Injibara University

@injiuniversity


Injibara University

18 Oct, 18:43


እንጅባራ ዩኒቨርስቲ ቀድም ሲል ለጥቅምት 14-15/2017 ዓ/ም የምዝገባ ጥሪ ማስተላለፍ ይታወቃል። በ2017 ዓ/ም አዲስ የተመደባችሁ እና በ2016 ዓ/ም የሬሜዲያል ተማሪዎች የነበራችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ላልተወሰነ ጊዜ የተራዘመ መሆኑን እናስታውቃለን።
ማሳሰቢያ። የሌሎቻችሁ ጥሪ እንደተጠበቀ መሆነን እናስታውቃለ

Injibara University

16 Oct, 12:59


#ማስታወቂያ
------
የድኅረ-ምረቃ ትምህርት የምዝገባ ቀን የተራዘመ መሆኑን ስለማሳወቅ!

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከዚህ በታች በተዘረዘሩት የ2ኛ(በመደበኛ እና ተከታታይ ት/ት) እና 3ኛ ዲግሪ ትምህርት ፕሮግራሞች አመልካቾችን ተቀብሎ ለማስተማር ቀደም ሲል ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል።

ነገር ግን በተለያዩ ምክንያቶች ምዝገባ ማካሄድ ላልቻላችሁ የምዝገባ ቀን ከጥቅምት 6 እስከ ጥቅምት 29/2017 ዓ.ም ድረስ የተራዘመ በመሆኑ በተጠቀሱት ቀናት በማመልከት መማር የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

በዚህሊንክ በመግባት በኦንላይን መመዝገብ ትችላላችሁ!
https://application.inu.edu.et/
ጥቅምት 6/2017 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

Injibara University

11 Oct, 13:52


የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ
------
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ባወጣው የሥራ ቅጥር ማስታወቂያ መሠረት ከታች ሥማችሁ የተዘረዘረ አመልካቾች በተጠቀሰው ቀን በዩኒቨርቲው ግቢ ውስጥ በመገኘት ፈተናውን እንድትወስዱ እናሳውቃለን።
የፈተና ቀናትም:-
1. ለጤና ሳይንስ ኮሌጅ አመልካቾች ጥቅምት 5/2017 ዓ.ም
2.ለተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ጥቅምት 7/2017 ዓ.ም
3. ለምህንድስናና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ አመልካቾች ጥቅምት 11/2017 ዓ.ም መሆኑን እንገልጻለን።

Injibara University

10 Oct, 12:47


ማስታወቂያ
-----
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ/ም የትምህርት ዘመን በሪሜዲያል ፕሮግራም በኤክስቴንሽን መርሃ-ግብር ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም በ2016 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለሪሜዲያል ትምህርት መግቢያ ውጤት ያላችሁ ተማሪዎች በሙሉ የምዝገባ ጊዜ ከጥቅምት 01 - 15 /2017 ዓ.ም ድረስ ስለሆነ ዘወትር ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ባሉት ቀናት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
የትምህርቱ አጠቃላይ ክፍያ፡-
1. ለተፈጥሮ ሳይንስ የመመዝገቢያ ክፍያን ጨምሮ 2,350 ብር
2. ለማኅበራዊ ሳይንስ የመመዝገቢያ ክፍያን ጨምሮ 1,950 ብር
አመልካቾች በዩኒቨርሲቲው የንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000258464428 አጠቃላይ ክፍያ በመክፈል ዋናውን የባንክ ደረሰኝ ከ 2 ፎቶ ኮፒ ጋር በመያዝ ሬጅስትራር ጽ/ቤት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

የተከታታይና ርቀት ትምህርት ዳይሬክቶሬት

Injibara University

04 Oct, 14:31


ማስታወቂያ፦
----
የመግቢያ ጊዜ የተራዘመ መሆኑን ስለማሳወቅ
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ 4ኛ ዓመት መደበኛ ተማሪዎች የምዝገባ ፕሮግራም መስከረም 29 እና30/2017 ዓ.ም መሆኑ ቀደም ሲል ተገልጾ የነበረ ቢሆንም የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ባለመጠናቀቃቸው የምዝገባ ጊዜ ጥቅምት 14 እና 15/2017 ዓ.ም መሆኑን እናሳውቃለን።

Injibara University

01 Oct, 13:03


በስርዓተ ትምህርት ዝግጅት እና ትምህርት ምዘና ላይ ያተኮረ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሰጠ፡፡
-----
ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ መምህራን በስርዓተ-ትምህርት ዝግጅት እና በትምህርት ምዘና ላይ ያተኮረ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሠጥቷል፡፡

ስልጠናውን የከፈተቱት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ጥራት ማረጋገጫ እና ማጎልበቻ ኦዲቲንግ ስራ አስፈጻሚ ዓለም አምሳሉ( ዶ/ር) የስልጠናው ዓላማ መምህራን በትምህርት ምዘና እና በመማሪያ ግብዓቶች ዝግጅት ዙሪያ የተሻለ ግንዛቤን እንዲኖራቸው ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።

ስልጠናውን የሰጡት የዩኒቨርሲቲው የመምህራን ትምህርትና ስርዓተ ትምህርት ጥናት ትምህርት ክፍል መምህርና የከፍተኛ ዲፕሎማ ስልጠና አስተባበሪ የሆኑት ቱጂ ኢሬሶ(ረዳት ፕሮፌሰር) እና የሳይኮሎጂ ትምህርት ክፍል መምህር የሆኑት ሙሉዓለም አለማየሁ ናቸው፡፡

ስልጠናው በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከትምህርት ጥራት ማረጋገጫ እና ማጎልበቻ ኦዲንቲንግ ስራ አስፈጻሚ በጋራ የተዘጋጀ ሲሆን ለሁለት ቀናት ሲሰጥ ቆይቶ በዛሬው እለት ተጠናቋል፡፡

መስከረም 21/2017 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

Injibara University

26 Sep, 12:14


እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለመስቀል ደመራ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልጻል።

መልካም በዓል
ድሩፃ!
መስከረም 16/2017 ዓ.ም

Injibara University

26 Sep, 10:52


የፈተና ውጤት ማሳወቂያ፦
-----
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ባወጣው የረዳት ሌክቸረር ማስታወቂያ ተወዳድራችሁ ያለፋችሁ ስማችሁ ከዚህ በታች የተገለጸ መሆኑን እያሳወቅን ማስታወቂያው ከወጣበት ከዛሬ ጀምሮ የሥራ መልቀቂያ/የሥራ አጥ ማስረጃ በመያዝ እስከ መስከረም 21/2017 ዓ.ም ድረስ በዩኒቨርሲቲው የብቃትና ሰው ሀብት አስተዳደር ሥራ አስፈጻሚ ቢሮ እንድታመለክቱ እናሳስባለን።

መስከረም 16/2017 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ