Publicaciones de Telegram de Farankaa - ፈረንካ

The primary goal of this page is to enhance the financial literacy of Ethiopians by offering valuable insights on investment, banking, insurance, capital markets, and taxation.
1,818 Suscriptores
276 Fotos
2 Videos
Última Actualización 09.03.2025 03:43
Canales Similares

1,523,073 Suscriptores

35,958 Suscriptores

30,123 Suscriptores
El contenido más reciente compartido por Farankaa - ፈረንካ en Telegram
አዲስ ረቂቅ መመሪያ‼️
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን የDematerialization directive ረቂቅ ለህዝብ ውይይት ክፍት አድርጓል።
በአማርኛው ሰነደ መዋዕለ ነዋዮችን/አክሲዮኖችን/ ግዑዝ አልባ ማድረግ ተብሎ የተተረጎመው dematerialization በቀላሉ ከእዚህ ቀደም በወረቀት ሰርተፊኬት የሚሰጡ የአክሲዮን ባለቤትነት ማረጋገጫዎችን በአንድ ማዕከል/Central Depository/ በሚቀመጥ በSoftcopy certificate መተካትን የሚመለከት ነው።
Dematerialization አክሲዮኖችን በቀላሉ ከአንድ ባለአክሲዮን ወደሌላው በሽያጭ ለማስተላለፍ የሚረዳ ነው። ሂደቱ በዋናነት አክሲዮናቸውን በኢትዮጵያ የአክሲዮን ገበያ ላይ የማስመዝገብ ግዴታ የተጣለባቸው ተቋማትን (ባንኮች፣ የኢንሹራስ ኩባንያዎች እንዲሁም ሌሎች የህዝብ ጥቅም ያለባቸው ተቋማት) እና አክሲዮን ለህዝብ በመሸጥ የሚደራጁ ተቋማትን የሚመለከት ነው።
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን የDematerialization directive ረቂቅ ለህዝብ ውይይት ክፍት አድርጓል።
በአማርኛው ሰነደ መዋዕለ ነዋዮችን/አክሲዮኖችን/ ግዑዝ አልባ ማድረግ ተብሎ የተተረጎመው dematerialization በቀላሉ ከእዚህ ቀደም በወረቀት ሰርተፊኬት የሚሰጡ የአክሲዮን ባለቤትነት ማረጋገጫዎችን በአንድ ማዕከል/Central Depository/ በሚቀመጥ በSoftcopy certificate መተካትን የሚመለከት ነው።
Dematerialization አክሲዮኖችን በቀላሉ ከአንድ ባለአክሲዮን ወደሌላው በሽያጭ ለማስተላለፍ የሚረዳ ነው። ሂደቱ በዋናነት አክሲዮናቸውን በኢትዮጵያ የአክሲዮን ገበያ ላይ የማስመዝገብ ግዴታ የተጣለባቸው ተቋማትን (ባንኮች፣ የኢንሹራስ ኩባንያዎች እንዲሁም ሌሎች የህዝብ ጥቅም ያለባቸው ተቋማት) እና አክሲዮን ለህዝብ በመሸጥ የሚደራጁ ተቋማትን የሚመለከት ነው።
ኢትዮ ቴሌኮም በሚቀጥለው ሳምንት 10% የባለቤትነት ድርሻ አዲስ በተቋቋመው የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ/Ethiopia Securities Exchange-ESX/ አማካይነት አክሲዮን ለህዝብ በመሸጥ የመጀመሪያው ተቋም ለመሆን ዝግጅት መጨረሱን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ብሩክ ታዬ ገልጸዋል።
ተጨማሪ ለማንበብ👇
https://www.reuters.com/business/media-telecom/ethio-telecom-kick-off-ethopian-stock-trading-with-10-flotation-next-week-2024-10-09/
ተጨማሪ ለማንበብ👇
https://www.reuters.com/business/media-telecom/ethio-telecom-kick-off-ethopian-stock-trading-with-10-flotation-next-week-2024-10-09/
አዲሱ የሪል ስቴት ልማት እና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግመታ ረቂቅ አዋጅ በዘርፉ ላይ ሲስተዋሉ የነበሩ ብዙ ችግሮችን ይፈታል ተብሎ ይገመታል።
ከእንግዲህ አማላይ ፎቶ መሸጥ አይቻልም፣ ቢሸጥ እንኳ ገንዘቡ በዝግ ሒሳብ ይቀመጣል፣ የተገነባው ሪልስቴት ስሙ ለባለቤቱ እስኪዘዋወር ድረስ በእግድ ውስጥ ይቆያል፣ እንደድሮው ከቤት ገዢ ገንዘብ ሰብስቦ ለባንክ ማስያዝ አይኖርም። ዘርፉ ስርዓት ሊይዝ ይገባል፣ እንደውም ዘግይቷል። ብዙዎች ጥሪታቸውን ተነጥቀዋል፣ አልቅሰዋል፣ ይበቃል መባሉ ትክክል ነው።
ከእንግዲህ አማላይ ፎቶ መሸጥ አይቻልም፣ ቢሸጥ እንኳ ገንዘቡ በዝግ ሒሳብ ይቀመጣል፣ የተገነባው ሪልስቴት ስሙ ለባለቤቱ እስኪዘዋወር ድረስ በእግድ ውስጥ ይቆያል፣ እንደድሮው ከቤት ገዢ ገንዘብ ሰብስቦ ለባንክ ማስያዝ አይኖርም። ዘርፉ ስርዓት ሊይዝ ይገባል፣ እንደውም ዘግይቷል። ብዙዎች ጥሪታቸውን ተነጥቀዋል፣ አልቅሰዋል፣ ይበቃል መባሉ ትክክል ነው።
አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የቀድሞ ተማሪዎቹ የፊታችን ቅዳሜና እሁድ ተሰባስበው ትዝታቸውን ያወጉ ዘንድ፣ ቤታቸውንና መነሻቸውን ይጎበኙ ዘንድ፣ ስኬታቸውን ያወጉ ዘንድ ጋብዟል።
እኔም እንደቀድሞ ተመራቂነቴ በኢሜል አድራሻዬ የጥሪ ካርድ ደርሶኛል። ከሁለቱ ቀን በአንዱ ተገኝቼ ትዝታዬን ከወዳጆቼ ጋር አወጋለሁ፣ ከሰዎች ጋር እተዋወቃለሁ።
መገኘት የምትችሉ የቀድሞ ተመራቂዎች ሁሉ ቤታችሁን፣ መነሻችሁን ትጎበኙ ዘንድ ተጋብዛችኋል።
እኔም እንደቀድሞ ተመራቂነቴ በኢሜል አድራሻዬ የጥሪ ካርድ ደርሶኛል። ከሁለቱ ቀን በአንዱ ተገኝቼ ትዝታዬን ከወዳጆቼ ጋር አወጋለሁ፣ ከሰዎች ጋር እተዋወቃለሁ።
መገኘት የምትችሉ የቀድሞ ተመራቂዎች ሁሉ ቤታችሁን፣ መነሻችሁን ትጎበኙ ዘንድ ተጋብዛችኋል።
በፋይናንስ ገበያ ውስጥ Haircut ምንድነው?
የኢትዮጵያ መንግስት በቅርቡ ከአበዳሪዎቹ ጋር አዲስ የብድር ማራዘሚያ ድርድር የጀመረ ሲሆን በዩሮቦንድ የተበደረው 1 ቢሊዮን ዶላር ብድር ላይ 20% Haircut እንዲደረግለት ጠይቋል።
በፋይናንስ ገበያ ውስጥ ተበዳሪ ከአበዳሪው ጋር በሚያደርገው አዲስ የብድር ማራዘሚያና አከፋፈል ስምምነት መሠረት ከዋናው ገንዘብ ላይ ተበዳሪው የተወሰነ ቅናሽ እንዲደረግለት ሲጠይቅ Haircut ተብሎ የሚገለጽ ሲሆን ቅናሹ የሚገለጸው በፐርሰንት ነው።
ለምሳሌ፣
የኢትዮጵያ መንግስት 20% haircut እንዲደረግለት ጠየቀ ማለት ከዋናው የዩሮቦንድ ብድር ላይ 20% እንዲቀነስለት ጠይቋል ማለት ነው።
በእዚህ መሠረት አበዳሪዎቹ ከተስማሙ አዲሱ የዩሮቦንድ የብድር መጠን፣
= $1,000,000,000 - (20%*$1,000,000,000)
=$800,000,000/ስምንት መቶ ሚሊዮን ዶላር ይሆናል ማለት ነው።
የኢትዮጵያ መንግስት በቅርቡ ከአበዳሪዎቹ ጋር አዲስ የብድር ማራዘሚያ ድርድር የጀመረ ሲሆን በዩሮቦንድ የተበደረው 1 ቢሊዮን ዶላር ብድር ላይ 20% Haircut እንዲደረግለት ጠይቋል።
በፋይናንስ ገበያ ውስጥ ተበዳሪ ከአበዳሪው ጋር በሚያደርገው አዲስ የብድር ማራዘሚያና አከፋፈል ስምምነት መሠረት ከዋናው ገንዘብ ላይ ተበዳሪው የተወሰነ ቅናሽ እንዲደረግለት ሲጠይቅ Haircut ተብሎ የሚገለጽ ሲሆን ቅናሹ የሚገለጸው በፐርሰንት ነው።
ለምሳሌ፣
የኢትዮጵያ መንግስት 20% haircut እንዲደረግለት ጠየቀ ማለት ከዋናው የዩሮቦንድ ብድር ላይ 20% እንዲቀነስለት ጠይቋል ማለት ነው።
በእዚህ መሠረት አበዳሪዎቹ ከተስማሙ አዲሱ የዩሮቦንድ የብድር መጠን፣
= $1,000,000,000 - (20%*$1,000,000,000)
=$800,000,000/ስምንት መቶ ሚሊዮን ዶላር ይሆናል ማለት ነው።
የመሬት ንዝረቱ ትዝብት፣
በትላንትናው የመሬት መንቀጥቀጥ በስድስተኛ ፎቅ ላይ ሆኜ ንዝረቱ እንደተሰማኝ ለክፉ ለደጉ በሚል ቆጣሪ አጥፍቼ፣ በር ቆላልፌ በደረጃ እግሬ አውጪኝ ብዬ ምድር ላይ ስወርድ ከእኔ እና አብሮኝ ከነበረ ጓደኛዬ በቀር አንድም የወረደ ሰው አልነበረም።
ይሄ ነገር ቅዥት ይሆን እንዴ ብዬ በመጠራጠር እዛው በምኖርበት ሰፈር ወዳለ ጓደኛዬ ስልክ መታሁ። "እኔ እኮ አዙሪት የያዘኝ መስሎኝ ነገ ሐኪም ቤት ስለ መሄድ እያሰብኩ ነበር?" አለኝ። በፍጥነት ከፎቅ እንዲወርድ መክሬው ተለያየን።
ታች ያሉ የህንጻው ጠባቂዎች ዘንድ በመሄድ ንዝረቱ ተሰምቷቸው እንደሁ ብጠይቅ ምንም እንዳልተሰማቸው ነገሩኝ። ምናልባትም 3ኛ ፎቅ ላይ የሆነ ዝግጅት ስለነበር የዝግጅቱ ሙዚቃ ሰዉን አዘናግቶት ሊሆን እንደሚችል ነገሩኝ። ወዲያው ወደ ማህበራዊ ድረ ገጽ አማተርኩ። ነገሩ እውነት መሆኑን አወቅኩ።
ስለጉዳዩ እርግጠኛ ከሆንኩ በኋላ ለጥበቃዎቹ ነዋሪውን እንዲያነቁ ነገርኳቸው። አንደኛው ሲከንፍ በየበሩ እያንኳኳ ያለውን ችግር ተናገረ። የሚደንቀው ነገር በጣት ከሚቆጠሩ ሰዎች ውጪ ሌላ ሰው የጥበቃውን መረጃ ከቁብ ቆጥሮ ከፎቁ የወረደ አልነበረም።
ይሄኔ ነበር እግዚአብሔር አይበለውና የከፋ ነገር ቢመጣ አንድም የተዘረጋ የአደጋ ጊዜ ማስጠንቀቂያ ስርዓት ስለሌለን አንድ ላይ ማለቃችን አይቀሬ የመሆኑ ነገር ውል ያለኝ።
አምላክ ሀገራችንን ይጠብቅ!
በትላንትናው የመሬት መንቀጥቀጥ በስድስተኛ ፎቅ ላይ ሆኜ ንዝረቱ እንደተሰማኝ ለክፉ ለደጉ በሚል ቆጣሪ አጥፍቼ፣ በር ቆላልፌ በደረጃ እግሬ አውጪኝ ብዬ ምድር ላይ ስወርድ ከእኔ እና አብሮኝ ከነበረ ጓደኛዬ በቀር አንድም የወረደ ሰው አልነበረም።
ይሄ ነገር ቅዥት ይሆን እንዴ ብዬ በመጠራጠር እዛው በምኖርበት ሰፈር ወዳለ ጓደኛዬ ስልክ መታሁ። "እኔ እኮ አዙሪት የያዘኝ መስሎኝ ነገ ሐኪም ቤት ስለ መሄድ እያሰብኩ ነበር?" አለኝ። በፍጥነት ከፎቅ እንዲወርድ መክሬው ተለያየን።
ታች ያሉ የህንጻው ጠባቂዎች ዘንድ በመሄድ ንዝረቱ ተሰምቷቸው እንደሁ ብጠይቅ ምንም እንዳልተሰማቸው ነገሩኝ። ምናልባትም 3ኛ ፎቅ ላይ የሆነ ዝግጅት ስለነበር የዝግጅቱ ሙዚቃ ሰዉን አዘናግቶት ሊሆን እንደሚችል ነገሩኝ። ወዲያው ወደ ማህበራዊ ድረ ገጽ አማተርኩ። ነገሩ እውነት መሆኑን አወቅኩ።
ስለጉዳዩ እርግጠኛ ከሆንኩ በኋላ ለጥበቃዎቹ ነዋሪውን እንዲያነቁ ነገርኳቸው። አንደኛው ሲከንፍ በየበሩ እያንኳኳ ያለውን ችግር ተናገረ። የሚደንቀው ነገር በጣት ከሚቆጠሩ ሰዎች ውጪ ሌላ ሰው የጥበቃውን መረጃ ከቁብ ቆጥሮ ከፎቁ የወረደ አልነበረም።
ይሄኔ ነበር እግዚአብሔር አይበለውና የከፋ ነገር ቢመጣ አንድም የተዘረጋ የአደጋ ጊዜ ማስጠንቀቂያ ስርዓት ስለሌለን አንድ ላይ ማለቃችን አይቀሬ የመሆኑ ነገር ውል ያለኝ።
አምላክ ሀገራችንን ይጠብቅ!
ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት አዲስ አበባ ላይ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ ነበር። በምኖርበት ኮንዶሚኒየም ላይ የተወሰንን ሰዎች ንዝረቱ ተሰምቶን ወደ ታች ወርደናል። ይሄንኑ ለማረጋገጥ Earthquake track የተሰኘ ገጽ ላይ ሳማትር እውነትነቱን አረጋግጦልኛል።
https://www.google.com/url?sa=t&source=web&rct=j&opi=89978449&url=https://earthquaketrack.com/et-44-addis-ababa/recent&ved=2ahUKEwi-7KqCqPqIAxWyBdsEHfsSKacQFnoECBIQAQ&usg=AOvVaw0n73D67_LsiJn1s8c3stEz
https://www.google.com/url?sa=t&source=web&rct=j&opi=89978449&url=https://earthquaketrack.com/et-44-addis-ababa/recent&ved=2ahUKEwi-7KqCqPqIAxWyBdsEHfsSKacQFnoECBIQAQ&usg=AOvVaw0n73D67_LsiJn1s8c3stEz