Medicine Daily @medicinedaily Channel on Telegram

Medicine Daily

@medicinedaily


Your Daily Dose of Health Insights!

Telegram: t.me/medicinedaily
Facebook: www.fb.com/medicinedailynet

Medicine Daily (English)

Looking for your daily dose of medical news and updates? Look no further than Medicine Daily! This Telegram channel, with the username @medicinedaily, provides you with the latest information on the world of medicine, from groundbreaking research to new treatment options. Whether you are a medical professional looking to stay informed or just someone interested in health and wellness, Medicine Daily has something for everyone.

Stay up to date with the latest medical breakthroughs, health tips, and news from the medical community. With regular updates and curated content, Medicine Daily is your go-to source for all things medical. Connect with like-minded individuals and engage in discussions about the latest trends and developments in healthcare.

Don't miss out on important updates and valuable insights. Join the Medicine Daily Telegram channel today and make sure you are always in the know when it comes to medical news and updates! For more information, you can also follow us on Facebook at www.fb.com/medicinedailynet.

Medicine Daily

15 Feb, 19:49


የተለያዩ የመንግስት ዩንቨርስቲዎች በዛሬው ዕለት በርካታ ተማሪዎቻቸውን በደማቅ ሁኔታ አስመርቀዋል።

መቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ 998 ተማሪዎችን አስመርቋል።

ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ የትምህርት ፕሮግራሞች ስልጠናቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ የ5ኛ ዙር ተመራቂዎች የምረቃ ስነ-ስርዓት ዛሬ አካሒዷል።

ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ 223 በድኅረ-ምረቃ ፕሮግራም ፤ 389  በመደበኛ፣ በተከታታይ እና በክረምት መርሐግብሮች በመጀመሪያ ዲግሪ  ያሰለጠናቸውን ተማሪዎችን ዛሬ አስመርቋል።

ከተመራቂዎቹ ውስጥ 127 ተማሪዎች በህክምና ትምህርት የተመረቁ መሆናቸው ተገልጿል።

ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 1,513 ተማሪዎችን ዛሬ አስመረቋል።

የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እንዲሁም በተከታታይ መርሐግብር የቅድመ-ምረቃ እና የድኅረ-ምረቃ ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲው ዛሬ ባከናወነው 14ኛ ዙር የተማሪዎች የምረቃ ስነ-ስርዓት መመረቃቸው ተገልጿል።

ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ የመጀመሪያ ባች ተማሪዎቹን ዛሬ አስመርቋል።

ዩኒቨርሲቲው ዛሬ ያስመረቃቸው የጤና ተማሪዎች ባለፈው ሳምንት የተሰጠውን የመውጫ ፈተና ወስደው ሙሉ በሙሉ ያለፉ መሆናቸው ተገልጿል።

ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ 232 በሁለተኛ ዲግሪ እና 107 በመጀመሪያ ዲግሪ በጤና ሳይንስ መስክ ያሰለጠናቸውን 339 ተማሪዎች አስመርቋል።

ዩኒቨርሲቲው በተጨማሪም በ Higher Diploma Program ስልጠናቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ 28 መምህራን በዛሬው ዕለት አስመርቋል።

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ከመጀመሪያ ዲግሪ እስከ ሦስተኛ ዲግሪ መርሐ ግብር  ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ 366 የሕክምና ተማሪዎችን አስመርቋል።

ተመራቂዎች እንኳን ደስ አላችሁ 🥳

@medicinedaily

Medicine Daily

15 Feb, 19:18


#ድሬዳዋ ፡ የግል መድሃኒት ቤት የሌሊት አገልግሎት ሰጪ ተረኞች ክፍለ ጊዜ ዝርዝር 👉 ከ 03-30/06/2017 ዓ.ም

Dire Dawa Administration Health Bureau

@medicinedaily

Medicine Daily

15 Feb, 17:01


Addis Ababa University College of Health Sciences 2025 Emergency medicine and Critical Graduates.

Tikur Anbessa Specialized Hospital

Congratulations! 🎉🎉🎉🎆🎆


@medicinedaily

Medicine Daily

15 Feb, 14:41


ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በዛሬው ዕለት የህክምና ተማሪዎቹን አስመርቋል።

#WachamoUniversity
#ዋቸሞ_ዩኒቨርሲቲ

@medicinedaily

Medicine Daily

15 Feb, 13:54


የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በህክምና እና ጤና ሳይንስ ዘርፍ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመረቀ

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በህክምና እና ጤና ሳይንስ ዘርፍ ያሰለጠናቸውን 366 ተማሪዎች በዛሬው ዕለት አስመርቋል።

ከተመራቂዎቹ 254 ወንድ እና 112 ሴት ስሆን በአጠቃላይ 366 ተመራቂ ተማሪዎችን በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ፣ በሶስተኛ ዲግሪ፣ በስፔሻሊቲና በሳብስፔሻላቲ አስመርቋል።

ዩኒቨርስቲው 40ኛ ዙር
#የህክምና እና 21ኛ ዙር #የፋርማሲ ተማሪዎችን ማስመረቁን ገልጸዋል።

የምረቃ በዓሉ ዩኒቨርስቲው 70ኛ አመት እና አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 100ኛ ዓመት ክብረ በዓል እየተከበረ ባለበት ወቅት መሆኑ ልዩ ያደርገዋል ስል ዩኒቨርስቲው ገልጸዋል።

🙏🙏እንኳን ደስ አላችሁ! 🎉🎉🎉🎆🎆
🙏🙏Congratulations 🎉🎉🎆🎆

የካቲት 08/2017

#UniversityofGondar

@medicinedaily