Últimas publicaciones de Farankaa - ፈረንካ (@farankaa) en Telegram

Publicaciones de Telegram de Farankaa - ፈረንካ

Farankaa - ፈረንካ
The primary goal of this page is to enhance the financial literacy of Ethiopians by offering valuable insights on investment, banking, insurance, capital markets, and taxation.
1,818 Suscriptores
276 Fotos
2 Videos
Última Actualización 09.03.2025 03:43

Canales Similares

Ethio Fm 107.8
20,597 Suscriptores
Addis Fortune
13,927 Suscriptores

El contenido más reciente compartido por Farankaa - ፈረንካ en Telegram

Farankaa - ፈረንካ

31 Oct, 16:47

660

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባንኮች እርስ በእርስ የሚበዳደሩበትን የገንዘብ ገበያ/Interbank money Market ይፋ አደረገ።
Farankaa - ፈረንካ

29 Oct, 11:22

837

የፋይናንስ መግለጫዎችን/Financial Statements ምንነት እና እንዴት አንብቦ መረዳት እንደሚቻል የሚያሳይ ሰነድ ከሊንክድኢን ላይ አውርጄ አጋርቻችኋለሁ።


የፋይናንስ እንዲሁም ከሌሎች ሙያዎች ጋር የተገናኙ ነጻ ስልጠናዎችን እንዲሁም ሰነዶችን ለማግኘት የLinkedin አካውንት ከፍታችሁ ከባለሙያዎች ጋር ተዋወቁ።
Farankaa - ፈረንካ

27 Oct, 09:17

960

የቱንም ያህል ጎበዝ ብትሆን፣ የተሳሳተ ቦታ ላይ (ያለቦታህ) ከተገኘህ ዋጋ የለህም!
Farankaa - ፈረንካ

26 Oct, 11:16

957

77 ጠቃሚ የፋይናንስ ጥያቄዎችና መልሶች..
Farankaa - ፈረንካ

24 Oct, 07:18

1,248

አልለወጥ ያለው የኢትዮጵያ የሒሳብ እና ኦዲት የሥራ ባህል ነገር...

****

ከወርኃ መስከረም አንስቶ እስከ ጥቅምት 30 እና ከእዛ ቀጥሎ ባሉ ጥቂት ሳምንታት የኢትዮጵያ የሒሳብ ባለሙያዎችና ኦዲተሮች የምጥ ሰሞን ነው። የሥራው ጫና እንቅልፍ ይነሳል።

የንግዱ ማህበረሰብ ባለቀ ሰዐት ነው ፋይሉን ተከሽሞ ወደ ሒሳብ ባለሙያ አሊያም ወደ ኦዲተር የሚተምመው። ጉዳዩ ወደ ባህልነት የተቀየረ ሁሉ ይመስላል። ሁሌም "ነጋዴው ግብርን ዘግይቶ የሚከፍለው ገንዘቡን እስከመጨረሻው ቀን ሊጠቀምበት ስለሚፈልግ ነው" የሚል አመክንዮ ይቀርባል። ይሁንና አመክንዮው ውኃ አያነሳም። ለእዚህ ምክንያቱ ደግሞ ነጋዴው ሂሳቡን አሰርቶ፣ ኦዲት አስደርጎ ታክስ ዲክሌር አድርጎ ሁሉ እስከ ጥቅምት 30 ደረስ ክፍያውን ያለቅጣት መፈጸም ይችላል። ሒሳቡ ሳይሰራ፣ ኦዲት ሳይደረግ መዘግየቱን ምን አመጣው?

ይህ በየአመቱ ለኦዲተሮች እና ለአካውንታንቶች መጉበጥ ምክንያት የሆነው ባለቀ ሰዐት በሚደረግ ሩጫ የሚሰራውን የሒሳብ ሥራም ሆነ የኦዲት ሥራ ጥራት ያጓድላል፣ የሒሳብ ባለሙያውንም ላልተገባ ጫና ይዳርጋልና የሚመለከተው አካል ተገቢውን የግንዛቤ ማስጨበጫ የግብር ወራት ከመድረሳቸው አስቀድሞ ሊሰጥ ይገባል በማለት ጽሁፌን እደመድማለሁ።
Farankaa - ፈረንካ

22 Oct, 11:06

1,186

https://youtu.be/xNNMraqMuxk?si=dqYNsWyyPbUXcV37
Farankaa - ፈረንካ

18 Oct, 16:38

1,397

የድንገቴ የኢንቨስትመንት አማካሪዎች ነገር..

***

የኢትዮ ቴሌኮም አክሲዮን ለህዝብ ሽያጭ ይፋ ከሆነ ወዲህ ብዙዎች የኢንቨስትመንት አማካሪ ሆነው ብቅ ብለዋል። የእራስን ሐሳብ መግለጽ ችግር የለውም። ይሁንና ምክንያታዊ ባልሆነ መረጃ ላይ ተመስርቶ "በመሰለኝ እና በደሳለኝ ለሌሎች ምክር መስጠት ዘርፉን ጠንቅቆ ባለማወቅ የሚደረግ ድፍረት ነውና ሊቆም ይገባዋል።

አንዳንዶች የአምናውን የተጣራ ትርፍ ላይ ተመርኩዘው Earning per Share ወይም Dividend per share በማስላት ከወለድ ያልበለጠ ነው ብለው ሲያብራሩ ገጥሞኛል። ተቋሙ ለህዝብ ይፋ ያደረገውን comparative financial statement ስቃኝ፣ አምና ላይ ኢትዮ ቴሌኮም ገቢው በከፍተኛ ደረጃ ቢጨምርም (ከ71 ቢሊዮን ወደ 90 ቢሊዮን) የሰጣቸው ብድሮች/Financial assets በወቅቱ ባለማስከፈሉ ምክንያት IFRSን ተከትሎ በተዘጋጀው የሂሳብ መግለጫ ላይ በያዘው ወደ ስምንት ቢሊዮን የሚጠጋ impairment provision ምክንያት ትርፉ ከካቻናው ትርፍ ጋር ተቀራራቢ ሆኗል። ይሁን እንጂ ተቋሙ የብድር አሰባሰቡን ካሻሻለ፣ የብድር ጥራቱን ካሻሻለ ይሄ ወጪ ከprovision ወደ ገቢነት መቀየሩ አይቀሬ ነው።

ኢንቨስተሮች አክሲዮን የሚገዙት Dividend ለመሰብሰብ ብቻ አይደለም። Capital appreciation ሌላኛው ባለአክሲዮኖች የሚያገኙት ትርፍ ነው። በአመቱ ዋጋዬን እመልሳለሁ የሚል የዋህ ኢንቨስተር ሊኖር አይችልም። የኢትዮ ቴሌኮም አፈጻጸም ሲጨምር በአክሲዮን ገበያው ላይ ዛሬ ላይ የገዙትን አክሲዮን በተሻለ ዋጋ በመሸጥ ትርፍ ለማግኘት አክሲዮን የሚገዙ ብዙዎች ናቸው።

አገሬው "ሥራ ለሰሪው እሾህ ላጣሪው" የሚለው ያለምክንያት አይደለም። በሙያው ላይ authority ያላቸው ሰዎች በጉዳዩ ላይ አስተያየት ይስጡ፣ ሌላው ያዳምጥ። በሁሉም ጉዳይ ላይ ሁሉ ተንታኝ፣ ሁሉ አውሪ፣ ሁሉ ጸሀፊ ሊሆን አይችልም።
Farankaa - ፈረንካ

17 Oct, 12:32

1,296

Ethiotelecom የአክሲዮን ሽያጩን በይፋ ጀምሯል። ምዝገባውን ከመጀመራችሁ በፊት፣

1. የታደሰ መታወቂያ/ፓስፖርት
2. ጉርድ ፎቶ ግራፍ

አዘጋጁ።

ምዝገባውን ከፈጸማችሁ በኋላ ክፍያውን አሁኑኑ አልያም በ48 ሰዐት ጊዜ ውስጥ መፈጸም ትችላላችሁ።
Farankaa - ፈረንካ

17 Oct, 05:11

1,182

ባንክ ያልሆኑ የውጪ ምንዛሪ ቢሮዎች የኮምፕሊያንስ ነገር...

*
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አምስት ለሚደርሱ ባንክ ያልሆኑ የውጪ ምንዛሪ ቢሮዎች ፈቃድ መስጠቱን ከሰማን ብዙም አልቆየንም።

እኒህ የውጪ ምንዛሪ ቢሮዎች ገዢው ባንክ የሚያወጣውን መመሪያ እንዲሁም መመሪያውን መጣስ የሚያስከትለውን ቅጣት በተመለከተ ያላቸው ግንዛቤ እምብዛም ይመስላል። እኒህ ተቋማት ብሔራዊ ባንኩ የውጪ ምንዛሪ አስተዳደርን ለሚያወጣቸው ፖሊሲዎች ከባንኮች እኩል ተጠያቂ ናቸው።

በብሔራዊ ባንኩ ስር መተዳደር እና በጥቁር ገበያ ስር መስራት እጅግ የተለያዩ ነገሮች ናቸው። በብሔራዊ ባንክ ፈቃድ ማሊያ የጥቁር ገበያን አደራለሁ ብሎ ፈቃድ ያወጣም አይጠፋም። ናይጄሪያ ለብዙ ሺህ ባንክ ያልሆኑ የውጪ ምንዛሪ ቢሮዎች ፈቃድ ሰጥታ በኋላ ላይ ህገ-ወጥ ግብይት ላይ በመሳተፋቸው ፈቃዳቸውን ሰርዛለች። ብልጥ ከሌላው ይማራል።

National Bank of Ethiopia ፈቃዱን ባንክ ላልሆኑ የውጪ ምንዛሪ ተቋማት መስጠቱ ይበል የሚያስብል ቢሆንም ለእነዚህ ተቋማት በቂ የአቅም ግንባታ ከመስጠት አንስቶ ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ ይኖርበታል። ይህ ካልሆነ የአልማዝን ጠባሳ እያዩ በእሳት እንደመጫወት ይቆጠራል።

ከእዚህ ጽሁፍ ጋር የተያያዘው የውጪ ምንዛሪ መግዣ እና መሸጫ ዋጋ በትላንትናው እለት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዢ ከጎበኟቸው ባንክ ያልሆኑ የውጪ ምንዛሪ ቢሮዎች መካከል በአንዱ ውስጥ የተሰቀለ የዶላር መግዣና መሸጫ ዋጋ ገዢው ባንክ በቅርቡ ያወጣውን የ2% spread ህግ የጣሰ ሆኖ ተገኝቷል። ነገሩ ሳይቃጠል በቅጠል ነውና ገዢው ባንክ ተቋማቱ ልክ እንደባንኮቹ ሁሉ ለሚወጡ ህጎች ተገዢ እንዲሆኑ ማድረግ ይጠበቅበታል።
Farankaa - ፈረንካ

15 Oct, 13:53

1,093

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አዲስ ፖሊሲ እንምታ ምንድነው?

አዲሱ ፖሊሲ ባንኮች spreadን (በዶላር መግዣና መሸጫ መካከል ያለ ልዩነት) በተመለከተ የሚያስቀምጡት ልዩነት ከ2% እንዳይበልጥ ተገድቧል።

ለምሳሌ የዛሬውን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የመግዣ እና የመሸጫ ዋጋ ብናይ፣

መግዣ = 113.1308

መሸጫ = 113.1308 + (2%*113.1308)
= 115.3934

ይሆናል ማለት ነው።

ይሁን እንጂ መመሪያው ባንኮቹ ለሚሰጧቸው የተለያዩ ከውጪ ምንዛሬ ጋር የተያያዙ አገልግሎቶች (የመተማመኛ ሰነድ/LC, ዶክመንት ሲቀርብ ካሽ ይከፈል/CAD እና ቅድመ-ክፍያ/TT የመሳሰሉት) ላይ ተጨማሪ ክፍያዎችን፣ ማለትም እንደ...

📌LC opening commission

📌PO approval commission

📌 Service Charge

📌Confirmation Charge

📌SWIFT Charge

እና የመሳሰሉ ክፍያዎችን የማስከፈል መብት ተሰጥቷቸዋል።

ከእዚህ ቀደም በነበረው የኢብባ ፖሊሲ መሰረት ባንኮች የአገልግሎት ክፍያዎችን በሙሉ Spread ውስጥ እንዲያካትቱ ይጠይቅ የነበረ ሲሆን አዲሱ ፖሊሲ የተለያዩ የአገልግሎት ክፍያዎች ከSpread ተለይተው ለብቻ ከአስመጪዎች እንዲሰበሰቡ አዝዟል።

ብዙዎች ባንኮች የሚሸጡት ዶላር ላይ ቅናሽ እንደተደረገ አድርገው እየዘገቡ ያሉት ነገር ትክክል አይደለም።

ይሁንና አዲሱ ፖሊሲ አስመጪዎች ቀደም ሲል በተጋነነ የመሸጫ ዋጋ መሠረት ሲከፍሉ የነበረውን import duty ስለሚቀንስ የገበያ ዋጋው ተረጋግቶ ከቀጠለ የገቢ ንግድ እቃዎች ላይ የተወሰነ ቅናሽ ያመጣል።