ተቋማት ከትርፍ ባሻገር በተለያየ መንገድ ማህበራዊ ግዴታቸውን መወጣታቸው፣ በተለያዩ ምክንያቶች ለተፈናቀሉ፣ በድርቅ ምክንያት፣ በድህነት ምክንያት ለተቸገሩ ወገኖች ከትርፋቸው ቀንሰው ማካፈላቸው፣ ለማህበረሰቡ መልሰው መስጠታቸው የሚያስመሰግናቸው ተግባር ነው።
ይሁንና ይሄንኑ ዜና ለማስታወቂያ ለመጠቀም እርዳታ የሚሰጣቸውን ግለሰቦች ፎቶግራፍ እያነሱ እና እየቀረጹ በየማህበራዊ ድረገጻቸው ማካፈላቸው በተለይም በረመዳንና በወርሀ ፋሲካ የጾም ወራት፣ ልግስና እና በድብቅ መስጠት በሚሰበክባቸው ወራት ሁኔታው ከማስታወቂያ ይልቅ ማሳቀቂያ ስለሚሆን እንዲሁም ዓላማውን ያልመታ የማስታወቂያ ሙከራ ከመሆን የዘለለ ትርፍ ስለማያስገኝላቸው ከእዚህ ድርጊት ቢታቀቡ ብዬ ቀና ምክሬን አስተላልፋለሁ።