳደር፣ የተግባቦት እና ሒሳዊ አስተሳሰብ ክህሎቶችን እንዲያገኙ የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

16 Jan, 12:13


#Update

በ2017 ዓ.ም አጋማሽ የሚሰጠውን የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ዳግም ለመውሰድ ፍላጎት ያላቸው አመልካቾች ምዝገባ ከጥር 8-14/2017 ዓ.ም እንደሚከናወን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡

ለመመዝገብ 👉 https://exam.ethernet.edu.et

ፈተና የሚሰጥበትን ጊዜ በቀጣይ እንደሚያሳውቅ ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡

ከምዝገባ ጋር ተያይዞ ለሚኖራችሁ ጥያቄ ዘውትር በሥራ ሰዓት በተከታዮቹ አማራጮች ማብራሪያ መጠየቅ የምትችሉ መሆኑን ተገልጿል፡፡

Email: [email protected]
☎️ 0911824528 / 0913678404 / 0913949676 / 0910076453 / 0923106826 / 0913866717 / 0911335683

Note:
➫ የመፈተኛ User Name እና Password በመመዝገቢያ ፖርታል በኩል የሚላክ ይሆናል።
➫ የመመዝገቢያ ክፍያ ብር 500 በቴሌብር በኩል ብቻ መፈፀም ይኖርባችኋል፡፡
➫ ምዝገባ ማድረግ የሚቻለው በተጠቀሱት የምዝገባ ቀናት ብቻ ነው፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

15 Jan, 16:30


#NGAT

ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ሲሰጥ ውሏል፡፡

በ2017 ዓ.ም ሁለተኛ ሴሚስተር የድኅረ-ምረቃ ትምህርት ለመከታተል የተመዘገቡ አመልካቾች ፈተና ትምህርት ሚኒስቴር ባስቀመጠው መርሐግብር መሰረት በተለያዩ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ዛሬ ተሰጥቷል፡፡

ምስል፦ ዲላ ዩኒቨርሲቲ፣ ወራቤ ዩኒቨርሲቲ፣ ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ፣ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ

@tikvahuniversity

Tikvah-University

15 Jan, 15:08


#AksumUniversity

በ2017 ዓ.ም ለአቅም ማሻሻያ ትምህርት (Remedial Program) አክሱም ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ቀናት ጥር 15 እና 16/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

የምዝገባ ቦታ፦
በዩኒቨርሲቲው ዋና ግቢ፣ አክሱም ከተማ

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

➫ የ8ኛ ክፍል ፈተና የወሰዳችሁበት ማስረጃ ዋናውና ኮፒው፣
➫ የ12ኛ ክፍል ፈተና የወሰዳችሁበት ማስረጃ ዋናውና ኮፒው፣
➫ የ2ኛ ደረጃ የትምህርት ማስረጃዎች ዋናውና ኮፒው፣
➫ 3×4 የሆነ ስድስት ጉርድ ፎቶግራፍ፣
➫ የመኝታ አልባሳት እና የስፖርት ትጥቅ፣
➫ ማንነታቸሁ የሚገልፅ የታደሰ መታወቂያ፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

15 Jan, 09:08


#EthiopianAviationUniversity

የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ የበረራ አስተናጋጅ (𝐂𝐚𝐛𝐢𝐧 𝐂𝐫𝐞𝐰) ስልጠና ለመውሰድ ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የመጡ 29 ሰልጣኞችን ተቀብሏል።

ሰልጣኖቹ ብቁ የአቪዬሽን ዘርፍ ባለሙያ ለመሆን የሚያስፈልጋቸውን ክህሎት የሚያገኙበት ስልጠና እንደሚወስዱ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

15 Jan, 09:08


#NGAT

ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) እየተሰጠ ነው፡፡

በ2017 ዓ.ም ሁለተኛ ሴሚስተር የድኅረ-ምረቃ ትምህርት ለመከታተል የተመዘገቡ አመልካቾች ፈተና ትምህርት ሚኒስቴር ባስቀመጠው መርሐግብር መሰረት በተለያዩ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ዛሬ ጠዋት መሰጠት ጀምሯል፡፡

ምስል፦ ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ፣ ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ፣ ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ

@tikvahuniversity

Tikvah-University

14 Jan, 19:43


ኢትዮጵያዊቷ ተማሪ የሁዋዌ ሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር ዓለም አቀፍ አምባሳደር ሆና ተመረጠች።

ሁዋዌ ሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር ከመረጣቸው 12 ዓለም አቀፍ አምባሳደሮች መካከል በኢትዮጵያ ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ የ4ኛ ዓመት የኮምፒውተር ሳይንስ ተማሪ የሆነችው አሲያ ከሊፋ አንዷ ሆናለች።

ተማሪ አሲያ በሁዋዌ ሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር 2024 ፕሮግራም ስኬታማ ተሳትፎ ማድረጓ ለ2025 አምባሳደር ሆና እንድትመረጥ አስተዋፅኦ ማድረጉ ተገልጿል።

ተማሪ አሲያ በቻይና በሚካሔደው የአይ.ሲ.ቲ. ታለንት ዲጂታል ጉብኝት የምትሳተፍና የተግባር ልምድ የምታገኝ ይሆናል። #MoE

@tikvahuniversity

Tikvah-University

14 Jan, 13:05


#Update

ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ለመፈተን የተመዘገቡ አመልካቾች ከፈተና ፕሮግራም ጋር ተያይዞ ማስተካከያ ማድረጉን ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል፡፡

አመልካቾች ዝርዝር መረጃውን https://ngat.ethernet.edu.et ላይ በመግባት ማየት እንደሚችሉ ሚኒስቴሩ ጠቁሟል፡፡

ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ነገ ረቡዕ ጥር 7/2017 ዓ.ም ይሰጣል፡፡

ምዝገባ ያደረጋችሁበትን አድራሻ ማለትም https://ngat.ethernet.edu.et በመጠቀም የፈተና ፕሮግራም እና የመፈተኛ መግቢያ ቲኬታችሁን ማግኘት ትችላላችሁ።

ተፈታኞች ወደፈተና ማዕከል ስትሔዱ ማንነታችሁን የሚገልፅ መታወቂያ እና የመፈተኛ Entrance Ticket መያዝ ይኖርባችኋል። ተንቀሳቃሽ ስልክ ይዞ ወደፈተና ማዕከል መግባት ፈፅሞ የተከለከለ መሆኑም ተገልጿል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

11 Jan, 17:14


ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የስፖርት ፌስቲቫል በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ከጥር 17-27/2017 ዓ.ም ይካሔዳል፡፡

ፌስቲቫሉ የዩኒቨርሲቲዎችን ተቋማዊ ግንኙነት እንዲሁም የተማሪዎችን ወንድማማችነት እና እህትማማችነት የሚያዳብር እንደሆነ ተገልጿል፡፡

ተሳታፊ ዩኒቨርሲቲዎች በእግር ኳስ፣ በአትሌቲክስ፣ በቴኳንዶ፣ በቼዝ፣ በገበጣ እና ጡብ የስፖርት አይነቶች እንደሚወዳደሩ ይጠበቃል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

11 Jan, 17:14


ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ ትምህርት (Remedial Program) ተማሪዎችን መቀበል ጀምሯል።

ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም ለሪሚዲያል ፕሮግራም የተመደቡ ተማሪዎች ለጥር 3 እና 4/2017 ዓ.ም ጥሪ ማድረጉ ይታወቃል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

11 Jan, 17:04


በጋዛ የሞቱ ንጹሀን ቁጥር በይፋ ከተገለጸው በ41 በመቶ ሊጨምር እንደሚችል ጥናተ አመላከተ

ከሟቾቹ መካከል 59 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች ፣ ህጻናት እነማ አረጋውን መሆናቸው ተጠቁሟል።
https://bit.ly/4h4GNZz

Tikvah-University

11 Jan, 17:04


በነገው ጨዋታ ጠንካራውን ማንችስተር ዩናይትድ ትመለከታላችሁ - ሩብን አሞሪም

ነገ ምሽት 12 ሰዓት በኤፍኤ ካፕ ፍልሚያ ከአርሰናል ጋር የሚገናኘው ዩናይትድ ዋንጫውን እንዲያነሳ እንደሚፈልጉ አሰልጣኙ ተናግረዋል።
https://bit.ly/429bec3

Tikvah-University

11 Jan, 17:04


በጎዳና ላይ ያሉ ሰዎችን ያለፈቃዳቸው መያዝና ወደ ማቆያ ማዕከላት ማስገባት ሊቆም ይገባል-ኢሰመኮ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ወደ ማቆያ የሚገቡ ሰዎች በማዕከሉ ከመቆየት እና የእርሻ ሥራ ከመሥራት እንዲመርጡ እየተደረጉ ነው ብሏል
https://bit.ly/3Wixe0v

Tikvah-University

11 Jan, 17:04


የጄጁ ኤየር አውሮፕላን 'ብላክ ቦክ' መረጃ መመዝገብ ያቆመው ከመከስከሱ ከአራት ደቂቃ በፊት እንደነበር የደቡብ ኮሪያ የትራስፖርት ሚኒስቴር ገለጸ

በደቡብ ኮሪያ ታሪክ እጅግ ከባድ የተባለው የአውሮፕላን መከስከስ አደጋ 179 ሰዎች ህይወት አልፏል።
https://bit.ly/4j4CDlP

Tikvah-University

11 Jan, 17:04


የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀመድ ወደ አዲስ አበባ እንደሚያቀኑ ተነገረ

በዲፕሎማሲ ውጥረት ውስጥ የቆዩት ሁለቱ ጎረቤት ሀገራት ከአንካራው የመሪዎች ስምምነት በኋላ ወደ አዲስአበባ እና ሞቃዲሾ ከፍተኛ ልዑካን ቡድናቸውን ልከው ተወያይተዋል
https://bit.ly/4afQ3XP

Tikvah-University

11 Jan, 17:04


ትራምፕ በሩሲያ ላይ የተጣሉ ማዕቀቦችን ሊያነሱ ይችላሉ በሚል የአውሮፓ ሀገራት ስጋት እንዳደረባቸው ተገለጸ

ሞስኮ ከዩክሬን ጋር በገባችበት ጦርነት በባይደን አስተዳደር የተጣሉ ማዕቀቦችን ተመራጩ ፕሬዝዳንት ሊሰርዙ እንደሚችሉ ተነግሯል።
https://bit.ly/4h8J0Th

Tikvah-University

11 Jan, 17:04


ትራምፕ ግሪንላንድ ለመቆጣጠር መፈለጋቸውን ተከትሎ ዴንማርክ የቅኝት መርከቦችን ለማሰማራት አቀደች

ትራምፕ ከግሪንላንድ በተጨማሪ የፓናማ ቦይን እንደሚጠቀልሉ እንዲሁም ካናዳ የአሜሪካ 51 ግዛት እንድትሆን እንደሚፈልጉ ተናግረዋል።
https://bit.ly/3DOOGDH

Tikvah-University

11 Jan, 17:04


ትራምፕ ቅጣት አልባ የጥፋተኝነት ፍርድ ተላለፈባቸው

ትራምፕ በወንጀል ጥፋተኛ ተብለው ወደ ኃይት ሀውስ የሚገቡ የመጀመሪያው ፕሬዝደንት ይሆናሉ ተብሏል።
ትራምፕ ጥፋተኛ አለመሆናቸውን እና ውሳኔውን ለማስቀልበስ ይግባኝ እንደሚሉም ዝተዋል።
https://bit.ly/4hbEF1G

Tikvah-University

11 Jan, 17:04


በሎስ አንጀለስ የተከሰተውን እሳት ለመቆጣጠር እስረኞች እንዲሰማሩ የካሊፎርኒያ ግዛት ፈቃድ ሰጥታለች

በተለያዩ ወንጀሎች ተፈርዶባቸው በማረሚያ ቤቶች ውስጥ የሚገኙት እስረኞች መጠነኛ ስልጠና ወስደው እሳቱን ለመቆጣጠር እያገዙ ነው ተብሏል
https://bit.ly/3Wamp0E

Tikvah-University

11 Jan, 14:22


#WerabeUniversity

በ2017 ዓ.ም ለሪሚዲያል ፕሮግራም ወራቤ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ቀናት ጥር 21 እና 22/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

➫ ከ8-12ኛ ክፍል የትምህርት ማስረጃዎች ዋናውና ኮፒው፣
➫ የታደሰ የቀበሌ መታወቂያ፣
➫ 3×4 የሆነ አራት ጉርድ ፎቶግራፍ፣
➫ ብርድ ልብስ፣ አንሶላ፣ ትራስ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

11 Jan, 14:22


#AmboUniversity

በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል አጠናቃችሁ ለአቅም ማሻሻያ ትምህርት (Remedial Program) አምቦ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች ምዝገባ ጥር 29 እና 30/2017 ዓ.ም እንደሚከናወን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

የምዝገባ ቦታ፦
➫ የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በዋናው ካምፓስ
➫ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በሃጫሉ ሁንዴሳ ካምፓስ

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

➫ የ8ኛ ክፍል ሰርቲፊኬት ዋናውና ኮፒው፣
➫ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
➫ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ስርቲፊኬት ዋናውና ኮፒው፣
➫ 3×4 የሆነ ሁለት ጉርድ ፎቶግራፍ፣
➫ አንሶላ፤ ብርድልብስ፣ ትራስ ልብስ እንዲሁም የስፖርት ትጥቅ፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

11 Jan, 14:22


ይመዝገቡ!

በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ ተፈታኞች ምዝገባ የፊታችን ማክሰኞ ጥር 6/2017 ዓ.ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ይጠናቀቃል፡፡

ምዝገባ ያላጠናቀቃችሁ ተማሪዎች ከቀነ ገደቡ አስቀድማችሁ ምዝገባችሁን እንድታጠናቅቁ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ማሳሰቡ ይታወቃል።

ያስተውሉ፦
ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ይዘት በአጠቃላይ ከ9-12ኛ ክፍሎች እንዲሁም የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ይዘት ከ7-8ኛ ክፍሎች እንደሚሸፍን አገልግሎቱ መግለፁ አይዘነጋም።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

10 Jan, 14:28


#MoH

የ2024 ብሔራዊ የህክምና ስፔሻሊቲ ስልጠና (ERMP) ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል፡፡

ታህሳስ 22/2017 ዓ.ም በ15 የፈተና ማዕከላት የተሰጠውን ፈተና፤ 1,811 ዕጩ ተፈታኞች የወሰዱ ሲሆን የአንድ ተፈታኝ ውጤት መሰረዙን ጤና ሚኒስቴር ገልጿል፡፡

ተፈታኞች የተሰጣቸውን User ID በመጠቀም ውጤታቸውን ከዛሬ ጀምሮ ማየት እንደሚችሉ ሚኒስቴሩ አሳውቋል፡፡

በውጤቱ ላይ ቅሬታ ያላቸው ተፈታኞች፤ ሥም፣ User ID፣ ውጤት እና የፈተና ማዕከል በመግለፅ በሚኒስቴሩ ነፃ የስልክ ጥሪ ቁጥር 952 እስከ ጥር 8/2017 ዓ.ም በሥራ ሰዓት ቅሬታቸውን ማቅረብ ይችላሉ ተብሏል፡፡

የስፔሻሊቲ እና/ወይም የዩኒቨርሲቲ ምርጫ ማስተካከያ እስከ ጥር 8/2017 ዓ.ም ማድረግ እንደሚቻልም ተገልጿል። 

ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ (Anesthesiology CCPM and Emergency & CCM)፣ ወሎ ዩኒቨርሲቲ (Orthopedics) እና መቐለ ዩኒቨርሲቲ (Dermatovenerology) ለዘንድሮ ERMP ስልጠና የተጨመሩ ፕሮግራሞች መሆናቸው ተገልጿል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

10 Jan, 09:09


#Update

ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ለመውሰድ የተመዘገቡ አመልካቾች ፈተና ጥር 7/2017 ዓ.ም ይሰጣል፡፡

የፈተና ፕሮግራም እና የመፈተኛ መግቢያ ቲኬትን ምዝገባ ባደረጋችሁበት አድራሻ ማለትም https://ngat.ethernet.edu.et በኩል ማግኘት የምትችሉ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።

አመልካቾች ወደፈተና ማዕከል ስትሔዱ ማንነታችሁን የሚገልፅ መታወቂያ እና የመፈተኛ ENTRANCE TICKET መያዝ ይኖርባችኋል።

ተንቀሳቃሽ ስልክ ይዞ ወደፈተና ማዕከል መምጣት ፈፅሞ የተከለከለ ነው ተባለ ሲሆን፤ ፈተና ከመጀመሩ ከ30 ደቂቃ በፊት የፈተና ማዕከል መገኘት ይኖርባችኋል ተብሏል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

09 Jan, 14:19


መቱ ዩኒቨርሲቲ የ2017 ዓ.ም የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም አዲስ ገቢ ተማሪዎችን በመቀበል ላይ ይገኛል፡፡

ወደ ተቋሙ የተመደቡ የ2017 ዓ.ም ሪሚዲያል ተማሪዎች ጥር 1 እና 2/2017 ዓ.ም ሪፖርት እንዲያደርጉ ዩኒቨርሲቲው ጥሪ ማድረጉ ይታወሳል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

07 Jan, 17:44


#ጥቆማ

የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ኢንሼቲቪ ስልጠናዎችን በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ይውሰዱ!

አስተዳደሩ ለስልጠናዎቹ የሚያስፈልጉ ምቹ ቦታ እንዲሁም የኮምፒውተር እና ኢንተርኔት አቅርቦት አዘጋጅቷል፡፡

ስልጠናው ጥር 3/2017 ዓ.ም ይጀምራል፡፡

የስልጠና ቀናት፦ ቅዳሜ እና እሁድ
የስልጠና ሰዓት፦ ከ2፡30-11፡30
የስልጠና ቦታ፦ ወሎ ሰፈር አካባቢ በሚገኘው የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ቢሮ

ይመዝገቡ 👇
https://shorturl.at/5mPqv

@tikvahuniversity

Tikvah-University

07 Jan, 17:44


የወለጋ ዩኒቨርሲቲ ሴኔት በ2017 ዓ.ም በመደበኛ ፕሮግራም ለሪሚዲያል ትምህርት ወደ ተቋሙ የተመደቡ ተማሪዎች ምዝገባ ጥር 19 እና 20/2017 ዓ.ም እንዲካሔድ ወስኗል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

06 Jan, 15:51


#ArsiUniversity

በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስዳችሁ ለአቅም ማሻሻያ ትምህርት (Remedial Program) አርሲ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች የመመዝገቢያ ቀናት ጥር 19 እና 20/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

➫ የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ዋናውና ኮፒው፣
➫ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
➫ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ስርተፊኬት ዋናውና ኮፒው፣
➫ ስድስት 3×4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣
➫ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ ትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ትጥቅ።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

06 Jan, 15:51


#JinkaUniversity

በ2017 ዓ.ም በአቅም ማካካሻ (ሪሚዲያል) ፕሮግራም ጂንካ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሔደው ጥር 13 እና 14/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ትምህርት ጥር 15/2017 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል፡፡

ለምዝገባ ስትሔዱ ከ8ኛ ክፍል ጀምሮ ያሉ የትምህርት ማስረጃዎች እንዲሁም ብርድ ልብስ፣ አንሶላ እና ትራስ ጨርቅ መያዝ ይጠበቅባችኋል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

06 Jan, 11:40


#ጥቆማ

የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ኢንሼቲቪ ስልጠናዎችን በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ይውሰዱ!

አስተዳደሩ ለስልጠናዎቹ የሚያስፈልጉ ምቹ ቦታ እንዲሁም የኮምፒውተር እና ኢንተርኔት አቅርቦት አዘጋጅቷል፡፡

ስልጠናው ጥር 3/2017 ዓ.ም ይጀምራል፡፡

የስልጠና ቀናት፦ ቅዳሜ እና እሁድ
የስልጠና ሰዓት፦ ከ2፡30-11፡30
የስልጠና ቦታ፦ ወሎ ሰፈር አካባቢ በሚገኘው የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ቢሮ

ይመዝገቡ 👇
https://shorturl.at/5mPqv

@tikvahuniversity

Tikvah-University

06 Jan, 11:40


#MoE

በክረምት በመምህርነት ሙያ ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና ስትከታተሉ ቆይታችሁ የመውጫ ምዘና ለመውሰድ የምትጠባበቁ መምህራን፥ ምዘናው ከየካቲት 10-12/2017 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡

ምዘናው በየአቅራቢያችሁ በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች የሚሰጥ ሲሆን፤ የመፈተኛ ማዕከላቱ በቀጣይ በክልል/ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች በኩል ይገለጻል ተብሏል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

06 Jan, 11:40


#AAU

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በቅርቡ የሰጠውን የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራም የሁለተኛ ሴሚስተር የመግቢያ ፈተና (GAT) የወሰዱ አመልካቾች የውጤት ሰርተፍኬታቸውን ማግኘት እንደሚችሉ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

ሰርተፍኬታችሁን ለማግኘት 👇
http://portal.aau.edu.et/Web/ApplyForAdmission/TestingStatus

@tikvahuniversity

Tikvah-University

06 Jan, 11:40


#SamaraUniversity

በ2017 ዓ.ም በሠመራ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ ትምህርት (Remedial Program) ለመከታተል የተመደባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ቀን ጥር 14/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

ምዝገባ ጥር 15 እና 16/2017 ዓ.ም የሚከናወን ሲሆን፤ ትምህርት ጥር 19/2017 ዓ.ም እንደሚጀምር ተገልጿል፡፡

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

➫ የ8ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሰርቲፊኬት ዋናውና ኮፒው፣
➫ የ12ኛ ክፍል ሠርቲፊኬት ዋናውንና ፎቶ ኮፒ
➫ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
➫ ስምንት 3×4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣
➫ አንሶላ፣ ትራስ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

05 Jan, 16:38


የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመላ ሀገሪቱ  ከ20 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች የአቪዬሽን ዘርፍ ፈተና እየሰጠ ነው።

አየር መንገዱ ከ20 ሺህ በላይ ለሚሆኑ አመልካቾች በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የፅሑፍ ፈተና እየሰጠ መሆኑን አሳውቋል።

የመግቢያ ፈተናው እየተሰጠ የሚገኘው በአዳማ፣ አምቦ፣ አርባ ምንጭ፣ አሶሳ፣ ባህርዳር፣ ደሴ፣ ድሬዳዋ፣ ጋምቤላ፣ ጎንደር፣ ሀዋሳ፣ ጅግጅጋ፣ ጅማ፣ መቐለ፣ ነቀምቴ፣ ሮቤ፣ ሰመራ፣ ወልቂጤ እና አዲስ አበባ በሚገኙ ዩኒቨርሲዎች እና የፈተና ጣቢያዎች መሆኑን አየር መንገዱ ገልጿል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች አመልካቾችን አወዳድሮ ለመቅጠር ባለፈው ህዳር ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

05 Jan, 08:59


#Update

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ምዝገባ ጥር 6/2017 ዓ.ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ላይ እንደሚጠናቀቅ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

ስለሆነም ምዝገባ ያላጠናቀቃችሁ ተማሪዎች ከቀነ ገደቡ አስቀድማችሁ እንድታጠናቅቁ አገልግሎቱ አሳስቧል።

አገልግሎቱ የ2017 ዓ.ም ፈተናዎች ይዘትን በተመለከተ ባስተላለፈው መልዕክት፤ የሀገር አቀፍ 12ኛ ክፍል ፈተና በአጠቃላይ ከ 9-12ኛ ክፍሎች እንዲሁም የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከ7-8ኛ ክፍሎች እንደሚሸፍን ገልጿል።

ተማሪዎች በተማሩበት የክፍል ደረጀ የተማሪ መጽሐፍን መሠረት አድርገው ሊዘጋጁ እንደሚገባ አገልግሎቱ ጠቁሟል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

03 Jan, 17:52


ዛሬ ለሊት ያበቃል። ይመዝገቡ!

ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) አመልካቾች ምዝገባ ዛሬ አርብ ታህሳስ 25/2017 ዓ.ም ለሊት 6:00 ሰዓት ያበቃል፡፡

ይመዝገቡ 👇
HTTPS://NGAT.ETHERNET.EDU.ET

አመልካቾች የመመዝገቢያ ክፍያ ብር 750 በቴሌብር በኩል ብቻ መፈፀም የሚጠበቅባችሁ ሲሆን፤ የመፈተኛ User Name እና Password በመመዝገቢያ ፖርታል በኩል የሚላክ ይሆናል፡፡

ፈተናው የሚሰጥበት ጊዜ በቀጣይ ይፋ እንደሚደረግ ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወቃል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

03 Jan, 14:47


#ጥቆማ

በአዲስ አበባና አካባቢዋ የሚኖሩና "የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ኢንሼቲቪ" ስልጠናን መውሰድ ለሚፈልጉ ጥሩ ዕድል ማመቻቸቱን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሳ) አሳውቋል።

ስልጠናውን ለመከታተል ለሚመጡ ሰልጣኞች የኮምፒውተር እና ኢንተርኔት አቅርቦት ዝግጁ መደረጉ ተጠቁሟል። የዕድሉ ተጠቃሚ ለመሆን የሚፈልጉ እንዲመዘገቡም ጥሪ ቀርቧል።

የአንደኛ እና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች፣ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንዲሁም የመንግሥት እና የግል ሠራተኞች ስልጠናውን መከታተል ይችላሉ ተብሏል።

ስልጠናው ከጥር 3/2017 ዓ.ም ጀምሮ ሁልጊዜ በሳምንቱ የዕረፍት ቀናት (ቅዳሜ እና እሑድ) እንደሚሰጥ ተገልጿል። (ቅዳሜ እና እሑድ ከጠዋቱ 2፡30 እስከ አመሻሽ 11:30)

የስልጠና ቦታ፦
አዲስ አበባ ወሎ ሰፈር አካባቢ በሚገኘው የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ቢሮ

ለመመዝገብ፦
https://awareness.insa.gov.et/index.php/143154?lang=am

@tikvahuniversity

Tikvah-University

03 Jan, 14:47


#AAU

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቅድመ-ምረቃ ተማሪዎቹ የተሻሻለውን የወጪ መጋራት ውል እንዲፈርሙ ጥሪ አድርጓል፡፡

የትምህርት ሚኒስቴር የተማሪዎች የምግብ ወጪ መጋራት ላይ ማሻሻያ ማድረጉን ተከትሎ የተቋሙ ተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት ወጪ መጋራት የተጠቃሚ ውል እየፈረሙ እንደሚገኙ ዩኒቨርሲቲው አስታውሷል፡፡

በርካታ ተማሪዎች ውሉን መፈረማቸውን የገለፀው ዩኒቨርሲቲው፤ አስካሁን ያልፈረሙ ጥቂት ተማሪዎች ለመጨረሻ ጊዜ እስከ ሰኞ ታህሳስ 28/2017 ዓ.ም ድረስ ውል በመፈረም ተማሪዎች አገልግሎት ቢሮ እንዲያስገቡ ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል፡፡

ከምግብ/መኝታ ወደ ጥሬ ገንዘብ ወይም ከጥሬ ገንዘብ ወደ ምግብ/መኝታ ለመቀየር የሚፈልጉ ተማሪዎች ከጥር 8-13/2017 ዓ.ም ድረስ ወጪ መጋራት ቢሮ መመዝገብ እንደሚችሉም ተገልጿል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

03 Jan, 14:47


#ጥቆማ

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛው መርሐ ግብር በሚድዋይፈሪ በ post-basic የመጀመሪያ ዲግሪ ሰልጣኞችን ተቀብሎ ለማስተማር ይፈልጋል፡፡

መስፈርቶች፦
➫ በሚድዋይፈሪ ዲፕሎማ ወይም ደረጃ IV የለው/ያላት እና COC ፈተና ያለፈ/ች፣
➫ ሁለት ዓመት እና ከዚያ በላይ የሥራ ልምድ ያለው/ያላት፣
➫ የመግቢያ ፈተና ወስደው ማለፊያ ነጥብ ማምጣት የሚችሉ፣
➫ ስፖንሰርሺፕ ማቅረብ የሚችሉ ወይም በግል መክፈል የሚችሉ፣
➫ የድጋፍ ደብዳቤ ማቅረብ የሚችል/የምትችል፡፡

የማመልከቻው ጊዜ የሚያበቃው፦ ጥር 2/2017 ዓ.ም

የማመልከቻ ቦታ፦
በዋናው ግቢ የህ/ጤ/ሳ/ኮሌጅ ቅ/ረጅስትራር (ህንጻ 26፣ ቢሮ ቁ. 5)

የመግቢያ ፈተና የሚሰጥበት ቀን፦ ጥር 15/2017 ዓ.ም

አመልካቾች ከላይ የተጠቀሱትን ማስረጃዎች ዋናውና ኮፒውን በአካል ወይም በተወካይ ማቅረብ ይጠበቅባችኋል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

03 Jan, 14:47


📽 😍 ክፍል ሦስት ተለቋል!

የሳፋሪኮም #1Wedefit ዲጂታል የሙዚቃ ውድድር ኮከቦቻችን ከበፍርዱ ጋር በሙዚቃ ቢዝነስ ዙሪያ ያደረጉትን ፀዴ ቆይታ በYouTube ገጻችን ይከታተሉ!

👉🏼 https://youtu.be/a-GxqX_InbY

#SafaricomEthiopia #1Wedefit #FurtherAheadTogether #DigitalMusicChallenge

Tikvah-University

02 Jan, 13:12


#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር በ2017 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራንን አቅም ለማጐልበት የሚያግዝ ስልጠና ለመስጠት የቅድመ ዝግጅት ሥራ እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጿል፡፡

የሚሰጠው ስልጠና የመምህራንን የስልጠና ፍላጐት ታሳቢ ያደረገ እንዲሆን በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ከሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ መምህራን መረጃ ለመሰብሰብ የሚያስችል የበይነ-መረብ መጠይቅ አዘጋጅቷል።

በመሆኑም በሁሉም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ጂኦግራፊ፣ ታሪክ፣ ኢኮኖሚክስ፣ ስነ-ዜጋ እና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ የትምህርት ዓይነቶች የምታስተምሩ መምህራን ከታች በተቀመጠው ሊንክ በመግባት የተዘጋጀውን መጠይቅ እንድትሞ ሚኒስቴሩ ጥሪ አድርጓል፡፡

መጠይቁን ለመሙላት
https://forms.gle/NTMzLQK6pohUpvkq6

@tikvahuniversity

Tikvah-University

02 Jan, 13:12


#ETA

የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በተለያዩ የሥራ መደቦች ባለሙያዎችን አወዳድሮ በዝውውር ለመቅጠር ታህሳስ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡

በሥራ መደቦቹ ላይ ተወዳድራችሁ በዝውውር ለመቅጠር የምትፈልጉ ባለሙያዎች ሽሮሜዳ አሜሪካ  ኤምባሲ ፊት ለፊት በሚገኘው የባለሥልጣኑ ዋና መ/ቤት የብቃትና ሰው ሃብት አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 226 እና 227 በአካል በመገኘት ማመልከት የምትችሉ መሆኑን ተቋሙ አሳውቋል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

02 Jan, 13:12


#WoldiaUniversity

በ2017 ዓ.ም ወልድያ ዩኒቨርሲቲ በአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ለመከታተል የተመደባችሁ አዲስ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ጥር 19 እና 20/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

በምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

➫ የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ካርድ ዋናውና ኮፒው፣
➫ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክርፕት ዋናውና ኮፒው፣
➫ አራት 3x4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣
➫ የሌሊት አልባሳት እና የስፖርት ትጥቅ፡፡

የመማር ማስተማር ሥራ ጥር 22/2017 ዓ.ም የሚጀምር መሆኑ ተገልጿል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

01 Jan, 15:54


#የሥራ_ቅጥር_ዕድል_ጥቆማ
#ETA

የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በተለያዩ የሥራ መደቦች ባለሙያዎችን አወዳድሮ በዝውውር መቅጠር ይፈልጋል፡፡

➤ ተፈላጊ ባለሙያዎች ብዛት፦ 49
➤ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፦ ከዲፕሎማ እስከ ማስተርስ ዲግሪ
➤ የሥራ ቦታ፦ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ዋና ቢሮ

(ተቋሙ ያወጣው ማስታወቂያ ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity

Tikvah-University

01 Jan, 15:54


#AssosaUniversity

በ2017 ዓ.ም አሶሳ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ወደ ተቋሙ የመግቢያ ጊዜ ጥር 22 እና 23/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

- ከ8-12ኛ ክፍል ሰርፍትኬት እና ትራንስክፕሪት ዋናውና ኮፒው፣
- 3x4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣
- አንሶላ፣ ብርድ ልብስ እና ትራስ ልብስ።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

01 Jan, 12:44


#ይመዝገቡ!

ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) አመልካቾች ምዝገባ አርብ ታህሳስ 25/2017 ዓ.ም ያበቃል፡፡

ይመዝገቡ 👇
HTTPS://NGAT.ETHERNET.EDU.ET

የመመዝገቢያ ክፍያ ብር 750 በቴሌብር በኩል ብቻ መፈፀም የሚጠበቅባችሁ ሲሆን፤ የመፈተኛ User Name እና Password በመመዝገቢያ ፖርታል በኩል የሚላክ ይሆናል፡፡

ፈተናው የሚሰጥበት ጊዜ በቀጣይ እንደሚደረግ ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወቃል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

01 Jan, 12:19


በመቀሌ ሰላማዊ ሰልፍ በመደረግ ላይ ነው

ህወሃት ኢትዮጵያን ለማፍረስ ሲል ባደራጀው ሃይል እየተዋከበ ፣እየተፈረካከሰ ይገኛል። ህወሃት የትግራይን ወጣት ከኢትዮጵያዊነቱ ነጥሎ፣የጥላቻ ትርክት ሞልቶ ኢትዮጵያን ለመበተን በቆፈረው የጥላቻና የሴራ ጉድጓድ እራሱ ህወሃት ከገባበት ዋል እደር ያለ ቢሆንም አሁን ግን እስትንፋሱን የሚያቋረጥ ሃይል ከዚያው ከትግራይ ተከስቷል። ህዝቡ እና ወጣቱ እንቢ በማለት ድምጼ ይሰማ ብሎ እንዲህ አደባባይ ወጥቷል::

አሁንም መፍትሄው ቀላል ነው።ህወሃት እራሱን ሊደፋው ከደረሰው ጥጋቡና ለስልጣን ፣ለጥቅም ሲል እርስበርሱ እየተሻኮተ ያለውን ነገር ማቆም፣በጥላቻ ያሳበደውን ወጣት ወደ ስልጠና ካምፕ ወስዶ ማሰልጠን፣ማስተማር ከሁሉም ብሄረሰብ ጋር ተግባብቶ መኖር አማራጭ እንዳልሆነ ደጋግሞ መንገር፣ህወሃት ለበደለው የትግራይ ህዝብ ይቅርታ መጠየቅ ፣ካሳ መክፈል ነው።

ይኸው ነው!

Tikvah-University

30 Dec, 18:44


#NGAT

ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) አመልካቾች ምዝገባ ከታህሳስ 21 እስከ 25/2017 ዓ.ም ይከናወናል፡፡

ለመመዝገብ 👇
HTTPS://NGAT.ETHERNET.EDU.ET

ከምዝገባ ጋር ለተያያዘ ማንኛውም ጥያቄ በሥራ ሰዓት በኢሜል አድራሻ [email protected] ወይም በስልክ ቁጥር 0920157474 (Enatnesh Gebeyehu) እና 0911335683 (Fasil Tsegaye) ማብራሪያ መጠየቅ የምትችሉ መሆኑን ተገልጿል።

የመፈተኛ USER NAME እና PASSWORD በመመዝገቢያ ፖርታል በኩል የሚላክ ሲሆን፤ የመመዝገቢያ ክፍያ ብር 750 በቴሌብር በኩል ብቻ መፈጸም ይጠበቅባችኋል ተብሏል፡፡

ፈተናው የሚሰጥበትን ጊዜ በቀጣይ እንደሚያሳውቅ ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

30 Dec, 11:48


#EAES

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በድጋሜ የሚወስዱ ተፈታኞች በራሳቸው የሚመዘገቡበት አድራሻን ይፋ አድርጓል፡፡

በድጋሜ ፈተናውን የሚወስዱ ተፈታኞች https://register.eaes.et/Online በመጠቀም በበየነ-መረብ መመዝገብ ይችላሉ ተብሏል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

30 Dec, 11:48


#MoH

የ2024 የብሔራዊ የህክምና ስፔሻሊቲ ስልጠና (ERMP) አመልካቾች ፈተና ማክሰኞ ታህሳስ 22/2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ ጤና ሚኒስቴር መግለፀሐ ይታወቃል፡፡

የ ERMP 2024 ተፈታኞች ዝርዝር ለማየት፦
https://www.moh.gov.et/en/media/170

@tikvahuniversity

Tikvah-University

30 Dec, 11:48


ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም የተመደቡለትን የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ተማሪዎች ዛሬ መቀበል ጀምሯል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

30 Dec, 11:48


እስካሁን ከ499,000 በላይ ተማሪዎች በ2017 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመውሰድ ተመዝግበዋል፡፡ - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

በ2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የማጠናቀቀቂያ ፈተና ለመውሰድ እስካሁን 499,200 ተማሪዎች መመዝገባቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል፡፡

በመደበኛ እና በግል 750,000 ተማሪዎች ይመዘገባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ በአገልግሎቱ የተፈታኞች ምዝገባ፣ የፈተና ዕርማትና ውጤት ጥንቅር ዴስክ ኃላፊ ማዕረፉ ሌሬቦ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ተናግረዋል።

የመደበኛ ተፈታኝ ተማሪዎች ምዝገባ በኦንላይን ከታህሳስ 8/2017 ዓ.ም ጀምሮ እየተከናወነ ሲሆን፤ ጥር 6/2017 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ ኃላፊው ገልፀዋል።

በመደበኛው ፕሮግራም 600,000 ተማሪዎች ለመመዝገብ ዕቅድ መያዙን የገለፁት ኃላፊው፤ እስካሁን 82 በመቶ የሚሆኑ መደበኛ ተማሪዎች መመዝገባቸውን ጠቁመዋል። በግል የሚፈተኑ 150,000 ተማሪዎች እንደሚመዘገቡ ሲጠበቅ፤ እስካሁን 1,100 ተማሪዎች ብቻ ምዝገባ አድርገዋል፡፡

የኢንተርኔት አማራጭ በሌለባቸው አካባቢዎች ተማሪዎች በወረቀት ከተመዘገቡ በኋላ ኢንተርኔት የሚሠራበት አካባቢ በመሔድ መረጃቸውን ወደ ኦንላይን መጫን እንደሚችሉ ኃላፊው ተናግረዋል። #FMC

@tikvahuniversity

Tikvah-University

29 Dec, 07:01


በሀረሪ ክልል "ከደረጃ በታች የሆኑ" ስድስት የግል ኮሌጆች መዘጋታቸውን የክልሉ የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ገለፀ።

ኮሌጆቹ አገልግሎታቸውን እንዲያሻሽሉ ኤጀንሲው ድጋፍና ክትትል በማድረግ ስልጠናዎችን ሲሰጣቸው ቢቆይም በተደረገ ክትትል የሚሰጡትን አገልግሎት ማሻሻል ሳይችሉ በመቅረታቸው እርምጃው መወሰዱን የኤጀንሲው ኃላፊ ነቢላ ማህዲ ገልፀዋል።

አፍራንቀሎ ኮሌጅ፣ ሪፍት ቫሊ ኮሌጅ፣ አዋሽ ቫሊ ኮሌጅ፣ ወሊፍ ኮሌጅ፣ ሉሲ ኮሌጅ እና ሙርቲ ጉቱ ኮሌጅ እንዲየዘጉ የተደረጉት ኮሌጆች መሆናቸውም ተገልጿል።

ኮሌጆቹ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ስትራቴጂ ከተቀመጠው 1 ለ 25 አሰራር በመውጣት አንድ መምህር ከ 50 እስከ 70 ተማሪዎችን እንዲያስተምር ሲያደርጉ መቆየታቸውንም አክለዋል።

ኮሌጆቹ በአግባቡ ያልተደራጁ፣ ምቹ የትምህርት አካባቢ የሌላቸው፣ በተበታተኑ ማዕከላት ሲያስተምሩ የነበሩ እና የትምህርት ጥራት ችግር የተስተዋለባቸው መሆናቸውንም ጠቁመዋል።

ኮሌጆቹ የማስተማሪያ ዕውቅናቸውን ሳያድሱ ግዜው ባለፈበት ፈቃድ ሲጠቀሙ የነበሩ ከመሆናቸው ባለፈ በርካታ የመመሪያ ጥሰት መፈፀማቸው ተመልክቷል።

ኮሌጆቹ ሲያተምሯቸው የቆዩ ተማሪዎች በተደጋጋሚ የብቃት ማረጋገጫ ፈተና እንዲወስዱ ቢደረግም ማሳለፍ ያልቻሉ መሆናቸውን ኃላፊዋ አረጋግጠዋል።

ኤጀንሲው ተማሪዎችን ደረጃቸውን ወዳሟሉ ኮሌጆች ለማዛወር እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን ከክልሉ ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ የተገኘ መረጃ ያሳያል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

28 Dec, 17:33


#MekelleUniversity

መቐለ ዩኒቨርሲቲ በግንባታ ቴክኖሎጂ እና አስተዳደር በማስተርስ ፕሮግራም ያሰጠናቸውን ቻይናውያን ተማሪዎች አስመርቋል።

ዓለም አቀፍ ተማሪዎቹ በዩኒቨርሲቲው ሲቪል ምህንድስና ትምህርት ቤት በግንባታ ቴክኖሎጂ እና አስተዳደር ትምህርት በማስተርስ ፕሮግራም ስልጠናቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ መሆናቸው ተገልጿል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

28 Dec, 17:33


#AAU

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሐሙስ የተሰጠው የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራም የሁለተኛ ሴሚስተር የመግቢያ ፈተና (GAT) ላመለጣችሁ አመልካቾች ፈተናው ማክሰኞ ታህሳስ 22/2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

የፈተና ቦታ፦
5 ኪሎ AAiT ካምፓስ እና 6 ኪሎ FBE ካምፓስ

የፈተና ሰዓት፦ ጠዋት ከ2:00-6:00 ሰዓት

ተፈታኞች ፈተናው መሰጠት ከመጀመሩ 30 ደቂቃ ቀድማችሁ መገኘት ይኖርባችኋል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

28 Dec, 09:26


#EAES

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በድጋሜ የሚወስዱ ተፈታኞች በራሳቸው የሚመዘገቡበት አድራሻን ይፋ አድርጓል፡፡

በድጋሜ ፈተናውን የሚወስዱ ተፈታኞች https://register.eaes.et/Online በመጠቀም በበየነ-መረብ መመዝገብ ይችላሉ ተብሏል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

28 Dec, 09:26


#MekelleUniversity

መቐለ ዩኒቨርሲቲ ከአዲሱ ብሔራዊ የተማሪዎች የምግብ ሜኑ ትግበራ ጋር ተያይዞ በተነሳው ጥያቄ የተከሰተን ረብሻ ተከትሎ የሞተም ሆነ ታፍነው የተወሰዱ ተማሪዎች እንደሌሉ ገለፀ።

በመተግበር ላይ የሚገኘው አዲሱ የዩኒቨርሲቲ ሜኑ ከብሔራዊው ሜኑ በበጀት እና በይዘት የሚጠበቅበትን መሰረት ሳይለቅ አስፈላጊው ማስተካከያ የማድረግ ሒደት እየተሠራበት እንደሚገኝ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡

ረብሻው ተከስቶ በነበረበት ወቅት "በፀጥታ አካላት በተካሔደ የማረጋጋት ሥራ ተማሪ እንደሞተ እንዲሁም ደብዛቸው የጠፋ ታፍነው የተወሰዱ ተማሪዎች እንዳሉ" ተደርጎ እየተሰራጨ ያለው መረጃ ከእውነት የራቀ እና ሐሰተኛ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ባወጣው መግለጫ አስረድቷል፡፡

የተቋሙ ተማሪዎች በሰላማዊ መንገድ የሚያቀርቧቸውን ጥያቄዎች ዩኒቨርሲቲው ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኑን ገልጿል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

28 Dec, 09:26


#ETA

84 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እስከ ጥር ወር መጀመሪያ ድረስ ተማሪዎቻቸውን ፈቃድ ወዳላቸው ተቋማት እንዲያዘዋውሩ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ትዕዛዝ አስተላለፈ።

ባለሥልጣኑ ባወጣው “አዲስ ስታንዳርድ” መሰረት ዳግም ምዝገባ እንዲያደርጉ ባለፈው መስከረም ለግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጥሪ አቅርቦ ነበር። በዚህም በድጋሜ ምዝገባ ሳያደርጉ የቀሩ እና በገዛ ፈቃዳቸው ሥራቸውን ለማቋረጥ የወሰኑ ኮሌጆች እስከ ጥር ወር ድረስ ተማሪዎቻቸውን ፈቃድ ወዳላቸው ተቋማት እንዲያዘዋውሩ ባለሥልጣኑ አዟል፡፡

84 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት “ከከፍተኛ ትምህርት የፈቃድ ስርዓት እንዲወጡ” የሚያደርጋቸውን ውሳኔ ባለስልጣኑ ከሁለት ሳምንት በፊት አስተላልፏል። ዘጠኝ በሚሆኑ የትምህርት ተቋማት ላይም ተመሳሳይ ውሳኔ በቅርቡ እንደሚተላለፍ ከባለስልጣኑ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።

በባለልጣን በመስሪያ ቤቱ የፈቃድ አሰጣጥ እና ጥራት ኦዲት ምክትል ዳይሬክተር አቶ ውብሸት ታደለ ፊርማ በታህሳስ ወር መጀመሪያ ለ84ቱ የትምህርት ተቋማት የተላከ ደብዳቤ፤ ውሳኔው የተላለፈው በተሰጣቸው የጊዜ ሰሌዳ ቀርበው ባለመመዝገባቸው እንደሆነ ይጠቅሳል። የዳግም ምዝገባው ካስፈለገባቸው ምክንያቶች አንዱ “ያልጠራ መረጃ” ያላቸው እና “ባለቤትነታቸው የማይታወቁ ተቋማት” በመኖራቸው” ምክንያት እንደሆነ አቶ ውብሸት ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።

የትምህርት ተቋማቱ በዳግም ምዝገባ እንዲያሟሉ ከተጠየቋቸው ጉዳዮች መካከል፤ የ500 ሺህ ብር ተመጣጣኝ ዋስትና፣ የታደሰ የንግድ ፈቃድ እና በአምሮዓዊ ንብረት የተመዘገበ የንግድ ሎጎ ይገኙባቸዋል። የጤና ትምህርት ለሚሰጡ የትምህርት ተቋማት ከእነዚህ ጉዳዮች ተጨማሪ መስፈርት ተቀምጦላቸዋል።

ባለስልጣኑ የሰጠው ቀነ ገደብ ከሁለት ሳምንት በኋላ ሲጠናቀቅ፤ ትዕዛዙን ተግባራዊ ባላደረጉ የትምህርት ተቋማት ላይ በፍትህ ሚኒስቴር በኩል ክስ እንደሚመሰርት አቶ ውብሸት ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። መስሪያ ቤቱ ደብዳቤ ከላከላቸው 84 የትምህርት ተቋማት መካከል እስካሁን ድረስ ሂደቱን አጠናቅቀው ከፈቃድ ስርዓቱ መውጣታቸው የተረጋገጠው አምስት ብቻ ናቸው። #ኢትዮጵያኢንሳይደር

@tikvahuniversity

Tikvah-University

28 Dec, 09:26


#አቢሲንያ_ባንክ

ይታፈሳል!
ቀጣይ ዙር የጥያቄ እና መልስ ውድድር ቅዳሜ ጥር 3 ከረፋዱ 4:30 በቴሌግራም ቻናላችን ላይ ይደረጋል። በየሳምንቱ አስር አሸናፊዎች ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀልና ቀላል ጥያቄዎችን በመመለስ ይሸለሙ!

የቴሌግራም ሊንክ 👇
https://t.me/BoAEth

አቢሲንያ የሁሉም ምርጫ!
#Telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ

Tikvah-University

28 Dec, 09:26


#RayaUniversity

በ2017 ዓ.ም ራያ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ የአቅም ማሻሻያ ትምህርት (Remedial Program) ተማሪዎች የምዝገባ ቀናት ጥር 15 እና 16 /2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትሔዱ ከ8ኛ-12ኛ ክፍል ሰርቲፊኬት እና ትራንስክሪፕት ከማይመለስ ኮፒ ጋር እንዲሁም ብርድ ልብስ፣ አንሶላ እና ትራስ ልብስ መያዝ ይኖርናችኋል ተብሏል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

26 Dec, 10:39


20ኛ ዙር ሙሉ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ (Principle and Practice of Accounting) የስድስት ወር የቅዳሜ እና እሑድ መርሐግብር ስልጠና በፒያሣ እና በመገናኛ ካምፓስ ምዝገባ ላይ ነን።

👉 100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና
👉 መሠረታዊ የአካውንቲንግ እና የኦዲት አሰራር፣ ሙሉ የአካውንቲንግ ሒሳብ አሰራር በፒስቺሪ ተደግፎ እና የግብር አያያዝ ትምህርቶችን አካቶ የሚሰጥ
👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት

☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦
ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ

Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute

Tikvah-University

26 Dec, 10:39


#MattuUniversity

በ2017 ዓ.ም ለአቅም ማሻሻያ ትምህርት (Remedial Program) መቱ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ጥር 1 እና 2/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

➫ ከ8-12ኛ ክፍል ሰርተፈኬት ዋናውና ኮፒው፣
➫ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
➫ አራት 3x4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣
➫ ብርድ ልብስ፣ አንሶላ፣ ትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ልብስ

Note:
የስማችሁ የመጀመሪያ ፊደል ከA-B የሚጀምር የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማኅበራዊ ሳይንስ መስክ ተማሪዎች ምዝገባችሁ በበደሌ ካምፖስ እንደሚከናወን ተገልጿል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

25 Dec, 16:04


#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር በቁልፍ የአፈጻጸም አመላካቾች (KPIs) ከሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ስምምነት ተፈራረመ።

ስምምነቱ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማቱ ብቃትና ችሎታ ያላቸው ምሩቃንን በማፍራት ሂደት ውስጥ ተጠያቂነትን ከማስፈን ባለፈ ውጤታማነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡

ስምምነቱ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ግልጽነትና ተጠያቂነትን ያሰፈነ አመራር እንዲከተሉ፣ አገሪቱ ለምታወጣው ሀብት ተመጣጣኝ ውጤት እንዲያስገኙ፣ የአፈጻጸም አቅማቸው እንዲገመገምና ለስኬቱም ዕውቅና እና ሽልማት እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል፡፡

በስምምነቱ ወቅት ንግግር ያደረጉት የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) "ዩኒቨርሲቲዎች የሚመደብላቸው በጀት ባስመዘገቡት ውጤት ልክ እንደሚሆን" ገለፀዋል።

የስምምነት ውሉ በየዩኒቨርሲቲዎቹ ስር ወደሚገኙ ኮሌጆች፣ ትምህርት ክፍሎች እና ሌሎች ፅህፈት ቤቶች በየደረጃው እንደሚወርድ ይጠበቃል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

25 Dec, 11:32


የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በራሳቸው ላይ ግለ ግምገማ እንዲያካሒዱ የሚደነግግ ረቂቅ መመሪያ ተዘጋጀ፡፡

ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን የጥራት ኦዲት ስታንዳርድ መሠረት፣ በየጊዜው በተቋም ወይም በፕሮግራም ደረጃ ግለ ግምገማ ማካሔድ እንዳለባቸው የሚደነግግ ረቂቅ መመሪያ ለግምገማ ቀርቧል፡፡

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ግለ ግምገማውን የሚያደርጉት ባለሥልጣኑ በሚያዘጋጀው የግለ ግምገማ መመሪያ መሠረት እንደሚሆን የተገለጸ ሲሆን፤ የማንኛውም ተቋም የግል ግምገማ ሪፖርት ተቀባይነት ባገኘ በአራት ወራት ጊዜ ውስጥ የጥራት ኦዲት ግምገማ መደረግ ይኖርበታል ተብሏል፡፡

በረቂቅ መመርያው እንደተገለጸው ተቋማዊም ሆነ የፕሮግራም ጥራት ኦዲት በተቋም ደረጃ የሚደረግ ሆኖ፣ ተቋሙ ከአንድ በላይ ካምፓሶች የሚኖሩት ከሆነ በተመረጡ ካምፓሶች የጥራት ኦዲት መደረግ አለበት፡፡

ረቂቅ መመሪያው በኢትዮጵያ ውስጥ በሚንቀሳቀስ በማንኛውም የመንግሥት እና የግል እንዲሁም ከውጭ ለሚመጣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋምና የትምህርት ፕሮግራም ላይ፣ በተጨማሪም በፌዴራል ደረጃ ለተቋቋመና ከውጭ አገር ለሚመጣ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋም ላይ ተፈጻሚ ይሆናል ተብሏል፡፡

የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን ሁሉም የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ በፌዴራል መንግሥት በጀት የሚተዳደሩና በውጭ አገር ባለሀብቶች በፌዴራል ደረጃ ፈቃድ የወሰዱ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት ረቂቅ መመርያውን አስመልክቶ ያላቸውን አስተያየት እንዲያቀርቡ ጠይቋል፡፡ #ሪፖርተር

@tikvahuniversity

Tikvah-University

25 Dec, 11:32


#MekelleUniversity

በቅርቡ በትምህርት ሚኒስቴር ፀድቆ የተላከው የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ወጥ-የሆነ የምግብ ሜኑ በመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተግባራዊ መደረግ መጀመሩን ተከትሎ የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ተቃውሞ አሰምተዋል፡፡

መቐለ ዩኒቨርሲቲ ከቅዳሜ ታህሳስ 12/2017 ዓ.ም ጀምሮ አንድ ዳቦ ለቁርስ እያቀረበ እንደሚገኝ የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ተናግረዋል። ከዚህ በፊት ዩኒቨርሲቲው መጠናቸው አነስተኛ የሆነ ሁለት ዳቦ ለቁርስ ያቀርብ እንደነበር ተማሪዎች አስታውሰዋል፡፡

"ዕለታዊ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የምግብ ተመን ወጪ አንድ መቶ ብር በሆነ ማግስት፥ አንድ ዳቦ ለቁርስ ማቅረብ ማሻሻል አይደለም" ሲሉ ተማሪዎቹ ቅሬታቸውን አቅርበዋል፡፡

ከታህሳስ 1/2017 ዓ.ም ጀምሮ የአንድ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ዕለታዊ የምግብ ወጪ ተመን ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) እንዲሆን መንግሥት መወሰኑ ይታወቃል። በዚህም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የምግብ ሜኑ በሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ወጥነት እንዲኖረው ለማድረግ ተመሳሳይ የምግብ ሜኑ በትምህርት ሚኒስቴር ተዘጋጅቶ ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ተልኳል፡፡

መቐለ ዩኒቨርሲቲ ከተቋሙ የተማሪዎች ህብረት ጋር በመነጋገር የመቐለ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች የምግብ ሜኑን አዘጋጅቶ ወደ ትግበራ መግባቱን ገልጿል። (አዱሱ የዩኒቨርሲቲው ሜኑ ከላይ ተያይዟል)

በማሻሻያውና በቀረበው የዳቦ መጠን ላይ ደስተኛ ያልሆኑ የዋናው ግቢ እና የዓዲ ሓቂ ግቢ ተማሪዎች ድርጊቱን በመቃወማቸው ለድብደባ እና ለእስር መዳረጋቸውን ገልፀዋል።

የክልሉ ፓሊስ ኮሚሽን ወደ ካምፓሶቹ የፀጥታ አካላት መላኩ ተነግሯል። በፓሊስ እና በተማሪዎቹ መካከል በተፈጠረ ግጭት ተማሪዎች የድብደባ ጥቃት እንደደረሰባቸው ተነግሯል። በዋናው ግቢ የተማሪዎች መመገቢያ አዳራሽ ላይ ጉዳት የደረሰ ሲሆን፤ ይህንንም ተከትሎ የታሰሩ ተማሪዎች መኖራቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ በሁለቱ ካምፓሶች የተፈጠረው ግርግር በአሁኑ ሰዓት ሙሉ በሙሉ መቆሙ ታውቋል።

ዩኒቨርሲቲው ባወጣው መግለጫ "በምግብ ሜኑው ላይ የሚስተካከሉ ነገሮች ካሉ ብሔራዊ ሜኑ በይዘት እና በጀት ደረጃ እስካልተለየ ድረስ ጥያቄዎች በተማሪዎች ህብረት በኩል ቀርበው ማስተካከል እንደሚቻል" ገልጿል፡፡ ተማሪዎች ቅሬታቸውን በሰላማዊ መንገድ መግለፅ እንዳለባቸውም ጠቁሟል፡፡

ከሚመለከተው የማኔጅመንት አካላት ጋር ውይይት መጀመሩን የገለፀው የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሀብረት፤ "ያለአግባብ የታሰሩ ተማሪዎች እንዲፈቱና ያለ በቂ መረጃ በተማሪዎች ላይ እርምጃ እንዳይወሰድ" ጠይቋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው ያዘጋጀው አዲሱ የምግብ ሜኑ ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ እስከሚሆን ድረስ ነባሩ ሜኑ እንዲቀጥልም ህብረቱ ጥሪ አድርጓል፡፡

መቐለ ዩኒቨርሲቲ በተፈጠረው ጉዳይ ላይ ይፋዊ መግለጫ እንደሚሰጥ ይጠበቃል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

24 Dec, 17:28


ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የ2017 ዓ.ም የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም አዲስ ገቢ ተማሪዎችን በመቀበል ላይ ይገኛል፡፡

ወደ ተቋሙ የተመደቡ የ2017 ዓ.ም ሪሚዲያል ተማሪዎች ታህሳስ 14 እና 15/2017 ዓ.ም ሪፖርት እንዲያደርጉ ዩኒቨርሲቲው ጥሪ ማድረጉ ይታወሳል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

24 Dec, 17:28


አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለአምስት የተቋሙ ምሁራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጠ።

የዩኒቨርሲቲው የሥራ አመራር ቦርድ ህዳር 25 ቀን 2017 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ለአምስት የተቋሙ ምሁራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ መስጠቱን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

በዚህም፦

➤ ዶ/ር አለማየሁ ተ/ማርያም በስፔሻል ኒድስ ኢጁኬሽን
➤ ዶ/ር አስራት ወርቁ በጂኦቴክኒካል ኢንጂነሪንግ
➤ ዶ/ር መኮንን እሸቴ በፕላስቲክ ሰርጀሪ
➤ ዶ/ር ሚርጊሳ ካባ በፐብሊክ ሄልዝ
➤ ዶ/ር ተባረክ ልካ በዴቨሎፕሜንት ጂኦግራፊ መስኮች ከላይ ከተጠቀሰው ቀን ጀምሮ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የተሰጣቸው መሆኑ ተገልጿል።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ''ስለ ራስገዝ ዩኒቨርሰቲ ለመደንገግ በወጣ'' አዋጅ ቁጥር 1294/2015 በተሰጠው ስልጣን መሠረት ነው በዩኒቨርሲቲው ሴኔት የቀረቡለትን የማዕረግ ዕድገት ማፅደቁ ተመላክቷል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

24 Dec, 13:48


#AdigratUniversity

በ2017 የትምህርት ዘመን ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች የመግቢያ ቀናት ጥር 1 እና 2/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትሔዱ የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የወሰዳቹበት ማስራጃዎች፣ ፎቶግራፍ፣ የመኝታ አልባሳት እና የስፖርት ትጥቅ መያዝ እንደሚገባችሁ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

05 Dec, 15:20


ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የ2017 ትምህርት ዘመን አዲስ ገቢ የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎችን ዛሬ መቀበል ጀምራል።

በ2017 ዓ.ም ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደቡ መደበኛ ተማሪዎች እንዲሁም በ2016 ዓ.ም በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን ተከታትለው የማለፊያ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች ህዳር 26 እና 27/2017 ዓ.ም ሪፖርት እንዲያደርጉ ዩኒቨርሲቲው ጥሪ ማድረጉ ይታወቃል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

05 Dec, 10:58


#ጥቆማ

5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደርስ ኢንሼቲቭ ነፃ ስልጠናን ለመከታተል ይመዝገቡ።

ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው ሰርትፍኬት ማግኘት የሚያስችልዎትን ስልጠና ይውሰዱ።

የስልጠና ዘርፎች፦

► ዌብ ፕሮግራሚንግ
► አንድሮይድ ማበልፀግ
► ዳታ ሳይንስ

ስልጠናውን በስምንት ሳምንት ያጠናቀቁ ሰልጣኞች ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው ሰርተፊኬት ይሰጣቸዋል።

ለመመዝገብ 👇
https://www.ethiocoders.et/

@tikvahuniversity

Tikvah-University

05 Dec, 10:58


ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከ2 ሺህ በላይ የ2017 ትምህርት ዘመን አዲስ ገቢ ተማሪዎችን ዛሬ መቀበል ጀምራል።

ዩኒቨርሲቲው በ2017 ዓ.ም ለተመደቡ የአንደኛ ዓመት አዲስ ገቢ ተማሪዎች እንዲሁም በ2016 ዓ.ም በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ትምህርታቸውን ተከታትለው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች ለህዳር 26 እና 27/2017 ዓ.ም ጥሪ ማድረጉ ይታወቃል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

04 Dec, 15:13


አክሱም ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርት ለመማር ለተመደቡ አዲስ ተማሪዎች አድርጎት የነበረውን ጥሪ አራዝሟል።

ዩኒቨርሲቲው የ2017 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም አዲስ ገቢ ተማሪዎች የመግቢያ ቀናት ታህሳስ 1 እና 2/2017 ዓ.ም ብሎ የነበረ ቢሆንም፤ የመግቢያ ቀናት ላልተወሰነ ጊዜ የተራዘመ መሆኑን አሳውቋል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

04 Dec, 15:13


#ጥቆማ

በህንድ አገር የሚሰጥ የአጭር ጊዜ ስልጠና ለመከታተል እድሎችን ይመልከቱ፡፡

የህንድ መንግስት በቴክኒካል እና ኢኮኖሚ ትብብር ፕሮግራም (ITEC) ሙሉ ወጪያቸው የሚሸፈን የተለያዩ ስልጠናዎች ለተለያዩ አገራት ይሰጣል፡፡

ዝርዝር መረጃ ለመጠየቅ 👇
[email protected]

ስለ ፕሮግራሙ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት፦
https://www.itecgoi.in/index

ምስል 1 ፦ በ ITEC ፕሮግራም ሙሉ ወጪያቸው ተሸፍኖ የአጭር ጊዜ ስልጠና ለመውሰድ ወደ ህንድ በቅርቡ የሚሔዱ ኢትዮጵያውያን

@tikvahuniversity

Tikvah-University

04 Dec, 15:13


በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በመደበኛ የማስተርስ ፕሮግራም በ General Public Health እና በ Reproductive Health የትምህርት መስኮች ለመማር ከጤና ቢሮ የተላካችሁና የመግቢያ ፈተና ተፈትናችሁ ያለፋችሁ ትምህርት የሚጀመረው ህዳር 30/2017 ዓ.ም መሆኑን ኮሌጁ አሳውቋል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

04 Dec, 15:13


#MizanTepiUniversity

በ2017 ዓ.ም ለሪሚዲያል ፕሮግራም ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁና ከዚህ በፊት በተላለፈው የጥሪ ጊዜ በተለያዩ ምክንያቶች መመዝገብ ያልቻላችሁ ተማሪዎች ህዳር 30 እና ታህሳስ 1/2017 ዓ.ም በአካል በመገኘት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡

የምዝገባ ቦታ፦
- የማኅበራዊ ሳይንስ መስክ ተማሪዎች ሚዛን አማን ከተማ በሚገኘው ዋናው ግቢ፣
- የተፈጥሮ ሳይንስ መስክ ተማሪዎች ቴፒ ከተማ በሚገኘው ቴፒ ግቢ፡፡

ለምዝገባ ስትሐየዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
- የ12ኛ ብሑራዊ ፈተና ውጤት፣
- ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
- ዘጠኝ የቅርብ ጊዜ 3x4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣
- ብርድ ልብስ፣ አንሶላ፣ ትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ትጥቅ፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

04 Dec, 15:13


Top Training Institute ከአሁን ቀደም ከሚሰጣቸው የኮምፒውተር እና የቋንቋ ስልጠናዎች በተጨማሪ በ Photography, Videography & Cinematography ስልጠናዎችን ዘመናዊ ካሜራዎችን በማሟላት በሙያው የረጅም ጊዜ ልምድ ባላቸው አሰልጣኞች መስጠት የጀመረ መሆኑን በአክብሮት ይገልጻል።

አድራሻ፦
● መገናኛ መተባበር ህንፃ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁ. 419 (ሊፍት ይጠቀሙ) ☎️ 0991929303
● ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ 6ኛ ፎቅ ቢሮ ቁ. 639 (2ኛውን ሊፍት ይጠቀሙ) ☎️ 0991929304
● ጀሞ 1 አንደኛ በር ካኩ ቢዝነስ ሴንተር 3ኛ ፎቅ ☎️ 0991926707

@Top_trainings

Join our Telegram Channel:
https://t.me/topinstitutes

Tikvah-University

04 Dec, 15:13


ሦስት የደቡብ ክልል ዩኒቨርሲቲዎች ከክልል የጤና ሳይንስ ኮሌጆች የትምህርት ዕድል ተሰጥቷቸው በሚማሩ መምህራን ላይ ሕገወጥ ተግባር እየተፈተመባቸው መሆኑ ተሰማ።

ዩኒቨርሲቲዎቹ መምህራኑን ከትምህርት ገበታቸው ማገድ፣ በገንዘብ መደራደር እና መምህራኑ ትምህርታቸውን የጨረሱበትን ማስረጃ ባለመስጠት ሕገወጥ ድርጊት ላይ መሰማራታቸው ለሕ/ተ/ም/ቤት በቀረበ ጥቆማ ተገልጿል፡፡

ይህ የተገለጸው ባለፈው ሳምንት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሰባተኛ መደበኛ ስብሰባ፣ የጤና ሚኒስቴር የሥራ ኃላፊዎች ከምክር ቤት አባላት ለቀረባለቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሲሰጡ መሆኑን ሪፖርተር ዘግቧል፡፡

አዳነ አደቶ (ዶ/ር) የተባሉ የምክር ቤት አባል ለጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ ባቀረቡበት ጥያቄ በሐዋሳ፣ በወላይታ ሶዶ እና በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ከክልል ጤና ሳይንስ ኮሌጆች የትምህርት ዕድል አግኝተው የሚማሩ መምህራን ላይ ሕገወጥ ተግባር እየተፈተመባቸው ነው ብለዋል፡፡

ሦስቱ ዩኒቨርሲቲዎች ከክልል ጤና ሳይንስ ኮሌጆች የትምህርት ዕድል ተሰጥቷቸው የሚማሩ መምህራንን ከትምህርት ገበታቸው እንዲታገዱ ማድረግ፣ በገንዘብ መደራደር እና ሌሎች ሕገወጥ ተግባሮች ላይ መሰማራታቸውን አስረድተዋል፡፡

ድርጊቱ የመልካም አስተዳደር ችግር ከመሆኑም በላይ የመንግሥትን ሥራ አደናቃፊ መሆኑን በማመን የሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመሆን ጉዳዩን እንዲያጣራ የም/ቤቱ አባል ጠይቀዋል፡፡

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ኃላፊ ዓለሙ ታምሶ እስካሁን በዩኒቨርሲቲው ይህንን ዓይነት ድርጊት ስለመኖሩ መረጃ የለኝም ብለዋል፡፡ ነገር ግን እንዲህ ዓይነት ድርጊት የሚፈፅሙ አካላት ካሉና ለፓርላማው የቀረበው ጥቆማ ተጨባጭ ከሆነ፤ ዩኒቨርሲቲው ድርጊቱን በፈፀሙ ግለሰቦች ላይ በፍጥነት ዕርምጃ እንደሚወስድ ለሪፖርተር አስረድተዋል፡፡

"በተለይ ይህንን ዓይነት ድርጊት የሚፈጽሙ ሰዎች ሕገወጥ መሆናቸው ታምኖበት ተጠያቂ እንዲሆኑ ይደረጋል" ያሉት ኃላፊው፤ አንድ መምህር ትምህርቱን በአግባቡ ከጨረሰ በኋላ የትምህርት ማስረጃ የማያገኝበት ምክንያት የለም ብለዋል፡፡

ሪፖርተር ከፓርላማ አባል የቀረበውን ጥያቄ መሠረት አድርጎ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ እና የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ኃላፊዎችን በስልክ ለማግኘት ጥረት ቢያደርግም ሳይሳካ መቅረቱን ጠቁሟል፡፡ #ሪፖርተር

@tikvahuniversity

Tikvah-University

03 Dec, 16:19


ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሜዲካል ኮሌጅ በኅብረተሰብ ጤና የማስተርስ ፕሮግራም (MPH) የ2017 ዓ.ም የእረፍት ቀናት መልካቾች ምዝገባ የሚካሔደው ህዳር 27 እና 28/2017 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።

ገለፃ ህዳር 28/2017 ዓ.ም የሚሰጥ ሲሆን ትምህርት ህዳር 29/2017 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

03 Dec, 16:19


ለማይቋረጥ የኢንተርኔት ጌም ወሳኙ የማይቋረጥ ኢንተርኔት ነው። አሁኑኑ የሳፋሪኮምን የ4G ዋይፋይ ጥቅል ከM-PESA ሳፋሪኮም mini app በመግዛት በጌማችን እንፍታታ!

#MPESASafaricom
#SafaricomEthiopia
#FurtherAheadTogether

Tikvah-University

03 Dec, 16:19


ነጻ የትምህርት ዕድል

ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ የማጠቃለያ ፈተና ወስደው ከፍተኛ ውጤት (500 እና ከዛ በላይ ከ600) ያስመዘገቡ ተማሪዎችን ሙሉ ነጻ የትምህርት ዕድል በመስጠት በ2017 ዓ.ም በመደበኛ መርሐግብር ማስተማር ይፈልጋል፡፡

የማመልከቻ ጊዜ የሚያበቃው፡-
ታህሳስ 3/2017 ዓ.ም

ለማመልከት የሚያስፈልጉ፦
➭ የ12ኛ ክፍል ካርድ ውጤት ዋናውና ኮፒ፣
➭ የማመልከቻ ክፍያ 300.00 (ሦስት መቶ) ብር

የማመልከቻ ቦታ፦
በየአካዳሚክ ክፍል ባሉ ሬጅስትራር ጽ/ቤቶች

የትምህርት ፕሮግራም ምደባ ከሌሎች የመደበኛ ተማሪዎች ጋር በውድድር እንደሚመደቡ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

03 Dec, 16:19


#ArsiUniversity

በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት በማምጣት አርሲ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ የመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ መረሐግብር ተማሪዎች የመግቢያ ቀናት ታህሳስ 1 እና 2/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
- የ8ኛ ክፍል ውጤት ዋናውና ኮፒው፣
- ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
- የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሰርተፊኬት ዋናውና ኮፒው፣
- ስድስት 3×4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣
- አንሶላ፣ ትራስ ጨርቅ፣ ብርድ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ።

የምዝገባ ቦታ፦
- የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በቦቆጂ ካምፓስ
- የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በግብርና ኮሌጅ ካምፓስ

Note:
ለሪሚዲያል ፕሮግራም አርሲ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ ተማሪዎች ወደፊት ጥሪ ይደረጋል ተብሏል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

03 Dec, 16:19


መቱ ዩኒቨርሲቲ ለ2017 ዓ.ም ሪሚዲያል ተማሪዎች ጥሪ አላደረገም።

"ዩኒቨርሲቲው ለ2017 ዓ.ም ሪሚዲያል ተማሪዎች ለታህሳስ 7 እና 8/2017 ዓ.ም እንደጠራ" ተደርጎ በማኅበራዊ ሚዲያ የተሰራጨው መረጃ ሐሰት መሆኑን ተቋሙ ገልጿል።

በይፋ ጥሪ እስከሚደረግ ድረስ ተማሪዎች በትዕግስት እንዲጠብቁ ዩኒቨርሲቲው ጠይቋል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

03 Dec, 16:19


ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በ2017 አዲስ ለተመደቡ የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ተማሪዎች ጥሪ አላደረገም።

"በ2017 ዓ.ም ከትምህርት ሚኒስቴር ወደ ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደቡ የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ህዳር 30 እና ታህሳስ 1/2017 ዓ.ም እንደሆነ" የሚገልፅ በማኅበራዊ ትስስር ገጾች የሚዘዋወረው መረጃ #ሐሰተኛ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

በ2017 ዓ.ም አዲስ የተመደቡ የሪሚዲያል ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜን ወደፊት የሚያሳውቅ መሆኑን የገለፀው ዩኒቨርሲቲው፤ ጥሪ እስከሚደረግ ተማሪዎች በትዕግስት እንዲጠብቁ ጠይቋል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

02 Dec, 15:20


ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከብሪትሽ ካውንስል ጋር በመተባበር 5ኛ ዙር የእንግሊዘኛ ቋንቋ ምዘና ፈተና (IELTS Test) ሰጥቷል።

29 ተፈታኞች በወረቀት የተሰጠውን ምዘና ወስደዋል።

6ኛ ዙር የ IELTS ምዘና ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በመጪው የካቲት እንደሚሰጥ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

02 Dec, 09:54


በ2017 የትምህርት ዘመን አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ቅበላ ረቡዕ ታህሳስ 2/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ምዝገባ ታህሳስ 3 እና 4/2017 ዓ.ም የሚከናወን ሲሆን፤ ትምህርት ታህሳስ 7/2017 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል፡፡

የምዝገባ ቦታ፦

- የተፈጥሮ ሳይንስ የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች አርባ ምንጭ ከተማ በሚገኘው አባያ ካምፓስ፣
- የስማችሁ የመጀመሪያ ፊደል ከ A እስከ R የሆናችሁ የማህበራዊ ሳይንስ የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች አርባ ምንጭ ከተማ በሚገኘው ጫሞ ካምፓስ፣
- የስማችሁ የመጀመሪያ ፊደል ከ S እስከ Z የሆናችሁ የማህበራዊ ሳይንስ የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ሳውላ ከተማ በሚገኘው ሳውላ ካምፓስ

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
- ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት፣
- የ12ኛ ክፍል ሰርተፍኬት ዋናውና ሁለት ኮፒ፣
- አንሶላ፣ የትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ትጥቅ፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

02 Dec, 09:54


በ2017 ዓ.ም በአክሱም ዩኒቨርሲቲ በሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርት ለመማር የተመደባችሁ አዲስ ተማሪዎች የመግቢያ ቀናት ታህሳስ 1 እና 2/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
- የ8ኛ፣ የ10ኛ እና የ12ኛ ክፍል ሰርተፊኬት ዋናውና ኮፒው፣
- ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
- የቅርብ ጊዜ አራት ጉርድ ፎቶግራፍ፣
- አንሶላ፣ የትራስ ጨርቅ፣ ብርድ ልብስ፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

01 Dec, 16:35


ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ 36 የ9ኛ ክፍል ተማሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ 'አክሰስ የእንግሊዘኛ ቋንቋ ስኮላርሺፕ ፕሮግራም' ማስጀመሪያ ስነ-ስርዓት አካሒዷል።

ፕሮግራሙ ለሁለት ዓመት የሚቆይ ነፃ የትምህርት ዕድል ሲሆን፤ ከስድስት የመንግስት ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ 18 ሴት እና 18 ወንድ በድምሩ 36 የ9ኛ ክፍል ተማሪዎችን ተጠቃሚ ያደርጋል።

ፕሮግራሙ (English Access Scholarship Program) የተማሪዎችን የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎት በማሻሻል የወደፊት የሥራ ዕድላቸውን ማሳደግ የሚያስችል ነው ተብሏል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

30 Nov, 10:00


በኤሌክትሪክ መኪኖች ላይ በልዩነት የሚሠራ ራሱን የቻለ የቴክኒክ እና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋም በሀገር ውስጥ ለመክፈት እንቅስቃሴ መጀመሩ ተሰምቷል፡፡

መንግሥት የኤሌክትሪክ መኪኖች በስፋት ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ እያደረገ ሲሆን፤ በቀጣዮቹ 10 ዓመታት በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚነዱ ተሸከርካሪዎች 95 በመቶ የሚሆኑት የኤሌክትሪክ መኪኖች እደንዲሆኑ ዕቅድ ተይዟል፡፡

እነዚህ መኪኖች የሚያጋጥሟቸውን ብልሽቶች የሚጠግኑ ባለሙያዎች ለማፍራት የትምህርት ዕድል እየተመቻቸ መሆኑን የፌደራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡

በዚህም በመጀመሪያ ዙር ወደ ቻይና ተጉዘው ስልጠናዎችን ወስደው የተመለሱ ወጣቶች ወደ ሥራ መግባታቸውን ገልፀዋል፡፡

መሰረታቸውን በቻይና ያደረጉ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በኢትዮጵያ ውስጥ ስልጠና መስጠት ጀምረዋል ብለዋል፡፡ #ShegerFM

@tikvahuniversity

Tikvah-University

29 Nov, 17:11


ጅማ ዩኒቨርሲቲ የ2017 ትምህርት ዘመን የቅድመ-ምረቃ መደበኛ አዲስ ገቢ ተማሪዎችን ከትናንት ህዳር 19/2017 ዓ.ም ጀምሮ በመቀበል ላይ ይገኛል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

29 Nov, 17:11


ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም አዲስ ለተመደቡ የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች አቀባበል እያደረገ ይገኛል።

ዩኒቨርሲቲው በዋናው ግቢ እና በዱራሜ ካምፓስ ነው ለአዲስ ገቢ ተማሪዎቹ አቀባበል እያደረገ የሚገኘው፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

29 Nov, 13:30


#አቢሲንያ_ባንክ

ቀጣይ ዙር የጥያቄ እና መልስ ውድድር ነገ ቅዳሜ ህዳር 21 ከረፋዱ 4:30 በፌስቡክ ፔጃችን ላይ ይደረጋል። በየሳምንቱ አስር አሸናፊዎች ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የፌስቡክ ፔጃችን በመቀላቀልና ቀላል ጥያቄዎችን በመመለስ ይሸለሙ!

የፌስቡክ ሊንክ 👇
https://www.facebook.com/BoAeth

አቢሲንያ የሁሉም ምርጫ!
#Facebook #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ

Tikvah-University

29 Nov, 13:30


ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሜዲካል ኮሌጅ በኅብረተሰብ ጤና የማስተርስ ፕሮግራም (MPH) ለ2017 ዓ.ም በመደበኛ እና በእረፍት ቀናት ተቀባይነት ያገኙ አመልካቾችን ዝርዝር ይፋ አድርጓል።

የትምህርት ፕሮግራሞች፦
- Epidemiology
- General Public Health
- HCP
- Nutrition

ተቀባይነት ያገኙ አመልካቾች ዝርዝርን ለመመልከት፦ https://sphmmc.edu.et/mph/List_of_applicants_selected_for_regular_extension_masters_program.pdf

@tikvahuniversity

Tikvah-University

29 Nov, 13:30


#Update

በዚህ ዓመት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የድኅረ-ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (GAT) ወስዳችሁ ከ 40% በላይ ውጤት ያመጣችሁ የሁለተኛ ዲግሪ አመልካቾች እንዲሁም ከ 50% በላይ ውጤት ያመጣችሁ የሦስተኛ ዲግሪ አመልካቾች በቀጣይ ወር የሚሰጠውን 3ኛ ዙር የድኅረ-ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና መውሰድ አይጠበቅባችሁም፡፡

በቀጥታ መማር የምትፈልጉት የትምህርት ክፍል በመሔድ ማመልከት እንደምትችሉ ተገልጿል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

29 Nov, 13:30


#UniversityOfKabriDahar

በ2017 ዓ.ም ቀብሪደሀር ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ ገቢ የሪሚዳል ፕሮግራም ተማሪዎች ሪፖርት ማድረጊያ ቀናት ህዳር 26 እና 27/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዝቸው የሚገቡ፦

➫ የ8ኛ ክፍል ውጤት ካርድ ዋናውና ኮፒው፣
➫ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
➫ የ12ኛ ክፍል ውጤት ሰርተፍኬት ዋናውና ኮፒው፣
➫ የቅርብ ጊዜ ስድስት 3x4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣
➫ የለሊት አልባሳት

@tikvahuniversity

Tikvah-University

29 Nov, 13:30


AAU Graduate Admission Test

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 3ኛ ዙር የድኅረ-ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (GAT) ታህሳስ 17 እና 18/2017 ዓ.ም ይሰጣል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ለ2017 ዓ.ም ሁለተኛ ሴሚስተር የድኅረ-ምረቃ ትምህርት (በቀን መርሐግብር ለሁለተኛ እና ለሦስተኛ ዲግሪ እንዲሁም በማታ መርሐግብር ለሁለተኛ ዲግሪ) አመልካቾች ለመቀበል ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡

ስለዚህም በዩኒቨርሲቲዉ ድረ-ገጽ http://www.aau.edu.et/ ላይ የተመለከቱትን መስፈርቶች በማሟላት ማመልከት እንደምትችሉ ያሳስባል፡፡

የድኅረ-ምረቃ መግቢያ ፈተና ለመውሰድ የማመልከቻ ቀናት፦
ከህዳር 23 እስከ ታህሳስ 11/2017 ዓ.ም

የድኅረ-ምረቃ መግቢያ ፈተና መፈተኛ ቀናት፦
ታህሳስ 17 እና 18/2017 ዓ.ም

አመልካቾች ውጤታችሁንና ምዝገባችሁን https://portal.aau.edu.et/Web/ApplyForAdmission/TestingStatus ላይ ማየት እና መመዝገብ ትችላላችሁ ተብሏል፡፡ በአካል በመገኘት የትምህርት ማስረጃ ማስገቢያ ቦታ አ.አ.ዩ. ሬጅስትራር ቢሮ ቁጥር 203 መሆኑ ተገልጿል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

28 Nov, 13:17


መቐለ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም ወደ ተቋሙ የተመደቡ የአንደኛ ዓመት (Freshman) ተማሪዎችን በዋናው ግቢ እና በዓዲ-ሓቂ ግቢ መቀበል ጀምሯል፡፡

ተማሪዎቹ ወደ ዩኒቨርሲቲው ሪፖርት ከማድረጋቸው አስቀድመው በኦንላይን ምዝገባ አድርገዋል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

28 Nov, 09:38


የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት በደረጃ ስምንት ስልጠና መስጠት ሊጀምር ነው።

ኢንስቲትዩቱ በ2017 ዓ.ም አጋማሽ በሁለት ፕሮግራሞች በደረጃ ስምንት ስልጠና መስጠት እንደሚጀምር የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) ተናግረዋል።

በተያዘው ዓመት አጋማሽ እንደአገር ለመጀመሪያ ጊዜ በደረጃ ስምንት በማኑፋክቸሪንግ ቴክኖሎጂ እና በቴክኒክና ሙያ አመራር መስኮች ማሰልጠን እንደሚጀምር ገልፀዋል።

ኢንስቲትዩቱ አሁን ላይ በደረጃ ስድስት በ22 እንዲሁም በደረጃ ሰባት በ19 ፕሮግራሞች ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

27 Nov, 19:34


በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ወስደው ከፍተኛ ውጤት ላመጡ የክቡር ዶ/ር ሀዲስ ዓለማየሁ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የገንዘብ እና የሞባይል ስልክ ሽልማት ተበረከተላቸው፡፡

በደብረ ማርቆስ ከተማ በሚገኘው የክቡር ዶ/ር ሀዲስ ዓለማየሁ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስደው ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ 32 ተማሪዎች፣ የስማርት ስልክ እና ከ38 እስከ 40 ሺህ ብር የገንዘብ የማበረታቻ ሽልማት ተሰጥቷቸዋል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

21 Nov, 16:39


11ኛ ዙር የብሔራዊ በጎ ፈቃድ አገልግሎት ስልጠና የመክፈቻ መርሐግብር በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ተካሒዷል፡፡

ስልጠናው በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ እና ሰላም ሚኒስቴር ትብብር የተዘጋጀ ነው፡፡

ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተመለመሉ 1,500 ወጣቶች ለ22 ቀናት በሚቆየው 11ኛው ዙር ስልጠና ይሳተፋሉ ተብሏል፡፡

በጎ-ፈቃድ ሰልጣኞቹ ስነ-ምግባር፣ አመለካከት፣ ክህሎት እና አካል ብቃት ላይ ትኩረት ያደረጉ ተግባር-ተኮር ስልጠና እንደሚሰጣቸው ተገልጿል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

21 Nov, 16:39


መቱ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ተመርቃችሁ ኦርጂናል ዲግሪ እንዲሰራላችሁ የምትፈልጉ የተቋሙ የቀድሞ ምሩቃን ምዝገባ በማድረግ መውሰድ እንደምትችሉ ገልጿል፡፡

በዚህም ከዚህ ቀደም የተሰጣችሁን ቴምፖራሪ (Temporary) ኦርጂናሉን እና አንድ ኮፒ በመያዝ እስከ ህዳር 20/2017 ዓ.ም በዋናው ሬጅስትራር ቢሮ ቁ. 28 መመዝገብ ትችላላችሁ ተብሏል፡፡

በመንግሥት የተማራችሁ ምሩቃን የሙያ ግዴታችሁን መጨረሳችሁን የሚገልጽ ደብዳቤ ከገቢዎች ሚኒስቴር ማቅረብ ይጠበቅባችኋል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

21 Nov, 16:39


መቐለ ዩኒቨርሲቲ የዲጂታል ትምህርት መስጠት የሚያስችለውን ዘመናዊ መልቲ ሚዲያ ስቱዲዮ አስመርቋል።

የዲጂታል ትምህርት (E-Learning) ለመስጠት የሚያስችሉ ሰባት ተመሳሳይ መልቲ ሚዲያ ስቱዲዮዎች በሀገር አቀፍ ደረጃ መገንባታቸው ይታወቃል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

21 Nov, 16:39


አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በግንቦት 2017 ዓ.ም ለሚያካሒደው 5ኛው ዓለም አቀፍ የምርምር ሲምፖዚየም የምርምር ረቂቅ መቀበል ጀምሯል፡፡

ሲምፖዚየሙ የሚካሔደው 👇
ግንቦት 1 እና 2/2017 ዓ.ም

ረቂቅ የማስገቢያ ጊዜ የሚያበቃው 👇
ጥር 12/2017 ዓ.ም

የምርምር ወረቀት ለማስገባት ይህን ሊንክ ይጠቀሙ፦ https://cmt3.research.microsoft.com/ASTUIRS2025/

ለበለጠ መረጃ፦
ያዴታ ጪምዴሳ (ዶ/ር) - 0947372481
ፈድሉ ከድር (ዶ/ር) - 0911301849

@tikvahuniversity

Tikvah-University

21 Nov, 16:39


#InfinixEthiopia

የዛንዚባር የቢዝነስ ክላስ ደርሶ መልስ የአውሮፕላን ቲኬት፣ የኢንፊኒክስ ስማርት ቲቪ፣ የኢንፊኒክስ ላፕቶፕ እንዲሁም ሌሎች አጓጊ ሽልማቶችን የኢንፊኒክስ ሆት 40፣ ኖት 40፣ ዜሮ 40 ሞባይል ስልኮችን እና የኢንፊኒክስ ስማርት TVን ሲገበያዩ ኩፖን በመውሰድ አብሮት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር በመረጡት ስፍራ ፎቶ በመነሳት #InfinixEthiopia የሚለውን ሃሽታግ በመጠቀም እና ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ በመለጠፍ ብቻ ከላይ በተጠቀሱት ሽልማቶች ይንበሽበሹ፡፡

መመሪያ

1. የኢንፊኒክስ ኢትዮጵያን ፌስቡክ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማኅበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የኢንፊኒክስ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስትዎት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡
3. #InfinixEthiopia የሚለውን ሃሽታግ መጠቀሞን አይርሱ፡፡

Tag ሲያደርጉ ለ Facebook @InfinixMobileEthiopia ፣ ለ Instagram @infinixethiopia  ለ TikTok @Infinixet  እና ለ Telegram @Infinixeth ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።

Tikvah-University

21 Nov, 13:15


#ይመዝገቡ

የሁዋዌ አይሲቲ ውድድር 2024/25 ፕሮግራም ይፋ ሆኗል፡፡

በ9ኛው ዓለም አቀፍ የ2024/25 አይሲቲ ውድድር ለመሳተፍ የምትፈልጉ እስከ ታህሳስ 2017 ዓ.ም መጨረሻ ድረስ መመዝገብ ይኖርባችኋል፡፡

ኔትዎርኪንግ፣ ክላውድ ኮምፒውተር እና አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ውድድሩ ከሚደረግባቸው የአይሲቲ ዘርፎች መካከል ይጠቀሳሉ።  

በሁዋዌ የICT ውድድር (Huawei ICT Competition 2024-2025) ለመሳተፍ በቅድሚያ የሁዋዌ ICT አካዳሚ አባል ይሁኑ።

የአካዳሚው አባል ለመሆን 👇
https://e.huawei.com/en/talent/portal/#/

ለውድድሩ ምዝገባ ለማድረግ 👇
https://bit.ly/SAR2024-2025

@tikvahuniversity

Tikvah-University

21 Nov, 13:15


በ2017 ዓ.ም ወደ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ አዲስ ገቢ ተማሪዎች እና የ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው በመግባት ላይ ናቸው፡፡

ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም አዲስ ገቢ ለሆኑ የአንደኛ ዓመት የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም መደበኛ ተማሪዎች ለህዳር 12 እና 13/2017 ዓ.ም ጥሪ ማድረጉ ይታወሳል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

20 Nov, 15:53


ጂንካ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደቡ የ2017 ዓ.ም አንደኛ ዓመት የቅድመ ምረቃ መርሐግብር መደበኛ ተማሪዎችን በመቀበል ላይ ይገኛል።

ዩኒቨርሲቲው ለአንደኛ ዓመት ተማሪዎች ለህዳር 11 እና 12/2017 ዓ.ም ጥሪ ማድረጉ ይታወሳል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

20 Nov, 15:53


ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ የ2017 ዓ.ም አንደኛ ዓመት የቅድመ ምረቃ መርሐግብር መደበኛ ተማሪዎችን በመቀበል ላይ ይገኛል።

ዩኒቨርሲቲው ለአንደኛ ዓመት ተማሪዎች ለህዳር 11 እና 12/2017 ዓ.ም ጥሪ ማድረጉ ይታወሳል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

20 Nov, 14:14


#MekdelaAmbaUniversity

በ2017 ዓ.ም መቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች፣ በ2015 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታችሁን ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ነገር ግን በተለያየ ምክንያት በ2016 ዓ.ም Freshman ፕሮግራም መቀጠል ያልቻላችሁ እንዲሁም በ2016 ዓ.ም አንደኛ ሴሚስቴር ያልተማራችሁ (ዊዝድሮዋል ሞልታችሁ የወጣችሁ) ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ህዳር 19 እና 20/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

በሁለቱም ግቢ (ቱሉ አውሊያ እና መካነ ሰላም) የተመደባችሁ ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሄደው በዋናው ግቢ (ቱሉ አውሊያ ካምፓስ) መሆኑ ተገልጿል፡፡

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

➫ የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ካርድ ዋናውና ኮፒው፣
➫ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
➫ አራት 3×4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣
➫ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ ትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ትጥቅ፡፡

በ2017 ዓ.ም መቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ለተመደባችሁ ተማሪዎች ወደፊት ጥሪ ጥደረጋል ተብሏል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

20 Nov, 14:14


አህመድ አብተው (ዶ/ር) የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሹመዋል፡፡

አህመድ አብተው (ዶ/ር) ከህዳር 10/2017 ዓ.ም ጀምሮ የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር በመሆን መሾማቸውን በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቀን ህዳር 9/2017 ዓ.ም ተፈርሞ የወጣ የሹመት ደብዳቤ ያሳያል፡፡

አህመድ አብተው (ዶ/ር) ከዚህ ቀደም የኢንዱስትሪ ሚኒስትርነትን ጨምሮ በተለያዩ የመንግሥት ኃላፊነቶች አገልግለዋል፡፡

ከጥቅምት 2/2015 ዓ.ም ጀምሮ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩት አምባሳደር ሽፈራው ሽጉጤ ሰሞኑን የኢትዮጵያ ህብረት ስራ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው መሾማቸው ይታወቃል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

20 Nov, 08:57


#የሥራ_ቅጥር_ጥቆማ
#JigjigaUniversity

ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ በተከታዮቹ የሙያ መስኮች ብቃት ያላቸውን ባለሙያዎች አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።

ተፈላጊ የሙያ መስኮች፡-
➫ Special Needs and Inclusive Education (MA level)
➫ Structural Geology (MSc/PhD)
➫ Geochemistry (MSc/PhD)
➫ Paleontology (MSc/PhD)
➫ Mining Geology (MSc/PhD)
➫ Economic Geology (MSc/PhD)
➫ Petrology (MSc/PhD)

መስፈርቶች፡-
- የአካዳሚክ ውጤት ለወንድ ከ3.00 በላይ እና ለሴት ከ2.75 በላይ
- የምርምር እና መመረቂያ ውጤት ከፍተኛ የሆነ/ች
- እድሜ ለመጀመሪያ ዲግሪ ከ35 ዓመት በታች እና ለማስተርስ ዲግሪ ከ45 ዓመት በታች

የሥራ ቦታ፦ ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ

መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ከህዳር 6/2017 ጀምሮ ባሉት አምስት ተከታታይ የሥራ ቀናት ማመልከት ትችላላችሁ ተብሏል፡፡ ተጨማሪ መረጃ የጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ አዲስ አበባ ወኪል ቢሮ ወይም የዩኒቨርሲቲው የሰው ሀብት ዳይሬክቶሬት ፖ.ሳ.ቁ. 1020 ጅግጅጋ መጠየቅ ይቻላል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

20 Nov, 06:53


#JimmaUniversity

በ2017 ዓ.ም ጅማ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ ገቢ የቅድመ-ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች ምዝገባ ህዳር 19 እና 20/2017 ዓ.ም እንደሚከናወን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

የምዝገባ ቦታ፦
- የተፈጥሮ ሳይንስ ዘርፍ ተማሪዎች በቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት እና በግብርናና እንስሳት ህክምና ኮሌጅ
- የማኅበራዊ ሳይንስ ዘርፍ ተማሪዎች በዋናው ግቢ

በ2016 ዓ.ም በጅማ ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታችሁን የተከታተላችሁ ተማሪዎች በቅርቡ https://portal.ju.edu.et ላይ የመለያ ቁጥራችሁን በማስገባት አጠቃላይ ውጤታችሁን ማወቅ የምትችሉ ሲሆን፤ ያለፋችሁ ተማሪዎች ምዝገባ ከላይ በተጠቀሰው ቀናት በተመሳሳይ የሚፈጸም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

በ2017 ዓ.ም በጅማ ዩኒቨርሲቲ በሪሚዲያል ፕሮግራም የተመደባችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ግዜ በቀጣይ ይገለፃል ተብሏል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

19 Nov, 15:30


#WolkiteUniversity

በ2017 ዓ.ም ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ መደበኛ ተማሪዎች እንዲሁም በ2016 ዓ.ም በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታችሁን ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሔደው ህዳር 26 እና 27/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

- ከ8ኛ-12ኛ ክፍል የትምህርት ማስረጃዎች ዋናውና ኮፒው፣
- አራት 3x4 መጠን ጉርድ ፎቶግራፍ፣
- ብርድ ልብስ፣ አንሶላ፣ ትራስ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ፡፡

በ2016 ዓ.ም አንደኛ ሴሚስቴር በውጤታችሁ መሰረት ዳግም ቅበላ የተፈቀደላችሁ ተማሪዎች በተጠቀሱ ቀናት እንድታመለክቱ ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

11 Nov, 17:11


#BuleHoraUniversity

በ2017 የትምህርት ዘመን ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ መደበኛ የቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች ወደተቋም የመግቢያ ጊዜ ህዳር 9 እና 10/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
- ከ8ኛ-12ኛ ክፍል የትምህርት ማስረጃ ዋናውና ሁለት ኮፒ፣
- ስምንት 3×4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣
- አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ ትራስ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

11 Nov, 17:11


#DebarkUniversity

ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም አዲስ የተመደባችሁ መደበኛ አንደኛ ዓመት እና በ2016 ዓ.ም በመደበኛ የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታችሁን ተከታትላችሁ ያለፋችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ቀን ህዳር 18 እና 19/2017 ዓ.ም መሆኑን ከዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

በቅጣት ምዝገባ፦ ህዳር 20/2017 ዓ.ም

ትምህርት የሚጀመርበት ቀን፦ ህዳር 20/2017 ዓ.ም

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
- የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ሰርቲፊኬት፣
- ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
- አራት 3×4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣
- አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ ትራስ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

11 Nov, 12:47


#MoH

የ2024 ትምህርት ዘመን የብሔራዊ የህክምና ስፔሻሊቲ ስልጠና (ERMP) አመልካቾች ምዝገባ ከህዳር 3-17/2017 ዓ.ም እንደሚከናወን ጤና ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡

ለበለጠ መረጃ፦
https://www.moh.gov.et/en/ermp-announcements

@tikvahuniversity

Tikvah-University

11 Nov, 12:47


#WolloUniversity

በ2017 ዓ.ም በወሎ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ የመጀመሪያ ዓመት መደበኛ ተማሪዎች እና በ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ተምራችሁ ያለፋችሁ መደበኛ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ህዳር 13 እና 14/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
- የ12ኛ ክፍል ሰርተፊኬት፣
- ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት
- የ8ኛ ክፍል ሰርተፊኬት ዋናውና ኮፒው፣
- አራት ጉርድ ፎቶግራፍ፣
- ብርድ ልብስ፣ አንሶላ፣ ትራስ ልብስ፣ የስፖርት ትጥቅ።

የተመደባችሁበትን ግቢ ለማወቅ 👇
Telegeram Bot: @WU_Registrar_bot
Website: https://tinyurl.com/wu-Registrar-s

@tikvahuniversity

Tikvah-University

11 Nov, 12:47


#GondarUniversity

በጎንደር ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የተመደቡ አዲስ ገቢ የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም የመደበኛ እና በ2016 የትምህት ዘመን አቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ሲከታተሉ ቆይተው የማለፊያ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ቀናት ህዳር 12 እና 13 2017 ዓ.ም መሆኑን ገልጿል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

11 Nov, 12:47


የኢትዮጵያ የግል ከፍተኛ ትምህርት እና ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት ማህበር የ2017 ዓ.ም መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አካሒዷል፡፡

በጉባኤው የማህበሩ የ2016 ዓ.ም የውጭ ኦዲተር ሪፖርት፣ የ2016 ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2017 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድ በማህበሩ ሥራ አስኪያጅ ተፈራ ገበየሁ ቀርቧል፡፡

የማህበሩ ፕሬዝዳንት አረጋ ይርዳው (ዶ/ር) የግል ትምህርት ዘርፉ አሁናዊ ሁኔታ እና ቀጣይ ስትራቴጂ ላይ ገለፃ አድርገው ሰፊ ውይይት ተደርጓል፡፡

በአጠቃላይ በአገሪቱ ከሚገኙ ተማሪዎች መካከል 41 በመቶ በግል ተቋማት እንደሚገኙና እንዚህ ተቋማት ባለፉት ሦስት አስርት ዓመታት በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ዜጎችን አስመርቀው ለስራ ያበቁና አሁንም እያበቁ እንደሆነ በትምህርት ሚኒስቴር የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዴስክ ኃላፊ እዮብ አየነው (ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡

በሀገሪቱ ካሉ 386 ተቋማት HEMIS የመረጃ ቋት መረጃቸውን ያስገቡ ተቋማት 131 ብቻ መሆናቸው ትልቅ ክፍተት መሆኑን አንስተዋል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

10 Nov, 18:51


#ሜድስኬፕ_ጤና_ሳይንስና_ቢዝነስ_ኮሌጅ_እንጅባራ_ካምፓስ

✔️ ሙሉ ዕውቅና እና ፈቃድ ያለው ኮሌጃችን፤ ልምድ ባላቸው ስፔሻሊስት ሀኪሞችና የጤና ባለሙያዎች የተቋቋመ ኮሌጅ ነው።

ለ2017 የትምህርት ዘመን በሚከተሉት የትምህርት መስኮች በመደበኛ፣ በቅዳሜና እሁድ፣ በኤክስቴንሽን መርሐግብር ምዝገባ ጀምረና

በመጀመሪያ ዲግሪ እንዲሁም በዲፕሎማ
➫ በፋርማሲ
➫ በነርሲንግ
➫ በማኔጅመንት
➫ በአካውንቲንግ እና ፋይናንስ
➫ በማርኬቲንግ ማኔጅመንት
➫ በኢኮኖሚክስ
➫ በኮምፒውተር ሳይንስ
➫ በእንሰሳት ጤና
➫ በአይሲቲ

በሪሚዲያል ፕሮግራም
➫ በ Natural Science
➫ በ Social Science

በኮሌጃችን ሲማሩ በነፃ የሚሰጡ ስልጠናዎች፦
✍️ Basic Computer Skills & Programming
✍️ የህይወት ክህሎት ስልጠና
✍️ Peachtree Accounting

አድራሻ፦
እንጅባራ ከተማ ዋናው አደባባይ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ፊት ለፊት

ስልክ ቁጥር፦
0995222294 / 0962791808 / 0921940650

Tikvah-University

10 Nov, 18:51


#ArbaMinchUniversity

በ2017 ዓ.ም አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ እና በ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ የቅድመ-ምረቃ መደበኛ ፕሮግራም ተማሪዎች ሪፖርት ማድረጊያ ቀናት ህዳር 7 እና 8/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ምዝገባ ኅዳር 9 እና 10/2017 ዓ.ም የሚከናወን ሲሆን፤ ትምህርት ረቡዕ ኀዳር 11/2017 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል፡፡

ሪፖርት ማድረጊያ ቦታዎች፦

- የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች አርባ ምንጭ ከተማ በሚገኘው አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ፣
- የስማችሁ የመጀመሪያ ፊደል ከ A እስከ Q የሆናችሁ የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች አርባ ምንጭ ከተማ በሚገኘው ጫሞ ካምፓስ፣
- የስማችሁ የመጀመሪያ ፊደል ከ R እስከ Z የሆናችሁ የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ሳውላ ከተማ በሚገኘው ሳውላ ካምፓስ።

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

- ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ሁለት ኮፒ፣
- የ12ኛ ክፍል ሰርተፊኬት ዋናውና ሁለት ኮፒ፣
- አራት 3×4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣
- አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ ትራስ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

10 Nov, 18:51


#BuleHoraUniversity

በ2016 ዓ.ም እና በ2017 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የድኅረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (NGAT) ወስዳችሁ ያለፋችሁ ተማሪዎች የሚያስፈልጋችሁን ሙሉ መረጃ በመያዝ ከጥቅምት 30/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ አስራ አምስት (15) የሥራ ቀናት ምዝገባ እንድታደርጉ ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል።

በቅድሚያ ኦፊሺያል ትራንስክሪፕት ማስላክ ይኖርባችኋል ተብሏል።

የድኅረ-ምረቃ የትምህርት መስኮች፦
1.Gadaa and Peace Studies (MA)
2.Gadaa and Governance Studies(PhD)

የምዝገባ ቦታ፦
ቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ህንጻ ቢሮ ቁ. 59

@tikvahuniversity

Tikvah-University

10 Nov, 07:06


#Infinix_HOT50_Pro+

አዲሱ የኢንፊኒክስ HOT 50 Pro+ ስልክ 7.8 ሚ.ሜ. ያህል ቀጭን ዲዛይን ይዞ የመጣ ሲሆን ይህም ስልኩን ለአያያዝ ምቹ ከማድረጉም በላይ እጅዎት ላይ እጅግ ያምራል፡፡

@Infinix_Et | @Infinixet

#Infinix #InfinixHOT50Pro+ #WOOOWNewHOT #InfinixHOT50Series

Tikvah-University

10 Nov, 07:06


#BoranaUniversity
#Revised

በ2016 ዓ.ም በቦረና ዩኒቨርሲቲ በሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታችሁን ስትከታተሉ ቆይታችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች፣ በ2016 ዓ.ም ትምህርት ጀምራችሁ በአንደኛ ሴሚሰቴር በውጤት እና በተለያዩ ምክንያቶች ዊዝድሮዋል በመሙላት ያቋረጣችሁ ተማሪዎች እንዲሁም በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት አምጥታችሁ ቦረና ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች ምዝገባ የሚከናወነው ህዳር 9 እና 10/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

ትምህርት የሚጀመረው ህዳር 12/2017 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል፡፡

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

- የ8ኛ ክፍል ሰርቲፊኬት ዋናውና ኮፒው፣
- ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
- የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ዋናውና ኮፒው፣
- ስምንት 3×4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣
- አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ ትራስ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

10 Nov, 07:06


መቐለ ዩኒቨርሲቲ ከ2,700 በላይ ተማሪዎች ዛሬ ማስመረቁ ይታወቃል።

በተማሪዎቹ የምርቃት ስነ-ስርዓት ላይ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ ምን አሉ?

በሰሜኑ ጦርነት ወቅት በመቐለ ዩኒቨርሲቲ ላይ ከደረሰው ቁሳዊ ውድመት ባሻገር፥ የሕይወት ዋጋ የከፈሉ፣ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው እና አድራሻቸው የጠፋ ተማሪዎች መኖራቸውን ፕሬዝዳንቱ ገልፀዋል።

ጦርነቱ በተማሪዎች እና በዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ላይ ከፍተኛ የማኅበራዊ ጫና ማስከተሉን ፕሬዝዳንቱ አንስተዋል።

መምህራንና የትምህርት አመራሮች ለ17 ወራት ያለ ደመወዝ በቀናነት ለሙያቸው ታምነው ማገልገላቸውን በማድነቅ አመስግነዋል።

የክልሉን የትምህርት ዘርፍ መልሶ ለማቋቋምና የደመወዝ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር እንደሚሰራ ተናግረዋል። #AshamTv

@tikvahuniversity

Tikvah-University

10 Nov, 07:06


ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለመጀመሪያ ጊዜ በእንስሳት ህክምና ያሰለጠናቸውን ሐኪሞች ዛሬ አስመርቋል።

ዩኒቨርሲቲው ለመጀመሪያ ጊዜ በእንስሳት ህክምና ሲያሰለጥናቸው የቆዩ 21 ሐኪሞችን አስመርቋል።

የዩኒቨርሲቲው Veterinary Medicine Department ወደ ትምህርት ቤት መሸጋገሩም ተገልጿል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

10 Nov, 07:06


#UniversityOfGondar

ለ2017 የትምህርት ዘመን በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ ገቢ ተማሪዎች እንዲሁም በ 2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች የነበራችሁና የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ቀናት ህዳር 12 እና 13/ 2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

የመጀመሪያ ቀን ትምህርት የሚጀምረው ህዳር 16/2017 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

10 Nov, 07:06


#EthiopianAviationUniversity

የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ ለ200 ጋቦናውያን ልዩ የአቪዬሽን ስልጠና የሚወስዱ ተማሪዎችን ተቀብሏል።

በተለያዩ የአቪዬሽን ዘርፎች ትምህርታቸውን ለሚከታተሉት ተማሪዎቹ በኢትዮጵያ አየር መንገድ እና በኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች አቀባበል ተደርጓል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

10 Nov, 07:06


#DillaUniversity

በ2016 ዓ.ም በሪሚዲያል ፕሮግራም ዲላ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታችሁን ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ እንዲሁም በ2017 ዓ.ም በፍሬሽማን ፕሮግራም ዲላ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ ገቢ ተማሪዎች ምዝገባ የሚከናወነው ህዳር 9 እና 10/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ

- ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት፣
- የ8ኛ ክፍል ካርድ ዋናውና ኮፒው፣
- ስምንት 3X4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣
- የትራስ ጨርቅ፣ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ።

በሌላ በኩል በዲላ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛው ፕሮግራም በ3ኛ ዲግሪ ለመማር አመልክታችሁ ተቀባይነት ያገኛችሁ እና በትምህርት ሚኒስቴር በመጀመሪያ እና 2ኛ ድግሪ ዲላ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ የስኮላርሺፕ (Scholarship) ተማሪዎች ተቋሙ ባሉት ፕሮግራሞች ምዝገባ የሚካሔደው ህዳር 9 እና 10/2017 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

09 Nov, 10:33


#TVTI

በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት በ2017 ዓ.ም በደረጃ-6 (BSc) ትምህርታችሁን ለመከታተል የመግቢያ ፈተና የተፈተናችሁ መደበኛ ሰልጣኞች ምዝገባ ህዳር 3 እና 4/2017 ዓ.ም እንደሚካሔድ ኢኒስቲትዩቱ አሳውቋል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

06 Nov, 06:41


ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሜዲካል ኮሌጅ በኅብረተሰብ ጤና የማስተርስ ፕሮግራም (MPH) መደበኛ እና የእረፍት ቀናት አመልካቾች የመግቢያ ፈተና ጥቅምት 30/2017 ዓ.ም ጠዋት 3:00 የሚሰጥ መሆኑን ገልጿል።

ለፈተና ስትሔዱ ማንነታችሁን የሚገልፅ መታወቂያ መያዝ ያስፈልጋል።

የፈተና ቦታ፦
ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሜዲካል ኮሌጅ የአካዳሚክ ህንፃ

@tikvahuniversity

Tikvah-University

06 Nov, 06:41


#JigjigaUniversity

ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም አዲስ ገቢ (1ኛ ዓመት) እና የሪሚዲያል ተማሪዎች የመግቢያ ቀናት ከህዳር 4 እስከ 6/2017 ዓ.ም ድረስ መሆኑን አሳውቋል፡፡

ለምዝገባ የሚያስፈልጉ፦
-ከ8ኛ እስከ 12ኛ ክፍል የትምህርት ማስረጃዎች ዋናውና ኮፒው፣
- ስምንት ጉርድ ፎቶግራፍ፣
- ብርድ ልብስ፣ አንሶላ እና የስፖርት ትጥቅ።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

05 Nov, 16:20


#AAU

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የብሪክስ+ ሀገራት ዩኒቨርሲቲዎች ማኅበር መስራች አባል ሆነ።

ማኅበሩ በዘጠኙ የብሪክስ+ ሀገራት ዩኒቨርሲቲዎች ጥምረት የተመሰረተ ሲሆን፤ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከመስራች ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አንዱ ሆኗል።

የብሪክስ+ ቡድንን ለመቀላቀል ፍላጎት ያላቸው የ 34 ሀገራት ዩኒቨርሲቲውዎችም የማኅበር አባል መሆናቸውን ከማኅበሩ ድረ-ገፅ ላይ የተገኘ መረጃ ያሳያል።

ዓለም አቀፍ ድጋፍ ማጠናከር፣ ልምድ ልውውጥ፣ የትምህርት ትብብርና ኔትወርኪንግ እንዲሁም ዓለም አቀፍ የአቅም ግንባታ ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማጎልበት ማኅበሩ የሚያከናውናቸው ተግባራት ናቸው።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

05 Nov, 14:24


#RayaUniversity

በ2017 ዓ.ም በራያ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ ተማሪዎች እና በ2016 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲው የማጠናከሪያ ትምህርት (Remedial Program) ወስዳችሁ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ቀናት ህዳር 2 እና 3/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

ትምህርት ህዳር 9/2017 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

05 Nov, 14:24


#HaramyaUniversity

በ2017 ትምህርት ዘመን ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ የፍሬሽማን ቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም ተማሪዎች እንዲሁም በ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታችሁን በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች ሪፖርት ማድረጊያ ጊዜ ከህዳር 9 እስከ 11/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

ምዝገባ ለማድረግ የሚያስፈልጉ፦
- የ8ኛ ክፍል ካርድ፣
- ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት፣
- የ12ኛ ከፍል ሰርትፍኬት ዋናውና ኮፒው፣
- 6 ፓስፖርት መጠን ፎቶግራፍ፣
- ብርድልብስ፣ አንሶላ፣ ትራስ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ መያዝ ይጠበቅባችኋል፡፡

ከላይ የተዘረዘሩትን የትምህርት ማስረጃዎች እና ፎቶግራፍ ስካን አድርጋችሁ በሶፍት ኮፒ መያዝ ይኖርባችኋል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

05 Nov, 14:24


#OdaBultumUniversity

በ2016 ዓ.ም የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ፕሮግራም ስትከታተሉ ቆይታችሁ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ ያስመዘገባችሁ እና በ2017 ዓ.ም ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ቀናት ህዳር 4 እና 5/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

ምዝገባ ለማድረግ የሚያስፈልጉ፦

- የ8ኛ ክፍል ስርትፊኬት ዋናውና ኮፒው፣
- የ10ኛ እና 12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ዋናውና ኮፒው፣
- ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
- አራት ፓስፖርት መጠን ፎቶግራፍ፣
- አንሶላ፣ ትራስ ጨርቅ፣ ብርድ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ መያዝ ይኖርባችኋል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

05 Nov, 14:24


#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር ለአስር የሀገር ውስጥ የምርምር ጆርናሎች ዕውቅና ሰጥቷል፡፡

በ2016 ዓ.ም ዕውቅና ለማግኘት ካመለክቱ የአገር ውስጥ የምርምር ጆርናሎች መካከል መስፈርቱን ላሟሉ አስር (10) የምርምር ጆርናሎች ለሦስት ተከታታይ ዓመታት የሚቆይ ዕውቅና መስጠቱን ሚኒስቴሩ አሳውቋል፡፡

ዕውቅና የተሰጣቸው ጆርናሎች፦

1. Berhan International Research Journal of Sciences and Humanities
2. Choke Journal of Science and Technology
3. Ethiopian Journal of Applied Sciences and Technology
4. Ethiopian Journal of Biological Sciences
5. Science, Technology and Arts Research Journal
6. Ethiopian Journal of Business and Social Science
7. Ethiopian Journal of Economics
8. Ethiopian Journal of Language, Culture and Communication
9. Ethiopian Journal of Sport Science
10. RADA Multidisciplinary Research

@tikvahuniversity

Tikvah-University

05 Nov, 14:24


#HawassaUniversity

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም በመደበኛ የዲግሪ ፕሮግራም አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ኀዳር 9 እና 10/2017 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል፡፡

የምዝገባ ቦታ፦
- የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በዋናው ግቢ
- የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ግቢ

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

➭ የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ዋናውና ኮፒው፣
➭ ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
➭ አራት ጉርድ ፎቶግራፍ፣
➭ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ እና ትራስ ጨርቅ፣
➭ የስፖርት ትጥቅ

@tikvahuniversity

Tikvah-University

04 Nov, 16:55


#ጥቆማ

የእንግሊዘኛ ቋንቋ ምዘና ፈተና (IELTS Test) በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ይውሰዱ፡፡

ብሪቲሽ ካውንስል ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የ IELTS ፈተና ኅዳር 21/2017 ዓ.ም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ይሰጣል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ፈተናውን መውሰድ የሚፈልጉ አመልካቾች ምዝገባ ማድረግ ጀምሯል።

የፈተና ቦታ፦ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ

ሁለት አይነት የ IELTS ፈተናዎች (IELTS Academic and IELTS General Training) ይሰጣሉ፡፡

ኦንላይን ይመዝገቡ 👇
https://ethiopia.britishcouncil.org/exam/ielts

በአካል ለመመዝገብ፦ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ ህንፃ ቁ. 130፣ ቢሮ ቁ. 408

ለበለጠ መረጃ፦ 0925629589

@tikvahuniversity

Tikvah-University

04 Nov, 16:55


#SamiTech

አዳዲስ ላፕቶፕች ከአንድ ዓመት ዋስትና ጋር!!
@samcomptech

በጥራት፣ በብራንድና በባትሪ ቆይታ አስተማማኝ የሆኑ የተለያዩ ሞዴል ላፕቶፖች በፈለጉት ስክሪን መጠን፣ ኮር አይ እና ጀነሬሽን አሉን።

ላፕቶፕ ከመገዛትዎ በፊት ማወቅ ያለባችሁን ወሳኝ ነገሮች እናስረዳለን። በላፕቶፖቻችን ጥራት ላይ አንደራደርም!

ለቢሮዎች፣ ለተማሪዎች፣ ለዲዛይን ባለሙያዎች፣ ለጌመሮች ወ.ዘ.ተ. ሁሉም አሉን።

የዕቃዎች ዋጋ፣ ዓይነት እና አድራሻ ለማግኘት 👉 @samcomptech

@sww2844

0928442662 / 0940141114

https://maps.app.goo.gl/H3PM1NrTcQ4SWkK17

Tikvah-University

04 Nov, 16:55


የ2017 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ምደባ ይፋ ሆኗል።

በ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግሥት ዩኒቨርስቲዎች የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ይፋ ተደርጓል።

ምደባችሁን ለማየት

በድረ ገጽ፦
https://placement.ethernet.edu.et

በቴሌግራም፦
https://t.me/moestudentbot

ትምህርት ሚኒስቴር የተቋም ይቀየርልኝ ጥያቄ #የማያስተናግድ መሆኑን ገልጿል።

@tikvahuniuversity

Tikvah-University

03 Nov, 11:31


ብሔራዊ ደኅንነት ዩኒቨርሲቲ ለመጀመሪያ ጊዜ በማስተርስ መርሐግብር ያሰለጠናቸውን የመረጃና ደኅንነት ሰልጣኞችን አስመርቋል።

በምረቃ መርሐግብሩ ወቅት የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ መረጃን መሰብሰብና መተንተን የሚችል ብቁ የመረጃና ደህንነት የሰው ኃይል ግንባታ እየተከናወነ ነው ተብሏል።

ብሔራዊ ደኅንነት ዩኒቨርሲቲ ከ40 ዓመታት በላይ የመረጃና ደህንነት የሰው ኃይል በማፍራት ላይ የሚገኝ ተቋም ነው።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

03 Nov, 11:31


ሁዋዌ በ8ኛው ዓለም አቀፍ የ2023/24 አይሲቲ ውድድር የተሳተፉ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎችን ሸልሟል።

ዘጠኝ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ባለፈው ዓመት በአገር አቀፍ እና በአህጉር አቀፍ የፍጻሜ ውድድሮች በክላውድ ትራክ፣ በኮምፒውቲንግ ትራክ እና በኔትወርክ ትራክ መወዳደራቸው ይታወሳል።

120 ተማሪዎች ለአገር አቀፍ የፍጻሜ ውድድር አልፈው የተሳትፎ ሰርተፍኬት መውሰዳቸውን ሁዋዌ ገልጿል፡፡

ከእነዚህ ውስጥ ዘጠኝ ተማሪዎች ኢትዮጵያን ወክለው በቱኒዚያ በተካሄደው ክፍለ አህጉራዊ ውድድር የሦስተኛ ደረጃን ሽልማት ማግኘታቸውና ሦስት ተማሪዎች ያሉት ቡድን ደግሞ፣ በቻይና ሼንዘን ከተማ በተካሄደው ዓለም አቀፍ የፍጻሜ ውድድር መሳተፋቸው አይዘነጋም፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

03 Nov, 11:31


#ይመዝገቡ

የሁዋዌ አይሲቲ ውድድር 2024/25 ፕሮግራም ይፋ ሆኗል፡፡

በ9ኛው ዓለም አቀፍ የ2024/25 አይሲቲ ውድድር ለመሳተፍ የምትፈልጉ እስከ ታህሳስ 2017 ዓ.ም መጨረሻ ድረስ መመዝገብ ይኖርባችኋል፡፡

ኔትዎርኪንግ፣ ክላውድ ኮምፒውተር እና አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ውድድሩ ከሚደረግባቸው የአይሲቲ ዘርፎች መካከል ይጠቀሳሉ።  

በሁዋዌ የICT ውድድር (Huawei ICT Competition 2024-2025) ለመሳተፍ በቅድሚያ የሁዋዌ ICT አካዳሚ አባል ይሁኑ።

የአካዳሚው አባል ለመሆን 👇
https://e.huawei.com/en/talent/portal/#/

ለውድድሩ ምዝገባ ለማድረግ 👇
https://bit.ly/SAR2024-2025

@tikvahuniversity

Tikvah-University

02 Nov, 11:19


#ECSU

የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በ2017 የትምህርት ዘመን ለሦስተኛ ዲግሪ (PhD) ትምህርት የተመረጡ ተማሪዎች የመጀመሪያ ሴሚስተር ምዝገባ የሚካሄደዉ ከጥቅምት 25-28/2017 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል፡፡

ትምህርት የሚጀምረው ጥቅምት 28/2017 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል፡፡

ምዝገባ ለማድረግ የሚያስፈልጉ፦

- የተፈረመና በማህተም የተረጋገጠ የስፖንሰርሺፕ ደብዳቤ፣
- ከሚሠሩበት ተቋም የድጋፍ ደብዳቤ፣
- የመጀመሪያ እና የሁለተኛ ዲግሪዎች ዋናውና የተማሪ ውጤቶች (Student Copies) ማስረጃዎች፣
- የድኅረ-ምረቃ ትምህርት የመግቢያ ፈተና ውጤት ሰርተፊኬት፣
- የሁለተኛ ዲግሪ አፊሺያል ትራንስክሪፕት በፖ.ሳ.ቁ. 5648 የተላከ መሆኑን የሚያረጋግጥ ማስረጃ፣
- ዲግሪዎቹ የተግኙት ከግል የትምህርት ተቋማት ወይም ከውጭ ሀገር ዩኒቨርሰቲዎች ከሆነ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን የአቻ ማረጋገጫ፣
- ሁለት ጉርድ ፎቶግራፍ፡፡

ምዝገባ ማድረግ የሚቻለው በግንባር በመቅረብ ብቻ እንደሆነ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

02 Nov, 11:19


#SamiTech

አዳዲስ ላፕቶፕች ከአንድ ዓመት ዋስትና ጋር!!
@samcomptech

በጥራት፣ በብራንድና በባትሪ ቆይታ አስተማማኝ የሆኑ የተለያዩ ሞዴል ላፕቶፖች በፈለጉት ስክሪን መጠን፣ ኮር አይ እና ጀነሬሽን አሉን።

ላፕቶፕ ከመገዛትዎ በፊት ማወቅ ያለባችሁን ወሳኝ ነገሮች እናስረዳለን። በላፕቶፖቻችን ጥራት ላይ አንደራደርም!

ለቢሮዎች፣ ለተማሪዎች፣ ለዲዛይን ባለሙያዎች፣ ለጌመሮች ወ.ዘ.ተ. ሁሉም አሉን።

የዕቃዎች ዋጋ፣ ዓይነት እና አድራሻ ለማግኘት 👉 @samcomptech

@sww2844

0928442662 / 0940141114

https://maps.app.goo.gl/H3PM1NrTcQ4SWkK17

Tikvah-University

02 Nov, 11:19


#MizanTepiUniversity

ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ወደ ተቋሙ አዲስ ለተመደባችሁ የመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ መርሐግብር ተማሪዎች እንዲሁም በ2016 ዓ.ም በሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታችሁን ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች የ2017 ትምህርት ዘመን ምዝገባ የሚከናወነው ኅዳር 2 እና 3/2017 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል፡፡

የምዝገባ ቦታ፦

- የማኅበራዊ ሳይንስ መስክ ተማሪዎች ሚዛን አማን በሚገኘው ዋናው ግቢ
- የተፈጥሮ ሳይንስ መስክ ተማሪዎች ቴፒ ከተማ በሚገኘው ቴፒ ግቢ

ለምዝገባ የሚያስፈልጉ፦

- የ10ኛ እና 12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት፣ - ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት፣
- ዘጠኝ 3×4 ፎቶግራፍ፣
- ብርድ ልብስ፣ አንሶላ፣ የትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ትጥቅ መያዝ ይኖርባችኋል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

02 Nov, 11:19


ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም አዲስ ለተመደቡ እንዲሁም የሪሚዲያል ፕሮግራም በመውሰድ የማለፈያ ነጥብ ላስመዘገቡ ተማሪዎች አቀባበል በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ለ2017 ትምህርት ዘመን አዲስ ገቢ ተማሪዎች ከጥቅምት 21-22/2017 ዓ.ም ይሪ ማድረጉ ይታዋሳል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

02 Nov, 11:19


#ጥቆማ

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የቴክስታይል እና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አመልካቾችን በመቀበል ላይ ነው።

ኢንስቲትዩቱ (BDU-EITEX) በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስዳችሁ የማለፊያ ነጥብ ያመጣችሁ ተማሪዎችን ይቀበላል።

የትምህርት መስኮች
- Textile Engineering
- Garment Engineering
- Leather Product Engineering
- Fashion Design
- Textile & Apparel Merchandising
- Visual Art
- Textile Chemical Process Engineering

የማመልከቻ ጊዜ የሚያበቃው፦
ጥቅምት 27/2017 ዓ.ም

ለበለጠ መረጃ፦ 0938882020

ለ2017 ዓ.ም በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የተመደባችሁ ተማሪዎች በዝውውር ማመልከት ትችላላችሁ ተብሏል።

ኦንላይን ለማመልከት 👇
https://forms.gle/gSypn17ttmm8k4746

@tikvahuniversity

Tikvah-University

01 Nov, 14:55


#Y12HMC

በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የኅብረተሰብ ጤና ትምህርት የድኅረ ምረቃ ፕሮግራም በኤክስቴንሽን መርሐግብር በ General Public Health, Reproductive Health, Epidemiology and Health Care Quality የትምህርት መስኮች ለመማር ላመለከታችሁ የመግቢያ ፈተና ቅዳሜ ጥቅምት 30/2017 ዓ.ም ጠዋት 2:30 እንደሚሰጥ አሳውቋል፡፡ የፈተና ቀን ማንነታችሁን የሚገልፅ መታወቂያ መያዝ ይኖርባችኋል ተብሏል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

01 Nov, 14:55


#TTI

የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት አዲስ የመደበኛ (የቀን) መርሐግብር ተመዝጋቢ ተማሪዎች የቃል ፈተና (Interview) ሰኞ ጥቅምት 25/2017 ዓ.ም ከሰዓት 7፡30 ላይ የሚሰጥ መሆኑን ገልጿል፡፡

በተጠቀሰው ቀን ለመደበኛ መርሐግብር ያመለከታችሁ በሙሉ በመፈተኛ ቦታ እንድትገኙ ኢንስቲትዩቱ አሳስቧል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

01 Nov, 14:55


#MoE

በ2017 የትምህርት ዘመን የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ፕሮግራም አይኖርም በሚል በአንዳንድ የማኅበራዊ ትስስር ገፆች እየተዘዋወረ የሚገኘው መረጃ #ሐሰተኛ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ገለፀ፡፡

ላለፉት ሁለት ዓመታት ተግባራዊ የሆነው የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ፕሮግራም "በዚህ ዓመት በበጀት እጥረት ምክንያት ተቋርጧል" በሚል የተሰራጨው መረጃ #ሐሰተኛ መሆኑን ሚኒስቴሩ በይፋዊ የማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮቹ ባጋራው መረጃ አረጋግጧል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

01 Nov, 14:55


#ETA

የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ዳግም ምዝገባ ያላደረጉ 102 ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ዝርዝርን ይፋ አድርጓል፡፡

ባለሥልጣኑ ይፋ ባደረገው ዝርዝር ውስጥ የተዘጉ እንዲሁም ለመዘጋት በሒደት ላይ የሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ይገኑበታል፡፡

በባለሥልጣኑ የዳግም ምዝገባ የሰነድ ማሰባሰቢያ የጊዜ ሰሌዳ ውስጥ ያልተመዘገቡ ተቋማት ከጥቅምት 18-22 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በወቅቱ ለመመዝገብ ያልቻሉበትን ምክንያት ለባለሥልጣን መ/ቤቱ በደብዳቤ እንዲያሳውቁ ባለሥልጣኑ አሳስቧል፡፡

በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ የማያመለክት ተቋም በአንቀጽ 2(11) መሠረት ከባለሥልጣኑ የወሰደው የማስተማር ፈቃድ በገዛ ፈቃዱ እንዳቋረጠ ተቆጥሮ የሚነጠቅ መሆኑን ተቋሙ ገልጿል፡፡

(የተቋማቱ ዝርዝር ከላይ ተያይዟል፡፡)

@tikvahuniversity

Tikvah-University

01 Nov, 09:19


#ጥቆማ

ዲላ ዩኒቨርሲቲ የአካባቢውን ማኅበረሰብ፣ የዩኒቨርሲቲውን ተማሪዎች፣ መምህራን እና ሰራተኞች ተጠቃሚ የሚያደርግ #ነጻ የኮሪያ ቋንቋ ስልጠና አዘጋጅቷል፡፡

ስልጠናው በዲላ ዩኒቨርሲቲ እና በኮሪያ መንግሥት ትብብር የተዘጋጀ ነው፡፡

ስልጠናውን ተከታትለው ለሚያጠናቅቁ ሰልጣኞች የምስክር ወረቀት ይሰጣል።

የምዝገባ ጊዜ፦
ከጥቅምት 25 እስከ ኅዳር 3/2017 ዓ.ም

የምዝገባ ቦታ፦ ኦዳያኣ ግቢ

@tikvahuniversity

Tikvah-University

01 Nov, 09:19


#DireDawaUniversity

ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛ እንዲሁም በተከትታይ እና በርቀት ትምህርት በቂ አመልካች በተገኘባቸው ፕሮግራሞች የድኅረ-ምረቃ አመልካቾች የ2ዐ17 ዓ.ም የመጀመሪያ ሴሚስተር ምዝገባ ከጥቅምት 25-27/2017 ዓ.ም ብቻ እንደሚከናወን አሳውቋል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

01 Nov, 09:19


#AAUAlumniNetwork

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ተመራቂ ከሆኑ የዩኒቨርሲቲውን የቀድሞ ምሩቃን ኔትወርክ (AAU’s Alumni Network) እንዲቀላቀሉ ተጋብዘዋል፡፡

ኔትወርኩ የቀድሞ ተማሪዎች አብረዋቸው ከተማሩ ጋር በቀላሉ ለመገናኘትና በኅብረት ለመስራት፣ ሙያዊ አበርክቶ ለማስፋት እንዲሁም ዩኒቨርሲቲው የሚያከናውናቸውን የለውጥ ተግባራት ለማገዝ የሚያስችል ነው ተብሏል።

ተከታዩን ሊንክ በመጫንና የራስዎን ፕሮፋይል በመሙላት አባል ይሁኑ 👉 https://alumni.aau.edu.et

@tikvahuniversity

Tikvah-University

28 Oct, 07:27


#ማስታወሻ

የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ የአንደኛ፣ የሦስተኛ እና የአራተኛ ዓመት ነባር መደበኛ ተማሪዎች ምዝገባ ጥቅምት 20 እና 21/2017 ዓ.ም ይካሔዳል።

በቅጣት ምዝገባ፦ ጥቅምት 22/2017 ዓ.ም
ትምህርት የሚጀምረው፦ ጥቅምት 25/2017 ዓ.ም

በ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ስትከታተሉ ቆይታችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ እና በ2017 ዓ.ም አዲስ ለተመደባችሁ የአንደኛ ዓመት እና በሪሚዲያል ፕሮግራም ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ለምትመደቡ ተማሪዎች በሌላ ማስታወቂያ በቅርቡ ጥሪ ይደረጋል ተብሏል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

28 Oct, 07:27


"በአምስት ዓመት መመረቅ ሲገባን አንድ ዓመት ተጨምሮብናል" - የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ኤክስቴንሽን ተማሪዎች

"መውሰድ ያለባቸውን ቀሪ ኮርሶች አጠናቀው ሲጨርሱ ይመረቃሉ" - የዩኒቨርሲቲው የሬጅስትራርና አልሙናይ ዳይሬክተር


በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሚማሩ በተለይ የአካውንቲንግ፣ ኢኮኖሚክስ እና ማኔጅመንት የኤክስቴንሽን ተማሪዎች "መማር ካለብን አምስት ዓመት ውጪ አንድ ዓመት ተጨምሮብን የምንመረቅ መሆናችን ተነግሮናል" የሚል ቅሬታ ለቲክቫህ አድርሰዋል።

"ስንጀምር ሰኔ 2017 ዓ.ም እንደምንጨርስ አውቀን ነበር ወደጊቢው የገባነው። በህጉ መሰረት ኤክስቴንሽን ተማሪ አምስት ዓመት ነበር መማር ያለበት። ነገር ግን በዚህ ዓመት አትመረቁም ተብለናል" ብለዋል ተማሪዎቹ።

ያልጨረሱት ኮርስ መኖሩን በዩኒቨርሲቲው የተገለፀላቸው ተማሪዎቹ፤ በኮቪድ-19 ወቅት ሦስት ሴሚስተር መማር ሲኖርባቸው አንድ ሴሚስተር ብቻ መማራቸውን ያነሳሉ።

"ይሁንና ተቋሙ ማካካሻ ትምህርት ሰጥቶ ሊያስመርቀን ሲገባ በወቅቱ ምላሽ ሳናገኝ፥ ቅሬታችንን የሚቀበለን አካል አጥተን ቆይተናል ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ላይ የጠየቃቸው የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የአካውንቲንግ እና ፋይናንስ ትምህርት ክፍል ኃላፊ መምህር ሀርካን ማሞ፥ በተማሪዎቹ ላይ አንድ ዓመት አለመጨመሩን ገልፀዋል።

በኮቪድ-19 ምክንያት ተማሪዎቹ ዘግይተው ግንቦት 2013 ዓ.ም ላይ ትምህርት መጀመራቸውን የገለፁት ኃላፊው፤ "ተማሪዎቹ በዓመት ሦስት ሴሚስተር ነው የሚማሩት፥ በገቡበት ዓመት ደግሞ አንድ ሴሚስተር ብቻ ነው የተማሩት" ብለዋል።

"እነሱ የገቡት ግንቦት ወር ላይ ነው። የዘለሉት ሁለት ሴሚስተር አለ። ምንም የተጨመረ ነገር የለም።" "ኮርሶችን ሳይጨርሱ መመረቅ ስለማይችሉ፥ ቀሪ ኮርሶቻቸውን አጠናቀው ይመረቃሉ" ብለዋል።

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሬጅስትራርና አልሙናይ ዳይሬክተር ዘሪሁን ክንፈ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ተማሪዎቹ በ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና የዘገየ በመሆኑ ወደ ሰኔ አካባቢ ትምህርት መጀመራቸውን አስታውሰዋል።

በተገለፀው ዓመት መማር የነበረባቸውን ሁለት ሴሚስተር አለመማራቸውንም አስረድተዋል።

ተማሪዎቹ የእረፍት ቀናት እና የማታ መርሐግብር በመሆናቸው በዓመት ውስጥ የክረምት ሴሚስተርን ጨምሮ ሦስት ሴሚስተር ስለሚማሩ፥ የማካካሻ ጊዜ እንዳልነበረ አንስተዋል።

ለተማሪዎቹ በ2017 ዓ.ሞ ጨርሳችሁ ትመረቃላችሁ ብሎ የገለፀ አካል አለመኖሩን ያነሱት ዳይሬክተሩ፤ መውሰድ ያለባቸውን ቀሪ ኮርሶች አጠናቀው ሲጨርሱ ይመረቃሉ ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahuniversity

Tikvah-University

27 Oct, 17:22


የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የፋሽን ቴክኖሎጂና ዲዛይን ትምህርት ስልጠና በዚህ ዓመት ይሰጣል።

የፋሽን ቴክኖሎጂና ዲዛይን ስልጠና በገበያው ተፈላጊ በመሆኑ በተያዘው ዓመት በደረጃ ስድስት ለመስጠት መወሰኑን የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) ለኢፕድ ተናግረዋል፡፡

ኢንስቲትዩቱ በደረጃ ስድስት በ21 መስኮች እንዲሁም በደረጃ ሰባትበ19 የስልጠና መስኮች ስልጠና እንደሚሰጥ ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።

በአጭር ጊዜ ስልጠና የሚሰጡ የሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ የሮቦቲክስ እና ሌሎች የስልጠና መስኮችን ወደ መደበኛ የስልጠና መስክ ለማሳደግ እየተሠራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

በባዮ-ሜዲካል ቴክኖሎጂ፣ ኤቪዬሽን፣ ማዕድን እና ባቡር ኢንጂነሪንግ መስኮች ስልጠና ለመስጠት የስርዓተ ትምህርት ቀረፃ እየተደረገ መሆኑንም ለኢፕድ ገልፀዋል።

የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት በፌዴራል ደረጃ ከደረጃ ስድስት ጀምሮ ስልጠና የሚሰጥ ተቋም ነው።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

27 Oct, 17:22


#ጥቆማ

የፕሮግራሚንግ ክህሎትንና የዲጂታል ዕውቀትን የሚያጎለብት የፕሮግራሚንግ መፅሐፍ ለመጀመሪያ ጊዜ በአማርኛ ለህትመት በቅቷል።

C++ Programming in Amharic የተሰኘው መፅሐፉ፥ በዘርፉና በሶፍትዌር ማበልፀግ የበርካታ ዓመታት ልምድ ባላቸው ዮሐንስ እዘዘው የተፃፈ ነው።

346 ገፆች ያሉት መፅሐፉ፤ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን፣ መምህራንን እና የዘርፉ ተመራማሪዎችን በፕሮግራሚንግ ቋንቋ ዙሪያ እንደሚጠቅም ፀሐፊው ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ተናግረዋል።

መፅሐፉ በነፃ የቀረበ ሲሆን፤ በኦንላይን https://t.me/eteldigital ሊያገኙት ይችላሉ ብለዋል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

26 Oct, 16:51


አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በሰው ሠራሽ አስተውሎት(Artificial Intelligence) የድኅረ-ምረቃ መርሐግብር ሊከፍት ነው።

ዩኒቨርሲቲው በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ፣ በቢግ ዳታ እና በሳይበር ሴኪዩሪቲ መስኮች የድኅረ-ምረቃ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር እየሠራ መሆኑን በተቋሙ የምርምርና ልህቀት ማዕከላት ዳይሬክተር ጌታቸው አዳም (ዶ/ር) ለኢዜአ ተናግረዋል።

ዩኒቨርሲቲው ባሉት ስምንት የልህቀት ማዕከላት የተለያዩ የድኅረ-ምረቃ መርሐግብሮችን በመክፈት ላይ እንደሚገኝ ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።

ባለፈው ዓመት በዩኒቨርሲቲው የተከፈተው የኒውክለር ሳይንስና ቴክኖሎጂ የድኅረ-ምረቃ መርሐግብር ተማሪዎችን ተቀብሎ እያስተማረ ይገኛል ብለዋል።

ዩኒቨርሲቲው የልህቀት ማዕከላቱን ታሳቢ ያደረገ የህንፃ ግንባታ እያካሕደ ሲሆን፤ እስካሁን የአራት ልህቀት ማዕከላት ግንባታ መጠናቀቃቸው ታውቋል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

26 Oct, 11:05


How is EdTech changing schools in Ethiopia? Catch our radio show as we discuss the impact of different initiatives and how they are transforming classrooms.

Tune in to Fana FM 98.1 on October 28th at 8:10pm for insights.

#EdTechMondays #EdTechMondaysEthiopia #Ethiopia #Africa #Education #EdTech #Tech #AddisAbaba #ICT #Infrastructure #Digital #DigitalLiteracy #Shega #mastercardfoundation

Tikvah-University

26 Oct, 11:05


#BoranaUniversity

በቦረና ዩኒቨርሲቲ በ Disaster Risk Management የማስተርስ ፕሮግራም ለመማር ያመለከታችሁ የመጀመሪያ ዓመት አንደኛ ሴሚስተር ምዝገባ ጥቅምት 22 እና 23/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡

በፕሮግራም ደረጃ የመግቢያ ፈተና ጥቅምት 25/2017 ዓ.ም ይሰጣል የተባለ ሲሆን፤ ትምህርት ጥቅምት 28/2017 ዓ.ም እንደሚጀምር ተገልጿል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

26 Oct, 11:05


#HaramayaUniversity

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ለ2017 ዓ.ም አዲስ የድኅረ-ምረቃ ትምህርት አመልካቾች የመግቢያ ፈተና ጥቅምት 18/2017 ዓ.ም ጠዋት የሚሰጥ መሆኑን ገልጿል፡፡

የፈተና ቦታ፦
ከጤናና ህክምና ኮሌጅ አመልካቾች ውጪ በዋናው ግቢ ሲሆን፤ የጤናና ህክምና ኮሌጅ አመልካቾች ሐረር ካምፓስ፡፡

አመልካቾች ለፈተና ስትሔዱ መታወቂያ፣ የትምህርት ሰነዶች፣ የስፖንሰርሺፕ ደብዳቤ እና የክፍያ ደረሰኝ ሜዝ ይኖርባችኋል፡፡

ለበለጠ መረጃ፦
0255530405 / 0255530332

@tikvahuniversity

Tikvah-University

25 Oct, 16:51


በ2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ወደ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ለሚገቡ አዲስ ተማሪዎች ምዝገባ ዛሬ ተጀምሯል።

የኦንላይን ምዝገባው ከዛሬ ጥቅምት 15/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለአስር ቀናት ይካሔዳል።

ሰልጣኞች በከተማዋ በሚገኙ 14 የመንግስት ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በተዘጋጀው ሊንክ በመግባት ምዝገባ ማከናወን ይችላሉ ተብሏል፡፡

በከተማዋ በዚህ ዓመት ከ23 ሺህ በላይ ተማሪዎች በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ከደረጃ 5 እስከ ደረጃ 2 ስልጠናዎችን እንደሚከታተሉ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ገልጿል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

25 Oct, 16:51


#MoH

ሰኔ 19/2016 ዓ.ም የፅሁፍ ፈተና እና መስከረም 30/2017 ዓ.ም የተግባር ፈተና (OSCE) የወሰዳችሁ የአንስቴዥያ ሙያ ተመዛኞች ከዛሬ ጥቅምት 14/2017 ዓ.ም ጀምሮ ውጤታችሁን ማየት ትችላላችሁ ተብሏል።

http://hple.moh.gov.et/hple ላይ በመግባት ሙሉ ስም እና የፈተና መለያ ቁጥራችሁን በማስገባት ውጤታችሁን መመልከት ትችላላችሁ።

በውጤታችሁ ላይ ቅሬታ ያላችሁ ተመዛኞች ከዛሬ ጀምሮ ባሉት አስር (10) ተከታታይ የሥራ ቀናት በስልክ ቁ. 952 / 0118275936 በመደወል ወይም በኢሜይል [email protected] ላይ ሙሉ ስም፣ ዲፓርትመንት፣ የመለያ ቁጥር እና የተማራችሁበትን የትምህርት ተቋም ስም በመሙላት ጥያቄዎቻችሁን ማቅረብ እንደምትችሉ ተገልጿል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

25 Oct, 07:23


#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር በአቅም ማካካሻ (Remedial) ፕሮግራም ውጤት አያያዝ ላይ ማሻሻያ አደረገ፡፡

ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ ከ50 በመቶ በታች ውጤት ካገኙ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች መካከል የተሻለ ውጤት ያላቸውን በመምረጥ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማካካሻ (Remedial)) ፕሮግራም ተመድበው የማካካሻ ትምህርት እንዲከታተሉ መደረጉ ይታወቃል።

በዚህ መሠረት ተማሪዎቹ 70% በማዕከል እና 30% በተቋማት የሚዘጋጁ ምዘናዎችን ተፈትነው ሲያልፉ የፍሬሽማን ፕሮግራም ተማሪዎች ሆነው እንዲቀጥሉ እየተደረገ ይገኛል።

ይሁን እንጂ ከ30% በተቋማት የሚሰጠው ውጤት አሰጣጥ ላይ ወጥነት የሌለ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በፃፉት ሰርኩላር ገልፀዋል፡፡

በዚህም ከ2017 የትምህርት ዘመን ጀምሮ የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ምዘና ከ100% የሚሰጠው ከማዕከል እንዲሆን ተወስኗል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

25 Oct, 07:23


#ማስታወሻ

የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ለ2017 ትምህርት ዘመን በመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራም የሰልጣኞች ምዝገባ ዛሬ ይጠናቀቃል፡፡

መስፈርቶች
▪️የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ የሆኑ፣
▪️በ2015/16 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና የማለፊያ ውጤት (50%) ያላቸው፣
▪️በ2014/15 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ተከታትለው ያጠናቀቁ

ስልጠናው በአዲስ አበባ ላምበረት መናኸሪያ አካባቢ በሚገኘው የኢንስቲትዩቱ ግቢ የሚሰጥ ሲሆን፤ በተጨማሪም የቻይንኛ እና ኮሪያኛ ስልጠናዎች ይሰጣሉ፡፡ ኢንስቲትዩቱ የምግብ እና የዶርም አገልግሎቶች ያቀርባል፡፡

የምዝገባ ጊዜ፦
ጥቅምት 11-15/2017 ዓ.ም
የመግቢያ ፈተና የሚሰጥበት ጊዜ፦
ጥቅምት 19/2017 ዓ.ም
ትምህርት የሚጀምረው፦
ኅዳር 2/2017 ዓ.ም

አስፈላጊ ሰነዶች
▪️ የ11ኛ እና የ12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት
▪️ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ሰርተፊኬት
▪️ የሪሚዲያል ፕሮግራም ሰርተፊኬት

@tikvahuniversity

Tikvah-University

24 Oct, 15:53


#MoE

የ2017 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ ምደባ ይፋ ሆኗል።

በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ በመደበኛው ፕሮግራም ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታችሁን ለመከታተል የሚያስችል የማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ይፋ ሆኗል።

ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ምደባችሁን ማየት የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል፦

በድረ-ገፅ 👇
https://placement.ethernet.edu.et

በቴሌግራም 👇
https://t.me/moestudentbot

የተቋም ይቀየርልኝ ጥያቄ የማያስተናግድ መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳውቋል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

24 Oct, 10:31


በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመምህራን ደመወዝ በመቋረጡ የ2017 ትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሥራ በተለያዩ ዞኖች በአግባቡ አለመጀመሩ ተገለፀ፡፡

በክልሉ የተለያዩ ዞኖች የመምህራን ደመወዝ በመቋረጡ የተነሳ እስካሁን በአንዳንድ ትምህር ቤቶች ትምህርት አለመጀመሩ ተሰምቷል፡፡

ከግል እና ከጥቂት የመንግሥት ትምህርት ቤቶች ውጪ አብዛኞቹ ትምህርት ቤቶች እንዳልተከፈቱ፣ ቢከፈቱም ከሁለት በላይ መመህራን ስለማይገቡ ትምህርት አለመጀመሩን አስተያየታቸውን ለቮኦኤ የሰጡ ወላጆች ስጋታቸውን ገልፀዋል።

በወላይታ ዞን፣ በጋሞ ዞን፣ በኮንሶ ዞን እና በጎፋ ዞን በሚገኙ 28 ወረዳዎች የሚያስተምሩ በሺዎች የሚቆጠሩ መምህራን ደመወዝ በወቅቱ እንደማይከፈል የክልሉ መምህራን ማኅበር ገልጿል።

በዞኖቹ ከሁለት እስከ ሦስት ወራት ደመወዝ ያልተከፈላቸው መምህራን መኖራቸውን የገለፁት የማኅበሩ ፕሬዝዳንት አማኑኤል ጳውሎስ፤ መምህራኑ በጣም በመቸገራቸው ኑሯቸውን ለመደጎም የቀን ሥራ ጭምር እየሠሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡

መምህራኑ የደመወዝ ይከፈለን ጥያቄ ሲያቀርቡ ዛቻ፣ ማስፈራሪያ እና እስራት እየተፈፀመባቸው እንደሆነም ወላጆች እና መምህራን ገልፀዋል፡፡

በአንዳንድ ክልሎች የመምህራን ደመወዝ በጊዜ አለመከፈል ብሎም እየተቆራረጠ በፐርሰንት መከፈል፣ ያለመምህራን ዕውቅናና ፈቃድ በተለያዩ ምክንያቶች የደመወዝ መቆረጥ፤ ይሄንን የሚቃወሙትን ደግሞ ማዋከብና ማንገላታት እንደሚፈፀም የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ባለፈው ሳምንት ባወጣው መግለጫ መግለፁ ይታወሳል፡፡

የቪኦኤን ዘለግ ያለ ዘገባ ያድምጡ  👇
https://amharic.voanews.com/a/south-ethiopia-school-disruption/7836277.html

@tikvahuniversity

Tikvah-University

24 Oct, 10:31


#UniversityOfGondar

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ለቅድመ-ምረቃ እና ድኅረ-ምረቃ ፕሮግራም መደበኛ እና ተከታታይ መርሐግብር ተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል፡፡

በዚህም የቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች የ2017 ትምህርት ዘመን የምዝገባ ቀናት ጥቅምት 21 እና 22/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

በተመሳሳይ የነባር እና አዲስ ገቢ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራም መደበኛ እና ተከታታይ መርሐግብር ተማሪዎች ጥቅምት 21 እና 22/2017 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል፡፡

በ2017 ዓ.ም ጎንደር ዩኒቨርሲቲ አዲስ የምትመደቡ ተማሪዎች እና በ2016 ዓ.ም በሪሚዲያል መርሐግብር ትምህርታችሁን ስትከታተሉ ቆይታችሁ የማለፊያ ነጥብ ያመጣችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ቀናት ወደፊት ይገለፃል ተብሏል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

24 Oct, 10:31


ኢንዲያን ዓለም አቀፍ ትምህርት ቤት እና አንድነት ዓለም አቀፍ ትምህርት ቤት የማስተማር ፈቃዳቸው እንዳልታደሰላቸው የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን አሳውቋል፡፡

በ2017 ትምህርት ዘመን በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች ፈቃድ ያላቸው፣ የሌላቸው እና የፈቃድ ዕድሳት ጥያቂያቸው በሒደት ላይ የሆኑ ዓለም አቀፍ እና የማኅበረሰብ ትምህርት ቤቶች ዝርዝርን ባለሥልጣኑ ይፋ አድረጓል፡፡

በዚህም ከኬጂ እስከ 12ኛ ክፍል የሚያስተምሩት ኢንዲያን ዓለም አቀፍ ትምህርት ቤት እና አንድነት ዓለም አቀፍ ትምህርት ቤት የማስተማር ፈቃዳቸው ያልታደሰላቸው መሆኑ ተገልጿል፡፡

የፈቃድ ዕድሳት ጥያቄ አቅርበው በሒደት ላይ የሚገኙ ተቋማት፦
▪️ብሪቲሽ ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤት
▪️ላየን ኸርት አካዳሚ
▪️ሄለኒክ ግሪክ ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤት

የፈቃድ ጥያቄ አቅርበው በሒደት ላይ የሚገኙ ተቋማት፦
▪️ትራንሴንድ አካዳሚ
▪️ማህሪፍ ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤት

ሌሎች 23 ዓለም አቀፍ እና የማኅበረሰብ ትምህርት ቤቶች ፈቃድ የተሰጣቸው እና ፈቃዳቸው የተሰጣቸው መሆኑንም የባለስልጣኑ መረጃ ያሳያል፡፡

(ባለሥልጣኑ ያወጣው ዝርዝር ከላይ ተያይዟል፡፡)

@tikvahuniversity

Tikvah-University

23 Oct, 19:03


በጦርነት ምክንያት ሥራ ያቆሙ መምህራንን ማዘዋወር ካልተቻለ ወደ ሥራቸው እስኪመለሱ ባሉበት ደመወዛቸው እንዲከፈላቸው የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር ጠየቀ፡፡

"መምህራን የኑሮ ውድነት በከፍተኛ መጠን እየፈተናቸው እንደሚገኙ፣ የረዥም ጊዜ አገልግሎት ያላቸው መምህራን የደረጃ ዕድገት ወይም ዕርከን እያገኙ አለመሆናቸው፣ በአንዳንድ ክልሎች የመምህራን ደመወዝ በጊዜ አለመከፈልና በፐርሰንት መቆራረጥ፣ ያለ መምህራን ፈቃድ በተለያዩ ምክንያቶች የደመወዝ መቆረጥና ይህንን ድርጊት የሚቃወሙትን ደግሞ ማዋከብና ማንገላታት እንዳለ" 37ኛ መደበኛ ጉባኤውን በቅርቡ ያካሔደው ማኅበሩ አሳውቋል፡፡

በተጨማሪም ከዓመታት በፊት የተጀመረው የመምህራን የመኖሪያ ቤትና የመሥሪያ ቦታ በሚፈለገው ፍጥነት እየተከናወነ አለመሆኑን፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን ደግሞ ጭራሽ አለመጀመሩን፣ በትርፍ ሰዓት ክፍያ ላይ ተደራራቢ ግብር መቆረጥ፣ የመጻሕፍትና ሌሎች ግብዓቶች እጥረት፣ የክረምት መምህራን ሥልጠናና ያጋጠሙ ችግሮች ማኅበሩ ባወጣው መግለጫ ተዳሰዋል፡፡

"መምህራን ክፍል ውስጥ ገብተው ማስተማር ባልቻሉበት ወቅት፣ አላሰተማሩም ተብሎ ደመወዛቸው ሊቆረጥባቸው አይገባም" ሲሉ የማኅበሩ ፕሬዝዳንት ዮሐንስ በንቲ (ዶ/ር) ለሪፖርተር ተናግረዋል።

ከወራት በፊት የ18 ወራት ውዝፍ ደመወዝ ስላልተከፈላቸው ለችግር መጋለጣቸውን የትግራይ ክልል መምህራን መጠየቃቸው ይታወሳል፡፡ በዚህም በቅርቡ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የአምስት ወራት ደመወዝ ለመምህራኑ እንደሚከፍል ቢናገርም፣ የቀሪው የአንድ ዓመት ውዝፍ ክፍያ ግን አሁንም መፍትሔ እንደሚፈልግ የማኅበሩ ፕሬዝዳንት ገልፀዋል፡፡

በጦርነት ምክንያት ሥራ ያቆሙ መምህራንን ማዘዋወር ካልተቻለ ወደ ሥራቸው እስኪመለሱ ባሉበት ደመወዛቸው እንዲከፈላቸው የጠየቁት የማኅበሩ ፕሬዝዳንት፤ መንግሥትም ሆነ ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት የመምህራኑን ችግር ሊረዱና መፍትሔ ሊሰጡት ይገባል ብለዋል፡፡

ከትግራይ ክልል በስተቀር በሌሎች ክልሎች እስከ ሦስት ወራት ደመወዝ ያልተለከፈላቸው በተለይም በቀድሞው ደቡብ ክልል ውስጥ የነበሩ ትምህርት ተቋማትም እንደሚገኙ የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፤ በአማራ ክልል በሚካሄደው ጦርነት ደመወዝ ያልተከፈላቸውና ሥራ ያቆሙ መምህራን መረጃ ተጠናቅሮ አልደረሰም ብለዋል። #ሪፖርተር

@tikvahuniversity

Tikvah-University

23 Oct, 19:03


ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ነባር መደበኛ ተማሪዎቹን በመቀበል ላይ ይገኛል።

ዩኒቨርሲቲው ለነባር መደበኛ እና የ2016 ሪሚዲያል ተማሪዎቹ ለጥቅምት 11 እና 12/2017 ዓ.ም ጥሪ ማድረጉ ይታወሳል።

@tikvahuniversity

Tikvah-University

23 Oct, 19:03


#ጥቆማ

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የድኅረ-ምረቃ ትምህርት አመልካቾች ምዝገባ ከዛሬ ጥቅምት 13 እስከ 19/2017 ዓ.ም ያከናውናል፡፡

ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ትምህርት የመግቢያ ፈተና (NGAT) ወስደው የማለፊያ ነጥብ በማምጣት ካመለከቱ መካከል፣ በቂ አመልካች ቁጥር የተገኘባቸውና በ2017 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲው ዋናው ግቢ የሚከፈቱ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች፦
▪️ Nutrition (መደበኛ)
▪️ Reproductive Health (መደበኛ)
▪️ MBA (መደበኛ እና ኤክስቴንሽን)

በሌሎች የትምህርት ክፍሎች ያመለከታቸሁ፣ በቂ የአመልካች ቁጥር ባለመገኘቱ የትምህርት ዝግጅታችሁ በሚያሳትፋችሁ በተከፈቱ ትምህርት ክፍሎች ላይ እንድትመዘገቡ ዩኒቨርሲቲው ጠቁሟል፡፡

በኦንላይን የተመዘገባችሁ ለምዝገባ ስትሔዱ ለማመልከት የተጠየቁትን መረጃዎች ይዛችሁ መቅረብ ይኖርባችኋል፡፡

@tikvahuniversity

Tikvah-University

23 Oct, 19:03


ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም በተቋሙ የሪሚዲያል ተማሪዎች የነበራችሁና የማለፊያ ነጥብ ያሰመዘገባችሁ እንዲሁም በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስዳችሁ በሰላሌ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሔደው ጥቅምት 21 እና 22/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

ለምዝገባ ስትሔዱ መያዝ የሚኖርባችሁ፦
▪️ ብርድ ልብስ፣ አንሶላ፣ ትራስ ጨርቅ
▪️ አራት 3x 4 ጉርድ ፎቶግራፍ

የምዝገባ ቦታ፦
ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ጀኔራል ታደሰ ብሩ ከምፓስ

@tikvahuniversity