Neueste Beiträge von የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia (@ministryofindustry) auf Telegram

የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia Telegram-Beiträge

የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia ቴሌግራም ቻናል ነው፡፡
የኢፊዴሪ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴርን የተመለከቱ መረጃዎችን
• ዜናዎች
• ሁነቶች
• የተለየያዩ ለአምራች ኢንዱስትሪ ማህበረሰብና ስለ ተቋሙ መረጃ የሚያገኝበት ቻናል ነው፡፡
https://t.me/+P0HOYJNw-wgyMmNk ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉ፡፡
10,024 Abonnenten
5,606 Fotos
143 Videos
Zuletzt aktualisiert 11.03.2025 07:50

Der neueste Inhalt, der von የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia auf Telegram geteilt wurde.

የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

20 Feb, 18:27

214

ዘላቂና አካታች ኢኮኖሚ ለመገንባት ለአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ ትኩረት መስጠት ግዴታ ነው (አቶ መላኩ አለበል)
=======================================
የካቲት 13/2017 ዓ.ም (ኢሚ) በኢትዮጵያ ታምርት 2017 ዓ.ም ኤክስፖ የማስጀመሪያ መርሐ ግብር ላይ በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉት የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ዓለማችን ከአራተኛው የኢንዱስትሪ አብዮት ወደ አምስተኛው እየተንደረደረች በመሆኑ ከወትሮው በተለየ ሁኔታ ሰዎችና ማሽን ተሰናስለውና ተቀናጅተው የሚያመርቱበት የምርት ስልት እየተገነባ ነው ብዋል።

በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ምክንያት ኢንዱስትሪ የላቀ ለውጥ እያሳየ ያለበት ዓለም ላይ ነን ያሉት አቶ መላኩ የሮቦቲክስ፣ አርተፊሻል ኢንተለጀንስ፣ ዓለማቀፍ የኢንተርኔት ትስስር ኢንዱስትሪን ወደ አዲስ ምዕራፍ እያሽጋገረ በመሆኑ ይህ ለውጥ የምርት ሂደትን የበለጠ ውጤታማ፣ ፈጣንና በተመጣጣኝ ወጭ ለማምረት በማስቻል ዓለም ወደ አዲስ የኢኮኖሚ ዘመን እያመራች እንደሆነም ማረጋገጥ መቻሉን በመጠቆም በመጪው ዘመንም ይበልጥ እየረቀቀና እየዘመነ እንደሚሄድ ይጠበቃል።

የሀገራት የቀደምት ስልጣኔ መለያ የሆኑት በግብርና እና በምግብ ማምረት፣ በጽህፈት፣ በስነ ህንፃና የምህንድስና፣ በሂሳብና የሳይንስ፣ በፖለቲካና የማኀበራዊ ስርዓቶች፣ በንግድና የኢኮኖሚ፣ በሃይማኖት እና የፍልስፍና፣ የውጭ ጠላትን በመከላከልና ድንበርን በማስከበር፣ በባህልና በኪነጥበብ ኢትዮጵያን ከቀዳሚ የዓለም ሃገራት ተርታ የሚያሰልፍ የሰው ልጅን ታሪክ፣ ባህልና ዕድገት የሆኑት የስልጣኔ ማሳያዎች ቀደምት ባለቤቶች ብንሆንም እንደ አጀማመራችን የአመራረት ስርዓታችንን ማዘመን ባለመቻላችን ግብርናችን ከበሬ፣ ኪነ ህንፃችን ከላሊበላ፣ ሂሳብና ሳይንሳችን ከቀንና ከኮከብ ቆጠራ እና ፖለቲካችን ልዩነት ማስፊያነት ያለፈ ለውጥ የሚያመጣ ማድረግ አለመቻላችንን ገልፀዋል ::

ዘላቂና አካታች ኢኮኖሚ ለመገንባት ለአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ ትኩረት መስጠት ግዴታ በመሆኑ መንግስት የቅድሚያ ትኩረት ከሰጣቸው አምስት ዘርፎች መካከል የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ ቀዳሚ ነው ያሉት ሚኒስትሩ ዘመናዊነትን ያልተከተለውን የአሰራር ስርዓታችንን በመቀየር ኢትዮጵያን የአፍሪካ የብልፅግና ተምሳሌት እናደርጋለን ስንል የትናንት ታሪካችንን በመልካም መነሻነት ተጠቅመን ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ አካተን ምርትና ምርታማነትን አሳድገን በሰለጠነ የፖለቲካ ባህል ልዩነቶቻችን በውይይት ፈተን እንደምናሳካው በማሰብ ነው ብለዋል፡፡

በ2014 ዓ.ም የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን ስንጀምር ሰፊ ገበያ፣ አማራጭ ግብዓት፣ አስተማማኝ የሃይል ምንጭ፣ ፈጥኖ ሰልጣኝ ጉልበት ከዲጂታል ዘመን ጋር ተደምሮ ኢንዱስትሪን በማስፋፋት የዘመናት ስብራታችን እንደሚጠገን በመተማመን ነው፡፡

እንደ ሀገር የጀመርነው የኢኮኖሚ ሪፎርም ማሻሻያ ፣ አምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍን ለመደገፍ የተቋቋመው ካውንስል፣ የመንግሥትን አገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል የተጀመሩ ሪፎርሞች፣ በክልል ደረጃ የተጀመሩ የኢትዮጵያ ታምርት ስቲሪንግ ኮሚቴ ስራዎች፣ ውድድርን የሚገቱ ህጎችንና አሰራሮችን ለማሻሻል በየተቋሙ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች የኢትዮጵያ ታምርት ስራን ውጤታማ እንዲሆን ያደረጉ ተስፋ ሰጭና ሁኔታ ቀያሪ ተግባራት ናቸው፡፡

የ2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ከሚያዚያ 29/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ 7 ቀናት የሚከናወን መሆኑን የጠቀሱት አቶ መላኩ ለኤክስፖው ስኬታማነት ሁሉም ባለድርሻ አካል የበኩሉን አዎንታዊ አስተዋፅኦ እንዲያበረክት አሳስበዋል ።

#ኢትዮጵያ_ታምርት
#እኛም_እንሸምት
http://linktr.ee/fdremoi
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

20 Feb, 15:33

510

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ኤክስፖ 2017 ዓ.ም የማስጀመሪያ መርሐ ግብር እየተካሄደ  ነው
=============================
የካቲት 13/2017 ዓ.ም (ኢሚ) የኤክስፖው የማስጀመሪያ መርሐ ግብር የኢንዱስትሪ  ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል፣ ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ የፌዴራል የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣የክልል የኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊዎች፣ የፋይናንስ ዘርፉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣የአምራች ኢንዱስትሪ ባለቤቶች፣ የዘርፉ ባለድርሻ አካላት፣ የዘርፍ ማህበራት ኃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በሂልተን ሆቴል እየተካሄደ ነው።

በሁነቱ የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ለዘርፉ ያበረከተው አዎንታዊ አስተዋፅኦ፣ ሚያዚያ 29 /2017 ዓ.ም ጀምሮ የሚካሄደውን 2017 ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ውጤታማ ለማድረግ ከማን ምን ይጠበቃልና ሌሎች የንቅናቄው ሀገራዊ ኢኮኖሚያዊ አበርክቶን የተመለከተ ገለፃ የሚከናወን ይሆናል።

#ኢትዮጵያ_ታምርት
#እኛም_እንሸምት
http://linktr.ee/fdremoi
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

19 Feb, 13:18

878

ሁለተኛው የንግድ ከባቢ ሁኔታ ሪፎርም ተጀመረ
===============================
የካቲት12/2017 ዓ.ም (ኢሚ) ሪፎርሙ እንደ ሀገር የንግድ ከባቢ ሁኔታውን ይበልጥ አመቺ ለማድረግ ተግባሩ በልዩ ክትትል እንዲመራ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ( ዶ/ር) በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት መሆኑ ተገልጿል።

ሪፎርሙን ተግባራዊ ለማድረግም በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የበላይ ሰብሳቢነት የሚመራ የስትሪግ ኮሚቴ እና የቴክኒክ ኮሚቴ ተቋቁሞ ላለፈው አንድ አመት ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸው ተገልጿል።

የተጀመረው ሁለተኛው የንግድ ከባቢ ሁኔታ ሪፎርም ከቀድሞ የሚለየውም ከ ውጪ አቅም ይልቅ የውስጥ አቅም ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑም ተጠቁሟል።

2ኛው የሪፎርም መርሃ ግብር በአምስት ዋና ዋና ማእቀፎች ማለትም የተረጋጋና የተናበበ ፖሊሲ ከመተግበር፣ የታክስና የጉምሩክ ሂደቶችን ከማቅለል፣ የመሰረተ ልማት አቅርቦትና ትራንስፎርሜሽንን ከማረጋገጥ ፣የፋይናንስ አቅርቦትን ከማሻሻል ፣ሙስናና የደህንነት ስጋቶች እንዲሁም የቢሮክራሲ ማነቆዎችን ከማሻሻል አንፃር 62 ኢኒሼቲቮች ተለይተው የጋራ መግባባት ላይ መደረሱ ተገልፀጿል።

ለሪፎርሙ ተግባራዊነትም በቀጣይ እንደሀገር ተግባራዊ ከተደረጉ ኢኒሼቲፎች ጋር መናበብና አላስፈላጊ ድግግሞችን ማስወገድ ፣ለአተገባበር በሚያስችል መልኩ ጠቅለል ባለ አቀማመጥ እንዲቀመጡ ማድረግ ፣አፈፃጻሙ ከእያንዳንዱ ታቋም አንፃር በዝርዝር ተለይቶ መቀመጥና መሰጠት እንዲሁም አግባብነት ያለው የኮምዩኒኬሽን ስራ መስራት በሚሉ አቅጣጫዎች ላይ ስምምነት ተደርሷል።

#ኢትዮጵያ_ታምርት
#እኛም_እንሸምት
http://linktr.ee/fdremoi
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

19 Feb, 12:37

719

እየተተገበረ ላለው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም መሳካት የንግድ ከባቢ ሁኔታ መሻሻል ወሳኝነት አለው (አቶ መላኩ አለበል)
=======================================
የካቲት12/2017 ዓ.ም (ኢሚ) ሁለተኛው የንግድ ከባቢ ሁኔታ ምቹነት የሪፎርም ማስጀመሪያ መርሃ ግብር የስትሪግ ኮሚቴ አባላት እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ተካሄደ።

ሁለኛው የንግድ ከባቢ ሁኔታ ምቹነት የሪፎርም ስራ 1 አመት ያስቆጠረ ነው ያሉት የኢንዱስትሪ ሚኒስትርና የስትሪንግ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ መላኩ አለበል በስትሪንግ ኮሚቴው እና በቴክኒክ ኮሚቴ በርካታ ስራዎች ሲሩ መቆየታቸውንና ከነዚህም ውስጥ የግሉ ዘርፍ ማነቆዎችን ለመለየትና ማሻሻያዎችን ለመቅረፅ የሚያስችል ጥናት በፈርስት ኮንሰልትና አዲስ አበባ ቻምበር መሰራቱን ገልፀዋል።

የእለቱ ውይይት አላማም በሁለተኛው የንግድ ከባቢ ሁኔታ ምቹነት ሪፎርም የተለዩ ኢኒሼቲቮች በምን አይነት የአመራር ቁርጠኝነትና ቅንጅት ሊተገብሩ ይገባል በሚሉ አስቻይ ሁኔታዎች ላይ ተወያይቶ የጋራ መግባባት ለመፍጠር እንደሆነ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል።

የመጀመሪያ ሪፎርም ምዕራፍ 100 ኢኒሼቲቮችን ይዞ ወደ ተግባር መግባቱን የገለፁት አቶ መላኩ ከነዛ ውስጥ 68ቱ በተሳካ ሁኔታ የተጠናቀቁና በንግድ ከባቢ ሁኔታ ላይ ለውጥ ማጣት የቻሉ፣ 22ቱ በሂደት ላይ ያሉና ያልተጠናቀቁ አንዲሁም 10ሩ በተለያየ ምክንያት ያልተጀመሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

አገር አቀፍና አህጉር አቀፍ ተወዳዳሪነታችንን ለማሰደግ የእኛን ቁመና ማሻሻል ያስፈልጋል ያሉት አቶ መላኩ እንደሀገር ለጀመርነው የብልፅግና ጉዞ ግቦቻችን መሳካት የግል ዘርፉን ተሳትፎ ወሳኝ በመሆኑ አጠቃላይ የንግድ ከባቢያዊ ሁኔታውን እየተሻሻለ የሚሄድ ኢንቨስትመንት የሚያመጣ የስራ እድልን የሚፈጥር የግል ዘርፉን እንቅስቃሴ ይበልጥ የሚያጠናክር ሊሆን ይገባልም ብለዋል።

በመጀመሪያ የሪፎርም ምዕራፍ በርካታ ውጤቶች የተመዘገበ ቢሆንም አሁንም ከፖሊሲ ተገማችነት፣ከቀልጣፋ አግልግሎት አሰጣጥ ፣ አዳዲስና ነባር ባላሃብቶቹን ወደ ዘርፉ ከማስገባትና ነባሮቹንም በአስፈላጊው የድጋፍ ማዕቀፍ ከማቆየት ፣ ከተቋማት ቅንጅት ፣ በየጊዜው የሚወጡ ህጎችና መመሪያዎች ተለዋዋጭነት አንፃር ኢንቨሰስትመንት ለመሳብና ለማቆየት የሚያስችል አለመሆኑን ጠቁመዋል።

እንደሀገር. ለተጀመረው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም መሳካት የንግድ ከባቢ ሁኔታ መሻሻል ወሳኝነት አለው ያሉት አቶ መላኩ ምርትና ምርታማነት የሚያሳድግ ፣ ኢንቨስመንትን የሚስብ፣ አዳዲስ የስራ እድል የሚፈጥር የተቀላጠፈ ፣ወጪ ቆጣቢ የሆነ አገልግሎት የሚሰጠበት ሁኔታ መፍጠር አለብን ይህንንም ታሳቢ በማድረግ 62 ኢኒሼቲቮች በ2ተኛው የሪፎርም መርሃ ግብር ተለይተዋል ሲሉ አክለዋል።

#ኢትዮጵያ_ታምርት
#እኛም_እንሸምት
http://linktr.ee/fdremoi
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

19 Feb, 09:00

233

የኢፌዴሪ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴርና ሳንኩ ፎርቲፊኬሽን ኢትዮጵያ በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ::
=========================
የካቲት 12/2017 ዓ.ም (ኢሚ) የኢፌዴሪ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴርና ሳንኩ ፎርቲፊኬሽን ኢትዮጵያ የጋራ ስምምነት በኢትዮጵያ ውስጥ በኢንዱስትሪ የሚመረቱ ምግቦች አስፈላጊ ማዕድናትን ያሟሉ ለማድረግና ተደራሽነታቸውን በማስፋት የህዝብ ጤናን ለማሻሻል እና የማይክሮኑትሪንት እጥረቶችን መቅረፍን ዓላማ ያደረገ ነው፡፡

በስምምነቱ መሰረት የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አምራች ኢንዱስትሪዎች በማይክሮኑትሪንት የበለፀጉ ምግቦችን ኢንዲያመርቱ የሚያስችል የፖሊሲና የአሰራር ማዕቀፎችን የሚያዘጋጅ ሲሆን ሳንኩ ፎርቲፊኬሽን ኢትዮጵያ በበኩሉ ዘርፉ ለሚመለከታቸው ባለሙያዎች የአቅም ልማት ማሻሻያ ስልጠናዎችን፣ ቴክኒካልና የፋናንስ ድጋፍ በማድረግ አምራቾች በተለይም ለምግብ የሚውሉ የዱቄት ምርቶች አስፈላጊ ንጥረ ነገሮችን ያሟሉ ሆነው ለተጠቃሚው ማህበረሰብ እንዲደርሱ ለማድረግ የሚሰራ ይሆናል፡፡

ሁለቱም ተቋማት በስምምነታቸው መሰረት የምግብ ማበልፀግን አስፈላጊነት ለህብረተሰቡ ለማስገንዘብ በጋራ የሚሰሩ ሲሆን ስምምነቱ ለሶስት (3) ዓመታት ይቆያል፡፡

ስምምነቱን በኢፌዴሪ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በኩል የእድገትና ተወዳዳሪነት ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ታረቀኝ ቡሉልታና የሳንኩ ፎርቲፊኬሽን ኢትዮጵያ ተባባሪ መስራትችን ዋና ስራ አስፈፃሚ ሚስተር ፍሊክስ ብሩክ ተፈራርመዋል፡፡

የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከሳንኩ ፎርቲፊኬሽን ኢትዮጵያ ጋር የምግብ ማበልፀግ ፕሮግራም ተግባራዊ እንዲሆን የአምስት ዓመት እስትራቴጂ የጤና ሚኒስቴርና ንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር በተገኙበት ነሐሴ 25 2017ዓ.ም ይፋ መሆኑንና ተግባራዊ በሚሆንበት ሁኔታ ላይ ሰፊ ውይይት ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

19 Feb, 08:44

310

በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አቶ መላኩ አለበል የተመራ ልኡክ ዳን ቴክኖ ክራፍት እና ዳን ሊፍት ቴክኖሎጂ የፋብሪካ ምልከታ እና ውይይት አካሄዱ ።
==========================
የካቲት 12/6/2017 ዓ.ም (ኢሚ) ዳን ሊፍት ቴክኖሎጂ የፋብሪካ በየጊዜው እያደገ የመጣ ከውጭ የሚገቡትን ምርቶች በሃገር ውስጥ በመተካት እየሰራ ያለ መሆኑን መረዳት ችለናል ያሉት የኢዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ገልፀዋል ባዩት የስራ እንቅስቃሴ መደሰታቸውን ገልፀዋል።

ፋብሪካውን ከዕድሜው ካለው የሰለጠነ የሰው ሃይል ፣ ዲጂታል የአደረጃጀት ሰርዓት፣ በማኔጅመንት ፣ በፋይናስ ፣በማርኬቲንግ እና ባሉት የፋብሪካ ማሽኖች ማስተዋወቅ ቢቻል ከዚህ በላይ ሊያድግና ስራተኛው በሽፍት የሚሰራበት ፣ ፋብሪካው 24 ሰዓት ምርት የሚያመርትበት ፣ የሃገር ውስጥ ፍላጉትን አሟልቶ ወደ ሌሎች የአፍሪካ ሃገሮች ሊደርስ የሚችልበት ዕድል ነበር ሲሉ ገልፀዋል ።

አብረን በጋራ እየተነጋገርን ፋብሪካው ያለበትን ችግር እየፈታን እንሄዳለን ያሉት ሚኒስትሩ ከሌሎች ተቋማት ጋር በጋራ የምትሰሩበትን ነገር ለማመቻቸት እና ድጋፍ ለማድረግ የሚጠበቅብን ሁሉ እናደርጋለንብለዋል ።

የዳን ቴክኖ ክራፍት እና ዳን ሊፍት ቴክኖሎጂ ፋብሪካ መስራች እና ባለቤት ኢንጂነር ዳንኤል መብራሃቱ በበኩላቸው ፋብሪካው ከተመሰረተበት 1965 ዓ ም ጀምሮ መኪና በመገጣጠም ፣ ፋይል ካቢኒቶች ፣ ካዝና ፣ የሆስፒታል አልጋ ፣ ሊፍት እንደሚያመርት ገልፀው ሌሎችም የእንጨት ፣ የብረታ ብረት ፣ ምርት ውጤቶች አስራለን ሲሉ ገልፀዋል ።

ፋብራካው በሚያመርተው ሊፋት Iso 9001-2000 የጥራት ተሸላሚ መሆናቸውን የገለፁት ኢንጂነር ዳንኤል መንግስት ለዘርፉ ትኩረት በመስጠት ፋብሪካውን በመጎብኘቱ አመስግነዋል ።
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

13 Feb, 15:56

2,137

በአምራች ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ዙሪያ ከጆርዳን ጋር ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ማጠናከር ያስፈልጋል፡፡ (አቶ ሀሰን መሀመድ)
==============================
የካቲት 06/2017 ዓ.ም (ኢሚ) የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የመሰረተ ልማትና ግብዓት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሀሰን መሀመድ የጆርዳን አምባሳደር ዶክተር ኢማድ ማሳለምህን በቢሯቸው ተቀብለው በንግድ፣ በአምራች ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት እንዲሁም በባህል ልውውጡ ላይ ያላቸውን የሁለትዮሽ ግንኑነት ለማጠናከር ያለመ ውይይት አካሂደዋል ፡፡

አቶ ሀሰን በውይይታቸው በዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት፣ በአምራች ኢንዱስትሪ ምርቶች የገበያ መዳረሻ፣ በዘርፍ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በማሳደግ፣ በቴክኖሎጂ እና በእውቀት ሽግግር የተሻሻለ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ በሁለቱ ሀገራት የስራ እድል ፈጠራ እና የኢኮኖሚ እድገት ትብብር በተጨማሪም በባህል ልውውጥ ላይ ያላቸውን የጋር የሁለትዮሽ ትብብር ለማጠናከር በጋራ እንደሚሰሩ ገልፀዋል።

ጆርዳን በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ አቅም በተለይም በግብርና በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ የመሰማራት ፍላጎት እንዳላቸው የጆርዳን አምባሳደር ዶክተር ኢማድ ማሳለምህ ገልፀዋል፡፡

#ኢትዮጵያ_ታምርት
#እኛም_እንሸምት
http://linktr.ee/fdremoi
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

13 Feb, 08:35

1,786

https://www.youtube.com/watch?v=wGdejKcoCLM

በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የማስፋፊያና ማበረታቻ መሪ ስራ አስፈፃሚ ጋር የተደረገ ቆይታ
#ኢትዮጵያ_ታምርት
#እኛም_እንሸምት
http://linktr.ee/fdremoi
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

10 Feb, 11:09

1,517

የኢትዮጵያ ታምርት ሀገራዊ ንቅናቄ ኢትዮጵያ ሀገራችን በምግብ ራሷን እንድትችል መንግስት ያላሰለሰ ጥረት እያደረገ ስለመሆኑ አንዱ ማሳያ ነው (አቶ ሀሰን መሃመድ)
===================================
የካቲት 03/2017 ዓ.ም (ኢሚ) የኢትዮጵያ ታምርት ሀገራዊ ንቅናቄ ኢትዮጵያ ሀገራችን በምግብ ራሷን እንድትችል መንግስት ያላሰለሰ ጥረት እያደረገ ስለመሆኑ አንዱ ማሳያ መሆኑን የኢትዮጵያ ዱቄትና የዱቄት ውጤቶች አምራቾች ማህበር 16ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉት በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የመሰረተ ልማትና ግብዓት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ሀሰን መሃመድ መንግስት ለምግብ አምራቾች ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው ብለዋል::

ሚኒስቴር መስርያ ቤታችን በአዋጅ በተሰጠው ስልጣን መሰረት በስሩ ብዙ የዘርፍ ማህበራትን አቅፎ መያዙን የገለፁት አቶ ሀሰን የኢትዮጵያ ዱቄትና የዱቄት ውጤቶች አምራቾች ማህበር አንዱ መሆኑን በመጥቀስ የዘርፍ ማህበሩ የምግብ አምራች ኢዱስትሪዎችን በስሩ አቅፎ ሀገሪቷ በምግብ እራሷን እንድትችል በሚደረግ እንቅስቃሴ እና ጥረት ውስጥ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ መሆኑን በመጥቀስ ጥረቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ያላቸውን እምነት ገልፀዋል፡፡

በሀገራችን ከ 340 በላይ የምግብ አምራች ኢንዱስትሪዎች መኖራቸውን የጠቀሱት ሚኒስትር ዴኤታው እንዱስትሪውች ለብዙ የሀገራችን ዜጎች የስራ እድል ከመፍትጠራቸውም ባሻገር ለሀገር እድገት ትልቅ ድርሻ እያበረከቱ ስለመሆኑ ገልፀዋል፡፡

መንግስት የማህበረሰብን ጤና ከመጠበቅ አኳያ በሀገራችን ብሎም በአለማችን እየታየ ያለውን የመቀንጨር እና መቀጨጭ ችግሮችን ለመቀነስ ብሎም ለማስቀረት የበለፀጉ ምግቦችን (Fortified foods) ብቻ ወደ ገበያ እንዲገቡ በማድረግ ረገድ ቁርጥ አቋም ይዞ እየሰራ ይገኛልም ብለዋል፡፡

የአለም ሀገራት የዜጎቻቸውን ደህንነትና የኑሮ ሁኔታ ምቹ ለማድረግ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ለመጣው የንግድና ኢንቨስትመንት ሂደት የፖሊሲና የአስተዳደር ችግሮችን መቅረፍ የሚያስችል ስነምህዳር በመፍጠርና የፈጠሩትን ስነ-ምህዳር ለዘላቂ ልማት ማስተግበሪያ በማድረግ በአምራች ኢንዱስትሪ ላይ አበክረውን ልዩ ትኩረት ሰጥተው በመስራታቸው የበለጸገ ዘላቂና አስተማማኝ ኢኮኖሚ በመገንባት ለዜጎቻቸው ምቹ ሁኔታ መፍጠር መቻላቸውን አንስተዋል፡፡

ለሀገር ለሁለንተናዊ ዕድገት፣ ለድህነት ቅነሳ፣ የመንግስት ተጠያቂነትን ለማሳደግ ፣ የሀገርን ተወዳዳሪነት ከፍ ለማድረግ ፣ የፈጠራ አቅምን ለመጨመር እና ለዘላቂ ልማት ለመብቃት ለግሉ ዘርፍ በሚፈጠር ምቹ ሁኔታ መሆኑን በኢኮኖሚ ከበለፀጉ ሀገራት ልምድ እንማራለን ብለዋል፡፡

የግሉ ዘርፍ ክፍለ ኢኮኖሚና ባለሀብቶች ምርታማነታቸው ከፋብሪካ የማምረት አቅም ስራ አመራር ጋር የተያያዘ በመሆኑ ግሎባላይዜሽን ከሚያሳድረው ተጽዕኖ የማያመልጡ በመሆናቸው ለወደፊት የንግድና ኢንቨስትመንት እንቅፋቶች ዙሪያ ይበልጥ አስተማማኝ ያልሆነ ሁኔታ ሲከሰት በአገሮች መካከል ያለው ትብብር እያደገ መምጣቱ በሀገር ደረጃም በጋራ ለመስራትና ለመምከር በር ካፋች መሆኑንም መውሰድ አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

"የምግብ አምራቾች ሚና በምግብ ማበልፀግ እና ማህበረሰብ ጤና" በሚል መሪ ቃል ከግብ ለማድረስ የምግብ አምራች ኢንዱስትሪዎች ድርሻችሁ የጎላ መሆኑን አውቃችሁ ሁሉም አምራች የበለጸገ ምግብ (fortified food) አምርታችሁ ለገበያ እንዲያቀርቡ አሳስበዋል፡፡

#ኢትዮጵያ_ታምርት
#እኛም_እንሸምት
http://linktr.ee/fdremoi
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር Ministry of Industry, Ethiopia

08 Feb, 11:07

1,785

የፕላስቲክ ፎርምዎርክ ከእንጨት የሚሰራውን የግንባታ ግብዓት በመተካት የደን መጨፍጨፍን መቀነስ እንደሚያስል ተገለፀ፡፡ ወ/ሮ ካሳነሽ አያሌው
============================
የካቲት 01/2017 ዓ.ም (ኢሚ) የኤች ኬ ቢዝነስ ግሩፕ ስራ አስፈጻሚና ባለቤት ወ/ሮ ካሳነሽ አያሌው ፋብሪካው በድጋሚ ጥቅም ላይ የሚውል የግንባታ ፕላስቲክ ፎርምዎርክ አምርቶ ለሀገር ውስጥ እና ለውጭ ገበያ ለማቅረብ መዘጋጀቱን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ በየዓመቱ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞች እየተከለች ቢሆንም በሌላ በኩል ለእንጨት ፎርምዎርክ መስሪያ ዛፎች እንደሚቆረጡ አንስተዋል።

የፕላስቲክ ፎርምዎርኩ ከእንጨት የሚሰራ የግንባታ ግብዓትን በመተካት የደን መጨፍጨፍን ለመቀነስ እንደሚያግዝም ጠቁመዋል።

የእንጨት ፎርምዎርኮች ቢበዛ እስከ 5 ጊዜ ቢያገለግሉ ነው ያሉት ስራ አስኪያጇ ፋብሪካው በእንጨት የሚመረቱትን በፕላስቲክ በመተካት የደን መጨፍጨፍን ከመቀነስ ባለፈ ፎርሞርኮቹ ከ50 ጊዜ በላይ የሚያገለግሉ በመሆናቸው የሚወጣውን ከፍተኛ ወጪ ይቀንሳል ሲሉ አብራርተዋል።

የፕላስቲክ ፎረምዎርኮች ከዚህ ቀደም ከውጪ የገቡ እንደነበር ያነሱት ወ/ሮ ካሳነሽ ይህም ከፍተኛ የውጪ ምንዛሪ የሚያሳጣ መሆኑን ገልፀዋል።

ምርቶቹ በሀገራችን ውስጥ መመረታቸው ከውጭ የሚገባውን ተመሳሳይ ምርት በመተካት በዓመት ከ15 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሪ ማስቀረት የሚችል መሆኑ ተገልጿል፡፡

#ኢትዮጵያ_ታምርት
#እኛም_እንሸምት
http://linktr.ee/fdremoi