Mereja Today

@merejatodayethiopia


Your News Destination

Mereja Today

23 Oct, 14:05


https://youtu.be/dAG80zelRj4?si=O6aAogOXafUcnSbX

Mereja Today

19 Oct, 09:45


https://youtu.be/68Vi5bQmSMs?si=iq1nGPfRHAUAroli

Mereja Today

18 Oct, 06:15


https://youtu.be/y4-eci4hlio?si=fwY_vpnLiXN9R35B

Mereja Today

04 Oct, 10:42


https://youtu.be/0m2nc6N-GpA?si=Jnnf3d9QnXqbQm4n

Mereja Today

26 Sep, 06:11


https://youtu.be/Lh85UZr5ATM?si=4SlVthMkbEs6W9kq

Mereja Today

23 Sep, 10:30


https://youtu.be/IxFnzSDh7Co?si=xX7fC_GOAjdCin7t

Mereja Today

19 Sep, 06:09


https://youtu.be/2ZCQ-f6fLQA?si=fsdexidixVN-MoN8

Mereja Today

17 Sep, 06:37


ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ አርፈዋል። ነፍስዎ በሠላም ትረፍ

Mereja Today

17 Sep, 06:32


ግብጽ፣ ኤርትራን ከሕወሓት ጋር ለማስታረቅ በምትችልበት ኹኔታ ዙሪያ ከኤርትራ ጋር እየመከረች መኾኗን የኢምሬቶች ጋዜጣ ናሽናል ዘግቧል። ኤርትራ እና ግብጽ የወታደራዊ ትብብርና የመረጃ ልውውጥ ለማድረግ አማራጮችን እየፈተሹ እንደኾነም ዘገባው ጠቅሷል። ሁለቱ አገራት ለመፈራረም ያስቡት ስምምነት፣ በቀይ ባሕር አካባቢ የመርከቦችን ደኅንነት ለማረጋገጥ ርምጃዎችን መውሰድን ያካትታል ተብሏል። የግብጽ ደኅንነት ሚንስትር ጀኔራል ከማል አባስና ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ባድር አብደላቲ ሰሞኑን አሥመራ ውስጥ ከፕሬዝዳንት ኢሳያስ ጋር መወያየታቸው ይታወሳል።

Mereja Today

17 Sep, 06:26


በእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ቡድን የሚመራው ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) የድርጅቱ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙባቸው 16 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ማባረሩና ከነበራቸው ድርጅታዊ ሃላፊነት ማንሳቱን አስታወቀ።

ድርጅቱ መስከረም 6/2017 ዓ.ም አካሄድኩት ያለውን ስብሰባ አስመልክቶ ባወጣው ባለ ሦስት ገፅ መግለጫ :- 

1. አቶ ጌታቸው ረዳ 
2. አቶ በየነ ምክሩ
3. ፕ/ር ክንደያ ገ/ሂወት
4. ዶ/ር ሓጎስ ጎዲፈይ
5. ወ/ሮ ኣልማዝ ገ/ፃዲቕ
6. አቶ ረዳኢ ሓለፎም
7. ወ/ሮ ሰብለ ካሕሳይ
8. አቶ ኢሳያስ ታደሰ
9. አቶ ሰለሞን መዓሾ
10. አቶ ሺሻይ መረሳ
11. ዶ/ር ገ/ሂወት ገ/ሄር 
12. አቶ ርስቁ አለማው
13. አቶ ሃፍቱ ኪሮስ
14. አቶ ብርሃነ ገ/የሱስ
15. አቶ ሩፋኤል ሽፋረ 
16. አቶ ነጋ ኣሰፋ 

ከአባልነትና ከድርጅት ሃላፊነት " አባርሪያችኃለሁ " ብሏል።

Mereja Today

17 Sep, 06:24


አስቸኳይ ስብሰባ በሶማሊያ

የሶማሊያ የፌደራል መንግስት ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ ፣የፓርላማ አፈ ጉባኤ ሼክ አዳነ ማዶቤ እና ጠቅላይ ሚንስትር ሃምሳ አብዲ ባሬ አስቸኳይ ስብሰባ እያካሄዱ መሆኑን ዘገባዎች አመልክተዋል። ይህ ስብሰባ በሶማሊያ እና በደቡብ ምዕራብ አስተዳደር መካከል ባለው ውጥረት ላይ ያተኮረ ነው ተብሏል።

ዛሬ ከሰአት በኋላ የደቡብ ምዕራብ ፕሬዝዳንት አብዲካሲስ ላፍታጋሬን እና የሶማሊያ ፓርላማ አፈ-ጉባኤ ሼክ አዳነ ማዶቤ በስልክ ተወያይተው የነበረ ቢሆንም ያለስምምነት መጠናቀቁ ተዘግቧል።

መረጃው እንደሚያመለክተው ሼክ አዳነ ማዶቤ ላፍታጋሪን ወደ ሞቃዲሾ እንዲመጡ ቢጠይቁም ላፍታጋሬን ጥያቄውን ውድቅ ማድረጉን ነው የተገለፀው።

በውይይታቸውም ሁለቱ ባለስልጣናት እላፊ ቃላት መለዋወጣቸው የተነገረ ሲሆን የሁለቱ ወገኖች ግጭት ምን ያህል የሰፋ እንደሆነ ያሳያል ተብሏል::

Mereja Today

17 Sep, 06:23


https://youtu.be/zT-KYIjzImQ?si=BddUHWIrFHlq8Bcm

Mereja Today

05 Sep, 11:45


‹‹የፕሪቶሪያው ስምምነት አደራዳሪዎች ህወሃትን የማጥፋት ስራ ሰርተዋል›› አቶ አማኑኤል አሰፋ 

በቅርቡ በተደረገው አወዛጋቢ ጉባኤ የህወሃት ምክትል ሊቀ-መንበር ሆነው የተሾሙት አቶ አማኑኤል አሰፋ የድርጅቱ ልሳን ከሆነው ወይን ጋዜጣ ጋር ቆይታ አድርገዋል፡፡

አቶ አማኑኤል በቆይታቸው በፕሪቶሪያው ስምምነት ውስጥ ህወሃትን የሚያፈርሱ፣የፓርቲውን አወቃቀር የሚያናጉና በድርድር ውስጥ የድርጅቱን ሚና የሚያሳንሱ ነጥቦች በአደራዳሪዎች ግፊት ተካተዋል ሲሉ ከሰዋል፡፡

Mereja Today

05 Sep, 11:44


“በመንገድ ላይ የምናሳልፈው ጊዜ ቤታችን ከምንቆይበት በላይ ነው”- ታክሲ ተጠቃሚዎች 

በአዲስ አበባ ከተማ የትራንስፖርት ችግር እየተባባሰ መምጣቱን እና ተጠቃሚዎች ተሽከርካሪ(ታክሲ) በመጠበቅ የሚያሳልፉት ጊዜ እንዳስመረራቸው ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል፡፡

በተለያዩ አካባቢዎች ሰራተኞች ወደ መስሪያ ቤታቸው ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው በሰዓቱ ለመድረስ የታክሲ አገልግሎት ማግኘት  እንዳልቻሉም ደጋግመው ሲገልጹ ይደመጣል፡፡

ለሙሉ ዘገባ፡ https://addismaleda.com/archives/38921

Mereja Today

04 Sep, 05:24


የኢትዮጵያ አየር መንገድ “የኤርትራ በረራ ያቋረጥኩበት አንዱ ምክንያት በሀገሪቱ የሚገኘው የባንክ ሂሳቤ በመታገዱ ነው” አለ

የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ትናንት በሰጡት መግለጫ፤ የአስመራ በረራን የማቅረጥ ውሳኔ ላይ የደረሰው በኤርትራ ውስጥ አገልግሎቱን ለመስጠት ባጋጠመው ከአቅም በላይ በሆነ የአሰራር ችግር ነው ብለዋል።

ዋና ሥራ አስፈፃሚ አክለውም፤ ምክንያቱን ባላወቅነው መንገድ አስመራ ውስጥ ያለንን የዶላር ገንዘብ እንዳናወጣ ተከልክለናል ብለዋል።

Mereja Today

04 Sep, 05:22


የኤርትራ እና የሶማሊያ ፕሬዝዳንቶች ከቻይና አፍሪካ የትብብር መድረክ ጎን ለጎን በሁለትዮሽ ጉዳይ መምከራቸው ተሰምቷል።

እንደ ቪላ ሶማሊያ ዘገባ ሁለቱ መሪዎች በቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውን ታውቋል።

ሁለቱ ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነታቸው ከላላ ወዲህ ወዳጅነታቸውን ለማጠናከር ብዙ ጊዜ አስመራና ሞቃድሾ ሲመላለሱ ይስተዋላሉ።ወቅታዊው የኢትዮ ሶማሊያ ጉዳይ ይበልጥ እንዳቀራረባቸው ይነገራል።

Mereja Today

04 Sep, 05:21


አነጋጋሪው የፓርላማ ድብድብ።
በሱማልያ ፓርላማ አባላት ኢትዮጵያ በሱማሌላንድ ጉዳይ ባላት አቋም ላይ ሲከራከሩም ሲጣሉም ታይተዋል።

ከማህበራዊ ሚዲያ የተገኘ

Mereja Today

04 Sep, 05:19


https://youtu.be/vElMF3mZpu8?si=e0e4PO6AuqFIx0Zx

Mereja Today

03 Sep, 06:13


ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ድንበር እንደዘጋች ሱዳን ትሪብዩን ዘገበ

የፋኖ ሀይሎች የመተማ ከተማን መቆጣጠራቸውን ተከትሎ ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ድንበር እንደዘጋች ሱዳን ትሪብዩን ዘገበ።

ሚድያው ዛሬ ባስነበበው ዘገባው የሱዳን ምስራቃዊ ግዛት የሆነችው የአል-ቃዳሪፍ 'ጋላባት' የተሰኘው ድንበር መሸጋገርያ ከትናንት እሁድ ጀምሮ ዝግ ሆኗል፣ ይህም የሆነው የፋኖ ሀይሎች የመተማ ከተማን በመቆጣጠራቸው ነው ብሏል።

ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ ፖሊስ አባላት ወደ ሱዳን እንዲገቡ እንደተደረገ፣ በሌላ በኩል ደግሞ የሱዳን ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ በፋኖ ሀይሎች እንደተደረገ ዘገባው ይገልፃል።

በዚህ ዙርያ ለማናገር የመከላከያ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ኮ/ል ጌትነት አዳነን በተደጋጋሚ በስልክ ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም ሲል መሰረት ሚዲያ አሳውቋል።