FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት @focusinternationalministry Channel on Telegram

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

@focusinternationalministry


NEW CREATION MANIFESTATION

👉በዚህ ቴሌግራም ቻናል #በፎከስ #ሚንስትሪ #ትምህርቶች ይቀርባሉ፡፡
እንዲሁም
#የፀሎት#የነፃ መውጣትና#የፈውስ አገልግሎት የምትፈልጉ#እንዲመለስላችሁ የምትፈልጉትን#ጥያቄ ያላችሁ#Facebook ላይ
👉 #Woubshet #Humaso የሚለውን #follow
        👉በማድረግ ማቅረብ ትችላላችሁ 👇
https://www.facebook.com/whumaso

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት (Amharic)

የአማርኛ ብለዋል የቴሌግራም ቤተሰብ እንደማለት በቤተሰብና ኀብት ላይ መጠቀም የሚሰጥህን መጀመሪያዎችን ለመተግበር የfocusinternationalministry የቴሌግራም አባል ይመልከቱ። ይህ ቴሌግራም ቤተሰብ የአማርኛ ቴሌግራም ብሆን እና በአማርኛ የቴሌግራም እና አማርኛ ብለዋል ትምህርቶችን ይቀርባሉ። ቅርብ ገጽም ጥጅን ያስቀምጠውን ታስርቆታ የሚያግዝህ ሊከተለው ይችላል። በስምምነት ተጨማሪ መጣጣሻን ቴሌግራም በመሰረተ ተጨማሪ በኮቪት ወይም በልተ ቤተሰብ ላይ ያገኙና ይህን ቴሌግራም አባል ይሙሉ። ከዚህም በተጨማሪ እና ፈጣን ምስጋና የተፈለገልን የትምህርት እና ቡሩክ ቲቪንዮችን በሚሊኒሸው ቡስቲን ተገቢ። ለመሸጥ እና ፈጥሬ እንዲመለስህ ያስችላሉ። አገልግሎት ማስነሳት ሰረምን እንዲጠቀሙት በፎከስን ማስነሳት ይችላሉ። አንደኛውን ለመለዋወጥ እና አቆራረጥ እንዲቻል ለሚስጥም ያደርሳሉ።

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

12 Feb, 13:57


#እስራት በህይወታችን ምን ያደርጋል ?

#እስራት ሰዎችን ውስን ያደርጋል እንዳትበዙ ፣ እንዳትወጡ ፣ እንዳትሰፉ ለብዙ ትውልድና ሀገር እንዳትሆኑ ነው እስራት የሚያደርገው ።

#ያቺ የአህያ ውርንጭላ ሰፈር ሊያስቀሯት ነው የፈለጓት ከቻሉ የራሳቸው ባሪያ ። እስራት ባሪያ ነው ሚያደርገው ። ፍቃድ የሌለን ፣ ምርጫ ፣ ሀሳብ የሌለን ፣ ራእይ የሌለን ነው ሚያደርገው ።

#እስራት ያለንን ህልም እና ራእይ እንዳንፈፅም paralized ነው ሚያደርገው ። ሳምሶንን የሚያክል ሰው አይኑን አውጥተው አስረውት ነበር ። #ኢየሱስ ያስነሳው አላዛር ተነስቷል ትንሳኤ መንፈስ ውስጡ አለ ግን አይራመድም ለምን ታስሯል #አያችሁ ከአጋንንት ቀጥሎ ወደ ብዙ አቅጣጫ እንዳትዘረጉ የሚያደርጉ ሰዎች አሉ እነዚህን ሰዎች እንድንለይ እግዚአብሔር አይናችንን ይክፈት አሜን

#ደግሞ አሉ በህይወታችን ጓደኛ ፣ ባል ፣ ሚስት ፣ ፓስተር ሆነው የተቀመጡ ለእግዚአብሔር ነገር ውስጣችን ላለው አቅም መንገድ ዘግተው እንዳንገለጥ አስረው ያስቀመጡ :- አንዳዶች ደግሞ ከእኔ ውጭ ምንም ማድረግ አትችይም አትችልም ብለው ያሰሩ ይሄ ክፉ እስራት ነው እግዚአብሔር ሲፈጥረን ብዙ አቅም አስቀምጧል ለሃገር ለትውልድ ሚሆን ሊገለጥ የተገባው ዛሬ ንቁ እስራቱን ፍቱ ውጡ ከወጥመድ ውስጥ

#አስባችሁት ታውቃላችሁ አንዳንድ የቅርብ የምትሏቸውን ሰዎች ውስጣችሁ ያለውን የስራ ፍላጎት ልታደርጉ ያሰባችሁትን ስታማክሯቸው እንዳትሰሩ ደግማችሁ እንዳታስቡ አድርገው ላትነሱ አድርገው ሚገድሏችሁ በቁም ሚያስሯችሁ በአሳብ ከማገዝ በርቺ በርታ ከማለት ይልቅ በቃ ድንዝዝ አድርገው እስር ሚያደርጉ ይሄ እስራት ነው አምልጡ ሽሹ ከእንደነዚህ አይነት ሰዎች ለምን ካላችሁ ውስጣችሁ ያለው አቅም ሊገለጥ ይገባል

#እያንዳዳችን ውስጥ የሆነ ሊገለጥ የሚገባው አቅም አለ ። ያቺ የአህያ ውርንጭላ ሰፈር አስረዋት ነበር ጌታ ደቀመዛሙርቱን ሲልካቸው የታሰረች የአህያ ውርንጫ አለች ፈታችሁ አምጡልኝ ማንም አንዳች ቢላችሁ ለጌታ ያስፈልጉታል በሉ አላቸው

#ዛሬ የሆነ አጥር ውስጥ ያላችሁ ምንም እንደማትጠቅሙ የተነገራችሁ አቅማችሁን የቀበሩባችሁ ተነሱ ውጡ ከወጥመዳችሁ አምልጡ እስራታችሁን ፍቱ የዛሬ መልእክቴ ነው

ቻናላችንን ይቀላቀሉ ለሌሎችም ሼር ያድርጉ

  🔺🀄️🀄️ሉ  ✓👇

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

10 Feb, 20:16


https://www.tiktok.com/t/ZT2BasnDE

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

09 Feb, 20:48


https://www.facebook.com/share/v/1Bd3p5atJt/?mibextid=wwXIfr

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

09 Feb, 13:21


#ስለልጅነት ማወቅ ያለብን እውነታዎች

#ልጅነት የሚገኘው በመጀመሪያ በመወለድ ነው ሚገኘው ። ልጅ ለመባል በክርስቶስ ኢየሱስ በተሰራው ስራ ማመን ያስፈልጋል ።

#በመጀመሪያ ይሄን ማወቅ ያስፈልጋል ሰይጣን እንድናውቅ የማይፈልገው ነገር ቢኖር ስልጅነታችን ነው ለምን መሰላችሁ ልጅነታችንን ስናውቅ እንዴት የድል ህይወት እንደምንኖር ያውቃል ስለዚህ በእግዚአብሔር ስላገኘነው ልጅነት እውቀት እንዲኖረን አይፈልግም

#ልጅነታችንን ስናውቅ የሰይጣንን መንግስቱን እናፈርሳለን ፣ ለሚጠይቀን መልስ እንሰጣለን ሰይጣን ለጌታ ሲፈትነው የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ ነው ያለው በልጅነቱ ነው ፈተናውን ያመጣው አያችሁ ጌታም ስለ አባቱ ስለ እግዚአብሔር ሙሉ እውቀት ስለነበረው መለሰለት

#ስለ አባታችን ካላወቅን ልጅነታችን ካልገባን ጠላት ድል ይነሳናል የድል ህይወት መኖር ሲገባን ስለዚህ ልጅነታችን ይግባን ። ልጅነት ውስጥ ስልጣን አለ ፣ ልጅነት ውስጥ መሰማት አለ ፣ በአብ ፊት ያለመሸማቀቅ በድፍረት መቅረብ አለ ፣ እግዚአብሔርን መስማት አለ ይሄ ልጅነት ውስጥ ያለ ስልጣን ነው ልጅ ያልሆነ አይሰማም አይሰማም ማለት ነው ። ምክንያቱም በጎቼ ድምፄን ይሰማሉ ነው ያለው ጌታ ኢየሱስ ።

#በዚህ ምድር በድል መኖር ትፈልጋላችሁ ልጅነታችሁን እወቁ : በልዩነት በተፅኖ ፈጣሪነት መኖር ትፈልጋላችሁ ልጅነታችሁን እወቁ ስለልጅነታችሁ እወቅት ሲኖራችሁ ጠላት እንደፈለ አይጫወትባችሁም እየኮረከመ አያስለቅሳችሁ ጠላትን እያስለቀሳችሁ የድል ህይወት ትኖራላችሁ መቼ ካላችሁ ልጅነታችሁ ሲገባችሁ ።

#በመጨረሻ ይሄን ልበላችሁ ልጅነታችሁ ከገባችሁ የልጅነት ባህሪ አኗኗር ይገለጥባችሁ ልጅነታችሁን ማይመጥን ስፍራ አትዋሉ አስተሳሰባችሁ ንግግራችሁ እንደ እግዚአብሔር ቃል ይሁን ። ልጅነት ውስጥ ማድረግ ያለብንን ግዴታዎቻችንን እንወቅ ይሄም የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ካልን ለንግግራችን እንጠንቀቅ እንደፈለግን አንኑር እንደፈለገው እንጂ ይሄን በማድረግ ለሌሎች ምሳሌ እንሁን

#መልእክቱን ለሌሎች ሼር በማድረግ አብረውን ያገልግሉ ።

  🔺🀄️🀄️ሉ  ✓👇

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

08 Feb, 11:01


#አገልግሎት

#አገልግሎት ምንድነው ? አገልግሎት ጥሪ ነው ። በእግዚአብሔር ፍቃድ ምርጫ የሚመጣ ነው ። አገልግሎት በሰው ምርጫ ፣ በሰው ችሎታ ፣ ፍቃድ አይመጣም በእግዚአብሔር ምርጫ ነው ።

#አገልግሎት በዘር በዘመድ ፣ በትውውቅ አይጀመርም ። አገልግሎት በስሜት አይጀመርም : የሆነ ሞቅ ያለን ቀን ጀምረን ሞቅታው ሲለቀን የምናቆመው አይደለም ። አገልግሎት ጥሪ ፣ ፀጋ ፣ ዝግጅት ያስፈልገዋል ።

#አገልግሎት ፍቃደኝነት ይጠይቃል ። እግዚአብሔር ስሩ አድርጉ ለሚለን ለሰጠን ፀጋ መታዘዝን እና ራስን መስጠት ይጠይቃል ።

#አገልግሎት ዋጋው ሽልማቱ በዚህ ምድር ላይ ቤት ፣ መኪና መግዛት ሳይሆን የሰጠንን ፀጋ በትጋት በመፈፀም የሚሰጥ አክሊል ነው ። #የአገልግሎት ዋጋው በቴሌቭዥን ወይንም በሚዲያ ቀርቦ መታየት አይደለም በእግዚአብሔር ፊት የተዘጋጀ ርእስትና ባለጠግነት ነው ።

#ሌላው አገልግሎት መስክ ላይ የተለያየ መከራና ችግር ሊገጥመን ይችላል ነገር ግን በእግዚአብሔር ዘንድ አክሊል እንደምንቀበል አውቀን በታማኝነት ልናገለግል ይገባል ።

#በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ አገልግሎት ትንሽና ትልቅ የለውም ። እግዚአብሔር እኛ ውስጥ ሊሰራ በወደደው ሀይል ፀጋ ስጦታ ይሰጠናል እግዚአብሔር በሰጠን ፀጋና ስፍራ ልናፈራ ይገባናል ። እግዚአብሔር ያልሰጠን ቦታ ልንያዝ አይገባም ለምን ካልን ምናፈራው ውጤታማ የምንሆነው እግዚአብሔር በሰጠን ስፍራ ቦታ ነው ።

#በመጨረሻም ይሄን ልበላችሁ አገልግሎት መድረክ ላይ መስበክ አሊያም መዘመር ብቻ አይደለም እግዚአብሔር የሰጠን ማንኛውም ስጦታ አገልግሎታችን ነው ። እግዚአብሔርም ባልሰጠን ነገር አይጠይቀንም ። ለምሳሌ:- ንግድ ፣ መሪነት ፣ ማስተማር ፣ መምከር ፣ ሰአሊነት ሊሆን ይችላል እግዚአብሔር በሰጠን በማንኛውም ስጦታ በትጋት በማገልገል ፍሬ ልናፈራ ይገባል ።


#ሼር እያረጋችሁ
           🔺🀄️🀄️ሉ  ✓👇


https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

07 Feb, 04:54


."#እጁም #በራሪይቱን #እባብ #ወጋች "ኢዮብ 26፥13
በኢየሱስ ስም እየተከታተለ የተስፉ መቁረጥ ሀሳብ ፣ የእርግማንና የምዋርት ቃል ፣ በሺታና አዚም ፣ አደጋና ጭንገፉ ፣ በእኔና በእናንተ ፣ቤተሰቦቻችንም ላይ የሚረጭ እባብ ፤ የደጋሚዎች ፣የመተተኞች ድግምትና መተት በቀንና በለሊት የሚላክ የፈራረሰ ይሁን ፣ አዘዝኩት ወደ ምዋርተኞቹ ወደራሳቸው መልሼ ላኩት ፤ በስማችንና በፎቶአችን ሁሉ ላይ የሚደገም ፣ በለሊት በህልማችሁ እየመጣ የሚናደፋችሁ እባብ በትንሳኤው ጌታ በኢየሱስ ስም የተወጋ ይሁን !! ዛሬ አዋጅን በአዋጅ እሽራለሁ በኢየሱስ ስም ..ሐዘናችንን የሚሹ ይዘኑ፣ መጥፋታችንን የሚፈልጉ ይጥፉ፣ መክሰራችንን የሚጠባበቁ ይክሰሩ ፣ በእኛ ላይ ክፉ ያወሩ ያወሩት ክፉት በእጥፉ ተመልሶ ራሳቸውን ያግኛቸው ፣ ለሞታችን የደገሱ የነሱን መርዶ ይሰማ ፣ ሊሰቅሉን እንደ ሀማ መስቀያ ያዘጋጁ እነርሱ ለኛ ባዘጋጁት ይሰቀሉ፣ ሊያስደነግጠን የወጣ ይደንግጥ፣ ሊያደክመን የተላከ ይድከም ፣ በኢየሱስ ስም።

"በፍርድ በሚነሳብሺ ምላስ ሁሉ ላይ ትፈርጂአለሺ "
ኢሳ54፤17

እግዚአብሔር የህዝቡ ጋሻና ተዋጊ ነው። አሜን !!🔥🔥🔥👉👉
አሜን !!🔥🔥🔥👉👉🔥

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

06 Feb, 15:42


#ሰላም

#ሰላም ምንድነው ? ሰላም እራሱ ክርስቶስ ነው ። “ሰላምን እተውላችኋለሁ፤ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጣችሁ አይደለም። ልባችሁ አይጨነቅ፤ አይፍራም።”
  — ዮሐንስ 14፥27 (አዲሱ መ.ት)

#ሰላሜን እሰጣቹኃለው እተውላችሁሃለው ያለው ጌታ ብቻ ነው ለምን ምንጩ እራሱ ስለሆነ ። #ሰላም ሰላም ሰጩውን በማመን ነው ሚገኘው ።

#ሰላም ብዙ ሀብት ፣ ቅንጡ ቤት ውስጥ በመኖር ፣ ቅንጡ መኪና በመንዳት ሰላም አይገኙም ። #ያቺ ሳምራዊት ሴት ስንመለከታት አምስት ባሎች ቀያይራለች ግን ሰላም እርካታ አላገኘችም ለምን ሰላም ባል በመቀያየር አይገኝም ።

#ስላም የሚገኘው ከሰላም ምንጭ ከራሱ ከኢየሱስ ጋ በመጣበቅ ነው ሚገኘው ። #አስተውላችሁ ታውቃላችሁ አንዳድ ሰዎች ሲጨንቀቸው ሰላም ሲያጡ ባህር ዳርቻ የተለያዩ መዝናኛ ቦታዎች በመሄድ ሰላም ማግኘት ይፈልጋሉ ዛሬ እነግራቹሃለው ባህር ዳርቻ በመዞር የተለያዩ መዝናኛ ቦታዎች በመሄድ ሰላም አይገኝም ለምን ካልን ምንጩ እራሱ ኢየሱስ ነው ።

#ሰላም ከውጭ የምንጠብቀው አይደለም ሰላም እራሱ ጌታ ነው ይሄን ጌታ በልባችን የሾምን ያመንን ሁሉ ሰላም ከውስጥ ወደ ውጭ የምናስወጣው ነው ። ለምን ካልን ሰላሙ እራሱ ውስጣችን ስለገባ ስለዚህ ከእኛ ሚጠበቀው ከውስጥ ወደ ውጭ በማውጣት ለሌሎች የሰላም በረከት ልንሆን ይገባል ።

#ይሄን ሰላም የምትፈልጉ ዛሬ ወደ ኢየሱስ ስለ ሰላማችሁ ዋጋ ወደከፈለው ጥሪ አደርግላችኃለው በሰላም እጦት ለተጨነቃችሁ ግራ ለገባችሁ ሞታችሁን ለናፈቃችሁ ኑ ወደ ኢየሱስ እርፍ ያደርጋቹኃል እኔ አርፌ ነው ይሄን ምፅፍላችሁ ወስኑ አለም አታታላችሁ ንቁ ዛሬ ይሄን የምታነቡ ይሄን መልእክት ለሌሎች አጋሩ

#መልእክቱን ለሌሎች ያካፍሉ 👇

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

05 Feb, 12:09


#ሁለት አይነት አለም አለ

#ግዑዝ አለምና መንፈሳዊ አለም ይባላሉ ።

#ሁለቱም አለም ሀይል አላቸው ። የእግዚአብሔርም አለም የሰይጣንም አለም ሀይል አላቸው ። ነገር ግን ከእግዚአብሔር አለም ይልቅ አንድም የአጋንንት አለም ስልጣን አለቅነት የያዘ የለም ።

#የሀይላት ሁሉ ሀይል የስልጣናት ሁሉ ስልጣን የአለቅነት ሁሉ አለቅነት የያዘ አለም የእግዚአብሔር አለም ብቻ ነው ።

#የእግዚአብሔር አለም ማንነት ውስጥ መላእክት ፣ ቅዱሳን ፣ በክርስቶስ ኢየሱስ የሆኑና ያመኑ የሚኖሩበት አለም ነው ። ይህ የእግዚአብሔር አለም የምንገናኘው በውስጥ መንፈሳችን ወይንም ደግሞ ዳግም በመወለድ ነው ።

#የግዑዙ አለም ጊዜያዊ ነው መንፈሳዊ አለም ዘላለማዊ ነው ። ግዑዙ አለም የሚጠፋ ነው የእግዚአብሔር አለም ዘላለማዊ ነው ። መፅሐፍ ቅዱስ ሲናገር አለምና ሞላዋ ያልፋሉ ሰማይ ምድር ያልፋሉ ይላል ዘላለም ሚቀጥለው የእግዚአብሔር አለም ብቻ ነው ።

#መንፈሳዊ አለም እውነት ነው ። መንፈሳዊ አለም በየትኛውም ምድራዊ እውቀት መረዳት ልናውቀው አንችልም ። መንፈሳዊ አለም የምናውቀው የምንረዳው በመንፈሳችን ነው ።

#ይሄን ማወቃችን የሚጠቅመን የእግዚአብሔር አለም የሰይጣንም አለም እንዳለ እናውቃለን ማወቅ ብቻ አይደለም የሰይጣን አለም እንዳለ ማወቃችን በድልነሺነት እንደ እግዚአብሔር ሃሳብ ፍቃድ እንድንኖር ያደርገናል ። ምክንያቱም ባላወቅነው ነገር ላይ ጠላት ስለሚጫወትብን ስለዚህ ይሄን እውነት ማወቅ ነፃ ያወጣል በድል ያኖራል ።

#ለሌሎች እንዲደርስ ሼር አድርጉ👇

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

04 Feb, 15:57


#የድል ህይወት ሚስጥር

#መዝ 91:1-16.

#የድል ህይወት ለመኖር እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ያለውን ሃሳብ ማወቅ ያስፈልጋል ይሄን ስናውቅ እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ሽንፈት ፣ ውድቀት እንደማያስብ እናውቃለን ፤ እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ጭንገፋ ፣ ሀዘን አያይም ። #የድል ህይወት እንድንኖር የእግዚአብሔር ሃሳብ ነው ።

#እግዚአብሔር ለእኔና ለእናንተ መንገድ አስጀምሮ ጥሎ የሚሄድ አምላክ አይደለም ። እግዚአብሔር በህይወታችን ውስጥ መንገድ አስጀምሮ ያስጀመረውን መንገድ ያስወርሰናል ።

#የድል ህይወት በምንጓዝበት መንገድ ውስጥ ሰልፍ ፣ ውጊያ ሊኖር ይችላል : በህይወታችን ውስጥ ብዙ ተራራ ሸለቆ ሊኖር ይችላል #ግን አንድ ተስፋ አለ በሚገጥሙን ነገሮች ሁሉ እያስመለጠ ለሚገጥሙን ነገሮች ሁሉ ጥላ ከለላ እየሆነ ከተናገረን ፍፃሜ ሊያደርሰን የእግዚአብሔር ሃሳብ ነው ።

#ያዕቆብን እግዚአብሔር እንደዚህ አለው የነገርኩህን እስካደርግልህ ድረስ ላንተ የገባሁትን ቃል ፣ የተስፋ ቃል እስከማደርግ ድረስ አልተውህም አለው ። እግዚአብሔር ለያዕቆብ ።

#እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ሃሳብ ካላወቅን የድል ህይወት መኖር አንችልም ልናሸንፍ ሲገባን በተሸናፊነት እንኖራለን ዛሬ እግዚአብሔር ለእኛ ያለው ሃሳብ ይግባን ።

#ሌላው ይሄ ቁልፍ ይግባን ድል በተነሳበት ቦታ ሁሉ ጦርነት አለ ። ትልቁ ጦርነት እግዚአብሔር አሸንፎታል ። ዋናው ቁልፍ በየእለቱ የድል ህይወት ለመኖር በክርስቶስ ተሰርቶ ያለቀውን ስራችንን ማወቅ ያንን አስጠብቆ መኖር ነው ።

#በመጨረሻ የድል ህይወት ለመኖር እግዚአብሔር ኤልሻዳይ መሆኑን እንወቅ ። የምናመልከው አምላክ የምናገለግለው ጌታ ከሌሎች አማልእክቶች የሚለየው ሁሉን ቻይ አምላክ መሆኑ ነው ። በዚህ አለም ላይ ሁሉን የሚችል አምላክ የለም ይሄን ማወቅ የያዘንን የሚጠነቀቅልንን እግዚአብሔርን ማወቅ የድል ህይወት ያኖራል ።

#መልእክቱን ለሌሎች ያጋሩ ቻናሉንም ይቀላቀሉ ሌሎች መልእክቶች እንዲደርሶት

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

02 Feb, 19:39


https://www.facebook.com/share/v/15bEYSp4Uw/?mibextid=wwXIfr

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

02 Feb, 15:40


#ማስተዋል

#1ሳሙ 18:5. #ሆሴ 4:4. #ምሳ 24:3.

#ማስተዋል ምንድነው ? ማስተዋል የትኩረት አቅም ወይም ሀይል ነው ። ማስተዋል የፈጠራና የሙያ ችሎታ ወይንም የሌለንን መፍጠር ማለት ነው ።

#ማስተዋል ማለት :- ነገሮችን የመለየት ብቃት ጨለማንና ብርሃንን ፅድቅንና ኃጢአትን መለየት ማስተዋል ነው ። ማስተዋል የመንፈስ ቅዱስ ባህሪ ወይንም ማንነት ነው ።

#“እውነትን ግዛት እንጂ አትሽጣት፤ ጥበብን፣ ተግሣጽንና ማስተዋልን ገንዘብህ አድርግ።”
— ምሳሌ 23፥23 (አዲሱ መ.ት)
#ማስተዋል የእግዚአብሔር ስጦታ ነው ።

#የማስተዋል ጥቅም ምንድነው ? የምናስበውን ነገር ይገልጥልናል ፣ ትክክለኛ ውሳኔ እንድንወስን እንድንደርስ ይረዳናል ።

#የማስተዋል ጥቅም ወይንም የሚያስተውል ሰው ነገሮችን ሲያይ የሆነ ግንኙነት ሊጀምር ሲያስብ ነገ ሊሳራ ልትሰራ ካቀዱት አንፃር ነው ሚወስኑትን ሚወስኑት በስሜት አይወስኑም በማስተዋል የሚወስኑ ሰዎች ።

#የመጣ ግብዣ አይቀበሉም ነገሩን በማስተዋል ይመረምራሉ የሚያስተውሉ ሰዎች ። የሚያስተውል ሰው በውስጡ ያለውን አቅም ይጠቀማል ይዞት መቃብር አይወርድም ። #የሚያስተውል ሰው የውስጡ ሰላም ብዙ ነው ።

#ማስተዋል ከእነዚህ ነገሮች ይያያዛል :- ከንግግር ፣ ከተግባር ፣ ከስሜት ፣ ከስራ ፣ ከቤተሰብ ፣ ከተግሳፅ ስለዚህ ልናስተውል ይገባል ።

#በመጨረሻም ይሄን ልበላችሁ ማንኛውም ውሳኔ ከመወሰናችሁ በፊት በጣም ልታስተውሉ ይገባል ባለማስተዋል የወሰናችሁት ውሳኔ ነገ ማትወጡት ችግር ውስጥ ይከታችኃል ስለዚህ አስተውሉ ።

#መልእክቱን ለሌሎች ሼር በማድረግ ያጋሩ 👇

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

01 Feb, 19:24


https://www.facebook.com/share/v/19teZFiJFh/?mibextid=wwXIfr

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

29 Jan, 13:50


#ስለ ፍቅር የተሰጡ ምክሮች

#ከውስጥ በወጣ ፍቅር መኖር ይቻላል ? አዎ !  እንዴት ?

#እንደተወደድን በማወቅ ። 1ኛ ዮሐንስ 3 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ የእግዚአብሔር ልጆች ተብለን እንድንጠራ አብ አትረፍርፎ ያፈሰሰልን ፍቅር ምንኛ ታላቅ ነው! እኛም እንዲሁ ልጆቹ ነን። ዓለም እኛን የማያውቀንም እርሱን ስላ ላወቀው ነው።
² ወዳጆች ሆይ፤ እኛ አሁን የእግዚአብሔር ልጆች ነን፤ ወደ ፊት ምን እንደምንሆን ገና አልተገለጠም። እርሱ በሚገለጥበት ጊዜ እናየዋለንና፣ እርሱን እንደ ምንመስል እናውቃለን።

#እንደተወደድን ካላወቅን ሰውን መውደድ አንችልም #ለመውደድ እንደተወደድን ሊገባን ይገባል ያልገባው ውስጡ ያለውን ፍቅር ሊገልጥ ለሌሎች ሊሰጥ አይችልም ።

#መፅሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ ውደዱ ሳይሆን የተባልነው እግዚአብሔር ስለወደደን ነው ውደዱ የተባልነው ። ይሄ ሲገባን ሰው ወደደን አልወደደን አይገርመንም ።

#ውስጣችን በፍቅር እንደተሞላ እንወቅ ። ውስጣችን በፍቅር እንደተሞላ ስናውቅ መስጠትን እንጂ መቀበልን አንጠብቅም

#ውስጣችን ያለውን የፍቅር ህይወት እንኮትኩተው ። አንድ አተክልት ተክለን ዝም እንደማንለው እንዲያድግ እንደምንከባከበው በውስጣችን ያለውም ፍቅር ልንከባከበው ልንጠነቀቅለት ይገባል ። ፍቅርን እንዴት ልኮትኩተው ካልን በእውቀት ፣ በመስተዋል እንከባከበው ።

#ፍቅራችንን በመስጠት ልንገልጠው ይገባል ። ገንዘብ ብቻ አይደለም ሚሰጠው ጊዜ በመስጠት ፣ ትኩረት በመስጠት ፣ ገንቢ ቃሎችን በመስጠት ልንገልጠው እንችላለን ።

#ፍቅራችን ያለግብዝነት ይሁን ፣ ፍቅራችን በተግባር የተገለጠ ይሁን ፣ በደልን አንቁጠር    2ቆሮ 8:7.

#በመጨረሻ ፍቅራችንን ሊያጠፋ ከሚችል ነገር እራሳችንን እንጠብቅ ።

#ሼር እያደረጋችሁ 👇

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

26 Jan, 19:48


https://www.facebook.com/share/v/1AMQhue4F1/?mibextid=wwXIfr

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

26 Jan, 17:32


. #ልመስክር . ( #ውርጃን #እቃወማለሁ) ዘመቻ
ትላንትና በ #whashington dc በነበረ አንድ ትልቅ ከብዙ
ግዛቶች የተሰበሰቡ አሜሪካውያን በተገኙበት ውርጃን (#የABORTION) ህግ በመቃወም የወጡ ከምክትል አዲሱ ፕሬዜዳንት JC VANCE ጭምር ተገኝተው ንግግር ባደረጉበት ስብሰባ ከተጋበዙ አንድ የእግዚአብሔር አገልጋይ ነብይት ብርትኳን ጋር ሁለተኛ ሆኜ የመገኘት ግብዣ አግኝቼ ነበር። ከዚሁ ስብሰባ መጨረሻ ላይ #THE WASHINGTON TIMES የተሰኘው የአሜሪካን ትልቁ የዜና አውታር ቃለ መጠይቅ አድርጎኝ ውርጃን በመቃወም እንደ እግዚአብሔር ቃል ልክ እንዳልሆነና፣ የብዙ እናቶችና ነገ ተወልደው ለትልቅ አላማ የሚበቁ ህፃናትን ነፍስ እየቀጠፈ ያለ ፣ የትውልድ የዘር ማጥፉት ክፍ ድርጊት እንደ ሆነ ለመናገር እድሉን አግኝቼ ነበር ፤ ክብር ሁሉ ለእግዚአብሔር ይሁን። በዚሁ ስብሰባ የታዘብኳቸውን ጥቂት ሀሳቦች ላጋራችሁ ፈልጌ ነው ይህንን ፅሁፍ የፃፍኩት በትእግስት አንብቡትና ከተስማማች በማጋራትና የውርጃን ሀጢአትና ክፍ የአጋንንት ስራም በመቃወም አቋማችሁን በመግለጥ ተባበሩኝ።
ከአስተዋልኩት
1:- የአሜሪካንን ህዝብ ነው። በሚገርም ሁኔታ የአመጻ ልጆችና ተልእኮ አስፈፃሚዎች እንዳሉ ለፅድቅ የጨከኑ የእግዚአብሔር ሀያላንን አይቻለሁ። ብርድ ሳይበግራቸው፣ በአደባባይ ማንንም ሰይፈሩ የሚቃወሙ አመፃን።
2:- በዚያው ተቃራኒ የአመፃ ልጆችና ለነፍሰ ገዳዩ አጀንዳ ያደሩ የተገዙ ውርጃን የሚደግፉ ብዙ በጠላት እና በፓለቲካ የታወሩ እንዳሉም ታዝቤአለሁ።
3:- በዚህ ዘመን በሀገራችንም በአለም ሁሉ ዙሪያ እንደዚህ አይነት በነፃነት ፣ ደግሞ ለፅድቅ ዋጋ ሳይፈሩና ሳያፍሩ የሚሟገቱ ቢበዙ የሚል ምኞት። በተራ የመንደር የዘረኝነት ፣ የሀይማኖት ስድድብና ወሬ ወተው።
4:- የመሪዎችን እግዚአብሔርን ማስቀደም። በቃ ለምርጫ ብለው የሰውን ስሜት ከማገልገል ወተው በየአደባባዩ የፅድቅን እውነት ፣ ትልቁን ንጉስ ያነገሱ ሳያፍሩ በአደባባይ የሚያውጁ ስለ እግዚአብሔር የወገኑ
መሪዎች በሀገራችን ቢበዙልን።
5:- በጣም እጅግ የደነቀኝ ሌላው ወጣቶች ናቸው። በእንደዚህ አይነት የፅድቅ ቅንአት ተሞልተው ከየግዛቱ ተጉዘው መተው፣ ያውም በከባድ ብረድ ላይ ቆመው፣ መፎክር ይዘው፣ ብዙ ርቀት እያወጁ እየተቃወሙ ሰልፍ ሲያደርጉ በማኡቴ የኛን ሀገር ሀይማኖተኞች ፣ በየሚዲያው የሚያሳፍር ነገር እያወሩ ሳንቲም ሲለቅሙ የሚውሉ አእምሮ የጎደለው ሰው ስራ የሚሰሩትን፣ እንዲሁም በመንፈሳዊ ስም የማይጠቅም ክርክር ፣ አሳፉሪ ልምምዶች ላይ የሚባክኑትን ሳይ ፣ ቀናሁ መቼ ይሆን ቀልብ የምንገዛው፣ ምናስተውለው፣ ለሚጠቅም ፣ ለከበረ ፣ ለፅድቅ የሚኖር የሚጮህ ትውልድ የሚነሳው ብዬ።
ብቻ መልእክቴ አንድ ነው
1:- ውርጃ ነፍስ መግደል ነው። ወንዱም ሴቷም የዚህ ሀጢአት ተባባሪና አስፈፃሚ ናቸው።
2:- ውረጃ የሚያካሂዱ ሀኪሞች ለዚህ በጣም ተጠያቂ ናቸው ለገቢአቸው ሲሉ ነፍስን ሲገሉ የማይሳሱ ጨካኞች
3:- የመንግስት የፓለቲካ ሰዎች የዚህ ደም በእጃቸው አለ።
4:- እኛም በእንደዚህ አይነት ትልክ ስህተት ውስጥ ያሉትን ፣ በሀሳብ፣ በገንዘብ ፣ በተለያዩ መንገዶች በመተባበር ያለን።
5:- ከዚህ ሁሉ የከፉው የቤተክርስትያን የአገልጋዩች ዝምታ።
:- እንድትረዱልኝ የምፈልገው አንዱ እውነት ደግሞ ሴቶች ተገደው ተደፍረው፣ እና የእናትየውን ነፍስ በልዩ ልዩ ከባድ የህመምና ውስብስብ ችግር ውስጥ ያሉትንቨለማዳን የሚደረገውን አይመለከትም ሀሳቤ።
ይልቁኑ በዝሙት ፣ ከትዳር በፊትና በትዳር ላይ ከሌላ ሰው ጋር በመማገጥ የመጣ ፣ ያንን ለመደበቅ እና ኑሮን ሰበብ
በማድረግ የሚደረገውን እና ያ እድሜአቸው ከሆኑት ጋር ፣ ከስጋ ዘመድ ጋር ወዘተ የተደረገን ሀጢአት ለመደበቅ እና ወዘተ ምክንያት የሚደረግን ውረጃ እያልኩ ነው። ብቻ እግዚአብሔር ምህረቱንን እና ማስተዋሉን ይመልስልን።

:- በውርጃ ያለፉችሁ ንስሀ ግቡ ጌታ መሀሪ ነው። ደግማችሁ አታድርጉት

:- ሌሎቻችን በዚህ ድካም ያለፉትን በፍቅር እናንሳ እናንፅ እንጂ አናግልል ፊት አንንሳ።

:- ውረጃ ለአጋንንት መግቢያ ዋና በር ስለሆነ በዚህ መንገድ ያለፍችሁ የነፃ መውጣት አገልግሎት ፈልጉና አፀልያችሁ ነፃ ውጡ

:- በውርጃ ያለፉችሁ እባካችሁ የህክምና ክትትል አድርጉ እንዲሁም የምክርም አገልግሎት ፈልጉ።

:- ውርጃ መንፈሳዊ ፣ አካላዊ፣ አእምሮአዊ፣ ማህበራዊ፣ ብዙ ተፅእኖ ያደርሳልና እንንቃ። እንጠንቀቅ።

:- የውርጃ ምክንያቶችን እናስወግድ ከዝሙት መሸሽ ፣ ከቅድመ ጋብቻ እና ፣ ከትዳር ውጪ ከሆኑ ሀጢአቶች እንቆጠብ።

:- የቤተሰብ መልካም ቅድመ ትምህርት ፣ ምክር በጣም ወሳኝ ነው።

:- ወንዶች ከዚህ የግፍ ስራችን እንመለስ በዚህ ከተመላለስን ካስረገዝን በኀላ። ገንዘብ ሰበብ እያደረግን፣ ለስልጣናችን፣ ለስማችን፣ ለአገልግሎታችን ፣ ለትዳራችን በሚል ሰበብ እባካችሁን ሁለት ህይወት አንግደል። ቆም ብለን የተሻለውን እናስብ። እግዚአብሔር መበደላችን ሰያንሰን ፣ ቤተሰባችንን መበደላችን ሳያንሰን ደግመን ሌላ ጥፉት ውስጥ አንግባ የእህቶቻችን እና የነገ ተስፉ ለሆነው ፅንስ እንዘን።

:- ከስጋ ዘመድ ፣ በማስገደድ፣ ያረገዛችሁ በጣም የጠለቀ ምክር ከመንፈሳዊ መሪዊቻችሁ ፣ ከባለሙያዎች ምክር አጥብቃችሁ ፈልጉ ምንም እርምጃ ከመውሰዳችሁ በፊት።

:- ያልፈለጋቹት እርግዝና ስለተፈጠረ ፣ወይም ባላችሁ ፣ ፍቅረኛችሁ አልፈልግም ስላለ እባካችሁን ራሳችሁን አታጥፉ። መርዝ አትጠጡ። ተረጋግታችሁ አስቡ። ፀልዩ። በእግዚአብሔር ታመኑ። ተስፉ አትቁረጡ የአለም መጨረሻ አይደለም። ነገሮችን በስሜት ብቻ አትዩ ተረጋጉ።
ወንድማችሁ ፓስተር ውብሸት ነኝ
https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

25 Jan, 13:23


. አድናቆታችንንም ወቀሳችንንም በልኩ እናድርገው !
" ስለ ሁሉም የፀጋው ክብር ይመስገን "
ዛሬ ከልክ ያለፈ አድንቀን ነገ የመጀመሪያ አዋራጆቹም ፣ተቺዎችም እኛው ሆነን ስንገኝ ሰውም እግዚአብሔርም ይታዘቡናልና ፤ ሆሳና ያልናቸውን ነገ ይሰቀሉ ማለታችን አይቀርም በደጅህ ነውና በልኩ እናድርግ! ምንጩን እናመስግን።
ዛሬ ከፍ ዝቅ አድርገን ያጣጣልናቸው፣ የናቅናቸው፣
ያዋረድናቸውን ፤ነገ እግዚአብሔር ሲያነሳቸው ተመልሰን ስናጎበድድ ትዝብት ውስጥ እንዳንወድቅ። የወደቀ አይነሳምን ፣የሳተስ አይመለስምን ፣ የደከመስ አይበረታምን ? ያለውን ጌታ እናስብ። ፀጋው ታሪክ ቀያሪ
እኮ ነው!

- የበረታን ያበረታ የደከመንም የሚያበረታው ፀጋው ነው

ሰውን ሁሉ በፀጋው ውስጥ ማየት ይሁንልን
የበረታን የተሳካለትን ካየን የፀጋውን ባለቤት እናክብር
የደከመን፣ ብዙ የሌለውንም ስናይ ነገ የሚያነሳው ፀጋ እንዳለ አንዘንጋ። ራሳችንንም በፀጋው ውስጥ እንይ።
. የብርታቴ ፣ የስኬቴ ምንጭም ምክንያትም ፣ ስደክም ደግሞ የምታበረታኝ ታሪኬ ኢየሱስ ነህ ክበርልኝ አባ!!
።። የፀጋው ክብር ፣ባለቤት ይመስገን።። ኤፌ1፤ 6

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

23 Jan, 12:37


ሁለቱ አደገኛ ፅንፎች ?!
1:- ስህተትን ትክክል ለማድረግ የሚኬድባቸው መጋጋጦች ..
ስህተትን በስህተት ለማረም መሞከር ..
:- ስህተትን ለመስራትና ሰርተን ስንገኝ እነ እንትናም እንዲህ ያደርጉ የለም እንዴ የሚል ምክንያት መስጠት ?!
:- ስህተቱን የሚደግፉለት ጥቅስ እየፈለጉ ራስን ለማታለል መሞከር። ይህ እጅግ ክፉ መመለሻ ወደ ሌለው ጥፉት የሚነዳ አጋንንታዊ አካሔድ ነው።
:- ስህተት ስንሰራ መሀሪ ጌታ ፊት ወድቀን ምህረት ከመጠየቅ ይልቅ የራሳችንን ግልድሞች ሰርቶ መልበስ። ከጌታ ፊት መሸሽ ፣ እግዚአብሔር በፍፁም እንደማይቀበለን ይቅር እንደማይለን በማሰብ ከቤቱ ፣ ከህብረት ፣ እየራቁ ፤ ይልቁኑ ጭልጥ ብሎ ወደ ተሳሳተ የህይወት ልምምድ መግባት። ጌታ ምህረቱ ብዙ ነው ፤ ንስሀ ግቡና ተመለሱ እንጂ በቃ አንዴ ገብቼበታለሁ ብላችሁ በዚያው አትቀጥሉ። ለመመለስ አልረፈደም።
በቃ ከተሳሳትን ንስሀ መግባት ፣ ይቅርታ መጠየቅ ነው። just say i was rong am sorry !

2:- ፈራጅነት ..የተወሰነ ጨዋነት ሲገኝብ በቃ ሌሎችን ለማሸማቀቅ ፃድቅ ፃድቅ የሚያጫውተን ነገር ፤ ምንም ስህተት ሰርቶ እንደ ማያውቅ ሰው። የትላንት ምህረቱን የጌታን ረስቶ ። ከእግዚአብሔር ፀጋ ምህረት ላይ ማላገጥ ነው ይሄ ደግሞ። ስናስተምር ፣ ስንገስፅ ፣ ስንመላለስ እንደ መልአክ ለመምሰል በቃ ፍርድ ፣ ቅጣት ፣ ብቻ ምኑ ይቀራል.. ሌላ አምላክ ለመሆን መሞከር .. ይህ በጣም አደገኛ ፤ ከፍቅር ፣ ከፀጋው ውጪ የሆነ አካሔድ ነው ብንመለስ ይሻላል።
" ማንም የቆመ የሚመስለው ቢኖር እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ፤ ይልቁኑ ያቆመውን አምላክ ፣ ፀጋ ያስብና ትሁት ይሁን። https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

22 Jan, 12:14


“ወንድሞች ሆይ፤ እኔ ገና እንደያዝሁት አድርጌ ራሴን አልቈጥርም፤ ነገር ግን አንድ ነገር አደርጋለሁ፤ ከኋላዬ ያለውን እየረሳሁ ከፊቴ ወዳለው እዘረጋለሁ።”
  — ፊልጵስዩስ 3፥13 (አዲሱ መ.ት)

#ከላይ ያለው ክፍል የሚናገረው ስለ አላማ ነው
#ምንድነው ከኃላ ያለው ?
#ምንድነው ከፊት ያለው ?

#ወዴት ነው ሚዘረጋው ? ከየት ነው የመጣው ?
#ጳውሎስን አመጣጡን ሁላችሁም ታውቃላችሁ ሃይማኖተኛ አሳዳጅ ነበር ሐዋርያት ስራ 9  ደማስቆ ላይ ጌን ከማግኘቱ በፊት ለሃይማኖት የቀና መስሎት ጥሩ አሳዳጅ ነበር ከዛ ሁሉ አውጥቶ ታሪኩ ተቀይሮ የሚያሳድደውን ወንጌል ሰባኪ ትውልድ ተናጣቂ ያደረገው ትላንት የሚያሳድደውን ወንጌል ዋጋ የሚከፍልለት ወንጌል እንዳደረገው

#ዛሬ አንድ ነገር ልበላችሁ ከየትም ኑ ትላንታችሁ ነጋችሁን አይወስነውም ይህ ማለት ነገ እግዚአብሔር ትደርሳላችሁ ካላችሁ ስፍራ ላይ እንዳትደርሱ ሊከለክላችሁ አይችልም

#ጳውሎስ እያለን ያለው የመጣውበት የኃላ ታሪክ መያዝ አልፈልግም ጳውሎስ ከየት እንደመጣ ታውቃላችሁ የመጣበት አለ ግን ሊደርስበት ካለው አላስቆመውም ።

#ትላንታችንን አልፎ ቀይሮ ታሪክ አድርጎ በእኛ ይሰራል ። መፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያሉ ሰዎች ትላንታቸው ብዙ የተበላሸ ነበር እግዚአብሔር ሊሰራ ትላንታቸው አልከለከለውም ።
#ትላንታችን ምስክር ፣ ልምድ ፣ ማመስገኛ ሊሆን ይችላል ትላንታችን እንቢ ካላልን ነገን እሺ ማለት አንችልም ።

#ትላንቱን ያልተፋታ ነገውን ማግባት አይችልም ። ትላንታችን ስኬት ሊሆን ይችላል ትላንታችን ውድቀት ሊሆን ይችላል ነገር ግን ውድቀትም ይሁን ስኬት ነጋችንን አይወስንልንም ከሁለቱም ሰብረን ወደታየልን ወደ ትልቁ ስፍራ ልንገሰግስ ይገባል ።

#ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

20 Jan, 14:48


#ታማኝነት

#ታማኝነት ማለት ምን ማለት ነው ?
ታመኝ ማለት አጥፍቶ ከሆነ ጥፋቱን አውቆ ይቅርታ የሚጠይቅ
#ታማኝ ማለት ይሄን አደርጋለው ብሎ ተናግሮ ከሆነ የተናገረውን ቃል የማያጥፍ
#ታማኝ ማለት ለእግዚአብሔር ቃል የሚታዘዝ ፣ የሚፀልይ ማለት ነው
#ታማኝ ማለት ለገባው ቃል የሚገኝ ማለት ነው ።

#የእግዚአብሔር ቃል ስለታማኝነት ምን ይላል ?

#ታማኝ ማለት Integration ከሚል ቃል የመጣ ነው ወይንም ቅዱስ ማለት ነው
እግዚአብሔር አንድ አምላክ ነኝ ሲል ሁለት ማንነት እኔጋ የለም እያለ ነው ።

#ውስጤና ውጭዬ አንድ አይነት ነው አይለያይም እያለን ነው ። “ሰዎችን የሚቀድሰውና የሚቀደሱት ሰዎች ከአንድ ቤተ ሰብ ናቸው፤ ስለዚህ ኢየሱስ ወንድሞች ብሎ ሊጠራቸው ዐያፍርም፤”
  — ዕብራውያን 2፥11 (አዲሱ መ.ት)

#አንድ እንደሆንን የሚቀደሱትና የሚቀድሰው ከአንድ ናቸው ይለናል  ሁለት አይነት መልክ የሌለው የማያስመስል የሚናገረውና የሚኖረው አንድ አይነት ማንነት ያለው ማለት ነው ።

#እግዚአብሔር ቃሌ ከሚያልፍ ሰማይና ምድር ቢያልፍ ይሻላል ያለው እኔና ቃሌ አንድ ነን ለማለት ነው ።

#ኢየሱስ ትላንትናም ዛሬም እስከለዘለአለም ህያው ነው ሲል አንድ አይነት ባህሪ ነው ያለኝ እያለ ነው ። ማቴ 25:11. ሉቃ 16:10.

#ሰአት አለማክበር አለመታመን ነው ስለዚህ ሰአት በማክበር ታማኝነታችንን ማሳደግ አለብን አነዛ አስሩ ቆነጃጅቶች ውስጥ አምስቱ መብራታቸውን ዘይታቸውን ይዘው ጌታን ሲጠብቁ 5ቱ ሰነፎች ዘይታቸው አልቆ የጌታ መምጫ ሰአት ላይ ዘይት ሊገዙ ወተው ሲመለሱ በሩ ተዘግቷል አያችሁ ሰአት አለማክበር የጌታን ቃል አለመጠበቅ ታማኝ አለመሆን ነው ።

#እግዚአብሔር ዛሬም ታማኝ ሁኑ ሲለን ቃላችሁን ጠብቁ የተናገራችሁትን ኑሩ እያለን ነው ።

#ሼር አድርጉ ሌሎችም ይጠቀሙ

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

16 Jan, 12:52


#ትጋትና ስንፍና

#ስንፍና ምንድነው ?  ስንፍና ከሌሎች ሰዎች ጋ ባለን ግንኙነት እንዴት ይገለጣል ? ስንፍና ከእግዚአብሔር ጋ ባለን ግንኙነት እንዴት ይገለጣል ?

#ስንፍና ህይወታችንን በትክክል እንዳንኖር ሰርተን እንዳንለወጥ ለሌሎች እንዳንተርፍ የሚያደርግ የሰው ባሪያ የሚያደርግ ባህሪ ነው ።

#ስንፍና ከሌሎች ሰዎች ጋ ባለን ግንኙነት በስራ ይገለጣል ፣ በንግግር ይገለጣል ፣ የተናገርነውን ባለመተግበር ቃልን ባለመጠበቅ ታማኝ ባለመሆን ይገለጣል ።

#ስንፍና ከእግዚአብሔር ጋ ባለን ግንኙነት በስራ ባለመትጋት የተሰጠንን አደራ ባለመወጣት ይገለጣል የወንጌል አደራ ተስጥቶናል ያን በትጋት አለመስራት የሆኑ ሰዎች ስራ ማድረግ ስንፍና ቸለተኝነት ነው ። ሌላው ባለመፀለይ ፣ ቃሉን ባለማጥናት ይገለጣል ። ስለዚህ ልንተጋ በሚገባን ሁሉ ልንተጋ ይገባል

#ሌላው  ስለአምላካችንና አባታችን ስለእግዚአብሔር  ማወቅ አለብን ?

#“ኢየሱስም፣ “አባቴ እስካሁን እየሠራ ነው፤ እኔም ደግሞ እሠራለሁ” አላቸው።”
  — ዮሐንስ 5፥17 (አዲሱ መ.ት)
ኢየሱስ አባቴ ሰራተኛ ነው እኔም እሰራለው አለ ስለዚህ እግዚአብሔር አባታችን የሚሰራ ከሆነ እኔና እናንተ ለምን እንሰፋለን ለምን ትሰፋላችሁ መንፈስ ቅዱስ ዛሬም በስራ ላይ ነው ስንፍና የአባታችን ህይወት አይደለም ።

#ከእግዚአብሔር ተወልጃለው ካልን የእግዚአብሔር ዘር እኔ ውስጥ አለ ካልን የእግዚአብሔር ዘር ውስጥ ስንፍና ከሌለ ስንፍናን ከየት እንዳመጣችሁት ፈልጉ ከዛ አባሩ ስንፍና የምትንከባከቡት ጉዳይ አይደለም ።

#በአንድ ነገር ሰነፍ ከሆናችሁ በብዙ ነገር ሰነፍ ትሆናላችሁ በመንፈሳዊ ነገር ብርቱ ነኝ በስራ ግን ሰነፍ ነኝ ብትሉ ትዋሻላችሁ በመንፈሳዊ ነገር ትጉ የሆነ ሰው በስራው ትጉ ነው ። በትምህርቱ ትጉ የሆነ ሰው በመንፈሳዊ ህይወት ትጉ ነው ።

#ስራን ስናስብ ብዙዎች የውድቀት የኃጢአት ውጤት ይመስለናል ግን አይደለም ትጋት ለሰው ልጅ የከበረ ሀብቱ ነው ። ትጋት ኃጢአት ነው አይልም ። ከንቱ ትንቢት እየሰማችሁ ሰርታችሁ መለወጥ አታስቡም ዘይት በመፍሰስ እጅ በማስጫን ብቻ መለወጥን ሚሊየነር መሆንን ታስባላችሁ ግን አይሆንም

#በዚህ አለም ላይ የምንኖርበት የህይወት ስርአት የእግዚአብሔር ህይወት እንድንካፈል ብቻ ሳይሆን እንድንሰራም ይፈልጋል በክርስቶስ ዳግም የተፈጠራችሁት መልካሙን ስራ ለመስራት ነው ። መልካም ስራ ወንጌል ብቻ አይደለም አጋንንት ማስወጣት ብቻ አይደለም ። #መልካም ስራ ንግድ ነው ፣ መሪ መሆን ነው ፣ በስራ ሁሉ በመሰማራት ተፅኖ ማምጣት ነው መልካም ስራ ስለዚህ በመልካም ስራ ሁሉ ትጋትን ጨምሩ ለስንፍና እድል ፈንታ አትስጡ የዛሬ መልእክቴ ነው ።

#ሼር አድርጉ 👇

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

15 Jan, 12:14


“በለሱን የጠበቀ ፍሬዋን ይበላል፥ ጌታውንም የሚጠብቅ ይከብራል።”
— ምሳሌ 27፥18

#መጠበቅ ማለት ምንም አለመስራት ሳይሆን የተሰጠንን በለስ መንከባከብ ነው #አዲሱ መደበኛ ትርጉም ላይ በለሱን የሚንከባከብ ይለዋል" እናም አንድ አትክልት ተክለን ባንከባከበው በቃ ውሃ ባናጠጣው ባንኮተኩተው ከመለምለም ወደ መድረቅ ነው ሚሄደው ለምን ነገ የምንፈልገውን ፍሬ ለማግኘት ዛሬ ከተከልንበት ቀን ጀምሮ መንከባከብ የሚያስፈልገውን ማድረግ ይጠበቅብናል።

#ሌላው አንዳዶቻችን በለሱን የጠበቀ የሚለው እጅና እግር አጣጥፎ ቁጭ ብሎ ጌታን መጠበቅ ይመስለናል ግን አይደለም።

#መጠበቅ ማለት የራስን አቋራጭ አለመጠቀም ጌታ በሚሰጠን መንገድ ዋጋ ቢያስከፍልም ነገ ትክክለኛው ፍሬ ጋ ለመድረስ ከእግዚአብሔር አሳብ ጋ መጓዝ ማለት ነው።

#መጠበቅ ማለት መቀመጥ አይደለም ከእግዚአብሔር ቃል ጋ ከፍቃዱ ጋር መስማማት ነው።ቃሉንም የራሴ ፍቃድ እያሉ እያምታቱ እጠብቃለው ማለት አይደለም።

#ከጠበቅን አይቀር እንደ ቃሉ ሆነን መጠበቅ ይሁንልን ጊዜያችን እንዳይባክን #እግዚአብሔር ለአብርሃም በልጅ እንደሚባርከው ቃል ገብቶለት መጠበቅ ያልቻለው አቋራጭ የተጠቀመው አብርሃም ነው #ታዲያ አቋራጭ ተጠቅሞ ያመጣው እስማኤል እንደገና ጭንቅ ሲሆንበት እናያለን #መጠበቅ ማለት ስፍራ አለመልቀቅ ነው አቋራጭ አለመጠቀም ነው አድካሚ ቢሆንም ወደፊት መራመድ ነው ።

#ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ👇

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

14 Jan, 11:43


PRIDE (ትእቢት) :- የሌዋታን መንፈስ ባህርይ ነው። 2ተሰ2፤4 ,
ትዕቢት አስጢንን :- ንግስናዋን አሳጥቷታል ፣ ትዳሯን አሳጥቷታል
ትእቢት ናቡከደነፃር የተባለን ንጉስ :- ሳር አስግጦታል ከቤተ መንግስት አስወጥቶ አዋርዶታል

:-እግዚአብሔርን ትዕቢትን ብቻ ሳይሆን ትእቢኛንም ይቃወማል !
GOD REJECT PRIDEFULL PERSONALITY ያቆ4፤6 ማቲ23፤12 ሉቃ18፤14 ምሳ11፣2 16፤18

:- ትእቢት ያዋርዳል ...ዳን4፤37
:- ትእቢት ለአጋንንት አሳልፎ ያሰጣል 1ጢሞ3፤6
:- ትእቢት ብዙ እድል ያስመልጠናል ።።። aportunity

ትእቢት :- ያለ ማደግ ፣ የስጋዊነት ፣፣ ምንጭን ያለማወቅ ፣ አላማን የመሳት ፣ በእግዚአብሔር ያለመታመን ውጤት ነው። 1ጢሞ3፤6, 6፤4 2ጢሞ3፤4 ሰፎ3፤13

:-ትእቢት ከአስተሳሰብ እና ከልብ ሞቲቭ ብልሹነት መንጭቶ ፤ በአንደበት የንቅ፣ የትእቢት ንግግር በማለፍ፣ በአለመታዘዝና በማመፅ የሚገለጥ ኑሮ ነው።

:- ትእቢት በአምነቱ የደከመን ስናይ የምናሳየው የልብ እና የእይታ ፣ የምንሰጠው አስተያየት ውስጥ የሚገለጥ በራስ የመመፃደቅ ባህርይ ነው ሮሜ11፤20
:-ትእቢት በነገሮች መሳካት ወቅት ምንጭንና አላማን በመሳታችን የሚታይብን ባህርይ ነው።


በትእቢት እግዚአብሔርን የሰጣችሁን እንዳታጡ ትሁታን ሁኑ

የትእቢት ምንጮች ምንድ ናቸው ??
ሰይጣን ነው
ምንጭን ያለማወቅ ነው
ነገን ማየት ያለመቻል ውጤት ነው
አላማን የመዘንጋት ውጤት ነው

ሰው በምን ምክንያት ትእቢት ውስጥ ሊገባ ይችላል ? 1ጴጥ1፤24
በተሰጠው ውበት ፣ቁመና
ባለው ሀብት ፣ባለጠግነት
ባለው ዝና ፣ክብር ፣እውቅና ፣ብዛት የተነሳ
ካለው እውቀትና ፣ጥበብ ፣ችሎታ የተነሳ
በተሰጠው ፀጋ ፣በሱ እግዚአብሔር ሲሰራበት

ከእግዚአብሔር በስተቀር የምንመካበት አይኑረን ሁሉ ጊዜአዊ ጠፊ ነው
1ቆሮ1፤ 28-30

ትህትናም ትእቢትም የአስተሳሰብ የልብ ከሞቲቭ መበላሸት ነው የሚጀምረው።
it is attitude . tought ሮሜ12፤16 ማር7፤22 ሮሜ12፤3 ሮሜ12፤20

ትእቢት ከአስተሳሰብ ብልሹነት መንጭቶ በአንደበት በንቀት ንግር በመገለጥ ፣ በጠብ ተግባር የሚገለጥ ክፉ መራራ ስር ነው። ይነቀል ። መዝ31፤18 ምሳ13፤13 14፤3

የትእቢት መድሀኒቱ በትህትና መመላለስ ነው። ያቆ4፤ 6 ፊሊ2፤1-5 ማቲ11፤29
ትህትናን በእግዚአብሔር ፊት። ያቆ4፤6 ቆላ3፤12
ትህትናን እርስ በእርሳችን እናሳይ። ሮሜ12፤16 ኤፌ4፤2

.ትህትና ቆላ3፣12
ትህትና እግዚአብሔርን የመምሰል ህይወት ባህርይ ነው።
ትህትና ምንጭን የማወቅ ፣ አላማን የማወቅ፣ ነገን የማየት ጥልቅ ብስለት ነው።
ብዙ የመቀበያ ፣ ከደረጃ ወደ ደረጃ የማደግያ ፣ በዙፉናችን የመቆያ ጥበብ ነው። ትህትና ለጠላት በር ይዘጋል፣ ህብረትን ይጠብቃል ፣ በሰላም ፣በደስታ ያለ ስጋት ያኖራል

ትሁት ሰው ማለት በእግዚአብሔር የሚታመን ሰው ማለት ነው ሶፎ3፤12

ትሁት ሰው ማለት
በእግዚአብሔር የሚታመን ሰው ማለት ነው ሶፎ3፤12
ትሁት ሰው ማለት ክርስቶስ የለበሰ ሰው ማለት ነው
ትሁት ሰው ማለት አስተሳሰቡ በኢየሱስ አይነት አስተሳሰብ የተሞላ ማለት ነው
ትሁት ሰው ማለት ምንጩን ያወቀ የሁሉን ሰጪ የተረዳ ማለት ነው
ትሁት ሰው ማለት የፍቅር ሰው ማለት ነው
ትሁት ሰው ማለት የተሰጠውን ነገር የተቀበለበትን አላማ የተረዳ ማለት ነው
https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

13 Jan, 05:29


#ስለ እግዚአብሔር አባትነት የማወቅ ጥቅም

#ዮሐንስ 8 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁷ የአብርሃም ልጆች መሆናችሁን ዐውቃለሁ፤ ነገር ግን ቃሌን ስለማትቀበሉ ልትገድሉኝ ቈርጣችሁ ተነሥታችኋል።
³⁸ እኔ በአባቴ ዘንድ ያየሁትን እናገራለሁ፤ እናንተም ከአባታችሁ የሰማችሁትን ታደርጋላችሁ።”

#በእግዚአብሔር ፊት በሙሉ ድፍረት ያለምንም መሸማቀቅ ለመመላለስ ፊቱ ለመቅረብ ይጠቅማል #የእግዚአብሔር አባትነት ስናውቅ በሰይጣንም በሰውም ፊት ሳንፈራ እንወጣለን እንገባለን #የእግዚአብሔርን አባትነት ማወቅ full confidence እንዲኖረን ያደርጋል

#ዮሐ 8. ስታነቡ ኢየሱስ ስለ አባቱ ስለ አብ በሙሉ confidence ይናገራል የሚያደርገውን ሁሉ ሲያደር እኔ ከአባቴ ያየሁትን እያለ ስለ እግዚአብሔር አባትነት በብዙ ይናገራል ስለ አባቱ ሙሉ እውቀት ነበረው ሊያጠምዱት ምክንያት ለሚሹ ዙሪያው ለሚዞሩ ስለእግዚአብሔር ስለአባቱ በደንብ ይነግራቸው ነበር ለምን ስለሚያውቅ

#ለዚህም ነው ሊገድሉ ይፈልጉት የነበረው #አንድ ልናውቅ ሚገባው ስለ እግዚአብሔር ስለ አባታችን ጠንቅቀን ባወቅን ቁጥር ሰይጣን እየፈራን ይመጣል

#ይሄ ብቻ አይደለም ስለ አባታችን ባወቅን ቁጥር የተገባንን ኑሮ መስራት ያለብንን ስለምንሰራ ስራውን ስለምናፈርስ ታውቃላችሁ እንድናውቅ አይፈልግም ለምን የእግዚአብሔር አባትነት በማወቅ ውስጥ ያለውን ጥቅም ያውቃል ለሰይጣን ግዛት እንደማንገኝ ያውቃል ለዚህ ነው አባታችንን እለት እለት ለማወቅ መበርታት ያለብን

#ወደ አሳቤ ስመለስ እግዚአብሔር አባታችንን ስናውቀው የምናየው የምንሰማው አያስደነግጠንም ፣ የሚፈስ ውሃ ሁሉ ይዞን አይሄድም ስለዚህ እግዚአብሔር አባቴ ማነው ብለን ለማወቅ እንትጋ

#ያወቅነው እውነት ነው አርነት ሚያወጣን #ዮሐ8:32

#ሼር ማድረጋችሁን ቀጥሉ 👇

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

12 Jan, 05:50


.                የሰላም  ዋጋ   !
"የውስጥ ሰላም  ከሁሉ ጋር  በሰላም የሚያኖር  የሰላም ምንጭ ነው"
      ሰላም ሰላምን ስለፈለግን ብቻ አይመጣም ! 
በአለም ላይ እስከዛሬ ውጤታማና ዘላቂ ሰላሞች የሚባሉት የመጡት በአሸናፊና ተሸናፊ መኖር ፤ በጦርነት የመጡት ሳይሆን በድርድር  እንዲሁም ሰቶ በመቀበል እና በእርቅ የመጡት ናቸው።

ሰላም የአንድ  ወገን ፍቃደኛነት እና ሀላፊነት ብቻ ሳይሆን የሁለቱም ወገን ቁርጠኛ በተግባር የተቃኘ እርምጃ  ውጤት ነው።

ሰላምን  ማምጣትና ማረጋገጥ  የሚቻለው ፣ችግሮችንና የመፍትሔውን አስፈላጊነት ፤ከራስ ጥቅም አስበልጦ ፤ አርቆ  ትውልድን ማሰብ ሲቻል ብቻ ነው

ለሰላም ሲባል ዝቅ ማለት ፣ ነገሮችን መተው መለማመድ ሞኝነትና ተሸናፊነት የሚመስላቸው ፤ በስሜት የሚጋልቡ ፣ ዛሬን ብቻ እንጂ ነገን የማያልሙ ፣ በትላንት ቂም በቀል እና በራስ ጥቅም የታወሩ  ሰነፎች አመለካከት ነው።
  
ተባርካችኀል

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

11 Jan, 03:56


#የፍቅር ባህሪያት

#ፍቅር ከሰጪው እንጂ ከተቀባዩ አይጀምርም ፍቅር እግዚአብሔር ነው ።
#ዮሐ 4:14. ፍቅር ስጦታን አይቶ አይጀምርም ። ፍቅር የዚህ አለም መፍትሄ ነው የመጨረሻውና የህይወት ጥግ ፍቅር ነው ።

#ፍቅር ከውጭ የምንጠብቀው ሳይሆን ከውስጣችን የሚወጣ ነው ። #እርሱ አስቀድሞ ወዶናልና እኛም እንወደዋለን ። #ፍቅር የሚጀምረው ከአፍ ቃል ወይም ከተፈቃሪው ሳይሆን ከአፍቃሪው ነው ።

#ፍቅር የኃጢአትን ብዛት ይሸፍናል ። #ሰዎች በፍቅር መኖር ሲያቆሙ የሰውን ውድቀት ኃጢአት ለመግለጥ ይታገላሉ ። #የጨለማን ስራ ግለጡ ማለት የወንድምን ሚስጥር ግለጥ አብራራ ማለት አይደለም ።

#እግዚአብሔር እውነትን አይሸቃቅጥም ኃጢአትን መግለጥ ስላልቻለ አይደለም ነገር ግን ፍቅር ስለሆነ ኃጢአትን ይደብቃል ከኃጢአት ሊያነፃ ያስተምራል ይመክራል የእግዚአብሔር መንፈስ ሰውን አይከስም ።

#ፍቅር ላይ ፍርሃት የለም 1ዮሐ4:19. እግዚአብሔር ይቀስፈኛል ብላችሁ የምትፈሩ ከሆነ ከምህረቱ ይልቅ እግዚአብሔር ነፍሰ ገዳይ ይመስለናል በእግዚአብሔር ፍቅር ሙላት ውስጥ የሚኖር ሰው በፍርሃት አይኖርም ።

#ፍቅር ሁልጊዜ ማካፈል ይወዳል ። 1ዮሐ3:16-17. እግዚአብሔር ፍቅሩን የገለጠልን ማንኛውንም ነገር የሰጠን ሸሽገነው እንድንቀመጥ አይደለም #ምህረቱን የሰጠን ምህረት እንድናደርግ ነው #ይቅር ያለን ይቅር እንድንል ነው #ፍቅር የሰጠን ፍቅር እንድንሰጥ ነው ።

#ስለዚህ እግዚአብሔር ያልሰጠንን ስጡ አላለንም ህይወት ስለተሰጠን ህይወት እንሰጣለን ።

#በመጨረሻ የእኛ ኃጢአት እንደተተወልን ካላስተዋልን ሌላውን አንተውም ባለዕዳው ሰውዬ የዕርሱ ዕዳ ተትቶለት እርሱ አለመተው ይገርማል እናም የተተወልን የኃጢአት እዳ ማስተዋል ይሁንልን የበዛልን የጌታ ምህረት ይታወቀን ። #ማቴ 18:28-35.

#ሼር ማድረግ እንዳይረሳ ሌሎችም ይጠቀሙ👇

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

10 Jan, 06:05


#ወንጌል ምንድነው ?

#መፅሐፍ ቅዱስ ስለ ወንጌል ምን ይላል ?
“ወንጌሉም ስለ ልጁ፣ በሥጋ ከዳዊት ዘር ስለ ሆነ፣”
  — ሮሜ 1፥3 (አዲሱ መ.ት)

#“ጳውሎስ፣ የክርስቶስ ኢየሱስ ባሪያ፣ ሐዋርያ ሊሆን የተጠራና ለእግዚአብሔር ወንጌል የተለየ፤”
  — ሮሜ 1፥1 (አዲሱ መ.ት)
#ጳውሎስ ለወንጌል እንደተለ ይነግረናል ።

#ታዲያ በዚህ ሰአት ሀሳባችንን የተቆጣጠረው ዝባዝንኬ ነገር ነው ወደ ወንጌል መመለስ አለብን ወንጌል የሚመስሉ ነገሮች እየተሰበከ ነገር ግን ወንጌል ያልሆነ ነገር እየተሰበከ ነው ።

#በዚህ በመጨረሻው ዘመን ከምን ጊዜውም በላይ የልጁ የኢየሱስ ክርስቶስ መገለጥ ዳግም መምጣት በተቃረበበት ዘመን የዚህ የወንጌል እውነት በተለያዩ መንገዶች እና በሚገርም ፍጥነት ለአለም መሰበክ በሚገባበት ጊዜ ሚዲያዎቻችንን መድረኮቻችንን የያዘው የተቆጣጠረው ሀይማኖት እና ፓለቲካ ነው ።

#ለእኛ ግን እግዚአብሔር ሊነግረን የሚፈልገው ከፖለቲካ : ከሀይማኖት እንድንወጣ እና ዋናና ቀዳሚ ዋና ነገራችን ወንጌል ላይ እንድናተኩር ትውልዱን ከጨለማ አለም እንድንናጠቅ ነው ።

#አለም በክፉ በጨለማ ተይዛለች ወንጌል ብርሃን ትፈልጋለች ይሄን ልናደርስ ይገባል በጨለማው አለም የልጁን መገለጥ ልናውጅ ልንናገር ያስፈልጋል ።

#መቅደም ያለበት ነገር ወደ ስፍራው ሊመለስ ስፍራ ያያዘ ተከታይ ነገር ስፍራ ሊለቅ ይገባል ። ቤተክርስቲያን ፣ አገልጋዮች ወደ ወንጌል መመለስ አለብን ።
#የስብከታችን ርዕስ ትኩረታችን ኢየሱስ መዳን ያለበት ትውልድ ላይ ሊሆን ይገባል ።

#ኢየሱስን ስጋ ለብሶ እንዲመጣ ያደረገው ምክንያት ወንጌል ነው ። ይሄ ወንጌል ልንዘነጋው በፋሽን ልንቀይረው አይገባም ። ዛሬ እንንቃ

#ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ 👇

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

09 Jan, 06:16


#የደህንነታችን እርግጠኛነት
. ከስጋት ውጪ የሆነ የፀና የተረጋገጠ መዳን
#የመዳናችን #እርግጠኛነት #የተረጋገጠ ነው።
በሰማያዊ ስፍራ በአብ ቀኝ አንዴ የተቀመጠ ተመልሶ አይባረርም።ወደ ኢየሱስ የመጣ ተመልሶ አይወጣም በኢየሱስ መንግስት በደሙ በሰራው ስራ በሱ ፀጋ አስገብቶናልና ፣ ስህተት ብንሰራ እንኳ ይመልሰናል ይገስፀናል ፤ እንጂ በፍፁም አያስወጣንም ከመንግስቱ ኤፌ2፤7 ዮሐ 6፤37

የዳነው በእግዚአብሔር ፀጋ ብቻ በማመናችን እስከሆነ ድረስ ፣መዳናችንን ሊያሳጣን የሚችል ምንም አይነት ስራ የለም። ኤፌ2፤8

የፀደቅነው ለዘለአለም እስከሆነ ድረስ ይህን ፅድቅ የሚያሳጣን የሚቀንስብን ፣ ምንም አይነት የሀጢአት ወይም የሰይጣን ሀይል የለም ዕብ10፤12,14

ካዳንን በኃላ የተያዝነው በራሱ በእግዚአብሔር እጅ ነውን
ከሱ እጅ የሚያወጣን ስለሌለ አንሰጋም መዳኔን ላጣ እችላለሁ ብለን። ዮሐ 10፤29

የተያዝነው በኢየሱስ እጅ ስለሆነ ከኢየሱስ እጅ ማንም ሊነጥቀን የሚችል የለም ዮሐ 10፤28

ኢየሱስ የሰጠን ህይወት የዘለአለምና ፣ ለዘለአለምም የማይጠፉ እንደሆነ እራሱ ስለነገረን አንሰጋም ፣ መዳኔን ላጣ እችል ይሆን ወይ ብለን። ዮሐ10፤ 28

የተጠበቅነው በራሳችን አቅም ሳይሆን በእግዚአብሔር ሀይል ስለሆነ በፍፁም ስለመፅናታችን አንሰጋም 1ጴጥ1፤5

የተወለድነው ተመልሶ ሊጠፉ ከማይችል ዘር ስለሆነ አንዴ ከዳንን በኃላ ተመልሰን አንጠፉም። 1ጴጥ 1፤ 23።

በእኛ መልካምን ስራ የጀመረው እራሱ እግዚአብሔር ፤ይህንን መዳን እስከመጨረሻው አፅንቶ የሚጨርስው እርሱ ስለሆነ ፤ እኛ የጀመርነው የምንጨርሰው ህይወት ስላልሆነ አንሰጋም፣ እርግጠኞች ነን። ፊሊ1፤6


#መሰረቱ የፀና ፍፁም ሰላም ያለው ፀጥታና መታመን ውስጥ ለዘለአለም ያለ ስጋት የሚያኖር ዘላለማዊ በመዳናችን እርግጠኛ አድርጎ የሚያኖር በእግዚአብሔር ፅድቅ ላይ የሆነ በእኛ ስራ ላይ ያልተመሰረተ ፅድቅ ነው ።

“የጽድቅ ፍሬ ሰላም፣ የጽድቅ ውጤትም ጸጥታና ለዘላለም መታመን ይሆናል።”
— ኢሳይያስ 32፥17 (አዲሱ መ.ት)

#እምነታችን በእግዚአብሔር ፅድቅ ላይ መሆኑ የደህንነታችንን መሰረት ፅኑ ያደርገዋል ። በራሳችን ስራ ካልፀደቅን የእግዚአብሔር ፅድቅ ደግሞ የማይሻር የማይደበዝዝ በኢየሱስ ደም የፀና ፅድቅ ስለሆነ ነገ እናጣው ይሆን ወይ ብለን በፍፁም በመዳናችን አንሰጋም ።

#ደህንነታችን ልክ በራሳችን ስራ እንዳመጣነው ጠብቆ ለመኖር ማሰብ ስህተት ነው ። ፍፁም ዋስትናን የሚሰጠው የእግዚአብሔር ፅድቅ ነው ። የሰው ስራ የራስ ፅድቅ መቼም ዋስትና አይሰጥም ሊሆንም አይችልም ።

#እግዚአብሔር አይዋሽም በእኔ የሚያምን የዘላለም ህይወት አለው አይጠፋም ካለን አንጠፋም ልናምነው ይገባል ። ወደ ፍርድ ላንመጣ ድነናል ። “ይዋሽ ዘንድ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ሰው አይደለም፤ ይጸጸትም ዘንድ የሰው ልጅ አይደለም፤ ተናግሮ አያደርገውምን? ተስፋ ሰጥቶስ አይፈጽመውምን?”
— ዘኍልቁ 23፥19 (አዲሱ መ.ት)

#“እነርሱ የአንተ ስለሆኑ እጸልይላቸዋለሁ፤ ለሰጠኸኝና የአንተ ለሆኑት እንጂ ለዓለም አልጸልይም።”
— ዮሐንስ 17፥9 (አዲሱ መ.ት)
#እርሱ ስለእኛ እየፀለየና እየማለደ ስለሚኖር በእሱ ሀይል ተጠብቀን እንኖራለን የሚያሰጋን ምንም ነገር የለም ።

. በነፃ የተሰጠ ፣ ከፍውሩ የተነሳ የተሰጠን ስጦታ ተመልሶ
አይወሰድብንም። ስጦታ ሰቶ የሚፀፀት የፍቅር ስጦታ የሰጠ አይደለም። ስጦታ የተቀባወዮን መልካም ስራ የሚያሳይ ሳይሆን ወይም የስራ ውጤት ሳይሆን የሰጪው የፍቅር መገለጫ ነው። እግዚአብሔር በፀጋ ስጦታውና በመጥራቱ ስለማይፀፀት መልሶ የሰጠንን ህይወት መዳን አይወስድብንም። ሮሜ11፤29

#ብዙዎች ዛሬ በመዳናቸው እርግጠኛ የማይሆኑበት ምክንያት ካዳናቸው ከሚጠብቃቸው የእግዚአብሔር ፀጋና ሀይል ወተው እምነታቸው በራሳቸው ስራና ብቃት ላይ ስለሚያደርጉ ነው ። እግዚአብሔርን ስለሚጠራጠሩ ነው ። እርሱ ግን አይዋሽም በመዳናቸን እርግጠኛ እንሁን ።

# ሼር አድርጉ ሌሎችም ይጠቀሙ👇 እናንተም ተከታተሉን
https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

08 Jan, 11:58


#ለምንድነው በፍቅር መመላለስ ያለብን ?

#ስለተወደድን :- እግዚአብሔር እንዴት አድርጎ እንደወደደን እንወቅ እርሱ አስቀድሞ ወዶናል እና እኛም እንወደዋለን ። ያልተወደደ ሰው መውደድ አይችልም ። እስከ ኃጢአቴ ስለተወደድኩ እወደዋለው ።

#በፍቅር የምንመላለሰው የተካፈልነው ዘር ፍቅር ስለሆነ እግዚአብሔር እርሱ በእኛ ውስጥ እያለ አለማፍቀር አንችልም ። ዳግም የተወለደ ሰው ፍቅር በውስጡ ስላለ መጥላት አይችልም ። የፍቅር ህይወት ፣ የፍቅር አለም ብቻ ነው በውስጡ ያለው ።

#የብርቱካን ዘር ሎሚ አያፈራም ። ጳውሎስ እኔ ህያው ሆኜ አልኖርም ክርስቶስ በእኔ ይኖራል አለ ገላ 2:20. ስለዚህ በእኛ የሚኖረው ፍቅር እራሱ ነው ። ያኔ የወደደን ኢየሱስ ዛሬም አልተለወጠም ።

#ከጨለማ ስራ ስለዳንን ወደ ፍቅሩ መንግሥት ስለፈለስን ። የገባንንበት መንግሥት ሰውን ሁሉ ውደዱ ስለሚል መንፈሳዊውንም አለማዊውንም ሀይማኖት ያለውንም የሌለውንም ውደዱ ስለሚል ሁሉን የወደደ እግዚአብሔር እኛ ውስጥ ስላለ በፍቅር መመላለስ አለብን ።

#ያለፍቅር የሚሰራ ስራ ስለሌለ ከፍቅር ውጭ የትኛውም ነገር አይሰራም ። “የምታደርጉትን ሁሉ በፍቅር አድርጉ።”
  — 1ኛ ቆሮንቶስ 16፥14 (አዲሱ መ.ት)
#ነገር ሁሉ ከፍቅር ጋር የተያያዘ ስለሆነ በፍቅር ስንኖር ጤናማ ህይወት ፣ጤናማ የስራ ግንኙነት ፣ ጤናማ መንፈሳዊ ህይወት ይኖረናል ስለዚህ በፍቅር መመላለስ አለብን ።


https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

07 Jan, 14:13


#የሰይጣንን አሳብ ማፍረስ

1ኛ ጢሞቴዎስ 1 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁸ ልጄ ጢሞቴዎስ ሆይ፤ አስቀድሞ ስለ አንተ በተነገረው ትንቢት መሠረት ይህን ትእዛዝ እሰጥሃለሁ፤ ይኸውም እርሱን በመከተል መልካሙን ገድል እንድትጋደል ነው።
¹⁹ እምነትና በጎ ኅሊናም ይኑርህ፤ አንዳንዶች ኅሊናቸውን ጥለው ባሕር ላይ አደጋ ደርሶበት እንደሚጠፋ መርከብ እምነታቸውን አጥፍተዋል።

#1ጢሞ 1:18-19 ያለው ክፍል ስንመለከት በእኛ ላይ የተነገረ የትንቢት ቃል በኑሮአችን በትዳራችን በአገልግሎታችን በምድር በምንኖርበት ዘመን ሁሉ መንፈሳዊ ተጋድሎ እንደሚገባን ይነግረናል ።

#ይሄን ጦርነት የምንዋጋው ደግሞ በእምነት ነው ። ይሄን ጦርነት ተዋግተን ድል የምናገኘው በአእምሮ መታደስ ስንለወጥ ነው ።

#መፅሐፍ ቅዱስ ላይ ስለ እኛ የተፃፈው በክርስቶስ ተሰርቶ ያለቀ እውነት አለ ይሄ እግዚአብሔር ለእኛ ያላቸው በረከቶች የመዋጀታችን ሚስጥር በእኛ ላይ አካል እንዲለብስ እኛ መንፈሳዊ  ጦርነት ማድረግ አለብን ።

#እኔና እናንተ እግዚአብሔር በክርስቶስ ሰርቶ የሰጠንን ጤና : ረጅም እድሜ በክርስቶስ የተባረክናቸው በረከቶች ሁሉ አካል እንዲለብሱ የምናደርገው ተንባርክከን በማለቃቀስ ስጠኝ እያሉ በመፀለይ ብቻ አይደለም ። አትንበርከኩ አላልኩም ብቻ አይደለም ነው ያልኩት

#ለምን ካልን አንድ ጊዜ በክርስቶስ ኢየሱስ ተሰቶናል ከእኛ የሚጠበቀው በታደሰ አእምሮ መፅሐፍ ቅዱስ ላይ ለእኛ የተፃፈውን በረከቶች የኔ ነው ብለን ተቀብለን ስንኖር ስንሰራ እኛ ላይ መገለጥ ይጀምራል ።

#በክርስቶስ ተሰርቶ ያለቀውን ስራችንን በህይወታችን በኑሮአችን እብዳይገለጥ የሚዋጋን ጠላት አለ ይህን የምንዋጋው በመንፈሳዊ ማንነታችን ነው ። ስለዚህ የጠላትን ስራ እያፈረስን በክርስቶስ ተሰርቶ ያለቀው እኛ ላይ ሊገለጥ የተገባው ህይወት ሊገለጥ ይገባል ።

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

02 Jan, 10:00


መንፈሳዊ ሰው
ባልንጀራው ከራሱ እንዲሻል በትህትና የሚቆጥር እንጂ ከባልንጀራው ጋር እየተሽቀዳደመ እኔ በልጣለሁ እና ልብለጥ እያለ የማይኖር ፣እርሱ ዝቅ ብሎ ባልንጀራውን ከፍ አድርጎ ለማሳየት ፣ስለ ባልንጀራው በሰዎች ሁሉ ፊት ክፉ ነገር ፣ ደካማ ነገር ማውራት ሳይሆን፣መልካምን ነገር ሳይሸማቀቅ ባልንጀራውን አክብሮ፣ አስውቦ ፣አተልቆና አግንኖ ለማውራት ያለ ግብዝነት ፣የበታችነትና የመበለጥ ስሜት ሳይሰማው የሚያወራ፤ባልንጀራውን ዝቅ ብሎ ለማገልገል ፣to serve ,to obey ምንም አይነት ማእረጉ፣ክብሩ የማይከለክለው፣ እርሱ ከማን ይበልጣል የማይል ፣ እኔ ከሱ አላንስም እኮ እያለ ለማስወራት፣እኔም እኮ ጌታ ይሰራብኛል ፣እኔም እኮ ባለ እንዲህ አይነት ዘር ነኝ ፣ሀብት አለኝ የማይል፣ እውቀቱ ፣ሀብቱ ፣ዝናው፣ውበቱ ዝቅ ብሎ መታዘዝና ማገልገል የማይከለክለው ከትእቢት፣ከውድድር ፣ከማን አንሳለሁ ባይነትና ፣ራስን አተልቆና ቆልሎ ለማሳየት ከመኖር ፣ከዚህ አለም ሰዎች አስተሳሰብና አንዋዋር ነፃ የወጣ ፣የኢየሱስን ፈለግና ምሳሌ በመከተል የሰማይን መርህ መርሁ ያደረገ ፣በትህትናና በእውነተኛ በተግባር በተገለጠ ከራሱ ይልቅ ሌሎችን በማስበለጥ የመለኮት የህይወት ስርአት የሚመላለስ ፣ የቃሉን እንጂ የአለምን መርህ መርሁ ያላደረገ ነው።
መንፈሳዊነት ትህትናና መታዘዝ ፣ዝቅ ማትና ሌላን ማስበለጥ ነው ፤ ውድድርና በልጦ አንደኛ ሆኖ ለመገኘት መሽቀዳደም ፣ መጠላለፍ ፣በናናቅና፣ስለራስ ያለ የሌለ እያወሩና እያስወሩ ለታይታና ለከበሬታ ፣ በሌሎች ልዩ ዝናና ጭብጨባ በመፈለግ መጠመድ ፣እንዲሁም ይህና ያ ተደረገልኝ አልተደረገልኝም እያለ ፣የሚከራከር ፣ የሚያኮርፍ ሳይሆን ፤ሌሎች እንዲያደርጉለት የሚፈልገውን እርሱ ለማድረግ የሚተጋ ነው።
ከኢየሱስ እንማር ከአለም ሳይሆን ! አመሰግናለሁ

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

29 Dec, 09:53


እንዲህ አይነቱ ነው ሊቀ ካህናችን።
ለሚሻል ኪዳን ዋስ የሆነ። ሐጢአት የሌለበት ስለ እኛ ሐጢአት የራሱን ስጋ ወይም ደም ያፈሰሰልን። ለዘለአለም ልጅ የሆነ የማይለዋወጥ ሊቀ ካህን። ስጋችንን ብቻ ሳይሆን ሕሊናችንን በንፁህ ደሙ ማንፃት የቻለ። አንዴ ለዘለአለም የማለደልን። አንዴ ለዘለአለም ሀጢአታችንን ያስወገደልን። አንዴ ለዘለአለም የቀደሰን። አንዴ ለዘለአለም ፍፁማን ያደረገን። አንዴ ለዘለአለም ይቅር ማለት ብቻ ሳይሆን ሀጢአታችንን ለዘለአለም የማያስታውስብን። ለዘለአለም ስለ እኛ የሚታይልን። እኛኑ ይዞ ወደ ቅድስተ ቅዱሳን የገባ። ስጋችንን ብቻ ሳይሆን ሕሊናችንን ጭምር በደሙ ያነፃልን። ለዘለአለም በኪዳን የወደደን መቼም ላይጠላን ፣ አውጥቶ ላይጥለን። የሰጠንን ህይወት መልሶ የማይወስድብን። ወደ እግዚአብሔር በኢየሱስ በኩል ሊመጡ የወደዱትን በሙሉ የሚያድን። አንዴ ለዘለአለም ወደ ውስጣችን የገባ በእኛ ውስጥ በመንፈሱ ለዘለአለም የሚኖር የማይለየን። ሀጢአት የሌለበት ፣ ስለሀጢአታችን ግን ሞትን የሞተ ፍርዳችንን ወስዶልን ፣ ቅጣታችንን ተቀጥቶልን እኛን ነፃ ያወጣን። ስለሞተ ኑዛዜው የፀናልን ሊቀ ካህን አለን።

ይህንን በእምነት ተረድተን በተረዳንበት እምነት በድፍረት በፊቱ እንቅረብ ፣ እንኑር፣ እንመላለስ ፣ እናምልክ ፣ እናገልግል። ዕብ10፤5,10,12,14, 20-22 1ዮሀ1፤7

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

28 Dec, 16:26


#በገዢነትና በፍሬያማነት መመላለስ

#ኃጢአታችን ይቅር እንደተባለ በማወቅ በማመን በግዢነት እንመላለስ ። 1ዮሐ2:12. ሉቃ 24:47. ሐዋ 10:47. ዮሐ6:62.

#የዳነው በኢየሱስ ሞትና ትንሣኤ ነው ። የእኛ ተጨማሪ ስራ በደሙ የተደረገልንን ማስተሰሪያ በእምነት መቀበል ብቻ ነው ።

#በኢየሱስ ስም ባመንን ጊዜ የእግዚአብሔርን የማይጠፋውን የዘላለም ህይወት ነው የገኘነው ። ይህም ህይወት እግዚአብሔር ያለው አይነት ሙሉ የእግዚአብሔር ክብር ፣ ስልጣን ዘላለማዊ የመለኮቱን ባህሪይ ነው የተሞላነው ። በዚህ ደስ ይበለን ።

#ከእንግዲህ ቦኃላ እንደማይፈረድብን በማወቅ በማመን እንመላለስ ። ዮሐ3:16-18
በኢየሱስ በማመናችን ምክንያት ከዘለም ፍርድ አምልጠናል ። ኢየሱስ በመስቀል ላይ የተሰቀለው የሰውን ዘር ሁሉ የኃጢአት ዋጋ ፍርድ ሊቀበልና የእኛን ቅጣት ሊቀጣልን ነው በመስቀል ላይ የተንጠለጠለው ይሄን አውቀን በገዢነት እንመላለስ

#ከዚህ የተነሳ ፍርዳችንን ስለወሰደልን ዳግመኛ አይፈረድብንም ። ፍርዳችንን ኢየሱስ አስወግዶልናል ። በስጋ የምንሰራው ኃጢአት በስጋ መበስበስን ታሳጭደናል ( ገላ 6:7. ) ለጣላት በር እንከፍታለን : ምስክርነታችን ይበላሻል አያችሁ ፍርድ ተወግዶልናል ማለት እንደፈለግን ሆነን በኃጢአት እንመላለስ ማለት አይደለም ፍርድ እንደተወገደለት ሰው የሰማይን አሳብ በምድር እየገለጥን በገዢነት መመላለስ ነው ያለብን ።

#ፍፁም ፃድቅ እና ቅዱስ እንደተደረግን በማወቅ በማን እርግጠኛነት እንመላለስ ። 1ቆሮ 1:30.  2ቆሮ 1:21-23. ዕብ 2:11

#መወደዳችንን ተቀባይነት ማግኘታችንን በማወቅ በእረፍት እንመላለስ ። መፅሐፍ ሲናገር ወዶኛልና አዳነኝ ይላል ስለወደድነው ሳይሆን ያዳነን ስለሚወደን አድናኖናል ስለዚህ በእግዚአብሔር መወደዳችንን አውቀን በገዢነት እንመላለስ ። 2ሳሙ 22:20.

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

26 Dec, 13:34


. በነዚህ 4 ሰዎች አንቅና
1:- ጥመትን በሚያደርግ ሰው አትቅና መዝ37፤7
2:- በክፉዎች አትቅና ከነርሱም ጋር መሆንን አትውደድ መዝ 37፤1,ምሳ24፤1,19
3:- በግፈኛ ሰው አትቅና ..መንገዱንም ሁሉ አትምረጥ ምሳ3፤31
4:- አመፃን በሚያደርጉ ላይ አትቅና መዝ37፤1
👇
ቅንአት :-
:- መንፈስ ነው
:- ያልታደሰ የተበላሸ አእምሮ ሀሳብ ውጤት ነው
:- ቅንአት የስጋ ስራ ወይም ባህርይ ወይም ልማድ
:- ቅንአት የሌሎችን ስኬት ፣ ማማር ስናይ የሚፈጠር የበታችነት ፣የተበለጥኩ ባይነት ስሜት መገለጫ
👇
ቅንአት :-
:- የነሱን የክፉት ፣የግፍ ፣የአመፅ መንገድ ለመከተል ያነሳሳሀል
:- ለአጋንንት በር ይከፍታል
:- ምስጋናችንን ፣ ደስታችንን ፣ሰላማችንን ይነጥቅብናል
:- እግዚአብሔርን እንድንበድል ያደርገናል
:- ቅንአት ወንድምህን እንድትገል የሚያነሳሳ ሀይል ነው
👇
👉ህብረት አታድርግ ከእንደዚህ አይነት ሰዎች ጋር
👉እነሱ የሔዱበትን መንገድ አትከተል
👉 በውስጥህ ይህ ስሜት መልኩን ቀይሮ መንፈሳዊም መስሎ፣ ለእግዚአብሄር የቀናንም መስሎ ስመጣ ቶሎ እንገስፅ ራሳችንን ፣ መንፈሱን ፣እንዲሁም የእግዚአብሔር ፅድቅ ባህርይ እናስብ። እግዚአብሔር በፅድቅ ነው የሚባርከው ብለን እናስብ ስለራሳችን። በአመፅ ከሚገኝ ፣ቃሉን ተላልፈን ከሚሆን ስኬትና ፍሪዳ በፅድቅ መደህየት፣ ቆሞ መቅረት ፣ ይበልጣል። ሰትቆጩ ፣አትፀፀቱ ያመለጣችሁ የለም ሁሉም አላፊ ነው።

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

25 Dec, 07:02


" ፍቅር የሚኖር ህይወት ነው"
ፍቅር በተግባር ሲኖር ጮክ ብሎ የሚታይ ፣ ሌሎች ስለ እኛ የሚያወሩት እንጂ ፣እኛው ለኛው የምናወራለት ህይወት አይደለም።
"የተገለጠ ዘለፋ ከተሰወረ ፍቅር ይሻላል " ምሳ 27፤5
ፍቅር የሚኖር ህይወት እንጂ ሮዝ አበባ የመስጠት ፣ግጥም የማሳመር ፣ዜማ የመደርደር ህይወት አይደለም !
ለዚህ ለዚህማ ገጣሚና ዘፋኞች ይበልጡናል።
ፍቅር ለጨለመበት ብርሀን ነው፣ ለበረደው ሙቀት ነው ፣ለተራበው ማእድ ነው፣ተስፉ ለቆረጠው ተስፉ ፣ለታመመው ፈውስ ፣ለወደቀው መነሳት፣ለታሰረው ነፃነት ነው
ፍቅርን አጠገባችን ካሉት ጋር በተግባር እንኑረው ፣በሩቅ ካሉት ጋር በቃላት ከምንሸነጋገል።
በፍቅር ተመላለሱ ኤፌ5፤2
ፍቅርን እንኑረው የሚኖር ኑሮ ስለሆነ!
ፍቅር የትህትና፣ሌላውን የማስበለጥ፣የይቅርታ፣የመስዋእትነት፣ የመስጠት፣የመሸፈን ህይወት ፣ የእውነተኛነት ፣ያለ መሸነጋገል ፣ ከአመፅም ጋር ያለመተባበር፣ የታማኝነት ፣ህይወት ነው1ቆሮ13፤1-8
ፍቅሬ አለቀብኝ የሚል ቀድሞም ፍቅር አልነበረውም፤ስሜት እንጂ
ፍቅር አያልቅም ፣ፍቅር ካለቀብን ቀድሞም ስላልነበረ ነው።ፍቅር ለዘወትር አይወድቅም።
ፍቅር አያስጨንቅም ፣አያስገድድም ፣ ይልቁኑ ነፃነት ይሰጣል። አስጨናቂው ፍቅርሺ 🙈🤣ይህ ጂኒ እንጂ ፍቅር አይደለም።
ፍቅር አይገልም ለሚያፈቅረው ይሞታል እንጂ። ፍቅር ሰቶ አይጠግብም ፣ ሰቶ አያወራም ፣ሰቶ መልሶ አይቀበልም። ፍቅር ንግድ ሳይሆን በአፍቃሪው ፈቃድ ላይ የተመሰረተ ነፃ ስጦታ ነው።
ፍቅር የአፍቃሪውን ማንነት፣ውበት ፣ ደግነት ፣መልካምነት እንጂ፤
የተፈቃሪውን ውበት፣መልካምነት፣ አይገልጥም።የተፈቀራችሁ ስለተፈቀራችሁ እኔ እንዲህ ስለሆንኩ ነው አትበሉ ፣ ይልቁኑ ባፈቀራችሁ ሰው ውበት፣መልካምነት፣ደግነት፣ተደነቁ ፣ዋጋ ስጡት አትኮፈሱ።

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

23 Dec, 16:21


#የዳነ ሰው ሁለት አይነት ማንነት የለውም።

#በክርስቶስ አምነን ስንድን ሁለት ማንነት የለም በውስጣችን ። በክርስቶስ በማመን አዲስ ፍጥረት በሆንን ጊዜ ኢየሱስ እኛን ወክሎ የሆነውን ሁሉ አብረን ሆነናል ከዚህ የተነሳ አሮጌው ማንነተችን ሙሉ በሙሉ ከክርስቶስ ጋ ስለተሰቀለና ስለሞተ ክርስቶስ ከሞት በተነሳ ወቅት ማንነታችን ሙሉ በሙሉ ነፃ ወተናል ።

#ከእንግዲህ ቦኃላ ሙሉ በሙሉ ማንነታችን ከአጢአት ፣ ከፍርድ ፣ ከሞት ብቻ ሳይሆን የዳንን እኛ በዛችው ቅፅበት ሌላ አዲስ ማንነት አግኝተናል ።

#እግዚአብሔር ያለው ህይወት ፣ ክብር ፣ ስልጣን ፣ ፅድቅ ፣ ቅድስና በመካፈል ማንነታችን ውስጥ የቀረ ምንም አይነት አሮጌ ማንነት የለም ።

“ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፣ አዲስ ሆኖአል።”
  — 2ኛ ቆሮንቶስ 5፥17 (አዲሱ መ.ት)

#በእኛ ውስጥ ሌላ አሮጌ ማንነት የሚባል ሳያስቀር ሙሉ በሙሉ አዲስ ፍጥረት ሆነናል ከዚህ ቦኃላ ከክርስቶስ መንፈስ ጋር የእኛ መንፈስ አንድ ሆኗል ሁለት ማንነት የለንም ። አሮጌው ነገራችን ሁሉ ተወግዷል ። 1ቆሮ6፤17

#ከዚህ ቦኃላ ክርስቶስን ተሞልተናል ከክርስቶስ ጋ አንድ ሆነናል እኛ ሳይሆን ሰይጣን ሳይሆን አሮጌው ሰው ሳይሆን ኢየሱስ መንፈስ ቅዱስ ብቻ በእኛ ውስጥ ይኖራል
ቆላ 3:1-5.  ሮሜ 6:1-20.   ገላ 2:20.

በነገራችን ላይ ይኼ እውነት ካልገባን በውስጣችን ሁለት ማንነት እንዳለ እያሰብን እውነተኛውን አዲሱን ህይወት መግለጥ አንችልም ። ክርስቶስ ኢየሱስ በእኛ እንዲገለጥ ከመፍቀድ ይልቅ በአእምሮአችን ውስጥ ባለው አሮጌ አስተሳሰብ የአዲሱን ሰው ህይወት ለመኖር ስንታገል ፍሬ ሳናፈራ እንኖራለን ።

#ክርስትና የትግል ህይወት አይደለም ክርስትና የሚጀምረው ከእረፍት ነው ። አሮጌው አስተሳሰብ የሚለወጠው በእውቀት ነው ። ሮሜ 12:2.

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

21 Dec, 07:28


INSIGHT FROM FOCUS /woub
እግዚአብሔር እስከዛሬ በመጣንበት ጎዳና በተለያዩ ሲዝኖች ውስጥ ሲያሳልፈን የገጠሙንን የሰው አይነቶች ባህርያቸውን ለይተን ካወቅን ፤ከዚህ በኃላ የሚገጥሙንን ማወቅ እንችላለን።
ያን ጊዜ ከማን ጋር እንዴት መኖር ፣መስራት ፣ማገልገል እንዳለብን፣ ለማን ምን መንገር እንዳለብንና እንደ ሌለብን ጥበበኛ እንሆናለን። ምንም ነገር አዲስ የተለየ የሚጎዳን አይሆንብንም። ከብዙ ኪሳራዎችም እናመልጣለን ፤ ምሳ 4፤ ጥበብ አይነተኛ ነገር ናት።
ህይወት ካለፈው እየተማርን ነገን የምንገነባባት ትምህርት ቤት ናት። ትላንት የመታን እንቅፉት ደግሞ ከመታን እያስተዋልን እየተራመድን አይደለምና በማስተዋል መኖር ይሁንልን።
የገባው ይንቃ ! ጥሩም መጥፎም ?!

እስከዛሬ ሰይጣን ልዩ ልዩ ሰዎችን የፈተነበትን ፣ ያጠቃበትን መንገድና ፣ የተገለጡበትን ባህርያቶች ካወቅን ከዚህ በኃላ እኛንም እንዴት እንደሚፈትን እና ሊዋጋን እንደሚመጣ ማወቅ እንችላለን ( አዲስ ሰይጣን የለም የቀደመው እባብ ነው ስሙ እራሱ ራእይ 12፤9
ከቃሉ አጥኑና እወቁት !?

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

20 Dec, 15:55


የሮሜ 8፤1 እውነቱ ይህ ነው NO #CONDEMENATION
ኩነኔ የሌለበት አዲስ ህይወት ሚስጢር ሲገለጥ
ኩነኔ የለበትም ማለት ምን ማለት ነው ??
ሮሜ8፤1
:- በክርስትስ መሆን ማለት ዳግ በመወለድ ፤አዲስ ፍጥረት በመሆን ኢየሱስ በሰራው ስራ የሱ አካል መሆን ማለት። ነው። በኢሱስ በኩል ብቻ መቅረብ የሚችል መሆን ማለት ነው፣ ኢየሱስ እዳውን የከፈለለት ሰው መሆን ማለት ነው። ሮሜ8፤9 በመንፈስ ቅዱስ አሮጌው ማንነቱ ተወግዶለት ኢየሱስን የተሞላ የለበሰ ሰው መሆን ማለት ነው። 2ቆሮ5፤21 በኢየሱስ የፀደቀ ማለት ነው ተቀባይነት ያገኘ። ሀጢአቱ በሙሉ የተወገደለት። ከፍርድ ፣ከዘለአለም ሞት ያመለጠ ማለት ነው።በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት የገኘ ማለት ነው።
:- ስለዚህ በኢየሱስ ከመሆኑ የተነሳ ይህ ሰው ኩነኔ የለበትም No condamenation who ever is christ.
ኩነኔ የሌበበት በክርስቶስ ያለ ማለት ???:-
1:- No more be rejected በእግዚአብሔር ፊትና መንግስት ተቃውሞ አልቀበልህም አልሰማህም አይባልም። በኢየሱስ በኩል በድፍረት በነፃነት ይቀርባል። ፀሎቱ ምስጋናው ተቀባይነት ያገኛል ማለት ነው።

2:- No more be judged ። አይፈረድበትም በሀጢአቱ ምክንያት ምንም አይነት የእግዚአብሔር ቁጣ አያገኘውም።

3:- No more be his sin be counted
ሐጢአቱ ፣ስህተቱ በፍፁም የማይቆጠርበት ሆኖአል ማለት ነው።
Rom4: 1-8 ሀጢአቱ ሳይሆን የክርስቶስ ፅድቅ ነው የሚቆጠርለት። ሀጢአቱ ተትቶለታል። ሀጢቱ የሰራው ሁሉ እየተቆጠረ አይቀጣም።

4:- he is free...ነፃ ነው ከየትኛውም ወንጀሉ እዳው ስለተከፈለለት እዳው ተከፍሎለታል። እርሱን ወክሎ ኢየሱስ ፍርዱን የወሰደለት ሆኖአል ማለት ነው።
ይህን የከበረ እውነት ስትረዱ ነፃ ትወጣላችሁ።

5:-he is new creation ..አዲስ ሰው የሆነ ማለት ነውቨ።
ሙሉ በሙሉ አሮጌው ሰው ተወግዶለት አዲሱን ሰው ኢየሱስን ብቻ የተሞላ 2ቆሮ5፤17 ቆላ2፤10 ። ቆላ1፤27
የእግዚአብሔርን ህይወት ፣ክብር ፣ ስልጣን ሙሉ በሙሉ ከመካፈሉ የተነሳ የቆሸሸ እና የጎደለ ምንም አይነት የሌለው ፤ከዚህ የተነሳ ፣የ አዲሱ ሰው ህይወተ ፍሬ በሙላት የሚገለጥበት፣እንደ ኢየሱስ በፍቅር ፣ በሰላምና በደስታ፣ በገዢነት የሚመላለስ ሰው ማለት ነው። ጠላት ሰይጣን ፊት የማይሸሽ የሚይኮነን ፣ ድፍረቱ ፅድቁ የሆነው ኢየሱስ እንደሆነለት አውቆ የሚዋጋ ማለት ነው።

SOLAS FOCUS INTERNATIONAL CHURCH USA🇺🇸

ይህንን የፀጋ ወንጌል በአካል ተገኝታችሁ መማር ምትፈልጉ በውስጥ መስመር አግኙን። በ dmv አከባቢ ያላችሁ
267 528 4014
አገልግሎታችንን በምትችሉት ሁሉ መደገፍ የምትፈልጉ በ zell መላክ ትችላላችሁ።
ypu all are blessed .ALL GLORY TO JESUS 🙏❤️🔥 https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

20 Dec, 04:55


#በእምነት እንድንጨምር የሚረዱ ልምምዶች

#እምነት እየጨመረና እየጠነከረ የሚሄድ ነው ።
#እምነታችን እንዲጨምር በእውቀት መጨመር አለብን ። “ነገር ግን ምን ይላል? “ቃሉ በአጠገብህ ነው፤ በአፍህና በልብህም ውስጥ ነው፤” የምንሰብከውም የእምነት ቃል ይህ ነው፤”
  — ሮሜ 10፥8 (አዲሱ መ.ት)
#የእግዚአብሔር ቃል ይህ የምንናገረው የእምነት ቃል ነው ይላል ። በእኛ ህይወት ውስጥ እምነታችን በመንፈሳችን ውስጥ ሊያሳድግ የሚችለው የእምነት ቃል ስንሰማ ነው ።

#የምንሰማው ትምህርት ፣ ስብከት ፣ ዜና በውስጣችን እምነትን የሚያሳድግ መሆን አለበት ። ጠንካራ እምነት የእምነት ትምህርት ውጤት ነው ።

#በእምነት አለመድከም : በሮሜ 4:19-21. በእምነት አለመድከምን መበርታትን ያሳየናል ። ስለዚህ በእምነት መድከም አለ : በእምነት መበርታት አለ ። እምነታችን የሚበረታው እግዚአብሔር ላይ ስናተኩር ፣ በእግዚአብሔር ቃል ላይ ስንቆም ፣ በስሜት መመላለስ ስናቆም ነው ። #በእምነት የበረታን የምንሆነው የእግዚአብሔር ሁሉን ቻይነት ፣ የእግዚአብሔር ትልቅነት ስናምን ነው ።

#የእግዚአብሔር ቃል የተናገረው የሚሆንለት የተናገረው የሚፈፀምለት ታማኝ የሆነ ቃል ነው ። በስሜት ከመነዳት መቆጠብ አለብን በእምነት እንድንጨምር ።

#የፀጋን መካፈል ማድረግ : በመንፈስ ቅዱስ ሀይል ተሞልተው በሚያገለግሉ በእግዚአብሔር ቃል ላይ ቆመው በሚያገለግሉ የእምነት አስተምሮ መሰረት ያደረጉ አገልጋዮች ስር ፀጋን መካፈል ።

#የእምነት አዋጅ የእምነት ቋንቋ እንለማመድ : ““አመንሁ፤ ስለዚህም ተናገርሁ” ተብሎ እንደ ተጻፈ፣ እኛም በዚያው የእምነት መንፈስ እናምናለን፤ ስለዚህም እንናገራለን፤”
  — 2ኛ ቆሮንቶስ 4፥13 (አዲሱ መ.ት)
ምሳሌ 18:20.   1ጴጥሮስ 3:10.   የምንናገረው ቃል በእኛ ውስጥ እምነትን ያሳድጋል ስለዚህ ንግግሮቻችን እንደቃሉ ይሁኑ የስንፍና ቃል አንናገር ፀሎታችን በእምነት ይሁን ።
#ከመለኮታዊ እምነት መፅሐፍ የተወሰደ


https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

19 Dec, 04:36


#በዶሮና በነስር መካከል ያለው ልዩነት

#ስለአዋፋት ወይንም ስለነስር ስታጠኑ አንድ የሚባል ነገር አለ ። አንድ አይነት አዋፋት አንድ አይነት ዝርያዎች አንድ ላይ ነው ሚበሩት ።

#ወፎች ከወፎች ፣ ንስሮች ከነስሮች ጋ ነው ሚበሩት ። ለምንድነው ካልን የራሱ የሆነ ጥቅም አለ ።

#በህይወታችን ፣ በኑሮአችን ፣ በጓደኝነት ውስጥ ከማን ጋ መዋል ከማን ጋ አብረን መስራት ማንን ማግባት እንዳለብን ማወቅ አለብን አለበለዚያ ህይወታችን አለአግባብ ነው የሚናደርገው ።

#እግዚአብሔር ዋዳየልን ግብ ራእይ መድረስ ከፈለግን በህይወታችን ደስተኛ መሆን ከፈለግን ህይወታችንን ደስታችንን ካለአግባብ ከሚጠቀሙ ሰዎች መጠበቅ አለብን ።

#እኛ ውስጥ ያለውን ራእይ አላማ ሊደግፉ ሊቀበሉ በውስጣችን ያለውን ነገር ሊደርስ ከሚገባው ስፍራ እንዲደርስ አቅም ሊሆኑን ከማይችሉ ስዎች ጋ መዋል የለብንም ።

#ማቴ 10:11-15. ጌታ ኢየሱስ ወደ አንድ ከተማ ወይንም ቤት ስትገቡ ሰላም ብላችሁ ገብታችሁ ሰላማችሁን ካልተቀበሉ ያን ቤት ወይንም ያንን ከተማ ለቃችሁ ውጡ ነው ያለው ።

#ታውቃላችሁ ውስጣችሁ ያለውን ፀጋ አቅም የሚያቃልሉ እንዲየድግ ምክንያት ከማይሆኑ አልፎ ውስጣችሁ ያለውን ሊያስጥሏችሁ ከሚታገሉ ሽሹ ያለቦታችሁ አትገኙ ሰፈርተኛ አትሁኑ

#ከላይ በርእሱ ወዳፃፍኩት ስመለስ ዶሮ ስናይ ሰፈር በመዋል በቃ ሰፈር ላይ ስትጭር ነው ምትውለው ውሎዋ እሩቅ አይደለም

#ንስርን ስናይ በከፍታ ከሚበሩ በጥንካሬ ከሚወራላቸው በራሪ አዋፋት አዱ ነው ይሄ ብቻ አይደለም የሞተ አይበላም ውሎው ይለያል ታውቃላችሁ #እንደ ንስር መሆን ምርጫ ነው እንደ ዶሮ ሰፈር ሰፈር መዋል ምርጫ ነው ምርጫችንን ተጠቅመን ከፍ ብሎ መብረር የእኛ ድርሻ ነው የታየልንን ስፍራ መድረስ የእኛ ድርሻ ነው ታዲያ ውሎ ወሳኝ ነው ።


https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

18 Dec, 06:53


መንፈስ ቅዱስ
አይኮንንም CONDEMENATION
አይከስም .ACCUSATIONS
:-መንፈስ ቅዱስ ይቅር እንደተባልን ፣ በኢየሱስ በኩል ተቀባይነት እንዳገኘን ፣እንደ ዳንን፣ እንደማንጠፉ ፣ እንደ ፀደቅን፣ ለመመስከር ነው በውስጣችን ያለው!
መንፈስ ቅዱስ የሰራነውን ሳይሆን ኢየሱስ የተሰራልንን ነው የሚነግረን የሚያሳየን። !
:- የወደቀው ሰይጣን እና የሰይጣን አጀንዳ የተዋሱ የሱ አፎች ፣እንዲሁም ያልታደሰ አእምሮአችን የሰራነውን ፣ ስህተት ፣የትላንት ድካማችንን ነው የሚነግሩን የሚያሳዩን።
የምንሰማውንና የምናምነውን እንምረጥ። !!
ዮሐ16፤9-11 ሮሜ8፤1 ራዕ12፤11
ራሳችንን ሰዎችንም መክሰስና መኮነን እናቁም።
"የኢየሱስ ደም የትላንት፣
የዛሬ፣የነገውንም የሀጢአት እዳችንን በሙሉ አንድም ሳያስቀር ከፍሎታል"።
"ለዘለአለም ፍፁማን ተደርጋችኀል ቀድሷችኀል" ! ዕብ10፤10,12,14

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

17 Dec, 04:46


#የፃድቅ ህይወት

#“የጻድቃን መንገድ ሙሉ ቀን እስኪሆን ድረስ፣ ብርሃኑ እየጐላ እንደሚሄድ የማለዳ ውጋጋን ነው።”
  — ምሳሌ 4፥18 (አዲሱ መ.ት)

#ፅድቅ ምንድነው ? ፅድቅ ማለት ማንነት ነዉ ።
#ፅድቅ ማለት በእግዚአብሔር ፊት ተቀባይነት ማግኘት ማለት ነው ።

#የፅድቅ ማንነት በስራ ሳይሆን በእምነት ነው ሚገኘው ። ሮሜ 4. ገላ 3.
አብርሃም ሰርቶ ሳይሆን በእምነት ነው የፀደቀው ።

#ታዲያ ይሄ ፅድቅ በስራ ማይገኝ ከሆነ መልካም ስራ አያስፈልግም ወይ የምትሉ ትኖራላችሁ #በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን የሚገኘውን ፅድቅ በስራ አናገኘውም አዎ አናገኘውም ።

#ነገር ግን በክርስቶስ ኢየሱስ አምነን ፅድቅን ያገኘን የፅድቅ ፍሬ ይጠበቅብናል እንደፈለጋችሁ ሁኑ አይለንም መፅሐፍ ቅዱስ #የፅድቅ ፍሬ እያፈራን በፍሬያችን ልንታወቅ አባታችን በእኛ ሊከብር ለሌሎች መዳን ምክንያት ልንሆን ይገባል ።

#እውነት ነው መልካም ስራ አያፀድቅም ፣ ተራራ መውጣት መውረድ አያፀድቅም ፣ ድሃን ማብላት ለድሃ ማልበስ አያፀድቅም ይሄን በማድረግ ለመፅደቅ የምታስቡ ጊዜ ዘመናችሁን እያባከናችሁ ነው በስራ ሚፀደቅ ከሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ በከንቱ በመስቀል ላይ ስለእኛ እርግማን ሆነ እያችሁ እኛን ለማፅደቅ እርሱ ስለእኛ እርግማን ሆነ

#ወደ አሳቤ ስመለስ አብርሃም ልጁን ስላቀረበ አልፀደቀም ልጁን ያቀረበው በእምነት ነው የእምነቱን መገለጫ ነው ልጁን ያቀረበው

#ለዚህ ነው ሮሜ 4 ላይ አብርሃም ያለው ፅድቅ አላችሁ የሚለን ። ገላ 3 መፅሐፍ ቅዱስ አሕዛብን በእምነት እንዲየፀድቅ አስቀድሞ አይቶ በአንተ አሕዛብ ሁሉ ይባረካሉ ብሎ ወንጌልን ለአብርሃም አስቀድሞ ሰበከ እንዲሁም በእምነት ያመኑ ከአብርሃም ጋ ይባረካሉ ።
#ተመልከቱ እግዚአብሔር ገና ሲያይ ከአብርሃም ቦኃላ አሕዛብን ያይ ነበር ። ፅድቅ በረከት ነው ያልኳችሁ ለዚህ ነው ።


https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

16 Dec, 10:59


ሀሳብን በሐሳብ የማሸነፍ ጦርነት
:-ኩነኔና ፍርድ ከህሊናና ከሰዎች የሚወረወር ሮሜ8፤1
:- ክስ ግን ከሰይጣን የሚወረወር የሀሳብ ፈላፃ ነው ራዕ12፤11
:- ጭንቀትና ፍርሀት ተስፍ መቁረጥ እምነት ከማጣት ማቲ6፤30
-ኩኔና ክስ እውቀት ከማጣት ሆሴ4፤6
-ጭንቀትና ፍርሀት ተስፍ መቁረጥ እምነት ከማጣት ማቲ6፤30
የተነሳ ጠላት እኛን ለማጥቃት የሚመጣባቸው መንገዶች ናቸው

ሁለቱንም አሸንፈን መኖር የምንችልበት መንገድ ግን :-
1:- ( በእግዚአብሔር ቃል የታደሰ አእምሮ ሲኖረን)
በክርስቶስ ያለንን ማንነት ፣የተቀመጥንበትን ስፍራ፣ የተሰራልንን ስራ ስንረዳና ስናውቅ ብቻ ነው !ዮሐ8፤32
2:- በእግዚአብሔር ላይ በመታመን በእምነት ነው !
2ቆሮ5፤7 ዕብ10፤38

ትላንትን በማስታወስ በኩነኔ እና በክስ ላለመኖር በክርስቶስ ያለንን ማንነት በማወቅ

ስለ ነገ በማሰብ ከመጨነቅ እና ተስፍ ከመቁረጥ ስለ እኛ የሚያስብ እንዳለ በማወቅ

ዛሬን ደግሞ በፍርሀት ደስታና ሰላማችንን አተን ሊያኖረን ከሚመጣ የሀሳብ ፈላፃ ለማምለጥ
:- በእምነት በመኖር ብቻ ነው

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

15 Dec, 08:36


የተወደዱ ልጆች ምልልስ እንመላለስ  ኤፌ5፤1 -20

👉#LOVE በእውነተኛ አጋፔ  ፍቅር   እና በትህትን ቁ2

👉 #LIGHT በብርሀን ፣በፅድቅ፣በቅድስና ፣በምሳሌነት  የጨለማን ስራ በመግለጥ ፣ባለ መተባበር ቁ3,7-13

👉#MOUTH በንግግራችን  በጨው እንደተቀመመ  በፀጋ ከንቱ፣ ዋዛ ና  የሚያሳፍር ንግግር  በመተው  ቁ4

👉#KINGDOM የእግዚአብሔርን መንግስት የወከለ ኑሮ ፣ለእግዚአብሔር መንግስት እንደሚገባ በመኖር ቁ5

👉#RENEWED MIND  በታደሰ አእምሮ  በእውቀት፣ በጥበብና  በማስተዋል እና  ቁ15

👉#INFLUENCE  ዘመኑን በመዋጀት  ተፅእኖ በመፍጠር በገባንበት ሁሉ ቁ15 -17

👉#HOLY SPIRIT በመንፈስ  ቅዱሱ እለት እለት በመሞላት በመለየትና ፣በፀሎት እና ምስጋና እንመላለስ  ቁ18-20
        መልካም እለተ ሰንበት ይሁንላችሁ


https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

14 Dec, 06:00


#ጥሪያችን በብርሃን የመመላለስ ነው

#““እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ፤ በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትደበቅ አትችልም፤”
  — ማቴዎስ 5፥14 (አዲሱ መ.ት)

#ብርሃኑ እግዚአብሔር ነው ። ብርሃን የሆነው እግዚአብሔር በክርስቶስ አምነን ስንድን በእኛ ውስጥ ገብቷል ። በእኛ ውስጥ የገባው ብርሃን መገለጥ አለበት ።

#ከላይ ማቴ 5:14. ላይ በተራራ ላይ ያለች ከተማ እንደማትሰወር በእኛ ውስጥ የገባውብርሃንም መደበቅ አይቻልም ሚገለጥ ሚወጣ ነው ።

#እኔና እናንተ በተቀበልነው ብርሃን እስካልተገለጥን ዓለም ልትነቃ ትውልድ ሊያመልጥ አይችልም ።

#እንደብርሃን ልጆች ልንመላለስ ይገባል ።
#ብርሃናችን በብዙ አቅጣጫ ሊገለጥ ይችላል ። የአንዳዶቻችን በምንሰራው የስራ ስምሪት ፣ የአንዳዶች በመምከር ፣ በማስተማር ፣ በመፀለይ ፣ በማፅናናት በብዙ አቅጣጫ ሊገለጥ ይችላል ።

#ብርሃን ናችሁ ብርሃናችሁ ግለጡ ስንባል በአንድ አቅጣጫ አንመልከት እግዚአብሔር ባሰማራን ስፍራ በፅድቅ በቅድስና እግዚአብሔርን በመፍራት ስንገለጥ ብርሃናችንን እያበራን ነው ማለት ነው ።

#እግዚአብሔር ብርሃን ይሁን ያለው ጨለማ ለወረሰው አለም ነው ።
#በጣም ደግሞ ልንጠነቀቅ ሚገባው ግለጡት በብርሃን ተመላለሱ እንጂ ብርሃናችሁን የሚያደፈርስ ቦታ ተገኙ ሕብረት አድርጉ አልተባልንም ይልቃንም ብርሃን ከጨለማ ጋር ሕብረት እንደላለው አውቀን ስፍራችንን ለይተን ብርሃናችንን ማብራት ነው ያለብን

#“ብርሃንም በጨለማ ያበራል፤ ጨለማውም አላሸነፈውም።”
  — ዮሐንስ 1፥5 (አዲሱ መ.ት)
በውስጣችን ያለው የአሸናፊ ማንነት ነው ይሄን በሙሉ ድፍረት እየገለጥን በማንነታችን ልክ መመላለስ አለብን 

#ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ ፀጋና ሰላም ይብዛላችሁ


https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

12 Dec, 13:22


. እንደ ልጆቹ እንኑር !የእግዚአብሔር መንገድ የእግዚአብሔር
ህግ ነው
. "ልጄ ....አይኖችህም መንገዴን ይውደዱ "
መዝ 23፤26
"በአእምሮአችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህንን አለም አትምሰሉ " ሮሜ12፤2, ኢሳ55፤9
የእግዚአብሔር አሰራር ከአለም አሰራር ይለያል
የእግዚአብሔር መርህ ከአለም መርህ ይለያል
የእግዚአብሔር ሀሳብ ከሰው ሀሳብ ይለያል
የእግዚአብሔር ፍቅር ከአለም ፍቅር ይለያል
የእግዚአብሔር ምርጫ ከሰው ምርጫ ይለያል
እግዚአብሔርን መከተል እንደ እግዚአብሔር ልጆች
የአባታችንን ድምፅ እየሰማን በፈቃዱ ውስጥ መኖርን ይጠይቃል። እንግዲህ እንደተወደዱ ልጆች እንደ አባታችን
ፈቃድ ፣ መርህ ፣ መንገድ እንጆ እንደ አለማውያን መኖር አይገባንም። እንደ ፈለግንም መኖር ፣የመረጥነውን እያደረግን እግዚአብሔርን መተህ ፈርምልኝ ማለት በፍፁም መንፈሳዊነት ሳይሆን አመፀኛነት ነው። የእግዚአብሔር መንገድ ከእኛም ከአለምም መንገድ ይለያል። እርሱ የጽድቅ ፣ የብርሀን፣ የትህትና፣ የይቅርታ፣ የማካፈል፣ የመገዛት ፣የመታዘዝ መንገድ ነው። የአመፃ ፣የውሸት፣የብልጣብልጥነት ፣ የግብዝነት፣ የአልከኛነት፣ የትእቢት መንገድ ሳይሆን።
"እንደተወደዱ ልጆች እግዚአብሔርን የምትከተሉ ሁኑ "
ኤፌ5፤1
የእግዚአብሔርን መንገድ አለማወቅ ፣በመንገዱ አለመሔድ ፍፃሜው ክስረትና ጉዳት ነው።
መዝ81፤13 , ዕብ3፤10 , ሚልክ2፤9 ሕዝ18፤25 ዘካ3፤7

መዝ119፤9 መዝ119፤105 ሮሜ8፤ 14 1ቆሮ2፤10
መንገዱን ማወቅ የሚቻለው ወደ ቅዱስ ቃሉ በመቅረብ በማንበብ እና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር የጠበቀ ህብረት በማድረግ ነው። መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔርን መንገድ ፈቃድ ፣ሀሳብ አንዳች ሳያስቀር ሊነግረን ነው በውስጣችን ያለው። እርሱን ስሙት ይነግራችኀል ትክክሉንና ስህተቱን ለይቶ።
በመንገዱ መሄድ ወደከፍታ ያወጣል፣ያሳርፉል፣ሰላም ይሞላል፣ በገዢነት ያመላልሳል ። ዘካ3፤7 መዝ 119፤165

የእግዚአብሔርን መንገድ መሄድ ብዙ ዋጋ ቢያስከፍልም ፤ጨክኖ ፀንቶ በመንገዱ መሄድ አያከስርም። መንገዳችንን በፊቱ ማፅናት ይሁንልን
ኢዮ13፤5።

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

10 Dec, 13:44


ምሳ 24፤9
"የስንፍና ሐሳብ ሐጢአት ነው" !
ስለዚህ የሰነፍ ሳይሆን የፃድቅ (የትጉ) አሳብ እናስብ
የተግባር ሐጢአት ምንጩ የስንፍና ሐሳብ ነውና ፤ የምታሰላስለው ሐሳብ ላይ አተኩር ! ያኔ በሐጢአት ላይ በአሸናፊነት ትመላለሳለህ
[ትእቢት ፣ ዝሙት፣ መግደል፣ሌብነት፣ አለማመን፣ ጥላቻ..
የሚጀምሩት ሐሳብ ላይ ነው !]
በሐሳብ ደረጃ እያለ ያልነገስንበት ማንኛውም ሀሳብ በተግባር በእኛ ላይ ነግሶ ያጠፉናል ዘፍ4፤ 7
በህይወትህ እየሆነ ያለው የተመኘሄው ሳይሆን በሀሳብህ ያሰብከው ነው !።
ህይወት የምኞት ሳይሆን የአስተሳሰባችን ውጤት ናት ፤ ምኞት ተደጋግሞ የታሰበ ሀሳብ ልጅ ናትና ።
ምሳ23፤7 ሚክ2፤1 ያእቆ1፤14-15

:- አብዛኛው ሀሳብ የሰይጣን ነው፣ መንፈሳው ውጊያው በአእምሮ ላይ ስለሆነ፣
ብዙ የሐጢአት ፣የርኩሰት፣ የትእቢት፣ የጥላቻ ፣የተስፉ መቁረጥ፣ ሀሳብ በመላክ እየተዋጋህ ስለሆነ ፤ሐሳቡን አትሳት ፣ንቃና በቃሉ እውነትና በፀሎት እንዲሁም እንቢ በማለት አፍርስበት።
2ቆሮ2፤11 2ቆሮ11፤3, ኤፌ6፤11 2ቆሮ10፤3-7.

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

09 Dec, 17:27


#እንዴት በተፅኖ አምጪነት እንመላለስ ?

#“በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ በክርስቶስ የባረከን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ፤”
  — ኤፌሶን 1፥3 (አዲሱ መ.ት)

#በመጀመሪያ በተፅኖ አምጪነት ለመመላለስ በክርስቶስ የተቀበልነውን ማንነት ማወቅ ነው ። ለምን የላወቅነውን መግለጥ አንችልም

#በክርስቶስ ኢየሱስ አምነን ስንድን ያልተቀበልነው ምንም ነገር እንደሌለ መፅሐፍ ቅዱሳችን ይነግረናል ። ስለዚህ ይሄን ስናውቅ መግለጥ እንችላለን

#እንዴት መግለጥ እንዳለብን የሚያስችለንን እውቀት እለት አለት በመሞላት በዚህ ምድር ላይ በተፅኖ አምጪነት መገለጥ እንችላለን

#“እንደዚሁም ሰዎች መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማይ ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ በሰዎች ፊት ይብራ።”
  — ማቴዎስ 5፥16 (አዲሱ መ.ት)
#ከላይ ያለውን ቃል ስናይ ብርሃን ትሆናላችሁ አይለንም የሆነውን እንድንገልጠው ነው ሚያዘን ። ብርሃን ውስጣችን ገብቷል

#ቅድስና ፣ ፍቅር ፣ ትህትና ለፍተን የምናመጣው አይደለም በክርስቶስ ኢየሱስ አምነን ስንድን ይህ ሁሉ ውስጣችን ገብቷል የእኛ ኃላፊነት የተቀበልነውን መግለጥ ነው ።

#እግዚአብሔር ቅዱስ ነው እኛም በቅድስና እንድንመላለስ ነው የታዘዝነው ።

#የብዙዎቻችሁ ችግር የተሰጣችሁን አለማወቅ ነው መግለጥ እንዳትችሉ በተፅኖ ፈጣሪነት እንዳትመላለሱ ያደረጋችሁ

#ዛሬ ግን የተቀበላችሁትን አውቃችሁ በማንነታችሁ ልክ በተፅኖ አምጪነት ትመላለሳላችሁ ብርሃን ናችሁ ብርሃናችሁን በጨለማ ስፍራ ሁሉ ታበራላችሁ ፣ ጨው ናችሁ ህይወት አልጫ ለሆነባቸው በማጣፈት ትገለጣላችሁ ፣ በቅድስና ፣ በፍቅር ፣ በትህትና በመመላለስ እግዚአብሔርን በምድር ላይ ታከብራላችሁ አሜን

#ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ 👇

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

07 Dec, 16:05


#ሰው መፅደቅ ይችላል ወይ ?
#ፅድቅ እንዴት ነው ሚገኘው ?

“ሰውስ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅ ይሆን ዘንድ፥ ከሴትስ የተወለደ ንጹሕ ይሆን ዘንድ እንዴት ይችላል?”
  — ኢዮብ 25፥4
#ኢዮብ ጥያቄ ነው ሚጠይቀው ሰው በአዳም ኃጢአት ምክንያት የእግዚአብሔር ክብር የራቀው ኃጢያተኛ የሆነ ሰው መፅደቅ ይችላል ወይ ነው ሚለው

#ሰው መፅደቅ ይችላል ወይ ? ሰው ብዙ ድካም አለበት ያጠፋል ህግ ተሰጥቶት ህግን መጠበቅ አልቻለም ስለዚህ ሰው ሆኖ ፃድቅ መሆን ይቻላል ወይ ?
#አዎ መፅደቅ ይችላል

#ፅድቅ እንዴት ነው ሚገኘው ? ሰው በክርስቶስ ኢየሱስ የመስቀል ስራ በማመን ክርስቶስ ኢየሱስ የእርሱን ኃጢአት እንደ ወሰደለት በማመን የእግዚአብሔር ፅድቅ መሆን ይችላል ።

#ፃድቅ ማለት ምን ማለት ነው ? ፃድቅ ማለት እግዚአብሔር ያለው ህይወት ያለው ሰው ማለት ነው ።
#እግዚአብሔር ቅዱስ ነው ቅዱስ በሆነው በእግዚአብሔር ፊት  መቆም የሚችል ብቃት ያለው ፣ መብት ያለው ፣ ሰው መለት ነው ።

#ፃድቅ ማለት ተቀባይነት ማግኘት ማለት ነው ።
#ፃድቅ ማለት የእግዚአብሔር ስልጣን የተካፈለ ማለት ነው ።
#ፃድቅ ማለት የተባረከ ማለት ነው ። እዚህ ጋ ማወቅ ያለብን በረከትን ከቁሳቁስ አንፃር ብቻ ልናየው አይገባም በረከት ማለት ከቁሳቁስ ያልፋ ነው

#ፃድቅ ማለት ፍጥረታዊውም መንፈሳዊው አለም የሚታዚለት ማለት ነው ።
ታዲያ ከላይ የዘረዘርኩት አይነት ሰው መሆን ይቻላል ወይ ? አዎ ይቻላል ።
#እንዴት ካልን እግዚአብሔር በብሉ ኪዳን ህግን ሰጠ ህግን መጠበቅ የሚችል ይፀድቃል ሰው ህግን ጠብቆ የእግዚአብሔር ፅድቅ መሆን ስለማይችል ነው. ለዚህም #ማቴ 19:16_24. አንቡ
#ለዚህ ነው  እግዚአብሔር ኃጢአት ያላወቀውን ልጁን በመላክ ኢየሱስ ፍፁም አምላክ ፍፁም ሰው የሆነ ኢየሱስ በስጋ ተገልጦ ለሰው ልጅ ፅድቅ ሆነ 2ቆሮ5:21.
ስለእኛ የሞተውን እኛን ስለመፅደቅ ደግሞ የተነሳውን ክርስቶስ ኢየሱስን በማመን የእግዚአብሔር ፅድቅ መሆን ይቻላል ።

#ሼር ማድረጉን እንዳይረሳ

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

05 Dec, 11:44


#ያለኝን ግን እሰጥሀለሁ
(ትልቁ ዋርካ የትንሺዬዋ ዘር ውጤት ነው፤ዘር አይናቅም)
👉ያለንን ማወቅ ::-

#እግዚአብሔር ማንንም ያለ ስጦታ  ፣ችሎታ አልፈጠረም። የተሰጠንን ነገር አውቀን ለይተን  እሱ ላይ እናተኩር ፤የሌላውን መመኘት ፣ የሌለንን ለመሆን ከመፈለግ ወተን። ያላቸውን በአግባቡ የሚጠቀሙትን በመተቸት ዘመናችንን ከመጨረስ ፣ለኛ የተሰጠንን በመጠቀም ላይ ብናተኩር መልካም ነው።  KNOWING WHAT WE HAVE  .

👉 የተሰጠንን ነገር አላማ ማወቅ :-
#እግዚአብሔር አምኖብን የሰጠን ነገር ሁሉ ለመልካም አላማ እንዲውል ፣ህዝብን እንዲጠቅም ነው ላልተሰጠን አላማ አናውለው። ላለን ነገር (ተሰጥኦ) ዋጋ  መስጠት
አለመናቅ ፤ የተሰጠን ነገር ሁሉ 3 አላማዎች አሉት:- 1:- እግዚአብሔርን ማክበር  2:- ሌላ ሰዎችን ለማነፅ ለማገልገል 3:- ለኛም ጥቅም ነው።  :- PURPOSE

👉 መትጋት :-
#ያለንን ነገር ማሳደግ እንዲያፈራ ማድረግ የኛ ሀላፊነት ነው። እኛ ያላከበርነውን ነገር ማንም አያከብርልንም።  ያለንን ሀሳብ፣ ፀጋ ፣ሙያ፣ በቻልነው አቅም ሁሉ በትምህርት፣ ከተለያዩ ሰዎች ጋር ግኑኝነት በመፍጠር፣ በመትጋት ማሳደግ የኛ እንጂ የእግዚአብሔር  ድርሻ አይደለም።  ማንም እንዲያሳድግልህ አትጠብቅ አንተ እየሰነፍክ።  ትጋት ለሰው የከበረ ሀብቱ ናትና ፣ባለህ ጥቂት ነገር ትጋ ፣ነገ በዝቶ ታየዋለህ  DELIGENCE

👉 ለተሰጠን ላለን ነገር  ነገር ትክክለኛ ስፍራውን እናግኝለት:-
#አብዛኛዎቻችን ያሉን ነገሮች ክብር ያጡት ፣ ፍሬ ማፍራት ያልቻሉት ፤ የኛን  ነገር የማይፈልጉ ፣እውቅና ማይሰጡ ወይም ማይፈለግበት የተሳሳተ ቦታ ወይም ገበያ መሀል ስላለ ነው።  ወርቅ የወርቅን ዋጋ በማያውቅና ፣ወርቅን ለመግዛት ባልመጣ ተገበያይ ፊት ዋጋ የለውም።  ሀኪም ክብር ያለው በሺተኞች መሀከል ሲገኝ ነው። RIGHT PLACE

👉ያለንን ነገር ማካፈል መስጠት ወደ ገበያ ማቅረብ :-
#ወደ እኔ ተመልከት ይሔ አለኝ ማለት ትክለኛ መንገድ ነው ያለንን ሰተን ሌሎች ለመጥቀም ፣እኛም የልፉታችንን ዋጋ ለማግኘት።  The power of marketing..advertisment..።  በፍፁም ያለንን ነገር ይሄ አለኝ ኑና ግዙ፣ ተጠቀሙ ብሉ በደንብ አሳምሮ ገዢ መፈለግ  ሀጢአት አይደለም።    ምንም ነገር የሚበዛው ስትዘራው ነው።  እስካላገለገልን ውጤቱን አናይም።  SALING YOUR PRODUCT AND MARKETING
ሐዋ3፤ 1-15

ሼር እያደረጋችሁ ሌሎችም ይጠቀሙ

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

04 Dec, 12:29


#ስለ መንፈሳዊ አለም ማወቅ ያለብን ነገሮች

#ማንኛውም ነገር ምንጭ አለው ። የማንኛውም ነገር ምንጩ ደግሞ ከመንፈሳዊ አለም ። የሚታየው ይሁን የማይታየው ምንጩ መንፈሳዊ ነው አለም ነው ።

#መንፈሳዊ አለም ሀይል አለው ። የሰይጣንና የእግዚአብሔር አለም የሚባል አለ ።
“እነሆ፥ እባቡንና ጊንጡን ትረግጡ ዘንድ፥ በጠላትም ኃይል ሁሉ ላይ ሥልጣን ሰጥቻችኋለሁ፥ የሚጐዳችሁም ምንም የለም።”
  — ሉቃስ 10፥19

#መፅሐፍ ቅዱስ ሰይጣን ሀይል የለውም ሀይለንም ስልጣን እንጂ ለዛ ነው በጠላት ሀይል ሁሉ ላይ ስልጣንን ሰጥቻችኃለው ሚለን ይሄን እውነት በትክክል ካልተረዳን ዘመናችንን ዝም ብለን ስንወድቅ ስንነሳ እንጨርሳለን የመጣንበትን አላማ ሳንፈፅም ስለዚህ ጠላት ሀይል እንዳለው አውቀን እኛ ስልጣን እንዳለን ገብቶን በጠላት ላይ ልንዘምትበት ሌት ተቀን አሳቡን ልናፈርስ ይገባል

#መንፈሳዊ አለም አላማ አለው ። ሁለቱም አለም አላማ አላቸው የእግዚአብሔርም የሰይጣንም ። የሰይጣን አለም መስረቅ ፣ ማረድ ፣ ማጥፋት ፣ ነው የእግዚአብሔር አላማ በእኛ ላይ ህይወት እንዲሆንልን እንዲበዛልን በክርስቶስ የተካፈልነውን ህይወት ገልጠን እንድናልፍ ነው ።

#መንፈሳዊ አለም የስልጣን ተዋረድ አለው ።
#መንፈሳዊ አለም ኤጀንት አለው ።

#የእግዚአብሔርም የሰይጣንም አለም ሶስት ነገሮችን ይጠቀማሉ

1# ህይወትን   2# ሀይልን. 3#  እውቀትን ይጠቀማሉ
2ኛ ቆሮ 10
³ በሰው ልማድ ምንም እንኳ የምንመላለስ ብንሆን፥ እንደ ሰው ልማድ አንዋጋም፤
⁴ የጦር ዕቃችን ሥጋዊ አይደለምና፥ ምሽግን ለመስበር ግን በእግዚአብሔር ፊት ብርቱ ነው፤
⁵ የሰውንም አሳብ በእግዚአብሔርም እውቀት ላይ የሚነሣውን ከፍ ያለውን ነገር ሁሉ እናፈርሳለን ለክርስቶስም ለመታዘዝ አእምሮን ሁሉ እንማርካለን፥

#ስለዚህ ከላይ የፃፍኩላችሁንን እውነታዎች ማወቃችን ተሸናፊ ሳይሆን አሸናፊ ሆነን በድል ነሺነት እንድንመላለስ ያደርገናል ።

#በክርስቶስ የተካፈልነውን እውነት በሙላት መግለጥ እንችላለን እንዴት ካልን በመንፈሳዊ አለም ላይ ጠላት አሳቡን ስናውቅ እያፈረስን የእግዚአብሔርን ህይወት ደግሞ እየገለጥን እንመላለሳለን ።

#ለሌሎች እንዲደርስ ሼር አድርጉ

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

01 Dec, 16:03


#ሰይጣን እንድትጠራጠር ሲያደርግህ ሀጢአት ግን በእምነት እርምጃ እንዳትወስድ ፈሪ ያደርግሀል።
  ፍረሀት እና ጭንቀት  በእምነት ያለመመላለስ መገለጫዎች ናቸው።
  #ሁላችንም የእምነት እጦት ችግር ሳይሆን ያለብን ፣የመጠራጠር ወይም ያለማመን ፈተና ነው ያለብን። 
  #እምነት የሌለው ዳግም የተወለደ አማኝ የለም ፤ሁሉም ዳግም አዲስ ፍጥረት የሆነ ሁሉ እምነት በውስጡ አለ
ሮሜ12፤3።   #በእምነት ውጤታማ የሆኑና ያልሆኑ ሰዎች መሀከል ያለው ልዩነት፤ እምነት እንዳላቸው አውቀው እርምጃ  መውሰድና አለመውሰድ ብቻ ነው።  እግዚአብሔር የሰጠህን በመንፈስህ ውስጥ ያለውን እምነት አንቀሳቅሰው፤ በስሜት ፤ በሁኔታ ከመመላለስ ወተን በእምነት መመላለስን ፣ማየትን፣ማቀድን፣መናገርን እንጀምር። 

#እምነት ስላለን ብቻ አይሰራም ደግሞ ውጤቱን አናይበትም፤ እርምጃ እስካልወሰድን ድረድ።
  please activate you faith . plan.speek ,and do it by faith. you will see the miracle in your life.
   ያለንን እምነት ሁል ጊዜ እንዲሰራልን እና ጠንካራ እንዲሆን ማይዋዥቅ ፤እንደ አማኝ  የእምነታችንን መሰረት መጣል ያለብን

  1:- እምነታችን በእግዚአብሔር በራሱ ላይ ይሁን በራስህ ፣ በሰዎች፣ በሁኔታዎች ላይ ሳይሆን በእራሱ በእግዚአብሔር ላይ እናድርግ  መታመናችንን።  ታማኝ ፣ ሀይል ያለው፣ ሁሉን የሚችል  አምላክን እንታመን።
ምሳ 22፤19 ዮሐ14፤1 ኢሳ26፤3-4  መዝ125፤1 ማር11፤22 ኢሳ26፤3
2:- እምነታችን ተሰርቶ ባለቀው በመስቀሉ ስራ ላይ እና በፀጋው ላይ ብቻ ይሁን።  ዮሀ14፤1  ኢሳ26፤12
3:- እምነታችን በሕያውና በሚሰራ መቼም ቃሉ በማታጠፍ በተፃፈው የእግዚአብሔር ቃል ተስፉ ላይ ይሁን።  #መዝ145፤14  ኢሳ45፤23 ኢሳ55፤10-11 ኤር1፤12 ማቲ24፤35
4:- አምኖ በመናገርና እርምጃ በመውሰድ ላይ መሆን አለበት።   ማር11፤ 22-24, 2ቆሮ4፤13,  ያዕቆ2፤17-22
ሮሜ10፤9-11
  👉 ስለ መለኮታዊ የሚሰራ እምነት የበለጠ በጠለቀ ለመማር ለማወቅ የምትፈልጉ በአለም ዙሪያ በ4 ቋንቋ 25 ምእራፎች ያሉት ድንቅ መፅሐፍ ተዘጋጅቶ ቀርቦላችኀል አገልግሎታችንን አቅማችሁ በቻለው መጠን በመደገፍ ማግኘት ትችላላችሁ። 
+1 267 528 4014  ይፃፉልን።  በTELEGRAM OR WHATSAPP OR DIRECT CALL .


https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

28 Nov, 05:26


#የሕብረት አስፈላጊነት

#መዝ 133 :1. ሐዋ 2:42. 1ቆሮ 1:9
#ሕብረት ለቅዱሳን አስፈላጊ ነው ከእግዚአብሔር የተሰጠ ትእዛዝም ነው
ከላይ የፃፍኩላችሁ ክፍሎች ላይ ስለ ሕብረት አስፈላጊነት እናያለን

#በሕብረት ውስጥ በረከት አለ
#በሕብረት ውስጥ አብሮነት አለ
#በሕብረት ውስጥ አብሮ በፀሎት መትጋት አለ
#የእግዚአብሔር ቤት ስራ ሚሰራውም በሕብረት ነው
መፅሐፍ ሲናገር አንዱ ሺ ሁለቱ አስር ሺ ያሳድዳሉ ይላል
ጠላት ይሄን ስለሚያውቅ ሕብረት እንድናደርግ አይፈልግም ልንነቃበት ይገባል
የተጠራነውም ወደ ሕብረትነው ።

#ይሄን አስተውላችሁ ታውቃላችሁ? ለሕብረት ተጠርተን ሕብረት አያስፈልገኝም ብለን ነጠል ብለን ስንቀመጥ ለአጋንንት እንደምንጋለጥ ልናውቅ ይገባል

#ለዚህም ጥሩ ምሳሌ ሄዋንን እባቡ ያገኛት ነጠል ብላ ብቻዋን ሆና ነው የአጋንንት ስብሰባ ውይይት ላይ የገባችው

#ሕብረት አለማድረግ ለጠላት በር ይከፍታል እኔ ምንም ሰው አያስፈልገኝም የሚለው አሳብ በራሱ አጋንንታዊ ነው

#ስለዚህ የመንፈስን አንድነት ጠብቀን በማስተዋል ከቅዱሳን ጋር ሕብረት ልናደርግ ይገባል

#በጣም ደግሞ ልናስተውል የሚገባው ሰው ስለሆንን ሁሌ መበርታት የለምና ብንደክም በሕብረት ስንሆን ይፀልዩልናል በፀሎት ያግዙናል ይሄ ብቻ አይደለም አንዳችን የአንዳችን ሸክም እንሸካከማለን ይሄን በማወቅ ሕብረት አያስፈልገኝም ብላችሁ ዳር የያዛችሁ ተመለሱ ሕብረት ውስጥ በረከት አለ ።

#ሼር እያደረጋችሁ ሌሎችም ይጠቀሙ

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

27 Nov, 09:58


" በምንም አይነት ሁኔታ ውስጥ ብትሆኑም እግዚአብሔር ይወዳችኀል ፣ ፍቅሩ አይለወጥባችሁም፣ በዘለአለም ፣ያለ ቅድመ ሁኔታ ፣ከራሱ ተነስቶ ወዷችኀል ሚል1፤2
ኤር31፤3 ሮሜ8፤38-39
" በፍቅሩ ስጋት አይግባባችሁ"
እግዚአብሔርን መውደዳችሁም ሆነ በእግዚአብሔር መውደዳችሁ እንዲሰማችሁ በማሰብ አትድከሙ ፤ፍቅር ስሜት ቢኖረውም ፤ስሜት ሳይሆን እውቀት ነውና የሚፈልገው ።
ኤፌ3፤17-19 ዮሀ3፤16 1ዮሀ3፤16, 1ዮሀ4፤10
በእግዚአብሔር በምን ያህል ፣እንዴት ባለ ፍቅር ፣ እስከመቼ እንደተወደዳችሁ ለማወቅ በርቱ።
LOVE IS NOT FEELING ,LOVE IS UNDERSTANDING

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

26 Nov, 15:37


#እትተባበሩ

#“ፍሬም ከሌለው ከጨለማ ሥራ ጋር አትተባበሩ፥ ይልቁን ግለጡት እንጂ፥”
  — ኤፌሶን 5፥11
#መፅሐፍ ቅዱስ የጨለማን ስራ ተባበሩ አባብሉት አይለንም ግለጡት ነው የሚለን ።

#አጋንንት በውስጡ ያለበት ሰው ሰነፍ ሰው ፣ ፈሪ ሰው ፣ የእግዚአብሔር ቃል በስርአት የማያውቅ ሰው ፣ ሐይማኖተኛ ሰው ስለአጋንንት ስንማር እና የጨለማን ስራ ስምገልጥ ይጠሉናል

#ስለ መናፍስት አለም የምንማረው መፅሐፍ ቅዱስ የጨለማን ስራ ግለጡት ስላለን ነው ።

#ስለ መናፍስት አለም ማወቅ ያለብን በጨለማ ውስጥ ያሉ ነፃ እንዲወጡ ነው
ኢየሱስ የመጣው ነፃ ለማውጣት ነው ።

#ሌላው ሰዎች የጨለማውን ስራ ገልጠን ካላሳየናቸው ማወቅ ስለማይችሉ ነው ።
በጠላት ላይ በር ለመዝጋት ነው ። ሰዎች ከተፈቱ ቦኃላ ተመልሰው ባሪያ እንዳይሆኑ ማወቅ መማር አለባቸው ።

#የሰይጣንን ሽንገላ አሰራሩን ካላወቅን መግለጥ አንችልም ስለዚህ ለመግለጥ ማወቅ አለብን በምን እንዴት እንደሚሰራ ሊገባን ይገባል ።

#በጣም ደግሞ ልንጠነቀቅ የሚገባው ካወቅን ቦኃላ መግለጥ ከመግለጥ አለመተባበር አለብን ምክንያቱም አውቆ አለመግለጥ በራሱ መተባበር ነው ። እናም ጨለማ ጨለማ መሆኑ መገለጥ አለበት ። እንገልጠዋለን ዝም እንልምም ትውልድ ያመልጣል ።

#ሼር እያደረግን ቅዱሳን

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

25 Nov, 16:29


#አማኝ ከእነዚህ ከሰይጣን እስራት ነፃ ሊወጣ ይገባል

#አንድ አማኝ በህይወቱ እግዚአብሔር ያየልኝን የተናገረኝን በእኔ ሊገልጥ ሊሰራ የተገባውን እንዲሰራ እንዲገልጥ ከታች ከምዘረዝርላችሁ አጋንታዊ እስራቶች ነፃ ሊወጣ ይገባል

#ከአለም አስተሳሰብ ፣ ከሰይጣን መንፈስ ፣ ከሃይማኖተኛነት ፣ ፣ ከእኔነት ፣ ከሱስ ነፃ መውጣት አለበት

#እኔነትንም ብናይ ለሌሎች ተርፈን ሳይሆን በቃ ሁሉ እሩጫችችን እኔ እኔ በእኔ ሆኖ እንዲቀር የደርጋል እግዚአብሔር ደግሞ በልጁ ዘላለምን ሲሰጠን ለኔ በእኔ ብለን እንድንኖር ሳይሆን ለሌሎች በተረፈ ማንነት ተገልጠን የእግዚአብሔር አላማ ፣ አጀንዳ ፈፅመን እንድናልፍ ነው ስለዚህ ነፃ መውጣት አለብን

#አንድ አማኝ ሱስ ውስጥ ከገባ ከአላማ ውጭ ይሆናል ፣ ሱስ ባሪያ ያደርጋል ፣ ድሃ ያደርጋል ፣ ለአጋንንት በር ይከፍታል አያችሁ ሱስ የጨለማውን ስራ የሚያስፋፋበት ትልቁ የሰይጣን በሩ ነው አማኝ የምንም ነገር ባሪያ ሆኖ ሊኖር አልተጠራም

#ሌላው የትላንት ልምድ ነው ነፃ ልንወጣ ሚገባው ትላንት በህይወታችን ብዙ ተአምራት ተደርጎ ሊሆን ይችላል ትላንት በህይወታችን ብዙ ነገር ተደርጓል ብለን ልምድ ሲሆንብን አዲስ ነገር እንዳይገለጥ ያደርጋል ከዚህም ነፃ ልንወጣ ይገባል

#“ለፍጥረታዊ ሰው የእግዚአብሔር መንፈስ ነገር ሞኝነት ነውና አይቀበለውም፤ በመንፈስም የሚመረመር ስለ ሆነ ሊያውቀው አይችልም።”
  — 1ኛ ቆሮንቶስ 2፥14

#ስጋዊነት እውነተኛውን መንፈሳዊ ህይወት እንዳንኖር የእግዚአብሔርን ክብር እንዳናይ በእግዚአብሔር አሰራር ላይ እምነት እንዳይኖረን መንፈስ ቅዱስን እንድንገፋ ያደርጋል ስለዚህ እግዚአብሔር ያየልንን ህይወት በሙላት እንድንኖር ገልጠን እንድናልፍ ከላይ ከዘረዘርኳቸው እስራቶች ልትፈቱ ይገባል ነፃ ያልወጣ ነፃ አያወጣም

#ነፃ ውጡ የሚባክን ዘመን እድሜ አይኑራችሁ ለብዙ ተጠርታችሁ ለራሳችሁ ሳትሆኑ ዘመናችሁ አይለቅ ።

#ሼር አድርጉ ቅዱሳን

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

23 Nov, 09:23


#የሚወድ እንጂ የሚያፈቅር አይጠላም 🤔
ያለ ምክንያት ያፈቀረ በምክንያት አይጠላም ፤በምክንያት የወደደ ግን ምክንያት ፈልጎ ይጠላል።

#አንድ አንድ ሰዎች የሚጠሏችሁ
እንዲጠሏችሁ የሚያደርግ ምክንያት ኖሮአቸው ወይም አግኝተውባችሁ አይደለም። ምክንያታቸው እነዚህ ናቸው
1:- የተሳሳተ እውቀት ስለ እናንተ
አእምሮአቸው ውስጥ ገብቶ ነው። ከሰይጣን ወይም ከሰው ወይም ካዩት ነገር ተነስተው የተሳሳተ ትርጉም ሰተውት።። የተሳሳተ እውቀት ስለገባባቸው ነው።
2:- ሰይጣን ጥላቻን በአእምሮአቸው ጨምሮባቸው ነው
3:- ሞገሳችሁ፣ ፀጋችሁ ፣ያላችሁ ነገር ፣ውበታችሁን ፣ስኬታችሁን ፣በብዙ ሰዎች መወደዳችሁን ሲያዩ ቀንተውባችሁ ነው።  ቀናተኛ ስለሆኑ ነው።
4:- እግዚአብሔርን ስለማያውቁ ነው
"ፍቅር የሌለው እግዚአብሔር አያውቅም"
5:-መንፈሳውያን ሳይሆኑ ስጋውያን ስለሆኑ ነው ገላ5፤22
6:- እግዚአብሔርን  ስለማይወዱ ነው ዮሐ15፤23

#ከፍቅር ውጪ መመላለስ :-
1:- ራስን ያስራል.ሰላምና ደስታን  ያሳጣል
2:- መስዋእትና መባን ተቀባይነት ያሳጣል
3:- አምልኮአችንን ከንቱ ያደርገዋል
4:- ለሰይጣን በር ይከፍታል
5:- በሰዎቹ ፀጋ ፣በረከት፣ተጠቃሚ እንዳንሆን ያደርገናል
6:- እግዚአብሔርን እንደማይወዱ ምልክቱ ነው ዮሀ15፤23
   
   #ለመውደድ ምክንያት አትፈልግ ፍቅር ከአፍቃሪው ማንነት የሚጀምር ስለሆነ።   1ዮሐ
"ፍቅር ከምክንያት አይጀምርም መውደድ እንጂ " wh
አፍቅሮ የሚጠላችሁ ሰው  ቀድሞውኑ አያፈቅራችሁም ነበር ቢወዳችሁ እንጂ  they like  you ,but not love you

የሚያፈቅርራችሁ ሰው ያለ ምክንያት ስለሚያፈቅራችሁ ፣ ምክንያት ፈልጎና ሲያገኝባችሐ አይጠላችሁም ፤ፍቅሩ አይቀዘቅዝም።

ሼር እያደረጋችሁ

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

22 Nov, 13:26


.     #የሚወድ እንጂ የሚያፈቅር አይጠላም 🤔
ያለ ምክንያት ያፈቀረ በምክንያት አይጠላም ፤በምክንያት የወደደ ግን ምክንያት ፈልጎ ይጠላል።

    #አንድ አንድ ሰዎች የሚጠሏችሁ እንዲጠሏችሁ
የሚያደርግ ምክንያት ኖሮአቸው ወይም አግኝተውባችሁ አይደለም።

#ለመውደድ ምክንያት አትፈልግ ፍቅር ከአፍቃሪው ማንነት የሚጀምር ስለሆነ።   1ዮሐ
"ፍቅር ከምክንያት አይጀምርም መውደድ እንጂ " wh
አፍቅሮ የሚጠላችሁ ሰው  ቀድሞውኑ አያፈቅራችሁም ነበር ቢወዳችሁ እንጂ  they like  you ,but not love you

#የሚያፈቅርራችሁ ሰው ያለ ምክንያት ስለሚያፈቅራችሁ ፣ ምክንያት ፈልጎና ሲያገኝባችሐ አይጠላችሁም ፤ፍቅሩ አይቀዘቅዝም።

#ፍቅር ስሜት አይደለም፤ምክንያታዊም አይደለም ፤ፍቅር የማንነት መገለጫ እና የልብ ምርጫና ውሳኔ ነው።
like is a feeling ,but love is your true identity manifastation and a choice .

.    ዮሐ15፤ 17,18,20,23
ኢየሱስን ለምን ጠሉት ?
ዮሴፍን ለምን ጠሉት
ዳዊትን ለምን ጠሉት

#ሲጠሉአችሁ መገለጫው:-
:- እናንተንና የናንተን ነገር ማየት አይፈልጉም፤ ስለ እናንተ ጥሩና መልካም ነገር ሲወራ መስማት አይወዱም

:- ስለ እናንተና የእናንተ  ነገር ምንም መልካም ማውራት አይወዱም ፤ይልቁኑ ስማችሁን ማጠልሸትና ተቃራኒ ያላዩትንና ያልሰሙት ፈጥረውና አጋነው ያወራሉ

:- እናንተን ሲያስቡና ሲያዩ ውስጣቸው ይበሳጫል

:- የእናንተን ነገር ለማበላሸት ፣ከቻሉም ለመግደል የተቻላቸውን ሁሉ ያደርጋሉ

    #በዚህ በጥላቻ እስራት ያላችሁ ራሳችሁን ፈትሹና በንስሀና በነፃ መውጣት ፀሎት እንዲሁም ያንን የምትጠሉትን ሰው በቀጥታ አግኝታችሁ ነግራችሁት ይቅርታ በመጠየቅና መልካም  በፍቅር የሆነ ግኑኝነት በመፍጠር ተፈወሱ።
"ፍቅር የሌለው እግዚአብሔርን አያውቅም "
" የምታየውን ወንድምህን ሳትወድ ያላየከውን እግዚአብሔርን ወዳለሁ እንዴት ትላለህ"


ክፍል ሁለት ይቀጥላል ሼር እያደረጋችሁ

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

21 Nov, 12:33


#እንዴት ወደ ማስተዋል እንምጣ ?

#መፅሐፍ ቅዱስ የመረጃ መፅሐፍ ነው ። ስለ እግዚአብሔር ሁሉ መረጃ አለ መረጃ ህይወት አይቀይርም ከመረጃ ቦኃላ ሬማ ወደሆነው ድምፅ መምጣት አለብን ካነበብነው ቦኃላ እግዚአብሔር ተናገረኝ ብለን ማሰብ አለብን ።

#የእግዚአብሔር ቃል የሚናገር ነው ። እንደተናገረን ማመን አለብን ። ለምሳሌ ስለ እስራኤል ካነበብን እና መረጃ ከያዝን ለኔ ነው ብለን ወስደን የህይወት መርህ አድርገን መመላለስ አለብን ።

#መፅሐፍ ቅዱስ ሲናገር ባሪያ መንገዱን በምን ያነፃል ቃልህን በማወቅ ይላል ካነበብነው ጊዜ ጀምሮ በቀረው ዘመናችን ሁሉ የህይወት ስርዓት እንዲሆን መውሰድ አለብን ። ሚከፈል ዋጋ እየከፈልን መኖር አለብን ።

#ጌታ ሶስቴ ተናገረኝ ካልን ስላልሰማን ሰምተን ስላላስተዋልን ነው ቀጥሎ መናገር ያቆማል እስክንሰማውና ተግባራዊ እስክናደርግ እግዚአብሔር በለአምን ተናገረው ደግሞ ተው አለው አልሰማ ሲል በአህያዋ ተናገረው ።

#መፅሐፍ ቅዱስ ሲናገር እግዚአብሔር አንድ ጊዜ ተናገረ እኔም ይሄን ሰማው ይላል እውነት ልቡ የሚሰማ ሰው አንድ ጊዜ በቂው ነው ። ሁለቴ ተናግሮ አንዴ አለመስማት በሽታ ነው ።

#እግዚአብሔር እንስማው ወደ ማስተዋል እንድንገባ ታውቃላችሁ ሄዋን ከእግዚአብሔር ሰምታለች እንጂ አላስተዋለችም ማዳመጥ ማለት የሰማነውን ቃል የህይወት ስርዓት መርህ ማድረግ በማስተዋል መመላለስ ማለት ነው ።

ሼር ማድረጉ እንዳይረሳ

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

20 Nov, 14:34


#ጣኦት ምንድነው ? ጣኦት እነማን ናቸው ?

#መዝ 96:5. ዘፀ 32:7. ዳን 5:7

#መፅሐፍ ቅዱስ የአሕዛብ አማልእክት ጣኦታት አጋንንቶች ናቻው ይለናል ።
ጣኦታት ማለት እርኩሳን ማለት ነው ።

#ወደ እርኩሰትና ወደ ክፋት የሰው ልጅን የሚመሩ ናቸው ። ጣኦታት ማለት የሰዎችን ልብ ፣ አይን ፣ አሳብ :  ከእግዚአብሔር ላይ አንስተው ወደ አማልእክቶች የሚያዞሩ ማለት ነው ።

#ሌላው ስለጣኦት ልናውቅ ሚገባው ከእግዚአብሔር በላይ የምንወደው ነገር ሁሉ ጣኦት ነው ። ከእግዚአብሔር በላይ ጊዜያችንን ፣ ገንዘባችንን ፣ ጉልባታችንን የሚይዝ ነገር ሁሉ ጣኦት ነው ።

# ጣኦት ማለት የአጋንቱን አለም ሰዎች የሚገናኙበት ቦታ ነዉ ። ጣኦታቶች በተለያየ ባህላቶች እራሳቸውን ይገልጣሉ ባህሎች ሁሉ መንፈሳዊ አይደሉም ከአጋንንት ጋ የተያያዙ ናቸው ። በመንፈስ ካልመረመርን ብዙዎቻችን ባህሌ በሚል ስም ወደ አጋንንት አለም ያስገቡናል ።

#ጣኦት እንዴት ይሰራል የሚለውን ስናይ በዘመናዊነት ይሰራል በሙዚቃ ፣ በፋሽን ይሰራል ።

#የእነዚህ አጋንንቶች ጣኦቶች ዋና አላማቸው ሰዎች እግዚአብሔርን ትተው አጋንንትን እንዲያመልኩ ነው ። ነገሮችን ፣ ሰዎች እራሳቸውን እንዲያመልኩ ማድረግ ነው ።

#ይሄን እውነት ማወቅ ነቅተን እንድንቀሳቀስ ጣኦት ማለት ማን ምን እንደሆነ ማወቅ በድንግዝግዝ ከመመላለስ እንተርፋለን በቀላሉ አንሸወደም ይሄ ብቻ አይደለም በመንፈስ መመርመር እንጀምራለን

#ታውቃላችሁ ሄዋን ጋ እባቡ መጥቶ ለምን ለሌላ ትገዢያለሽ አንቺ እራስሽ የራስሽ ገዢ  መሆን ትችያለሽ ነው ያላት ዛሬም ብዙዎች ጣኦት መሆኑ ያልገባቻው ነገር ግን እራሳቸውን የሚያመልኩ ሞልተዋል ይሄ ደግሞ ፈፅሞ ስህተት ነው ።

#ሰው እራሱን ለማምለክ አልተፈጠረም ። ስለዚህ እውቀት ነፃ ያወጣል ነፃ ውጡ በእውቀት ያለወቅነው ነገር ላይ ማምለጥ አንችልም ዛሬ ንቁ ጠላት አያታላችሁ ዘመናችሁ ለጣኦት በመገዛት አይለቅ ።

ሼር ማድረጉን እንዳትረሱ

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

17 Nov, 16:36


#ስለ እምነት ማወቅ ያለብን እውነታዎች

#እምነት ህግ ነው ። እምነት የእግዚአብሔር መንግሥት የሚሰራበት ህግ ነው ለሁሉ የሚሰራ ደግሞም ሁልጊዜ የሚሰራ ነው ። ህግ ሁሉንም በእኩል የሚያስተናግድ ለማንም የተለየ የአሰራር መንገድ የሌለው ነገር ነው ።

#እምነት ምኞት አይደለም ባባዶ ነገር ላይ ያለ ፉከራ አይደለም ። ታዲያ ምንድነው ? እምነት የእግዚአብሔር ቋንቋ ነው ። የመንፈሳዊ አለም መገበያያ የእግዚአብሔር ህግ ነው ።

#ሌላው ስለእምነት መወቅ ያለብን ኢየሱስ በምድር በነበረው ቆይታ የኖረው በእምነት ነው ሐዋሪያት አባቶቻችን የኖሩት በእምነት ነው ።

#“ጻድቅ ግን በእምነት ይኖራል ወደ ኋላም ቢያፈገፍግ፥ ነፍሴ በእርሱ ደስ አይላትም።”
  — ዕብራውያን 10፥38
እምነት የፅድቅ ፍሬ ነው ። እምነት በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን የሚገኝ የፅድቅ ፍሬ ነው ። እምነት በፆም ፀሎት ወይም በብዙ ጥረት የሚመጣ አይደለም ። ሰው በክርስቶስ ሲያምን የእግዚአብሔር ባህሪ ማንነት ተካፋይ ይሆናል ።

#እምነት ምርጫ ነው ። በማንም ሰው ላይ የሚሆነው ግለሰቡ ያመነው ነገር ነው ። እግዚአብሔር ህይወትን አለመጥፋትን ፋቅዶ ሰው ግን ሰው ግን ከእግዚአብሔር አሳብ ይልቅ ሞትንና ጥፋትን ቢያምን የሚሆንበት የእግዚአብሔር አሳብ ሳይሆን ግለሰቡ በልቡ ያመነው ነገር ነው ። ስለዚህ ፃድቅ ሲመላለስ እምነት ያስፈልገዋል ያለ እምነት ፃድቅ አይኖርም ።

#ከመለኮታዊ እምነት መፅሐፍ የተወሰደ
ይህን መፅሐፍ የምትፈልጉ በውስጥ አናግሩን ፃፉልን

#መልእህክቱን ሼር በማድረግ ለሌሎች አካፍሉ

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

15 Nov, 13:16


#ትጋት

ትጋት የጠቢብ ሰው ባህሪ ነው
ትጋት የአስተሳሰብ ውጤት ነው
#ትጋትም ስንፍናም የሚጀምረው አስተሳሰብ ላይ ነው

#ስለትጉ ሰው ስናይ
“የታካች እጅ ችግረኛ ታደርጋለች፤ የትጉ እጅ ግን ባለጠጋ ታደርጋለች።”
  — ምሳሌ 10፥4

#ትጉ ሰው ይገዛል ምሳሌ 19:6. ምሳሌ 18:16.
ትጉ ሰው በሄደበት ሁሉ በር ይከፈትለታል በሰዎች ተወዳጅ ነው ።
#አያችሁ ትጉ ሰው ባለጠጋ ነው ስለዚህ ለስንፍናችሁ ምክንያት ከመስጠት ተቆጠቡ ና ትጋታችሁን በሁሉ ጨምሩ

#ይሄን አስተውላችሁ ታውቃላችሁ በፀሎት ፣ በቃሉ ፣ በስራ የበረቱ ሰዎች ቀርባችሁ እኔም እንዲህ በበረታው ብላችሁ ታውቃላችሁ ይህ ማለት ትጋታቸው ተጋብቶባችሁ ነው ምን ልላችሁ ነው ሰነፍም ስትቀርቡ ከሰነፍ ጋ ስትውሉም ይህ ነው ሚሆነው ስንፍና ይጋባል

#ትጋት በምን በምን ያስፈልጋል ካልን በፀሎት ፣ እንግዳ በመቀበል ፣ በቃሉ ፣ ከቅዱሳን ጋ ሕብረት በመድረግ ፣ ለእግዚአብሔር ቃል በመታዘዝ ትጋት ያስፈልጋል
ስለዚህ በዚህ ሁሉ የተጋችሁ የበረታችሁ ሁኑ

#ትጋት ይብዛላችሁ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ቴሌግራም ይቀላቀሉን

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

14 Nov, 07:36


. ለእናንተ ጥቅም ብሎ የሚፈልጋችሁ ፣የሚጣላችሁ ፣ የሚያኮርፉችሁ ሰው የለም ፤ ለራሱ ጥቅም ሲል እንጂ !
ፊሊ2፤1-4
" እያንዳንዱ ለራሱ የሚጠቅመውን አይመልከት ፤ለባልንጀራው እንጂ"
እያንዳንዱ ባልንጀራውን ከራሱ ይልቅ እንዲሻል በትህትና ይቁጠር "

ገላ6፤1-2
" ከእናንተ እያንዳንዱ የአንዱን ሸክም ይሸከም ፤እንዲሁ የክርስቶስን ህግ ፈፅሙ"

ሸክምህን ልሸከምልህ ፣ በጦርነትህን ልዋጋልህ፣ እዳህን ልክፈልልህ፣ ብር ልስጥህ ፣ በአንተ ቦታ እኔ ልድከም ፣ ብሎ የሚጣላችሁ ፣ የሚያኮርፉችሁ የለም። ሸክሜን አልተሸከምክልኝም ብሎአችሁ እንጂ። ይህ ከራስ ጥቅም ፈላጊነት የተነሳ እንጂ ከፍቅር የተነሳ የሚደረግ ግኑኝነት አይደለም።
ሁሉም ሰው ራሱ ያለበትን ችግር ፣ ጥያቄ፣ መከራ፣ ፈተና፣ እርዳታ እንደሚያስፈልገው እንጂ፣ እናንተ የምታልፉበትን መከራ፣ፈተና፣ ችግር የሚያስብና፣ ፈልጎአችሁ መቶ ልርዳህ ብሎ የሚጣላችሁ የለም። ይህ የእራስ ወዳድነት ህይወት እንጂ የእውነተኛ ፍቅር መገለጫ አይደለም።

መክ4፤9-11
አንዳችን ለአንዳችን መነሳች ፣ ምቾት ፣ የጥንካሬ ምክንያት እንድንሆን እንጂ፣ አንዳችን ሌላውን፣ ጥለን አልፈን፣ አሸናፊ፣ታላቅ ሰው፣ ባለሀብት ፣ የተሳካለት ለመባል እንዲሁም ፣ አንዳችን ስንወድቅ አንዳችን በወደቀው ሰው ለመሳቅና ለመሳለቅ፣ ለመተቸትና ስም ለማጥፉት ፣ በወደቀው ሰው ታሪክ እኛ ለመመፃደቅ፣ ገቢ ማስገኛ ለመሆን ሳይሆን ፤ የወደቀውን ለማንሳት ፣ የበረደውን ለማሞቅ(ለማበረታታት ፣ ለማሳደግ፣ ትልቅ ቦታ ለመድረሳቸው ምክንያት ለመሆን ) ነበር የተፈጠርነው።

ይህ አልነበረም የወንጌል ትምህርት
እግዚአብሔር አንዳችንን ለአንዳችን ሲፈጥርና ሲሰጠን ፤ ለሌላኛው ሰው ምቾትና ፣ ለተፈጠረበተረ አላማ ስኬት እረዳትነት ነበር። ዘፍ2፤18,20።
የዘመን መጨረሻ መልክ "የእራስ ወዳድነት" አስተሳሰብና ህይወት አይውረሰን በክርስቶስ የነበረው " "ወንድሜ ከኔ ይሻላል የሚለው" " የራሳችንን ጥቅም ብቻ ሳይሆን የሌላችንን ጥቅም ማስበለጥ " ሀሳብ ይውረሰን።
ለራሳችን ጥቅም ስንል ብቻ አንፈላለግ ለፍቅር እንጂ!

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

10 Nov, 14:50


#በህይወታችን ልንሸሻቸው የሚገቡ ሰዎች

*በአገልግሎት
*በስራ
*በትዳር
*ብጓደኝነት ሊሆን ይችላል ልንሸሻቸው የሚገቡ ሰዎች #በየትኛውም መንገድ እነዚህን ሰዎች ካልሸሸን ከህይወታችን ካላስወጣን ስኬት የሚባል መንገድ ውስጥ አንገባም ደስተኛ አንሆንም

#ሁልጊዜ ደስ ልታሰኟቸው ከሚፈልጉ ሰዎች ሽሹ ለምን ሁልጊዜ ሰው ሰውን መስደሰት አይችልም

#ስለእናንተ አሉታዊ ነገር ከተሞሉ ሰዎች ሽሹ ስለእናንተ አወንታዊ ነገር ተፈጥሮ ፣ ፀጋ ፣ውበት ፣ ባህሪ እነዚህን እና የመሳሰሉ ነገሮች ስለእናንተ መልካም ያልሆነ ሁልጊዜ አሉታዊ ንግግር ብቻ እናንተ ላይ ከሚናገሩ ሰዎች ሽሹ

#አንድ ነገር ልንገራችሁ ስለእናንተ አሉታዊ ነገር ከተሞሉ ሰዎች እየዋላችሁ  እነግራቹሃለው የትም አትደርሱም

#ሌላው ለእናንተ አክብሮት ፍቅር ከሌላቸው ሰዎች ሽሹ በአገልግሎት አታገልግሏቸው ትልቅ ይሁኑ ትንሽ የተማሩ ይሁኑ ያልተማሩ የቅርብ ይሁኑ የሩቅ በቃ ማደግ መለወጥ እግዚአብሔር ባየላችሁ ከፍታ ልክ መገለጥ ምትፈልጉ ከሆነ ከእነዚህ ሰዎች ሽሹ

#በመጨረሻም ሰው ውሎውን ይመስላል ታዲያ ምን ከሚመስሉ ምን አይነት ልምድ ካላቸው ሰዎች ጋ ነው ምትውሉት የዋልንበትን ነው ምንመስለው ስለዚህ በንግግራችን ጤናማ ተናጋሪዎች በአስተሳሰባችን የተቀረፀ አስተሳሰብ እንዲኖረን ውሎአችንን ማስተካከል አብረን ምናሳልፋቸውን ሰዎች ማን መሆናቸው ማወቅ ተገቢ ነው

#ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ቴሌግራም ይቀላቀሉን

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

09 Nov, 10:43


#እግዚአብሔር መስማት ፍቃዱን ማወቅ መጠየቅ
#ክፍል ሁለት ከትላንት የቀጠለ

#ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ

#ሮሜ 8. ላይ በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩ እነዚህ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸው ይላል
ስለዚህ ለእግዚአብሔር ድምፅ ፍቃድ ልንገዛ ይገባል ልጆች ነን ካልን

#ታውቃላችሁ ድምፁን የማንሰማው ፍቃዱን የማንጠይቀው #ለማዳ ስንሆን ነው ለቃሉ ለመድረክ ለድምፁ ለማዳ ስንሆን ድምፁን አንሰማም

#በህይወታችን ዋጋ ያስከፈሉን ነገሮች ዋጋ ያስከፈሉን የእግዚአብሔርን ድምፅ ስላልሰማን ነው

#በአገልግሎት እግዚአብሔርን እየሰማን ብናገለግል አገልግሎታችን ረጅም ይሄዳል #የክርስትና የህይወት ስኬት ያለው የእግዚአብሔርን ድምፅ በመስማት ውስጥ ነው


#አብርሃምን ስናይ እግዚአብሔርን ሰምቶ በወጣበት ሁሉ ፍሬያማ ነበር የእግዚአብሔርን ድምፅ ባልሰማበት ዋጋ ከፍሏል ። እኔና እናንተ እንደ እግዚአብሔር ልጅ ምን ያህል የአባታችንን ድምፅ እየሰማን ነው ምንወጣው ምንገባው ?

#ዳዊት ሊወጣ ሲል ለእግዚአብሔር ልውጣን ብሎ ይጠይቅ ነበር ውጣ ሲለው ነበር ሚወጣው
#ሌላው ልናውቅ ሚገባው ለውሳኔ ጫፍ ደርሰን በቃ አጠናቀን ጨርሰን ፍቃድ የምንጠይቅ እንደዚህ አይጠየቅም ይሄ ማለት እግዚአብሔርን መምራት ነው እናም እግዚአብሔር እኛን ይምራን

#“ያለ እርሱ ፈቃድ የበላ ደስ ብሎትም ተድላን የቀመሰ ማን ነው?”
— መክብብ 2፥25
#ያለፍቃዱ የቀረበ ምግብ መብላት እንኳ አይቻልም ሲፈቅድልን ነው ስለዚህ በራሳችን ማስተዋል አንደገፍ #መፅሐፍ ቅዱስ ሲናገር በፍፁም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን በራስህ ማስተዋል አትደገፍ ይላል ሁልጊዜ ያለ እግዚአብሔር ምንም ነኝ ልንል ይገባል
#ፍቃዱን አለመጠየቅ ድምፁን ሰምቶ አለመውጣት በራስ መደገፍ ነው

#በመጨረሻም እግዚአብሔርን ፍቃድ ጠይቀን ደግሞ መታዘዝ መቻል አለብን እግዚአብሔር ተው ሲለን መተው እግዚአብሔር ተው ብሎን እሩቅ እንኳ ከተጓዝን ለመመለስ ዋጋ ቢየስከፍልም ከፊት ከለው መከራ አይበልጥምና መመለስ መቻል አለብን

#ተመለሱ ተው ሲለን ብቻ ሳይሆን ሂዱ ሲለንም ፍቃዱን ጠይቀን መሄድ መቻል አለብን ስንሄድ ፊት ለፊት ላይ ምንገጫገጭበት ቦታ ሊኖር ይችላል ግን ሂዱ ስንባል መሄድ ነው ሂዱ ያለ ጌታ ፍቃዱን የጠየቅነው ጌታ መሀል ላይ በሚገጥመን challenge ዝም አይለንም ያሻግረናል ስለዚህ ውጡ ሲለንም አትውጡ ሲለንም ለሁለቱም ድምፅ መታዘዝ አለብን እግዚአብሔር ይርዳን ተባርካቹኃል
ሊንኩን በመጫን ቴሌግራም ይቀላቀሉ

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

08 Nov, 12:41


#እግዚአብሔር መስማት #ፍቃዱን መጠየቅ

ዘፍጥረት 12. ዮሐ 10. ሮሜ

#አለማወቅ የእግዚአብሔርን ድምፅ እንዳንሰማ ሰምተን ተግባራዊ እንዳናደርግ ያደርገናል
#የእግዚአብሔር ድምፅ ሚያስፈልገን የችግር ጊዜ ብቻ አይደለም #ድምፁ ለየለት ህይወታችን ያስፈልገናል

#አንዳድ ጊዜ ታስተውላላችሁ ለምንም ነገር ፍቃድ ጠይቀን አናውቅም ልክ ልናገባ ስንል ጌታ ሆይ እንላለን እኛ ትልቅ አጀንዳ ብለን ያሰብነው ላይ ፍቃድህ ነው እንላለን የእግዚአብሔርን ድምፅ መስማት ፍቃዱን መጠየቅ ያለብን ሁልጊዜ ነው ።

#ዮሐ10 ላይ በጎቼ ድምፄን ይሰማሉ ይላል አያችሁ በግ የእረኛውን ድምፅ ይሰማል ሰምቶም ይታዘዛል መሰማሪያም ያገኛል ከአውሬዎችም ይተርፋል መስማት ያስመልጣል ሰምቶ መታዘዝ ፍሬያማ ያደርጋል

#እግዚአብሔርን የሚሰማ ሰው በየትኛውም ሁኔታ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋ ይሆናል መሀል ላይ መንገዱ ላይ ችግር ቢገጥመው ያሻግረዋል ስለዚህ እግዚአብሔርን መስማት ይሁንልን በዘፈቀደ በልምድ ከመኖር እግዚአብሔር ይጠብቀን

#እግዚአብሔርን መስማት የአንድ ሰሞን ወረት አይደለም የህይወት ስርሃት ነው ።
በግ እረኛውን ቀን እየመረጠ ወይም ሲርበው አይሰማም ሁልጊዜ ነው ሚሰማው ።

#በጎች ነን ካልን የእረኛውን ድምፅ ልንሰማ ግድ ነው ።

#ክፍል ሁለት ይቀጥላል ሼር አድርጉ ተባርካችኃል ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ቴሌግራም ይቀላቀሉን

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

07 Nov, 16:50


ከእግዚአብሔር የተሰጠህንን ፀጋ ፣ ሁሉ #እግዚአብሔርን #ለማክበር እና #ለሌሎች #የመፍትሔ ሰው ለመሆን እንጠቀም ፤ለዝና እና ለገንዘብ ብቻ ብለን ሳይሆን። ለተፈጠርንበት አላማ እንኑር ሳንወሰድ !
(እውቀት፣ ጊዜ፣ ገንዘብ፣ድምፅ፣ መድረክ ፣ ሙያችንን ሁሉ)
. ተባርካችኀል።

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

26 Oct, 08:28


. "እርሱ በመንፈስ ቅዱስ በእሳትም ያጠምቃችኀል "
ማቲ3፤11🔥
አጥማቂ ምረጡ ?
ኤረ ኢየሱስ ያጥምቃችሁ 🔥
በሰይጣን ክፉት ፣ በስጋዊነት ትእቢትና ቂመኛነት ፣ በፓለቲካ የዘረኝነት ጥላቻ ፤ በአለም ሴሰኝነት መዳራትና ገንዘብ ወዳድነት ፣ በሀይማኖት የግብዝነትና ማስመሰል አትጠመቁ። ! ! !
ኢየሱስ የሚያጠምቀን በመንፈስ ቅዱስና በእሳት ፣ በተቀጣጠለ በፀሎት መንፈስ፣ የራሳችንን ግዛት በማስፉፉት ሳይሆን በእግዚአብሔር መንግስት ራእይ ፣ በፍቅር በይቅርታና በትህትና መንፈስ ፣ በቃሉ እውነት ፣ለሌሎች ራስን አሳልፎ ሰቶ በመኖር መንፈስ፣ በሰማይ ፍቅር ፣ ወደ ሞት የሚነዱትን በወንጌል ለመድረስ በሆነ የነፍሳት ሸክም ፣ በመስጠት መንፈስ በቅስናና በፅድቅ ህይወት በሚያኖር መንፈስ እና በፀጋው ላይ በተመሰረተ የእምነት መልእክት ያጠምቃል። እንጂ :-!
:- ኢየሱስ በክፋት ፣ በጥላቻ፣ በወሬ፣ በቅንአት፣ በዘረኝነት፣ በሴሰኛነት፣ በገንዘብ ፍቅር ፣ ፣ በአለም ፍቅር፣ በግብዝነት (በአስመሳይነት) ፣ በክፉ መንፈስ፣ በትእቢት ፣ በራስ ወዳድነት አያጠምቅም። ዛሬ ከኢየሱስ ውጪ የሆኑ የተጠመቅንባቸው ነገሮች መንፈስ ጨምር በኢየሱስ
ስም የተደፉ ይሁኑ።
:- አሁኑኑ ላመነ ሰው ይሁንለት በእሳት በመንፈስ ቅዱስ በሚቀድስ ፣በሚያበረታ፣ በሚቀባ፣ ወደ ፀሎት እና አምልኮ በሚከት፣ ኢየሱስን ላገኘነው ሰው አውርተን መስክረን
እስከማይሰለቸን በሚያደርግ ፣የድፍረትና የሀይል መጠመቅ
ይሁንልን። መንፈስ ቅዱስ ይሙላባችሁ #ኤፌ5፤18
:- በመንፈስ ቅዱስ እሳት ስንጠመቅ በእምነት መንፈስ ተሞልተን ያለ ፍርሀት እንመላለሳለን

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

17 Oct, 13:40


. #እግዚአብሔርን #መፍራት #እንማር. አንብቡት👇
:- መዝ34፤1 ዛሬ ዛሬ ብዙ አይነት ትምህርቶች በበዙበት ዘመን ፣ብዙ አይነት ትምህርት ለመማር የምንሰለፈውንና ፣ በየሚዲያው ተጥደን የምንውለውን ያህል እግዚአብሔርን ስለ መፍራት ለመማር የሚፈልግ ሰው መሆን አለመፈለጋችንን ያህል ክስረት የለም።
እግዚአብሔር መፍራትን የሚያስተምሩንን እንፈልግ።

:- እግዚአብሔርን በመፍራት ለመኖር የሚፈልግ እግዚአብሔርን ስለመፍራት እውቀትን ይፈልጋል አጥብቆ ይማራል ፣ እግዚአብሔርን መፍራት በትምህርት ነው የሚመጣው። መዝ34፤1 ዘዳ14፤23, 17፤19, ምሳ2፤5, 9፤10
ምሳ15፤33።

:- መዝ 34፤1 እውነተኛ የእግዚአብሔር አገልጋይ ትልቁ ትምህርቱ ለትውልዱ ከምንም ነገር ( ከገንዘብ፣ከፃታ፣ ከቁሳቁስ..) በላይ የሚያስተምረው ፤ እግዚአብሔርን መፍራትን ነው።

:- 2ዜና26፤5 በተለይ በዚህ ዘመን ከምንም ነገር በላይ ልንፀልይ የሚገባን ነገር ቢኖር እግዚአብሔር መፍራትን የሚያስተምሩንን ሰዎች እግዚአብሔር እንዲያስነሳልን ነው።

:- ኢዩብ28፤28, ትልቁ ጥበብ እግዚአብሔርን መፍራት ነው ፤ ስለ ብዙ ነገሮች ማወቅና መተንተን ሳይሆን። ምሳ1፤7, 9፤10

:- ኢዩብ15፤4 እግዚአብሔርን መፍራት በእግዚአብሔር ፊት ሊቋረጥ የማይገባው አምልኮም ነው። it is #worship

:- መክ12፤13 እግዚአብሔርን መፍራት ማለት :-
የእግዚአብሔርን ህግ ወይም ቃል በተግባር መኖር ማለት ነው። በተጨረማመ ሀይማኖተኛ ፉት መታየትና መንፈሳዊ ንግግር በማብዛት መንፈሳዊ መስሎ ለመታየት መሞከር ሳይሆን።። it is #obedance to the word !

:- ምሳ3፤7 እግዚአብሔርን መፍራት ማለት:- ለሁሉ ነገራችን እግዚአብሔርን በመታመን መኖር ማለት ነወ
it is #Trusting God.

:- 2ዜና19፤7 እግዚአብሔርን መፍራት ማለት :-
- ሌላውን ሰው ላለመበደል መትጋት
- በሰው ፊት አለማዳላት። ዘር። ሀብት ማእረግ እያየን
- ጉቦ አለመስጠትም አለመቀበልም ነው።

:- ምሳ8፤13 ,መክ5፤7 እግዚአብሔር መፍራት ማለት :-
- ክፉ ድርጊትንና መንገድን መጥላት ማለት ነው
- ከትእቢተኛነትና አልታዘዝ ባይነት ወቶ ትሁትና ታዛዥ መሆን ማለት ነው
- በአንደበቱ ጠማማነት ፣ስድብን፣ውሸትን የማይናገር ሰው መሆን ማለት ነው

:- ሮሜ13፤18, መዝ14፤6 እግዚአብሔርን መፍራት የሌላቸው ሰዎች ፤ የሰላምን የእርቅን መንገድ አይቀበሉም

:- ዘዳ6፤13, 10፤20 እግዚአብሔርን ስለ መፍራትን እንድንማር ብቻ ሳይሆን ፤ እግዚአብሔርን በመፍራት እንድንኖር ታዘንማል። it is a #commandment

:- መክ5፤7 በንግግራችን ሁሉ እግዚአብሔርን እንድንፈራ ማስጠንቀቂያ ተሰቶናል ።when we #talk let us fear God

:- ዘፍ20፤11 እግዚአብሔርን መፍራት የሌለበትን ቦታ ለይተን ማወቅና ከዚያ ስፍራ ስፍራ መሸሽ ፣ካልሆነም በጥንቃቄና በጥበብ መመላለስ ይገባናል። run away or walk in wisdom , when you see the place that no fear of God .

:- ምሳ10፤27, 14፤27, 24፤4 ኢሳ33፤6 ምሳ19፤2 እግዚአብሔርን የመፍራት ጥቅሞችና ትሩፋቶች :-
- ዘመንን ታረዝማለች
- ከሞት ወጥመድ ታስመልጣለች
- የህይወት ምንጭ ናት
- ትህትናና ክብርን ታስገኛለች
- ባለጠግነት፣ክብርና ህይወት ታስገኛለች
- ወደ ህይወት ይመራል
- በጥጋብ ያኖራል
- ከክፉ ነገር ይጠብቀናል
- በዘመናችንን የሰላምና የፀጥታ ፣የጤንነት ያደርግልናል

👉 በመጨረሻም እግዚአብሔርን ወደ መፍራት እሚወሰወዱንን ትምህርቶች ፈላጊ፣ እግዚአብሔርን መፍራትን ለትውልዳችን የምናስተምር አስተማሪዎች፤ እግዚአብሔርን በመፍራት የምንኖር ልጆች መሆን ይብዛልን።
ትውልዴ ሆይ በቃ እግዚአብሔር በሁሉ እንፍራ !!🙏
ፓስተር ውብሸት ነኝ
ከ focus international ministry/solas 🙏

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

13 Oct, 13:03


. #አምልኮ #ለእግዚአብሔር #ብቻ ! 🙌
#አምላካችን :- በሙሉ #ልባችን ፣#ሀሳባችን እና #ሀይላችን #የምንወደውና #የምናገለግለው ነገር ሁሉ ነው።

#አምላካች :- ከምንም ነገር በላይ የምንወደው ፣ የምናከብረው ፣ የምንፈራው ፣ጊዜአችንን የምንሰጠው ፣ ገንዘባችንን የምናውልበት ፣ ያለ ማቋረጥ የምናስበው፣ የምንታመንበት ፣ ተስፉ የምናደርገው ፣ለሰዎች ሁሉ ለማሳየት የምንተጋለት ነገር ነው።

#አምልኮ ማለት :- ለዚያ ከሁሉ በላይ ላደረግነው ፣ለምንወደው የምንሰጠው ምላሽ እና በመታዘዝ ፣ በመቀደስ ፣ በትህትና ፣ በፍትህ ፣ በምህረት ፣ በመስጠትና በመሰጠት ፣ እንዲሁም በመዝሙር ጭምር የሚገለጥ ኑሮ ነው።
#አምልኮ ማለት :- በህይወታችን አምላክ ካደረግነው ጋር ያለን #ጤናማና #ቅዱስ የሆነ #ግኑኝነት እና #ምላሽ ነው። !
#አምላካችን ማለት:- በሙሉ #ልባችን ፣#ሀሳባችን እና #ሀይላችን #የምንወደውና #የምናገለግለው ነገር ሁሉ ነው።
ስለዚህ :-
👉ሰይጣንን እና የባእድ አማልክትን፣ ሙታንን አታምልኩ
👉ራሳችሁን (ውበታችሁን፣እውቀታችሁን፣ችሎታችሁን አታምልኩ)
👉ቤተሰባችሁን፣ ልጆቻችሁን፣ አታምልኩ
👉ገንዘባችሁን እና ቁሳቁስን አታምልኩ
👉ሀይማኖታችሁን ፣ዘራችሁን፣ ባህላችሁን አታምልኩ
👉ሚዲያ አታምልኩ ፣ ስራችሁን አታምልኩ።
" እኔና ቤቴ እግዚአብሔርን እናመልካለን "፣ እናንተም ይህንን ፅሁፍ የምታነቡ ሁሉ የምታመልኩትን( ከሁሉ በላይ የምትወዱትን፣ ሁሉ ነገራችሁን የምትሰጡትኑ፣ የምትታመኑትን፣ የምትፈሩትን፣ የመትሰውለትን ዛሬ ምረጡ ?!ለጣኦታት ፣ ለገንዘብ ፣ለራሴ፣ ለባህሌን አላመልክም !
መዝሙር ጋበዝኳችሁ
የአስቴር አበበን።። ሳሙኤልን እንካ !!

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

05 Oct, 14:14


#እንንቃ #ሁሌም #መንፈሳዊ #ጦርነት #ውስጥ #ነን !
:-ሰይጣን በር ከፈትንለት አልከፈትንለት እኛን መዋጋት አይተውም። መንፈሳዊ ጦርነት ውስጥ ነን ! ሰይጣን ቀልዶ አያውቅም ፣ መቼም አይዘናጋም! መቼም አይራራም!
:- ሰይጣን ከእኛ በበለጠ በብዙ ልምድ ፣ ዘዴ ለዘመናት የተካነ ነው ፤ በማሳት ፣ በመክሰስ፣ በመፈታተን፣በማታለል፣ በመጣል፣ ተስፉ በማስቅረጥ ፣አደጋ በማድረስ፣ በመለያየት ፣ በማድከም ፣ ብዙ ተቃዋሚዎችን ቀብቶ በማስነሳት፣ ክፉ በሳቦችን በመላክ።

:- ዳግም የተወለድን በሙሉ የጌታ በመሆናችን፣ በሱ መንግስት ላይ በበቀል እንደተቀባን ስላወቀ ፣ ህልማችን የሚያደርስበትን ኪሳራ ስለሚያውቅ፣ እኛ ብንባረክ ፣ጤና ቢኖረን፣ ብንበረታ ኪሳራውን ያውቃልና።

:-ስለዚህ በብዙ የእግዚአብሔር ሀይል ፣ የፀሎት ትጋት፣ በመንፈሳዊ ጦርነት መጋደል ፣በመንቃት መመላለስ ሁሌም ያስፈልገናል።
2ቆሮ2፤11 ኤፌ6፤10-16 ራእ12፤9-11 2ቆሮ10፤3-7, 11፤3

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

02 Oct, 11:59


. "#መንፈስ #ቅዱስ #ይሙላባችሁ " ኤፌ5፤18
. ነገራ ነገር፣ አለምና የአለም ኮተት፣ ወሬ ሀሜትና ጥላቻ
፣ዘረኝነትና ምቀኝነት ፣ቅንአትና ትእቢት ፣ቂምና ክፉት፣ እኔነትና እልከኛነት ፣ዝሙትና ርኩሰት አይሙላባችሁ። መንፈስ ቅዱስ ይሙላባችሁ።🔥🙏🔥
እርሱ ሲሞላባችሁ በየቀኑ :-
:-ሀይልና ልዩ ልዩ የፀጋ ስጦታዎች ትሞላላችሁ ትበረታላች
:- ደስታ ፣ሰላም፣እረፍትና ሀሴት ይሞላባችኀል
:- ንግግራችሁ በጨው እንደተቀመመ የፀጋ ቃል ይሆናል
:- በቅድስና ለመኖር ሀጢአትን እንቢ የማለት አቅም ታገኛላችሁ
:- ህይወታችሁ በፍቅርና በይቅርታ የተሞላ ይሆናል።
:- ሰጪዎች ትሆናላችሁ
:- የእምነት መንፈስ ይሞላባችኀል
:- እርሱ ትሁት ያደርጋችኀል ግብዝነትና ትእቢት ይወገዳል
:- የምታሁት ህልምና ራእይ አጋንንታዊና በእርኩሰት የተሞላ አይሆንም
:- በምድራዊው ኮተትና በአለማዊ ነገሮች ፍቅር ልባችሁ አይወረስም
:- በእሳት የተሞላ ፤አጋንንት አብሮት የማይኖር ሰው ትሆናላችሁ
:- ያለማቋረጥ በአላማችሁ ላይ ያተኮራችሁ ፣በመንፈስ የምትቃጠሉ ትሆናላችሁ።
:- በፀሎት በምስጋና በአምልኮና በመንፈሳዊ ውጊያ በበቀል ይሞላናል
:- ለነፍሳት ሸክም ወንጌልን ላልዳኑት ለመናገር ያነሳሳናል በድፍረትም ይሞላናል
ነገራ ነገር፣አለምና የአለም ኮተት፣ ወሬ ሀሜትና ጥላቻ፣ዘረኝነትና ምቀኝነት ፣ቅንአትና ትእቢት ፣ቂምና ክፉት ፣እኔነትና ግትርነት እልከኝነት፣ ዝሙትና አመፅ አይሙላባችሁ። መንፈስ ቅዱስ ይሙላባችሁ።
ይሄን እያነበባችሁ አሁን በመንፈስ ቅዱስ እሳት ይሙላችሁ ጌታ። 🔥🙏🔥

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

25 Sep, 02:57


. #ጠላቶቻችሁ #ይሳቀቁ #የአባቴ #ብሩካን #ሳቁ
. ደስታ ነፃ የወጣ ሰው ህይወት መገለጫ ነው።በአጋንንት
እስራት ውስጥ ያለ ሰው ሰላምና ደስታ የራቀው፣ፊቱ ጨምዳዳ ነው።
. ደስታ ለሌሎች ሰዎች መልካምን የማሰብና የማድረግ ውጤት ነው።በሰው ላይ ክፉት ያረገዘ መቼም አይደሰትም
. በእግዚአብሔር መንፈስ ቁጥጥር ስር በሙላት ስትሆን ደስታህ ሞልቶ ይፈሳል። መንፈስ ይሙላባችሁ። አሜን
. በእግዚአብሔር የመታመን የእምነት ኑሮ ውጤት ነው።
የሚጨነቅ ሰው ደስታው የተነጠቀበት በራሱ የታመነ ነው
. ደስታ በበጎ ህሊና በንፁህ ልብ የመመላለስ ውጤት ነው።
ቅንነቱን ያጣ ፣በልቡ ቂም የያዘ ፣ መቼም ደስታ አያይም
. ደስታ የሁሉ ነገራችን ምንጭ ጌታን ብቻ የማድረግ ውጤት ነው። በጌታ ላይ አይናችንን ፣ተስፉችንን ስናደርግ ደስታ አይናፍቀንም ፣በሙላት እንኖረዋለን እንጂ።
. ደስታ በአላማ የተሞላ ፣በራሱ ጉዳይ ላይ ያተኮረ ሰው መገለጫ ነው።
. ደስታ የፀሎት ህይወት ያላቸው ሰዎች ሰማያዊ ሀይል ነው
"የእግዚአብሔር ደስታ ሀይልችን ነው "
:- ደስተኛ ስትሆን ጠላት የሚደነግጥብህ፣ ሀይልህ ብዙ ፣በስጋ ጤናማ፣ በመንፈስ ቅዱስ እየተሞላህ ፣በብዙ ፀጋ የምታገለግል እና ለአከባቢህ ሁሉ ሰላምና ሳቅን የምታጋራ ሞገሳም ትሆናለህ። .

በአጋንንት እስራት ውስጥ ያለ ሰው ደስታ የራቀው፣ፊቱ ጨምዳዳ ነው። ጌታ የፈታው ፣ሰማይ ብድራቱ ፣ኢየሱስ ጌታው የሆነ ሰው ይደሰታል ፤ ደስታው አይወሰድበትም።
REJOICE IN THE LORD ፊሊ4፤4
እስቃለሁ ጠላቴ እያየ እስቃለሁ ሁኔታው እያለ እስቃለሁ
"ሰይጣን ይሳቀቅ ጌታ ያላችሁ እናንተ ሁሌም ሳቁ " p wou
https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

20 Sep, 10:08


.በልዩ ልዩ #ፈተና #መከራ #ስደት ለምታልፉ ሁሉ :- ጠላት
1:- እግዚአብሔርን ከማመን፣ ከመከተልና ከማምለክ
2:- እግዚአብሔርን ከማገልገል ከጥሪአችሁ እናንተን ማውጣትና ማስቆም ስለሚፈልግ ነው ይህንን ሁሉ እያደረገባችሁ ያለው ስለዚህ :-
:- ይህ ሁሉ በእናንተ ላይ የተቀመጠ ታላቅ ፀጋ ፣የተለየ አላማና ጥሪ እግዚአብሔር በአናንተ እንዳለው ሰይጣን ስለሚያውቅ ፣ እናንተ አምልጣችሁ ብዙዎችን ቤተሰቦቻችሁን እንደምታስመልጡ ስለገባው፣የእናንተ ነገ በብዙ በረከት ፣ ክብርና ከፍታ እንደሆነ ስለተረዳ፣ ቀንቶ ፣ተናዶ፣ እኛን ከዚያ ለማስቀረት ፈልጎ ነው።
:- በምንም አይነት የህይወት ውጣውረድ፣ በምንም አይነት መከራና ፈተና እንዲሁም ልባችሁን የሚያሳዝን ነገር ውስጥ ብታልፉም ከመስቀሉ ስር ፣ከፀጋው ዙፉን አትጥፉ።
:-አገልግሎታችሁን አታቁም። የጠራችሁ ሰው ሳይሆን እግዚአብሔርን ነው። የከፋባችሁ ፣ፊታቸውን ያጠቆሩባችሁ ፣ የገፋአችሁ ሰዎች እንጂ እግዚአብሔር አይደለም። እግዚአብሔር እንደሆነ ፍቅሩ ለእናንተ ዛሬም ያው ነው፣ በእናንተ ላይ ያለውን አላማውን፣ ሀሳቡን ፣ጥሪውን ፣አልቀየረም። ይልቁኑ በዚህ ሁሉ በብዙ አበርትቶ ፣ አስተምሮ በሚበልጥ እጥፍ ፀጋና ሀይል በበቀል ያስነሳችኀል።
:- የዛሬ ማጣት ፣ በገፋት ፣መናቅ ፣ የሰው እጅ ማየት ቀን አልፎ በብዙዎች የምትፈለጉበት፣ለሌሎች የምትትረፈረፉበት ጊዜ ሩቅ አይደለም። በምንም አይነት ችግር ውስጥ ብትሆኑም እንኳን አምልኮና አገልግሎታችሁን አታቁሙ። እግዚአብሔር የሚያመልኩትን ከመከራ ያወጣቸዋል።
:- የትዳር መፍረስና ግጭቶች ፈተና፣የገንዘብ እጦት፣በወዳጅ መከዳት፣ የስም መጠልሸት ፣ በሀሰት ክስ፣ በሰዎች ደባ ፣ በስራ ማጣት ፣ በስጋ በሀጢአት መውደቅ ፣በልዩ ልዩ ህመሞች ውስጥ ብታልፉም እነዚህን 3 ነገሮች አስተውሉ :-
1:- በብዙ መከራ የፀናውን፣ የታገሰውን የአምላኩን ፈቃድ ማድረግ ሳያቆም ጥሪውን ፈፅሞ ያለፈውን ኢየሱስን ተመልከቱት። እርሱ ከፊቱ ያለውን ደስታ እያሰበ በመስቀል ፣በመከራ እንደታገሰ እናንተም ከፊታችሁ ያለውን ደስታና ታላቅ ብድራታችሁን እያሰባችሁ ታገሱ።
#ዕብ12፤1-4
2:- የትኛውም አይነት ችግር ውስጥ የምታልፉት እግዚአብሔር ስለማይወዳችሁ፣ ስለማያይ፣ ለመከራ ስለፈጠራችሁ፣ጠላታችሁ ከእግዚአብሔር በላይ ስለሆነ ወይም እናንተ ከአለም ሁሉ ህዝብ የተለየ ሀጢአተኛ ስለሆናችሁ አንደ አይደለ ማወቅ አለባችሁ። ብዙ የእምነት አባቶቻችንም በብዙ ልዩ ልዩ መከራ፣ፈተናና ስደት አልፈዋል። #ዕብ12፤1
3:- የኔ የተለየ ነው ፣አትበሉ ከማጉረምረም ተጠበቁ ፣ ሌሎች ብዙዎች አሉ እንደ እናንተው በልዩ ልዩ መከራ የሚያልፉ። ይህ ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔርን ከምትችሉት በላይ እንድትፈተኑ የማይፈቅድ ፣ የፀጋውን አቅም በእናንተ ያስቀመጠውን የሚተማመን እንደሆነና በፀጋው ችላችሁ ፣ፀንታችሁ እንደምታልፉት ዛሬን እመኑ። በመጨረሻም ከመከራው ጋር መውጫንም እግዚአብሔር እንደሚያዘጋጅላችሁ አትርሱ። ይህ መጨረሻችሁ አይደለም ማለፊያችሁ እንጂ የከፍታ፣የመትረፍረፍ፣ የክብር ዘመን ከፊታችሁ ስላለ ፤ በትግስት፣በመፅናትና በእምነት አምልኮአችሁንና አገልግሎታችሁን ቀጥሉ።
#1ቆሮ10፤13
ወደ ኀላ በሚያፈገፍግ፣ አቋራጭን ለመጠቀም በሚቸኩል፣ በሚያጉረመርም ሰው ነፍሱ ደስ አትሰኝም።
" ፃድቅ ግን በእምነት በህይወት ይኖራል"#ዕብ10፤38-39
:- መከራ ውስጥ ከመግባታችሁ በፊትም ከገባችሁ በኀላም ፀልዩ
:- በምንም አይነት መከራ ውስጥ ሆናችሁ ጌታን ማምለክ፣ ማመስገን እና ማገልገላችሁን አታቁሙ።
ወንድማችሁ የእግዚአብሔር ሰው ፓስተር ውብሸት ነኝ
Focus international ministry/solas

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

15 Sep, 15:30


#አጋንንት #ማስወጣት እና #ነፃ #መውጣት ባለበት በዚያ
1:- መንፈስ የሆነው ጌታ ኢየሱስ በጌትነቱ በትንሳኤው ሀይል በዚያ በሙላት የመኖሩ ምልክት ነው 2ቆሮ3፤17
"ጌታ ግን መንፈስ ነው የጌታ መንፈስ ጌታ በሆነበት
በዚያ አርነት "
2:- የእግዚአብሔር መንግስት በዚያ በሙላት የመኖሩ ምልክት ነው
ሉቃ11፤ 20
3:- ለአማኞች የልጅነት ስልጣናቸው መመለሱና በዚያ ስልጣን የመመላለስ ምልክት ነው
ማር16፤17 ሉቃ10፤19
4:- ሰይጣን በኢየሱስ ትንሳኤ የመሸነፉና ስልጣኑን የመገፈፉ ምልክት ነው
ቆላ2፤15 ማቲ28፤18
5:- በመንፈስ ቅዱስና በሀይል አጋንንትን በማስወጣት
ፀጋ የመቀባታችን ምልክት ነው
ሐዋ10፤38
6:- በመካከላችን ነፃ አውጪው መንፈስ ቅዱስ በስራ
ላይ በበላይነት ተገልጦ እንዳለ ምልክት ነው።
https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

12 Sep, 08:06


🎆🙏 የምስራች
"እንግዲህ በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን ኩነኔ የለባቸውም"
ሮሜ8፤1
የቀድሞ የአሁን የወደፊቱ ሀጢአታችን ሁሉም፣በፈሰሰው የኢየሱስ ደም ይቅር ተብሏል።

ኢየሱስ አንዴ ለሁሌ ሞቶልናል!
ስለዚህ
" ዓመፃቸው የተሰረየላቸው ኃጢአታቸውም የተከደነላቸው ብፁዓን ናቸው፤" ጌታ ኃጢአቱን የማይቆጥርበት ሰው ብፁዕ ነው።"ሮሜ 4:7-8
ብፁእ ነኝ !
የቆጠረልንን ትተን ያማይቆጠርብንን መቁጠር እናቁም !
"ቀንና ለሊት በአምላካችን ፊት የሚከሳቸው የወንድሞች ከሳሽ ተጥሏል " ራዕ12፤10
የሰውን ሀጢአት ቆጠራ ላይ ያላችሁ የሰይጣን የከሳሹ አገልጋዮችና ፤ የራሳችሁን ደብቃችሁ ሌላውን ለመውገር ድንጋይ ይዛችሁ ፤ያላችሁት ግብዞች ,
ያላችሁት በኢየሱስ ፊት መሆኑን ላስታውሳች ፤ እንዲያውም ደስ ይበላችሁ የእናንተም አይቆጠርባችሁም !!

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

08 Sep, 16:16


. " #በራሳችሁ #መንገድ #ላይ #አጠብጥቡ"
አንዳችን ከሌላችን መገፉፉት፣መጠላለፉ ያቆሳስለናል፣
ያዘገየናል፣ሀይል ያባክንብናል፣ ለጠላት በር ይከፍታል .!
"እያንዳንዱም በመንገዱ ላይ ይሮጣል..አንዱም ከአንዱ ጋር አይጋፉም ፤እያንዳንዱም በመንገዱ ይጠበጥባል፣ በሰልፉም መሀል ያልፉሉ እነርሱም አይቆስሉም" ኢዩ2፤7-8
አንዳችን ሌላችንን ልንረዳ እንጂ ልንጎዳ አልተፈጠርንም
" "WE ARE NOT CALLED TO COMPET EACH OTHER,BUT TO COMPLETE EACH OTHER "
:- በአላማችን ላይ ስናተኩር ፣ መስመራችንን ጠብቀን ስንሮጥ ሀይላች እና ፍጥነታችን እየጨመረ ይሔዳል
:- አንዳችን ከሌላችን ጋር መገፉፉት ትተን በመደጋገፍ ወደ ህልማችን ፍፃሜ ሁላችንም እንደርሳለን።
:- የእግዚአብሔር መንግስት ሌላውን በመቅደማችንና በመብለጣችን ሳይሆን የኛን ሀላፊነት በመወጣታችን ብቻ ነው የሚሸልመን። አትድከሙ ላላውን ለመብለጥ
:- በአላማው ላይ በማተኮር ፣ለሌላው ሩጫ እንቅፉት ከመሆን የተቆጠበ ሰው የራሱን ፍፃሜ ክብር ያያል
:- በራሱ መስመር ላይ በማተኮር በሚገጥሙን ፈተናዎች፣ ተቃውሞዎችና ተግዳሮቶች ወደ ኀላ #ሳናፈገፍግ በትእግስት፣ ራሳችንን በመግዛት እና በእምነት ፣በተስፉ ተሞልተን እንሩጥ ሩጫችንን። መውረሳችን አይቀሬ ነው
:- አንዳችን ከሌላችን መገፉፉት ብዙ ቁስለኛ ያበዛል፣
ይል ይጨርሳል፣ ከራሳችን ፍፃሜ ክብር ያዘገየናል።
በራሳችሁ ጉዳይ ላይ አተኩሩ #1ተሰ4፤11
:- በሰላምና በፀትታ መኖር ከፈለጋችሁ
:- ስኬታማ እና ፍሬያማ መሆንና መብዛት ከፈለጋችሁ
የምንሸለምበትን ሩጫ እንሩጥ
p woub 🦅🎯🔥
focus international ministry/solas
https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

01 Sep, 08:53


. #የሰው #እጅ #የለበትም #100% #ፀጋ ብቻ ነው

ኢየሱስ ማለት :-#ፀጋና #እውነት ማለት ነው ዮሐ1፤15,17
ኢየሱስ ህግ ሰጪውም ህግ ፈፃሚውም እሱ ኢየሱስ ነው።
ይህ ነው ወንጌል
"የሆንኩትን ሁሉ #የሆንኩት፣በኔ የተሰራው ሁሉ #የሰራው #ፀጋወ ብቻ ነው።"። #1ቆሮ 15፤10

"እኔ ህያው ሆኜ አልኖርም ክርስቶስ በእኔ ይኖራል" ገላ2፤20
መንፈሳዊነት እኛ የምንኖረው ህይወት ሳይሆን ኢየሱስ ራሱ በእኛ የሚታይበት፣የሚሰራበት፣የሚኖርበት ህይወት ነው።

ኢየሱስ ህግ ሰጪውም ህግ ፈፃሚውም እሱ ነው።ይህ ነው ወንጌል
:- " እኔም አልፈርድብሺም ..ሐጂ ....ደግመሽም ሀጢአትን አትስሪ"
ዮሐ8፤ 11
ኢየሱስ የትላንት ሀጢአቷን ብቻ ሳይሆን ይቅር ያለው ፣ከዚህ በኀላ በቅድስናም የምትኖርበትን አቅም ነው የሰጣት። ሰው በራሱ አቅም
ሀጢአት አለመስራት መለወጥ አይችልም። የፀጋው ውጤት ነው የቅድስና የተለወጠ ህይወት። ቲቶ2፤11-14

:- ፀጋ ማለት የዳንነት ፣የሚለውጠን ፣የቆምንበት፣የምንኖርበት፣
የምናሸንፍበት፣ የምንሰጥበት፣ የምንወድበት ፣ይቅር የምንልበት ሁሉ
ነገራችን ነው። በራሳችን ከፀጋው ውጪ የምንጥረው፣ህይወት በፍፁም የፀጋ ህይወት ፣የፅድቅ ፍሬ ፣ እግዚአብሔር የሚደሰትበት እና
የሚቀበለውም ህይወት አይደለም።

:- መንፈስ ቅዱስ የተሰጠን ፣በውስጣችን ያለው እግዚአብሔር የሚቀበለውን ፣የሚደሰትበትን የፀጋ ህይወት በእኛ ለመግለጥ ነው።
:ገላ5፤22 የመንፈስ ፍሬ የሰው የጥረት ውጤት አይደለም የፀጋ እንጂ"

:- 1ቆሮ 15፤10 2ቆሮ12፤8-10 ጳውሎስን ያዳነው፣ የለወጠው ፀጋው፣ በሱ የተሰሩትን ተአምራት የሰራው ፀጋው፣የፃፋቸውን መልእክቶች ሁሉ ያፃፈው ፀጋው፣ በዚያ ሁሉ መከራ ፣ስደት፣ መከራ ያቆመው ፣ ያበረታው ፀጋ ነው። ከፀጋው ውጪ የራሱ የሆነ ብቃት የሌለው እንደኛው ደካማ ስጋ ለባሽ የሆነ ፣ በብዙ የሚፈተን፣የሚያዝን፣
የሚሳሳት ሰው ነበረ። ኤፌ1፤7 የፀጋው ክብር የተመሰገነ ይሁን።

ዛሬም በእኛ ህይወት ፀጋው ብቻ ነው 100% የሰው እጅ የለበትም
"በህግ ልትፀድቁ የምትፈልጉ ከክርስቶስ ተለይታችሁ ከፀጋው ወድቃችኀል " ፅድቅ ፣ቅድስና የፀጋው ውጤት እንጂ በራስ ጥረትየሚመጣ፣የሚኖር ህይወት አይደለም። እንፍቀድለት ለፀጋው።
:- መፍጨርጨር ፣ጌታንም ለማገዝ መጣር እናቁምና ለመንፈስ ቅዱስ፣ለፀጋው ራሳችንን እናስገዛ፣ እኔ አልችልም አንተ በእኔ ትችላለህ ፣አንተ ለፈለከው ህይወት ፈቅድልሀለሁ አንተ በኔ ኑር በሉት በህይወታችሁ በእርሱ ፀጋ በሆነ ፣በጥረት ያልሆነ፣መለወጥ ይሆናል፣
ያስቸገራችሁን ሱስ ተነቅሎ ሔዶ ታዩታላችሁ፣ትደነቃላችሁም።

ገላ2፤20 " እኔ ህያው ሆኜ አልኖርም ክርስቶስ በኤ ይኖራል"
100% ፀጋው ብቻ
ፓስተር ውብሸት ነኝ የፀጋው ፍሬ።
focus / Solas international

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

31 Aug, 14:00


. #ከሰይጣን #የከፋም #አለ #ለካ
:- በመፅሀፍ ቅዱስ ውስጥ አንድም ቦታ #ሰይጣን #ከሰይጣን ሲዋጋ፣ሲጣላ እርስ በርሱ ሲከፉፈል አይታይም።
:- ሰይጣን እንኳ እርስ በእርሱ #አይለያይም #አይበላላም #አይካሰስም፣#አይጠላላም፣እንዲህ አንዱ ሌላውን ሊበቀል፣ሊጎዳ ፣ሊያጠፉ አይተጋም።
" እርስ በእርስዋ የምትለያይ #መንግስት ሁላ ትጠፉለች፤ #እርስ በእርሱ #የሚለያይ #ከተማም ሁሉ ወይም #ቤት #አይቆምም። ማቲ12፤25
" እርስ በርስዋ የምትለያይ መንግስት ሁሉ ትጠፋለች ቤትም በቤት ላይ የወድቃል"... ሰይጣን ደግሞ እርስ በርሱ ከተለያየ መንግስቱ እንዴት ይቆማል ? #ሉቃ11፤17-18

:- አንዱ ወንድም ሌላው ወንድሙ ጋር፣አንዱ አገልጋይ ከሌላው አገልጋይ ጋር፣ አንዱ ሀይማኖት ከሌላው ሀይማኖት ጋር፣አንዱ ብሔር ከሌላው ብሔር ጋር ፣ እርስ በእርሳችን ስንጓተት፣ስንጠላለፍ፣ስንካሰስ፣ ስንወነጃጀል፣ ስንጣላ ፣ ሰይጣን እንኳን የሌለው ባህሪይ ያለን አንድ አዲስ ፍጡር የሆንን ያህል ይሰማኛል፣ የኛ የኢትዮጲያውያንና ኤርትራውያንን ባህርይ ሳይ። ኤረ ወገን እንንቃ ሰው እንሁን።

:-እኛ ኢትዮጲያውያን ከሰይጣን እንኳ የከፉ ተግባር፣አላማ ውስጥ ተጠምደን መገኘታችን ምን የሚሉት እርግማን ፣የክፉት ጥግ ፣ጨለምተኝነት እንደሆነ ሳስብ አዝናለሁ

:- አጋንንቶች ሲሸነፉ እንኳ ተባብረው ፣ተያይዘው ፣ተደጋግፈው የጋራ አላማቸውን ለማሳካት ፣የፈለጉትን ስፍራ ፣ግለሰብ ለመያዝ ፣ ጠላቶቻችን ናቸው ያሉትን ለማጥቃት ሲተጉ፣እኛ ኢትዮጲያውያን ፣የገዛ ወንድማችንን፣ሀገራችንን ለማጥፉት ለሊትና ቀን ከጋራ ጠላቶቻችን ጋር እንኳን ሳይቀር የምንስማማው ነገር በጣም ለማመን አይደለም ለማሰብ የሚከብደኝ የክፉት ፣የራስን ወንድም፣ወገን፣ሀገር የመጥላታችን የምቀኝነታችን ጥግ ያሳየኛል።

:- እርስ በእርሳችን ስንካሰስ፣ ስንቆሳሰል፣ ስንዋጋ፣ አንዱ የሰራውን ሌላችን ስናፈርስ፣ አንዳችን ሌላችንን ለመጉዳት ጉድጓድ ስንቆፍር ፣ በውሸት በፈጠራ ክስ ስም በማጠልሸት ስንጠመድ፣ አንዳችን ሌላው የሰራውን መልካም ስራ ከማድነቅና ከማመስገን ይልቅ ለማጣጣል ፣ ያለመሰልቸት ስንጋጋጥ ኤረ ምን አይነት የጉድ ህዝብ ነን ያሰኛል።

:- በሌላው ሀገር ሰዎች አንዱ ለአንዱ መስዋእት ሆነው ፣ድልድይ ሆነው፣ ህይወታቸውን፣ ሀገራቸውን ሲቀይሩ ፣እኛ በራሳችን ሀገር እንኳን ተረዳድተን ሰርተን ከመለወጥ ይልቅ፣ እኛ የኛኑ ሰው ለመግደል፣ለማክሰር ፤በየጠንቋዩ ቤት ሊቱን ሙሉ ስንዞር እናድራለን።

:- በዚህ ከቀጠልን የቤተክርስትያን ትልቁን ተልእኮ እንዴት መወጣት እንደሚቻል ፣እንደ ሀገር እንዴት ሳንፈራርስ በአንድነት ፀንተን እንደምንቀጥል፣ እንደ ቤተሰብ የሚቀጥለውን ትውልድ እንዴት መታደግ እንደምንችል አላውቅም። ቆም ብለን ቢያንስ ቢያንስ ባንደጋገፍ ፣ ወዳጅ መሆን ካልቻልን ጠላት አንሁን፣
ከጠላት ጋር አናብር። ብዙ የማያስማሙን ጉዳዮች ቢኖሩ እንኳ በዋና ነገሮቻችን ላይ ተስማምተን ፣ተደጋግፈን ፣እንደ ቤተሰብ፣እንደ ቤተክርስቲያን ፣እንደ ሀገር ፣ ህልውናችንን ለማስቀጠል፣ እየመጡ ያሉትን ከፊታችን የተጋረጡብን የመበታተን አደጋዎች ብናስቀር፣ መቆሳሰል ብንተው ይበጀናል።
. ከሰይጣን የከፋን አንሁን ፣ ሰይጣን እንኳን እርስ በርሱ አይባላም፣አይመቀኝም፣አንዱ አንዱን ሊያጠፉ እንቅልፍ አቶ አያድርም። ሰው ነንና ሰው እንሁን። 🙏😭🇪🇹🇪🇷
! መልእክት ነውና ጆሮ ያለው ይስማ ? https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

30 Aug, 07:53


#ልባርካችሁ #እውነተኛ #ወዳጅ #ይስጣችሁ #ያድርጋች !
#እውነተኛ #የልብ #ወዳጅ #እንሁን
:-ከጀርባ የማያማችሁ ፣ሚስጢራችሁን የሚጠብቅ
:-በችግራችሁ ቀን ማንም በማይደርስላችሁ ቀን ሚደርስላችሁ
:-ለውድቀታችሁ ጉድጓድ እየቆፈረ ስማችሁን እያጠፉ የማይዞር
:-ከመጣ ከሔደው ጋር የማይነፍስ ፣በክፉ ቀን የማይከዳ
:-ከጠላቶቻችሁ ጋር ማይመክርባችሁ
:-ሁሉ ሲሸሹአችሁ ፊታቸውን ሲያዞሩ ፊቱን የማያዞርባችሁ
:-በበረታችሁ ቀን ብቻ ሳይሆን በደከማችሁም ቀን የማይለያችሁ
:-ሊጠቀምባችሁ ብቻ ሳይሆን ሊጠቅማችሁ የሚፈልጋችሁ
:-በጠላቶቻችሁ ፊት በአደባባይ ስለ እናንተ የሚሟገትላችሁ፣ ስለ እናንተ በላላችሁበት ስማችሁ ሲነሳ የሚያስቆም
:-በጥቅም የማይሸጣችሁ የማይለውጣችሁ
:-በሰላም ጊዜ ያወራችሁትን የሰራችሁትን በተጣላችሁ ቀን ሚስጢር የሚጠብቅ ፣መልሶ እናንተን ለመጉዳት የማይጠቀምን
:-እውነትን በፍቅር ለራሳችሁ ቀርቦ የሚነግራችሁ
:-የሚፀልይላችሁ ፣የሚያበረታታችሁ ፣ በግል ሚገስፃችሁ
:-በደስታችሁ የሚደሰት ፣በሀዘናችሁ ቀን የሚያዝን
:-አምሮባችሁ ሲያይ ደስ ብሎት የሚያደንቃችሁ ማይቀናባችሁ
:-ሀሳባችሁን የሚረዳችሁ ፣ለመፍረድ የማይቸኩልባችሁ
:-ሌሎች ስለ እናንተ ከሚነግሯቸው ይልቅ እናንተ የነገራችኀቸውን የሚያምኑ
:- ለቁም ነገር፣ለጫወታም፣ ለመንፈሳዊም ነገር የሚመች
🙏 እንዲህ አይነት #የልብ ወዳጅ #ሁን !#ሁኚ #እንሁን !!
እንደ #ይሁዳ ያልሆነ.. ጥቅም የማይለውጠው
እንደ #ጴጥሮስ .በክፉ ቀን እንደማያውቃችሁ ማይከዳ
እንደ ደሊላ የማይላጭ ፣ለጠላት ሚስጢራችሁን ማያወጣ
:-ነገር ግን እንደ ዮናታን ያለ ወዳጅ ይስጠንም እንሁንም!
ፓስተር ውብሸት ነኝ
focus /solas international
https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

29 Aug, 09:00


እባካችሁን በቸርነቱ የተሰጠንን :- #እድሜ #ፀጋ #አእምሮ #ገንዘብ #አንደበት #ስልጣን #እድል #ጥበብ #ሚዲያ አናባክን ፤#በማስተዋል ፣#እግዚአብሔርን #በመፍራት #ለመልካም #አላማ #እንጠቀም።ህይወት #አጭርና #በሀላፊነት የተሞላች ናት #ነገ #እንጠየቅባታለን።🙏😭
" ኢየሱስም መልካምን እያደረገ ዞረ " ሐዋ10፤38
"በክርስቶስ መልካሙን ለማድረግ ተፈጠርን" ኤፌ2፤10

👉እባካችሁን ከእግዚአብሔር በቸርነቱ የተሰጠንን ሁሉ:-

1:- #እግዚአብሔርን ለማክበር for the glory of God ፣ መንግስቱን ለማስፋት ፣ ለወንጌል ተልእኮ እንጠቀም
2:- #ሌሎች ሰዎችን ለማነፅ፣ለመጥቀም፣ፀጋን ልንጨምርላቸው ፣ ለመለወጥ ፣ለማዳን ፣ ነፃ ለማውጣት እንጠቀም። ለማዋረድ፣ ለማሸማቀቅ፣ተስፉ ለማስቆረጥ፣
ሳይሆን።
3:- #ሀገርን ለመገንባት ፣ ትውልድን በመልካም ስብእና፣ አስተሳሰብ ለማነፅ እንጠቀም እንጂ፤ለመለያየት ፣ ለመከፉፈል፣ አይሁን።
4:-#ለራሳችንም የሚጠቅመውን ፣ነገ በጌታ ፊት የሚያሸልመንን፣ በእድሜአችን ፍፃሜ ዞር ብለን ስናይ የማንፀፀትበትን፣ህሊናችንን የማይከሰንን ሰርተን እንለፍ።
"የተፈቀደ ነገር ፣ማድረግ የቻልነው ነገር ሁሉ አይጠቅምምና ፤በማስተዋል እንኑር ፣እንናገር፣ እንፃፍ።
ታናሽ ወንድማችሁ ፓስተር ውብሸት ነኝ 🙏
ከጠቀማችሁ ለሌሎች ማጋራትን አትርሱ
focus/solas international ministry USA
https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

22 Aug, 09:28


. "#ሀሳብ #ቶሎ #ካልነገስክባት #ትነግስብሀለች "
. " ሀጢአት በደጅህ ታደባለች ንገስባት ሳትነግስብህ"
ሀጢአትን ፣ጥላቻን፣ ቅንአትን፣ ትእቢትን ፣ በሀሳብ ደረጃ ገና ስትመጣ ቶሎ አንተ ካልገደልካት እርስዋ ቆይታ አንተን ትገልሀለች !
የሰይጣን ዋናው ትኩረት ሐሳባችንን ማበላሸት ነው 2ቆሮ11፤3። አእምሮአችንን አናከራየው !!
የተበላሸ ሀሳብ ማሰላሰል ፣የሚገልህን አውሬ ማሳድግ ነው፤ ወይም መርዝ እየጠጡ አልሞትም የማለት ያህል ትልቅ ድድብና ነው። wake up .
:- ሀሳብ እንደ መርዝ ነው ይመርዛል ፣ይበክላል ፣ያበላሻል ያረክሳል
:- ሀሳብ እንደ መሪ ነው ወደ ወደደው ይመራሀል፣
:- ሀሳብ እንደ በር ነው ሰይጣንን ያስገባብሀል
:- ሀሳብ እንደ አይን ነው ነገሮችን ስሎ ያሳይሀል
:- ሀሳብ ቦታ ፣ጊዜ ፣ደረጃ አይመርጥም የትም ፣ሁሉም በየትኛውም ሰአት ይመጣል
:- ሀሳብ እንደ ዘር ነው አንድ ተዘርቶ ብዙ ያፈራል
:- ሀሳብ ምንጭ ነው የምናየው ነገር፣ የተግባር ፣የንግግር የባህርይ ሁሉ ምንጭ ነው
:-ሀሳብ ገዢ ነው ሁለመናን መቆጣጠር ይችላል
"አጥብቀህ ልብህን(ሀሳብህን) ጠብቅ የህይወት መውጫ ነውና"
:- ሀሳብ ፈሪ ያደርጋል ፣በመሀል ያስቆማል እንዲሁም ሀሳብ ያጀግናል ያስቀጥላል
:- ሀሳብ የድህነትም የብልጥግናም መጀመሪያ ነው
በሀሳቡ የደሄዬ በተግባሩና በኑሮው አይበለጥግም።
:-ሰውን በሀሳባችንን እየጠላነው በተግባራችን መውደድ አንችልም። ሀሳባችንን እንለውጥ ተግባራችን እንዲለወጥ።
:- ፍቅርም ጥላቻም፣ትህትናም ትእቢትም፣ መድሀኒትም መርዝም መስራት ፣በሀሳባችን ውስጥ ነው የሚጀምሩት
:- ሰው በሀሳቡን ለሊት ያሰበውን በቀን ከማድረግ አይመለስም ፤ስለዚህ ሀሳባችንን እንለውጥ።

። ። የሰይጣን ጥይቱ ሀሳብ ነው
:- ሰው አስተሳሰቡ ከተበላሸ ሁሉም ነገሩ ነው የሚበላሸው
:-ወደ አእምሮአችሁ ለሚገቡ ሐሳቦች ጥንቃቄ አድርጉ
የምታሰላስሏቸውን ሀሳቦች ቆም ብላችሁ አጣሩ መርምሩ በቃሉ ብርሀን !? ፊሊ4፤8

አእምሮአችሁን የምንለውጥባቸው ሁለቱ መንገዶች
1:- ነፃ ማውጣት ወይም መማረክ 2ቆሮ10፤5 ፊሊ4፤8 2ቆሮ2፤11 2ቆሮ11፤3
:- ከአለማዊ የተበላሸ ፣የረከሰ፣የተጣመመ ሀሳብ ፣ ነፃ አውጡ
:- እግዚአብሔር ከካደ የሰይጣን ሀሳብ ፣
:- በአለማመን ፣ በአመፅ፣ በውሸት ፣ በትእቢት ፣ በክፉ ሀሳብ ፣ ከተሞላ ሀሳብ ነፃ አውጡ
:- ሌሎች ሰዎችን በሚጎዳ ፣ በተንኮልና በራስ ወዳድነት ብቻ ላይ ካተኮረ ሀሳብ ነፃ አውጡ
:- በጭንቀት ፣በፍርሀት ፣ በተስፉ መቁረጥ ፣ በሁከት ከተሞላ ሀሳብ ነፃ አውጡ
:- በስንፍና፣ በማጉረም፣ በማያመሰግን ፣ በሚኮንንና በክስ በተሞላ ሀሳብ ነፃ አውጡ

2:- ማደስ :- በእውነት እውቀት መሙላት ሮሜ12፤2, ምሳ19፤2 ቆላ3፤10 ,,16
:-በክርሰቶስ የተሰራልንን ስራ በማወቅ በዚያ ውስጥ ብቻ ማንነታችንን ማወቅ IDENTITY
:- ቃሉ እንደሚለው ብቻ ማሰብ ፣በቃሉ መርህ መሞላትና መኖር PRINCEPLE
:- እንደቃሉ ብቻ መናገር .CONFESION...SPEAKING ....
P woubshet
Focus/solas international 🇪🇹🇪🇷🇺🇸

https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

21 Aug, 12:45


መንፈሳዊ ወጣት
ከክፉ የጎልማሳነት ምኞት እንደ ዮሴፍ የሚሸሽ ነው

ዛሬ ላይ ሆኖ ለነገ ህልም ያለው ፣ በከንቱ የማይባዝን ፣በአላማ የሚማር የሚሰራ ነው።

የዘመኑን የአለባበስ ፣ አነጋገር እስታይል አሳዳጅ ሳይሆን እግዚአብሔርን በመምሰል ፣ በጭምትነትና ራሱን በመግዛት ፣ ለፉሺን ደንታ የሌለው ነው

የቤተሰቡን፣የሀገሩን የድህነት ቀንበር ለመስበር ተግቶ ዝቅ ብሎ የሚሰራ እንጂ የወጣት ጡረተኛ ፣የቤተሰቡንና የሀገሩን ሀብት አባካኝ አይደለም

በወሬና በአሉባልታ መንደር በየሚዲያው ተጥዶ እየዋለ ፣ጊዜውን ፣ውስጡ ያለውን እምቅ አቅም የማያባክን አስተዋይና እራሱን ከአልባሌ ሱሶች የሚጠብቅ ነው።

ከቤተክርስትያን የማይቀር ፣በትጋትና በታማኝነት ፣ቃሉን የሚማር፣ የሚፀልይ፣ መሪዎቹን የሚታዘዝ፣ለወንጌል ስርጭት ያለመታከት የሚተጋ ነው

በትምህርት ቤት፣በስራው ስፍራ፣ ኑሮው የሚናገርለት፣ሁሉም የጌታ ስለመሆኑ ( አይጠጣም፣ዘፈን አይሰማም፣ ጭፈራ ቤት አይሔድም፣አያጨስም፣ አይሰርቅም እያሉ ፣የሚመሰክሩለት ፤ የጌታ በመሆነኑ የማያፍር ነው።

እግዚአብሔርን እየመሰሉ ሊኖሩ ከሚወዱት ጋር፣ ፍቅርን፣ፅድቅን፣ ሰላምን የሚከታተል፣በንፁህ ልብ የጌታን
ስም ከሚጠሩት ጋር መንፈሳዊ ህብረት የሚያደርግ ፣ ከአመፅ ሁሉ የሚሸሽ ነው።

ስለ ሀገሩ የሚፀልይ፣ለሀገሩ መሪዎች እና ህግ የሚገዛ፣በአመፅ ህብረት ውስጥ ፣በጥላቻና ዘረኝነት ስብሰባዎችና ተግባሮች መሀል የሚይሳተፍ፤ በሀገሩ ላይ የልማት፣የለውጥ ፣መምጣትን የሚመኝና ለዚያ የተቻለውን ሁሉ ሀላፊነት የሚወጣ፤ ልማት እንጂ ጥፉት መንደር የማይገኝ ፣አስተሳሰቡ የታደሰ ፣ ብዙ የፈጠራ ሀሳቦች የሚያመነጭ ፣ በስሜት ብቻ ሳይሆን በአላማ፣ በእውቀት ፣ በመርህ የሚመላለስ ነው።
ይህ ነው መንፈሳዊ ወጣት
ውብሸት ነኝ
FOCUS /SOLAS INTERNATIONAL

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

15 Aug, 08:29


ዋጋችን!
እኛ ስህተታችን፣ ሰዎችና ሰይጣንም ያሉንን አይደለንም።
:- የእኛ ዋጋ እኛ የተሰራንበት እቃ ልክ ነው። ለእኛ በተከፈለው መስዋእትነት ፣እኛን ለመስራት በዋለው እቃ ልክ ነው።

:- ለአንድ ነገር ትክክለኛ ዋጋው የሚተመነው በሰሪው እንጂ በገዢው አይደለም። የእኛም ትክክለኛ ዋጋ የሚተመነው በሰሪአችን ነው። ወይም የሚያውቀው ባለቤቱ ሰሪው ነው። ማንም እየተነሳ ተመን /ስም እንዲሰጣች አትፍቀዱም አትቀበሉም።

:- ማንኛውም የከበረ እቃ ምንም ያህል የከበረ ቢሆንም ፣የእቃውን ክብር በማያውቁት ሰዎች መሀል እስከተቀመጠ ድረስ የረከሰ ፣ዋጋ ቢስ
እንዲሁም ተፈላጊነት የሌለው ነው የሚሆነው። የት እንደምንገኝ እንምረጥ። ዋጋችንን በማያውቁ መሀል ከተገኘህ ርካሽ እንሆናለን።
በማይመጥነን ቦታ ፣ ለማንነታችን ትክክለኛ ክብር በማይሰጡን መሀከል አንቀመጥ

:- የከበረ ውድ እቃ መጠቅለያው የማያምር ወይም በአቧራና በጭቃ የተሸፈነ ከሆነ ፤ምንም የከበረ እቃ ቢሆንም ተፈላጊነቱ ይቀንሳል። አንዋዋራችን ፣ባህርያችን፣አነጋገራችን ፣ተግባራችን ዋጋችንን እንዳያራክስብን እንጠንቀቅ።
:- የከበረ ነገር አቧራ ስለሸፈነው፣ ዋጋውን አይቀንስም፣አቧራውን አጥበን አንፅተን ብናየው የተሰራበት ማንነቱ ዛሬም ያው ነው። በተለያዩ ፈተናዎች ፣ማጣቶች ፣ ውድቀቶች ውስጥ መገኘታችን ለጊዜው ተፈላጊነታችንን ቢገዳደሩትም ፣ ማንነታችን ግን አይቀየርም። እኛ ስህተታችንን አይደለንም። ማንነት በድካም፣ በማጣት፣ በልብስ አይለካም። ሰዎችን ከውጪ አይተን ፣ከስህተታቸው ተነስተን አንናቃቸው።
don’t judge the book by its cover መፅሀፉን በውጫዊ ሽፉኑ አትመዝነው
p woubshet
FOCUS /SOLAS INTERNATIONAL USA
https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

20 Jul, 09:29


https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

18 Jul, 12:44


https://t.me/focusinternationalministry

FOCUS IN'T MINISTRY ባለ ራዕይ ትውልድ ማስነሳት

17 Jul, 13:09


ለወንዶች እንፀልይ እንዲሁም ወንዶች እንንቃ !!!
ONE OF JEZEBEL & FARON SPIRIT FOCUS IS MAN !
አንዱ የኤልዛቤል እና የፈርኦን መንፈስ ትኩረት ወንድ ላይ ነው !?
1ነገ20፤25
በእግዚአብሔር ፊት ክፉት ለመስራት ራሱን እንደ ሸጠ ፣ሚስቱም ኤልዛቤል እንደ ነዳችው ፣ እንደ አክአብ ያለ ሰው አልነበረም
ዘፀ1፤ 16 ,22
እናንተ የእብራውያንን ሴቶች ስታዋልዱ፣ለመውለድ እንደደረሱ ባያችሁ ጊዜ፤ወንድ ቢሆን ግደሉት እና ወደ ወንዝ ጣሉት ሴት ብትሆን ግን በህይወት ትኑር

WHY ? ለምን ? እርሱ ወንድ
BECAUSE HE IS :-
THE HEAD OF THE HOUSE
THE LEADER OF THE HOUSE
THE PROVIDER OF THE HOUSE
THE PROTECTOR OF THE HOUSE
THE SOURCE OF GENERATION
GOD ASSIGNED OR ORDEND REPRESENTATIVE OF GOD
THE DELIVERER AND LEADER TO PROMIS LAND

THIS BOTH SPIRIT WANT :-
ይህ መንፈስ የሚፈልፈው ?
TO DESTROY HIS VISION AND CALLING
TO CONTROL HIM AND HIS POSITION
TO MAKE AND FEEL HIM WORTHLESS
TO DESTROY HIS FELLOWSHIP WITH GOD /SPIRITUAL LIFE
TO DISCONNECT HIM FROM HIS WIFE AND HIS CHILDREN
TO KILL HIM EARLY
👇
MAN LET US WAKE UP AND
FOCUS ON :-
FIXING OUR SPIRITUAL LIFE
TAKE BACK GOD GIVEN VISION
TAKE BACK OUR MAN POSITION OR ROLL OF LEADERSHIP
TAKE BACK OUR RESPONSIBILITY AS A FATHER AND MODEL
LET US BE A LOVING ,CARRING ,PROTECTIVE HOUSBAND FOR OUR WIFE

ዛሬ በአቋም ፣በአላማ የጨከኑትን ፣ትልቅ ራእይ ሰንቀው የሚነሱ ወንዶች ላይ ያተኮረ
የሚያስጨንቅ፣ባሪያ ያደረገ ፣ የሚያስፈራራ
ስልጣኑን ፣መሪነቱን ለመቆጣጠር የሚተጋ አመፀኛ መንፈስ
የሚያሳድድ ፣ከቤቱ፣ከራእዩ፣ከልጆቹ የሚያለያይ
እንዲሁም ራእዩንም እሱንም በስጋ ጭምር ያለ ጊዜው የሚገል መንፈስ
በኢየሱስ ስም የተመታ ይሁን
P WOUBSHET
FOCUS/SOLAS INTERNATIONAL
https://t.me/focusinternationalministry