በአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪነት ለመመዝገባ ጥያቄ ላቀረባችሁ አመልካቾች
በአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪነት ለመመዝገብ የክ/ሃገር መሸኛ አስገብታችሁ በመጠባበቅ ላይ ያላችሁ ተገልጋዮች ያቀረባችሁትን መረጃ የማጥራት ሂደት በማጠናቀቅ አገልግሎቱን ከህዳር 1 ጀምሮ ለመጀመር ዝግጅት ተደርጓል።
በመሆኑም ከነገ ጥቅምት 14/2017ዓ.ም ጀምሮ በነዋሪነት ለመመዝገብ ያመለከታችሁበት የሲቪል ምዘገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት የወረዳ ጽ/ቤታችን እስከ ጥቅምት 22 ቀርባችሁ ሪፖርት እንድታደርጉ እያሳሰብን የፋይዳ ምዝገባ አስገዳጅና ምዝገባው በኤጀንሲው ጽ/ቤት እዛው የሚከናወን በመሆኑ የክ/ሃገር መልቀቅያ ባስገባችሁበት ወቅት ከጽ/ቤታችን የተሰጣችሁን ማስረጃ ይዛችሁ እንድትቀርቡ በአክብሮት እንገልፃለን።
ውድ ተገልጋዮቻችን በዚህ የማጥራት ሂደት ያላለፈ አመልካች በነዋሪነት ተመዝግቦ አገልግሎት ማግኘት የማይችል መሆኑን በመገንዘብ በተቀመጠው የግዜ ገደብ ዘውትር ከሰኞ እስከ እሁድ ቀርባችሁ ሪፖርት እንድታደርጉ እናሳውቃለን።
ኤጀንሲው
CRRSA
ለበለጠ መረጃ፣ ጥቆማ ወይም ማብራርያ በተገልጋይ የስልክ መስመራችን 7533 ደውለው ያግኙን
ዌብ ሳይት (website): https://www.aacrrsa.gov.et
ዩትዩብ (youtube)፡ https://www.youtube.com/@CRRSA1935
ፌስቡክ (facebook):
https://www.facebook.com/pr
ቴሌግራም (telegram): https://t.me/lemikurawereda9crrso