Tikvah ethiopia @tikivahethiopiae Channel on Telegram

Tikvah ethiopia

@tikivahethiopiae


You will get best orginal goods here

Tikvah ethiopia (English)

Welcome to Tikvah Ethiopia, your one-stop destination for the best original goods! Our Telegram channel, @tikvahethiopiae, is dedicated to providing you with high-quality products that are truly unique and authentic. Whether you are looking for traditional Ethiopian crafts, handmade jewelry, or stylish clothing, you can find it all here.

Who are we? Tikvah Ethiopia is a team of passionate individuals who have a deep appreciation for Ethiopian culture and craftsmanship. We believe in supporting local artisans and promoting their incredible work to a global audience. By shopping with us, you are not only getting top-notch products but also contributing to the livelihood of talented individuals in Ethiopia.

What can you expect from our channel? We regularly update our channel with new arrivals, exclusive deals, and behind-the-scenes glimpses into the creative process of our artisans. From intricate woven baskets to beautifully designed leather goods, there is something for everyone at Tikvah Ethiopia.

So why wait? Join our Telegram channel today and start discovering the best original goods that Ethiopia has to offer. Let Tikvah Ethiopia be your go-to source for authentic products that embody the rich heritage and craftsmanship of this beautiful country. We can't wait to welcome you into our community of discerning shoppers who appreciate the beauty of handmade products. Shop with us and experience the magic of Tikvah Ethiopia!

Tikvah ethiopia

16 Nov, 14:40


ምርጥ የሆነ የኤሌክትሪክ ፀጉር መቁረጫ, ቅርፅ ማውጫ  አራት ደረጃ መቁረጥ የሚችል ባትሪው  አንዴ ቻርጅ ከተደረገ እስከ 3 ቀን (ባትሪው ሳያልቅ የአራት ሰው ፀጉር ማስተካከል የሚችል)
ዋጋ 2000 ብር ብቻ!! ይዘዙን
#0922415892

Revolutionary Electric Hair Clipper – Designed for Perfection!
Upgrade your grooming experience with the ultimate electric hair clipper. This stylish, efficient, and easy-to-use device delivers professional-quality results at your convenience!
Features
1. Long-Lasting Power: Powered by a rechargeable battery for extended use.
2. Elegant Design: Traditional-inspired engravings paired with modern functionality.
3. Precision Trimming: Sharp blades and multiple clipper guards for any style.
4. User-Friendly: Lightweight, compact, and portable for home or professional use.
5. Complete Set: Comes with a rechargeable battery, USB cable, oil, and comb attachments.

Tikvah ethiopia

29 Oct, 11:04


👇👇👇👇👇👇👇 በጣም ጠቃሚ መረጃ!!!!

ፓይ ኔት ወርክን በመቀላቀል በቀን እስከ አርባ ዶላር ያግኙ !! ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን አፕሊኬሽኑን ማይን ማድረግ ያስጀምሩ አፕሊኬሽኑ በራሱ ፓይ ኮን ማይን በየሰዐቱ ያደርጋል!!! ሞክሩት ራሳችሁ ጉግል ላይ በመግባት የአንድ ፓይ ኮይን(pi coin) ዋጋ ገበያ ላይ 40 dollar እየተሸጠ እንደሆነ ማረጋገጥ ትችላላችሁ!! አያምልጣችሁ
Pi is a new digital currency developed by Stanford PhDs, with over 55 million members worldwide. To claim your Pi, follow this link https://minepi.com/teddyalem and use my username (teddyalem) as your invitation code.

Tikvah ethiopia

01 Oct, 12:45


https://qwickbirr.com/?aff=150740

Tikvah ethiopia

29 Aug, 07:45


#Ethiopia🇪🇹

" በዝምታ አንመለከትም " - ኢትዮጵያ

በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት የሽግግር ተልዕኮ (አትሚስ) በቀጣይ የሚኖረው አዲስ የሰላም ተልዕኮ አወቃቀር ሁኔታ በአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ላይ አዲስ ስጋት ይዞ መምጣቱ ኢትዮጵያን እንዳሳሰባት አሳውቃለች።

" የአፍሪካ ህብረትና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለዚሁ አዲስ ሽግግር እየተዘጋጁ ባሉበት ወቅት፣ ቀጠናው ሊተነበይ ወደማይቻል ፈተና ውስጥ እየገባ ይገኛል"ም ብላለች።

በሁኔታው ላይ ቀደም ሲል ኢትዮጵያን ጨምሮ በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት ተልዕኮ ውስጥ ወታደር ያዋጡ አገሮች ተደጋጋሚ ጥሪዎችና አስተያየቶች ትኩረት እንዳልተሰጣቸው አስገንዝባለች።

" የኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሠራዊት መልካም ስምና ዝናን እንዲሁም መስዋዕትነት የሚያጠለሹ ተከታታይ መግለጫዎች ሲወጡ ኢትዮጵያ በዝምታ እንድታልፍ ከአንዳንድ ወገኖች በኩል ፍላጎት መኖሩ ይታያል " ብላለች።

ሌሎች ተዋናዮች የአፍሪካ ቀንድ ክልልን ለማተራመስ እርምጃ ሲወስዱ ኢትዮጵያ በዝምታ እንደማትመለከት አሳውቃለች።

ይህም በመሆኑ በቀጣናው የብሄራዊ ደህንነቷን አደጋ ላይ ሊጥሉ የሚችሉ ሁኔታዎችን ሁሉ በንቃት እየተከታተለች እንደሆነም አመልክታለች።

የሶማሊያ መንግስት በቀጠናው ሰላም ለማስፈን የሚደረጉ ጥረቶች ከማጠናከር ይልቅ ቀጠናውን ለማተራመስ ከሚሹ የውጭ ኃይሎች ጋር እየሰራ እንደሚገኝ ኢትዮጵያ አጽንኦት ሰጥታ ገልጻለች።

በሶማሊያ ለማሰማራት የታቀደውን አዲስ የሰላም ተልዕኮ የማዘጋጀትና የመፍቀድ ኃላፊነት ያለባቸው አካላት ሁሉ በቀጠናው የሚገኙና ቀደም ሲል ወታደር አዋጭ የሆኑ አገራትን ተገቢ የሆኑ ስጋቶች ሁሉ ትኩረት ሊሰጡ ይገባል ብላለች።

ኢትዮጵያ ፥ " ለአጭር ጊዜ ፍላጎታቸውና ከንቱ አላማቸው ሲሉ በክልሉ ውጥረትን ለማቀጣጠል የሚሞክሩ ኃይሎች ዕኩይ ተግባራቸው የሚያስከትሏቸዉን መዘዞች መሸከም ይኖርባቸዋል " ብላለች።

ቀደም ሲል አህጉራዊና አለምአቀፋዊ አሸባሪ ቡድኖች ላይ የተገኘውን አበረታች ውጤት አደጋ ላይ የሚጥሉና የሚቀለብሱ ድርጊቶችን እንደማትታገስ ተናግራለች።

ኢትዮጵያ ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት እና ከሶማሊያ ህዝብና ከአለምአቀፉ ማህበረሰብ ጋር በመሆን በቀጠናው ሰላምና መረጋጋት ላይ የሚደርሱ አደጋዎችን ለመከላከል አሁንም ቁርጠኛ አቋም እንዳላት አመልክታለች።

#ኢትዮጵያ #Ethiopia🇪🇹

@tikvahethiopia

Tikvah ethiopia

29 Aug, 07:45


#Oromia : በኦሮሚያ ክልል ተፈርዶባቸው እስር ላይ የነበሩ 3,611 ታራሚዎች በይቅርታ ከእስር እንዲፈቱ መወሰኑን የክልሉ ጠቅላይ አቃቤ ህግ አሳውቋል።

247ቱ ሴቶች ናቸው።

የሞት ቅጣት ያለባቸው የህግ ታራሚዎች፤

ተደጋጋሚ ወንጀል የፈጸሙ

➡️ ሀሰተኛ ማስረጃ በማዘጋጀትና በማሰራጨት የተጠየቁ የህግ ታራሚዎችን ይቅርታው አያካትትም ተብሏል።

የይቅርታው መስፈርት ፦
° በማረሚያ ቤት ቆይታቸው የታረሙ
° ከተጎጂ ቤተሰብ ጋር የታረቁ
° የገንዘብ መቀጮ የከፈሉና ይቅርታ እንዲደረግላቸው የጠየቁ ናቸው ሲል ጠቅላይ አቃቤ ህግ አስረድቷል።

@tikvahethiopia

Tikvah ethiopia

29 Aug, 07:45


#Update
 
የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ከሚመራው የህወሓት ቡድን ጋር መወያየታቸው ተሰምቷል።

በህወሓት የማህበራዊ  የትሰስር ገፅ የተሰራጨው መረጃ እንዳለው ፤ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ዛሬ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አፈፃፀም ዙሪያና በክልሉ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ከድርጅቱ ሊቀመንበር እና ምክትል ሊቀመንበር (ማለትም በቅርቡ በተካሄደው ጉባኤ ከተመረጡት አቶ አማኑኤል አሰፋ) እና ሌሎች አመራሮች ጋር ተወያይቷል። 

አምባሳደሩ በውይይቱ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ሙሉ በሙሉ እንዲፈፀም አገራቸው አሜሪካ እንደምትደግፍ ተናግረዋል።

አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ትላንት " በህወሓት እና የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር መካከል ያለው ውጥረት እንዲረግብ " በማስመልከት ከጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜደንት አቶ ጌታቸው ረዳ ጋር መወያየታቸውን መዘገባችን ይታወቃል።

@tikvahethiopia

Tikvah ethiopia

29 Aug, 07:45


#Ethiopia " ሌሎች ተዋናዮች የአፍሪካ ቀንድ ክልልን ለማተራመስ እርምጃ ሲወስዱ በዝምታ አንመለከትም " - ኢትዮጵያ

@tikvahethiopia

Tikvah ethiopia

29 Aug, 07:45


#ETHIOPIA #GERD 🇪🇹

የታላቁ የሕዳሴ ግድብ መስሪያ ቤት ምን አለ ?

(ለፈረንሳይ ዜና አገልግሎት / አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ የሰጠው ቃል)

- በቅርቡ 2 የግድቡ ተጨማሪ ተርባይኖች አገልግሎት በመጀመራቸው ከግድቡ የሚመረተው የኤሌክትሪክ ኃይል መጠን ወደ 1 ሺሕ 550 ሜጋዋት ከፍ ብሏል።

- ከዚሕ ቀደም ብሎ ሥራ የጀመሩ ሁለት ተርባይኖች እያንዳዳቸዉ 375 ሜጋዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ያመነጫሉ።

- ከሰሞኑን የተመረቁት ሁለት ተጨማሪ ተርባይኖች እያንዳዳቸዉ 400 ሜጋዋት ኃይል ያመነጫሉ።

- ሙሉ በሙሉ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ከ5 ሺሕ ሜጋዋት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ያመነጫል።

- የግድቡ ግንባታ አሁን ወደ መጠናቀቁ ነው።

መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ከፍተኛ ዋጋ የከፈለበት እና ብዙ ቢሊዮን ዶላር ያፈሰሰበት ግድብ ከአፍሪቃ ትልቁ የኃይል ማመነጫ ነው።

ቪድዮ ፦ PM OFFICE

#Ethiopia #AFP

@tikvahethiopia

Tikvah ethiopia

29 Aug, 07:45


ሶማሊያ ?

ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ #ሶማሌላንድ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ከተፈራረመች ወዲህ ሶማሊያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት አሻክራለች።

የሀገሪቱ ፕሬዜዳንትም በየጊዜው በተለይ ወደ ግብፅ ሲመላለሱ ነው የከረሙት።

በቅርብ ደግሞ ግብፅ ሄደው ከፕሬዜዳንት አልሲሲ ጋር ወታደራዊ ስምምነት ፈጽመው ነው የመጡት።

ትላንት ደግሞ የጦር መሳሪያዎችን የጫኑ ሁለት የግብጽ የጦር አውሮፕላኖች በሞቃዲሾ ገብተዋል።

ጥይት እና የተለያዩ መሳሪያዎች ናቸው ተብሏል።

የዲፕሎማቲክ ምንጮች ግብፅ ለሶማሊያ ያደረገችው ወታደራዊ ድጋፍ ነው ብለዋል።

ግብፅ በሶማሊያ በሰላም ማስከበር ስም ወታደሮቿን ለማሰማራትም ጠይቃለች።

ቪድዮ፦ ሀሩን ማሩፍ

@tikvahethiopia

Tikvah ethiopia

29 Aug, 07:45


#ATTENTION🚨

ከ6 ሽህ በላይ ወገኖቻችን ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል።

በስልጤ ዞን ባሉ 2 ወረዳዎችና 8 ቀበሌዎች ከአንድ ሺህ በላይ አባዉራ ቤትና ማሳዉ በውሀ መዋጡን ተከትሎ ከአካባቢዉ መነሳታቸው ተሰምቷል።

እስካሁን ባለዉ መረጃ ከ6 ሺህ በላይ ሰዎች ድጋፍ እንደሚሹ የዞኑ የአደጋ ስጋት ኃላፊ ወሲላ አሰፋ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ጎርፉ የፈጠረዉን ሀይቅ በዚህ ወቅት ማፋሰስ አሰቸጋሪ መሆኑን ያነለከቱት ኃላፊዋ " የሁለቱን ወረዳ ነዋሪዎች በክልሉና በዞኑ ድጋፍና ትብብር አውጥተን በትምህርት ቤቶችና በአርሶ አደሩ የስልጠና መዕከላት አስፍረን ስላልበቃን ትርፍ ቤት ያለዉ ሁሉ ትርፍ ቤቱን በመስጠት በጊዜያዊነት ለማስጠለል ተሞክሯል " ብለዋል።

" የመሬቱ አቀማመጥና የጎርፉ ብዛት የፈጠረዉ የዉሀ መጠን ከፍተኛ በመሆኑ ዝናቡ እስኪቆም ዘላቂ መፍትሄ መስጠት አንችልም ፤ ይሁንና አንዳንድ ቦታ ላይ ቋሚ ሰብሎች እንዳይጎዱና ቤቶች እንዳይበሰብሱ አንዳንድ ስራዎች እየሰራን ነው " ሲሉ አክለዋል።

አሁን ላይ ለተጎጂዎች እየቀረበ ያለው የምግብ እና አልባሳት ድጋፍ በቂ ባለመሆኑ የዞኑ አደጋ ስጋት ምክር ቤት ተቋቁሞ ድጋፍ የሚሰበሰብበት መንገድ መመቻቹትን አመልክተዋል።

የስልጤ ዞን የጎርድ ድጋፍ ማሰባሰቢያ አካዉንት 1000647585535 (የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ) መሆኑ ተገልጿል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia

Tikvah ethiopia

29 Aug, 07:45


#FederalPolice

የፌዴራል ፖሊስ " በሽብር እና በሲቪል አቪየሽን ሕግ ጥሰት ወንጀል ጠርጥሬያቸዋለሁ " ብሎ በቁጥጥር ካዋላቸው መካከል ኤሊያስ ድሪባ በዳኔ የተባለው ተጠርጣሪ ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ ከ1989 ዓ ም ጀምሮ እሰከ 1999 ዓ ም በተለያዩ ከባድ ወንጀሎች ተከሶ ዳዊት ድሪባ በዳኔ በሚል ስም 3 ጊዜ የሞት ፍርድ የተፈረደበት ደጋጋሚ ወንጀለኛ መሆኑን ፖሊስ አስታውቋል።

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት  2ኛ ወንጀል ችሎት ታህሳስ 25 ቀን 1999 ዓ.ም በዋለው ችሎት ፦
- በዘረፋ፣
- በቅሚያ፣
- በሌብነት፣
- በቤት ሰብሮ  ስርቆት እና በደንብ መተላለፍ በዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበት ነበር።

ተጠርጣሪው ኤሊያስ ድሪባ በዳኔ ፣ ጀማል ኑሩ እና ዳዊት ድሪባ በዳኔ የሚሉ ስሞችን በመጠቀም ፦

➡️ 11 ጦር መሣሪያ መዝረፍ ወንጀል፣

➡️ 6 ቅምያ ወንጀል፣

➡️ 3 ሌብነት ወንጀሎች፣

➡️ 3 ሰው #መግደል ወንጀል፣

➡️ 2 ስርቆትና ቤት ሰብሮ ስርቆት ወንጀሎች፣

➡️ አንድ ሐሰተኛ ሰነድ መገልገል ወንጀል፣

➡️ ከእስር ማምለጥ ወንጀል

➡️ አንድ ደንብ መተላለፍ የወንጀል ሪከርድ በአጠቃላይ 28 የወንጀል ሪካርዶች እንዳሉበት ፖሊስ አመልክቷል።

ከዚህ ውስጥ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 2ኛ ወንጀል ችሎት መጋቢት 24 ቀን በዋለው ችሎት ስድስት መዝገቦችን ሦስት ጊዜ አጣምሮ  ሦስት ጊዜ በሞት እንዲቀጣ ውሳኔ ተላልፎበት ነበር።

እንደገና የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 2ኛ ወንጀል ችሎት ሚያዚያ 30 ቀን 2000 ዓ.ም በዋለው ችሎት በጦር መሣሪያ የታገዘ የዘረፋ፣ ከአስር ቤት የማምለጥና በሌብነት ወንጀል የዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት ቅጠት አስተላልፎበት ነበር።

ተጠርጣሪው በውሳኔው መሠረት ማረሚያ ቤት የገባው ይግባኝ ጠይቆ ሞት ፍርዱ ወደ እድሜ ልክ የተቀየረለት ቢሆንም በድጋሚ ይግባኝ በማለቱ ቅጣቱ ወደ 25 ዓመት ተቀንሶለት ለ17 ዓመታት በማረሚያ ቤት ከቆየ በኋላ #በይቅርታ መፈታቱን ከፖሊስ የምርመራ ማህደር ማረጋገጥ እንደተቻለ ተገልጿል።

#EthiopianFederalPolice

@tikvahethiopia

Tikvah ethiopia

29 Aug, 07:45


የNGAT ፈተና መቼ ይሰጣል ?

ትምህርት ሚኒስቴር ፥ የድህረምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ተጨማሪ የምዝገባ ጊዜ እና የፈተና ቀንን አሳውቋል።

በ2017 የትምህርት ዘመን የድህረምረቃ ፕሮግራሞች ለመማር ፍላጎት ያላቸው እና በተለያዩ ምክንያቶች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ምዝገባ ያመለጣቸው አመልካቾች እስከ ነሐሴ 26/2016 ዓ.ም ድረሰ በ https://ngat.ethernet.edu.et በኩል መመዝገብ ይችላሉ ብሏል።

ለፈተናው የተመዘገቡ በየተመደቡበት የፈተና ማዕከላት እና የመፈተኛ ፕሮግራም መሰረት ከነሐሴ 30 እስከ ጳጉሜን 1 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ፈተናው እንደሚሰጣቸው ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።

ተፈታኞች በፈተና ወቅት የተሰጣቸውን User Name and Password፣ እና ማንነታቸውን የሚገልጽ መታዋቂያ ይዘው መቅረብ እንዳለባቸው ማሳሰቢያ ተላልፏል።

#MoE

@tikvahethiopia

Tikvah ethiopia

29 Aug, 07:45


#ዮናታን_ቢቲ_ፈርኒቸር
Yonatan BT Furniture

በዓሉን ምክንያት በማድረግ በቤት እቃዎቻችን ላይ ከ10 እስከ 25% ቅናሽ ማድረጋችንን ስንገልጽ በታላቅ ደስታ ነው! 🌼🌼 ይምጡ እና ይጎብኙን በዕቃዎቻችን ጥራትና ጥንካሬ ይደመማሉ!

የውበት እና የጥራት ዳር ድንበር ዮናታን ቢቲ ፈርኒቸር!

አድራሻችን፦
1.ዊንጌት አደባባዩን ተሻግሮ: +251995272727
2.ፒያሳ እሪ በከንቱ : +251957868686
3.ሲ ኤም ሲ አደባባዩን አለፍ ብሎ: +251993828282

👉 Telegram
👉 Facebook
👉 Instagram
👉 TikTok

#yonatanbtfurniture #furniture #modernfurniture #sofa #diningtable