Dernières publications de የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia (@ministryofindustry) sur Telegram

Publications du canal የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia ቴሌግራም ቻናል ነው፡፡
የኢፊዴሪ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴርን የተመለከቱ መረጃዎችን
• ዜናዎች
• ሁነቶች
• የተለየያዩ ለአምራች ኢንዱስትሪ ማህበረሰብና ስለ ተቋሙ መረጃ የሚያገኝበት ቻናል ነው፡፡
https://t.me/+P0HOYJNw-wgyMmNk ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉ፡፡
10,024 abonnés
5,606 photos
143 vidéos
Dernière mise à jour 11.03.2025 07:50

Le dernier contenu partagé par የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia sur Telegram

የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

27 Jan, 05:12

1,982

በአምራች ኢንዱስትሪዎች መካከል ጠንካራ የእሴት ሰንሰለት መኖር ለአቅም አጠቃቀም መሻሻል ወሳኝ ነው (አቶ መሳይነህ ውብሸት)
===========================
ጥር 19/2017 ዓ.ም (ኢሚ) በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የተኪ ምርቶች ተወዳዳሪነት ስራ አስፈፃሚ ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ፣ ተጠሪ ተቀማትና ለአምራች ኢንዱስትሪ ባለሙያዎች ከጥር15/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ ሶስት ቀናት የአምራች ኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም ማሻሻልን በተመለከተና በዕሴት ሰንሰለት ዙሪያ የሰጠውን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና አጠናቋል፡፡

በማጠናቀቂያ መርሀ ግብሩ ተገኝተው ንግግር ያደረገጉት የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተኪ ምርቶች ተወዳዳሪነት መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ መሳይነህ ውብሸት የአምራች ኢንዱስትሪዎችን ውስጣዊ ችግር በመፍታት የመንግስትን ጥረት ልናግዝ ይገባል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

አቶ መሳይ አምራች ኢንዱስትሪዎች ትርፋማ ሆነው ከሌሎች ሀገራት ጋር ተወዳዳሪ እንዲሆኑ በመካከላቸው የዕሴት ሰንሰለት እንዲኖር በትኩረት መሰራት እንዳለበትና በቀጣይም የአምራች ኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም የሚያጎለብቱ ተመሳሳይ ስልጠናዎች እንደሚሰጡ አክለዋል፡፡

የስልጠናው ዋና ዓላማ ሰልጣኞች ጥሩ የኢንዱስትሪ አመራር ክህሎት ኑሯቸው አምራች ኢንዱስትሪዎች ደረጃውን የጠበቀና ጥራት ያለው ምርት እንዲያመርቱ የራሳቸውን ሚና እንዲጫወቱ ማስቻል እንደሆነ ከስልጠናው ይዘት ማወቅ ተችሏል፡፡

በስልጠናው መሰረታዊ የአምራች ኢንዱስትሪ አመራር ክህሎት፣ የኢንዱስትሪዎች ማምረት አቅም የሚሻሻልበት ዘዴ፣ በኢንዱስትሪዎች መካከል የዕሴት ሰንሰለት መፍጠርን በተመለከተና የዕሴት ሰንሰለትን እንዴት መጠቀም እንደሚቻል ተብራርቷል፡፡

#ኢትዮጵያ_ታምርት
#እኛም_እንሸምት
http://linktr.ee/fdremoi
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

24 Jan, 11:35

1,563

ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ለተስፋ አዲስ ፓረንትስ ቻይልድ ሁድ ካንሰር ድርጅት የልብስ ስፌት መኪና ድጋፍ አደረገ ፡፡
==============================
ጥር 16/2017 ዓ.ም (ኢሚ) የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በተጠሪ ተቋሙ በጨርቃ ጨርቅ ኢዱስትሪና አልባሳት ምርምር ልማት ማእከል አማካይነት ለተስፋ አዲስ ፓረንትስ ቻይልድ ሁድ ካንሰር ድርጅት የልብስ ስፌት መኪና ድጋፍ አደረገ ፡፡

ድጋፉን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የሚኒስትር ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀዱሽ አለፎም ለድርጅቱ ስራ አስኪያጅ ወ/ት ሳራ ኢብራሂም አስረክበዋል ፡፡

የተቋሙ ድጋፉ ይህ ለሶስተኛ ዙር ሲሆን ከአሁን ቀደም በገንዘብ በጨርቃ ጨርቅ በሌሎች ቁሳቁሶች ድጋፍ ማድረጋቸው ይታወሳል ፡፡

ወደፊት በተስፋ አዲስ ፓረንትስ ቻይልድ ሁድ ካንሰር ድርጅት ልጆቻቸውን እያስታመሙ ለሚገኙ ወላጆች የልብስ ስፌት መኪና ስልጠና እንደሚሰጥ ቃል ገብተዋል፡፡

ተስፋ አዲስ ፓረንትስ ቻይልድ ሁድ ካንሰር ድርጅት ማንኛውንም በካንሰር የተያዙ ልጆች ተገቢውን ህክምናና እንክብካቤ አግኝተው ከካንሰር ነፃ የሆነ ሕይወት እንዲመሩ ድጋፍ የሚያደርግ ግብረ ሰናይ ድርጅት ነው ፡፡

የተስፋ አዲስ ፓረንትስ ቻይልድ ሁድ ካንሰር ድርጅት ስራ አስኪጅ ወ/ት ሳራ ኢብራሂም ህፃናትን መደገፍ ለነገ ሃገር ተረካቢ ማዘጋጀት በመሆኑ ሰብአዊነት ብቻ ሳይሆን ግዴታም ጭምር መሆኑን በመግለፅ ስለተደረገላቸው ድጋፍ አመስግነዋል ፡፡

#ኢትዮጵያ_ታምርት
#እኛም_እንሸምት
http://linktr.ee/fdremoi
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

10 Jan, 19:42

2,672

የጥራት መንደርን የመጎብኘት መርሀ ግብር ተካሄደ
==============================
ጥር 2/2017 ዓ.ም (ኢሚ) የኢንዱስትሪ ሚኒስቴርና በስሩ ያሉ ተጠሪ ተቋማት የስራ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች በጥራት መንደር ውስጥ የሚገኙ ተቋማትን አሰራርና በውስጣቸው ያሉ ዘመናዊ የመስሪያ ቁሳቁሶችን ጎብኝተዋል፡፡

በጥራት መንደር ውስጥ የተስማሚነትና ምዘና ድርጅት፣ የኢትዮጵያ ጥራት ደረጃዎች ኢንስቲትዩት፣የኢትዮጵያ ስነ-ልክ ኢንስቲትዩት፣ የኢትዮጵያ ኢነርጅ ባለስልጣንና የኢትዮጵያ አክሪዲኬሽን አገልግሎት የሚገኙ ሲሆን አምስቱ የጥራት መሰረተ ልማት ተቋማት በአንድ ቦታ መደራጀታቸው ብሔራዊ የምርት ጥራትን ለማስጠበቅ እንደ ሚረዳ በአስጎብኝዎች ተገልጿል፡፡

በመጨረሻም ተቋማቱ በዚህ መልኩ የተደራጁት በሀገር አቀፍ ደረጃ የኢንዱስትሪያላይዜሽን መሰረት እንዲሆኑ ታስቦ እንደ መሆኑ መጠን የጉብኝቱ ተሳታፊዎች የኢንዱስትሪያላይዜሽንን ፅንሰ ሀሳብ ለሌላው ማህበረሰብ የማስተዋወቅ ሀላፊነታቸውን መወጣት እንዳለባቸው የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ደኤታ ክቡር አቶ እንዳለ መኮንን መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

#ኢትዮጵያ_ታምርት
#እኛም_እንሸምት
http://linktr.ee/fdremoi
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

06 Jan, 08:35

2,326

ታህሳስ 28/2017 ዓ.ም (ኢሚ) የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች የተቋሙን አመራሮች እና ሰራተኞች እንኳን አደረሳችሁ ሲሉ
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

06 Jan, 08:34

1,221

ታህሳስ 28/2017 ዓ.ም (ኢሚ) የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች የተቋሙን አመራሮች እና ሰራተኞች እንኳን አደረሳችሁ ሲሉ
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

06 Jan, 08:34

527

ታህሳስ 28/2017 ዓ.ም (ኢሚ) የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች የተቋሙን አመራሮች እና ሰራተኞች እንኳን አደረሳችሁ ሲሉ
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

03 Jan, 14:53

763

የአምራች ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም አጠቃቀም ከፍ ብሏል ( አቶ ጥላሁን አባይ)
==========================
ታህሳስ 25/2017 ዓ.ም (ኢሚ) የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት የዕቅድ አፈፃፀሙን ከአጠቃላይ አመራርና ሰራተኞቹ ጋር ውይይት ባደረገበት ወቅት የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርቱን ያቀረቡት በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈፃሚ አቶ ጥላሁን አባይ እንደገለፁት መንግስት ለዘርፉ በተሰጠው ልዩ ትኩረት፣ በተሰሩ ቅንጅታዊ ስራዎችና ድጋፎች የአምራች ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም አጠቃቀም የተሻለ አፈፃፅም ማስመዝገብ መቻሉን ገልፀዋል ።

አቶ ጥላሁን አክለውም አፈፃፀሙ ከ2016 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት አፈፃፀም ጋር ሲነፃፀር ከፍ ያለ መሆኑን ጠቁመዋል ።

#ኢትዮጵያ_ታምርት
#እኛም_እንሸምት
http://linktr.ee/fdremoi
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

03 Jan, 14:40

677

ቀልጣፋና ተደራሽ የአሰራር ስርዓት መዘርጋት ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት ማደግ ከፍተኛ ሚና አለው፡፡ (አቶ ታረቀኝ ቡሉልታ)
===============================
ታህሳስ 25/2017 ዓ.ም (ኢሚ) ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አጠቃላይ ሰራተኞች የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ውይይት ላይ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የዕድገትና ተወዳዳሪነት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታረቀኝ ቡሉልታ አምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ በኢኮኖሚው ዕድገት ውስጥ የሚጠበቅበትን ሀገራዊ ድርሻ እንዲወጣና ጉልህ ሚና እንዲኖረው ለማድረግና የማምረት አቅምን ለማሳደግ አቅም አጠቃቀም የአለካክ ስልቶች የጋራ ግንዛቤ በሁሉም ደረጃ መፍጠር ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

የአምራች ኢንዱስትሪዎችን ከአቅም አጠቃቀም ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን የመለየት እና አቅም አጠቃቀምን ለማሳደግ የሚያስችሉ አሰራሮችን መዘርጋት ለአምራች ኢንዱስትሪ የምርት ማደግ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ገልፀዋል፡፡

#ኢትዮጵያ_ታምርት
#እኛም_እንሸምት
http://linktr.ee/fdremoi
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

03 Jan, 12:37

709

ከተቋማት ጋር የተጀመረው የቅንጅት ስራ ለአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ውጤት እያመጣ መሆኑ ተገለፀ፡፡ (አቶ ሀሰን መሀመድ)
==============================
ታህሳስ 25/2017 ዓ.ም (ኢሚ) ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አጠቃላይ ሰራተኞች የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ውይይት ላይ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሀሰን መሀመድ የአምራች ኢንዱስትሪውን በተሻለ ሁኔታ ለማስፋፋት የግብአት አቅርቦት ችግር ፣ የመሰረተ ልማት ችግሮችን ለመፍታ ከተቋማት ጋር የተጀመረው የቅንጅት ስራ ለዘርፉ ውጤት እያመጣ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በተለይም ዘርፉ በደላላ ተጠልፎ የነበረውን የግብዓት አቅርቦት ሰንሰልት ለማስተካከል የአሰራር ስርዓት የማስተካከል ስራዎች በመስራት ችግሩን በማቃለል የአምራች ኢንዱስትሪ ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የጀመርናቸው ተግባራት ችግር ፈቺ በመሆናቸው አጠናክረን መቀጠል ያስፈልጋል ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው የዘርፉን የማሳደግ አቅምና መልካም አጋጣሚዎች አሟጦ ለመጠቀም እና ከዘርፉ ተለዋዋጭ ባህሪያት በመረዳት ለውጥ ማምጣት ኢንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡

#ኢትዮጵያ_ታምርት
#እኛም_እንሸምት
http://linktr.ee/fdremoi
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

03 Jan, 08:56

800

አምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ ተስፋ ሰጪ ስኬቶች አስመዝግቧል።
==========================
ታህሳስ 25/2017 ዓ.ም (ኢሚ) የኢፌዴሪ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በ2017 በጀት የመጀመሪያ ስድስት ወራት ዋና ዋና በሆኑ የስራ ማሳያዎች እንደ ውጭ ምንዛሬ ግኝት፣ ተኪ ምርት፣ የአቅም አጠቃቀም፣ የግብዓት አቅርቦትና ሌሎች የዘርፉ ስራዎች ተስፋ ሰጪ ስኬቶች መመዝገባቸውን ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ገልፀዋል።

ሚኒስትሩ አክለውም ዘርፉ የሚመለከታቸው ሚኒስትሮችንና ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎችን ያካተተ የአምራች ኢንዱስትሪ ብሔራዊ ካውንስል ተቋቁሞ ወደ ስራ በመግባቱ በዘርፉ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በቋሚነት በየሁለት ሳምንቱ እየተገናኘ በመወያየት የተለዩ ችግሮች ለሚመለከተው ተቋም አፋጣኝ መፍትሔ እንዲያስቀምጥ በማድረግ እየተሰራ በመሆኑ የዘርፉ እድገት ተስፋ ሰጪ መሆኑን ገልፀዋል።

ሁሉም አመራርና ሰራተኛ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራት የተመዘገቡ ስኬቶችን አጠናክሮ በማስቀጠልና ጉድለት የታየባቸውን ስራዎች አስተካክሎ በበጀት ዓመቱ መጨረሻ የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ በቁርጠኝነት ርብርብ ማድረግ እንደሚጠበቅ አሳስበዋል።

ሚኒስቴሩ ከአጠቃላይ አመራርና ሰራተኞቹ ጋር የ2017 በጀት የመጀመሪያ ስድስት ወራት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ውይይት እያደረገ ነው።

#ኢትዮጵያ_ታምርት
#እኛም_እንሸምት
http://linktr.ee/fdremoi