Bahirdar University

@bahrdar_university


It is a channel about Bahir Dar University all Campuses' Students!
ይህ የBahir Dar University ይፍዊ የቴሌግራም ቻናል ነው። በዚህ ቻናል አዳዲስ መረጃዎች ይለቀቁበታል

Bahirdar University

21 Oct, 18:06


ለዩኒቨርሲቲው መምህራን በአፈጻጸምና ግምገማ ላይ መሰረት ያደረገ የሦስት ቀን የTOT ስልጠና በመሰጠት ላይ ነው
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ (ጥቅምት 11/2017 ዓ.ም)
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከተለያዩ የአካዳሚክ ክፍሎች ለተውጣጡ መምህራን በአፈጻጸምና ግምገማ ላይ መሰረት ያደረገ የTOT ስልጠና (TOT Training on Performance-Based Assessment) በሚል ርዕሰ ጉዳይ ከዛሬ በ11/02/17 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የአቅም ግንባታ ስልጠና በፔዳ ግቢ የስልጠና ማዕከል በሙያው በሰለጠኑ መምህራን በመሰጠት ላይ ነው፡፡
ስልጠናውን በንግግር ያስጀመሩት የዩኒቨርሲቲው የፈተና ማዕከል (Testing Center) ዳይሬክተር ዶ/ር ጥሩወርቅ ታምሩ ማዕከሉ የሚያከናውናቸው ተግባራት የዩኒቨርሲቲውን የፅንሰ ሃሳብም ሆነ የተግባር ትምህርቶችን የፈተና ጥራት የማሻሻል፣አገር አቀፍ፣የውጭና የቅጥር ፈተናዎች ጥራታቸውን ጠብቀው ማዘጋጀትና ማስፈተን እንዲሁም ዓለም አቀፍ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ፈተና (International English Language Tasting Center /IELTC/) እና የመሳሰሉ ፈተናዎችን መስጠት መሆኑን አስስረድተዋል፡፡
እንደ ዳይሬክተሯ ገለፃ የሶስቱ ቀን ስልጠና ዓላማ ተግባር ተኮር ለሆኑ ትምህርቶች የመመዘኛ መሳሪያዎችን ለማሻሻል ታልሞ የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በተጨማሪም ከስልጠናው መልስ ይህ ሰልጣኞች ከተለያዩ የተግባር ተኮር ምዘናዎች ጋር ተዋውቀው ምዘናዎችን በመስራት በኮሌጃቸው ላሉ መመህራን ስልጠናውን በመስጠት ተደራሽ እንደሚያደርጉት እና የተለያዩ መመዘኛዎችን አዘጋጅተው ለማሰልጠኛ ማኑዋሉ ተጨማሪ ግብዓት እንደሚሰጡ በንግግራቸው ጠቁመዋል፡፡
ለሰልጣኞች የተግባር ስልጠናውን የሚሰጡ መምህራን በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ካሉ ስድስት የአካዳሚክ ክፍሎች ማለትም ከባህሕር ዳር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት፣ ከኢትዮጲያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት፣ ከሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ፣ ከግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ፣ ከሳይንስ ኮሌጅ እና ከስፖርት አካዳሚ የተውጣጡ 32 አሰልጣኝ መምህራኖች መሆናቸውን ዶ/ር ጥሩወርቅ አክለው ገልፀዋል፡፡
ስልጠናውን ያዘጋጁት የዩኒቨርሲቲው የፈተና ማዕከል እና የስልጠና ዳይሬክቶሬት በጋራ ሲሆኑ ስልጠናው ከ11/02/17-13/02/17 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ የስራ ቀናት የሚሰጥ መሆኑ ታውቋል፡፡
#share #share
@Bahrdar_university

Bahirdar University

21 Oct, 15:55


1/2ኛ አመት ተማሪዎች የፊልድ ምርጫ ተጀምሯል!!

https://studentportal.bdu.edu.et/Account/Login

🙏🙏🙏🙏🙏(🙏(🙏(🙏🙏🙏🙏

JOIN AND SHARE
 @Bahrdar_university
@Bahrdar_university

Bahirdar University

21 Oct, 12:27


#share #share
@Bahrdar_university

Bahirdar University

21 Oct, 07:48


Announcement: Training on Basics of GIS and Remote Sensing

The Geospatial Data and Technology Center (GDTC) of Bahir Dar University is excited to announce a comprehensive training session on the fundamentals of GIS and remote sensing.

This training is designed to introduce participants to the basic principles and practical applications of these technologies. The training is a face-to-face training designed for thirty trainees, divided into two sessions of fifteen participants each.

Date:
1st Round: 13 - 16/02/2017 E.C
2nd round: 19 - 22.02.2017 E.C
Time: Morning 2:30 - 6:30 and afternoon 8:00 - 11:00 LT
Venue: GDTC, Lab (Wisdom)

Contents of the training:

🎯Basics of GIS: concept of GIS, GIS Data Models, and Coordinate System & Projection
🎯Data management: Integrating data from various sources
🎯Fundamentals of Remote Sensing
🎯Data acquisition from open source Earth observation satellites
🎯Map production

Who should attend:
This training is ideal for:

postgraduate students and researchers who wish to incorporate GIS and remote sensing technology into their research; and
professionals keen to learn about geospatial data and its diverse applications.
Why do you attend:
• Enhance your knowledge and skills in GIS and remote sensing.
• Learn from experienced instructors.
• Gain practical insights and hands-on experience.
Requirements:
Basic computer skills are mandatory for this training.
How to register:
To register for the training, please visit our registration page __

Join us for an informative and engaging session designed to enhance your knowledge and skills in GIS and remote sensing
#share #share
@Bahrdar_university

Bahirdar University

19 Oct, 21:50


የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ትምህርት ኮሌጅ ባዘጋጀው ስልታዊ እቅድ ዙሪያ ከዩኒቨርስቲው ፕሬዚደንት እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት አደረገ

********
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ (ጥቅምት 9/2017 ዓ.ም) የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ኮሌጅ አመራርና ሰራተኞች ዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንት እና ም/ ፕሬዚዳንቶች እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ትምህርት ኮሌጁ ባዘጋጀው የአምስት ዓመት ስልታዊ እቅድ ዙሪያ በዋናው ግቢ የመሰብሰቢያ አዳራሽ የግማሽ ቀን ውይይት አካሂዷል፡፡

የቀድሞው ፔዳ የአሁኑ ትምህርት ኮሌጅ ከምስረታው ጀምሮ በውጭ ሀገር እና በሀገር ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ
የትምህርት ተቋማት የሚያገለግሉ አንቱ የተባሉ በርካታ መምህራንን ያፈራ ኮሌጅ በመሆኑና፤ በስሩ ያሉ አንጋፋ

መምህራን በማስተማር ስራቸው የካበተ ልምድ ያላቸው እና እስካሁን ላለው ለሀገሪቱ የትምህርት ጥራትም
የበኩላቸውን አስተዋፆ ያበረከቱ ብርቱ መምህራንን ያቀፈ ተቋም መሆኑ ተገልጿል፡፡ በቅርቡ እንደተቋም ራስ ገዝ
ሆኖ መደራጀት ተገቢ መሆኑን ተከትሎ ለአዲሱ አደረጃጀት የሚመጥን የአምስት ዓመት ስልታዊ እቅድ አዘጋጅቶ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር መንገሻ አየነ እና ም/ፕሬዚዳንቶች በተገኙበት የግማሽ ቀን ውይይት አካሂዷል፡፡

በውይይት መድረኩ ላይ የትምህርት የኮሌጁ መምህር እና ተመራማሪ የሆኑት አቶ ደረጄ ታዬ ቀድሞ ከነበረበት ፔዳ ጎጂ አካዳሚ ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ያለውን የትምህርት ኮሌጁን ቀደምት ታሪኮችን የሚያሳይ አጭር ፁሁፍ አቀርበዋል፡፡ በተመሳሳይ የኮሌጁ መምህር የሆኑት ዶ/ር ሙሉጌታ አዋየሁ የኮሌጁን የአምስት ዓመት ስልታዊ ዕቅድ እና የዝግጅት ሂደቱን አስመልክቶ ለውይይት የመነሻ ፁሁፍ አቅርበዋል፡፡ ትምህርት ኮሌጁ ሁለት ትምህርት ቤቶች school of Teacher Education and school of Educational science እንዲሁም Institute of Pedagogical and Educational Research (IPER) የጥናትና ምርምር ተቋም እና Bahir dar Journal of Education ባለቤት ቢሆንም በምርምር ስራ ላይ ከፍተኛ የሆነ የሰው ሀይል እና የበጀት እጥረት እንዳለበት ዶ/ር ሙሉጌታ ያየህ ስለምርምር ተቋሙ ባቀረቡት ፁሁፍ ላይ አመላክተዋል፡፡

ዶ/ር መንገሻ አየነ በበኮላቸው ለትምህርት ኮሌጁ አዲስ እንደልሆኑ እና ካሁን በፊት የማስተማር ስራ መስራታቸው እና በቅርበት እንደሚያውቁት ተናግረው፤ የኮሌጁን ጥንካሬ እና በትምህርት መስኩ ለሀገር ያበረከተውን ከፍተኛ የሰለጠነ የሰው ኃይል አንጻር የሀገሪቱ የትምህርት አምባሳደር መሆኑን ጠቅሰው ወደፊትም ይህንን ጠንካራ ስማችንን በስራ ገልጠን ፋና ወጊ የትምህርት ተቋም መሆን አንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ የቀረበውን የአምስት አመት ስልታዊ እቅድ አሰመልክቶ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ያሉ BiT, EITEX እና CoMHS ኮሌጆች ጠንከር ያለ አደረጃጀት እና መዋቅር ስላላቸው በዩኒቨርሲቲው ጎልተው መውጣት ችለዋል ያሉት ፕሬዚዳንቱ በተመሳሳይ የትምህርት ኮሌጁን የሚያሳድግ አደረጃጀት እና ጠንከር ያለ ስልታዊ እቅድና መዋቅር እንዲሁም አለማቀፍ አውደጥናቶችን ማድረግና ለኮሌጁ በሚጠቅም መልኩ ድንበር ሳይገድበን መስራት የሚችሉ ሰዎችን በቦርድ አባልነት ማካተት እንደሚችሉ ተናግረዋል፡፡

የትምህርት የኮሌጁን ቀደምት ታሪክ ፣ የዓምስት አመት ስልታዊ ዕቅድን እና Institute of Pedagogical and Educational Research (IPER ) አስመልክቶ በቀረቡት ፁሁፎች ላይ የውይይት መድረኩ ተሳታፊዎች ጥያቄዎች ቀርበው የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር አሰይ ከበደ እና የአስተዳደር እና ልማት ም/ፕሬዚዳንት ወ/ሮ ገዳም ማንደፍሮ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
@Bahrdar_university