Dernières publications de የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia (@ministryofindustry) sur Telegram

Publications du canal የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia ቴሌግራም ቻናል ነው፡፡
የኢፊዴሪ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴርን የተመለከቱ መረጃዎችን
• ዜናዎች
• ሁነቶች
• የተለየያዩ ለአምራች ኢንዱስትሪ ማህበረሰብና ስለ ተቋሙ መረጃ የሚያገኝበት ቻናል ነው፡፡
https://t.me/+P0HOYJNw-wgyMmNk ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉ፡፡
10,024 abonnés
5,606 photos
143 vidéos
Dernière mise à jour 11.03.2025 07:50

Le dernier contenu partagé par የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia sur Telegram

የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

06 Dec, 10:39

959

የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታረቀኝ ቡሉልታ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ ጋር ከዉጭ ሀገር የሚገቡ የህክምና ግብዓቶችን በሀገር ውስጥ ምርቶች መተካት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተወያዩ
======================================
ህዳር 27/2017 ዓ.ም (ኢሚ) የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታረቀኝ ቡሉልታ ከጤና ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ ጋር የሀገር ውስጥ የህክምና ግብዓት በተለይም የህክምና ጎዝ፣ ባንዴጅ፣ እስዋብ እና ጥጦችን ሀገራዊ ፍላጎቶች እና የሀገር ውስጥ የማምረት አቅምን የሚያሳይ የዳሰሳ ጥናት ዉጤት መነሻ በማድረግ ግብዓቶቹን ሙሉ በሙሉ በሀገር ዉስጥ ምርቶች መተካት በሚቻልበት ሁኔታ ተወያይተዋል፡፡

የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታረቀኝ ቡሉልታ የሀገር ውስጥ ምርት መበረታታት ከአቅርቦት በተጨማሪ የስራ ዕድል እና ዘላቂ ኢኮኖሚ የሚፈጥር በመሆኑ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባዋል ብለዋል።

በመሆኑም ተግዳሮቶችን ለመፍታትና በቀጣይ ሌሎች ከውጪ የሚገዙ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርቶች ለመተካት ቅንጅታዊ አሰራር በማጠናከር አምራቶች በአቅማቸዉ ልክ እንዲያመርቱ ለማደረግ በተሰራዉ ጥናት መሠረት ተገቢዉ ድጋፍና ክትትል ስርዓት መዘርጋት እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡

የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ በበኩላቸዉ እስካሁን ይሰራበት የነበረውን የውጪ ግዥ የሚያበረታታ አሰራርን በመተካት የሀገር ውስጥ ምርት ግዥ የሚያበረታታ ስረዓት በመዘርጋት የዉጭ ጥገኝነትን መቀነስና መንግስትን የያዘዉን "ኢትዮጵያ ታምርትን" አላማ በማሳካት ለኢትዮጵያ ብልፅግና የበኩላችን መወጣት ጊዜ የማይሰጥ ጉዳይ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል፡፡

አክለዉም የህክምና ግብዓት ጥራቱን የጠበቀ እና የህብረተሰቡን የመግዛት አቅም ያገናዘበ እንዲሆን ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅርበት እንደሚሰሩ በማብራራት ጥራት ያለውና የህብረተሰቡን የመግዛት አቅም ያገናዘበ ምርት እንዲያቀርቡ ከሀገር ውስጥ አምራቾች ጋር በቅርበት ይሰራል ብለዋል።

በውይይቱ ማጠቃለያ ከላይ የተዘረዘሩ ግብዓቶች የሀገር ዉስጥ ፍላጎትን በሀገር ዉስጥ ምርት ብቻ መሸፈን እንደሚቻል ሁለቱ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች በመስማማት አፈፃፀሙን እንዲከታተሉ ከሁለቱም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች የተውጣጡ የባለሙያዎች ቡድን ተዋቅሯል።
#ኢትዮጵያ_ታምርት
#እኛም_እንሸምት
http://linktr.ee/fdremoi
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

05 Dec, 12:03

1,182

Yesterday , president Putin was Witnessing the development miracle happening in Ethiopia on the Russian Calling : Investment forum
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

05 Dec, 12:01

964

የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እና የአምራች ከአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት 19ኛውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ብሄረሰቦችና ህዝቦችን ቀን በዓል አከበሩ
==================================
ህዳር 26/2017 ዓ.ም (ኢሚ) 19ኛዉ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን "ሀገራዊ መግባባት ለህብረ-ብሄራዊ አንድነት'' በሚል መሪ ቃል የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እና ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት አመራሮችና ሰራተኞች በድምቀት አከበሩ ፡፡

የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሚልኬሳ ጃገማ (ዶ/ር) የብሔር ብሄረሰቦችና ህዝቦችን ቀን ስናከብር ኢትዮጵያ የብዙ ብሔሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ሃገር ናት ፣በ21ኛው ክፍለ ዘመን እያንዳንዳችን ሃገራችንን መውደድ መጠበቅና በየተሰማራንበት የስራ መስክ በታማኝት ሃለፊነታችንን መወጣት አለብን ሲሉ ገልፀዋል ፡፡

ወደፊት ለመራመድ፣ ለአገራዊ መግባባት እና ለህብረብሄራዊ አንድነት መጠናከር በዓሉ ትልቅ አስተዋፆዖ አለው ብለዋል ፡፡

የብሔር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን አስመልክቶ ስለ ህገመንግስት፤ ዲሞክራሲዊነት እንዲሁም ፊደራሊዝም አተገባበር ላይ የፓናል ውይይት ተደርጓል ፡፡

1987 ዓ.ም የኢፊዴሪ ህገ መንግስት የፀደቀበትን ቀን ምክንያት በማድረግ በየዓመቱ ህዳር 29 ቀን የኢትዮጵያ ብሔር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን ይከበራል ፡፡
#ኢትዮጵያ_ታምርት
#እኛም_እንሸምት
http://linktr.ee/fdremoi
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

19 Nov, 09:27

1,101

በኢንዱስትሪ የዘርፍ ማህበራት አደረጃጀትና መመሪያ ዙርያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ ነው።
=============================
ህዳር 10/2017 ዓ.ም (ኢሚ) የኢፌዴሪ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ለክልልና ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪ ቢሮ ምክትል ኃላፊዎች፣ ለኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ኃላፊዎች እንዲሁም ዘርፉ ለሚመለከታቸው ባለሙያዎች በኢንዱስትሪ የዘርፍ ማህበራት አደረጃጀትና መመሪያ ዙርያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ ነው።

የዘርፍ ማህበራት የመተዳደሪያ ደንብ አዘገጃጀት፣ የምህንድስና ባለሙያዎችና የኢንዱስትሪ ተቋማት የብቃት ማረጋገጫ ስርተፊኬት አሰጣጥ መመሪያ ቁጥር 527/2013፣ የንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ 341/1995 እና በዘርፍ፣ የሙያ ማህበራትና የዘርፍ ማህበራት ም/ቤቶች አደረጃጀትና ድጋፍ አሰጣጥ መመሪያ ቁጥር 2/2007 ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ይሰጥባቸዋል ተብሎ ይጠበቃል።

#ኢትዮጵያ_ታምርት
#እኛም_እንሸምት
http://linktr.ee/fdremoi
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

19 Nov, 08:16

895

ኢትዮጵያ በጥጥ፣ በቆዳና በብረት ማዕድን ሀብት የበለፀገች ሀገር ናት። (አቶ መላኩ አለበል)
=====================================
ህዳር 10/2017 ዓ.ም (ኢሚ) የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል በኢትዮጵያ ጂሗ ግሩፕ (Jihua Group) በወታደራዊ ልብስ፤ ጫማ፤ ኮፍያ፤ የጥይት መከላከያ ኢንዱስትሪ ዘርፍ መሰማራት ፍላጎት ካላቸው ቻይና የባለሀብቶች ልዑክ ጋር ተወያዩ ።

በኢትዮጵያ ሰፊ አምራች ኃይል፣ ምቹ የኢንቨሰትመንት ፖሊሲ፣ ለስራ ዝግጁ የሆኑ የኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ የታክስ እፎይታ፣ ከቀረጥ ነፃ እድሎች እና መሰል ለኢንቨስትመንት የተመቻቹ የአሰራር ስርዓቶች መኖራቸውን ለልዑክ ቡድኑ የገለፁት ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ በጥጥ፣ በቆዳና ብረት ማዕድን አሰፈላጊ በሆነ ጥሬ ሀብት የበለፀገች ሀገር መሆኗን አስረድተዋል ።

ኢትዮጵያ 120 ሚሊየን ሕዝብ ተሰማሚ የሆነ የአየር ንብርት የትልቅ የገበያ እድል ያላት ሃገር ናት ፡፡

በተጨማሪም ኢትዮጵያ ወደ ተለያዩ አፍሪካ ገበያ ለመግባት የመልክዓምድር አቀማመጥ፤ የአፍሪካ ነፃ ገበያ ዕድል ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ በሰፊው ተደራሽ መሆኑ፤ አዲስ አበባ የአለማቀፍ ማህበረሰቡ መኖሪያ መሆኗ ለኢንዱስትሪ ዘርፉ ምቹ የገበያ እድል የሚፈጥር መሆኑን አብራርተዋል ።

ኢትዮጵያና ቻይና በኢኮኖሚ በማህበራዊ በትምህርት እንዲሁም በብሪክስ ጥምረት ዘርፍ ብዙ ግንኙነት ያላቸው ሃገራት እንደ መሆናቸው ወደ ስራ ስትገቡ የሚያጋጥማችሁን ችግሮች በመፍታት በስራችሁ ስኬታማ እንድትሆኑ ለማገዝ ዝግጁ ነን ሲሉ ገልፀዋል፡፡

ጂሗ ግሩፕ (Jihua Group) ለቻይና መከላከያ 60% የሚሊቴሪ አላባሳት፤ መጫሜዎች፤ ኮፍያ ፤የጥይት፤ መከላከያ አቅራቢ መሆኑ ታውቋል ፡፡

ባለሀብቶቹ በበኩላቸው ስለተደረገላቸው አቀባበል አመስግነው በኢትዮጵያ ባለው የኢንቨስትመንት እድል እንደሚጠቀሙ ገልፀዋል።

#ኢትዮጵያ_ታምርት
#እኛም_እንሸምት
http://linktr.ee/fdremoi
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

18 Nov, 17:18

1,025

ኢትዮጵያ አምራች ኢንዱስትሪውን ዘላቂ፣ ለአከባቢ ተስማሚ እና አካታች እንዲሆን እያደረገች ያለውን ተሞክሮ አቀረበች
=============================
ህዳር 9/2017 ዓ.ም (ኢሚ) በአዘር ባጃን ባኩ እየተካሄደ ባለው COP29 ላይ ኢትዮጵያ አምራች ኢንዱስትሪውን ዘላቂ፣ ለአከባቢ ተስማሚ እና አካታች እንዲሆን እያደረገች ያለውን ተሞክሮ አቀረበች፡፡

ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አምራች ኢንዱስትሪውን ዘላቂ፣ ለአከባቢ ተስማሚ እና አካታች እንዲሆን እያደረገች ያለውን ተሞክሮ ከማቅረብ በተጨማሪ በሀገር ደረጃ የሰርኩላር ኢኮኖሚን ለመተግበር ምቹ ሁኔታን ለመፍጠርና በኢንዱስትሪ ዘርፍ ያሉ ዘመናዊ አሰራሮችን በተመለከተም ከዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር የአቻ ለአቻ ውይይትም ተካሄዷል፡፡

በውይይቱ የሀይል ብክነትን ማሻሻል፣አማራጭ የሀይል ምንጭን ማልማትን በተመለከተና ዝቅተኛ የካርበን መጠን ያላቸውን ጥሬ ዕቃዎች እንዴት መጠቀም እንደ ሚቻል በስፋት መብራራቱን ሚኒስቴር መስሪያቤቱን ወክለው መርሀ ግብሩን የተሳተፉት የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የአየር ንብረት ለውጥ ፐርፎርማንስ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ አቶ ዳዊት አለሙ ገልጸዋል፡፡

አቶ ዳዊት ዓለሙ አለም አቀፍ ድርጅቶች በኢትዮጵያ አካባቢን የማይበክሉ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ለመገንባት የገንዘብ፣የቴክኖሎጅና የቴክኒክ ድጋፍ የሚያደርጉበትን ሁኔታም በተመለከተ መወያየታቸውን ተናግረዋል፡፡

#ኢትዮጵያ_ታምርት
#እኛም_እንሸምት
http://linktr.ee/fdremoi
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

08 Nov, 16:31

644

10ኛው የአፍሪካ ጨርቃ ጨርቅ እና ፋሽን ሳምንት (ASFW) ተከፈተ፡፡
======================================
ጥቅምት 29/2017 ዓ.ም (ኢሚ) ከ30 ሀገራት የተውጣጡ የጨርቃ ጨርቅ እና ቆዳ ኢንዱስትሪዎች በአፍሪካ ሶርሲንግ ፋሽን ሳምንት (ASFW) ከዛሬ ጥቅምት 29 እስከ ህዳር 2 /2017 ዓ.ም እንደሚካሄድ ተገልጿል ፡፡

የፋሽን ሳምንቱ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚንስቲር አቶ መላኩ አለበል እና የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ሳላማዊት ካሳ እና  ሌሎች በርካታ እንግዶች በተገኙበት ተከፍቷል፡፡

ሚኒስትሩ አቶ መላኩ እንዳሉት አፍሪካ በተፈጥሮ ሃብት የበለፀገች እና ትልቅ አምራች ሃይል ያለባት እንደመሆኗ አሁን ያለችበት ድህነት የማይገባት ነው ብለዋል ፡፡

ሚኒስትሩ አክለውም አፍሪካን ለመቀየር አመራር እና ተቋምን መገንባት ይገባናልም ብለዋል፡፡

ከሁለት አመት በፊት በጀመር ነው ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በጨርቃ ጨርቅ፣ በቆዳ ዘርፍ እና በኢንዱስትሪ ውጤቶች ተስፋ ሰጪ ለውጥ እየተመዘገበ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በዝግጅቱ ከ60 በላይ ሀገራት የሚመጡ ከ7 ሺህ በላይ የንግድ ትስስሩን የሚያሳልጡ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል ።

በጨርቃጨርቅና ቆዳ ፋሽን  ሳምንቱ ልምድና ተሞክሮ የሚቀሰምባቸው  የዘርፉን ችግሮች መፍታት ላይ ያተኮሩ ኮንፈረንሶችና የፓናል ውይይቶች እንደሚኖሩም ይጠበቃል ።

የአፍሪካ ሶርሲንግና ፋሽን ሳምንት በ10 አመት ቆይታው ከ50 ሺህ በላይ አዳዲስ ሥራዎችን መፍጠር የቻለ መሆኑም ተገልጿል።

#ኢትዮጵያ_ታምርት
#እኛም_እንሸምት
http://linktr.ee/fdremoi
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

08 Nov, 09:33

764

በ "ከረሃብ ነፃ ዓለም" ጉባኤ ላይ ተሳታፊ የነበሩ መሪዎች ወደ ሀገራቸው ተመለሱ
====================
ጥቅምት 29/2017 ዓ.ም (ኢሚ) ባለፉት ቀናት በአዲስ አበባ በተካሄደው "ከረሃብ ነፃ ዓለም" ጉባኤ ላይ ተካፍለው የነበሩ የተለያዩ ሀገራት መሪዎች ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።

#ኢትዮጵያ_ታምርት
#እኛም_እንሸምት
http://linktr.ee/fdremoi
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

08 Nov, 07:09

779

ከረሃብ ነጻ ዓለም ጉባኤን አስመልክቶ ከኢንዱሰትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ጋር የተደረገ ቆይታ
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

08 Nov, 06:22

803

World Without Hunger Conference